You are on page 1of 39

የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

በብንያም ከድር

የተማሪው ስም፡- -----------------------------------------


ክፍል -----------------
ቁጥር --------------

ታህሳስ 2013
አ.አ

ማውጫ
1.የአማርኛ ቋንቋ ሆሄያት እና ብዛታችው...............................................................................................................3

1
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

2.የኢትዮጵያውያን ቁጥር እና ስያሜያቸው............................................................................................................4

3. የኢትዮጵያውያን የቀን አቆጣጠር......................................................................................................................5

4. በአማርኛ ቋንቋ ውስጥ የሚገኙ የባዕድ ሀገራት ቃላቶች ትክክለኛ የግዕዝ ፍቺያቸው.................................................5

5.ስነ ድምፅ.........................................................................................................................................................7

6. ምንባብ አንድ..................................................................................................................................................7

7. ዘመናዊ የአማርኛ ቋንቋ የንግግር ክፍሎች............................................................................................................9

8. ምንባብ ሁለት...............................................................................................................................................11

9.የስም እርባታ..................................................................................................................................................14

10.የቅፅል አይነቶች............................................................................................................................................15

11.ግስ..............................................................................................................................................................16

12. ተውሳከ ግስ.................................................................................................................................................17

13. መስተዓምር፡-..............................................................................................................................................18

14. ምዕላድ.......................................................................................................................................................19

15 የምስረታ ምዕላድ.........................................................................................................................................20

16.ምንባብ ሶስት...............................................................................................................................................21

17. አ.ነገር........................................................................................................................................................24

18. ሥርዓተ ነጥብ..............................................................................................................................................26

19.የቃላት ትርጉም /ፍቺ/...................................................................................................................................28

20.ሥነፅሁፍ.....................................................................................................................................................30

21.ግጥም.........................................................................................................................................................32

22.የግጥም አይነት.............................................................................................................................................33

23.ቲያተር........................................................................................................................................................33

24. ዘይቤ..........................................................................................................................................................34

25.ቅኔ..............................................................................................................................................................38

26.አንቀፅ.........................................................................................................................................................38

1.የአማርኛ ቋንቋ ሆሄያት እና ብዛታችው


ሀ ሁ ሂ ሃ ሄ ህ ሆ ጀ ጁ ጂ ጃ ጄ ጅ ጆ

2
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

ለ ሉ ሊ ላ ሌ ል ሎ ገ ጉ ጊ ጋ ጌ ግ ጎ

ሐ ሑ ሒ ሓ ሔ ሕ ሖ ጠ ጡ ጢ ጣ ጤ ጥ ጦ

መ ሙ ሚ ማ ሜ ም ሞ ጨ ጩ ጪ ጫ ጬ ጭ ጮ

ሠ ሡ ሢ ሣ ሤ ሥ ሦ ጰ ጱ ጲ ጳ ጴ ጵ ጶ

ረ ሩ ሪ ራ ሬ ር ሮ ጸ ጹ ጺ ጻ ጼ ጽ ጾ

ሰ ሱ ሲ ሳ ሴ ስ ሶ ፀ ፁ ፂ ፃ ፄ ፅ ፆ

ሸ ሹ ሺ ሻ ሼ ሽ ሾ ፈ ፉ ፊ ፋ ፌ ፍ ፎ

ቀ ቁ ቂ ቃ ቄ ቅ ቆ ፐ ፑ ፒ ፓ ፔ ፕ ፖ

በ ቡ ቢ ባ ቤ ብ ቦ ቨ ቩ ቪ ቫ ቬ ቭ ቮ

ተ ቱ ቲ ታ ቴ ት ቶ

ቸ ቹ ቺ ቻ ቼ ች ቾ

ኀ ኁ ኂ ኃ ኄ ኅ ኆ

ነ ኑ ኒ ና ኔ ን ኖ

ኘ ኙ ኙ ኛ ኜ ኝ ኞ

አ ኡ ኢ ኣ ኤ እ ኦ

ከ ኩ ኪ ካ ኬ ክ ኮ

ኸ ኹ ኺ ኻ ኼ ኽ ኾ

ወ ዉ ዊ ዋ ዌ ው ዎ

ዐ ዑ ዒ ዓ ዔ ዕ ዖ

ዘ ዙ ዚ ዛ ዜ ዝ ዞ

ዠ ዡ ዢ ዣ ዤ ዥ ዦ

የ ዩ ዪ ያ ዬ ይ ዮ

ደ ዱ ዲ ዳ ዴ ድ ዶ

 የመጀመሪያ ፊደላት ብዛት 34 ሲሆን አጠቃላይ ሁሉም ፊደላት ብዛት 238 ናቸው
ማሳሰብያ
 የአማርኛ ቋንቋ ከግዕዝ 24 ፊደላትን ወስዷል እነሱም
ሀ፣ለ፣ሐ፣መ፣ሠ፣ረ፣ሰ፣ቀ፣በ፣ተ፣ኀ፣ነ፣አ፣ከ፣ወ፣ዐ፣ዘ፣የ፣ደ፣ገ፣ጠ፣ጸ፣ፀ፣ፈ፣ፐ ናቸው፡፡
 ጰ ከግሪክ
 ፐ እና ቨ ከእንግሊዘኛ
 ኸ፣ዠ፣ጀ፣ጨ፣ቸ፣ሸ፣ኘ፣የ ከኩሽ ቋንቋ የተወሰዱ ፊደላት ናቸው፡፡

3
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

 ስለዚህ አማርኛ የራሱ የሆኑ ፊደላት የሉትም ሁሉንም ፊደሎች ከ ግዕዝ ከኩሽ ቋንቋዎች ከግሪክ እና
ከእንግሊዘኛ የወሰዳቸው ናቸው፡፡

የአማርኛ ሞክሼ ሆሄያት

 ሀ ፣ ሐ፣ ኸ፣ ኀ ሠ፣ ሰ አ፣ ዐ ጸ፣ ፀ

የሆሄያት ስያሜ

ሀ ግዕዝ ሁ ካብዕ ሂ ሳልስ ሃ ራብዕ ሄ ሀምስ ህ ሳድስ ሆ ሳብዕ

2.የኢትዮጵያውያን ቁጥር እና ስያሜያቸው


1 ፩ አሀዱ 2 ፪ ክልኤቱ 3 ፫ ሰልስቱ

4 ፬ አርባዕቱ 5 ፭ ሐምስቱ 6 ፮ ስድስቱ

7 ፯ ሰባቱ 8 ፰ ስምንቱ 9 ፱ ተሰዓቱ

10 ፲ አስርቱ 20 ፳ እስራ 30 ፴ ሰላሳ

40 ፵ አርብዓ 50 ፶ ሃምሳ 60 ፷ ስድሳ

70 ፸ ሰባ 80 ፹ ሰማንያ 90 ፺ ተሰዓ

100 ፻ ምዕት 200 ፪፻ ክልዔቱ ምዕት

1,000 ፲፻ አስርቱ ምዕት 2,000 ፳፻ እስራ ምዕት

10,000 ፻፻ እልፍ 20,000 ፪፻፻ ክልዔቱ እልፍ

100,000 ፲፻፻ አስርቱ እልፍ 200,000 ፳፻፻ እስራ እልፍ

1000000 ፻፻፻ አእላፍት 10,000,000 ፲፻፻፻ ትእልፊት

100,000,000 ፻፻፻፻ ትልፊታት 1,000,000,000 ፲፻፻፻፻ ምዕልፊት

ማስገንዘቢያ

 ከ 10 -19 ለመፃፍ አስርን ከፊት አስቀድሞ ከ አንድ እስከ ዘጠኝ ያሉትን ቁጥሮች ማስከተል ነው፡፡
 ከ 20-90 ያሉትን ለመፃፍ ከ 20 እስከ 90 ያሉትን ከፊት አስቀድሞ ከ አንድ እስከ 9 ያሉትን ቁጥሮች
ማስከተል፡፡
 ከ 100 -900 ለመፃፍ ከ 1-9 ያሉትን ቁጥሮች አስቀድሞ መቶን ማስከተል፡፡
 ከ 1000- እስከ 9000 ለመፃፍ ከ 10-90 ያሉ ቁጥሮችን በማስቀደም 100 ማስከተል ነው፡፡
 ከ 10 ሺህ እስከ 90 ሺህ ያሉትን ለመፃፍ ከ 1-9 በማስቀደም አስርሺን መጻፍ፡፡ ወ.ዘ.ተ

3. የኢትዮጵያውያን የቀን አቆጣጠር

1.1 ዘመን ለመስራት

4
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

ሰው ከገነት ከተባረረ በኋላ በአምላኩ ቃል የተገባለት 5500 ዘመን በኋላ ተመልሶ መጥቶ እንደሚያድነው ነው
እነሆ የሰው ልጅ ከዳነ ዘንድሮ 2012 ዓመታት ተቆጠሩ
5500 አመታት ሲቆጠሩ ዓመተ ዓለም ይባላል
2012 ኣመታት ሲቆጠሩ ዓመተ ምህረት ይባላል
ስለዚህ ዘመንን ለመስራት የሚከተለውን መንገድ እንጠቀማለን

አ.አ + አ.ም = ሰው የተፈጠረበት


5500 + 2012 = 7512
ሰው የተፈጠረበትን ካወቅን በኋላ መጠነ ራቢት መስራት አለብን
መጠነ ራቢትን ለመስራት፡- ሰው የተፈጠረበት ሲካፈል ለ 4 ነው
7512 ÷4 = 1878
ቀሪው 1 ከሆነ ዘመኑ ማቲዮስ
ቀሪው 2 ከሆነ ዘመኑ ማርቆስ
ቀሪው 3 ከሆነ ዘመኑ ሉቃስ
ቀሪው 4/0/ ከሆነ ዘመኑ ዮሐንስ ይሆናል፡፡
 መጠነ ራቢታችን 1878 ነው፡፡

ዘመን ለመስራት፡- ሰው የተፈጠረበት - (4 x መጠነ ራቢት)

7512- (4 x 1878)

7512 - 7512 ቀሪ 0 ስለሆነ ዘመኑ ዮሐንስ ነው

3.2 መባቻ

መባቻ ማለት መስከረም 1 የሚውልበትን ቀን ማለት ነው፡፡

መባቻ ለመስራት ፡- (ሰው የተፈጠረበት + መጠነ ራቢት) ÷ 7

ቀሪ 0 ከሆነ ሰኞ ቀሪ 2 ረብዑ ቀሪ 4 ከሆነ ዓርብ

ቀሪ 1 ከሆነ ማክሰኞ ቀሪ 3 ሐሙስ ቀሪ 5 ቅዳሜ ቀሪ 6 እሁድ

(7512 + 1878) ÷ 7

9390 ÷ 7

1341 ደርሶ ቀሪ 3 ስለዚህ በ 2012 መባቻው ሐሙስ ቀን ነበር፡፡

4. በአማርኛ ቋንቋ ውስጥ የሚገኙ የባዕድ ሀገራት ቃላቶች ትክክለኛ የግዕዝ ፍቺያቸው

1.ኮሌጅ፡- መካነ ትምህርት - አስትሮኖሚ፡- ሥነ ሕይወት - ፊዚክስ፡- የተፈጥሮ ጥናት


2.ዩኒቨርሲቲ፡- መካነ አእምሮ - ኬሚስትሪ፡- ሥነ ውሕደት
3.ሌክቸር፡- ትምህርተ ጉባኤ - ባይሎጂ፡- ሥነ ሕይወት
4.ሌክቸረር፡- መምህረ ጉባኤ - ቪዛ፡- የይለፍ ቃል
5.ዲን፡- ሊቀ ጉባኤ - ፓስፖርት፡- የኬላ ማለፊያ
6.ቢሮ፡- መስሪያ ቤት - ፓስዋርድ፡- የይለፍ ቃል
7. ሲቪል ሰርቪስ፡- ሰላማዊ አገልግሎት - ቴሌኮሚኒኬሽን፡- ምሕዋረ ዜና
8.ኮምፒዩተር፡- መቀመሪያ - ስካን፡- ምክታብ - ፕሬዝዳንት፡- ሊቀ ሀገር/ ሙሴ
9.ድግሪ፡- ማዕረግ - ሳሎን፡- የእንግዳ መቀበያ - ቱሪዝም፡- ስነሕዋፄ

5
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

10. ሚኒስቴር ፡- ምሉክ - ኢኮኖሚክስ፡- ስነ ብዕል - ሀዋላ፡- ምሕዋረ ንዋይ


11. ማስ ሚዲያ፡- ምህዋረ ዜና - ኢምባሲ፡- የእንደራሴ ፅ/ቤት -ዲፕሎማት፡- የመንግስት መልዕክተኛ
12. ፎቶ ግራፍ፡- ብራናዊ ስዕል - ኢንተርኔት፡- የህዋ አውታር - ዶክተር፡- ለቀ ሙሁር
13. ራዲዮ፡- ንፋሰ ድምፅ - ፖሊስ ፡- የህግ ዘበኛ - ሎሬት፡- አምበል ተሸላሚ
መልመጃ አንድ
መመሪያ አንድ፡- ለሚከተሉት ጥያቄዎች ትክክለኛ መልስ ስጡ
1. ስምንቱ ምዕት ወ ስልሳ ---------------------- 2. እስራ ምዕት ወ አሀዱ ምዕት ወ ክልኤቱ ------------
3. ተሰዓቱ ምዕት ወ ክልኤቱ ------------------- 4. ሀምሳ ምዕት ወ ሰልስቱ ምዕት --------------------
5. ክልኤቱ ምዕት ወ ሰላሳ ወ አርባኣቱ -------------------------
መመሪያ ሁለት፡- ለሚከተሉት የአረብ ቁጥር ትክክለኛውን የግዕዝ ፍቺ ፃፉ ማለት በቁጥር

6. 507 ------------------- 7. 1245 ------------------ 8. 6785 ------------------ 9. 8975 ----------------

10. 1675---------------- 11. 709 ------------------ 12. 1267 --------------------13. 9876 -------------------

መመሪያ ሶስት፡- ለሚከተሉት ጥያቆዎች ሰርታችሁ አሳዩ

14. በ 2067 ዓ.ም ዘመን እና መባቻ ምን ላይ ይውላል


15. በ 3056 ዓ.ም ዘመን እና መባቻ ምን ላይ ይውላል
መመሪያ አምስት፡- ለሚከተሉት ቃላት ትክክለኛ የግዕዝ ፍቺያቸውን ስጡ
16. ኮሌጅ፡- ---------------------------------- 23. ዩኒቨርሲቲ -----------------------------
24. ሌክቸር፡- ---------------------------------- 25. ሌክቸረር-------------------------------
26. ዲን፡- ------------------------------------ 27. ቢሮ፡- ----------------------------------
28. ሲቪል ሰርቪስ፡---------------------------- 29. ሰላማዊ --------------------------------
30. ኮምፒዩተር፡- -------------------------------- 31. ድግሪ፡- --------------------------------
32. ሚኒስቴር ፡- -------------------------------- 33. ሚኒስቴር ፡- ---------------------------------
33. 34.ማስ ሚዲያ፡- ------------------------------- 35. ፎቶ ግራፍ፡- --------------------------------
36. ራዲዮ፡- --------------------------------- 37. ፖሊስ ፡- --------------------------------
38. ኢንተርኔት፡- ---------------------------- 39. ሎሬት፡- ---------------------------------
40. ዶክተር፡- --------------------------------- 41. ኢምባሲ፡- -------------------------------
42. ዲፕሎማት፡- ---------------------------- 43.ኢኮኖሚክስ፡- -----------------------------
44. ሀዋላ፡- ----------------------------------- 45. ሳሎን፡- -----------------------------------
46. ቱሪዝም፡- -------------------------- 47. ስካን፡- ---------------------------------
48. ፕሬዝዳንት፡- ------------------------------- 49. ቴሌኮሚኒኬሽን፡- -----------------------
50. ቪዛ፡- -------------------------------------- 51. ፓስፖርት፡- -----------------------------

6
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

5.ስነ ድምፅ
 ለማንኛውም ቋንቋ መሰረቱ ድምፅ ነው፡፡

 የንግግር ድምፅ ለመፍጠር አየር እና የአንደበት እንቅስቃሴ ያስፈልጋል፡፡

 ድምፅ በአብዛኛው የሚፈጠረው ከሳንባችን በሚወጣ አየር ነው፡፡

 የአንደበት አካላት የሚባሉ የታችኛው ከንፈር፣ምላስ እንጥል፣ሰርን፣ከንፈር፣ድድ፣ላንቃ፣ትናጋ፣እንጥል፣ጉሮሮ እና ማንቁርት ናቸው፡፡

 የታችኛው ከንፈር፣ምላስ የሚንቀሳቀሱ የአንደበት አካላት ናቸው፡፡

 የአማርኛ ቋንቋ ሁለት አይነት ድምፆቸ አሉት እነሱም ተነባቢ እና አናባቢ ይባላሉ፡፡

ተነባቢ ድምፆች
 አማርኛ 30 ተነባቢ ድምፆች ያሉት ሲሆን 27 ተራ 3 ውስብስብ ናቸው፡፡
 ከ 27 ተራ ተነባቢ ድምፆች መካከል 3 ቱ የተውሶ ድምፆች ናቸው፡፡ እነሱም /ፕ፣ጵ እና ፅ/ ናቸው፡፡
 ክው፣ቅው፣ቅው የሚባሉት ድምፆች ውስብስብ ተነባቢ ድምፆች ይባላሉ፡፡
የአናባቢ እና የተነባቢ ቅንጅት
ፊደል ተነባቢ አናባቢ ቅንጅት
በ ብ ኧ ብኧ
ቡ ብ ኡ ብኡ
ቢ ብ ኢ ብኢ
ባ ብ ኣ ብኣ
ብ ብ እ ብእ
ቦ ብ ኦ ብኦ
ምሳሌ፡- 1. በር /ብኧር/
2. ጠርሙስ /ጥኧርምኡስ/

6. ምንባብ አንድ
------------------- በመጨረሻም በሰው አቆጣጠር በ 1770 ዓ.ም ተከታዩ ትዕዛዝ ደረሰን እስከዚህ ጊዜ ድረስ ማለትም የመጨረሻውን
6 ኛውን ክፍል ተግባራዊ አድረገን እስክናጠናቅቀቅና ተከታዩን ትዕዛዝ እስኪደርሰን ድረስ የመጨረሻ ጎላችን የትኛዋ አህጉር ውስጥ
የምትገኝ ምን የምትባል አገር እንደሆነች አናውቅም ነበር፡፡ ይህ ለኛ ገና አልተገለፀልንም ነበር፡፡ እናም ትእዛዙ ደረሰን አዲስቷን የምድር
መንግስት በዘመናዊ መልክ የመገንባት ስራችሁን ጀምሩ ተባልን፡፡

ይህ ማለት የቲዮሪው ትምህርት በሙሉ ወደ ተግባር ተለውጦ ተጨባጭ ውጤት ወደሚያስገኝበትና ወደ ሌላ አዲስ ስልጣኔ ሽግግር
መግባትና ማስቀጠል መቻል ተፈቀደልን ማለት ነው፡፡

ይህ ማለት በዚህ መፅሐፍ ውስጥ እንደሌሎቹ ያልተብራሩ በስም ብቻ የተጠቀሱና እኛ ድቅሎችና የሰው ልጅ ከስማቸው በቀር
አይነታቸውን እና መገኛ ቦታቸውን የማያውቃቸውን ነገሮችንም ሆነ በምድር እና በውስጧ ያሉ በርካታ ጠቃሚ የሆኑ ነገር ከምን ጋር
ሲጣመር እና ሲዋሀድ ምን እንደሚያስገኝ የዚያ ግኝት መጨረሻ ምን እንደሚሆን እና ሰዎች በምን መንገድ ጥቅም ላይ አውለው
ሊገለገሉበት እንደሚችሉ እየተሻሻለ ሄዶ የት እንደሚደርስና ሄዶ ሄዶ እንዴት ለልዑላችን ዋና አላማ ሊውል እንደተፈለገ ግልፅ ሆነልን
ማለት ነው፡፡ ይህ ማለት ጎላችንን እንድናውቅ ተፈቀደልን ማለት ነው! እናም እነዚህን ነገሮች የሚያብራሩ ቁጥራቸው የበዛ መንፍሳዊ
ጭፍሮች እንዳሉና እነሱን እንድንገናኝ ተነገረን፡፡ ቀጣይ ትዕዛዝ ያልኳችሁ ይህንን ነው፡፡ እንጠብቀውና እንፈልገው የነበረው ይህኑኑ ነው፡፡

ስለዚህ እነዚህን የልኡላችን ጭፍሮች በስምና በስልጣን ለይተን እና አውቀን የትኛው መንፈሳዊ አካል በየትኛው ጉዳይ እንደተሾመ
ተረድተን የትኛው ለየትኛው እውቀትና ጥበብ ሊረዳን እንደሚችል ተገንዝበን ሁሉንም በየስማቸው እየጠራን ማዘዝ እና ለምንፈልገው
አላማ አማካሪ ማድረግ እንደምንችል ተነገረን፡፡ ነገር ግን እነሱንም ለማወቅ እና ለመገናኘት ተገናኝተንም እውቀታቸውን ለመካፈልና
ለመጠቀም እንቻል እንጂ ፈልገን የማግኘቱ ስራ ግን ለኛ ለንጉሳውያን ቤተሰቦች የተተወ የቤት ስራ ሆነ፡፡ የሰው ልጅ የመጀመሪያ
ፅሕፈት በሆነው ከሰው ልጅ ጋር በጥፋት ውሀ በዳነው የግዮን ምንጭ ባለበት አገር በአንድ ደብር የተቀመጠውን ሚስጥሩን ማንም
ባልፈታው በሄኖክ መፅሐፍ ሁሉንም እወቁት ሁሉንም ድረሱበት ይህ የእናንተ ስራ ነው በእናንተም መሰራት ያለበት ስራ ነው፡፡የእናንተ

7
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

የዘር ሀረግ የሚመዘዘው ከእነማን እንደሆነ የተዘረዘረበትም መፅሐፍ ስለሆነ የአያቶቻችሁን ቅድመ አያት ዋና ምንጭ የምታገኙበትም
ስለሆነ አግኙት ታሪክ እና ማንነታችሁን እዛ ስታገኙ ማን በምን ላይ እውቀት እንዳለው ማን በምን ላይ እንደተሾመ ከዚያ መፅሐፍ
ትረዳላችሁ ከአምስቱም የሄኖክ መፅሐፍት አግኙ የሚል ትዕዛዛ ነበር የደረሰን፡፡ ጎላችንን አወቅን ማለት ነው፡፡

ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ወደ ሽግግሩ ገብተን አዲሲቷን የምድር መንግሰት ምስረታ እጅግ ዘመናዊ በሆነ መንግድ ጀመርን፡፡ ስለ መፅሐፈ ሄኖክ
ከዚህ ቀደም በደንብ ተብራርቶላችኋል መፅሐፈ ሄኖክ፣ ሚስጠረ ሄኖክ፣ራዕየ ሄኖክ፣ ትንቢተነ ሄኖክ፣ነገረ ሄኖክ የሚባሉትን ናቸው
በእርግጥም ለኛ የጠቀመንና አሁን ለምንለው ነገር ሁሉ ሙሉ ምላሽ የነበረው ሚስጥረ ሄኖክ የሚለው ነው፡፡

ከዚያም የልዑላችን ታማኝ አገልጋይ የሖኑት አጠገባችሁ ያሉት ጳጳስ ቀደም ሲል እንዳብራሩላችሁ የእኔ ቅድመ አያት ተብላ
የምትታወቀው ነገር ግን እኔ እራሴ ከኛ ወገን የሖነውን ጀምስ ብሩስን በ 1770 ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ ገንዘብና በቂ ስንቅ አስይዘን ላክነው፡፡
ሁሉንም የሄኖክ መፅሐፍት አገኛቸው በ 7 ዓመት ቆይታው መፅሐፈ ሄኖክን አዘበራርቆ ቀሪ ትቶላቸው ሌሎቹን ግን ቀሪ ሳይተው ይዞልን
መጣ በ 7 ዓመት ቆይታው በእኛ ትዕዛዝ ተምሮት እንዲመጣ በተደረገው የግዕዝ ቋንቋ፤ የግዕዝን የመጀመሪያ ፅሑፍ በቤተመንግስታችን
አብራራልን አቤት የጠደሰትነው ደስታ ----------!ያኔ እንደዛሬው ውስጥ አብርቶ ቋንቋን እንዲሁ መሞላት መቻልና በግዕዝ ልዑላችንን
እስከማምለክ የተደረሰበት ዘመን አልነበረም፡፡ እናም መፃህፍቱን አስረከበን፡፡ ሚስጥረ ሄኖክ ለጥያቄዎቻችን ሁሉ ምላሽ የሚሰጠንን
መንፈሳዊ ኣካለትን በስም ከመዘርዘር አልፎ ከፒራሚዳችን በላቲን ቋንቋ ተረቆ ከተሰጠን ቅድም ካያችሁት መፅሐፍ ጋር በማጣመር
ብቻ ያለማንም እገዛ በእኛ እውቀት ወደ ተግባር የምንለውጠው ጥበብ እስከ ማወቅ የደረሰ ሆነ፡፡

በእርግጥ ሄኖክ የበላይ አካሉ ተከታይ የሆነ እና ነ,ተነጥቆ ወደ ሰማይ የሄደ ነውና በመፅሐፉ የበላይ አካሉን እያሞገሰ እና የኛን ዘሮች እና
የልዑላችንን አላማ እያወገዘ ነበር የፃፈው፡፡ እኛ ግን በተቃራኒው በመፍታት ለወሳኝ ግብዓትነት ተጠቀምንበት፡፡

በሚስጥረ ሄኖክ ሁሉ በእጃችን ሁሉ በደጃችን ሲሆን የዘር ሀረጋችንን ከነሙሉ ታሪካችን በግልፅ አወቅንበት በጦርነቱ ስለተሰዉ
ዘሮቻችንም በጥልቀት ተረዳንበት፡፡ በራዕየ ሄኖክ እንዴት አድርገን ልኡላችንን በመጨረሻው ጦርነት እንደምናግዘው ተረዳን በራዕየ ሄኖክ
የበላይ አካሉ ልኡላችንን እንዴት አድርጎ በፍፃሜው ጦርነት ድል እንደሚነሳበት የተገለፀበትን ታሪክ መነሻ በማድረግ እንዴት መከላከል
እንዳለብንና እንዴት ልኡላችንን በእኛ እገዛ ለድል እንደምናበቃው ተገነዘብንበት፡፡ በትንቢተ ሄኖክ የበላይ አካሉ የመላዕክቱን ጭፍሮች
እንደሚያዘምት እና እንደሚያሰልፍ ተረድተን የራሳችንን አወቃቀርና አሰላለፍ እንዴት ማድረግ እንዳለብን ተገነዘብንበት፡፡

የሔኖክ መፅሐፍት ከኢትዮጵያ መጥተው እጃችን ከገቡ በኋላ በራሳችን መንገድ ተንትነን ጥቅም ላይ በማዋል ወደ አስደናቂ የሽግግር
ዘመን ተሻገርንባቸው የዘር ማንዘሮቻችንን ታሪክ መፅሐፉ እጃችን ሲገባ በስማቸው ሳይቀር ተዘርዝሮ ስናገኝማ በቤተ መንግስታችን
ታላቅ ፌሽታ ሆነ፡፡

ከኛ ጋር በመገናኘት የልኡላችን ትዕዛዝ የሚያሳውቁን የነበሩና በእኛ ለሚፈፀሙ ስራዎች ዝርዝር ትዕዛዝ ተቀብለው የሚያዙን
የልኡላችን ጭፍሮች ከዚህ ታሪካዊ መጽሐፍ ከመገኘት በኋላ የእነሱ በመልዕክተኝነት የማገልገል ቆይታ እንዳበቃና በቀጥታ ከዘሮቻችን
ጋር መገናኘት የምንችልበት መንገድ እንደተፈጠረ አወቅን፡፡ እኛም በቀጥታ ከዋና ዋና ከገዛ የዘር ሀረጎቻችን መናፍስት ጋር በነፃነት
እየተገናኘን የልኡላችንን ዓላማ የሚያሳካውን መንገድ ሁሉ በምንታዘዘው መሰረት በዘመናዊ መልኩ አዋቅረን ቀጠልንበት፡፡
በምንፈልገው ጉዳይ ላይ ማናቸውን ማዘዝና ማማከር እንዳለብን አውቀናልና ሁሉንም በስም እየጠራን የሚገባቸውን መስዋዕት
እያቀረብን ማዘዝ እና የተሰወረውን መግለጥ ገልጦም ወደ ተጨባጭ ነገሮች መለወጥ ማዘዝና የተሰወረውን መግለጥ ገልጦም ወደ
ተጨባጭ ነገሮች መለወጥ ቻልን፡፡ ከዚህ መፅሐፍ መገኘት በኋላ እየመነጠርን ያዘጋጀናትን ከተማ በቀደምት የዘሮቻችን መጠሪያ ስም
እየሰየምን በየኮከብና በምልክታቸው አርማ መሰረት የሕንፃዎች ግንባታ እያከናወንን ድንቅ አድርገን አሜሪካ የተባለችውን አገር
በመታሰቢያ ህንፃዎች አንቆጠቆጥናት ሰዎቻችንን አሰፈርን የጥበብ መፍለቂያ የሆነች የኛን የራሳችንም አገር ጨምረን በእንግሊዝ፣
በአሜሪካና በግዛታችን ካናዳ ሳይቀር ለዋና ዋናዎቹ የዘር ግንዶቻችን ሀውልት አቆምን ስልጣኔ ተቀጣጥሎ ቀጠለ፡፡ አዲስቷ የምድር
መንገስት ምስረታ በዘመናዊ መልክ ቀጥሎ ማንም ሕዝብ ዛሬም ድረስ ሳያውቀው ያማረና ቅርፅ የያዘ ሆኖ ታየ፡፡--------!አሉና እንደ
ህፃን ልጅ ፍልቅልቅ የሚል ገፅታ እያሳዩ በሳቅ እየተንከተከቱ መድረኩ ላይ እንደመዝለል አሉና ቀጠሉ፡፡

‹‹ አዎን! እያንዳንዱ የጥበብ ውጤት የቴክኖሎጂ ውጤት የሳይንስ ውጤት የምርምር ውጤት በልኡላችና በጭፍቹ የተገኙና በኛ
በባለተልዕኮቹ አማካኝነት ወደ ተግባር ተለውጠው ለውጤት የበቁና ለምደር ህዝብ እንዲደርሱ የሆኑ ናቸው! ይህ የዕውቀት ቀመር
በፒራሚዳችን እጅግ በተራቀቀ መንገድ በተግባር መተርጎም ከጀመረ ከ 7 ሺ ያህል አመታት ቢሆነውም ውጭ ያለውና ተጠቅልሎ
በልዑላችን ስራ መሆን እንዳለበት በታመነበት በኋላ ቀሩ የምድር ሕዝብ ዘንድ መታወቅና ወደ ተግባር እየተለወጠ ወደ ስልጣኔ ደረጃ
እንዲያደርሰው የተፈለገው ግን ቀስ በቀስ እና በዝግታ ነበር፡፡ እኛም ይሄን የእውቀት ቀመር ለአለም ሕዝብ ስናዳርስ ቀስ በቀስ እና
በዝግታ ነበር፡፡ እናም ከልዑላችንና ከተከታዮቹ ጎን ቆመን የእርሱን ረቂቅ ጥበብ እየተካፈልን ለአለም ህዝብ እያካፈልን እዚህ ደረስን
ሲሏቸው ተሰብሳቢዎቹ በጋራ ተነስተው አዳራሹን በጭብጨባ አደመቁት፡፡

ክብር ለልኡላችን ሲሊ አሜን አሉና ከልኡላቸውን አመስገነው ልቀጥል አሉና መሀል ላይ የነበረውን ግዙፍ ጥራዝ አንሸራተው ወስደው
ግድግዳ ላይ በመለጠፍ ግድግዳውን ሙሉ በሙሉ በሰፊው ስክሪን ለወጡት ከዛም እባካችሁ በየዘመናችሁ ተመራምራችሁ አለምን
መለወጥ የቻላችሁ የረቂቅ ግኝት ባለቤቶች የሖናችሁ በዘር ሀረግ ከኛ ወገን የሆናችሁና ያልሆነችሁ ነገር ግን በልዑላችን ምክንያት በዘር
ሀረግ ከማንም ጋር ሳትበላለጡ በእኩልነት ቤተሰብ መሆን የቻላችሁ የልዑላችን ታማኝ ልጆች የሆናችሁ አብረቅራቂውን ስጋ ለብሳችሁ
ያላችሁ ከልዕላችን ድል በኋላ የምንገናኝና እንደሌሎች ሹማምንት የምትሆኑ ሊቃውንቶች እና ሳይንቲስቶቻችን አንድ አፍታ ጎራ በሉና
ለተሰብሳቢዎች ታይታችሁ የምንለውን ነገር አጠናክራችሁ በዚያውም ወንድማዊ ሰላምታችሁን አቅርቡላቸው ካሉ በኋላ ፈገግ አሉና
ከሰፊው ስክሪን ዳር ላይ ሆነው እጆቻቸውን አጣምረው ቆመው መጠበቅ ጀመሩ ያይታመን ክስተት ነበር! ነገሩ ብታምኑ እመኑ
ባታምኑም ተውት! የሚባል አይነት ነው፡፡ እኒህ የሰይጣን ቁራጭ የሆኑ ጎባጣ አሮጊት የእንጊልዝ ንግሰት ይህን ብለው ጥጋቸውን
እንደያዙ የእንግሊዝ እና የአሜሪካን ዜግነት የነበራቸው የቀድሞ የግኝት ባለቤቶች ጥቁር በጥቁር ለብሰው ጥቁር ቦቲ ጫማ ተጫምተው
ግር ብለው እየተጋፊ በሰፊው ስክሪን ውስጥ መታየት ጀመሩ፡፡ ግፊያው መበተርታቱን የተመለከቱት ንግስቲቱ ጥቂቶች ትበቃላቹ

8
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

ወንድሞች እባካችሁ አሉ ሊሰሟቸው አልፈለጉም ግፊያቸው ጠነከረ ትርምሱ በረታ በዚህ ጊዜ ንግስቲቱ ጠንከር አሉና በየተራ
እምጠራችሁ እና ለምናወራው ነገር ማጠናከሪያነት የፈለግናችሁ ብቻ ትመጣላችሁ አሉና ቶማስ ቅደም ቀጥሎ አሌክሳንደር ከዛ
አንስታይን ብለው ወደ ጥጉ ሄደው ቆሙ፡፡

መመሪያ 1፡- ለሚከተሉት ጥያቄዎች ትክክለኛ መልስ ስጡ


1. ከአንደበት አካላት መካከል የሚንቀሳቀሱ የአንደበት አካላት የሚባሉትን ጥቀሱ ---------------፣---------------፣------------
2. የአማርኛ ቋንቋ ከውጭ የተዋሳቸው ተነባቢ ድምፆች ብዛት ስንት ነው እነማናቸው --------------------------------
3. አማርኛ ከኩሽ ቋንቋዎች የወሰዳቸው ድምፆች መካነ ፍጥረታቸው ምን ላይ ነው---------------------------
4. አማርኛ ስንት ፈንጂ ድምፆች አሉት -----------------------
5. በንበት እና በፅፈት ወቅት የሚፈጠር የድምፅ ልዩነት ምን ተብሎ ይጠራል-------------------------------
6. አማርኛ ስንት ከፊል አናባቢ ድምፆች አሉት----------------
7. ከአማርኛ የድምፆች አይነቶች መካከል ሙሉ በሙሉ ነዛሪ የሆነው ድምፅ ማነው---------------------------
8. ተነባቢ ድምፆች የሚፈጠሩበት ቦታ ምን ተብሎ ይጠራል-------------------
9. አማርኛ ስንት ኢ.ነዛሪ ድምፆች አሉት----------------------

7. ዘመናዊ የአማርኛ ቋንቋ የንግግር ክፍሎች


1.ስም 2.ግስ
3. ቅፅል 4. ተውሳከ ግስ
5. መስተዋድድ 6. መስተዓምር
1. ስም
 በዓ.ነገር ውስጥ ባለቤት እና ተሳቢ በመሆን ያገለግላል፡፡
 /-ኦች/ የሚል አብዢ ምዕላድን ይወስዳል
 ቅፅል ቀድሞት ይገባል
የስም አይነቶች
ሀ. የገሀድ ስም፡- በአይን የሚታይ በእጅ የሚነካ እና የሚቆጠሩ ሲሆን /-ኦች/ የሚል አብዢ ምዕላዶችን ይወስዳል፡፡
ለ. የረቂቅ ስም፡ በአይን የማይታይ/የማይታይ/ በእጅ የሚነካ/የማይነካ/ እና የማይቆጠሩ ሲሆን /-ኦች/ የሚል አብዢ ምዕላዶችን
አይወስዱም፡፡
ሐ. የጥቅል ስም፡- የተለያዩ አንድ አይነት የሆኑ ስሞች በአንድ ላይ ተጠቅልለው የሚጠሩበት ስም ሲሆን አብዢ ምዕላድ አይወስዱም
ምክንያቱም መጠሪያው ስም ብዙ ነገሮቸን በአንድ ላይ ስለያዘ፡፡
መ. የወል ስም፡- ሁለት የተለያየ ፆታ ያላቸው ነገሮች በጋራ የሚጠሩበት ስም ሲሆን አብዢ ምዕላድ ይወስዳሉ
ሠ. የተፀውኦ ስም፡- የቦታ ፣የሰው፣የወንዝ፣የሀይቆች መጠሪያ ሲሆን አብዢ ምዕላድ አይወስድም፡፡

ተ.ቁ የገሀድ ስም የረቂቅ ስም የጥቅል ስም የወል ስም የተፀውኦ ስም


1 ሰው ጨለማ ወፍ በግ አለሙ
2 ወንበር ሰውነት ዓሳ ውሻ አባይ
3 መፅሐፍ ልጅነት መንጋ ዶሮ አ.አ
4 እስራስ ሞት አራዊት ፍየል ዝዋይ
5 ደብተር ብርሀን ሰራዊት አህያ ጣና
6 ሳሙና ቅብጠት ጫካ ሰው ሰለሞን

9
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

7 ሶፋ ውፍረት ምግብ መ/ር ጃፓን


8 ስልክ ሰላም አህል ደ/ር ኢራን

መልመጃ 2

መመሪያ 1 የሚከተሉትን ቃላቶች በየስም አይነቶች መድቧቸው

ሞት፣ ዕውቀት፣ ላም፣ ጀግንነት፣ ክፋት፣ ደብተር ፣መኪና፣ ተራራ ፣ፍሬ፣ ላም፣ አልጋ፣ ግመል፣ አንበሳ፣
ጅብ፣አዋሽ ድሬደዋ፣ጎንደር፣ካሳ፣መንጋ፣ዶሮ፣ሰላም፣ላፕቶፕ፣ራዲዮን፣ሳህን፣ብርጭቆ፣ማር፣ዘይት፣ስኳር
እስራስ፣መሶብ፣ፍራፍሬ፣ብርሀን፣ደብተር

የወል የገሀድ የረቂቅ የጥቅል የተፀውኦ

1. -------------------------- --------------------- -------------------- ------------------------- -----------------------

2. -------------------------- --------------------- -------------------- ------------------------- -----------------------

3. -------------------------- --------------------- -------------------- ------------------------- -----------------------

4. -------------------------- --------------------- -------------------- ------------------------- -----------------------

5. -------------------------- --------------------- -------------------- ------------------------- -----------------------

6. -------------------------- --------------------- -------------------- ------------------------- -----------------------

7. -------------------------- --------------------- -------------------- ------------------------- -----------------------

8. -------------------------- --------------------- -------------------- ------------------------- -----------------------

9. -------------------------- --------------------- -------------------- ------------------------- -----------------------

10. -------------------------- --------------------- -------------------- ------------------------- -----------------------

8. ምንባብ ሁለት
አንዳንዴ ሀገር አርብ ላይ ትውላለች

አርብ አዳም እየዳነ ነው፤ ነገር ግን ክርስቶስ እየተገረፈ እና እየተሰቀለ ነው፤ ፀሐይ ጨልማለች ጨረቃ ደም ለብሳለች፤ ምድር
ትንቀጠቀጣለች፤ ሐዋሪያት ሸሽተዋል ፤ መፃጉ በሀሰት መስክሯል፤ ጲላጦስ የእውነት ፍርድ ለመፍረድ ተቸግሯል፡፡

በጥብሪያዶስ ባህር ሲበላ ‹ካልነገስክ› ያለው ሕዝብ ተገልብጦ ‹ካልተሰቀለ› እያለ ነው፡፡ ያቺ ቀን የክርስትና የመጨረሻዋ ቀን ትመስል
ነበር፡፡ የክርስቶስ ሆኖ የተገኘ ሁሉ ይቀጠቀጣል፡፡ ለዚህም ነበር ወጣቱን ማርቆስ ያባረሩት፡፡ ሀና እና ቀያፋ ጉልበት አግኝተል፡፡
የጭካኔያቸውን ልክ ሁሉ እያወረዱት ነው፡፡ ዮሐንስ ያለቅሳል፤ እመቤታችን በሐዘን ቆማለች፡፡ ሁሉም ነገር ያበቃና የተቆረጠ መስሏል፡፡

በዚህ መከከል ግን የሚነሱ ሙታን ነበሩ፤ የሚቀደድ የጥል መጋረጃ ነበር፤ ፈያታዊው ዜይማን ገነት እየገባ ነበር፤ የጲላጦስ ሚስት ስለ
እውነቱ እየመሰከረች ነበር፡፡ ሮማዊው መቶ አለቃ ስለ ክርስቶስ እውነቱን እየተናገረ ነበር፡፡ ግን እነዚህን ጣፋጭ ድምፆች ሌሎች የክፋት
እና የጨለማ ድምፆች ውጦዋቸው ስለነበር በቂ ሰሚ አላገኙም፡፡ በቂ ሰሚ ያገኙት በኋላ ነው፡፡ሀገርም እንዲህ ትሆናለች ፡፡ አርብ ላይ

10
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

ስትሆን ፀሐይ የጨለመባት ጨረቃም ደም የለበሰችባት ትመስላለች፡፡ መድሐኒት አልባ ተስፋ የማታገኝ ሁሉም እንደጨለመ የማይነጋ
ህልም እንጂ እውን የሚባል ነገር የሚታይባት አትመስልም፡፡

ክፎዎች ሀይል አግኝተው ቅኖች የተሸነፉ ይመስላሉ፤ ወንጀለኞች ደስታ ተጎናፅፈው ንፁሐን መስቀል ስር ያለቅሳሉ፡፡ ትናንሽ
ጭላንጭሎች ደስታ ተጎናፅፈው ንፁሐን መስቀል ሥር ያለቅሳሉ፡፡ ትናንሽ ጭላንጭሎችን የሚያያቸው ጥቃቅን ብርቱ ድምፆችን
የሚሰማቸው ያጣሉ፡፡ ሁሉም የዋጠውን ጨለማ እንጂ የተሰቀለውን ብርሀን አያያም፡፡

ግን አርብ ያልፋል ፤ ቅዳሜ ይነጋል፤ እርሱም በዝምታ ይመሻል፤ እሁድም ይደርሳል፤ ትንሳኤም ይመጣል፤ አረብም በእሁድ ትተካለች፡፡
ከአርብ ወደ እሁድ ለመሻገር ግን እንደ እመቤታቸን እና ዮሐንስ ያሉ ፅኑአንን ይፈልጋል፡፡ ዛሬ ኢትዮጵያ አርብ ላይ ናት ግን በቅዳሜ በኩል
ተሻግራው እሁድ እንደምትደርስ እናምናለን፡፡

ምንጭ ፡- ዲ/ን ዳንኤል ክብረት

መመሪያ አንድ፡- ከላይ በቀረበው ምንባብ መሰረት ለሚከተሉት ጥያቄዎች ትክክለኛ መልስ የያዘውን ፈደል ምረጡ /የእውቀት ጥያቄዎች/

1. ትናንሽ ጭላንጭሎች ደስታ ተጎናፅፈው ንፁሐን መስቀል ሥር ያለቅሳሉ፡፡ ይሄንን ሀሳብ ሊተካ የሚችለው ሀሳብ የትኛው ነው
ሀ. የተፃፈውን ሁሉ አንብብ በሕሊና መዝገብ ከመመዝገብህ በፊት በህሊና ሚዛና አብጠርጥር
ለ. መስጠት እማያውቁ ሰዎች ሌሎች ሲሰጡ ይታመማሉ
ሐ. የእብደት የመጀመሪያው ምልክት እራስን አዋቂ አድርጎ ማሰብ ነው
መ. መሆን ያለበት ሳይሆን መሆን የሌለበት ሆነ
2. እመቤታችን እና ዮሐንስ በምንባቡ ውስጥ ምን አይነት ሰዎች ናቸው
ሀ. የወደዱት የሚወዱ ለ. የጠላቸውን የሚወዱ
ሐ. የሚያፈቅሩትን የሚወዱ መ. ወደ ፍፅምና የተጠጋ ፍቅር ያለቸው
3. ከአርብ ወደ እሁድ ለመሻገር ግን እንደ እመቤታቸን እና ዮሐንስ ያሉ ይፈልጋል፡፡ ሲል ምን ማለቱ ነው
ሀ. ከሚታየው እውነታ ጀርባ ያለውን እውነታ የሚያይ
ለ. ከእውነታው ጀርባ ያለው ውሸትን ቀድሞ የሚያውቅ
ሐ. የሚታየውን እውነታ በተሻለ እውነታ የሚቀይር መ. መልስ የለም
4. በምንባቡ ውስጥ አርብ ምን አይነት ቀን ናት
ሀ. ክፉዎች የበለጠ የሚከፉበት ለ. እውነት የሚገለጥበት ሐ. ድሕነት ያለበት መ. ሁሉም
5. ከአርብ እና እሁድ የተሻለው ቀን የትኛው ነው
ሀ. አርብ ለ. እሁድ ሐ. ከጣት መካከል የሚሻለውን መምረጥ ይከብዳል መ. መ.የለም
6. እንደ ምንባቡ ሀሳብ የጥል መጋረጃ ሲል ምን ማለት ነው
ሀ. ፍቅር የበዛበት ለ. ፀብ የሌለበት ሐ. የኖረ ፀብ መ. ሀ እና ለ
7. ዛሬ ኢትዮጵያ አርብ ላይ ናት ሲል ምን ማለቱ ነው
ሀ. ችግር፣ሀዘን እና ሰቆቃ ብቻ የበዛባት ለ. በችግር እና በመከራ ውስጥ ተስፋ የሚታይበት
ሐ. የማያልፍ የሚመስሉ የሀዘን ጎርፍ ብቻ የሚታይባት መ. ሀ እና ሐ
8. በምንባቡ ውስጥ ቅኔ የሆነው ቀን የትኛው ነው
ሀ. ቅዳሜ ለ. እሁድ ሐ. አርብ መ. ቅዳሜ እና እሁድ
9. እንደ ምንባቡ ሀሳብ ቅዳሜ ምን አይነት ቀን ነው
ሀ. አሸናፊዎች የተሸነፉበት ለ. ፀጥታ የነገሰበት ሐ. የደስታ ጎርፍ የዘነበበት መ. ግርግር የበዛበት
10. ድህነት ያለ የማይመስል ነገር ግን ድህነቶች የሚበዙበት ዕለት የትኛው ነው
ሀ. ቅዳሜ ለ. እሁድ ሐ. አርብ መ. ቅዳሜ እና እሁድ

11
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

መመሪያ ሁለት፡- ለሚከተሉት ሰዋሰዋዊ ጥያቄዎች ትክክለኛ መልስ የያዘውን ፊደል ምረጡ/የዕውቀት ጥያቄዎ
11. ከሚከተሉት መካከል አንዱ ለምስረታ ቃል ምሳሌ አይሆንም
ሀ. ብልግና ለ. ሰውነት ሐ.ጉልበተኛ መ. ወታደሩን
12. ከሚከተሉት የቃል ክፍሎች መካከል ቅፅል ቀድሞት የሚገባው የቃል ክፍል የትኛው ነው
ሀ. መሰተዋድድ ለ. ግስ ሐ. ስም መ. መስተዓምር
13. ለቁጥር፣ለፆታ፣ለሙያ እና ለእምርነት የሚረባው የቃል ክፍል የትኛው ነው
ሀ. ተውሳከ ግስ ለ. ግስ ሐ. ስም መ. መስተዓምር
14. ቅፅሎች ለእምርነት ሲረቡ ተባዕት ፆታ እንዲኖራቸው የሚያደርገው ምዕላድ
ሀ. -ኡ ለ. -ኢት ሐ. ተባዕት ፆታ አይወስዱም መ. -ዋ
15. ምንም አይነት ቅጥያ ሳይጨመርበት ከግሱ እግሮች ውስጥ /ኧ/ን የሚጨምር የግስ አምድ የቱ ነው
ሀ. ተደራጊ አምድ ለ. አድራጊ አምድ ሐ. አስደራጊ አምድ መ. አዳራጊ አምድ
16. አድራጊ አምድ ላይ/ተ-/ የሚል ምዕላድ ሲጨመርበት የሚሆነው አምድ --------------- ነው
ሀ. ተደራጊ አምድ ለ. አድራጊ አምድ ሐ. አስደራጊ አምድ መ. አዳራጊ አምድ
17. ለመደብ፣ለፆታ፣ለቁጥር እና ለጊዜ የሚረባው የቃል ክፍል የትኛው ነው
ሀ. ተውሳከ ግስ ለ. ግስ ሐ. ስም መ. ቅፅል
18. ከጊዜ፣ ከቦታ፣ ከሁኔታ እና ከቁጥር አንፃር የሚጎላመሰው የቃል ክፍል የቱ ነው
ሀ. ተውሳከ ግስ ለ. ግስ ሐ. ስም መ. ቅፅል
19. ከሚከተሉት ድህረ ግንድ ቅጥያ የሆነው የትኛው ነው
ሀ. እንደ ለ. ኣችን ሐ. አስ መ. የ
20. ከሚከተሉት ቁጥር አመልካች ምዕላድ ያልሆነው የትኛው ነው
ሀ. እነ- ለ. -ኣን ሐ. -ኣት መ. -ነት
21. ከሚከተሉት ምዕላዶች መካከል ከቅፅል ጋር ሲገባ የምስረታ ከስም ጋር ሲገባ ደግሞ የእርባታ ምዕላደ የሚሆነው የትኛው ነው
ሀ. -አዊ ለ. -አማ ሐ. -አም መ. -ነት
22. ከሚከተሉት ለስማዊ ሀረግ አጎላማሽ መሆን የሚችለው ሀረግ የትኛው ነው
ሀ. ግሳዊ ሀረግ ለ. ዓ.ነገር ሐ. መስተዋድዳዊ ሀረግ መ. ተ.ግሳዊ ሀረግ
23. ለቅፅላዊ ሀረግ አጎላማሽ መሆን የሚችለው ሀረግ የትኛው ነው
ሀ. ግሳዊ ሀረግ ለ. መስተዋድዳዊ ሀረግ ሐ. ስማዊ ሀረግ መ. ቅፅላዊ ሀረግ
24. አንድ አ.ነገር ከመቋጨታችን በፊት የሚዘረዘሩ ነገሮች መኖራቸውን ለመግለፅ የሚጠቅመው ሥርዓተ ነጥብ የትኛው ነው
ሀ. ነጠብጣብ ለ. ድርብ ሰረዝ ሐ. ሁለት ነጥብ ከሰረዝ መ. ነጠላ ሰረዝ
25. ከሚከተሉት አንዱ ቃላትን አሳጥሮ ለመፃፍ የሚያገለግል ሥርዓተ ነጥብ የትኛው ነው
ሀ. እመጫት ለ. እዝባር ሐ. አግድም ሰረዝ መ. ትምህርተ አንክሮ
መመሪያ ሶስት፡- ለሚከተሉት ሥነፅሑፋዊ ጥያቄዎች ትክክለኛ መልስ የያዘውን ፊደል ምረጡ
26. ከግሪክ ቋንቋ የተገኘ ሲሆን ትዕይንቱን ብቻ ሳይሆን ትዕይንቱ የሚከወንበትን ሕንፃ ጭምር የሚወክለው ቃል የትኛው ነው
ሀ. ድራማ ለ. ተውኔት ሐ. ቲያትር መ. ፊልም
27. ከሚከተሉት የሥነፅሁፍ ዘውጎች መካከል ገፀባህሪያቱ ምናባዊ ያልሆኑት በየትኛው ላይ ነው
ሀ. በመፅሐፍ ላይ ለ. በፊልም ላይ ሐ. በተውኔት ላይ መ. ሀ እና ለ
28. በሁካታ እና በሳቅ የተሞላ ሆኖ ብዙም ጥያቄ የማይነሳበት ዋናው የተነሳው ሀሳብ ያስቃል ወይስ አያስቅም የሚለው ብቻ
የሚታይበት የተውኔት አይነት የትኛው ነው
ሀ. ትራጀዲ ለ. ኮሜዲ ሐ. ድንቃይ መ. ቧልታይ
29. ከጠቀሜታ ቅርርቦሽ አንፃር አንዱን በሌላ የምንወክልበት የዘይቤ አይነት -------------- ነው

12
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

ሀ. ንቡር ጠቃሽ ለ. በስመሀዳሪ ሐ. እንቶኔ ዘይቤ መ. ተምሳሌት ዘይቤ


30. በአንድ አንቀፅ ውስጥ የሚቀርቡ ሀሳቦች በሙሉ በአንድ ጉዳይ ላይ ብቻ የሚያተኩሩ ከሆነ የትኛውን የአንቀፅ ባህሪያትን አሟልቷል
ማለት እንችላለን
ሀ. ግጥምጥምነት ለ. ብቁነት ሐ. አንድነት መ. በይለቃል
31. የአንድን ነገር አሰራር ቅደም ተከተል የሚገልፅ የድርሰት አይነት የትኛው ነው
ሀ. ተራኪ ድርሰት ለ. ሥዕላዊ ድርሰት ሐ. ገላጭ ድርሰት መ. አመዛዛኝ ድርሰት
32. ምክንያቱ እና ውጤቱ ጥብቅ ያልሆነበት እንዲሁም ተደራሲያንን የማያሳም የሴራ አይነቶች አይነት የትኛው ነው
ሀ. ጥብቅ ሴራ ለ. ልቅ ሴራ ሐ. ነጠላሴራ መ. መልስ የለም
33.-------------የገቢር ክፍል ሆኖ የመድረክ እነፃውን፣የተዋንያንን አልባሳት፣የመድረኩን ገፅታ ይመለከታል
ሀ. ቃለ ተውኔት ለ. ገፀባህሪያት ሐ. ትዕይንት መ. ሙዚቃ
34. ከሚከተሉት መካከል የሥነቃል ተግባራት ያልሆነው የቱ ነው
ሀ. ማዝናናት ለ. የወል ሀብት ሐ. ማስተማር መ. የቁጥጥር
35. ከሚከተሉት ሥነፅሑፎች መካከል ፅሁፋዊ ሥነፅሑፍ ያልሆነው የቱ ነው
ሀ. ሥነቃል ለ. ልቦለድ ሐ. ተውኔት መ. ኢ-ልቦለድ

9.የስም እርባታ
 ስሞች፡-
 ለቁጥር
 ለፆታ
 ለሙያ/ተሳቢ/
 ለእምርነት ይረባል፡

ሀ. ስሞች ለቁጥር ሲረቡ

 የአማርኛ ቃላቶች /-ኦች/ የሚል አብዢ ምዕላዶችን ሲወስዱ የግዕዝ ቃላቶች ደግሞ /-ኣን እና ኣት/ ይወስዳሉ፡፡
ምሳሌ ቃላት አብዢ ምዕላድ ቃላቶች
አያት -ኦች አያቶች

ፍየል -ኦች ፍየሎች

በሬ -ዎች በሬዎች
ምዕመን -ኣን ምዕመናን
ገዳም -ኣት ገዳማት
ለ. ስሞች ለፆታ ሲረቡ
ምሳሌ
ተባዕት ምዕላድ አንስታይን
1. ልጅ -ኢት ልጅት
2. ድመት -ኡኣ ድመቷ
3. በሬ ላም
4. ድንጉላ ባዝራ
5. ወይፈን ጊደር
 ከ ምሳሌ 3 እስከ 5 ያሉ ቃላቶች ምንም አይነት ምዕላዶች ሳይጨመርባቸው ፆታን ያመለክታሉ፡፡
ሐ. ስሞች ለተሳቢ ሲረቡ
 ተሳቢ አመልካች ምዕላድ /-ን/ ናት
ምሳሌ 1.
ስም ተሳቢ አመልካች ምዕላድ ስሙ ተሳቢ ከወሰደ በኋላ
1. ብንያም -ን ብንያምን
ምሳሌ 2
አበበ ብንያምን መታው፡- የተሰመረበት ቃል ስም ሆኖ ለተሳቢ ስለረባ ድርጊት ተቀባይ ሆኖ ይታያል፡፡
መ. ስሞች ለዕምርነት ሲረቡ
 አንድን ስምየታወቀ እንዲሆን ማድረግ ማለት ነው እምር አድራጊ ምዕላድ/-ኡ/ ናት

13
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

ስም ምእላድ እምር
ምሳሌ በግ -ኡ በጉ
2. ቅፅል
 ከስም በፊት ወይም በኋላ በመግባት ስምን ይገልፃል

10.የቅፅል አይነቶች
ተ.ቁ የባህሪ የመጠን ቅርፅ ቀለም ወገን

1 ባህሪ ትንሽ ክብ ቀይ ጃፓን

2 ጥሩ ትልቅ ሞላላ ጥቁር ጎጃሜ

3 ደግ ብዙ ወልጋዳ ነጭ ጎንደሬ

4 ክፉ አያሌ ጠማማ ቢጫ

5 መጥፎ ጥቂት ቆልማማ ግራጫ

የቅፅል እርባታ
 ቅፅሎች ለቁጥር ለሙያ ለእምርነት እና ለሙያ ይረባሉ
ቅፅሎች ለቁጥር ሲረቡ
 ቅፅሎች ለቁጥር በሁለት አይነት መንገድ ይረባሉ
1. /-ኦች/ በመውሰድ የሚረቡ
ምሳሌ ነጠላ ምዕላድ ብዙ
1. ጅል -ኦች ጅሎች
2. ጠባብ -ኦች ጠባቦች
3. ጎበዝ -ኦች ጎበዞች
2. ተናባቢ እግር በመድገም የሚረቡ
ምሳሌ ነጠላ ምዕላድ ብዙ
1. ረዥም -ኣ ረዣዥም
2. ሰፊ -ኣ ሰፋፊ
3. ቀይ -ኣ ቀያይ
ቅፅሎች ለፆታ ሲረቡ
 ቅፅሎች -ኢት እና -ኡኣ የሚሉ ምዕላዶችን በመውሰድ እራሳቸውን ለፆታ ያረባሉ፡፡
ምሳሌ ተባዕታይ ምዕላድ አንስታይ
1. ትልቅ -ኢት ትልቂት
2. ትንሽ -ኡኣ ትንሷ
3. ደግ -ኢት ደጊት

ቅፅሎች ለእምርነት ሲረቡ


 ቅፅሎች ለእምርነት ሲረቡ ተባዕታ ፆታ ያላቸው /-ኡ/ ሲወስዱ አንስታይን ፆታ ደግሞ /-ኢት/ ወይም /-ዋ/ ይወስዳሉ፡፡
ምሳሌ ቅፅል ተባዕታይ አንስታይ
1. ትልቅ ትልቅ -ኡ ትልቅ -ኢት
2. አዲስ አዲስ -ኡ አዲስ -ኢት
3. ሰነፍ ሰነፍ-ኡ ሰነፍ- ዋ
ቅፅሎች ለሙያ ሲረቡ
ቅፅል ምዕላድ ከረባ በኋላ
ምሳሌ አሮጌ -ን አሮጌውን
አዲሱ -ን አዲሱን

14
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

11.ግስ
 በዓ.ነገር መጨረሻ ላይ የሚገኝ እና ባለቤት አመልካች ምዕላድ ያስከትላል፡፡
ምሳሌ 1. እሱ አንበሳ ገደል -ኧ
2. አንቺ በግ ገዛ -ሽ
3. እሷ ምሳዋን በላ -ች
4. እኔ ወተት ጠጣ -ሁ
5. አንተ ዛሬ ትመጣለ -ህ
የግስ አምድ
ሀ. አድራጊ አምድ፡-
ምንም አይነት ቅጥያ ሳይጨመርበት ከግሱ እግሮች ውስጥ/ኧ/ን በመጨመር ነው፡፡ አምዶቹም የተፈፀመ ድርጊትን የሚጠቀሙ
በመሆናቸው ሀላፊ አምዶች ናቸው፡፡
ምሳሌ ስር አድራጊ አምድ
ነገር ንኧግኧርኧ
ለወጠ ልኧውኧጥኧ

ለ. ተደራጊ አምድ፡-
 አድራጊ አምድ ላይ /ተ-/ የሚል ምዕላድ በመጨመር የሚፈጠር ነው፡፡
ምሳሌ አድራጊ ተደራጊ
1. ሰበረ ተ-ሰበረ
2. ገደለ ተ-ገደለ
3. ወደደ ተ- ወደደ
ሐ. አስደራጊ አምድ፡-
 በአድራጊ አምድ ላይ /አስ-/ የሚል ምዕላድ በመጨመር የሚፈጠር አምድ ነው፡፡
ምሳሌ አድራጊ አምድ አስደራጊ አምድ
1. ገደለ አስ-ገደለ
2. ለመነ አስ-ለመነ
3. ተከለ አስ-ተከለ
መ.አዳራጊ አምድ፡-
 አድራጊ አምድን ወደ ማገዝ፣መርዳት ተግባር መቀየር ማለት ነው፡፡
ምሳሌ አምድ አዳራጊ አምድ
ፈለገ አፋለገ
ለመደ አላመደ
ለመነ አላመነ
የግስ እርባታ
 ግሶች
 ለመደብ
 ለፆታ
 ለቁጥር
 ለጊዜ ይረባሉ፡፡

ቁጥር ግስ ጊዜ
መደብ ነጠላ ብዙ የአሁን ሀላፊ ትንቢት
1ኛ ፆታ እኔ በላ እየ-በላሁ በላሁ እበላለሁ
2ኛ ተባ አንተ በላ እየ-በላ-ህ በላ-ህ ት-በላለ-ህ
አን እንቺ በላ እየ-በላ-ሽ በላ-ሽ ት-በላለ-ሽ
3ኛ ተባ እሱ በላ እየ-በላ- በላ ይ-በላል
አን እሷ በላ እየ-በላ-ች በላ-ሽ ት-በላለ-ች
እኛ በላ እየ-በላ-ን በላ-ን እን-በላለ-ን
እናንተ በላ እየ-በላ-ችው በል-ኣችው ት-በላል-ኣቸው
እነሱ በላ እየ - በል-ኡ በል-ኣችው ይ-በል-ኣሉ

መልመጃ ሶስት

15
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

መመሪያ አንድ፡- ለሚከተሉት ጥያቄዎች ትክከለኛ መልስ ስጡ


1. ሰሞች ለምን ለምን ይረባል
ሀ. ------------------ ለ.---------------------
ሐ. ------------------ መ. -------------------
2. ቅፅሎች ለምን ለምን ይረባል
ሀ. ------------------ ለ.---------------------
ሐ. ------------------ መ. -------------------
3. ግሶች ለምን ለምን ይረባል
ሀ. ------------------ ለ.---------------------
ሐ. ------------------ መ. -------------------
4. ስድስት የገሀድ ስም ፃፉ
ሀ. ------------------ ለ.---------------------
ሐ. ------------------ መ. -------------------
ሠ.-------------------- ረ.----------------------
5. ስድስት የወል ስም ፃፉ
ሀ. ------------------ ለ.---------------------
ሐ. ------------------ መ. -------------------
ሠ.-------------------- ረ.----------------------
6. ስድስት ቅፅሎችን ፃፉ
ሀ. ------------------ ለ.---------------------
ሐ. ------------------ መ. -------------------
ሠ.-------------------- ረ.----------------------

መመሪያ ሁለት፡- ለሚከተሉት ጥያቄዎች ትክክል ከሆኑ እውነት ትክክል ካልሆኑ ሀሰት በማለት መልሱ
1. በዓ.ነገር ውስጥ ቅፆሎች የግስ ገላጭ በመሆን ያገለግላሉ-----------------
2. የተፀውኦ ስም -ኦች የሚለውን ምዕላድ ይወስዳል-------------------
3. አስደራጊ አምድ የሚመሰረተው ተደራጊ አምድ ላይ /-አስ/ የሚል ምዕላድን በመጨመር ነው፡፡-------------------
4. አስቴር ሽንኩርት አስተከለች፡፡ ይሄ ዓ.ነገር በተደራጊ አምድ የተመሰረተ ነው------------------
5. ስም በዓ.ነገር ውሰጥ ባለቤት እና ተሳቢ በመሆን ያገለግላል--------------
6. /-ን/ የሚለው ምዕላድ ተሳቢ አመልካች ምዕላድ ነው፡፡-------------------
7. የወል ስም እና የጥቅል ስም አንድ አይነቶች ናቸው፡፡--------------------
8. የስም ገላጭ ሁሉ ቅፅል መሆን ይችላሉ፡፡------------------------
መመሪያ ሶስት፡- የሚከተሉት ጥያቄዎች ከ ሀ ክፍል ወደ ለ ክፍል አዛምዱ
ሀ ለ
---------1. ጊደር ሀ. ስም
---------2. ወይፈን ለ. ቅፅል
---------3. ጎንደሬ ሐ. ግስ
---------4. ለመነ
---------5. ፎቅ
---------6. ቀይ
---------7. መምህር
---------8. አለ
---------9. ክፉ
---------10. ወልጋዳ
---------11. አልጋ
---------13. ነው
---------14. በግ

12. ተውሳከ ግስ
 ተውሳከ ማለት በግዕዝ ጭማሪ ማለት ሲሆን ተውሳከ ግስ በግስ ላይ የሚጨመር ማለት ነው፡፡
 ተውሳከ ግስ ከግሱ በፊት በመግባት ግሱን የሚገልፅ ነው፡፡
 የተውሳከ ግስ ሌላይኛው መጠሪያ የግስ ገላጭ ነው
 በአማርኛ ቋንቋ ውስጥ ተውሳከ ግስ ብዛታቸወ እጅግ በጣም ትንሽ ነው
 በተፈጥሮ ተውሳከ ግስ ሆኑ ቃላት ጅልኛ ፣ክፉኛ፣ምንኛ፣ቶሎ ፣ገና እና ግመኛ ናቸው፡፡
 ተውሳከ ግሶችን ከጊዜ፣ከቦታ፣ከሁኔታ እና ከቁጥር አንፃር ያጎላምሳለ
ምስሌ

16
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

ተ.ቁ ተ.ግስ

ከጊዜ ከቦታ ከሁኔታ ከቁጥር

1 ትናንት ጎጃም ድንገት እንደገና

2 ዛሬ ራስጌ ክፉኛ ደጋግሜ

3 ነገ ጎንደር እንዴት ስንቴ

4 ዘውትር መርካቶ

5 ቶሎ ግርጌ

ምሳሌ 1. ካሳ ዛሬ ይመጣል፡፡
2. ሰለሞን እባክፍ ከራስጌዬ አትቁም፡፡
3. ካሳ በድንገት ወደ ጎጃም ሄደ፡፡
4.ሰለሞን አራተኛ ክፍልን ስንቴ ወደቀ፡፡
5. መስተዋድድ፡-
 የሚያዋድድ ወይም የሚያስማማ ማለት ሲሆን ቃላትን ከቃላት የሚያስማማ ማለት ነው፡፡
ምሰሌ፡- እንደ፣ አስ፣ ስለ፣ ወደ፣ በ፣ ከ፣ለ ፣እስከ ፣ወደ ፣ውስጥ፣ባሻገር ወዘ.ተ

ምሳሌ፡- 1. እንደ አባቱ ሰው አክባሪ እስከ ቤቴ ድረስ ሸኘኝ ወደ ጅማ ሄደ

13. መስተዓምር፡-
 መጣኝ
 ኢመጣኝ
 አገናዛቢ እና
 ጠቋሚ መስተዓምር ተብለው የሚከፈሉ ሲሆን ስምን እና ቅፅሎችን ያጎላምሳሉ
ምሳሌ

ተ.ቁ መጣኝ ኢ.መጣኝ አገናዛቢ ጠቋሚ

1 አንድ ብዙ የ ካሳ እነዚህ

2 ሁለት አያሌ የ ብንያም እነዚያ

3 አስር መዓት ያ

4 ስምንት ጥቂት ይህ

5 መቶ ትንሽ

6 ሁለት መቶ ነፍ

7 አንድ ሺህ

ምሳሌ 1 እነዚያ የከሳ አስር በጎች ትናትና ታረዱ፡፡


2. ብንያም ብዙ ደብተሮችን ገዛ፡፡
 በምሳሌ 1 እና 2 ላይ የተሰመረባቸው ቃላቶች መስተዓምር ናቸው፡፡

14. ምዕላድ
 ሊሸነሸን የማይችል የቋንቋ የመጨረሻ ቅንጣት አካል ነው
 ምዕላድ ትርጉም ሊኖረውም ላይኖረውም ይችላል፡፡
 ምዕላድ በሁለት ይከፈላል እነሱም፡- ነፃ ምዕላደ እና ጥገኛ ምዕላድ ይባላሉ፡፡

ነፃ ምዕላድ፡- ትርጉም የሚሰጥ ሲሆን ማንኛውም ቃል ምዕላደ ናቸው፡፡

17
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

ጥገኛ ምዕላ፡- ትርጉም የማይሰጥ ሲሆን ከነፃ ምዕላድ ጋር ሲጨመር ትርጉም ይሰጣል ወይም የቃል ክፍልን ከአንዱ ወደ ሌላው
ይቀይራል
 ጥገኛ ምዕላድ በሶስት ይከፈላሉ እነሱም፡- ቅድመ ግንድ፣ውስጠ ግንድ እና ድህረ ግንድ ተብለው ይጠራሉ፡፡
ምሳሌ
1. እንደአስተማሪዎቻችን
 እንደ- ፣ አስ- ቅድመ ግንድ ቅጥያ ሲሆኑ
 ተማረ፡- ዋና ቃል/ስርወ/ ቃል ነው፡፡
 -ኢ፣-ዎች፣-ኣችን የሚሉት ደግሞ ድህረ ግንድ ቅጥያዎች ናቸው፡፡
2. ቅጠላ ቅጠል
 ቅጠል አንድ ስርወ ቃል ሲሆን ሌላይኛው ቅጠል ደግሞ ሁለተኛው ዋና ቃል ነው፡፡
 እነዚህን ሁለት ዋና ቃሎች ያገናቸው ምዕላድ /-ኣ/ ናት ይህቺ ምዕላድ ደግሞ ውስጠ ግንድ ቅጥያ ትባላለች፡፡
 ቅድመ ግንድ፣ውስጠ ግንድ እና ድህረ ግንድ ቅጥያዎች በአንድ ላይ በሁለት ይከፈላሉ እነሱም፡- የእርባታ እና የምስረታ ምዕላድ
ይባላሉ፡፡
1.የእርባታ ምዕላድ
 አንድን የቃል ክፍል ወደ ሌላ የቃል ክፍል አይቀይሩም ነገር ግን አንድን ቃል ቅርጹን ይቀይሩታል፡፡
 የእርባታ ምዕላድ የሚባሉት እራሳቸውን ለቁጥር ለመደብ ለፆታ እና ለእምርነት እንዲሁም ለባለንብረትነት ያረባሉ፡፡
የእርባታ ምዕላድ እራሳቸውን ለቁጥር ሲያረቡ
 የእርባታ ምዕላዶች እራሳውን ከቃል በፊት እና በኋላ በመግባት ለቁጥር እራሳቸውን ያረባሉ፡፡
ከቃል በፊት በመግባት ለቁጥር እሚረቡ ምዕላዶች

ምሳሌ ምዕላድ ነጠላ ቁጥር ብዙ ቁጥር

1. እነ- ብንያም እነብንያም


2. እነ- እሱ እነሱ
ከቃል በኋላ በመግባት ለቁጥር እሚረቡ ምዕላዶች
ምሳሌ ነጠላ ቁጥር ምዕላድ ብዙ ቁጥር
1. በግ -ኦች በጎች
2. በሬ -ዎች በሬዎች
3. ቀን -ኣት ቀናት
4. ፃድቅ -ኣን ፃድቃን
 እነ-፣-ኦች፣-ዎች፣-ኣን፣-ኣት ቁጥርን ለማመልከት የሚጠቅሙ ምዕላዶች ናቸው፡፡
 የእርባታ ምዕላድ ለመደብ ሲረቡ ከቃል በኋላ/-ን/ የሚል አመልካች ምዕላድን ይወስዳሉ፤ ለእምርነት ሲረቡ ደግሞ ከቃሉ በኋላ
/-ኢት/፣/ኡኣ/ ዋ ይወስዳሉ፡፡
 የእርባታ ምዕላድ እራሳቸውን ለመደብ ሲያረቡ
ምሳሌ መደብ ቃል ምዕላድ
እኔ በላሁ -ሁ
እኛ በላን -ን
አንተ በላህ -ህ
አንቺ በላሽ -ሽ
እናንተ በላችው -ኣችው
እሱ በል -ኧ
እሷ በላች -ች
እነሱ በሉ -ኡ
 የእርባታ ምዕላድ እራሳቸውን ለመደብ ሲያረቡ
ምሳሌ መደብ ቃል ምዕላድ
እኔ ቤቴ -ኤ
እኛ ቤታችን -ኣችን
አንተ ቤትህ -ህ
አንቺ በላሽ -ሽ
እናንተ ቤታችሁ -ኣችው
እሱ በት -እ
እሷ በቷ -ኡኣ
እነሱ ቤታቸው -ኣቸው

15 የምስረታ ምዕላድ
 አንድን የቃል ክፍል ወደ ሌላ የቃል ክፍል ይቀይራል፡፡
1. -ኣም ከስም ወደ ቅፅል ይቀይራል

18
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

2. -ኣማ ከስም ወደ ቅፅል ይቀይራል


3. -አዊ ከስም ወደ ቅፅል ይቀይራል
4. -ኤ ከስም ወደ ቅፅል ይቀይራል
ምሳሌ ስም ምዕላድ ቅፅል
1. ተራራ -ኣማ ተራራማ
2. ስስት -አም ስስታም
3. ኢትዮጵያ -አዊ ኢትዮጵያዊ
4. ጎንደር -ኤ ጎንደሬ
 /-ኢ/ ከግስ ወደ ስም ይቀይራል፡፡ ምሳሌ ተማረ /-ኢ/ ተማሪ
 /-ነት/ ከቅፅል ወደ ስም ይቀይራል፡፡ ምሳሌ ደግ /-ነት/ ደግነት
 /-ነት/ ከስም ጋር ሲገቡ ስምነታቸውን አይቀይሩም፡፡ /ልጅነት/

መመሪያ አንድ፡- ለሚከተሉትን ጥያቄዎች ትክክለኛ መልስ የያዘውን ፊደል ምረጡ

1. ከየት መጣ ሳይባል ድንገት ሰይፉን ወደ ---------- መልሰው የሚል ድምፅ ሰማ፡፡


ሀ. ማህደሩ ለ. ቦታው ሐ. ቀፎቱ መ. አፎቱ
2. ሰዎቹ በአዘቦቱ እንመጣለን ብለዋል፡፡ የተሰመረበት ቃል ትርጉም
ሀ. በሰንበት ለ. በስራ ቀን ሐ. በእረፍት ቀን መ. በዓመት በዓል
3. ለፋሲካ ከታረደው በግ ወርቹን ስጡኝ፡፡ የተሰመረበት ቃል ትርጉም
ሀ. የኋላ እግሩን ለ. ደንደሱን ሐ. የፊት እግሩን መ. ሽንጡን
4. ልጅቷ እንደሙሉ ጨረቃ ክብፊት አላት፡፡ ይህ ዓ/ነገር በምን ዘይቤ የቀረበ ነው፡፡
ሀ. ምፀት ለ. ሰውኛ ሐ. ተለዋዋጭ መ. አነፃፃሪ
5. የፀጉሯ ዘለላ ከሸረሪት ድር ይቀጥናል፡፡ ይህ በምን ዓይነት ዘይቤ የተፃፈ ነው
ሀ. ተለዋጭ ለ. ተምሳሌት ሐ. አያዎ መ. ግነት
6. ዘመን አህያ ነው፤ የተጫነውን ሁሉ ተሸክሞ ወደ ፊት ይጓዛል፡፡ ይህ ፅሁፍ በየትኛው ዘይቤ ቀርቧል
ሀ. በምስያ ለ. በተምሳሌት ሐ. በግነት መ. በተለዋጭ
7. “አንተ እኮ ህይወት ያለህ በድን ነህ፡፡ በማለት አዛውንቱ ተናገሩ፡፡ የተሰመረበት ሀረግ የቀረበው በየትኛው ዘይቤ ነው
ሀ. በምስያ ለ. በሰውኛ ሐ. በኩሸት መ. በአያዎ
8. ለማንኛውም ቋንቋ መሰረት የሚባለው የቱ ነው
ሀ. ቃላት ለ. የአንደበት አካላት ሐ. ሆሄ መ. ድምፅ
9. አለ በለኝ ቀበሌን ሞተ በለኝ-------------------- ክፍት ቦታው ላይ መግባት ያለበት ቃል
ሀ. ከፈኔን ለ. ጉድጓዴን ሐ. ሰሌኔን መ. ሁሉም

10. ጋዜጠኛዋ ጭምብልህን አውጣ ብላ ተናገረች፡፡ ለተሰመረበት ቃል አቻ ፍቺ


ሀ. ሀሳብህን ለ. የተሸፈንክበትን ሐ. ንግግርህን መ. ሀ እና ሐ
መመሪያ ሁለት፡- ለሚከተሉት ቃላት ትክክለኛ አማራጭ የያዘውን ፊደል ምረጥ
11. ልዕልና
ሀ. ዋህድ ለ. መሪነት ሐ. ብኩርና መ. የበላይ
12. ብሔረ መንግስት
ሀ. ብዙ ብሔር ያላቸው ማህበረሰብ አስተዳዳሪ
ለ. አንድ ብሔር ያለው ማህበረሰብ አስተዳዳሪ
ሐ. አንድ ሀይማኖት ብቻ ያላቸው ማህበረስ አስተዳዳሪ
መ. አንድ ሐይማኖት ብዙ ብሔር ያላቸው ማህበረሰብ አስተዳዳሪ
13. ህዳጣን
ሀ. ቁጥራቸው ብዙ የሆኑ ማህበረሰቦች ለ. ቁጥራቸው ዝቅተኛ የሆነ ማህበረሰብ
ሐ. ማንነታቸው የጠፋ ማህበረሰብ መ. ቋንቋቸው ደብዘዛው የጠፋ ማህበረሰብ
14. ፅንፈኛ
ሀ. መመሳሳል የሚችል ለ. መመሳሰል የሚፈልግ
ሐ. አደገኛ መ. እኔ ብቻ አዋቂ ነኝ እሚል
15. ዶ/ር አብይ አሕመድ በንግግራቸው ላይ ስድብ ረብ የለሽ ነው አሉ፡፡ የተሰመረበት ቃል ትርጉም
ሀ. ምሳሌነት የሌለው ለ. የማያግባባ ሐ. ፋይዳቢስ መ. የማያስከብር
መመሪያ ሶስት፡- ለሚከተሉት ልዩ ልዩ ጥያቄዎች ትክክለኛ መልስ የያዘውን ፊደል ምረጡ
16. አይቡ ዳኛ፣--------------- ምሳሌያዊ አነጋገሩን ሊያሟላ የሚችለው የትኛው አማራጭ ነው
ሀ. ሰውየው ለቅሶኛ ለ. ልጁ ሀይለኛ ሐ. ቅቤው መልከኛ መ. አሬራው ጤነኛ
17. ---------------------- እኛም አለን ቁስል ምሳሌያዊ አነጋገሩን ሊያሟላ የሚችለው የትኛው አማራጭ ነው
ሀ. ልብ የሚያማልል ለ. ያንተን የሚመስል
ሐ. እንዳንተ ያለ ስል መ. አእምሮ የሚያነግል

19
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

18. እድሜዋ በመግፋቱ ምክንያት የወር አበባዋን ያቆመች ሴት ________ትባላለች፡፡


ሀ. አረጠች ለ. በከረች ሐ. ሃብቷቀና መ. ቅሪት
19. ከስራና ከህብረተሰብ የምርት ግንኙነት የሚመነጭ የነባራዊ ዕውነታ ነፀብራቅ ምን ይባላል?
ሀ. ርዕዮተ ዓለም ለ. ንቃተ ህሊና ሐ. አብዮት መ.መልሱ አልተሰጠም
20. የማትወልድ/ መውለድ ያቆመች/ ላም ምን ተብላ ትጠራለች
ሀ. መሲና ለ. መካን ሐ. ያረጠች መ. ጥጃ
መመሪያ አራት ከጥያቄ ቁጥር 21-28 የሚገኙትን ጥያቄዎች ከቀረቡት አማራጮች መካከል ከትርጉም አንፃር ልዩ
የሆነውን ምረጥ

21. ሀ. ረቡኒ ለ. መምህር ሐ. ነገረ ፈጅ መ. መጋቢ

22. ሀ. ነዳይ ለ. ምንዱባን ሐ. ሎተሪ አዟሪ መ. ችግርተኛ

23. ሀ.አልፋ ለ. የመጀመሪያ ሐ. ሀሌታ መ. አንደኛ

24. ሀ. ዋልጌ ለ. ባለጌ ሐ. ታራሚ መ. ሰነፍ


25. ሀ. አርአያ ለ. አብነት ሐ. ጎበዝ መ. ምሳሌ
26. ሀ. ቀጭን ጌታ ለ. ሀብታም ሐ. ዲታ መ. ምንዱባን
27. ሀ. ባድማ ለ. ወና ሐ. ጠፍ መ. ማቅ
28. ሀ. ትዕምርት ለ. ገቢር ሐ. ምልክት መ. መ. የለም

16.ምንባብ ሶስት
በንግዱ አለም ውስጥ የመጨረሻ ከፍታ ጫፍ የሚባለው ቦታ ደርሻለሁይሁን እንጂ ከዚህ ሁሉ ሀብት ደስታን ማግኘት አልቻልኩም በልፋቴ ከካመቸሁት
ሀብት ያገኘውት ደስታ እዚህ ግባ የማይባል ነው አሁን በሕይወቴ የመጨረሻው ሰአት አከባቢ አልጋ ላይ ሆኔ ያሳለፍኩትን ነገር ሁሉ ወደኋላ ሳስበው
እኮራበት የነበረው ሀብትና ዝናዬ ከንቱ እና ትርጉም አልባ እንደሆነ ተረድቻለሁ
አንድ ሰው መኪና እንዲነዳልህ ወይም ሰርቶ ገንዘብ እንዲያስገባልህ ልትቀትረው ትችላለህ እየተሰቃየህበት ያለውን በሽታ እንዲሸከምልህ ግን
ልትቀጥረው አትችልም
ምድራዊ የሆኑ ቁሳቁሶች ሁሉ ሊጠፉ ዳግምም ሊገኙም ይችላሉ አንድ ጊዜ ካመለጠህ ልታገኘው የማትችለው አንድ ነገር ግን አለ ------- እሱም
ሕይወትህ ነው
አንድ ሰው የቀዶ ጥገና ወደሚያደርግበት ክፍል ሲገባ አንብቦ ያልጨረሰው መፅሀፍ ትዝ ቢለው የመፅሀፉ ርዕስ ‹‹ጤናማ ህይወት የመኖር ሚስጥር››
የሚል ሊሆን እንደሚችል ጥርጥር የለውም
በየትኛውም የሕይወት ከፍታ ላይ ብንሆን የህይወታችን መጋረጃ የሚዘጋበት ቅፅበት ፊት ለፊት የምንጋፈጥበት አንድ ቀን መምጣቱ አይቀርም
ለቤተሰብህ፣ለትዳር አጋር እና ለጓደኞችህ የፍቅርን ውርስ አስቀምጥላቸው ራስህን ተንከባከብ ከሌሎች ጋር መልካም ግንኙነት ይኑርህ እያደግን ስንሄድና
የህይወት ትርጉም ሲገባን ውድ ሰዓትም አሰርን ርካሽ ሰዓት---- ሁለቱም የሚነግሩን ጊዜ እኩል መሆኑ ይገባናል
በኪሳችን ውድ ቦርሳም ያዝን ርካሽ ቦርሳ ----- በውስጡ የሚኖረውን የገንዘብ መጠን አይቀይረውም
የአንድ ሚሊዮን ብር መኪና ነዳን የሶስት መቶ ሺህ ብር መኪና የመንገዱን ርዝመት አይቀይረውም .አቅጣጫውም ያው አንድ ነው የምንደርሰውም ያው
እዚያው ቦታ ነው
ሰፊ ግቢ ውስጥ ኖርንም ጠባብ ቤት ብቸኝነቱ ያው እኩል ነው የውስጥ ደስታ በቁሳቁስ እንደማይገኝ ያን ጊዜ ይገባሃል አውሮፕላን ላይ የክብር ቦታም
ተቀመጥክ ወይም ተራ ቦታ አውሮፕላኑ ከተከሰከሰ እኩል ቁልቁል ትወርዳለህ እውነተኛ ደስታ የሚገኘው ከቤተሰብህ ከጓደኛችህ ከዘመዶችህ ጋር
በሚኖርህ ውብ ጊዜአት ብቻ ነው ከእነርሱ ጋር በምታሳልፈው ጊዜ በምትጫወተው ጨዋታ በምትዘምረው መዝሙር በምትስቀው ሳቅ እውነተኛ ደስታን
ታገኛለህ 5 ሊካዱ የማይችሉ የሕይወት እውነታዎች አሉ ልጆችህ ሀብታም እንዲሆኑ አታስተምራቸው ይልቅ እንዴት ደስተኛ መሆን እንደሚችሉ
አስተምራቸው ሲያድጉየነገሮች ዋጋ ሳሆን ጥቅማቸው ይገባቸዋል ምግብህን እንደ መድሀኒት ውሰድ ካልሆነመድሀኒት እንደምግብ ትወስዳለህ የሚወድህ
ሰው በቀላሉ አይለይህም ከአንተ ለመለየት 99 ምክንያት ቢኖረው እንኳ መለየት በማይችለበት አንዲት ነገር ላይ ፀንቶ ይቆማል ሰው ሆኖ በመፈጠርና
ሰው በመሆን መካከል ትልቅ ልዩነት አለ ይህ የሚገባቸው ጥቂት ሰዎች ናቸው ስትወለድ ውድ ነበርክ ስትሞትም ውድ ትሆናለህ በመካከል ያለውን
ማስተካከል ያንተ ፈንታ ነው በፍጥነት ለመሄድ ከፈለክ ብቻህን ሂድ ሩቅ ለመድረስ ከፈለክ ግን ከሌሎች ጋር አብረህ ተጓዝ
በዓለም ላይ ያሉስድስት ፈዋሽ ነገሮች የሚከተሉት ናቸው
የፀሀይ ብርሀን፣ እረፍት፣ስፖርት፣ ጥሩ ምግብ፣በራስ መተማመን እና ጓደኛ እነዚህን አጥብቀህ ያዝ ደስተኛ ህይወትን አጣጥም
ምንጭ፡- ከማህበራዊ ድረ ገፅ የተወሰደ የያዘውን ፊደል ምረጥ
መመሪያ አምስት፡- ከላይ በቀረበው ምንባብ መሰረት ለሚከተሉትን ጥያቄዎች ትከክለኛ መልስ
29. የምንባቡ ርዕስ ሊሆን የሚችለው
ሀ. ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ ለ. የነብስ ጥሪ ሐ. የመኖር ሚስጠር መ. መ.የለም
30. በኪሳችን ውድ ቦርሳም ያዝን ርካሽ ቦርሳ ----- በውስጡ የሚኖረውን የገንዘብ መጠን አይቀይረውም የሚለውን ሀሳብ ሊተካ የሚችለው የቱ ነው
ሀ. ወርቅ ወርቅነቱን የሚታወቀው በእሳት ሲፈተን ነው ለ. ሰው ሰውነቱን ካለረከሰው ሁሌም ውድ ነው
ሐ. ውድም ነገር ያለቦታው ርካሽ ነው መ. መ.የለም
31. የአንድ ሚሊዮን ብር መኪና ነዳን የሶስት መቶ ሺህ ብር መኪና የመንገዱን ርዝመት አይቀይረውም ሲል ምን ማለቱ ነው
ሀ. ምንም ሀብታም ብንሆን እንጀራ በወጥ እንጂ በወርቅ አንበላም

20
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

ለ. ደስተኛ የምንሆነው ገንዘብ ሲኖረን ነው


ሐ. ሁሉም ነገር ያው ነው በገንዘብ የሚለወጥ ነገር የለም
መ. መ.የለም
32. የህይወታችን መጋረጃ የሚዘጋበት ሲል ምን ማለቱ ነው
ሀ. የችግራችን ጊዜ ማለፉ ለ. የደስታችን ጊዜ መምጣቱን
ሐ. የህልፈታችን ጊዜ መቃረቡ መ. ማልቀሳችን
33. ሰፊ ግቢ ውስጥ ኖርንም ጠባብ ቤት ብቸኝነቱ ያው እኩል ነው
ሀ. የደስታችን መጠን የሚለካው ባለን ገንዘብ መጠን ነው
ለ. የሀዘናችን መጠን የሚለካው በገንዘብ መጠን ነው
ሐ. ገንዘብ እያለህ ካልሆነ ከሌለህ የለህም
መ. ፍቅር ከሌለ ሁሉም ነገር ከንቱ ነው
34. አውሮፕላን ላይ የክብር ቦታም ተቀመጥክ ወይም ተራ ቦታ አውሮፕላኑ ከተከሰከሰ እኩል ቁልቁል ትወርዳለህ ሲል ----------------ማለቱ ነው
ሀ. በገንዘብህ አልጋ ልትገዛ ትችላለህ እንቅልፍህን ግን አትገዛም
ለ. በገንዘብ መድሀኒት ልትገዛ ትችላለህ ጤናህን ግን አትገዛም
ሐ. ባይኖርህም ትኖራለህ ቢኖርህም ትሞታለህ
መ. ሁሉም
35. አጠቃላይ የምንባቡ ሀሳብ ------------------ነው
ሀ. ገንዘብ ጥቅም የለውም ለ. ገንዘብን ብቻ የምታስብ ከሆነ ብቻህን ትቀራለህ
ሐ. ገንዘብ ምንም አያደርግም ፍቅር ብቻ በቂ ነው መ. ጊዜህን በአግባቡ ተጠቀም ገንዘብን ብቻ ሳይሆን ፍቅርን አስብ
36. የሚወድህ ሰው በቀላሉ አይለይህም ከአንተ ለመለየት 99 ምክንያት ቢኖረው እንኳ መለየት በማይችለበት አንዲት ነገር ላይ ፀንቶ ይቆማል ይሄንን
ሀሳብ የሚያጠናክረው የትኛው ሀሳብ ነው
ሀ. ፍቅሬን ለመርሳት እወስንና ቀድሜ እምረሳው መወሰኔን ነው
ለ. ገንዘብህን ብሎ የቀረበህ ገንዘብህ ሲያልቅ ጥሎ ይሄዳል
ሐ. መልክህን ብሎ የቀረበህ መልክ ሲጠፋ ይተውሀል
መ. ለ እና ሐ
37. እንደምንባቡ ሀሳብ ለሰዎች ማስቀመጥ የሚኖርብን ውርስ------------ነው
ሀ. ፍቅርን ለ. ጤናን ሐ. ገንዘብ መ. ጥላቻን
መመሪያ ስድስት ለሚከተሉትን ጥያቄዎች ትከክለኛ መልስ የያዘውን ፊደል ምረጥ

38. ከሚከተሉት ተውሳከ ግሥ የሆነው ቃል የቱ ነው


ሀ. ክፉኛ ለ. እንደ ሐ.ስለ መ. ሞኝ

39. . ከሚከተሉት ምዕላዶች መካከል ሁለተኛ መደብ አንስታይን ፆታ አመልካች የሆነው የቱ ነው


ሀ. -ኣችን ለ.-ሽ ሐ. -ኣችሁ መ. -ህ

40. ከሚከተሉት ምዕላዶች መካከል ከግስ ወደ ስም የሚቀይረው ምዕላድ የቱ ነው


ሀ. አም ለ. አዊ ሐ. -ኢ መ. ነት

41. ሰላማዊነት የሚለው ቃል ------የቃል ክፍሉ ------------ ነው


ሀ. ግስ ለ. መስተዋድድ ሐ. ቅፅል መ. ስም

42. ከሚከተሉት ስሞች መካከል አብዢ ምዕላድ የማይወስደው የቱ ነው


ሀ. ብር ለ. በሬ ሐ. ቤት መ. ወተት

43. ከሚከተሉት ስሞች መካከል ኦች የሚለውን አብዢ ምዕላድ የማይወስደው የትኛው ነው


ሀ. በግ ለ.ቤት ሐ. ላም መ. ሞት

44. በአ.ነግር ውስጥ ባለቤትም ተሳቢም መሆን የሚችለው የቃል ክፍል የትኛው ነው
ሀ. ተ.ግስ ለ. ቅፅል ሐ. ግስ መ. ስም

45. ከሚከተሉት ከቅፅል ወደ ስም የሚቀይረው ምዕላድ የቱ ነው


ሀ. -አማ ለ. -ነት ሐ. -አዊ መ. ሀ እና ለ

46. መጣ የሚለው ግሥ ለሶስተኛ መደብ ተባዕታይ ፆታ ሲረባ ----------- ይሆናል

21
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

ሀ. መጣን ለ. መጣ ሐ. መጣህ መ. መጣው

47. በአማርኛ ቋንቋ ውስጥ ከሁሉም አነስተኛ ቃላት ያለው የቃል ክፍል ማነው
ሀ. መስተዋድድ ለ. ተ.ግስ ሐ. ቅፅል መ. ግስ

48. ከሚከተሉት ቃላዊ ሰነ ፅሁፍ የሆነው የቱ ነው

ሀ. ልቦለድ ለ.ተረት ሐ. ተውቴት መ. ሀ እና ሐ

49. ከሚከተሉት የተፀውኦም የረቂቅም ስም የሚሆነው የትኛው ነው

ሀ. ፍቅር ለ. ሰላም ሐ. ብርሀን መ. ሁሉም

50. ከሚከተሉት ምንም አይነት የፆታ አመልካች ሳይወስድ ሴቴ/አንስታይን/ ፆታ የሚያመለክተው የቱ ነው

ሀ. ጊደር ለ.በሬ ሐ. ድንጉላ መ. በግ

51. . ከሚከተሉት አንዱ የተፀውኦ ስም ነው


ሀ. ሰላም ለ.ወንበር ሐ. ዶሮ መ. መምህር
52. ቤት ብሎ አብያት ካለ ክንፍ ብሎ -------------ይላል
ሀ. አክናፍ ለ.ክንፎች ሐ. አክናፋት መ. ክንፋን
53. . በገፀባህሪያት መካከል የሚፈጠር ግጭት እየከረረ ሲሄድ የሚፈጠረው ነገር ከልቦለድ አላባውያን አንፃር ምን ይባላል
ሀ. ሴራ ለ.መቼት ሐ.ግጭት መ. ጡዘት
54. የቃል ክፍልን ከአንድ የቃል ክፍል ወደ ሌላ የቃለ ክፍል የሚቀይረው የትኛው ምዕላድ ነው
ሀ.የምስረታ ለ. የእርባታ ሐ. ጥገኛ መ. ነፃ
55. ሻይ የሚለው ቃል በአረብኛ ቋንቋ ውስጥም ሻይ ነው ይህ የትኛውን የቋንቋ ባህሪ ያሳያል
ሀ. ተወራራሽነት ለ. ዘፈቀዳዊነት ሐ. ትዕምርታዊነት መ. ስርአታዊነት
56. ከሚከተሉት ውስብስብ ዓ.ነግር የሆነው የቱ ነው
ሀ. ካሳ በልቶ ተኛ ለ. ካሳ ትናንት መጣ ሐ. ካሳ ወደ ቤቱ ሄደ መ. መ.የለም
57. ከሚከተሉት የቃለ ጉባዔ አፃፃፍ መመሪያ ያልሆነው
ሀ. የስብሰባ ርዕስ መፃፍ
ለ. የስብሰባ ቦታ እና ጊዜ መፃፍ
ሐ. በስብሰባ ላይ ያልተገኙ አባላትን መፃፍ
መ. መ. የለም
58. እስራ ምዕት ወ ሰባ
ሀ. 207 ለ. 2007 ሐ. 270 መ. 2070
59. የ 2078 ዓምዘመን እና መባቻ ምን ላይ ይውለል
ሀ. ዘመን ሉቃስ መባቻ አርብ ለ. ዘመን ማርቆስ መባቻ ሐሙስ
ሐ. ዘመን ማቲዮስ መባቻ ሰኞ መ. ዘመን ዮሐንስ መባቻ ቅዳሜ
60. በአማርኛ ቋንቋ ውስጥ በቃል መጀመሪያም፣ መካከልም ሆነ መጨረሻ ላይ ቢገባ የማይጠብቅ ድምፅ የትኛው ነው
ሀ. ል ለ. ፍ ሐ. ጥ መ. ፕ

ሀረግ

 ከቃል ከፍ ያለ ከዓ.ነገር የሚያንስ ሲሆን ትርጉም የማይሰጥ ነው፡፡


 በሀረግ ውስጥ መሪ፣ አጎላማሽ እና መሙያ የሚባሉ አካላት አሉት፡፡
 መሪ፡- የሀረጉ ዋና ክፍል ሲሆን የሀረጉን የአይነት የምናውቅበት መንገድ ነው፡፡
 መሙያ፡- መሪው የተሰራበትን ነገር የሚጠቁም ነው፡፡
 አጎላማሽ፡- መሪውን የሚገልፅ የሚያጎላምስ ማለት ነው፡፡

17. አ.ነገር
 ከስማዊ እና ግሳዊ ሀረግ ጋር ተጣምሮ ይፈጠራል
 ሙሉ ሀሳብን/ መልዕክትን/ ያስተላልፋል/
 ቢያንስ በውስጡ ባለቤት እና ግስ መያዝ አለበት

22
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

የአ.ነገር አይነት

1. ሀተታዊ ዓ.ነገር፡- አወንታዊ እና አሉታዊን ይይዛል

2. መጠይቃዊ ዓ.ነገር

3. ትዕዛዛዊ ዓ.ነገር

1. አወንታዊ፡- የተደረገን ድርጊት በአወንታዊ መልኩ መግለፅ ነው፡፡

ምሳሌ፡- አበበ ምግብ በላ፡፡

2. አሉታዊን ይይዛል ፡- የአወንታዊ ዓ.ነገር ተቃራኒ ነው፡፡

ምሳሌ፡- አበበ ምግብ አልበላም

አሉታዊ ዓ.ነገር በግሱ መጀመሪያ እና መጨረሻ ላይ አል- እና -ም የሚሉትን ምዕላድ ይወስዳል፡፡

 አወንታዊ እና አሉታዊ ዓ.ነገሮች በዓ.ነገሩ መጨረሻ ላይ አራት ነጥብን ይወስዳል

3. መጠይቃዊ ዓ.ነገር፡- ጥያቄያዊ ሀሳብ ያላቸው ሀሳቦችን የሚያነሳ ዓ.ነገር ነው እነዲሁም በዓ.ነገሩ መጨረሻ ላይ ጥያቄ
ምልክትን ይወስዳል

ምሳሌ ማን ጫማ ገዛልህ ?

4. ትዕዛዛዊ ዓ.ነገር ፡- የትዕዛዝ ስሜት ያለው ሲሆን ቃል አጋኖ ስርዓተ ነጥብን ይወስዳል፡፡

ምሳሌ፡- 1. ምግቡን ብላ! 2. ወደ ቤትህ ሄደህ ተኛ

ከላይ የተገለፁት ዓ.ነገሮች አይነቶች ተጠቅልለው በሁለት ይከፈላሉ

1. ተራ ዓ.ነገር፡- በውስጡ አንድ ብቻ ግስ የያዘ

2. ውስብስብ ዓ.ነገር፡- በውስጡ ሁለት እና ከዚያ በላይ ግሶችን የያዘ ነው፡፡

ምሳሌ 1 ሰለሞን አስር በጎችን ገዛ /ተራ ዓ.ነገር/

2. ቤቴልሄም ወደ ቤት ሄዳ እንጀራ ጋገረች /ውስብስብ ዓ.ነገር/

በምሳሌ 1 ላይ ገዛ ብቻ የሚል ግስ ሲሆን ያለው በምሳሌ 2 ላይ ግን ሄዳ የሚል እና ጋገረች የሚል ግሶች አሉ ስለዚህ ምሳሌ
1 ተራ ዓ.ነገር ሲሆን ምሳሌ 2 ግን ውስብስብ ዓ.ነገር ነው፡፡

መልመጃ 3 የሚከተሉትን ጥያቄዎች ተራ እና ውስብስብ ዓ.ነገር በማለት ለዩ፡፡

1. ለዕስራ ምዕቱ በዓል ምን ገዛ?


2. የአስቴር መፅሀፍ ገዛች፡፡
3. አለሙ ትናትና በመኪና ወደ ጎጃም ሄደ፡፡

23
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

4. እነዚያ የካሳ አስሩ በጎች ትናትና በመኪና ተገጭተው ሞቱ ፡፡


5. ከበደ ትናትና ሞተ፡፡

መልመጃ 4 የሚከተሉትን ጥያቄዎች በአጭሩ መልሱ

1. ከቃል ከፍ ያለ ከዓ.ነገር የሚያንስ እና ትርጉም የማይሰጥ አካል ምን ተብሎ ይጠራል -------------------------------


2. በሀረግ ውስጥ ሊኖሩ የሚችሉ አካለት -------------፣------------እና -------------ናቸው፡፡
3. -------------------የሀረጉ ዋና ክፍል ሲሆን የሀረጉን የአይነት የምናውቅበት መንገድ ነው፡፡
4. ------------------ መሪው የተሰራበትን ነገር የሚጠቁም ነው፡፡
5. -------------------መሪውን የሚገልፅ የሚያጎላምስ ማለት ነው፡፡
6. በሀረግ ውስጥ አይቀሬ አካል ----------------- ነው፡፡
7. ለስማዊ ሀረግ መሙያ በመሆን የሚያገለግለው -----------------ነው፡፡
8. ለስማዊ ሀረግ አጎላማሽ በመሆን የሚያገለግሉ የቃል ክፍሎች -------------------------------------------------------- ናቸው
9. ከንዑስ ሀረግ የሚወጣ የሀረግ አካል ----------------- ይባላል
10. ከዐብይ ሀረግ የሚወጣ የሀረግ አካል -----------------ይባላል
11. የአረፍተ ነገር አይነቶችን ግለፁ
ሀ.---------------------------------
ለ.---------------------------------
ሐ.--------------------------------
መ. -------------------------------

18. ሥርዓተ ነጥብ


 በፅሕፈት ወቅት የፅሕፈቱን መልዕክት በትክክለ ለመረዳት ይጠቅማል፡፡
 አማርኛ ቋንቋ የተለያዩ ስርዓተ ነጥቦች አሉት
የስርዓተ ነጥብ አይነቶች እና አገልግሎታቸው
1. አንድ ነጥብ /./
 ቃላትን በምፅሀረ ቃል ወይም በአፅሮተ ቃል አሳጥሮ ለመፃፍ ይጠቅማል፡፡
ምሳሌ፡- ዓመተ ምህረት /ዓ.ም/ አዲስ አበባ /አ.አ
 ብርን ከሳንቲም ለመለየት
ምሳሌ፡- ሶስት ብር ከሀምሳ /3.50/
አስር ብር ከዘጠና /10.90/
2. ሁለት ነጥብ /፡/
 ቃላትን ከቃላት ለመለየት እንዲሁም ሰዓትን ከደቂቃ ለመለየት ይጠቅማል፡፡
 በአሁን ሰዓት ቃልን ከቃል ለመለየት ብዙም አገልግሎት አይሰጥም፡፡
ምሳሌ 1 አበበ፡በሶ፡በላ፡፡ 2 ስድስት ሰዓት ተኩል ለማለት /6፡30
3. ሶስት ነጥብ/- - -/…
 በጅምር የቀረ ሀሳብን ለመግለፅ ያገለግላል፡፡
ምሳሌ 1. ሰማዩ በጭጋግ እንደከበደ ------- ምደር ቁልቁል ተጭኗል፡፡
4. አራት ነጥብ
 የአረፍተ ነገርን መግቻ /መቋጫ ነው፡፡

24
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

ምሳሌ 1 የአድዋ ድል የሁሉም አፍሪካውያን ድል ነው፡፡


5. ነጠላ ሰረዝ /፣/
 አንድ አይነት ሀሳቦች ያላቸውን ነገሮች ለመዘርዘር
ምሳሌ፡- አንበሳ፣ጅብ፣ቀበሮ እና ተኩላ የዱር እንስሳት ናቸው፡፡
 የመፅሐፍን ምዕራፎች እና ቁጥሮችን ለመለየት
ምሳሌ፡- የሉቃስ ወንጌል፣ ምዕራፍ 4፣ ቁጥር 6
 የግጥሞችን ቤት መምቻ ስንኞችን ለመለየት ፡፡
6. ሁለት ነጥብ ከሰረዝ /፡-/
 አንድ አረፍተ ነገር ከመቋጨታችን በፊት የሚዘረዘሩ ነገሮች መኖራቸውን ለመግለፅ ይጠቅማል፡፡
ምሳሌ የኪነ ጥበባት አይነቶች በርካታ ቢሆኑም አንዳንዶቹን ለመጥቀስ ያክል፡- ሥነፅሁፍ፣ ሥነስዕል፣ ሙዚቃ እና ቲያትር
ወ.ዘ.ተ
7. ድርብ ሰረዝ/፤/
 አብይ ሀረጎችን አጣምሮ ለማቅረብ /አረፍተ ነገር የሚመስሉ ሀሳቦችን ለመለየት ይጠቅማል፡፡
ምሳሌ 1 በጠዋት እንደሚደርስ አስረግጦ ቢነግረኝም፤ በቀጠረኝ ሰዓት ግን ሊደርስ አልቻለም፡፡
ምሳሌ 2 በቀጠርኩህ ሰኣት ስለምደርስ ፤ እንዳትዘገይ ፤ አደራ ለሌሎቹም ግን ንገራቸው፡
8. አግድም ሰረዝ /-/
 እስከ የሚለውን ሀሳብ ይወክላል
ምሳሌ ፡- ከአ.አ -ጅማ ምን ያክል እሩቅ ነው
 ሁለት ቃላትን ለማጣመር ይጠቅማል
ምሳሌ፡- ሥነ-ፅሁፍ ፣ቤተ-ክርስቲያን
9. እዝባር (/)
 ቃልን አሳጥሮ ለመፃፍ
ምሳሌ፡- ገብረ ኪዳን ገ/ኪዳን ትምህርት ቤት ት/ቤት ምክትል ርዕሰ መምህር ም/ር/መ/ር
10. ጥያቄ ምልክት /?/
 ጥያቄያዊ ስሜቶችን ለመግለፅ ይጠቅማል
ምሳሌ 1 ስምህ ማነው?
11. ትምህርተ አንክሮ /ቃል አጋኖ/ /!/
 አድናቆትን ፣ መገረምን ፣ ደስታን ፣ ድንጋጤ ፣ የምስራች የመሳሰሉትን ስሜቶች በፅሑፋችን ውስጥ ስንገልፅ
እንጠቀመዋለን፡፡
ምሳሌ፡- ሀ. አምላኬ ሆይ! ተባረክ!
ለ. ይሄ ጉዳይማ አይገርምም!
ሐ. ፐ! ምን አይነት ?ውበት ነው፡፡
12. ትምህርተ ስላቅ/ Ì/
 ምፀትን ሹፈትን ስላቅን ሽሙጥን ለመግለፅ እንጠቀምበታለን፡፡
13. ትምህረተ ጥቅስ/ ‹‹ ››/
 የእኛ ያልሆነን ሀሳብ በፅሁፋችን ውስጥ ስንጠቀም የምንገለገልበት ስርዓተ ነጥብ ነው፡፡
ምሳሌ 1 ‹‹ አታምጣው አታምጣው ስለው ከቤቴ በላይ ቆልሎት ሄደ›› የሚለው የእናቴ አባባል ትዝ ይለኛል፡፡
14. ቅንፍ ( )

25
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

 በፅሁፋችን ውስጥ የገባውን ዋና ቃል ለማብራራት ይጠቅማል


ምሳሌ፡- አሽከርካሪዎች(ሾፌሮች) በሙሉ ለትራፊክ ሕግ ሊታዘዝ ይገባል፡፡
መልመጃ 6 ለሚከተሉት ጥያቄዎች አጭር መልስ ስጥ
1. ደቂቃ እና ሰዓትን ለመለየት የሚጠቅመው ስርዓተ ነጥብ -----------------------ይባላል
2. እስከ የሚለውን ሀሳብ የሚተካ ስርዓተ ነጥብ --------------------- ተብሎ ይጠራል
3. ቃላትን ለማጣመር የሚጠቅም ሰርዓተ ነጥብ ---------------------- ተብሎ ይጠራል
4. አድናቆትን ፣ መገረምን ፣ ደስታን ፣ ድንጋጤ ፣ የምስራች የመሳሰሉትን ስሜቶች በፅሑፋችን ውስጥ ስንገልፅ
የምንጠቀመው ስርዓተ ነጥብ -------------------------ይባላል፡፡
5. ብርን ከሳንቲም ለመለየት የምንጠቀመው ስርዓተ ነጥብ ----------------------------ይባላል
6. የግጥሞችን ቤት መምቻ ስንኞችን ለመለየት የምንጠቀመው ስርዓተ ነጥብ ---------------------ይባላል፡፡
7. አረፍተ ነገሮችን ከአረፍተ ነገሮች ለመለየት የምንጠቀመው ስርዓተ ነጥብ -----------------------
8. የቃል አጋኖ ሌላይኛው ሰም ማን ይባላል-----------
9. የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር ዐብይ አሕመድ ስንኖር ኢትዮጵያዊ፤ ሰንሞት ደግሞ ኢትዮጵያ እንሆናልን አሉ ፡፡ይሄ
አነጋገር ሊወስድ የሚገባው ስርዓተ ነጥብ ------------------------
10. አንድ አረፍተ ነገር ከመቋጨታችን በፊት የሚዘረዘሩ ነገሮች ሲኖሩ የምንጠቀመው ስርዓተ ነጥብ ---------------------------
ይባላል፡፡

19.የቃላት ትርጉም /ፍቺ/


ቃላት በሚከተሉት መልኩ ይፈታሉ

1. ተመሳሳይ ተቃራኒ 2. እማራዊ ፍካራዊ 3. አውዳዊ ፍቺ 4. አቻ ፍቺ 5. ላልቶ እና ጠብ

ተመሳሳይ ተቃራኒ

ቃላት ተመሳሳይ እና ተቃራኒ የሆነ ፍቺያቸው የሚታይበት መንገድ ነው

ተ.ቁ ቃላት እማራዊ ፍቺ ፍካራዊ ፍቺ ምሳሌ

1 ሬሳ በድን ደካማ
ተ.ቁ ቃላት ተመሳሳይ ተቃራኒ
2 ቄጤማ የሳር አይነት ልፍስፍስ
1 ሰርክ ዘውትር አልፎ አልፎ
3 ውሻ የእንስሳ ስም ልክስክስ
2 ተሰድረው ተስተካክለው ተመሰቃቅለው
4 እንግሊዝ የሀገር ስም ብልጥ
53 ሀኬት
ወስፌ ስንፍና
መስፊያ ጉብዝና
ቀጭን
64 በላ
ባህር ተመገበ
የተኛ ውሃ ጠጣሰፊ
7 እርግብ የእንስሳ ስም የዋህ
8 አንበሳ የእንስሳ ስም ጀግና ደፋር
9 እፉኝት የእባብ ዘር መርዘኛ እማራዊ እና ፍካራዊ ፍቺ

እማራዊ፡- ቀጥተኛ ትርጉም ሲሆን ፍካራዊ ደግሞ ድብቁ ፍቺ

ምሳሌ

26
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

አውዳዊ ፍቺ

 ቃላት በሚገቡበት አውድ የሚኖራቸው ትርጉም ማለት ነው

ምሳሌ 1. ነገ የፋሲካ በዓል ነው

2. የእኛ ፋሲካችን የሆነው ክርስቶስ ታርዶልናል

3. የዘንድሮ ትዳር በፍቺ ነው እሚያልቀው

4. ከሰው ሰው የቃላት ፍቺ የተለያየ ነው፡፡ በአራቱ ምሳሌዎች ውስጥ ያሉ ቃላት ፋሲካ እና ፍቺ የሚሉት ቃላት
እንደገቡበት አረፍተ ነገር የተለያየ ፍቺ ስለሰጡ የተገኘው ፍቺ አውዳዊ ፍቺ ይባላል፡፡

አቻ ፍቺ

 የአንድ ቃላት ሌላይኛው ቀጥተኛ /ጥሬ ፍቺን/ ይመለከታል፡፡


ምሳሌ

ተ.ቁ ቃላት አቻ ፍቺ

1 ሀሌታ ምስጋና
2 ህብር ስም
3 ህዳግ ጠርዝ
4 ለሆሳስ ቀስታ
5 ምንዳ ደሞዝ
6 ሲሳይ በረከት
7 ሲራክ ብልህ
8 በተሀ ለጋ ጠጅ
9 አንድምታ ትርጓሜ
10 ዘማዊ ሴሰኛ
11 ጃንደረባ ስልብ
12 ግልድም ሽርጥ
13 ጦማር ደብዳቤ
14 ፍስሀ ደስታ

27
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

15 ፍላፃ ቀስት
16 ፍኖት መንገድ

ላልቶ እና ጠብቆ
 አንድ ቃል ጠብቆ እና ላልቶ ሲነበብ የሚሰጠው ፍቺን ይመለከታል፡፡
ምሳሌ

ተ.ቁ ቃላት ላልቶ ጠብቆ

1 ታነባለች ታለቅሳለች መፅሐፍ ታነባለች

2 ልረዳ እገዛ ላደርግ ልገነዘብ/እርዳታ ላገኝ

3 መላ ዘዴ በሙሉ/ሁሉም

4 በሬ የሚያርስ እንሰሳ መዝጊያዬ

5 አያት እመለከታት የእናቴ/አባቴ/ እናት/አባት

6 አካፋ አፈር መዛቂያ ዝናብ ዘነበ

7 ይበራል ብርሀን አለ በአየር ላይ ይሄዳል

8 ስልጣኔ ማዕረጌ ማደግ መሻሻል

9 ጥሬ ያልበሰለ ለፍቼ

10 ገላ ሰውነቴ ሰው ገላ

20.ሥነፅሁፍ
 በቃልም ሆነ በፅሁፍ መልክ የሚቀርብ ሀሳብ ሲሆን ይሄ ሀሳብ የአንድ ማህበረሰብ ባህል ፣ወግ ፣ እምነት ፣ አስተሳሰብ
፣ፍቅር በደራሲ አማካኝነት ለተደራሲ የሚቀርበብት መንገድ ነው
 ሥነ ፅሁፍ በሁለት ይከፈላል
1. ፅሁፋዊ ስነ ፅሁፍ
2. ቃላዊ ስነ ፅሁፍ
1. ፅሁፋዊ ስነ ፅሁፍ

ፅሁፋዊ ስነ ፅሁፍ ማለት የተፃፉ እና በብዕር ተከትበው በመፅሀፍ መልክ ወይም በኤልክትሮኒክስ መሳሪያዎች አማካኝነት ለተደራሲ
የሚቀርቡ ምናባዊ ፈጠራዎች አልያም እውነታዊ ክስተቶች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

ፅሁፋዊ ስነ ፅሁፎች በሁለት መልኩ ሊቀርቡ ይችላል አንድም በግጥማዊ መልክ አንድም በዝርው መልክ

28
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

የፅሁፋዊ ስነፅሁፍ ዘርፎች

1. ልቦለድ
2. ግጥሞች
የልቦለድ አላባውያን
1. ታሪክ፡- በልቡለዱ ውስጥ ሊተላለፍ የተፈለገውን አጠቃላ ነገር የሚይዝ ነው፡፡
2. ገፀባህሪያት፡- በልቦለዱ ውስጥ የሚተላለፈውን ሀሳብ ወክለውየሚንቀሳቀሱ የደራሲው ምናባዊ ፍጡራን ናቸው
3. ሴራ ፡- በገፀባህሪያት መካከል የሚፈጠረው ግጭት ከፍ እያለ ሲሄድ እና አለመግባባታቸው ሲከር የሚፈጠር ነገር ነው፡፡
የሴራ አይነት
4. ጭብጥ፡- በአንድ ልቦለድ ውስጥ ሊተላለፍ የተፈለገው ፍሬ ሀሳብ ወይንም መልዕኩ ምንድን ነው የሚለውን የሚመልስ ነገር
ነው
5. ግጭት፡- በገፀባህሪያት መካከል የሚፈጠር አለመግባባት ነው፡፡
6. መቼት፡- ታሪኩ መቼ እና የት ተፈጠረ የሚለውን ይመልሳል፡፡
7. አንፃር፡- ማለት ታሪኩ እንዴት ይቅረብ የሚለውን ሀሳብ የሚተርክብት መንገድ ሲሆን ሶስት አይነት አንፃር አለ፡፡
ሀ. ሁሉን አቀፍ፡- በሶስተኛ መደብ የሚተረክ ሲሆን ተራኪው ሁሉንም ነገር በሚገባ ያውቃል ከተራኪው የሚደበቅ ሚስጥር
እሚባል ነገር የለም ስለዚህ የእያንዳንዱን ገፀባህሪያት ገበና አውጥቶ ለተደራሲያን ያቀርባል ወደፊት ምን ሊፈጠር ይችላል
የሚለውን ሀሳብ ሁሉ መገመት ይችላል፡፡
ሁሉን አወቅ አንፃር ድክመቱ ተደራሲያን ግምት እንዳይሰጡ ያደርጋል፡፡
ለ. ውሱን ሁሉን አወቅ አንፃር፡- የሚቀርበው በ 3 ኛ መደብ ሆኖ ተራኪው ሁሉንም የማወቅ እድል የለውም እውቀቱ
በአንፃራዊነት የተገደበ ነው፡፡ እንዲሁም በግል ስለሚፈጠር ነገር የመገመት ዕድል የለውም ትረካዎቹም የሚቀርቡት ከዋናው
ገፀባህሪ አንፃር ብቻ ሲሆን ንዑስ ገፀባህሪያትን ለማወቅ አዳጋች ይሆናል
ይሄ አንፃር ቀለል ያለ እና የተሻለ ነው በሚል ብዙ ደራሲን ይመርጡታል
ሐ. አንደኛ መደብ አንፃር
ተራኪው እኔ ወይም እኛ እያለ በአንደኛ መደብ ይተርካል፡፡
እኔ ወይም እኛ እያለ የሚተርከው ተራኪ ዋና ወይም ንዑስ ገፀባህሪ ሊሆን ይችላል፡፡
አጭር እና ረጅም ልቦለድ
አጭር ልቦለድ
 በውሱን ቦታና ጊዜ ይወሰናል
 የገፀባህሪያት ቁጥር ጥቂት ነው
 ቅልብጭ ያለ እና ተደራሲያን አንዴ ሊያነቡት የሚችሉ ታሪክ አለው፡፡
 ደራሲው ሶስቱንም አንፃር መርጦ መጠቀም ይችላል
 ሴራው ተዓማኒ ፈጣን እና ወዲያውኑ የሚታይ ጥድፍ ጥድፍ ባይ ነው፡፡
 ውሱን ቁጥብና በውጤት ላይ ያነጣጠረ ቋንቋና ገለፃ ይጠቀማል
 አንድ ነጠላ ብቻ ጭብጥ አለው፡፡
ረጅም ልቦለድ
 ሰፊ ቦታና ጊዜ ያካልላል
 የገፀባህሪያት ቁጥር በርካታ ነው
 ከልደት እስከሞት ካሻው ደግሞ ከልደት እስከ ሞት ያለ ታሪክ አለው፡፡
 ደራሲው ሶስቱንም አንፃር መርጦ መጠቀም ይችላል

29
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

 ሴራው ውስብስብ ነው፡፡


 ከቋንቋ አንፃር አንባቢን ግራ እስካላጋባ ድረስ መራቀቅ ይችላለል
 ዐብይ ጭብጥ አንድም ሁለትም ሊሆን ይችላል ሌሎች በርካታ ንዑሳን ጭብጥ አለው፡፡
የሁለቱ ልቦለዶች መሰረታዊ ቴክኒኮች
ሀ.ምልሰት፡- ያለፈን ታሪክ ወደ ኋላ በመመለስ የማስታወሻ ዘዴ ነው፡፡
ለ. ንግር፡- ገና ያልተደረሰበት ታሪክ በተራኪው አማካኝነት በረቀቀ ዘዴ ፍንጭ የሚጠጥበት መንገድ ነው፡፡

21.ግጥም
 ዜማ አለው አጭር እና እምቅ ነው ቃላት ላይ ቁጥብነት አለው
 በትንኝ ቃላት ብዙ መልዕክት ማስተላለፍ ይቻላል፡፡
የግጥም ባህሪያት
 ተጨባጭነት
 ቁጥብነት
 ሙዚቃዊነት
 ምናባዊነት
ተጨባጭነት፡- ያለ ምክንያት እማይገጠም ሲሆን ረቂቅ የሆነ ነገርን እንድናውቃቸው እና የበለጠ ተጨባጭ እንዲሆኑ የማድረግ
አቅም አለው፡፡
ቁጥብነት፡- በጥቂት ቃላት ብዙ ሀሳብ መግለፅ ይችላል፡፡
ሙዚቃዊነት፡- ግጥም ሲነበብ የራሱ የሆነ ዜማ አለው፡፡
ምናባዊነት፡- ግጥም ሲገጠምም ሆነ ሲነበብ በተደራሲያን አእምሮ ላይ ምስል የመከሰት አቅም አለው፡፡
የግጥም ሙያዊ ቃላት
1. ሀረግ፡- የአንድ ግጥም ግማሽ ስንኝ አካል ነው፡፡ በአንድ ትንፋሽ የሚነበብ ነው፡፡
 ሀረግ በሁለት ይከፈላል እነሱም፡- መነሻ እና መድረሻ ሀረግ ይባላሉ
ምሳሌ፡- ወይ አዲስ አበባ/ ወይ አራዳ ሆይ፣
ሀገርም እንሰው/ ይናፍቃል ወይ፡፡
 ከላይ የቀረበው ግጥም አራት ሀረጋት አሉት፡፡
2. ስንኝ፡- የግጥም አንድ መስመር ተሳክቶ ሲያልቅ ነው፡፡
ምሳሌ፡- ትመር እንደሆነ ምረር እንደ ቅል፣
አልመርም ብሎ ነው ዱባ ሚቀቀል፡፡
 ከላይ የቀረበው ግጥም ሁለት ስንኞች አሉት፡፡
3. ቤት፡- በግጥም ስንኞች መጨረሻ ላይ የሚገኝ ሆሄ ነው
ምሳሌ፡- ማሽላና ስንዴ/ባንድ አድርገን ስንቆላ፣
እያረረ ሳቀ የባህር ማሽላ፡፡
 ከላይ የቀረበው ግጥም የመጨረሻው ፊደላት ቤት ይባለሉ
4. ቤት መምቻ፡- የመጀመሪያው ስንኝ የመጨረሻ ቃል ነው፡፡
5. ቤት ደፋ፡- የግጥሙ የመጨረሻው ስንኝ ተሳክቶ ሲያልቅ ነው፡፡
ምሳሌ፡- ምንሊክ ተነስቶ ባያነሳ ጋሻ
ግብሩ እንቁላል ነበር ይህን ጊዜ አበሻ

30
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

 ቤት መምቻ፡- ጋሻ
 ቤት ደፋ፡- አበሻ
6. አርኬ፡- በአንድ አይነት ቤት ወይም ድምፅ የተደረደሩ የስንኞች ስብስብ ነው፡፡
 በግጥም ውስጥ ትልቁ ክፍል ነው
 በአራት ነጥብ ይጠናቀቃል
7. ምጣኔ ፡- በግጥም ውስጥ የቀለማትን መጠን የምንለካበት ስልት ነው፡፡
 ግጥም ምጣኔ ከሌለው ምቱ ይዛባል፡፡
 ምት ከሌለው ደግሞ ዜማ አይኖረውም
8. ቀለም፡- በግጥም ውስጥ ጠብቀው የሚነበቡ ሆሄያት ቀለም ይባላል
 ሳድስ ሆሄያት በቃል መጀመሪያ ከመጣ ቀለም ሆኖ ይቆጠራል፡፡
 ሁለት ሳድሶች ተከታትለው ከመጡ እንደ አንድ ቀለም ይቆጠራል፡፡
ምሳሌ፡- ምነው ተቀየረ/የልጆች መንፈሱ
የጨዋታ ሱስ/የቡረቃ ምሱ

22.የግጥም አይነት
1. የወል ቤት፡- በሁለት ስንኘ በአራት ሀረጋት የተዋቀረ ሲሆን እያንዳንዱ ሀረጋት እኩል ሰድስት ስድስት ቀለማት አሉት፡፡

ምሳሌ የደንቆሮ መንፈስ ምነኛ ታደለ 6/6

ብልጥነት አላጣም ጅል እየመሰለ

2. ሰንጎ መገን፡- በሀረግ አምስት በስንኝ 10 ቀለማት አሉት፡፡ 5/5


ምሳሌ፡- ገለል በሉለት አንደዜ ለሱ
ግልግል ያውቃል ከነፈረሱ፡፡
3. ቡሄ በሉ፡- በሀረግ 4 በስንኝ 8 ቀለማትን ይይዛል፡፡ 4/4
ምሳሌ፡- ሆያ ሆዬ

23.ቲያተር
 ከግሪክ ቋንቋ የተገኘ ቃል ሲሆን ቲያትር የሚለው ቃል ትዕይንቱን ብቻ የሚወክል ቃል ሳይሆን ትዕይንቱ የሚከናወንበትን
ሕንፃ የሚወክል ቃል ነው፡፡
ድራማ
 ድራማ የሚለው ቃል ከግሪክ ቋንቋ የተገኘ ሲሆን በጥንታዊ ትርጉሙ ድርጊትና ተግባር የሚሉ ፅንሰ ሀሳቦችን ተሸክሟል፡፡
ተውኔት
 ተውኔት የሚለው ስያሜ የተገኘው ተዋነየ ከሚለው ከእኛው የግዕዝ ቋንቋ ሲሆን ትዕይንታዊ የሆኑ እንቅስቃሴዎችንና
መዝናኛዎች ያመለክታል፡
 ተውኔት የሚለው ስያሜ በመድረክ ላይ ለሚቀርበው ትርዒት ድራማን ወይንም ቴአትርን ወክሎ ግልጋሎት ይችላል፡፡
 ለተደራሲያን በመድረክ ላይ የሚቀርብ ነው፡፡

 ገፀባህሪያቱ ከተደራያን ፊት ለፊት ሆነው ይተውኑበታል፡፡

31
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

 ገፀ ባህሪያቱ ምናባዊ አይደሉም፤ ስለሆነም ገፀባህሪያቱ ሲያወሩ፣ሲደሰቱ፣ሲያዝኑ፣ሲበሉ፣ሲጠጡ በገሀድ ይታያሉ፡፡


የተውኔት ዘውጎች/ዓይነቶች/
1.ትራጀዲ፡- ሀዘን ፣ ፍርሀት ፣ጭንቀት እና ስቃይ የተጋነነበት የተውኔት አይነት ነው፡፡
2. ኮሜዲ፡- የትራጀዲ ተቃራኒ ሲሆን ደስታ ሀሴት መዝናኛ በእጅጉ የሚስተዋለበት የተውኔት አይነት ነው፡፡
3. ድንቃይ፡- እኩይ እና ሰናይ ገፀባህያት እንደየባህሪያቸው የሚፋለሙበት እና ሰናይ ገፀባህሪው ሲያሸንፍ የሚስተዋልበት ነው፡፡ እንዲህ
አይነቱ ተውኔት ሥነ ምግባርን ለማስተማር ይመረጣል፡፡
4.ቧልታይ፡- በፌዝ እና ቧልታዊ ትዕይንቶች የተሞላ ሲሆን በሁካታ እና በሳቅ የተሞላ ነው በዚህ ተውኔት ጥያቄ ላይጠየቀ ይችላል
ዋናው የነተሳው ሀሳብ ያስቃል አያስቅም የሚለው ብቻ ነው የሚታየው፡፡

24. ዘይቤ
 በዕለት ተዕለት ግንኙነታችን ውሰጥ የምንጠቀማቸው ሲሆን ዘይቤዎች ለንግግሮቻችን ለዛ ለመስጠት ንግግሮቻችንን ውበት
ለመስጠት እንጠቀማቸዋለን፡፡
 በንግግራቸውን ውስጥ ሆን ብሎ ማፈንገጥ ነው፡፡
የዘይቤ አይነቶች
1. ተለዋዋጭ ዘይቤ፡- የአንድን ነገር ባህሪ ለሌላ ነገር ሙሉ በሙሉ መስጠት ነው፡፡
ምሳሌ፡- ልጅቷ ተርብ ነች፡፡ ልጁ አንበሳ ነው፡፡
2. አነፃፃሪ ዘይቤ፡- አንድን ነገር ከሌላ ነገር የምናነፃፅርበት መንገድ ሲሆን እንደ እና ይመስላል ያክላል የሚሉ ቃላቶችን ወስዶ
ያነፃፅራል፡፡
ምሳሌ ልጁ እንደ አንበሳ ይጮሃል ልጅቷ በሬ ታክላለች
3. ሰወኛ ዘይቤ፡- ሰው ያልሆኑ ነገሮች የሰውን ስሜት ተላብሰው ንግግር የሚያደርጉበት መንገድ ነው፡፡
ምሳሌ 1. መሬት እልል አለች
2. እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል አለች አህይ

4. ተምሳሌት ዘይቤ፡- አንድነ ነገር በሌላ ነገር መመሰል ነው

ምሳሌ 1. የእውቀት ተምሳሌት ብርሀን ነው

2. ድንቁርና ተምሳሌት ጨለማ

5. እንቶኔ ዘይቤ፡- አጠገብ የሌለን ነገር አጠገብ እንዳለ በማሰብ እና እንደሚሰማን በማሰብ ማወያየት ነው፡፡

ምሳሌ የአባቴ ውቃቢ አንተ ተለመነኝ

ምነው ኢትዮጵያ ጭንቅሽ በዛ

6. ግነት ዘይቤ፡- ጥቂት እውነት ኖሮት አብዛኛው ነገር ውሸት የሆነ ነገር ነው

ምሳሌ፡- ቤቱ ፈረስ ያስጋልባል የሰማይ ስባሪ እሚያክል ዳቦ በላው

7. አያዎ፡- መጀመሪያ አይ ቀጥሎ አዎ የሚያስብል ነው

ምሳሌ፡- እየሰሙ አለመስማት እያዩ አለማየት

32
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

8. በስመሀዳሪ፡- ከጠቀሜታ አንፃር አንዱን በሌላ መወከል ነው


ምሳሌ፡- ወንበሩ አዳላብን ቀሚስ ካየ ልቡ ይጠፋል
9. ንቡር ጠቃሽ፡- ቀደም ሲሉ በምድር ላይ የቆዩ ሰዎችን ወይመ ሌሎች ነገሮችን በማጣቀስ መናገር ነው
ምሳሌ፡- የእዮብ ትዕግስት ይኑርህ የማቱሳላን ዕድሜ ይስጥህ

መልመጃ
መመሪያ 1፡- ለሚከተሉት ጥያቄዎች ትክከለኛ መልስ ስጡ
1. የተውኔት አይነቶችን ግለፁ
ሀ.------------------------------ ለ.-----------------------
ሐ.---------------------------- መ.------------------------
2. የግጥም አይነቶችን ግለፁ
ሀ.------------------------------ ለ.-----------------------
ሐ.---------------------------- መ.------------------------
3. ልቦለዶች መሰረታዊ ቴክኒኮች ግለፁ
ሀ.------------------------------ ለ.-----------------------
4. የልቦለድ አላባውያንን ግለፁ
ሀ.------------------------------ ለ.-----------------------
ሐ.---------------------------- መ.------------------------
ሠ.--------------------------- ረ.-------------------------
ሰ.----------------------------
5. የልቦለድ አንፃርን ጥቀሱ
ሀ.------------------------------ ለ.-----------------------
ሐ.----------------------------
መመሪያ 2. ለሚከተሉት ጥያቄዎች አጭር መልስ ስጡ
1. ---------------በልቡለዱ ውስጥ ሊተላለፍ የተፈለገውን አጠቃላ ነገር የሚይዝ ነው፡፡
2. ----------------በልቦለዱ ውስጥ የሚተላለፈውን ሀሳብ ወክለውየሚንቀሳቀሱ የደራሲው ምናባዊ ፍጡራን ናቸው
3. ---------------- በገፀባህሪያት መካከል የሚፈጠረው ግጭት ከፍ እያለ ሲሄድ እና አለመግባባታቸው ሲከር የሚፈጠር ነገር ነው፡፡
4. -----------------በአንድ ልቦለድ ውስጥ ሊተላለፍ የተፈለገው ፍሬ ሀሳብ ወይንም መልዕኩ ምንድን ነው የሚለውን የሚመልስ
ነገር ነው
5. --------------- በገፀባህሪያት መካከል የሚፈጠር አለመግባባት ነው፡፡
6. ---------------ታሪኩ መቼ እና የት ተፈጠረ የሚለውን ይመልሳል፡፡
7. ------------------ ሀዘን ፣ ፍርሀት ፣ጭንቀት እና ስቃይ የተጋነነበት የተውኔት አይነት ነው፡፡
8. ------------------ የትራጀዲ ተቃራኒ ሲሆን ደስታ ሀሴት መዝናኛ በእጅጉ የሚስተዋለበት የተውኔት አይነት ነው፡፡
9. ------------------ እኩይ እና ሰናይ ገፀባህያት እንደየባህሪያቸው የሚፋለሙበት እና ሰናይ ገፀባህሪው ሲያሸንፍ የሚስተዋልበት
ነው፡፡ እንዲህ አይነቱ ተውኔት ሥነ ምግባርን ለማስተማር ይመረጣል፡፡
10. ------------ በፌዝ እና ቧልታዊ ትዕይንቶች የተሞላ ሲሆን በሁካታ እና በሳቅ የተሞላ ነው በዚህ ተውኔት ጥያቄ ላይጠየቀ
ይችላል ዋናው የነተሳው ሀሳብ ያስቃል አያስቅም የሚለው ብቻ ነው የሚታየው፡፡
መመሪያ 3 የሚከተሉትን ዘይቤዎች ትክክለኛ የዘይቤ አይነታቸውን ፃፉ

33
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

1. አንቺ እመብርህን---------------------------
2. የአንበሳ ደቦል የመሰለ ልጅ-------------------
3. ጠባይዋ ወርቅ ነው------------------
4. ሺ ቢታለብ ያው በገሌ አለች ድመት-----------------
5. የዳዊትን ብልሀት ይስጥህ------------------
6. ኪዳነምህረት ፈጥነሽ አቤት በይኝ----------------
7. እንደ ሸማኔ መወርወሪያ----------------
8. ሰማይ ምድሩ ይደበላለቅብኛል-----------------
9. ገፅታዋ ጣረሞት ይመስላል--------------------

26.ስነ ቃል

 ከትውልድ ወደ ትውልድ በመተረት፣በመዜም፣በመነገር በአጠቃላይ በቃል የሚተላለፍ ነው፡፡


የሥነ-ቃል ባህሪያት
1. አፋዊነት፡- ሥነ-ቃል ከተፈጠረ በኋላ የሚተላለፈው ወይም የሚነገረው በአፍ ነው፡፡
2. አጭርነት፡- አብዣኛው የሥነቃል ቅርፆች አጭር ናቸው፡፡ ከሁሉም ረጅም እሚባለው ተረት ነው እሱም አንዴ ተነግሮ እዛው
የሚያልቅ ነው፡፡
3. ተለዋዋጭነት፡- ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፈው በአፍ እንደመሆኑ መሰረት ከውስጡ የሚረሱ የሚቀሩ ቃላት ወይም
ሀረጋት ይኖራሉ፡፡
4. የወል ሀብት፡- ሥነ ቃል ደራሲ አልባ ነው ደራሲው ማህበረሰቡ እንደመሆኑ መጠን ሁሉም በፈለገ ሰዓት እንደፈለገ ይጠቀማል
ምክንያቱም ሥነቃል የወል ሀብት ስለሆነ፡፡
5. ተደጋጋሚነት፡- ሥነቃል ቦታውን እና አጋጣሚው በተፈጠረ ቁጥር እየተደጋገመ ይከናወናል፡፡
6. ቀመራዊነት፡- ሥነ ቃል የራሱ የሆነ የሚከተለው ሥርዓት ወይም ቀመር አለው፡፡ለምሳሌ ተረት ሲቀር ተረት ተረት ተብሎ ነው
የሚጀመረው ተረቱ ሲያልቅም የሚባለው የራሱ ሥርዓት አለው፡፡እንቆቅልሽም እንደዛው፣እሰጥ አገባም ሌሎችም ስነቃል
የየራሳቸው ሥርዓት አላቸው
7. ክዋኔ፡- ሥነቃል ካልተከወነ ሕይወት የለውም
ሥነቃል እንዲከወን የመከወኛ አውድ ይፈልጋል ለምሳሌ የሙሾ ግጥሞች እንዲደረደሩ ሙሾ የግድ ይፈልጋል ሌላውም
እንደዛው ምናልባት አውድ የማይፈልገው ሥነቃል ተረት እና ምሳሌ እንዲሁም ፈሊጣዊ ንግግሮች ናቸው፡፡ በማንኛውም ቦታ
ሊባሉ ይችላሉ፡፡

የሥነቃል ተግባራት
1. የማዝናናት ተግባር፡- ሥነቃል የሚከወነው አዝናኝ በሆነ መንገድ ነው፡፡ በሥነቃል ጌዜ የሚገኘው ደስታ የምንገልፀው በሳቅ
ወይም በሲቃ ነው፡፡
በሰርግ ጫወታ፣በቀረርቶ፣እንቆቅልሽ እና በእንካ ሰላምታ ጊዜ ልንስቅና ልንዝናና እንችላለን፡፡
2. የማስተማር ተግባር፡- የሥነ ቃል አላማ በመጀመሪያ ማዝናናት ነው ከማዝናናት ቀጥሎ ደግሞ አንዳች ቁምነገርን ለተደራሹ
ማስተማር ነው፡፡ በተለየም ሥነቃል ላልተማሩ እና ላልሰለጡ ማህበረሰብ ብቸኛ የማስተማሪያ መንገድ ሆኖ ቆይቷል፡፡
ለምሳሌ፡- በተረት ውስጥ ጅብ እና ጦጣ የሚሳሉበት መንገድ ተረቱን ለሚያዳምጡ ልጆች ከጦጣ ብልሀትን ከጅብ ደግሞ
በጉልበት ብቻ ማሰብ ጥቅም እንደሌለው ይማራሉ፡፡ በእንቆቅልሽም እንደዛው የሚጠይቀው ሰው ሲጠይቅ መላሹ ደግሞ
ያስባል ይመልሳል በዛ ውስጥ ብዙ ትምህርተችን ይማራል፡፡

34
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

3. የቁጥጥር ተግባር፡- በሥነ ቃል ማህበረሰቡን ሥነ ምግባር ማስተማር ይቻላል ሰዎች ከማህበረሰቡ አስተሳሰብ ውጭ ሲሆኑ በሥነ
ቃል ከማህበራሰቡ ያፈነገጠውን በማስተማር ይመለስበታል፡፡
4. የመቃወም እና ማሞገስ፡- በሥነ ቃል ጥሩ የሰራ ይሞገሳል ያጠፋም ይወቀሳል
ምሳሌ፡- ለምስለኔው ሙክት ለጭቃው ወጠጤ
እንዲህ ሆኘ ነወይ ባገር መቀመጤ/በኀይለስላሴ የተማረሩ
ምንሊክ ተነስቶ ባያነሳ ጋሻ
ግብሩ እንቁላል ነበር ይህን ጊዜ አበሻ /ምንልክን ለማሞገስ/
የሥነ ቃል አይነቶች
 የሥነቃል አይነቶች እንደየማህበረሱ ባህል እና አመለካከት የተለያዩ ናቸው፡፡ ቢሆንም ግን የስነ ቃል አይነቶችን በሁለት መክፈል
ይቻላል እነሱም፡- በግጥማዊ እና በዝርው መልኩ የሚቀርቡ ናቸው፡፡
በግጥም መልኩ የሚቀርቡ የስነቃሎች አይነቶች
1. የክበረ ባዕላት ዘፈኖች
ምሳሌ፡- አየኸው ደመረ መስቀል ሲያበረ /2/
መስቀል አለ ወይ ቆሟል ወይ
አለ እንጂ ለምፅ ያነፃል እንጂ
ያው ቆሟል ድዊ ይፈውሳል
2. የሰርግ ዘፈኖች፡-
ምሳሌ፡- አንቺ ቤላ ቤላ ቤላ ቤላ
ነይ እንሂድ ሀረር ---ሀረር
ብርቱካን እነብላ ----ቤላ
3. ፉከራ፡-
ምሳሌ፡- ፈሪ ጨነቀው ተርበደበደ፣
ጥይት ዘነመ እሳት ወረደ፣
ውረድ እንውረደ ተባባሉና፣
አስደበደቡት አፋፍ ቆሙና፡፡
4. እንካ ሰላምታ፣ልመና፣ሙሾ፣መነባነብ እና እሰጥ አገባ ግጥማዊ ስነቃሎች ናቸው፡፡
5. ምሳሌያዊ ንግግሮች እና እንቆቅልሾች ግጥማዊም ዝርውም ስነቃል ናቸው፡፡
በዝርው መልኩ የሚቀርቡ ስነቃሎች
1. ተረት፡- በሁለት ቡድኖች የሚከወን ሲሆን አንደኛው አድማጭ አንዱ ሰሚ ነው፡፡ ከዚህ ውጭ አብዛኛው ጊዜ ተረት ለህፃናት
የሚቀር ሲሆን በተረቱ አማካኝነት ተረቱን የሚያዳምጡ ሰዎች ሥነ ምግባርን እንዲማሩ ይደረጋል
የተረት ገፀባህሪያት እንስሳት ሰዎች እኩይ መንፈሶች እና ሰናይ መናፍስት ሊሆኑ ይችላሉ፡፡
2. አፈ ታሪክ፡-በተፈጠረ ታሪክ ወይም በአንድ ሁነት ላይ የፈጠራ ታሪክ ተጨምሮበት የሚነገር ነው፡፡ ምሳሌ የአንድ ሰፈር
አሰያየም ወዘተ
3. ሀተታ ተፈጥሮ፡- ሰዎች የተፈጥሮን ሁኔታ በማየት ስለ አፈጣጠራቸው በራሳቸው ግምት መልስ የሚሰጡበት መንገድ ነው
ማለትም ሳይንሳዊ ለሆኑ ጥያቄዎች ኢሳይንሳዊ መልስ የሚሰጡበት ነው፡፡
ምሳሌ፡- በቅሎ ለምን ልጅ አልወለደችም የዝንጀሮ ቂጥ ለምን መላጣ ሆነ

35
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

25.ቅኔ
 በልዩ ልዩ አይነት ግጥም የሚቀርብ ነው፡፡
 ቅኔ ሶስት ክፍሎች አሉት እነሱም ሕብረ ቃል ሰም እና ወርቅ ናቸው
 ሕብረ ቃል፡- ሰም እና ወርቅን በአንድ ላይ የሚይዝ ቃል ወይም ሀረግ ነው፡፡
 ሕብረ ቃል፡- አብዛኛውን ጊዜ የሚገኘው በቅኔው የመጨረሻ ስንኝ ላይ ነው፡፡
ሰም ፡- የቅኔው ቀጥተኛ ፊቺ ነው
ወርቅ፡- የቅኔው ድብቅ ፍቺ ነው
ምሳሌ፡- 1. ሀረገሬ አታልቅሺ እኔ አሳይሻለው
ከጂማ መኖሩን ባይኔ አይቻለው

ሕብረቃል፡- ከጂማ
ሰም፡- ጅማ ከተማውን
ወርቅ፡- ከዳተኛ/ከጂ/
ምሳሌ፡- 2 አልተከልኩ እንኳ ከጓሮዬ
ዱባ ለመከራዬ
ሕብረ ቃል፡- ዱባ ለመከራዬ
ሰም፡- ለችግር የሚሆን ዱባ
ወርቅ፡- መከራ ድንገት ዱብ አለብኝ
ምሳሌ 3 ብሄድ በወለጋ ብሄድ በጎጃም
እንዳንቺ አይነት በቅሎ አይቼ አላውቅም
ሕብረ ቃል፡- በቅሎ
ሰም፡- እንዳንቺ አይነት ቆንጀ ተወልዶ አላየሁም
 ምሳሌ 1 በጥቅሻ ይወድቃል እንኳንስ በጠጠር፡፡

26.አንቀፅ
 አንቀፅ ማለት ተያያዥነት ያላቸው ዓ.ነገሮች ተገጣጥመው ስለ አንድ ፍሬ ሀሳብ ብቻ የሚያቀርቡበት ፅሁፍ ነው፡፡
 የአንቀፅ ባህሪያት
1. አንድነት፡- በአንድ አንቀፅ ውስጥ የሚቀርቡ ሀሳቦች በሙሉ በአንድ ጉዳይ ላይ ብቻ የሚያተኩሩ መሆኑን ያመለክታል፡፡
2. ግጥምጥምነት፡-የሚቀርቡት ሀሳቦች አንድነታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ ሰንሰለታዊ ቁርኝነታቸውና ተጠየቅያዊ ፍሰታቸው የተስተካከለ መሆን
እንዳለበት ያመለክታል፡፡
3. ብቁነት፡- የሀሳባቦቹ ጥልቀትና ብስለት ብቃቱን የጠበቀ መሆን እንዳለበት ያመለክታል፡፡
4. ሀይለቃል፡- የአንቀፁ ዋና ሀሳብን የሚያመለክት ዓ.ነገር ነው፡፡
 የሀይለ ቃል መገኛ እና የአንቀፅ ቅርፅ
ሀ. ሀይለ ቃል መነሻ ላይ ሲገኝ
ሀይለ ቃል
ዝርዘር ዓ.ነገር
ለ. ሀይለ ቃል መጨረሻ ላይ ሲገኝ
ዝርዝራ ዓ.ነገር

36
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

ሀይለ ቃል
ሐ. ሀይለ ቃል መሀከል ላይ ሲገኝ

ዝርዝራ
ሐይለ ቃል
ዝርዝር

መ. ሀይለ ቃል በመነሻም በመድረሰሻም ሲገኝ


ሀይለ ቃል
ዝርዝር

ዝርዝር
ሀይለ ቃል

 ኢ-ልቦለድ ድርሰት አፃፃፍ


1.ርዕስ መምረጥ 2. አስተዋፅኦ መንደፍ
3. መረጃ መሰብሰብ 4. ድርሰት መፃፍ
 የድርሰት ክፍሎች
1. መግቢያ 2. ሀተታ 3. መደምደሚያ ይባላሉ
 የድርሰት አይነቶች
1. ተራኪ ድርሰት፡- ተፈፅመው ያለፉ ነገሮችን የምንተርክበት ድርሰት ነው፡፡ ምሳሌ የአፄ ቴዎድሮስ ታሪክ
2. ገላጭ ድርሰት፡- የአንድን ነገር አሠራር ቅደም ተከተል የሚገልፅ የድርሰት አይነት ነው፡፡ ምሳሌ የቤት አሰራር
3. ስዕላዊ ድርሰት፡- ይሄንን ድርሰት ስናነብ በአእምሮአችን ምስል እንድንከስት የሚያደርገን ሲሆን በተመረጡ እና ምስል ከሳች በሆኑ
ቃላቶች ይፃፋል፡፡
4. አመዛዛኝ ድርሰት፡- ሁለት እና ከዚያ በላይ የሆኑ ነገሮችን በማንሳት እያመዛዘነ እያወዳደረ እያከራከረ የሚያቀርብ ሲሆን በመጨራሻም
አሳማኝ ምክንያት በማቅረብ አንዱን ደግፎ ሌሎችን በመንቀፍ ተደራሲያንን ማሳመን ነው፡፡
 የጥሩ ድርሰት ባህሪያት
 አጭር፣ግልፅ እና ማራኪ ርዕስ ይይዛል
 የተመረጡ፣ወብና ሳቢ ቃላትን ይጠቀማል
 አንድነት፣ግጥምጥምነትና ብርታት ባላቸው አንቀፆች ይገነባል
 ተአማኒነት ባለው ሀሳብ ላይ ይመሰረታል
 ተገቢውን ስርዓተ ነጥብ በተገቢው ቦታ ይጠቀማል፡፡
 ቃለ ጉባኤ
ቃለ ጉባኤ፡- በአንድ ስብሰባ ላይ ከተወያዮች የሚነሱ የተመረጡ ሀሳቦች የሚፃፉበት አጀንዳ ነው፡፡
 የቃለ ጉባኤ አፃፃፍ
1. የስብሰባው ርዕስ ወይም መጠሪያ መፃፍ
ምሳሌ፡- የቅዱስ ዮሴፍ ት/ቤት የስራ አመራር ቦርድ 2 ኛ መደበኛ ስብሰባ
2. ቦታና ጊዜ መፃፍ
ምሳሌ፡- ቀን 8/8/2011 ዓ.ም የስብሰባ ቦታ የት/ቤቱ ር/መምህር ቢሮ ውስጥ

37
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

3. በስብሰባው ላይ የተገኙትን እና ያልተገኙትን አባላት መፃፍ


4. በእለቱ ለመወያያነት የቀረበውን አጀንዳ መፃፍ
 ዋናው ትኩረቱ ተውኔቱ ያስቃል ወይንስ አያስቅም ነው እንጂ ደራሲው የሚያነሳው ሀሳብ ትክክል ነው ወይም ምክንያታዊ ነው ወይ
የሚለው ነገር አይታይም፡፡
ነው፡፡

የሴራ አይነቶች
 ጥብቅ ሴራ፡- ሴራው በተደራሲያን ዘንድ የእውነት እስኪመስል ድረስ ስሜትን በእጅጉ ይይዛል
 ልቅ ሴራ፡- ምክንያትና ውጤቱ ጥብቅ አይደለም በአጠቃላይ ግጭቱ ተደራሲያንን አያሳምንም
 ነጠላ ሴራ፡- የአንድ ሁነት ግጭት ብቻን ያመለክታል/ በአንድ ዘለላ ጉዳይ ላይ ብቻ ያጠነጥናል
ገፀባህሪያት፡-ፀሀፌ ተውኔቱ የሚቀርፃቸው ሆነው ተዋናዮቹ ህያዋን ናቸው፡፡

 ቃለ ተውኔት፡- ገፀባህሪያት የሚግባቡበት ቋንቋ ነው፡፡

ሙዚቃ፡- በተውኔቱ ሊተላለፉ የሚፈለጉ ማንኛውንም አይነት ስሜት የምናጅብበት መንገድ ነው/የተውኔት ማጀቢያ ነው፡፡

 ትዕይንት፡- የገቢር ክፍል ሲሆን የመድረክ እነፃውን፣ የተዋንያንን አልባሳት፣ የመድረኩን ገፅታ ይመለከታል በአጠቃላይ በገፀባህሪያት

መካከል ከቃላት ውጭ የሚፈጠሩትን መግባባቶች በሙሉ ይመለከታል፡፡

መመሪያ አንድ፡- ለሚከተሉት ጥያቄዎች ትክክለኛ መልስ ስጡ

1. --------------- ሥነ-ቃል ከተፈጠረ በኋላ የሚተላለፈው ወይም የሚነገረው በአፍ ነው፡፡


2. -------------- አብዣኛው የሥነቃል ቅርፆች አጭር ናቸው፡፡ ከሁሉም ረጅም እሚባለው ተረት ነው እሱም አንዴ ተነግሮ እዛው
የሚያልቅ ነው፡፡
3. --------------- ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፈው በአፍ እንደመሆኑ መሰረት ከውስጡ የሚረሱ የሚቀሩ ቃላት ወይም
ሀረጋት ይኖራሉ፡፡
4. -----------------ሥነ ቃል ደራሲ አልባ ነው ደራሲው ማህበረሰቡ እንደመሆኑ መጠን ሁሉም በፈለገ ሰዓት እንደፈለገ ይጠቀማል
ምክንያቱም ሥነቃል የወል ሀብት ስለሆነ፡፡
5. ----------------- ሥነቃል ቦታውን እና አጋጣሚው በተፈጠረ ቁጥር እየተደጋገመ ይከናወናል፡፡
6. ---------------- ተፈፅመው ያለፉ ነገሮችን የምንተርክበት ድርሰት ነው፡፡ ምሳሌ የአፄ ቴዎድሮስ ታሪክ
7. ---------------- የአንድን ነገር አሠራር ቅደም ተከተል የሚገልፅ የድርሰት አይነት ነው፡፡ ምሳሌ የቤት አሰራር
8. --------------- ይሄንን ድርሰት ስናነብ በአእምሮአችን ምስል እንድንከስት የሚያደርገን ሲሆን በተመረጡ እና ምስል ከሳች በሆኑ ቃላቶች
ይፃፋል፡፡
9. ---------------- ሁለት እና ከዚያ በላይ የሆኑ ነገሮችን በማንሳት እያመዛዘነ እያወዳደረ እያከራከረ የሚያቀርብ
10. -----------------በልቡለዱ ውስጥ ሊተላለፍ የተፈለገውን አጠቃላ ነገር የሚይዝ ነው፡፡
11. ----------------- በልቦለዱ ውስጥ የሚተላለፈውን ሀሳብ ወክለውየሚንቀሳቀሱ የደራሲው ምናባዊ ፍጡራን ናቸው
12. -------------------- በገፀባህሪያት መካከል የሚፈጠረው ግጭት ከፍ እያለ ሲሄድ እና አለመግባባታቸው ሲከር የሚፈጠር ነገር
ነው፡፡
13. ------------------- በአንድ ልቦለድ ውስጥ ሊተላለፍ የተፈለገው ፍሬ ሀሳብ ወይንም መልዕኩ ምንድን ነው የሚለውን የሚመልስ
ነገር ነው
14. ------------------- በገፀባህሪያት መካከል የሚፈጠር አለመግባባት ነው፡፡
15. --------------------ታሪኩ መቼ እና የት ተፈጠረ የሚለውን ይመልሳል፡፡

38
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሞጁል ለ አስረኛ ክፍል በብንያም ከድር ታህሳስ 2013

መመሪያ ሁለት፡- ለሚከተሉት ጥያቄዎች ትክክለኛ መልስ ስጡ


1. የስነ ቃል ባህሪያትን ጥቀስ
ሀ.------------------------ ለ.------------------------ ሐ.--------------------
መ.----------------------- ሠ.----------------------- ረ.---------------------
2. የስነቃል ተግባር ግለፁ
ሀ.------------------------ ለ.------------------------
ሐ.----------------------- መ.-----------------------
3. የሴራ አይነቶችን ግለፁ
ሀ.------------------------ ለ.------------------------
ሐ.-----------------------
4. የተውኔት አይነቶች ግለፁ
ሀ.------------------------ ለ.------------------------
ሐ.----------------------- መ.-----------------------
5. የድርሰት አይነቶችን ግለፁ
ሀ.------------------------ ለ.------------------------
ሐ.----------------------- መ.-----------------------
6. የሴራ አይነቶችን ግለፁ
ሀ.------------------------ ለ.------------------------
ሐ.----------------------- መ.----------------------

39

You might also like