Professional Documents
Culture Documents
Jehova
Jehova
ከመጽሐፍ ቅዱስ ጸሐፊዎች አንዱ እንደሚከተለው በማለት ጠይቆ ነበር:- “ነፋስንስ በእጁ
የጨበጠ ማን ነው? ውኃንስ በልብሱ የቋጠረ ማን ነው? የምድርን ዳርቻ ሁሉ ያጸና ማን
ነው? ይህን ታውቅ እንደ ሆንህ፣ ስሙ ማን የልጁስ ስም ማን ነው?” (ፊደላቱን ጋደል
አድርገን የጻፍናቸው እኛ ነን።) (ምሳሌ 30:4) እኛስ የአምላክ ስም ማን እንደሆነ ልናውቅ
የምንችለው እንዴት ነው? ይህ በጣም አስፈላጊ የሆነ ጥያቄ ነው። ፍጥረት አምላክ
ለመኖሩ ጠንካራ ማረጋገጫ የሚሰጠን ቢሆንም ስሙን ግን አይነግረንም። (ሮሜ
1:20) ፈጣሪ ራሱ ባይነግረን ኖሮ የአምላክ ስም ማን እንደሆነ ለማወቅ አንችልም ነበር።
የራሱ መጽሐፍ በሆነው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስሙን ገልጦልናል።
ታዲያ እንደ ያህዌህ ያሉት አጠራሮች የመጡት ከየት ነው? የመጀመሪያውን የአምላክ
ስም አጠራር ለማወቅ ሙከራ ያደረጉ ዘመናዊ ምሁራን የተሻሉ ናቸው ያሏቸው
አጠራሮች ናቸው። ሁሉም ሳይሆኑ አንዳንድ ምሁራን ከኢየሱስ ዘመን በፊት የነበሩት
አይሁዳውያን የአምላክን ስም ያህዌህ ብለው ሳይጠሩ አይቀሩም ብለው ያስባሉ። ይሁን
እንጂ በእርግጠኛነት ሊናገር የሚችል ሰው የለም። በዚህ ዓይነት አጠራር ሊጠቀሙም
ላይጠቀሙም ይችላሉ።
የይሖዋ ስምም ቢሆን ከዚህ የተለየ አይደለም። በዘመናችን የተለመደው ይሖዋ ወይም
ጅሆቫ የተባለው አጠራር ከመጀመሪያው የጥንት አጠራር ጋር አንድ ዓይነት ላይሆን
ቢችልም የስሙን አስፈላጊነት በምንም ዓይነት መንገድ አይቀንሰውም። ኢየሱስ
“በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ፣ ስምህ ይቀደስ” ያለው ፈጣሪ፣ ሕያው የሆነው
አምላክና የሁሉ የበላይ የሆነው ልዑል ተለይቶ የሚታወቅበት ስም ነው።—ማቴዎስ 6:9
ታዲያ እንዲህ ሲባል ያህዌህ ከሚለው አጠራር ጋር በሚመሳሰል አጠራር መጠቀም ስህተት
ነው ማለት ነውን? በፍጹም አይደለም። ይሖዋ የሚለው አጠራር “በብዙ ቋንቋዎች ጆሮ
የተለመደ” አጠራር በመሆኑ ምክንያት በአንባቢዎች ዘንድ የተሻለ ተቀባይነት ስለሚያገኝ
ብቻ ነው። ዋናው ነገር በስሙ መጠቀማችንና ስሙን ለሌሎች ማሳወቃችን ነው።
“ሕዝቦች ሁሉ ይሖዋን አመስግኑ! ስሙንም ጥሩ። ሥራዎቹን ለሕዝቦች ሁሉ አሳታውቁ።
ስሙ ከፍ ያለ መሆኑን ተናገሩ።”—ኢሳይያስ 12:4 አዓት
[የግርጌ ማስታወሻዎች]
^ አን.5 በአዲሲቱ ዓለም የቅዱሳን ጽሑፎች ትርጉም ፣ 1984 እትም ላይ ተጨማሪ ክፍል
(አፔንዲክስ) 1A ተመልከት።
^ አን.22 በአዲሲቱ ዓለም የቅዱሳን ጽሑፎች ትርጉም የ 1984 እትም ተጨማሪ ክፍል
(አፔንዲክስ) 1A ተመልከት።
‘ሪቫይዝድ ሴጐንድ ቨርሽን’ በተባለው የፈረንሳይኛ መጽሐፍ ቅዱስ የቃላት መፍቻ በገጽ 9
ላይ የሚከተለው አሳብ ተሰጥቷል:- “አንዳንድ የቅርብ ጊዜ ትርጉሞች
የተጠቀሙበት ያህቬ የሚለው አጠራር በማያጠራጥር ሁኔታ የተረጋገጠ ሳይሆን በአንዳንድ
የጥንት መረጃዎች ላይ የተመሠረተ ነው። እንደ ኤልያስ (ኤልያሁ) ያሉትን መለኮታዊው
ስም ተካትቶ የሚገኝባቸውን የተጸውኦ ስሞች ከተመለከትን የአምላክ ስም
አጠራር ያሆ ወይም ያሁ ሊሆን ይችላል።”
አማርኛ – ይሖዋ
Direct from Jehovah witness site
አዋባካልኛ – የሖዋ
ቡጎቱኛ – ጂሆቫ
ካንትንኛ – የህወዋህ
ዳንሽኛ– ጅሆቫ
ዳችኛ – ጅሆቫ
ኤፊክኛ – ጅሆቫ
እንግሊዝኛ ጅሆቫ
ፍጅያንኛ – ጅዮቫ
ፍንሽኛ – ጅሆቫ
ፈረንሳይኛ – ዢሆቫ
ፍቱናኛ – እሆቫ
ጀርመንኛ –ይሖቫ
ሀንጋሪያንኛ – ጅሆቫ
እግቦኛ – ጅሆቫ
ጣሊያንኛ – ጅኦቫ
ጃፓንኛ – ኢሆባ
ማውሪኛ – እሆዋ
ሞቱኛ – ኢየሆቫ
ሟላ ሟሉኛ – ጅሆቫ
ናሪንያሪኛ – ጅሆቫ
Direct from Jehovah witness site
ኔምቤኛ –ጅሆቫ
ፔታትስኛ – ጅሁቫ
ፖላንድኛ –ጅሁቫ
ፖርቱጋልኛ – ጅኦቫ
ሮማኒያንኛ – ኢየሆቫ
ሳሞአንኛ –ኢየወቫ
ሶቶኛ –ጅሆቫ
ስፓንኛ – ጅሆቫ
ስዋሒሊኛ – የሖቫ
ስዊድንኛ – ጅሆቫ
ታሂቲያንኛ – ኢየሆቫ
ታጋሎግኛ – ጅሆቫ
ቶንጋንኛ – ጅሆቫ
ቤንጃኛ – ይሖቫ
ቆሳኛ – ኡይሆቫ
የሩባኛ – ጅሆፋህ
ዙሉኛ – ኡጅሆቫ
የጀርመን ፌደራል ባንክ በ 1967 አሳትሞ ባወጣው ዶቸ ታለር (የጀርመን ገንዘብ) የተባለ
መጽሐፍ ውስጥ የ“ይሖዋ” ስም የሚገኝበት እጅግ ጥንታዊ ከሆኑት ሳንቲሞች አንዱ
የሆነውና ከሲሌሲያው ግዛት የተገኘው የ 1634 ራይኽታለር ሥዕል ወጥቷል። መጽሐፉ
በሳንቲሙ ጀርባ ላይ ስላለው ሥዕል እንዲህ ብሏል።:- “የብርሃን ነጸብራቅ ከሚወጣበት
ጅሆቫ ከሚለው ስም ግርጌ ከዳመና ውስጥ የሚወጣና አክሊል የደፋ የሲሌስያ ካባ
ይታያል።”