You are on page 1of 2

ለኢስላም እና ለሙስሊሙ ማን ጠበቃ

ይሁን?
በአለም ላይ የሙስሊሙ ቁጥር ከየትኛውም የሃይማኖት ተከታይ የበለጠ መሆኑ የማይታበል ሀቅ ነው።

ነገር ግን ስንቶች ናቸው ራሳቸውን የኢስላም ዘብ አድርገው የሚያስቡት ብለን ስንጠይቅ ጥቂቶች ሆነው
እናገኛለን።

ልብ ብለን ካጤንን አብዛኛውን በአለም ላይ የተከሰቱ ለውጦች እና ተሀድሶዎች_ ሃይማኖታዊ ሆኑም


አልሆኑም_ የተመሩት በጥቂቶች ነበሩ። ይህ ማለት ብዙሀኑ ማህበረሰብ ለውጥን ተቀብሎ የሚያራምድ እንጅ
የለውጥ ፈጣሪ አይደለም ማለት ነው ነጮችም እንዲህ አይነቱን ነው (the law of few) የሚሉት።

ታዲያ እኛ ሙስሊሞች ለለውጥ መጣር ያለብን ሁላችንም ወይስ የለውጡን ነገር ለጥቂቶች እንተወው? ማን
ለኢስላም ጠበቃ ይሁን ? ስልም ይህን ማለቴ ነው ።

የተለያዩ እስላማዊ የታሪክ ማህደሮችን ስናገላብጥ የሙስሊሙ መሪዎች፣ ኡለማዎች...ማን ለኢስላም ጠበቃ
ይሁን? ሲባል

ሁሉም እኔ እኔ ነበር መልሳቸው እስኪ ጥቂት ምሳሌዎችን እንመልከት፦

-ሱለይማን አዳራኒ የተባሉ ታላቅ አሊም እንዲህ ይሉ ነበር፦ “ሰዎች ሁሉ ሃቅን (ኢስላምን)ቢተዉት እና
ብቻየን ብቀር ስለኢስላም እውነተኛነት ሳልጠራጠር ስራየን በቀጠልኩ ነበር! “ ብለዋል።

-በ ታላቁ ከሊፋ ዑመር ቢን አልኸጧብ- አላህ ስራችውን ይውደድላችው- ዘመን አመረማድ(‫)عام الرماد‬
እየተባለ የሚታወቅ ትልቅ ድርቅ የደረሰበት አመት ነበር የኡመርን ጭንቀት ያስተዋሉ ጓደኞቻቸው እንዲህ
ብለው ነበር : “ አላህ ይህን ድርቅ ባያነሳልን ኖሮ ኡመር በጭንቀት ይሞታሉ ብለን ሰግተን ነበር!”

-ከለታት አንድ ቀን ኡመር - አላህ ስራቸውን ይውደድላቸው- ቁጭ ብለው ያንቀላፉ ነበር ጓደኞቻቸውም :
ምነው ለምን አረፍ አይሉም? ሲሏችው “ ቀን ከተኛሁ የህዝቦቼን ሀቅ፣ ማታ ከተኛሁ ደሞ የገታዬን
ሃቅ(ኢባዳ) ላጎድል ነው! ” ብለው መለሱ።

-ኢማዱዲን ማህሙድ አዘንኪ ታላቅ ሙጃሂድ እና አላህን የሚፈራ ታላቅ የሙስሊሞች መሪ ነበር ኢብኑል
አሲር የተባሉ የታሪክ ጸሃፊ ስለሳቸው እንዲህ ብለው ነበር ፦ “ ፈሪሀ አላህ እና በፍትህ ኡማውን ያስተዳደረ
መሪ ከኡመር አ/አዚዝ በኋላ እንደ ማህሙድ ዘንኪ አላየሁም! ” በማለት መስክረውለታል ።

ከለታት አንድ ቀን የመስቀል ጦር አራማጆች ኢማዱዲን ያስተዳድራቸው ከነበሩት ግዛቶች አንደኛውን


ይከባሉ ኢማዱዲን ተጨንቆ ተጠቦ በትካዜ ተውጦ ፈገግታ ሳይቀር ርቆት ነበር ለምን አይስቁም ሲባሉ ፦ “
ሙስሊሞች በፈረንጀች ተከበው እያለ ፈገግ ብዬ አላህ እኔን ማየቱ ያሳፍረኛል!” ነበር ያሉት።

-ኡወይስ አልቀርኒ ማታ ማታ የተራበውን ካበሉ የታረዘውን ካለበሱ በኃላ እንዲህ ይሉ ነበር ፦ “ ጌታዬ ሆይ
በረሃብ ወይም በእርዛት ምክንያት አንድ ሙስሊም ቢሞት ተጠያቂ አታድርገኝ!”

ይህ እንግዲ ከብዙው ጥቂቱ ነው ታሪክም ነው ታሪክ ደሞ እራሱን ይደግማል ሲባል ነው የምናውቀው ታድያ
እኛ ሙስሊሞች ታሪክን መድገም ለምን ተሳነን? ወይስ አባባሉ ነው የተሳሳተው? ።
እኛ ሙስሊሞች ምን ያህል ለኢስላም እየተጨነቅን ነው? አንድ ቀን የኡማው ጉዳይ አስጨንቆን ራሳችንን
አሞን ያውቃል!?

ለኢስላም ምን ሰርተናል? ምንስ ለመስራት አስበናል? ማንንስ እየጠበቅን ነው? በተለይ እኛ ወጣቶች አላህ
በተለያዩ ዘርፎች የሰጠንን ተሰጥኦና ዝንባሌ ዲናችንን ለመርዳት እናውል እያልኩ እስላማዊ ጥሪየን
አቀርባለሁ።

ድል የእውነተኞች ናት!

You might also like