Professional Documents
Culture Documents
በጎ ፈቃድ መመሪያ
በጎ ፈቃድ መመሪያ
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አሰራር 2013
መመሪያ ቁጥር 1/2013
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አሰራር መመሪያ ቁጥር 1/2013
ማውጫ
ክፍል አንድ.................................................................................................................................. 4
1. ጠቅላላ ድንጋጌ .................................................................................................................................. 4
1.1 አጭር ርዕስ .......................................................................................................................... 4
1.2 ትርጓሜ .......................................................................................................................................... 4
1.3 የተፈፃሚነት ወሰን ................................................................................................................. 8
ክፍል ሁለት ................................................................................................................................ 9
2.1 የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዕቅድ ............................................................................................. 9
2.2 ምዝገባ ................................................................................................................................ 11
2.3 የበጎ ፈቃደኞች ምልመላና መረጣ .......................................................................................... 14
2.3.1 ተቋሙ በጎ ፈቃደኞችን የሚመለምልበት ስርዓት ................................................................ 14
2.4 ግንዛቤ መፍጠር/ Cognition/ ............................................................................................ 15
2.5 ገለፃ / Oreintation / ....................................................................................................... 15
2.6 ስልጠና / Training / ........................................................................................................... 16
2.7 ስምሪት ............................................................................................................................... 17
2.8 የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ክትትል፤ ድጋፍና የምዘና ስርዓት ...................................................... 18
2.8.1 ክትትልና ድጋፍ............................................................................................................... 18
2.8.2 ምዘና .............................................................................................................................. 19
ክፍል ሶስት................................................................................................................................ 21
3.1 የበጎ ፈቃድ መርሆዎች፣ መብትና ግዴታዎች እና ስነ - ምግባር ............................................. 21
3.1.1 የበጎ ፈቃድ መርሆዎች ..................................................................................................... 21
3.1.2 የበጎ ፈቃደኞች መብት...................................................................................................... 22
3.1.3 የበጎ ፈቃደኞች ግዴታ ...................................................................................................... 23
3.2 በጎ ፈቃደኞችን የሚያሳትፉ ተቋማት መብትና ግዴታዎች ................................................... 24
3.2.1 በጎ ፈቃደኞችን የሚያሳትፉ ተቋማት መብት ...................................................................... 24
3.2.2 በጎ ፈቃደኞችን የሚያሳትፉ ተቋማት ግዴታዎች ................................................................ 25
3.3 ስነ ምግባር .......................................................................................................................... 26
3.4 የስነምግባር ጥሰቶች ......................................................................................................... 27
3.5 ይግባኝ ............................................................................................................................ 30
ክፍል አራት ............................................................................................................................... 31
ክፍል አንድ
1. ጠቅላላ ድንጋጌ
1.1 አጭር ርዕስ
ይህ መመሪያ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አሰራርን በተደራጀና
ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመምራት የተዘጋጀ መመሪያ ቁጥር 1/2013 ዓ.ም; ተብሎ
ሊጠቀስ ይችላል፡፡
1.2 ትርጓሜ
የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ መመሪያ ውስጥ፡-
የፆታ አገላለጽ
ክፍል ሁለት
2. የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ አመራር ስርዓት
2.1 የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዕቅድ
2.1.1 በቢሮው የሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች በሙሉ የታቀዱ
መሆን ይኖርባቸዋል
2.1.2 ቢሮው የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶችን ሲያቅድ የታላሚ ቡድኖችን
መሰረት በማድረግ ከዕድሜ አንፃር /የህፃናት፣ የወጣቶች፣ የጎልማሶችና
የጡረተኞች/ ፣ ከግዜ አንፃር የአጭር የመካከለኛ እና የረዥም ግዜ የበጎ
ፈቃድ አገልግሎቶች፣ ከአገልግሎት ወሰን አንፃር/ አካባቢያዊ፣
ክልላዊ፣አህጉራዊና ዓለማአቀፋዊ/፣ ከሙያዊ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት
አንፃር፣ አገልግሎቱን መስጠት ከሚፈልጉ በጎ ፈቃደኞች አንፃር/
በግል፣በቡድን፣በቤተሰብ / ወ.ዘ.ተ በማቀድ ወደ ተግባር ሊያስገባ ይችላል
2.1.3 በተራ ቁጥር 2.1.2 የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ የአጭር ግዜ
የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች የቆይታ ግዜ እስከ 4 ወር የሚፈጅ ሲሆን ፣
የመካከለኛ ግዜ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ከ6 ወር እስከ 8 ወር የሚቆዩ
እንዲሁም 1 አመትና ከዛ በላይ የሚቆዩ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች
የረዥም ግዜ አገልግሎቶች በመባል የሚታቀዱ ይሆናል፡፡
2.1.4 በቢሮው የሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች ዕቅድ የከተማው
ህብረተሰብ ያለበትን የአገልግሎት ክፍተት መነሻ በማድረግ በቢሮው በራሱ
የሚታቀዱ እንዳሉ ሁሉ ከማንኛውም በጎ ፈቃድ አገልግሎት መስጠት
ከሚፈልግ በጎ ፈቃደኛ ግለሰብ፣ መደበኛና መደበኛ ያልሆነ ማህበር፣ ተቋም
ወ.ዘ.ተ በሚቀርቡና ጠቀሜታቸው በተረጋገጠ ዝክረ ተግባሮችም
የሚከናወን ይሆናል፡፡
2.1.5 በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዕቅድ ዝግጅት ወቅት የበጎ ፈቃድ
አገልግሎት ስራው ለየትኛው የልማት አጀንዳ ስኬት አስፈላጊ እንደሆነ
ከሚመለከተው አጋር/ባለድርሻ አካል ጋር በመሆን በጥናት የተለየ እና
ማህበረሰባዊ ፋይዳው የጎላ መሆኑ መረጋገጥ ይጠበቅበታል
[Type the company name]| ክፍል ሁለት 9
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አሰራር 2013
መመሪያ ቁጥር 1/2013
2.7 ስምሪት
2.7.1 የበጎ ፈቃደኞች የስራ ስምሪት ሂደት የሚከናወነው በጎ ፈቃደኞች
እንዳላቸው ምርጫ፣ ችሎታና ልምድ ብቻ ነው፡፡
2.7.2 በስራ ስምሪት ላይ እያለ በጎ ፈቃደኛው ከአቅም በላይ የሆነ እክል
ቢገጥመው ከስራ መቅረቱን ለቅርብ ሃላፊው የማሳወቅ ግዴታ አለበት፡፡
2.7.3 ማንኛውም በጎ ፈቃደኛ በስራ ስምሪት ወቅት በዚህ መመሪያ በመደበኛነት
የፀደቀውን የተቋሙን የስራ መለያ ልብስ መልበስና እና የበጎ ፈቃደኝነት
መታወቂያ መያዝ ግዴታ አለበት፡፡
2.7.4 በጎ ፈቃደኞች ወደ ስራ ሲሰማሩ እንደአስፈላጊነቱ የስራ ላይ ግብአቶች
ቁሳቁሶች ሊሟሉላቸው ይገባል፡፡
2.7.5 ማንኛውም በጎ ፈቃደኛ በስራ ስምሪት ወቅት በታማኝነትና በቅንነት
የማገልገል ግዴታ አለበት፡፡
2.7.6 በስራ ስምሪት ወቅት ሁሉም በጎ ፈቃደኞች ከተቋሙ የተሰጣቸውን የስራ
መመሪያ/ የስራ መዘርዝር ማክበርና መተግበር ይጠበቅባቸዋል፡፡
2.7.7 በጎ ፈቃደኞች የስራ ስምሪት ሲሰጣቸው የሚሰሩበት የስራ መደብ የስራ
ዝርዝር፣በጎ ፈቃደኛው ያለው የሥራ ሃላፊነት፣የተመደቡበት
መደብ፣የቅርብ ተቆጣጣሪውን ወ.ዘ.ተ ማክበርና መተግበር
ይጠበቅባቸዋል፡፡
[Type the company name]| 2.8 የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ክትትል፤ ድጋፍና የምዘና ስርዓት 18
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አሰራር 2013
መመሪያ ቁጥር 1/2013
2.8.2 ምዘና
2.8.2.1 ቢሮው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ፕሮግራሞችን እንቅስቃሴ፣ ባህሪ
ዉጤታማነትና ፋይዳ በቂ መረጃ በመሰብሰብና በመተንተን በጥልቀት
የሚገመገምበት የምዘና ስረዓት ያካሄዳል፡፡
2.8.2.2 ቢሮው በአጠቃላይ በምዘና ስርዓት በጎ ፈቃደኞች በተለያዩ ፕሮግራሞች
ታቅፈዉ ባከናወኗቸዉ ተግባራት ለህብረተሰቡ ብሎም ለሃገር ያለዉ
ጠቀሜታ ወይም ፋይዳ ይለካል፡፡
ክፍል ሶስት
3.1 የበጎ ፈቃድ መርሆዎች፣ መብትና ግዴታዎች እና ስነ - ምግባር
3.1.1 የበጎ ፈቃድ መርሆዎች
በከተማችን አዲስ አበባ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚሰጡ ግለሰቦች፣ማህበራት እና ተቋማት
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በሚሰጡበት ወቅት ሊያሟሏቸዉ የሚገቡ ዓለም ዓቀፍ ፣አካባቢያዊ
ወጎችና ባህሎችና እሴቶችን መጠበቅ የሚያስችሉ የበጎ ፈቃድ መርሆዎች፣ መብትና
ግዴታዎች እና ስነ - ምግባር በዚህ ምዕራፍ ተብራርተዉ ተደንግጓል፡፡
3.3 ስነ ምግባር
ቢሮው በጎ ፈቃደኞች በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ ላይ ሲሰማሩ ሊከተሏቸው
የሚገቡ የስነምግባር ደንቦች እንደሚከተለው አዘጋጅተዋል ተዘርዝሯል፡፡
3.3.1 የቢሮው በጎ ፈቃደኞች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በሚሰጡበት ወቅት የተሰጣቸውን
ኃላፊነት ለግል ጥቅማቸው ወይም ለዘመዶቻቸው ጥቅም ወይም ለጓደኞቻቸው
ጥቅም በማዋልና ሥልጣናቸውን ያለአግባብ መጠቀም የለባቸውም፤
3.3.2 የቢሮውን ሀብት፣ መረጃ ወይም የቢሮውን በጎ ፈቃደኝነታቸውን ለሌላ ሶስተኛ
ወገን ጥቅም ማዋል አይኖርባቸውም፤
3.3.3 ለስራ የተሰጣቸውን ማንኛውም ዓይነት የቢሮው ንብረት/ቁሳቁሶች ለቢሮው የበጎ
ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ብቻ መጠቀም አለባቸው፤
3.3.4 በኃላፊነታቸው ምክንያት ያወቁትን የቢሮውን/የሰራተኞችን/የሌሎች በጎ ፈቃደኞችን
መረጃዎች ሚስጥራዊነት የመጠበቅ ኃላፊነት አለባቸው፤
3.3.5 የበጎ ፈቃድ ስራቸውን በሚያከናውኑበት ወቅት ለስርዓተ-ፆታ ጉዳዮች ትኩረት
መስጠትና በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከማንኛውም ዓይነት ፆታዊ ትንኮሳ ድርጊቶች
ከመፈፀም መጠንቀቅ ይኖርባቸዋል፤
3.3.6 ለህብረተሰቡና ለስራው ተስማሚ የሆነ የአለባበስ ሥርዓት በመጠበቅ በቢሮው
አጋሮችና በህብረተሰቡ ዘንድ መልካም ገጽታ መገንባት ይጠበቅባቸዋል፤
3.3.7 ከቢሮው ጋር በሚሰሩበት ወቅት ከፍተኛ የተአማኒነትና ኃላፊነት መንፈስ
ሊኖራቸው ይገባል፤
3.3.8 በቢሮው በሚሰሩበት ጊዜ አለምዓቀፉን እንዲሁም የተቋሙን የበጎ ፈቃደኞች
እንቅስቃሴና መርሆዎቹን ወክለው እንደሆነ ማስታወስ አለባቸው፤
3.3.9 ማንኛውንም ተግባር ሲያከናውኑ በቢሮው የአሰራር ደንቦችና መርሆች መሰረት
መሆኑን ማረጋገጥ አለባቸው፤
3.3.10 ምንግዜም ቢሆን የሌሎች ሰዎችን ፍላጎት በንቃት መጠበቅ አለባቸው፤
3.3.11 የቢሮውን ዓርማ አጠቃቀም ደንብ ማክበርና ምንጊዜም ቢሆን ያለአግባብ የሆነ
አጠቃቀምን መከላከል አለባቸው፤
ለ. ለዉይይት መጠራትን
ሐ. መመርመርን ያካትታል
ሀ. ግልግል
ለ. ሽምግልና
ሐ. ሙግት/ክርክር
ሀ. የቃል ማስጠንቀቂያ
መ. እግድ
ረ. ስንብትን ያካትታል
3.5 ይግባኝ
3.5.1 ማንኛውም የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለመስጠት ከቢሮው ጋር ዉል ወስዶ እየሰራ
ላለ አካል ለተወሰደበት እርምጃ ከተወሰደበት ዕለት አንስቶ በሚኖሩ አምስት የስራ
ቀናት ለቢሮው ከፍተኛ የማኔጅመንት ኮሚቴ ይግባኙን በጽሁፍ ማቅረብ
ይኖርበታል፡፡ይግባኙም የሚመራዉ በቢሮ ሃላፊው ሲሆን ዉሳኔዉ የመጨረሻ ነዉ
ነገር ግን የይግባኙ ሰሚ አመራር የስነ ምግባር ጥሰት ዕርምጃ ዉሣኔ ካሳለፉት
ከፍትኛ የማናኔጅመነት ኮሚቴዎች ውጪ መሆን አለበት፡፡
3.5.2 በዚህ መመሪያ በቢሮው አሰራር እና አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ላይ ለሚቀርቡ
ቅሬታዎችና አቤቱታዎች የቅሬታ አቀራረብ፣ ቅሬታን ማጣራት እና ለቀረቡ
ቅሬታዎችና አቤቱታዎች ውሳኔ አሰጣጥ ሂደት የሚከናወነው ቢሮው ባለው
መደበኛ የቅሬታ አቀራረብና አፈታት ስርዓት ይሆናል፡፡
ክፍል አራት
4 የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ግብዓት አቅርቦት
4.1 የበጎ ፈቃደኞች የስራ መለያ
4.1.1 በቢሮው የሚሰማሩ መደበኛ በጎ ፈቃደኞች በስራ ላይ በሚሆኑበት ጊዜ
4.1.2 ቢሮው ከላይ በተመረጠው የቢሮው የበጎ ፈቃደኞች አልባሳት መለያ ቀለምና
የጨርቅ አይነት በመጠቀም የመለያ አልባሳቱ እንደየ በጎ ፈቃድ ፕሮግራሞቹ
ምቹነት በሰደርያ፣ በሽርጥ፣ በሸሚዝ፣ በቲ - ሸርት፣ በቱታ፣ በኮፊያ መልክ
የተለያየ የአልባሳት ዲዛይኖችን ይጠቀማል፡፡
4.1.3 የቢሮው የበጎ ፈቃደኞች የስራ ላይ መለያ አልባሳት ግዥና ስርጭት ማከናወን
የሚቻለው በቢሮ ደረጃ ብቻ ነው፡፡
4.1.4 በቢሮ ደረጃ የተዘጋጁ የበጎ ፈቃደኞች የስራ ላይ አልባሳት ስርጭት የሚከናወነው
በቢሮ፣ በክፍለ ከተማና በወረዳ ደረጃ በመደበኛ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት
ለመሰማራት በተመዘገቡና በመረጃ ቋት ውስጥ በተደራጀ የበጎ ፈቃደኞች መረጃ ላይ
ብቻ የተመሰረተ ይሆናል፡፡
4.1.5 የበጎ ፈቃደኞች የሥራ ላይ አልባሳት በየደረጃው ላለ አስፈፃሚ አካል ስርጭት
የሚከናወነው በመንግስት የግብዓት ወጪና ገቢ ስረዓት አፈፃፀም ይሆናል፡፡
4.1.6 በተራ ቁጥር 4.1.6 የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ በክፍለ ከተማና በወረዳ ደረጃ
ለበጎ ፈቃደኞች የሚሰጥ የስራ መለያ አልባሳት ሲኖር ክፍለ ከተማው/ወረዳው
[Type the company name]| ከሃገር ውጪ/ ከከተማ ውጪ ለሚደረጉ ጉዞዎች የወጪ መተኪያ 36
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አሰራር 2013
መመሪያ ቁጥር 1/2013
[Type the company name]| 4.5.1. የበጎ ፈቃደኛ የጤናና የህይወት መድህን ዋስትና ሽፋን ክፍያ 38
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አሰራር 2013
መመሪያ ቁጥር 1/2013
ክፍል አምስት
5.1 የእዉቅና፣ ማበረታቻ እና ሽልማት አሰጣጥ ስርዓት
5.1.1 ቢሮው በበጎ ፈቃድ ተግባር ላይ ለተሰማሩ በጎ ፈቃደኞች የዕውቅና፣ ማበረታቻ እና
ሽልማት ይሰጣል፡፡
5.1.2 ቢሮው የበጎ ፈቃደኞች ዕውቅና፣ ማበረታቻ እና ሽልማት የሚሰጠው በጎ ፈቃደኞቹ
በምዝገባ ወቅት የሞሉት ፎርም ላይ ባሰፈሩት የዕውቅና አይነት ይሆናል፡፡
5.1.3 ቢሮው የዕውቅና ፣ማበረታቻ እና ሽልማት ስርዓት ሲፈፅም የሚከተላቸው
የዕውቅና አሰጣጥ ደረጃዎች በጀማሪ፣ በመካከለኛ እና ከፍተኛ ተብለው ይለያሉ፡፡
5.1.4 ቢሮው የዕውቅና ፣ማበረታቻ እና ሽልማት ስረዓት ሲፈፅም የሚከተላቸው
የዕውቅናና ሽልማት አይነቶች ዕለታዊ፣ መካከለኛና፣ ዋና ተብለው ይለያሉ፡፡
5.1.5 ቢሮው ለሁሉም በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለተሳተፉ በጎ ፈቃደኞች ዕውቅና ይሰጣል
5.1.6 ቢሮው በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳትፈው የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ላበረከቱ በጎ
ፈቃደኞች ማበረታቻ ይሰጣል፡፡
5.1.7 ቢሮው በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳትፈው የጎላ/የተለየ አስተዋፅኦ ላበረከቱ በጎ
ፈቃደኞች ሽልማት ይሰጣል፡፡
5.1.8 ቢሮው ለበጎ ፈቃደኞች የሚሰጠው ማበረታቻና ሽልማት ደረጃዎች የሚወሰነው በጎ
ፈቃደኞቹ በአገልግሎት ወቅት ባስመዘገቡት የስራ ሰዓት፣ የሃብት፣ የጉልበት፣
የሙያ/ዕውቀት መጠን፣ የአገልግሎት ቆይታ ዘመን እና በስራ ላይ በነበራቸው
ስነ-ምግባር/ዲስፕሊን መሰረት ይሆናል፡፡
5.1.9 ቢሮው ለበጎ ፈቃደኞች የሚሰጠው ዕውቅና ማበረታቻ እና ሽልማት ይኖራቸዋል
ተብሎ የተለዩ ደረጃዎች እና አይነቶች እንደ በጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ባህሪ አንደኛው
ከሌላኛው የሚዋረሱት ደረጃና አይነቶች ይኖራል፡፡
5.1.10 የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዕውቅና የሚሰጠው በየዕለቱ/በየወቅቱ ይሆናል ፤
5.1.11 ማበረታቻ የሚሰጠው በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ ወቅት እና ፕሮግራም
ማጠቃለያ ላይ ነው፡፡
5.1.12 ሽልማት የሚሰጠው በዓመት አንድ ግዜ በቢሮ ደረጃ በሚዘጋጅ የዕውቅና
ማበረታቻ እና ሽልማት መርሃ ግብር ነው፡፡
[Type the company name]| ክፍል አምስት 39
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አሰራር 2013
መመሪያ ቁጥር 1/2013
መለጠፍ/ማሳተም/ማሰራጨት
ክፍል ስድስት
6. ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
6.1 ትስስራዊ የተግባር አፈጻጸም አግባቦት
6.1.1 ለጋሽ በጎ ፈቃደኛ ፣ተቋም እና አስተባባሪ የመመሪያዉ
አተገባበር
6.1.1.1 የተቋሙን አጠቃላይ ህልዉና በማያናጋ ሁኔታ
በሁለትዮሽ፣ሶስትዮሽ እና ከዚያም በላይ በሆነ ትስስራዊ
የአጋርነት ዉል ተፈራርሞ ወደ ተግባር ሲገባ የለጋሽ አካሄድ
ልግስናዉን የሚቀበለዉ ተቋም ዉስጣዊ አሰራርና የአሰራር
አፈጻጸም መመሪያን አክብሮ መስራት ይጠበቅበታል፡፡
6.1.1.2 ለጋሽ የበጎ ፈቃደኛ ዓለም አቀፍና ሃገር በቀል ተቋም የበጎ
ፈቋድ ልግስና ተቀባይ ተቋም፣ማህበር ኔትዎርክ፣ፎረም፣ቡድን
ወይም ግለሰብን የአእምሮ ንብረት፣የህጋዊ ተደራሽነት
ወሰን፣የተቋም መመሪያ ፣ደንብና ስርዓት ብሎም የተቋሙ
የዉስጥ አሰራር፣የስነ ምግባር አፈጻጸም መመሪያና አሰራር
አክብሮ መንቀሳቀስ ይጠበቅበታል፡፡
6.1.1.3 የአዲስ አበባ ወጣቶችና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ቢሮ
በየደረጀዉ ለአንድ ዓላማ በሚያሰልፋቸዉና ፣በትብብር
እንዲሁም በጋራ አብሮ ለመስራት እሺታዉን ያሳያቸዉ
ወይም በአስተባባሪነት አብሮ ለመስራት ዉል የተዋዋላቸዉን
የበጎ ፈቃድ ቡድኖች ፣ተቋማት እና አጋሮች ላይ ህጋዊ
አሰራራቸዉንና የተቋቋሙበትን ዓላማ በጠበቀና ባከበረ ብሎም
በማይቀረን አሰራር በትብብር መንፈስና በአሳላጭነት
(አስተባባሪነት) ብቻ ሊሰራ የገደዳል፡፡
6.1.1.4 እንደየአስፈላጊነቱ በዚህ መመሪያ ክፍል ሶስት በክትትልና
ድጋፍ የተቀረፀና የፀደቁ ቅፃቅፆች ለአሰራርና ለአፈፃፀም
[Type the company name]| 6.1.1 ለጋሽ በጎ ፈቃደኛ ፣ተቋም እና አስተባባሪ የመመሪያዉ አተገባበር 47