Professional Documents
Culture Documents
ሰላማዊ ሰልፍ ብዥታዎቹና መልሶቹ
ሰላማዊ ሰልፍ ብዥታዎቹና መልሶቹ
ማውጫ
ብዥታ አንድ ገፅ
ገፅ
ብዥታ ሁለት
ብዥታ ሶስት ገፅ
ገፅ
ብዥታ አራት
ገፅ
ብዥታ አምስት
ብዥታ ስድስት ገፅ
ገፅ
ብዥታ ስምንት
ብዥታ ዘጠኝ ገፅ
ብዥታ አስር ገፅ
ብዥታ አስራ አንድ ገፅ
ብዥታ አስራ ሁለት ገፅ
ገፅ
ብዥታ አስራ ሶስት
ብዥታ አስራ አራት ገፅ
ብዥታ አስራ አምስት ገፅ
ብዥታ አራት
ኢብን ዓባስ - ረዲዬሏሁ ዓንሁማ - የሚከተለውን ተናግሯል፡-
إنما سعى رسول هللا ﷺ ورمل بالبيت ليري:"عن ابن عباس رضي الله عنهما قال
“المشركين قوته
“ረሡል ﷺበከዕባ (ዙርያ) የገሰገሱት እና ሶምሶማ የሮጡት ሀይላቸውን
ለአጋሪዎች ለማሳየት ነው፡፡” ቡኻሪ፡ ሙስሊም፡
“ይህ ምክንያት የተወገደ ቢሆንም ፤ እስከ ትንሳኤ ቀን ድረስ በረሡል ﷺ ተከታዮች
ላይ ሶምሶማው የኢስላም ህግ ሆኖ ይቀጥላል፡፡”
(ሸርሁ ሶሂህ አል ቡኻሪ ሊብኒ በጧል፡ )
(ሲልሲለቱ አልአሓዲሲ ሶሂሃቲ፡ )
ብዥታ አምስት
አቡዳውድ በዘገቡት ሐዲስ ፡ “ኢያስ ብን ዓብዲላህ ብን አቢ ዙባብ የአላህ
መልክተኛ “ ﷺየአላህ ሴት ባሮችን አትምቱ” አሉ ፤ ዑመር ወደረሡል ﷺሄዱና ፡
“ሴቶች በባሎቻቸው ላይ ተዳፈሩ እኮ!” አሏቸው ፤ ከዚያም ባሎች ሚስቶቻቸውን
እንዲገርፉ ፈቃድ ሰጡ፤ ከዚያ በኋላ ባሎቻቸው ያደረሱባቸውን በደል አቤቱታ
ለማቅረብ በርካታ ሴቶች በረሡል ﷺቤተሰቦች ዙሪያ ተሰባሰቡ፤ ከዚያም ነብዩ ﷺ
“በረሡል ቤት ዙሪያ በርካታ ሴቶች ስለባሎቻቸው አቤቱታ ለማቅረብ ተሰባሰቡ ፤ እነዚህ
ባሎች ምርጦች አይደሉም፡፡”) በማለት ተናገሩ፡፡ አቡዳውድ፡
ስለዚህ ይህ ሐዲስ ሰዎች መብታቸውን ለመጠየቅ ወይም የደረሰባቸው በደል
ከእነርሱ ላይ እንዲነሳ በይፋ ወይም በአደባባይ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ እንደሚቻል
ማስረጃ ነው የሚል ብዥታ ቢቀርብ፡
መልስ፡ በዚህ ሐዲስ ውስጥ ሰላማዊ ሰልፍን የሚደግፍ ሐሳብ ምንም የለበትም፤
ይልቁንም ሰዎች አቤቱታ ካላቸው ሸሪዓዊ መንገድን ተጠቅመው የሙስሊሞችን መሪ
በቀጥታ ማናገር እንደሚገባ ነው የሚያስረዳው፡፡
ብዥታ ስድስት
አቡዳውድ በዘገቡት ሐዲስ፡ አቡሁረይራ 4 የሚከተለውን ሐዲስ አስተላልፈዋል፡-
(ስለጎረቤቱ ስሞታ ለማቅረብ አንድ ግለሰብ ወደረሡል ﷺሄደ ፤ “ወደቤትህ
ሂድ ትዕግስት አድርግ” በማለት ረሡል ﷺመከሩት ፤ ሁለት ጊዜ ወይም ሶስት ጊዜ
ወደረሡል ﷺተመላለሰ፡ አሁንም “ወደቤትህ ሂድና እቃህን በሙሉ አውጥተህ
መንገድ ላይ አድርገው” አሉት ፤ ከዚያም እቃውን በሙሉ አውጥቶ ህዝብ
ከሚያልፍበት አውራ ጎዳና ላይ አደረገው፤ ከዚያም ሰዎች ጥያቄ ማቅረብ ጀመሩ፤
እርሱም ያለውን እውነታ ነገራቸው፤ ከዚያ በኋላ አላፊ አግዳሚው ሁሉ ጎረቤቱን
መራገም ጀመረ ፤ አላህ የሚሰራውን ሰራ ፤ ከዚያም ጎረቤቱ ወደርሱ መጣና ፤
“እባክህ ወደቤትህ ተመለስ ፤ ከዚህ በኋላ ከእኔ ላይ የምትጠላው ነገር አታያም፡፡
አለው፡፡ አቡዳውድ፡
“ነዞራቱ ሸርዒየቲ ፊ ወሳኢሊ ተዕቢሪል አስሊየቲ” በሚል ፕሮግራም ላይ ዶ/ር ሱዑድ ፈኒሳን የሰጠውን ፈትዋ ይመልከቱ
መልስ፡ ይህ ሐዲስ ሰላማዊ ሰልፍን በቅርብም ይሁን በሩቅ የሚያስረዳ መረጃ ሊሆን
ፍጹም አይችልም ፤ “ሙዟሀራ” ወይም ሰላማዊ ሰልፍ የሚለው ቃል የት ላይ ነው
ያለው?
ሸይኽ ረቢዕ አልመድኸሊ - ረሂመሁሏህ - የሚከተለውን ተናግረዋል፡-
(በሐዲሱ የተመለከትነው የሰዎች መሰባሰብ ከዚህ በፊት እንዳየነው ልክ
በመሪው ላይ ተቀናጅተው አድማ እንደሚያደርጉ ሰዎች አይነት ስብስብ አይደለም ፤
ጉዳዩ ግለሰቡ በሚያስደንቅ ሁኔታ መንገድ ላይ ተቀመጠ፤ ሰዎች ወደስራቸው
ወጠዋል፤ አንድ ሰው ይመጣና ይህን አስገራሚ ትዕይንት ይመለከታል ፤ ሁለተኛው
ሶስተኛው እያለ ቁጥራቸው እየበዛ ይሄዳል፤ ከዚያ በኋላ በዚህ ጎረቤት ድርጊት ሰዎች
ተቃውሟቸውን ያሰማሉ፤ ስለዚህ አሁን ባወሳንልህ መልኩ የተደረገው መሰባሰብ
ምንም ከሰላማዊ ሰልፍ ጋር ግንኙነት የሌለው መሆኑን ይጠቁማል፤ ምክንያቱም
የሰላማዊ ሰልፍ አይነት ግብ እና አላማ የለውም፤ ስለዚህ አንድን ቃል ከተቀመጠበት
ቦታ ከማጣመም በአላህ እንጠበቃለን፡፡)
ሸይኻችን አብዱልሙህሲን አልዓባድ - ሀፊዞሁሏህ - የሚከተለውን ተናግረዋል፡
(ይህ ሐዲስ አዲስ ለተፈጠረው ሰላማዊ ሰልፍ መፈቀድ ምንም አይነት መረጃ ሊሆን
አይችልም፡፡ ረሡል ﷺእቃውን እንዲያወጣ የፈቀዱለት ግለሰብ ሶሃባ ነው፤ ሶሃቦች
ደግሞ እውነተኞች ናቸው፤ ከእነርሱ በኋላ ለመጣ ሰው ይህ አቅጣጫ የሚሰጥ
አይደለም ፤ ምክንያቱም ይህን አይነት መሰል የሞገተ ሁሉ እውነተኛ ይሆናል ማለት
አይደለም ፤ እንዴውም ነገሮችን የሚያበላሽ ጎረቤቱን የሚያሰቃይ ሊሆን ይችላል፡፡)
ብዥታ ሰባት
ዶክተር ሃቲም አልዓውንይ የሚከተለውን ተናግሯል የሚል ብዥታ ቢቀርብ፡
(አልዓዋሲሙ ሚነልቀዋሲሚ ፊትህቂቂ መዋቂፉ ሶሃበቲ በዕደ ወፋቲ ነብይ ﷺ ሊአቢ በክር ብን አልዓረቢ ገፅ/155)
ብዥታ ዘጠኝ
ሰላማዊ ሰልፍ አሁን ላለንበት ዘመን ወደመልካም ለማዘዝ ከመጥፎ ለመከልከል እና
ዳዕዋ ለማድረግ ምቹ የሆነ መንገድ ነው የሚል ብዥታ ቢቀርብ፡
መልስ፡- ሸይኽ ሷሊህ ብን ገስወን - ረሂመሁሏህ - ፡ (በመልካም ማዘዝ፣ ከመጥፎ
መከልከል እና ዳዕዋ ማድረግ ከአላህ ዲን መሰረቶች ናቸው፡፡
ነገር ግን አላህ የሚከተለውን ተናግሯል፡
َ ت َوتَ َوا
ص ْوا ِ صا ِل َحا َ سانَ لَ ِفي ُخ ْس ٍر۞ ِإ َّال الَّذِينَ آ َمنُوا َو
َّ َ ِملُوا ال ِ ْ ص ِر۞ ِإ َّن
َ اْلن ْ ﴿ َو ْال َع
صب ِْرَّ ص ْوا ِبالَ ق َوتَ َواِ ِب ْال َح
“በጊዜያቱ እምላለሁ፤ ሰው ሁሉ በእርግጥ በከሳራ ውስጥ ነው፤ እነዚያ
ያመኑትና መልካሞችን የሰሩት ፣ በእውነትም አደራ የተባባሉት፣ በመታገስም
አደራ የተባባሉት ብቻ ሲቀሩ፡፡” ዓስር ፡
(አፍ የሚያዘጋ የሆነው መልስ ደግሞ የሚከተለው ነው፡ የካፊር አገር ስርዓት
መፍቀዱ ማስረጃ ሊሆን በፍጹም አይችልም ፤ ምክንያቱም የሰው ሰራሽ ህግ ነው ፤
እኛ ደግሞ በሸሪዓ ህግ ሀራም እናደርጋታለን፡፡)
(ሁክሙል ሙዛሃራቲ በሚል ዩቲውብ ላይ ሸይኽ ዓብዱልዓዚዝ ፈውዛን የተናገረው)
(ሊቃኡ አልባቡል መፍቱህ 18/179)
ብዥታ አስራ ሁለት
ለመሪዎች ጠንካራ ህዝብ መመስረት ቅንና ኢስላማዊ መንሐጅ በመሆኑ ፤ በኢስላም
ህግ የሚመሩ አገሮች መንግስታቸውን የሚያጠናክሩበት መንገድ አንዱ ሰላማዊ ሰልፍ
በመሆኑ በህጋቸው ውስጥ ማካተት ይኖርባቸዋል፤ ሰላማዊ የሆነች ሰልፍ ህጋዊ መሆን
አለበት ለሚለው የሚከተለውን የዶክተር ሃቲም አልዓውኒይን ንግግር ማስረጃ
አድርገው ብዥታ ቢያቀርቡ፡
(ኢስላማዊ ለሆነች አገር ሁሉ በህዝቡ ላይ ጫና ለማሳደር የሚያግዝ ህግ
መደንገግ ይገባል፤ ምክንያቱም ህዝቡ አደገኛ ወደሆነ ጥመት እና መበታተን
እንዳይሄድ ዋስትና ነው፤ መበታተን በደል ነው፤ በደል ደግሞ በዚህ ዓለምም ይሁን
በወዲያኛው ዓለም ጨለማ ነው፤ አገር በእግሯ ልትቆም የምትችለው በምታሰፍነው
ፍትህ ነው ፤ አንድ መሪ ህዝብን በትክክለኛው ጎዳና ቀጥ አድርጎ መምራት ኢስላማዊ
መንሐጅ ነው፤ በዚህ የመጀመሪያው ኸሊፋ አቡበክር -ረዲየሏሁ ዓንሁማ-
ቀድሟል፤ መሪነትን እንደተሾመ የመጀመሪያው ኹጥባው ላይ የሚከተለውን ተናገረ፡
“ እናንተ ሰዎች ሆይ! እኔ በእናንተ ላይ ተሹሚያለሁ ነገር ግን በጣም መልካማችሁ
አይደለሁም፤ ካሳመርኩ እገዙኝ፤ ካከፋሁ አስተካክሉኝ…” እርሱ ነው “ካከፋሁ
አስተካክሉኝ” ያለው ፤ በዚህም መሪውን ለማስተካከል በህዝቡ ጫንቃ ላይ
መሰረታዊና መንግስታዊ የስልጣን ህግ ያስቀመጠ እርሱ ነው ፤ እርሱ መስተካከል
ሲያስፈልገው የእርሱን መጣመም ለማስተካከል አስገዳጅ የሆነች ህግ በእርሱ ላይ
ደነገገ፤)
መልስ፡- ከዚህ ቦታ ሰላማዊ ሰልፍ የሚል ቃል የታል? ስህተት ሲገኝ አቡበክርን -
ረዲየሏሁ ዓንሁማ- ለማስተካከል ህዝቡ ሰላማዊ ሰልፍ ወጦ ነበር? በፍጹም፤ ሶሀቦችም
ከአቡበክር -ረዲየሏሁ ዓንሁማ- ንግግር ይህን አልተረዱም ፤ እንዴውም የሶሃቦች
አስተያየት ከአቡበክር አስተያየት የተለየ የሆነበት ክስተት በርካታ ነው ፤ ከፊሎቹ
ወደርሱ መጠው ይከራከሩት ነበር፤ ይህ ብቻ አይደለም ወደርሱ የሚከራከር ሰው
ይልኩ ነበር፤ ለምሳሌ ዘካ የከለከሉ አካላትን ለመዋጋት በተነሳ ጊዜ እንዲሁም
የኡሳማን -ረዲየሏሁ ዓንሁማ- ሰራዊት በመላክ ዙሪያ የተከሰተው ጉዳይ ለዚህ ክርክር
ጠቃሚ የሆነ ማሳያ ነው፡፡
(“ሁክሙ አልሙዛሃራቲ አስሰሊመቲ” በሚል ዶ/ር ሃቲም አልዓውኒ አሽሸሪፍ የተናገረው በሚከተለው ማስፈንጠሪያ
ያገኙታል )
ሶሃቦቹ ወደአቡበክር አስተያየት ተመለሱ ምክንያቱም አስተያየቱ ሐቅ ስለነበር፤ ሰልፉ
ሰላማዊ ከሆነ ኢስላማዊ ነው ማለት ባጢል የሆነ ንግግር ነው፡፡
(የዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ህጋዊነት ባህላዊና የከተማ ህይወት አካል በመሆኑ እንዲሁም
የነገሮች መሰረት መፈቀድ ወይም ሀላል መሆኑ ነው፡፡)
(አልሙዟሀራቱ ወልኢዕቲሷማቱ ወልኢድጢራባት ገፅ/63)
(በዶ/ር ዩሱፍ አልቀርዷዊ ድህረ ገፅ በሚከተለው ማስፈንጠሪያ ይገኛል
)
ዶክተር ሰልማን አልአውዳ ደግሞ የሚከተለውን ተናግሯል፡
(እነዚህን ጉዳዮች አስመልክቶ መሰረቱ መፈቀድ ነው፤ ልዩ የሆነ መረጃ
አያስፈልገውም ፤ ሰነዱ ደካማ ቢሆንም እንኳ ሀምዛ እና ዑመር በሰለሙ ጊዜ በሁለት
ሶፍ መውጣታቸው የሙስሊሞች ታሪክ ሆኖ ተዘግቧል፡፡ ለእኛ በቂ ማስረጃ የሚሆነን
ግን ይህን ጉዳይ ለመከልከልም ለመፍቀድም ምንም አይነት መረጃ አለመኖሩ ነው፡፡)
መልስ፡- ሸይኽ አልባኒ - ረሂመሁሏህ - የሚከተለውን ተናግረዋል፡-
( ትክክል ነው፡ ወሳኢል (መዳረሻ ነገሮች) ከሸሪዓ ጋር ካልተጋጩ መሰረቱ
ይበቃል ፤ ይህ ምንም ችግር የለበትም ፤ ነገር ግን ወሳኢሉ (መዳረሻው) ከኢስላም
ውጭ የሆነን መንሀጅ (ጎዳና) ለመከተል መገለጫ ከሆነ ግን እነዚህ ወሳኢሎች
(መዳረሻዎች) ሸሪዓዊ አይሆኑም ፤ አለመውደድን ወይም መውደድን ለመግለጽ
ሰላማዊ ሰልፍ መውጣቱ ወይም ለአንዳንድ ውሳኔዎች ወይም ህጎች ድጋፍ ወይም
ተቃውሞን ለመግለጽ ሰላማዊ ሰልፍ መውጣቱ ይህ “ፍርድ ለህዝብ” ወይም “ፍርድ
ከህዝብ ወደህዝብ” ከሚለው ሰው ሰራሽ ስርዓት ጋር የሚስማማ ነው፤ ማህበረሰቡ
ኢስላማዊ ከሆነ ግን ጉዳዩ ሰላማዊ ሰልፍ አያስፈልገውም፤ የሚያስፈልገው የአላህን
ህግ በጣሰው ዳኛ ላይ ማስረጃን ማቆም ብቻ ነው፤ ኢስላማዊ ማህበረሰብ ከሆነ
የሰላማዊ ሰልፍ ስርዓት እና ከእርሱ ጀርባ የሚከተሉት ነገሮች ሁሉ አያስፈልጉም፤
ኢስላማዊ ማህበረሰብ ከተረጋገጠ አንድ ሰው አስተያየቱን ማስረጃውን ጉዳዩ
ወደሚመለከተው አካል ወይም ቢያንስ ቢያንስ ለተወከለው አካል ማቅረብ ብቻ ነው፤
በመሆኑም ከምዕራባውያን ባህል በወሰድነው በሰላማዊ ሰልፍ መንገድ አቤቱታን
ማቅረብ አስፈላጊ አይደለም፡፡
እውነታው ግን በአሁኑ ሰዓት ሙስሊሙ ማህበረሰብ የምእራባውያንን ባህልና
ልማድ ወስዶ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል ፤ ስለዚህ የግድ ከእነርሱ የምንወስደውን እና
የምንተወውን ነገር ለይተን ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ ለምሳሌ ፡ መዳረሻዎቹ ወደ ሸሪዓዊ
አላማዎች የሚያደርሱ ከሆነ ከእነርሱ ብንወስድ ችግር የለውም ፤ ከከሀዲዎች ጋር
መመሳሰል ከሚለው ትርጉም ውስጥ አይገባም፡፡
(ሸበከቱ አድዲፋዕ ዓኒስሱንነቲ በሚል ድህረ ገፅ በሚከተለው ማስፈንጠሪያ ይገኛል
)
ሰላማዊ ሰልፍ ውዴታንም ይሁን ተቃውሞን ለመግለጽ መዳረሻ ሊሆን በፍጹም
አይችልም፤ በሙስሊሙ ማህበረሰብ ውስጥ የሰላማዊ ሰልፍን ተጨባጭ ሁኔታ
ሳስተውል ቀስ በቀስ ሙስሊሙን የምዕራባዊ ልማድ ውጦት ክህደት ይቆጣጠረዋል
ብየ አስባለሁ፡፡
ሰላማዊ ሰልፍ የአንድን አገር ስርዓት ሊቀይረው ይችላል? የሚል ጥያቄ ቢነሳ፡
ስንት ጊዜ ሰላማዊ ሰልፍ ተደርጓል? ስንት ሰዎች ተገድለዋል? እውነታው ግን
ከሰላማዊ ሰልፉ በኋላ ያለው ሁኔታ ሰላማዊ ሰልፉ ከመደረጉ በፊት ካለው ሁኔታ ጋር
ተመሰሳሳይ ነው፤
ይህ ሰላማዊ ሰልፍ ከምዕራባውያን የወሰድነው በመሆኑ “አንድ ነገር መሰረቱ ሀላል
ነው ወይም መብቃት ነው፡፡” በሚለው ህግና መርሆ መካተቱ አይታየኝም፡፡)
እንዴውም ከኢስላም በፊት ዓረቦች ሰላማዊ ሰልፍ ይወጡ ነበር የሚለው አባባል
ትክክል ነው ብለን ብንቀበለው እንኳ ፤ ይህ ኢስላም ያላጸደቀው የጃሂልያ ባህሪ ነው
የሚል መልስ ይሰጣቸዋል ማለት ነው፡፡
الحمد لله
عبدالرحمن بن سعد بن علي الشثري:تاليف