You are on page 1of 2

በዐረብኛ ቋንቋ ውስጥ “ኢስተዋ” በ“ኢስተውላ/ተቆጣጠረ /ተሸመ” የተተረጎመበት አጋጣሚ አለ?

መልሱን ለምሁራን

1. ኢብኑል አዕራቢ ረሒመሁላህ ከቀዳሚዎቹ የዐረብኛ ቋንቋ ምሁራን ውስጥ ነው፡፡ ስለ “ኢስተዋ” እንዲህ
ይላል፡ “አሕመድ ኢብኑ አቢ ዱኣድ በዐረብኛ ቋንቋ ውስጥ ‘አረሕማኑ ዐለል ዐርሺ ኢስተዋʼ የሚለው
በ‘ኢስተውላʼ መልእክት የመጣበትን እንድፈልግለት ጠይቆኝ እንዲህ አልኩት ‘ወላሂ እንዲህ አይሆንም
አላገኘሁትም!ʼ(ኸጢቡልበግዳዲ ወላለካኢ፡3/399)፡፡

በነገራችን ላይ ይሄ ፈልግልኝ ባዩ አሕመድ ኢብኑ አቢዱኣድ ለነ ኢማሙ አሕመድ ፈተና ላይ መውደቅ ምክኒያት
የሆነው ጀህሚይ ነው፡፡ ከዚህ የምንረዳው “ኢስተዋን” በ“ኢስተውላ” መተርጎም የነኢማሙ አሕመድ ጠላቶች
አካሄድ እንደሆነ ነው፡፡

2. አልኸሊል ኢብኑ አሕመድ ረሒመሁላህ ከዐረብኛ ቋንቋ ምሁራን ውስጥ ከቀዳሚዎቹ ነው፡፡ “‘ኢስተዋንʼ
በ‘ኢስተውላʼ ትርጉም ያገኘህበት አለ?” ተብሎ ሲጠየቅ “በዚህ መልኩ ዐረቦች አያውቁትም፡፡ ቋንቋቸውም
አይፈቅደውም” ብሏል(መጅሙዑልፈታዋ፡5/146)

3. ኢብኑልጀውዚ፡ “ይሄ የቋንቋ ምሁራን ዘንድ የተጠላ ነው(ዛዱል ሙየሰር፡3/213)

4. ኢብኑ ዐብዱል በር፡ “ኢስተዋን ኢስተውላ ማለታቸው ትርጉም የለውም ምክኒያቱም በዐረብኛ የተለመደ
ስላልሆነ” (አተምሂድ፡7/131)

ስለዚህ “ኢስተዋን” በ“ኢስተውላ” ለመጀመሪያ ጊዜ የተረጎሙት ዘግይተው የመጡ ሰዎች ናቸው፡፡ ለዚህም
አቋማቸው ሰነዱ የማይታወቅ ግጥም ማጠናከሪያ አድርገው ያቀርባሉ፡፡ ኢብኑ ከሢር ይህንን ግጥም መረጃ
የሚያደርጉት ጀህሚያዎች እንደሆኑ ከጠቀሰ በኋላ “እንደ ጀህሚያ ደካማ ማስረጃ ያለው አናገኝም፡፡ የመረጃ
ድህነታቸው አንድ አስቀያሚ የክርስቲያን ግጥም እስከሚጠቀሙ አድርሷቸዋል” ይላል (አልቢዳያ ወኒሃያህ፡9/295)
፡፡መቼም ግጥም ቀርቶ ሐዲሥን እንኳ ማስረጃ አድርጎ ለማቅረብ ሶሒሕነቱ እንደሚፈተሽ ይታወቃል፡፡

5) ኑዓይም ኢብኑ ሀማድ (228 ሂጅራ)


የኢማሙ ቡኻሪ መምህር የሆኑት ኑዓይም ኢብኑ ሀማድ አል-አክዛኢ እንዲህ ብለዋል፡-
"አላህን ከፍጡ ሮቹ ያመሳሰለ ከፈረ፣ አላህ እራሱን የገለፀበትን ባህሪንም ያስተባበለ ከፈረ፣ አላህ እራሱን
የገለፀበት አገላለፅ ማመሳሰል አይደለም ፡፡ እንደዚሁም ነቢያችን (ሶዐወ) ስለ አላህ (ሱወ) የተናገሩትን መቀበል
ማመሳሰል አይደለም ፡፡ ስለ አላህ (ሱወ) በግልፅ የተገለፁትንም ሆነ በሰሂህ ሀዲስ የመጡትን ባህሪያት ለጌታ
እንደሚ ገባ ሳያመሳስል አምኖ የተቀበለ ትክክለኛውን ጎዳና ተመራ" ብለዋል ፡፡
/ሲያር አዕላሚ ኑበለእ ገጽ 610/
6) ኢማሙ ቁርጠቢ
ኢማሙ ቁርጠቢ በተፍሲራቸው እንዲህ ይላሉ፡-
"ኢብኑ አባስ (ረዐ) እንዲህ ብለዋል (አአሚንቱም መንፊሰማዕ) ማለት (አአሚንቱም አዛብ መንፊሰማዕ ኢን
አሰይቱሙሁ) /ከሰማ ይ በላይ ያለን ትተማመናላችሁ (ምንም አያደርገንም ብላችሁ) (ከሰማ ይ በላይ ያለን
ብትወነጅሉት አዛብ ምንም አያደርገንም ብላችሁ ታምናላችሁ?) በማለት ፈስሯል ፡፡ ከሰለፎች ውስጥ የጌታችንን
ከዓርሹ በላይ መሆንን ያስተባበለ አንድም የለም፡፡ ከዓርሹ በላይ መሆኑን ለይቶ ሲናገር ዓርሽ ከፍጡ ሮቹ ውስጥ
ትልቁ ስለሆነ ነው ፡፡ ነገር ግን ከዓርሹ በላይ እንዴት እንደሆነ ለማወቅ አይቻልም ፡፡"
(ተፍሲር አል-ቁርጠቢጁ 17-18 ገጽ 215-216)
7) ኢማሙ ቲርሚዚ (279 ሂጅራ)
ኢማሙ ቲርሚዚ እንዲህ ብለዋል
"እርሱ (አላህ) ከዓርሹ በላይ ነው ፡፡" (ኪታቡ ሰደቃ) አላህ ከዓርሹ በላይ የመደላደሉ ተፍሲር /ትርጉም/ አላህ
ለታላቅነቱ በሚስማማ መልኩ በላይ መሆኑ የሰለፎች ተፍሲር ነው ፡፡
8) ኢብኑ ጆሪር (310 ሂጅራ)
የሙፈሲሮች መሪ የሆነው ኢብኑ ጀሪር በተፍሲር ውስጥ እንዲህ ብሏል፡፡
"ኢስቲዋእ ማለት ከበላይ መሆንና ከፍ ማለት ነው ፡፡" /ሰሪሕ አል-ሱና/
9) ኢብኑ ኩዘይማ (311 ሂጅራ)
አቡበከር ሙሀመድ ኢብን ኢስሃቅ ኢብኑ ኩዘይማ እንዲህ ማለታቸው ተዘግቧል፡-
"አላህ ከፍጥሩ ሳይወሃድ ከሰባት ሰማይ በላይ ከዓርሽ በላይ ነው በማለት የማያረጋግጥ ሰው እርሱ በጌታው የከፈረ
(የካደ) ነው፡፡ ደሙም ሀላል ነው ፡፡
" (አቂዳቱል ሰለፍ ወአሰሃቡል ሀዲስ ዱምነ መጅሙዓ አ-ረሳኢል አል ሙኒይራ 1/111)

በመጨረሻም

ኢማሙ ማሊክ “ኢስቲዋእ የታወቀ ነው” ብለዋል፡፡ ይህንን ንግግር የአላህን ከዐርሹ በላይ መሆን
የሚያስተባብሉም ሰዎች መልእክቱን አንሻፈው ይጠቀሙበታል፡፡ ስለዚህ ጉዳዩ ይሄ የታወቀው የኢስቲዋእ ትርጉም
ምንነት ላይ ነው ማለት ነው፡፡ ሰለፎች ዘንድ የሚታወቀው የ“ኢስቲዋእ” መልእክት ደግሞ አላህ ከዐርሹ በላይ
እንደሆነ በግልፅ ይጠቁማል፡፡ ይህም ከኢብኑ ዐባስ፣ ከሙጃሂድ፣ ከኢብኑ ዓሊያህ፣ ከኢስሓቅ ኢብኑ ራህዊያህ
በሶሒሕ ሰነድ መጥቷል፡፡ “ኢስተዋን” በ“ኢስተውላ” የሚተረጉሙ ሰዎች ግን ከዚያ ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም
ምርጥነቱን ከመሰከሩለት ትውልድ አንድም ቀጥተኛ ማሳመኛ ማምጣት አይችሉም- አንድም!!

አላህ ቀጥተኛውን መንገድ ይምራን!!!

You might also like