Professional Documents
Culture Documents
አንቀፅ ማለት አንድ ነጠላ ሀሳብን ለመግለፅ ሲባል በቁጥር አንድ ወይም ከአንድ የበለጡና የሀሳብ
ተዛምዷቸውን የጠበቁ ዓ.ነገሮች የሰፈሩበት የድርሰት ቅርፅ ነው፡፡ አንቀፅ ብዙውን ጊዜ አንድ ሀይለቃል
(መንደርደሪያ ዓ.ነገር) እና ከአንድ በላይ መዘርዝር ዓ.ነገሮችን ሊይዝ ይችላል፡፡
የአንቀፅ ቅርፅ /መልክ / ማለት ዓብዩን ሃሳብ ወይም ሀይለቃሉን የሚይዘው መንደርደሪያ ዓ.ነገር
በአንቀፅ ውስጥ የት የት እንደሚገኝ የሚወስን ማለት ነው፡፡ በዚህ መሰረት የአንቀፁ ሀይለቃል ወይም
መንደርደሪያ ዓ.ነገር ስፍራ አራት ቦታዎች ላይ ይገኛል፡፡ በሀይለ ቃሉ አንፃር ሌሎችን ዓ.ነገሮች ዝርዘር
ዓ.ነገሮች እንላቸዋለን ፡፡ ስለሆነም በሀይቃሉ የሚጀምር አንቀፅ ዝርዘር ይከተላቸዋል፡፡ ባጠቃላይ አንደ
አንቀፁ ሀይለቃል መገኛ ቦታ የዝርዝር ዓ.ነገሮች መገኛ ይወሰናል ማለት ነው፡፡
ሀ. ሀይለቃል በአንቀፅ መጀመሪያ ላይ ሲገኝ፡-ይህ ማለት የአንቀፁ ቅርፅ ከሰፊው ሀሳብ ወደ ጠባቡ
ወይም ወደ ዝርዝሩ ሀሳብ አቅጣጫ ይሄዳል ማለት ነው፡፡ ቅርፁም፡-
ሐይለቃል
ዝርዝር ዓ.ነገር
ምሰሌ፡- ሶፊያ አና ፅጌ መንታዎች ናቸው፡፡ እናታቸው ብርሀነ በተወለደች በአስራ ሶስት ዓመቷ
አግብታ በአስራስድስት ኣመቷ እነሱን ወለደች ፡፡ መንትዮዎቹ ከተወለዱ በኋላ አራት ቀን ብቻ ቆይታ
ሞተች፡፡ አባታቸው ተድላ የሚስቱ እሬሳ ሲወጣ አብሮ እንደወጣ የደረሰበት አልታወቀም፡፡ ስለዚህ
ሶፊያን ደብረሊባኖስ ገዳም መንኩሰው የሚኖሩ እማሆይ ጥሩነሽ የሚባሉ የእናቷ ታላቅ እህት ወስደው
ያሳድጓት ጀመር፡፡ በዚህ አንቀፅ ውስጥ ሀይለቃሉ በመጀመርያ ላይ ይገኛል፡፡ ሌሎቹ ሀይለቃሉን
የሚዘረዝሩ ዘርዛሪ ሀሳቦች ናቸው፡፡
ይህ ማለት የአንቀፁ ቅርፅ ከጠባቡ ሀሳብ ወደ ሰፊው ሀሳብ አቅጣጫ ይሄዳል ማለት ነው፡፡
ምሳሌ፡- እስክንድር እራሱን አከከ፡፡ ሰው ሰራሽ ጥርሱንም ወደውስጥ ገፋ አደረገ፡፡ ከሲራክ ባሻገር
መስኮቱን ዘልቆ ሩቅ ተመለከተ፡፡ አይኑ ከአድማስ ጋር ተጋጨ፡፡ የነበረው ተሰጦ እንደጉም በኖ ሲጠፋ
ታየው፡፡ አንድ ወይም ገፍ ቢል ሁለት ወር ስሙን የያዘው መፅሀፍ ታትሞ ሰው እጅ ገብቶ ሲነበብ
ለማየት የነበረው ተስፋ ይታየው የነበረው ጣፋጭ ኅይልም በሲራክ ክፋት ምክንያት ድንገት መጥፎ
ቅዠት ሆኖ ሲቀር ደብዛ ሲጠፋ፣ ሲጨልም ….የገራ ስሜቱ ከስሎ አመድ ሲሆን ታየው፡፡ ህይወት
መራራ ሆነችበት ሲራክን ከልቡ ጠላው፡፡ ልቡንበጦር ቢወጋው ምንኛ ደስ ባለው ነበር፡፡ የተሰመረበት
የመጨረሻው ዓ.ነገር የአንቀፁ ሀይለቃል ነው፡፡ ቅርፁም፡-
ዝርዝር ዓ.ነገር
ሐይለቃል
ዝርዝር ዓ.ነገር
ሐይለቃል
መ. ሀይለ ቃል በአንቀፅ መካከል ላይ ሲገኝ ፡-ይህ ማለት ከዝርዝር ሃሳብ ወደ ሰፊ እንደገና ከሰፊው
ሀሳብ ወደ ዝርዝር ዓ.ነገሮቹ ይሄዳሉ፡፡
ምሳሌ፡- ‹‹ፊታውራሪ መሸሻ ሳይሸመግሉ ከስው ጋር ተጣልተው ካልተከሰሱ እሳቸው ከሰው በዘመድ
ይሁን በአካል ዳኛ ፊት ቆመው አየኋቸው የሚል ሰው አልነበረም፡፡ብዙ ጊዜ ከሰው አይጣሉም፤
ከተጣሉም ግን አከሰዋለሁ ከማለት እፋለመዋለሁ ማለት ይቀናቸዋል፡፡ ለዳኛ አቤት ማለት ደካማነትን
ወይንም ፈሪነትን አምኖ እርዳታ መለመን ነው›› ይሉ ነበር፡፡ ተመቶ ወይም ተሰድቦ ካሱኝ ከሚል
መትቶ ወይም ሰድቦ ካሳ የሚክሰውን የሚያከብሩ መሆናቸውን በማንም ዘንድ የታወቀላቸው ነበሩ፡፡
አገረ ገዢ ሆነው በዳኝነት ወንበር ይቀመጡ በነበረ ጊዜ እንኳ ተመቶ ላቤቱታ የመጣባቸውን ‹‹እጅ
የለህም ወይ››ተሰድቦ የመጣባቸውን አይን የለህም ወይ›› ይላል፡፡
በዚህ አንቀፅ ውስጥ መሀል ላይ የተሰመረበት ዓ.ነገር የአንቅፁ ሀይለቃል ነው፡፡ ቅርፁም፡-
ዝርዝር ዓ.ነገር
ሐይለቃል
ዘርዝር ዓ.ነገር
አስተዋፅኦ/ ቢጋር/
1. ርእስ መምረጥ ርእስ መምረጥ፡- ለአንድ ፀሀፊ የመጀመሪያ ተግባር ነው፡፡ በመሆኑም ፀሀፊው
በሚስበው መልኩ የተሰጠውን ርእስ ማደራጀት የፀሀፊው ተቀዳሚው ተግባር ነው፡፡
2. ርእስ ማጥበብ ወይም መወሰን፡- የሚፃፍበት ርእስ የሚፃፍበትን ዓላማ የሚያ ሟላ ወይም
ግብ የሚመታ መሆን አለበት ስለዚህ ልኩን ፣መጠኑን ወዘተ የሚመጥን መሆን ይኖርበታል፡፡
ምክንያቱም የሚፃፈው ድርሰት በጊዜ ፣ በቦታና በቃላት መጠን የሚወሰን በሆን አለበት፡፡
3. አስተዋፅኦ ወይም ቢጋር መንደፍ ፡- ቢጋር የሚለው ቃል ዋናውን ድርሰት በፅሁፍ ከማስፈር
በፊት አጠቃላይ የፅሁፉን አካሄድ የሚያሳየውን ዝርዝር እቅድ ወይም ንድፍ ይመለከታል
እንዲሁም ድርሰት ከመፃፉ በፊት የኀሳቡን ቅንጅት ለማየትና ለማስተካከል ፤ በተጨማሪም
መልእክትን ለማስተላለፍ ራሱን የቻለ መሳሪያ በመሆን ያገለግላል፡፡ ይህ ከሆነ ድርሰቱ ከመፃፉ
በፊት በድርሰቱ ውስጥ መካተት ያለባቸውን ዋናዋና ፍሬ ነገሮች በቢጋር መልክ ማዘጋጀት
ለድረሰቱ ውጤታማነት አስፈላጊ ደረጃ ነው፡፡ ይህም የአስተዋፅኦ ወይም የቢጋር አነዳደፍ
የሚከተለውን ምስሌ መመልከት ይቻላል፡፡
ምሳሌ፡- ፀሀፊው ‹‹መስከረም ሲጠባ›› በሚል ርእስ ድርሰት ለመፃፍ አሰበና በቅድሚያ
የሚከተለውን አስተዋፅኦ ነደፈ፡፡
መስከረም ሲጠባ
1. አካባቢው አስደሳች ይሆናል
1.1 አበቦች ያብባሉ
1.2 የደፈረሱት ጅረቶች ይጠራሉ
1.3 በክረምት ተደብቀው የነበሩ አእዋፍ ብቅ ብቅ ይላሉ
1.4 ሰማዩ ይጠራል፤ ደመና ይወገዳል
2. ሰዎች መልካም ምኞታቸውን ይገልፃሉ፡፡
2.1. በዘፈን፣
2.2. ስጦታ በመለዋወጥ
2.3. እርስበርስ በመመራረቅና በመመሰጋገን
2.4. በአምልኮ ቦታዎች በመገኘትና ፈጣሪያቸውን በማመስገን፡፡
ልቦለድ
የልቦለድ አይነቶች
ለ. አጭር ልቦለድ ፡- አጭር ልቦለድ ስሙ እንደሚያመለክተው ቅርፁ አጭር የሆነ በስድ ፅሁፍ የሚቀርብ
የፈጠራ ድርሰት ነው፡፡ አጭር ልቦለድ ከ 10 ሺ ቃላት በታች የሚይዝ አንድ ዋንኛ ግብ ለማምጣት
የተዋቀረና ተውኔታዊነት የሚታይበት አጠር ያለ ትረካ ነው፡፡ አጭር ልቦለድ በአንድ ቅፅበት በአንድ
ነጠላ ሁነት ውስጥ የሚያልፍ አንድ ገፀባህሪ ላይ ያተኩራል፡፡ አጭር ልቦለድ በተወሰነ መቼት
የተቀረፁና አንድ ሁነት ወስጥ ገብተው በህሊናዊ ወይም በአካላው ድርጊት የሚሳተፉ አንድ ወይም
ጥቂት ገፀባህርያትን ይይዛል፡፡ ግጭት ወይም ተፃፃሪ ሀይላት ፍጭት የማንኛውም አጭር ልቦለድ
አምብርት ነው፡፡ በአጭር ልቦለድ ቅርፁ አጭር ከመሆኑ የተነሳ ጥድፊያ ፣ ነጠላ ውጤትና ቁጥብነት
ይታይበታል፡፡
የልቦለድ አላባዎች
በሁለቱም የልቦለድ አይነቶች ማለትም በአጭር ልቦለድ እና በረጅም ልቦለድ ውስጥ በመገኘት
ልቦለዶቹ ልቦለድ እንዲሆኑ የሚያደርጓቸው የልቦለድ አላባውያን ወይም ፍሬ ነገሮች በመባል
የሚታወቁት ታሪክ፣ ገፀባህሪ፣ መቼት፣ ግጭት፣ ትልም፣ አንፃር እና ጭብጥ ናቸው፡፡ እነዚህ
አላባውያን ምንነታቸውን ለማጥናት ሲባል ተለያይተው ይቅረቡ እንጂ በልቦለድ ውስጥ በተናጠል
የሚታዩ አይደሉም፡፡ ልቦለድ የሚኖረውም እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት አላባውያን ወይም ፍሬ ነገሮች
ተጣምረው ሲገኙ ብቻ ነው፡፡ እነዚህም የልቦለድ አላበውያን የሚባሉት የሚከተሉት ናቸው፡፡
1.ታሪክ ፡- ታሪክ የልቦለዱ መሰረት ነው፡፡ ልቦለዱን ከነበብን በኋላ ላላነበበ ሰው ስንገልፅ መጀመሪያ
እንደዚህ ሆነ ከዚያም እንደዚህ ሆነ ፣ በመጨረሻም እንደዚህ ሆነ ብለን የምንተርከው የልቦለድ ታሪክ
ይባላል፡፡ ታሪክ የጊዜ ቅደም ተከተልን መሰረት አድረገው በመቀናጀት የሚቀርቡትንና በገፀባህርያቱ
የሚፈፀሙ ድርጊቶችን ፣አነሳስ አካሄድና የመጨረሻ ውጤት የሚይዝ የልቦለድ ህይወት ወይም የመፃፉ
ሰበብና የህልውናው መሰረት ነው፡፡
3.ትልም/ሴራ/፡- በምክንያትና ውጤት የተሳሰሩ የሁነቶች ቅደም ተከተል ማለት ነው፡፡ ትልም የልቦለድ
ምሰሶ ነው፡፡ ልክ የሰውን ልጅ አጥንታቸው ደጋፏቸው አንደሚሄድ ሁሉ ትልምም ልቦለዱን
የሚደግፈው የጀርባ አጥንት ነው ማለት ይቻላል፡፡ ትልም ዋንኛው ትኩረቱ ምክንያትና ውጤት ላይ
ነው፡፡ ምሳሌ ንጉሱ ሞተ፡፡ ከዚያም ንግሰቲቷ ሞተች ፡፡ ሲል ይህ ታሪክ ይሆናል፡፡ በንጉሱ ሞት
ምክንያት ንግስቲቷ ሞተች፡፡ ይህ ትልም ነው፡፡ ምክንያቱም ለሆነ ነገር መከሰት ምክንያት
ስለሚያስፈልግ ነው፡፡ ባጠቃላይ ትልም በሴራ የተሞላ ነው፡፡
4. ግጭት፡- በልቦለድ አለም የሚኖሩ ገፀባህርያት በታሪኩ ውስጥ በተፈጠረላቸው እርስ በርሳዊ ግንኙነት
የተነሳ በተለያዩ ምክንያቶች ቅራኔዎች ወይም አለመግባባቶች ሳቢያ የሚፈጠረው ፍጭት ወይም
ፈልሚያ ግጭት ይባላል፡፡ በሁለት ተፃራሪ ሀይላት መካከል በሚደረገው ትግል አንዱ ሌላውን ለማሸነፍ፣
አንዱ ሌላውን ለመጣል፣ሌላው ላለመሸነፍ ሲል፣ ላለመበለጥ ሲፍጨረጨር ይታያል፡፡ እግጭት ውስጥ
ሊገቡ የሚገባቸው ተፃራሪ ሀይላት ተመጣጣኝ ወይም አቻ መሆን አለባቸው ፤ ምክንያቱም
የሚሸነፈው ገና ከወዲሁ ከታወቀ ልብ ሰቀላ አይኖረውም፡፡ ግጭት መነሻ፣ እድገት፣ ልብ ሰቀላ፣
ርግበትና ልቅት ይኖረዋል፡፡ እነዚ የግጭት ደረጃዎች ወይም ባህርያቶች በመባል ይታወቃሉ፡፡
5. መቼት፡- የልቦለድ ገፀባህርያት እንደእውኑ አለም ሰዎች የመኖሪያ አካባቢ አላቸው፡፡ ይህም ቦታና
ጊዜን ይመለከታል፡፡ በልቦለድ አለማቸው የሚነቀሳቀሱና ታሪካቸውን የሚፈፅሙት ደራሲው በፈጠረው
የተወሰነ አካባቢ ሲሆን የሚኖሩበትና ታሪካቸውን የሚፈፅሙበት ታሪካዊ ጊዜ፣ ወቅት፣ እለትና ሰዓትም
ይኖራቸዋል፡፡ ይህ የገፀባርያቱ መገኛ ስፍራና ጊዜ ባንድነት መቼት ይባላል፡፡
7.አንፃር፡- ደራሲው የልቦለዱን ታሪክ የሚያቀርብበት የተራረክ አቅጣጫ ማለት ነው፡፡ አንፃር
የሚገልፀው ፅሁፉ ወይም ታሪኩ በየትኛው መደብ ቀርቧል የሚለውን ነው፡፡
ባጠቃላይ እነዚህ አላባዎች በረጅም ልቦለድ ውስጥ ረጅም፣ ሰፊና ብዙ ሲሆኑ በአጭር ልቦለድ ውስጥ
ደግሞ አጭር፣ ቁጥብና ጠባብ ናቸው፡፡
የቃል ክፍሎች
የአማርኛ የቃል ክፍሎች የንግግር ክፍሎች በመባል ይታወቃሉ፡፡ በዘመናዊ ምሁራን አመለካካት
የአማርኛ የቃል ክፍሎች በአምስት ይመደባሉ፡፡ እነሱም፡- ስም፣ ግስ ፣ቅፅል፣ መስተዋድድና ተውሳከ ግስ
ናቸው፡፡
1. ስም
ለ. የዓ.ነገር ባለቤት በመሆን የሚያገለግል፡፡ ምሳሌ 1፡- ቶሎሳ ከብቶቹን አሰማራ፡፡ ባለቤት የሚለው ቃል
ቶሎሳ ነው፡፡
ሐ. የዓ.ነገር ተሳቢ በመሆን ያገለግላል፡፡ መሳሌ 1፡- ገመቹ ውሻውን መታው፡፡ ውሻውን የሚለው ቃል
ተሳቢ ነው፡፡
መ. አመልካች ወይም መጣኝ መጠንን የሚጠቁሙ ቃላትን የሚወስዱናቸው፡፡ ምሳሌ፡- እነዚያ ወወፎች፡፡
ምሳሌ 2. ሁለት ጠርሙስ ፣ አንድ ቤት ወዘተ… እነዚያ፣ ሁለት አና አንድ የሚሉት መጣኝ
መሰተዓምር ናቸው፡፡
ምሳሌ፡- ጥሩ ሰው፣. ጥቁር በሬ፣ ረዥም ዛፍ ናቸው፡፡ የተሰመረባቸው ቃላት ገላጮች ናቸው፡፡
በቀድሞው ሰዋሰው ራሱን የቻለው ተውላጠ ስም በዚህ የቃል ክፍል ተካቷል፡፡
1. ቅፅል
ቅፅል የስም ገላጭ ከመሆን ተጨማሪ በጣም የሚል ቃል ጨምሮ የሚነገር ቃል ቅፅል ይባላል፡፡ ገላጭ
ወይም ቅፅል የምንለው ስምን ከተለያየ ባህርያት አንፃር ይገልፃል ፡፡ እሱም፡-
ሀ. ስምን ከመጠን እንፃር የሚገልፁ ቅፅሎች የሚባሉት፡- ረዥም ፣ ወፍራም፣ ቀጭን፣ አጭር ወዘተ
ናቸው፡፡ ምሳሌ አጭሩ ሰውዬ መጣ፡፡ የተሰመረበት ቃለ ቅፅል ነው፡፡
ለ.ስምን ከባህሪ አንፃር የሚገልፁ ቅፅሎች የሚባሉት፡-ብልህ፣ ደግ፣ የዋህ፣ ክፉ፣ አዋቂ ወዘተ ናቸው፡፡
ምሳሌ፡- ደጉ ልጅ መጣ፡፡ የተሰመረበት ቃል ቅፅል ነው፡፡
ሐ. ስምን ከመልክ አንፃር የሚገልፁ ቅፅሎች የሚባሉት፡- ቀይ፣ ቢጫ፣ ጥቁር፣ አረንጓዴ ወዘተ.. ምሳሌ፡-
ቀይ ክር እወዳለሁ፡፡ የተሰመረበት ቃል ቅፅል ነው፡፡
መ. ስምን ከሁኔታ አንፃር የሚገልጹ ቅፅሎች የሚባሉት ፡- ደጋማ፣ ቆላማ፣ አይናማ፣ ቡናማ፣ አሸዋማ፣
ገደላማ ወዘተ…. ምሳሌ. ገደላማ መሬት ነው፡፡ የተሰመረበት ቃል ቅፅል ነው፡፡
ሠ. ስምን ከቅርፅ አንፃር የሚገልፁ ቅፅሎች የሚባሉት ፡- ሞላላ፣ ክብ፣ ጠፍጣፋ፣ ሹል ወዘተ… ናቸው፡፡
ምሳሌ 1. ጠፍጣፋ ጠረጴዛ ምሳሌ 2. ሹል እንጨት የተሰመረባቸው ቅፅሎች ናቸው፡፡
ረ. ስምን ከወገን አንፃር የሚገልፁ ቅጥሎች፡- ኢትዮያዊ፣ ሱዳናዊ፣ ተርካዊ ወዘተ ናቸው፡፡
3.ግስ
4.ተውሳከ ግስ
ግስን የሚገልፅ ቃል ተውሳከ ግስ ተብሎ ይጠራል፡፡ በተውሳከ ግስ የቃል ክፍል ውስጥ ሊመደቡ
የሚችሉት ቃላት በቃላዊ ማንነታቸው እንጂ በሰዋሰዋዊ አገልግሎት መሆን የለበትም፡፡ ምስሌ 1.
ጫላ በሩጫ መጣ ፡፡ 2. ካሳ እሁድ ይመጣል፡፡ እነዚህ የተሰመረባቸው ቃላት በጥንታውያኑ የቃል
ክፍል አመዳደብ የተመደቡ ናቸው፡፡ በዘመናዊ የቃል ክፍል አመዳደብ ግን በቃላዊ ምንነታቸው ላይ
ብቻ የሚያተኩር መሆን አለበት፡፡ እነሱም፡- ቶሎ፣ ገና፣ ጅልኛ፣ ምንኛ፣ ክፉኛ ናቸው፡፡ ምሳሌ፡- ልጁ
ከፉኛ ታመመ፡፡ አስቴር ምንኛ ታሳዝናለች፡፡
5. መስተዋድድ
ሀረግ
የሀረግ አይነቶች
ዘይቤ ለአገላለፅ ትኩስነትና ጥንካሬ ለመስጠት ሲባል ከመደበኛው የቃላት ፍቺ ወይም የቃላት አደራደር ስርኣት
ይሁነኝ ብሎ ማፈንገጥ ነው፡፡ ዘይቤ አንድን ሁኔታ የሚገልፀው የቃላትንና የሀረጋትን ትርጉምና አገባብ
ከተለመደውና በውል ከታወቀው ወጣ ወይም ለየት በማድረግ ለሀሳብ ላቅ ያለ ደረጃ ለመስጠት ነው፡፡ ዘይቤ
የሚፈጥረውም አንድን ባህሪ ስሜት፣ ድርጊት፣ ሁኔታ ሰው ወይም እንሰሳ ከሌላ ነገር ጋር በማወዳደርእና
በማመሳሰል የአንድን ባህሪ ለሌላ በመስጠት ወይም በመለወጥ የአንድን ባህሪ በመለወጥና በመቅዳት እንዲሁም
በሌላ በመወከል ነው፡፡
ዘይቤዎች በአይነታቸው ብዙ ናቸው፡፡ አንድ አንድ ምሁራን 250 የዘይቤ አይነቶች አንዳሉ ይናገራሉ፡፡ነገር ግን
እነዚህን ዘርዝሮና ለይቶ የገለፀ እሰካሁን የለም፡፡ ብዙዎቹ እሰካሁን በጣም የተለመዱትና ዋናዋና የሚባሉት
ከአስራሁለት እሰከ አስራምስት የሚደርሱ ናቸው፡፡እነሱም ፡-
የዘይቤ አይነቶች
1. አነፃፃሪ ዘይቤ፡- ይህ የዘይቤ አይነት ነገሮችን ፣ሀሳቦችን ባህሪዎችንእና ድርጊቶችን በማነፃፀር ወይም
በማወዳደር የሚፈጠር ነው፡፡በዚህ የዘይቤ አይነት ሁለት ተነፃፃሪዎች ከተለያዩ ጎራዎች የመጡና
አብዛኛው የተለያዩ ባህርያት ያላቸው መሆን አለባቸው ፤ ነገር ግን የሚነፃፀሩበት አንድ የጋራ ባህሪ
ይኖራቸዋል፡፡ በአነፃፃሪ ዘይቤ እንዲጎላ ወይም እንዲደመቅ የተፈለገው ነገር ተገላጭ ሲባል ተገላጩን
አጉልቶ ወይም አተልቆ ወይም አድምቆ ለመግለፅ የሚገባው ደግሞ ገላጭ ይባላል፡፡ በተነፃፃሪዎቹ
መካከል መኖር ያለበት የጋራ ባህሪ ደግሞ ሰበበ ንፅፅር ይባላል፡፡ በዚህ የዘይቤ አይነት መነፃፃሪያው ቃል
እንደ፣ ይመስል እና ያህል የሚሉት ናቸው፡፡
ምሳሌ፡- አስቴር እንደጦጣ እየዘለለች ከመቀመጨዋ ተነስታለች ፡፡
ተገላጭ፡- አስቴር -- ገላጭ፡- እንደጦጣ-- የጋራ ሰበበንፅፅር፡- ሁለቱም መዝለላቸው ነው
ምሳሌ ሁለት፡- ገመቹ ጅብ ይመስል ሌሊት መሄድ ይወዳል፡፡
ተገላጭ ፡- ገመቹ -- ገላጭ፡- ጀብ------ሰበበ ንፅፅሩ ሁለቱም ሌሊት መሄዳቸው፡፡
2. ተለዋጭ ዘይቤ ፡- ይህ የዘይቤ አይነት የአንዱን ባህሪ ለሌላ በመስጠት የሚፈጠረ ነው፡፡ አንድን ሰው ፣
እንሰሳ ፣ተክል ወይም ግኡዝ ነገር ወይም አካል ወስዶ ለሌላው በመስጠት ሀሰቡን በጎላ ሁኔታና በምስል
ይገልፃል፡፡ ምሳሌ 1፡- አዶናይ ፀሀይ ነች፡፡ እዚህ ምሳሌ ላይ የፀሀይን በህሪ የወሰደቸው አዶናይ ነች፡፡
ምሳሌ 2፡- ካሳ አንበሳ ነው፡፡ ምሳሌ 3፡- አልማዝ ጊንጥ ነች፡፡
3. ሰውኛ ዘይቤ፡- ይህ የዘይቤ አይነት የሰውን ልዩ ልዩ ባህርያት ድርጊትና ችሎታ ሰው ላልሆነ ነገር
ለእንሰሳ ለግኡዝና ለተክሎች በመስጠት የሚፈጠር ነው፡፡ በዚህ የዘይቤ አይነት ሰው ያልሆኑ ነገሮች
ሲበሉ፣ ሲጠጡ፣ ሲያሥቡ ሲናገሩ ፣ሲጠማቸው ሲያዝኑ እና ስራን ሲሰሩ ይታያሉ፡፡ ሰውኛ ዘይቤ
ብዙውን ጊዜ በሶስተኛ መደብ ነጠላ ቁጥር ይጠቀማል፡፡
ምሰሌ 1፡- ምድር ጎዘጎዘች ቅጠል መንጣፏን
በጣም ደስ እንዲላት መኖሪያቸው ደን
ምሳሌ 2፡- ጸደይ ልትመጣነው ደገሰች አበባ
ቁንን ተሰናድታ አቀረበች ኮልባ
አደይም ጀመረች ቀይ ቀለም ትቀባ
በለስ ከተፍ አለች ሰውነቷን ታጥባ ፡፡ በዚህ ምሳሌ የተገለፀው የፀደይ ወራት ድምቀትን ፣
ልምላሜ፣ የአበቦች መፍካትና የወንዞች መጥራት ነው የተገለፀው፡፡
ተውኔት
ተውኔት ከኪነ ጥበብ ዘርፎች ማለትም ከስነ ፅሁፍ ከስነ ስዕል፣ ከሙዚቃ፣ከቅርፃቅርፅና ከፊልም አንዱ
ነው፡፡ ተውኔት ወይም ድራማ የሚለው ቃል የተገኘው ‹ዴራን›› ከሚለው የግሪክ ቃል ነው፡፡
ትረጉሙም ማድረግ ወይም መከወን ማለት ነው፡፡
የተውኔት አላባውያን
የተውኔት አላባውያን የሚባሉት የሚከተሉት ናቸው፡፡
1. ገፀባህርያት ፡- በአንድ ተውኔት ውስጥ በፀሀፌ ተውኔቱ የሚፈጠሩ እና በተፈጠሩበት ተውኔት
ውስጥ የሚከናወኑት የስራ ድርሻ ያላቸው በገሀዱ አለም ሰውን መስለውና ሰውን ወክለው አንድ
ሰው በመናገርና የተለያዩ ተግባራትን በመፈፀም የሚያገለግሉ ናቸው፡፡ ገፀባህርያት የሚናገሯቸው
ድርጊቶች ለአንባቢያን ሆነ ለተመልካቾች ሙሉ በሙሉ ግልፅ ናቸው፡፡
2. መቼት፡- በአንድ ተውኔት ውስጥ ድርጊቱ መቼ እንደተፈፀመ ጊዜውንና የት እንደተፈጸመ
ቦታውን ይገልፃል፡፡
3. ታሪክ፡- በአንድ ተውኔት ውስጥ በንግግርም ሆነ በገጸባህርያት በድርጊት የሚከናወነውን የአንድ
ተውኔት ታሪክ ነው፡፡ የተውኔት ታሪክ ሌሎችን አላባውያን ይይዛል ማለት ነው፡፡ ገጸባህርያት፣
መቼት፣ ትልምና ግጭት የሚፈጥሩት በአንድ ተውኔት ታሪክ ውስጥ ነው፡፡
4. ትልም፡- ሌላው የተውኔት አላባ ነው፡፡ ገጸባህርያት የሚፈፅሟቸው ድርጊቶች ምክንያትና
ውጤትን ተከትለው የሚካሄዱ አንደመሆናቸው ትልም በተውኔቱ ውስጥ የሚካሄዱትን ነገሮች
ምክንያትና ውጤት ያሳያል፡፡
5. ግጭት፡- በአንድ ተውኔት ውስጥ የሚገኘው ሌላው አላባ ግጭት ነው፡፡ በአንድ ተውኔት ውስጥ
ገፀባህርያት በሚያራምዱት ተግባር ወይም በሚያከናውኑበት ታሪክ እርስበርሳቸው ወይም ይህን
ላድርግ ወይስ አላድርግ በሚል በግል ከራሳቸው ጋር ይጋጫሉ፡፡ ማንኛውም የተውኔት ታሪክ ያለ
ግጭት ሊፈጠር አይችልም፡፡ ያለ ግጭት የሚፈጠር ታሪክ እንጂ የተውኔት ታሪክ አይሆንም፡፡
የተውኔት መዋቅር