You are on page 1of 32

????

ጥምቀት ምንድን ነው?


መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?
“መጠመቅ” የሚለው አገላለጽ፣ ሙሉ በሙሉ ውኃ ውስጥ መጥለቅን
ያመለክታል።a በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለተለያዩ ሰዎች ጥምቀት የሚገልጹ ብዙ
ዘገባዎች አሉ። (የሐዋርያት ሥራ 2:41) ከእነዚህ ዘገባዎች መካከል አንዱ ኢየሱስ
በዮርዳኖስ ወንዝ ውስጥ በመጥለቅ እንደተጠመቀ የሚገልጸው ነው። (ማቴዎስ 3:13, 16)
ኢየሱስ ከተጠመቀ ከዓመታት በኋላ አንድ ኢትዮጵያዊ፣ እየተጓዘ ባለበት መንገድ አጠገብ
በሚገኝ ውኃ ውስጥ በመግባት ተጠምቋል።—የሐዋርያት ሥራ 8:36-40
ኢየሱስ፣ ተከታዮቹ መጠመቅ እንዳለባቸው አስተምሯል። (ማቴዎስ 28:19, 20)
ሐዋርያው ጴጥሮስም ይህን ትምህርት የሚያጠናክር ሐሳብ ጽፏል።—1 ጴጥሮስ 3:21

በዚህ ርዕስ ውስጥ፦

 ጥምቀት ምን ያመለክታል?
 መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ሕፃናት ጥምቀት ወይም ክርስትና ስለማስነሳት ምን
ይላል?
 በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም መጠመቅ ሲባል ምን ማለት ነው?
 ድጋሚ መጠመቅ ኃጢአት ነው?
 በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኙ ስለ ጥምቀት የሚናገሩ ሌሎች ዘገባዎች
 የክርስቲያኖችን ጥምቀት በተመለከተ ብዙዎች ያላቸው የተሳሳተ አመለካከት
ጥምቀት ምን ያመለክታል?
ጥምቀት አንድ ሰው ከኃጢአቱ ንስሐ እንደገባና በማንኛውም ሁኔታ ሥር የአምላክን
ፈቃድ ለማድረግ እንደተስማማ በሰዎች ፊት ይፋ ለማድረግ የሚወስደው እርምጃ ነው።
ይህም በመላ ሕይወቱ አምላክንና ኢየሱስን መታዘዝን ይጨምራል። አንድ ሰው ሲጠመቅ፣
ወደ ዘላለም ሕይወት በሚወስደው ጎዳና ላይ መጓዝ ይጀምራል።
ውኃ ውስጥ መጥለቅ፣ አንድ ሰው በሕይወቱ ውስጥ ያደረገውን ለውጥ ጥሩ አድርጎ
የሚገልጽ ምልክት ነው። እንዲህ የምንለው ለምንድን ነው? መጽሐፍ ቅዱስ መጠመቅን
ከመቀበር ጋር ያመሳስለዋል። (ሮም 6:4፤ ቆላስይስ 2:12) ግለሰቡ ውኃ ውስጥ መጥለቁ፣
ለቀድሞ አኗኗሩ እንደሞተ ያሳያል። ከውኃው መውጣቱ ደግሞ ራሱን ለአምላክ የወሰነ
ክርስቲያን በመሆን አዲስ ሕይወት መጀመሩን ይጠቁማል።
መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ሕፃናት ጥምቀት ወይም ክርስትና
ስለማስነሳት ምን ይላል?
“ክርስትና መነሳት” ወይም “ክርስትና ማስነሳት” የሚሉት አገላለጾች በመጽሐፍ ቅዱስ
ውስጥ አይገኙም።b መጽሐፍ ቅዱስ ሕፃናት መጠመቅ እንዳለባቸውም አያስተምርም።
ሕፃናትን ማጥመቅ፣ መጽሐፍ ቅዱስ ከሚያስተምረው ነገር ጋር አይጣጣምም። መጽሐፍ
ቅዱስ አንድ ሰው መጠመቅ ከፈለገ የተወሰኑ መሥፈርቶችን ማሟላት እንዳለበት
ያስተምራል። ለምሳሌ ቢያንስ መሠረታዊ የሆኑትን የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርቶች
መረዳትና እነዚህን ትምህርቶች በሕይወቱ ተግባራዊ ማድረግ ይኖርበታል። ከኃጢአቱ
ንስሐ መግባት ይጠበቅበታል። እንዲሁም በጸሎት አማካኝነት ራሱን ለአምላክ መወሰን
ያስፈልገዋል። (የሐዋርያት ሥራ 2:38, 41፤ 8:12) ሕፃናት ደግሞ እነዚህን ነገሮች
ማድረግ አይችሉም።
በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም መጠመቅ ሲባል ምን
ማለት ነው?
ኢየሱስ ለተከታዮቹ የሚከተለውን መመሪያ ሰጥቷቸዋል፦ “ሰዎችን ደቀ መዛሙርት
አድርጉ፤ በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፣ ያዘዝኳችሁንም
ሁሉ እንዲጠብቁ [አስተምሯቸው]።” (ማቴዎስ 28:19, 20) “በ . . . ስም” የሚለው
አገላለጽ፣ የሚጠመቀው ግለሰብ አብና ወልድ ያላቸውን ሥልጣንና ቦታ እንዲሁም
የአምላክ ቅዱስ መንፈስ የሚጫወተውን ሚና መረዳትና መቀበል እንዳለበት ያመለክታል።
ነጥቡን በምሳሌ ለማስረዳት ያህል፣ ሐዋርያው ጴጥሮስ ሲወለድ ጀምሮ ሽባ ለነበረው ሰው
“በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነስና ተራመድ!” ብሎታል። (የሐዋርያት ሥራ 3:6) ይህ ምን
ማለት እንደሆነ ግልጽ ነው፦ ጴጥሮስ የክርስቶስን ሥልጣን የተቀበለ ከመሆኑም ሌላ ሽባ
የነበረው ሰው የተፈወሰው በኢየሱስ እንደሆነ እውቅና ሰጥቷል።
 “አብ” የተባለው ይሖዋ c አምላክ ነው። ይሖዋ ፈጣሪ፣ ሕይወት ሰጪና ሁሉን
ቻይ አምላክ እንደመሆኑ መጠን ከሁሉ የላቀ ሥልጣን አለው።—ዘፍጥረት
17:1፤ ራእይ 4:11
 “ወልድ” የተባለው ሕይወቱን ለእኛ ሲል የሰጠው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። (ሮም
6:23) ኢየሱስ፣ አምላክ ለሰው ልጆች ባለው ዓላማ አፈጻጸም ውስጥ
የሚጫወተውን ወሳኝ ሚና ካልተረዳንና ካልተቀበልን መዳን ልናገኝ
አንችልም።—ዮሐንስ 14:6፤ 20:31፤ የሐዋርያት ሥራ 4:8-12
 “መንፈስ ቅዱስ” አምላክ የተለያዩ ነገሮችን ለማከናወን የሚጠቀምበት ኃይል
ነው።d አምላክ ለመፍጠር፣ ሕይወት ለመስጠት፣ ለነቢያቱና ለሌሎች
መልእክቱን ለማስተላለፍ እንዲሁም ፈቃዱን ለመፈጸም የሚያስችላቸውን
ኃይል ለመስጠት ቅዱስ መንፈሱን ተጠቅሞበታል። (ዘፍጥረት 1:2፤ ኢዮብ
33:4፤ ሮም 15:18, 19) አምላክ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጸሐፊዎች የእሱን ሐሳብ
እንዲጽፉ ለመምራትም ቅዱስ መንፈሱን ተጠቅሟል።—2 ጴጥሮስ 1:21
ድጋሚ መጠመቅ ኃጢአት ነው?
ሃይማኖታቸውን ለመለወጥ የሚወስኑ በርካታ ሰዎች አሉ። ሆኖም እነዚህ ሰዎች ቀደም
ሲል በነበሩበት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተጠምቀው ከነበረስ? ድጋሚ ቢጠመቁ ኃጢአት
ይሆንባቸዋል? አንዳንዶች አዎ የሚል መልስ ይሰጣሉ፤ ምናልባት እንዲህ የሚሉት ኤፌሶን
4:5 ላይ የሚገኘውን “አንድ ጌታ፣ አንድ እምነት፣ አንድ ጥምቀት አለ” የሚለውን ጥቅስ
መሠረት በማድረግ ሊሆን ይችላል። ሆኖም ይህ ጥቅስ አንድ ሰው ድጋሚ መጠመቅ
እንደሌለበት የሚጠቁም አይደለም። እንዴት?
የጥቅሱ አውድ። የኤፌሶን 4:5ን አውድ ስንመለከት ሐዋርያው ጳውሎስ እውነተኛ
ክርስቲያኖች በእምነት አንድ መሆናቸው ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ጎላ አድርጎ እየገለጸ
ነበር። (ኤፌሶን 4:1-3, 16) እንዲህ ያለው አንድነት ሊኖር የሚችለው አንድ ጌታ
ማለትም ኢየሱስ ክርስቶስን ከተከተሉ፣ አንድ እምነት ካላቸው ማለትም መጽሐፍ ቅዱስ
ስለሚያስተምረው ነገር ተመሳሳይ አረዳድ ካላቸው እንዲሁም ከጥምቀት ጋር በተያያዘ
አንድ ዓይነት ቅዱስ ጽሑፋዊ መሥፈርት ከተከተሉ ብቻ ነው።
ሐዋርያው ጳውሎስ ቀደም ሲል የተጠመቁ አንዳንድ ሰዎች ድጋሚ እንዲጠመቁ
አበረታቷል። ምክንያቱም እነዚህ ሰዎች የተጠመቁት የክርስትናን ትምህርት ሙሉ በሙሉ
ሳይረዱ ነው።—የሐዋርያት ሥራ 19:1-5
አምላክ የሚቀበለው ጥምቀት። ጥምቀት በአምላክ ዘንድ ተቀባይነት እንዲኖረው ከተፈለገ
በትክክለኛው የመጽሐፍ ቅዱስ እውቀት ላይ የተመሠረተ መሆን አለበት። (1 ጢሞቴዎስ
2:3, 4) አንድ ሰው የተጠመቀው ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር በሚጋጩ የሐሰት ሃይማኖት
ትምህርቶች ላይ ተመሥርቶ ከሆነ ጥምቀቱ በአምላክ ዘንድ ተቀባይነት አይኖረውም።
(ዮሐንስ 4:23, 24) ግለሰቡ ይህን እርምጃ የወሰደው ከልቡ ተነሳስቶ ቢሆንም “በትክክለኛ
እውቀት ላይ [ተመሥርቶ]” አይደለም። (ሮም 10:2) በአምላክ ፊት ተቀባይነት ለማግኘት
የመጽሐፍ ቅዱስን እውነት መማር፣ የተማረውን ነገር ተግባር ላይ ማዋል፣ ሕይወቱን
ለአምላክ መወሰንና ድጋሚ መጠመቅ ይኖርበታል። በዚህ ሁኔታ ሥር ድጋሚ መጠመቁ
ኃጢአት አይሆንበትም። እንዲያውም እንዲህ ማድረጉ ተገቢ ይሆናል።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኙ ስለ ጥምቀት የሚናገሩ
ሌሎች ዘገባዎች
መጽሐፍ ቅዱስ የክርስቶስ ተከታዮች ውኃ ውስጥ በመጥለቅ ከሚጠመቁት ጥምቀት፣
የተለየ ትርጉም ወይም ዓላማ ስላላቸው ሌሎች ጥምቀቶችም ይናገራል። እስቲ አንዳንድ
ምሳሌዎች ተመልከት።
መጥምቁ ዮሐንስ ያከናወነው ጥምቀት።e አይሁዶችና ወደ ይሁዲነት የተለወጡ ሰዎች
የሙሴን ሕግ ማለትም አምላክ በሙሴ አማካኝነት ለእስራኤላውያን የሰጣቸውን ሕግ
በመጣስ ለፈጸሙት ኃጢአት ንስሐ መግባታቸውን ለማሳየት ወደ ዮሐንስ እየሄዱ ይጠመቁ
ነበር። የዮሐንስ ጥምቀት ሕዝቡ መሲሑን ይኸውም የናዝሬቱን ኢየሱስን ማወቅና
መቀበል እንዲችሉ አዘጋጅቷቸዋል።—ሉቃስ 1:13-17፤ 3:2, 3፤ የሐዋርያት ሥራ 19:4
ኢየሱስ ራሱ የተጠመቀው ጥምቀት። ኢየሱስ በመጥምቁ ዮሐንስ የተጠመቀው ጥምቀት
ለየት ያለ ነበር። ኢየሱስ ፍጹም ሰው ሲሆን ምንም ኃጢአት አልነበረበትም። (1 ጴጥሮስ
2:21, 22) ስለዚህ የእሱ ጥምቀት ንስሐ መግባትን ወይም ‘ጥሩ ሕሊና ለማግኘት
ለአምላክ ልመና ማቅረብን’ አይጨምርም። (1 ጴጥሮስ 3:21) ከዚህ ይልቅ አስቀድሞ
የተነገረለት መሲሕ ወይም ክርስቶስ በመሆን የአምላክን ፈቃድ ለመፈጸም ራሱን
ማቅረቡን የሚያሳይ ነበር። አምላክ ለኢየሱስ ያለው ፈቃድ ደግሞ ለእኛ ሲል ሕይወቱን
መስጠቱን ይጨምራል።—ዕብራውያን 10:7-10

በመንፈስ ቅዱስ መጠመቅ። መጥምቁ ዮሐንስም ሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈስ


ቅዱስ ስለመጠመቅ ተናግረዋል። (ማቴዎስ 3:11፤ ሉቃስ 3:16፤ የሐዋርያት ሥራ 1:1-5)
ይህ ጥምቀት በመንፈስ ቅዱስ ስም ከመጠመቅ ጋር አንድ አይደለም። (ማቴዎስ 28:19)
እንዲህ የምንለው ለምንድን ነው?
በመንፈስ ቅዱስ የሚጠመቁት ከኢየሱስ ተከታዮች መካከል የተወሰኑት ብቻ ናቸው።
እነዚህ ሰዎች ከክርስቶስ ጋር ነገሥታትና ካህናት ሆነው በምድር ላይ እንዲገዙ ስለተጠሩ
በመንፈስ ቅዱስ ይቀባሉ።f (1 ጴጥሮስ 1:3, 4፤ ራእይ 5:9, 10) ገነት በምትሆነው ምድር
ላይ ለዘላለም የመኖር ተስፋ ያላቸው በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የኢየሱስ ተከታዮች
ተገዢዎቻቸው ይሆናሉ።—ማቴዎስ 5:5፤ ሉቃስ 23:43
በክርስቶስ ኢየሱስ እና በሞቱ ውስጥ መጠመቅ። በመንፈስ ቅዱስ የሚጠመቁ ሰዎች
‘በክርስቶስ ኢየሱስ ውስጥም’ ይጠመቃሉ። (ሮም 6:3) በመሆኑም ይህን ጥምቀት
የሚጠመቁት ከኢየሱስ ጋር አብረው በሰማይ የሚገዙት ቅቡዓን ተከታዮቹ ናቸው። እነዚህ
ሰዎች ኢየሱስ ውስጥ በመጠመቅ፣ ቅቡዓን ተከታዮቹን ያቀፈው ጉባኤ አባል ይሆናሉ።
ኢየሱስ የጉባኤው ራስ፣ እነሱ ደግሞ አካል ናቸው።—1 ቆሮንቶስ 12:12,
13, 27፤ ቆላስይስ 1:18
ቅቡዓን ክርስቲያኖች ‘የኢየሱስ ሞት ውስጥም’ ይጠመቃሉ። (ሮም 6:3, 4) የኢየሱስን
ምሳሌ በመከተል አምላክን በመታዘዝ ላይ ያተኮረ የመሥዋዕትነት ሕይወት ይመራሉ
እንዲሁም በምድር ላይ ለዘላለም የመኖር ተስፋቸውን ይተዋሉ። ከሞቱ በኋላ መንፈሳዊ
ፍጡር ሆነው በሰማይ ለመኖር ትንሣኤ ሲያገኙ ይህ ምሳሌያዊ ጥምቀት ይጠናቀቃል።—
ሮም 6:5፤ 1 ቆሮንቶስ 15:42-44
በእሳት መጠመቅ። መጥምቁ ዮሐንስ እያዳመጡት ለነበሩት ሰዎች እንዲህ ብሏቸዋል፦
“እሱ [ኢየሱስ] በመንፈስ ቅዱስና በእሳት ያጠምቃችኋል። ላይዳውን በእጁ ይዟል፤
አውድማውንም ፈጽሞ ያጸዳል፤ ስንዴውንም ወደ ጎተራ ያስገባል፤ ገለባውን ግን
በማይጠፋ እሳት ያቃጥለዋል።” (ማቴዎስ 3:11, 12) በእሳት በመጠመቅና በመንፈስ
ቅዱስ በመጠመቅ መካከል ልዩነት እንዳለ ልብ በል። ዮሐንስ ይህን አገላለጽ የተጠቀመው
ምንን ለማመልከት ነው?
ስንዴው የሚያመለክተው ኢየሱስን ሰምተው የሚታዘዙትን ሰዎች ነው። እነዚህ ሰዎች
በመንፈስ ቅዱስ የመጠመቅ ተስፋ አላቸው። ገለባው፣ ኢየሱስን ለመስማት ፈቃደኛ
ያልሆኑ ሰዎችን ያመለክታል። የእነዚህ ሰዎች መጨረሻ በእሳት መጠመቅ ነው፤ ይህም
ዘላለማዊ ጥፋትን ያመለክታል።—ማቴዎስ 3:7-12፤ ሉቃስ 3:16, 17
የክርስቲያኖችን ጥምቀት በተመለከተ ብዙዎች ያላቸው
የተሳሳተ አመለካከት
የተሳሳተ አመለካከት፦ ሰዎች ለመጠመቅ የግድ ውኃ ውስጥ መጥለቅ አያስፈልጋቸውም፤
ውኃ ከተረጨባቸው ወይም ከፈሰሰባቸው በቂ ነው።

እውነታው፦ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተመዝግበው የሚገኙት ስለ ጥምቀት የሚናገሩት


ዘገባዎች፣ ሰዎቹ ሙሉ በሙሉ ውኃ ውስጥ እንደጠለቁ ይጠቁማሉ። (ማቴዎስ
3:13, 16፤ የሐዋርያት ሥራ 8:36-39) ውኃ እንደተረጨባቸው የሚገልጽ አንድም ዘገባ
የለም።g አንድ ሰው ውኃ ውስጥ መጥለቁ፣ ግለሰቡ ለቀድሞው አኗኗሩ እንደሞተና አሁን
ራሱን የወሰነ የአምላክ አገልጋይ በመሆን አዲስ ሕይወት እንደጀመረ የሚያሳይ ነው፤ ውኃ
መርጨት ግን ይህን ምሳሌያዊ ትርጉም አያስተላልፍም።

የተሳሳተ አመለካከት፦ በፊልጵስዩስ የእስር ቤት ጠባቂውና ‘መላው ቤተሰቡ እንደተጠመቁ’


የሚናገረው የመጽሐፍ ቅዱስ ሐሳብ ሕፃናትም እንደሚጠመቁ የሚያሳይ ነው።—
የሐዋርያት ሥራ 16:25, 31-34

እውነታው፦ አንደኛ ነገር ጥቅሱ ስለ ሰዎቹ ዕድሜ የሚናገረው ነገር የለም። ሌላው ነገር
ደግሞ የእስር ቤቱ ጠባቂና ቤተሰቡ ከመጠመቃቸው በፊት “የይሖዋን ቃል” እንደሰሙና
እንደተቀበሉ ዘገባው ይናገራል። (የሐዋርያት ሥራ 16:31, 32, 34) በመሆኑም
የሚነገረውን ነገር መረዳት እንዲሁም በአምላክና በጌታ በኢየሱስ ላይ ማመን የሚችሉበት
ዕድሜ ላይ ደርሰው መሆን አለበት።
a ቫይንስ ኮምፕሊት ኤክስፖዚተሪ ዲክሽነሪ ኦቭ ኦልድ ኤንድ ኒው ቴስታመንት ወርድስ የተባለው መጽሐፍ
እንደሚገልጸው “መጠመቅ” የሚለው የግሪክኛ ቃል “መግባትን፣ መጥለቅንና መውጣትን” ያመለክታል።

b “ክርስትና ማንሳት” የሚለው አገላለጽ አንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት ለሕፃናት ስም በማውጣት ከዚያም
ራሳቸው ላይ ውኃ በመርጨት ወይም በማፍሰስ የሚፈጽሙትን ሃይማኖታዊ ሥርዓት ያመለክታል።

c ይሖዋ የአምላክ የግል ስም ነው። (መዝሙር 83:18) “ይሖዋ ማን ነው?” የሚለውን ርዕስ ተመልከት።

d “መንፈስ ቅዱስ ምንድን ነው?” የሚለውን ርዕስ ተመልከት።

e “መጥምቁ ዮሐንስ ማን ነው?” የሚለውን ርዕስ ተመልከት።

f “ወደ ሰማይ የሚሄዱት እነማን ናቸው?” የሚለውን ርዕስ ተመልከት።

g መጽሐፍ ቅዱስ “ጥምቀት” የሚለውን አገላለጽ ዕቃዎችን እንደመንከር ያሉ የመንጻት ሥነ ሥርዓቶችን


ለማመልከት ይጠቀምበታል። (ማርቆስ 7:4 ግርጌ፤ ዕብራውያን 9:10 ግርጌ) እርግጥ ነው፣ ይህ ዓይነቱ
ጥምቀት ኢየሱስም ሆነ ተከታዮቹ ከተጠመቁበት ውኃ ውስጥ መጥለቅን የሚጠይቅ ጥምቀት የተለየ ነው።
መንፈስ ቅዱስ ምንድን ነው?
መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?
መንፈስ ቅዱስ በሥራ ላይ ያለ የአምላክ ኃይል ነው። (ሚክያስ 3:8፤ ሉቃስ 1:35) አምላክ
ፈቃዱን ለመፈጸም ሲፈልግ እሱ በመረጠው ነገር ላይ ኃይሉን ያኖራል፤ መንፈሱን
የሚልከው በዚህ መንገድ ነው።—መዝሙር 104:30፤ 139:7
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “መንፈስ” ተብሎ የተተረጎመው የዕብራይስጥ ቃል ሩአህ ሲሆን
የግሪክኛው ቃል ደግሞ ንዩማ ነው። እነዚህ ቃላት ብዙውን ጊዜ የተሠራባቸው በሥራ ላይ
ያለውን የአምላክ ኃይል ይኸውም መንፈስ ቅዱስን ለማመልከት ነው። (ዘፍጥረት 1:2)
ይሁንና በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እነዚህ ቃላት ሌሎች ነገሮችንም ለማመልከት
ተሠርቶባቸዋል፦
 እስትንፋስ—ዕንባቆም 2:19፤ ራእይ 13:15
 ነፋስ—ዘፍጥረት 8:1፤ ዮሐንስ 3:8
 በሕያዋን ፍጥረታት ውስጥ የሚገኘው ወይም ሕይወት እንዲኖራቸው
የሚያደርገው ኃይል—ኢዮብ 34:14, 15
 የአንድ ሰው ባሕርይ ወይም ጠባይ—ዘኍልቍ 14:24
 መንፈሳዊ አካላት (አምላክና መላእክት)—1 ነገሥት 22:21፤ ዮሐንስ 4:24
ሁሉንም የሚያመሳስላቸው አንድ ነገር አለ፤ ሁሉም በሰው ዓይን ሊታዩ ባይችሉም
የሚያሳድሩትን ውጤት ግን መመልከት እንችላለን። በተመሳሳይም የአምላክ መንፈስ “ልክ
እንደ ነፋስ ሁሉ የማይታይና የማይዳሰስ እንዲሁም ኃይል ያለው ነው።”—አን
ኤክስፖዚተሪ ዲክሽነሪ ኦቭ ኒው ቴስታመንት ዎርድስ
ከዚህም በተጨማሪ የአምላክ ቅዱስ መንፈስ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የአምላክ ‘እጅ’ ወይም
‘ጣት’ እንደሆነ ተደርጎ ተገልጿል። (መዝሙር 8:3፤ 19:1፤ ሉቃስ 11:20፤ ከማቴዎስ
12:28 ጋር አወዳድር) አንድ የእጅ ባለሙያ በእጁ እና በጣቶቹ ተጠቅሞ ሥራውን
እንደሚያከናውን ሁሉ አምላክም በመንፈሱ ተጠቅሞ የሚከተሉት ውጤቶች እንዲገኙ
አስችሏል፦
 ጽንፈ ዓለም—መዝሙር 33:6፤ ኢሳይያስ 66:1, 2
 መጽሐፍ ቅዱስ—2 ጴጥሮስ 1:20, 21
 የጥንት አገልጋዮቹ የፈጸሟቸው ተአምራትና በቅንዓት ያከናወኑት የስብከት ሥራ—
ሉቃስ 4:18፤ የሐዋርያት ሥራ 1:8፤ 1 ቆሮንቶስ 12:4-11
 እሱን የሚታዘዙ ሰዎች የሚያሳዩዋቸው ግሩም ባሕርያት—ገላትያ 5:22, 23

መንፈስ ቅዱስ አካል አይደለም


መንፈስ ቅዱስ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የአምላክ ‘እጅ፣’ ‘ጣት’ ወይም “እስትንፋስ” ተደርጎ
መገለጹ አካል እንዳልሆነ ይጠቁማል። (ዘፀአት 15:8, 10) የአንድ የእጅ ባለሙያ እጆች
ከአንጎሉ ወይም ከሰውነቱ ተነጥለው ብቻቸውን እንደማይሠሩ ሁሉ መንፈስ ቅዱስም
መንቀሳቀስ የሚችለው በአምላክ አመራር ብቻ ነው። (ሉቃስ 11:13) መጽሐፍ ቅዱስ
የአምላክን መንፈስ ከውኃ ጋር የሚያነጻጽረው ሲሆን እንደ እምነትና እውቀት ካሉ ነገሮች
ጋር ተያይዞ የተጠቀሰበት ጊዜም አለ። እነዚህ ሁሉ ንጽጽሮች መንፈስ ቅዱስ አካል
እንዳልሆነ ይጠቁማሉ።—ኢሳይያስ 44:3፤ የሐዋርያት ሥራ 6:5፤ 2 ቆሮንቶስ 6:6
የአብ ስም ይሖዋ፣ የወልድ ስም ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ
ተገልጿል፤ ይሁንና መንፈስ ቅዱስ ስም እንዳለው በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የትም ቦታ
አልተጠቀሰም። (ኢሳይያስ 42:8 NW፤ ሉቃስ 1:31) ሰማዕት የሆነው ክርስቲያኑ
እስጢፋኖስ በሰማይ ላይ ያለውን ሁኔታ ተአምራዊ በሆነ መንገድ በራእይ በተመለከተበት
ወቅት ሁለት እንጂ ሦስት አካላትን አላየም። መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፦ “በመንፈስ
ቅዱስ ተሞልቶ ትኩር ብሎ ወደ ሰማይ ሲመለከት የአምላክን ክብር እንዲሁም ኢየሱስ
በአምላክ ቀኝ ቆሞ አየ።” (የሐዋርያት ሥራ 7:55) መንፈስ ቅዱስ አምላክ ነገሮችን
ለማከናወን የሚጠቀምበት ኃይል እንደመሆኑ መጠን እስጢፋኖስ ራእዩን እንዲመለከት
ያስቻለው ይኸው መንፈስ ነው።

መንፈስ ቅዱስን አስመልክቶ የሚነገሩ የተሳሳቱ እምነቶች


የተሳሳተ እምነት፦ “መንፈስ ቅዱስ” አካል ያለው ከመሆኑም በላይ የሥላሴ ክፍል ነው፤
በአንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች ውስጥ በ 1 ዮሐንስ 5:7, 8 ላይ ያለው ሐሳብ ይህን
ያሳያል።
እውነታው፦ በ 1879 ትርጉም ላይ 1 ዮሐንስ 5:7, 8 የሚከተለውን ሐሳብ ይዟል፦ “በሰማይ
የሚመሰክሩ ሦስት ናቸውና እርሳቸውም አብ ቃልም መንፈስ ቅዱስም። . . . ሦስትም
አንድም ናቸው።” ይሁንና ተመራማሪዎች ሐዋርያው ዮሐንስ ይህን ሐሳብ እንዳልተናገረ
ደርሰውበታል፤ በመሆኑም ሐሳቡ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል አይደለም። ፕሮፌሰር ብሩስ
ማኒንግ ሜትስገር እንዲህ በማለት ጽፈዋል፦ “እነዚህ ቃላት ውሸት በመሆናቸው የአዲስ
ኪዳን ክፍል ሊሆኑ አይገባም።”—ኤ ቴክስቹዋል ኮሜንታሪ ኦን ዘ ግሪክ ኒው ቴስታመንት
የተሳሳተ እምነት፦ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ መንፈስ ቅዱስ፣ አካል ያለው ነገር
የሚያደርጋቸውን ነገሮች እንዳከናወነ ተደርጎ መገለጹ አካል እንዳለው ያሳያል።
እውነታው፦ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ መንፈስ ቅዱስ አካል ያለው ነገር የሚያደርጋቸውን
ነገሮች እንዳደረገ ተደርጎ የተገለጸበት ጊዜ አለ፤ ይሁንና ይህ በራሱ መንፈስ ቅዱስ ራሱን
የቻለ አካል እንዳለው አያሳይም። ጥበብ፣ ሞትና ኃጢአትም በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ አካል
ያለው ነገር የሚያደርገውን ነገር እንዳከናወኑ ተደርገው ተገልጸዋል። (ምሳሌ 1:20፤ ሮም
5:17, 21) ለምሳሌ ያህል፣ ጥበብ “ሥራ” እንደምትሠራ እና ‘ልጆች’ እንዳሏት ተገልጿል፤
ኃጢአት ደግሞ እንደሚያታልል፣ እንደሚገድልና የመጎምጀት ፍላጎት እንደሚፈጥር ተደርጎ
ተገልጿል።—ማቴዎስ 11:19፤ ሉቃስ 7:35፤ ሮም 7:8, 11
በተመሳሳይም ሐዋርያው ዮሐንስ እንደጻፈው ኢየሱስ፣ መንፈስ ቅዱስን ‘ረዳት’ ብሎ
የጠራው ከመሆኑም ሌላ ይህ ረዳት አሳማኝ ማስረጃ የሚያቀርብ፣ የሚመራ፣ የሚናገር፣
የሚሰማ፣ የሚያሳውቅ፣ የሚያከብርና የሚወስድ ወይም የሚቀበል እንደሆነም ተናግሯል።
(ዮሐንስ 16:7-15) ዮሐንስ በሌላ ጥቅስ ላይ ስለ መንፈስ ቅዱስ ሲናገር
የተጠቀመው ንዩማ የሚለው ግሪክኛ ቃል ፆታ አመልካች የሌለውና ለግዑዝ ነገር
የሚያገለግል ቃል መሆኑ ትኩረት የሚስብ ነው።—ዮሐንስ 14:16, 17
የተሳሳተ እምነት፦ ሰው የሚጠመቀው በመንፈስ ቅዱስ ስም መሆኑ መንፈስ ቅዱስ አካል
እንደሆነ ያሳያል።
እውነታው፦ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ስም” የሚለው ቃል ሥልጣንን ወይም ቦታን
ለማመልከት የተሠራበት ጊዜ አለ። (ዘዳግም 18:5, 19-22፤ አስቴር 8:10) ለምሳሌ ያህል፣
“በሕግ ስም” የሚል የተለመደ አባባል አለ፤ ይህ አባባል ሕግ አንድ ዓይነት አካል እንደሆነ
የሚጠቁም አይደለም። አንድ ሰው “በመንፈስ ቅዱስ ስም” መጠመቁ መንፈስ ቅዱስ
የአምላክ ፈቃድ እንዲፈጸም በማድረግ በኩል ያለው ሥልጣንና ድርሻ አምኖ መቀበሉን
የሚያሳይ ነው።—ማቴዎስ 28:19
የተሳሳተ እምነት፦ የኢየሱስ ሐዋርያትና ሌሎች የጥንት ክርስቲያኖች፣ መንፈስ ቅዱስ
አካል እንደሆነ ያምኑ ነበር።
እውነታው፦ መጽሐፍ ቅዱስም ሆነ ታሪክ ይህን ሐሳብ አይደግፍም። ኢንሳይክሎፒዲያ
ብሪታኒካ እንዲህ ይላል፦ “መንፈስ ቅዱስ ራሱን የቻለ መለኮታዊ አካል እንደሆነ . . .
የሚገልጸው ሐሳብ የመጣው በ 381 ዓ.ም. ከተካሄደው የቁስጥንጥንያ ጉባኤ በኋላ ነው።”
ይህም የሆነው የመጨረሻው ሐዋርያ ከሞተ ከ 250 ከሚበልጡ ዓመታት በኋላ ነው።
ኢየሱስ የአምላክ ልጅ ተብሎ የተጠራው ለምንድን
ነው?
መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?
መጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ጊዜ ኢየሱስን “የአምላክ ልጅ” በማለት ይጠራዋል። (ዮሐንስ 1:49)
“የአምላክ ልጅ” የሚለው አገላለጽ አምላክ ፈጣሪ እንደሆነ ማለትም ኢየሱስን ጨምሮ
የሁሉም ፍጥረታት ምንጭ እሱ እንደሆነ የሚጠቁም ነው። (መዝሙር 36:9፤ ራእይ
4:11) መጽሐፍ ቅዱስ አምላክ እንደ ሰዎች ቃል በቃል ልጅ እንደወለደ አይናገርም።
መጽሐፍ ቅዱስ መላእክትንም “የእውነተኛው አምላክ ልጆች” በማለት ይጠራቸዋል።
(ኢዮብ 1:6) በተጨማሪም የመጀመሪያው ሰው ማለትም አዳም “የአምላክ ልጅ” እንደሆነ
ይገልጻል። (ሉቃስ 3:38) ያም ቢሆን ኢየሱስ የአምላክ የመጀመሪያ ፍጥረት በመሆኑና
በቀጥታ በአምላክ የተፈጠረው እሱ ብቻ በመሆኑ ኢየሱስ የአምላክ የበኩር ልጅ እንደሆነ
መጽሐፍ ቅዱስ ይገልጻል።
 ኢየሱስ ምድር ላይ ከመወለዱ በፊት በሰማይ ይኖር ነበር?
 ኢየሱስ ወደ ምድር ከመምጣቱ በፊት ምን ያደርግ ነበር?

ኢየሱስ ምድር ላይ ከመወለዱ በፊት በሰማይ ይኖር ነበር?


አዎ። ኢየሱስ ሰው ሆኖ ምድር ላይ ከመወለዱ በፊት በሰማይ የሚኖር መንፈሳዊ ፍጡር
ነበር። ኢየሱስ ራሱ ‘ከሰማይ እንደመጣ’ ተናግሯል።—ዮሐንስ 6:38፤ 8:23
አምላክ ኢየሱስን የፈጠረው ሌሎች ነገሮችን ከመፍጠሩ በፊት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ
ኢየሱስን አስመልክቶ ሲናገር እንዲህ ይላል፦
 “እሱ . . . የፍጥረት ሁሉ በኩር ነው።”—ቆላስይስ 1:15
 “ከአምላክ ፍጥረት የመጀመሪያ” ነው።—ራእይ 3:14
“ምንጩ ከጥንት፣ ከረጅም ዘመን በፊት” ስለሆነ መሲሕ የሚናገረው ትንቢት በኢየሱስ ላይ
ተፈጽሟል።—ሚክያስ 5:2፤ ማቴዎስ 2:4-6
ኢየሱስ ወደ ምድር ከመምጣቱ በፊት ምን ያደርግ ነበር?
በሰማይ ከፍተኛ ሥልጣን ነበረው። ኢየሱስ “አባት ሆይ፣ ዓለም ከመመሥረቱ በፊት በጎንህ
ሆኜ ክብር እንደነበረኝ ሁሉ አሁንም . . . አክብረኝ” በማለት ያቀረበው ጸሎት ሰማይ ላይ
ስለነበረው ሥልጣን የሚገልጽ ነው።—ዮሐንስ 17:5
አባቱ ሌሎች ነገሮችን ሲፈጥር በሥራው ተካፍሏል። ኢየሱስ “የተዋጣለት ሠራተኛ”
በመሆን ከአምላክ ጋር ሠርቷል። (ምሳሌ 8:30) መጽሐፍ ቅዱስ ይህን አስመልክቶ ሲናገር
“በሰማያትና በምድር ያሉ ሌሎች ነገሮች በሙሉ . . . የተፈጠሩት በእሱ አማካኝነት ነው”
ይላል።—ቆላስይስ 1:16
አምላክ ሌሎች ነገሮችን የፈጠረው በኢየሱስ አማካኝነት ነው። ከእነዚህ መካከል ጽንፈ
ዓለምና መንፈሳዊ ፍጥረታት ይገኙበታል። (ራእይ 5:11) አምላክና ኢየሱስ አብረው
የሠሩበት መንገድ በመሐንዲስና በግንበኛ መካከል ካለው ዝምድና ጋር ሊወዳደር ይችላል።
መሐንዲሱ ንድፉን ያወጣል፤ ግንበኛው ደግሞ ግንባታውን ይሠራል።
ቃል ሆኖ አገልግሏል። መጽሐፍ ቅዱስ ኢየሱስ ሰው ከመሆኑ በፊት ስለነበረው ሕይወት
ሲናገር “ቃል” በማለት ይጠራዋል። (ዮሐንስ 1:1) በመሆኑም አምላክ ለሌሎች መንፈሳዊ
ፍጥረታት መረጃና መመሪያ ለማስተላለፍ በልጁ ይጠቀም ነበር ማለት ነው።
ኢየሱስ ምድር ላይ ላሉ ሰዎችም የአምላክ ቃል አቀባይ ሆኖ ሳያገለግል አልቀረም።
አምላክ በኤደን ገነት ለአዳምና ለሔዋን መመሪያ የሰጣቸው ኢየሱስን እንደ ቃል አቀባይ
ተጠቅሞ ሳይሆን አይቀርም። (ዘፍጥረት 2:16, 17) በተጨማሪም እስራኤላውያንን
በምድረ በዳ የመራቸው እንዲሁም ቃሉን እንዲታዘዙ የተነገራቸው መልአክ ኢየሱስ ሊሆን
ይችላል።—ዘፀአት 23:20-23a
a አምላክ የተናገረው ቃል በተባለው መልአክ በኩል ብቻ አይደለም። ለምሳሌ ያህል፣ አምላክ ሕጉን ለጥንቶቹ
እስራኤላውያን ለማስተላለፍ አንድያ ልጁን ሳይሆን ሌላ መልአክ ተጠቅሟል።—የሐዋርያት ሥራ
7:53፤ ገላትያ 3:19፤ ዕብራውያን 2:2, 3

የአምላክ ስምና “አዲስ ኪዳን”


የአምላክ ስምና “አዲስ ኪዳን”
የአምላክ ስም በዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሑፎች ማለት “በብሉይ ኪዳን” ውስጥ ያለው ቦታ
ፈጽሞ የማይናወጥ ነው። አይሁዳውያን ሲውል ሲያድር መለኰታዊውን ስም በአፋቸው
መጥራት ቢተውም እንኳን ሃይማኖታዊ እምነታቸው የመጽሐፍ ቅዱስን ጥንታዊ ቅጂዎች
በሚገለብጡበት ጊዜ የአምላክን ስም እንዳያስወጡ ያግዳቸው ነበር። በዚህም ምክንያት
በዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሑፎች ውስጥ የአምላክ ስም ከማንኛውም ስም ይበልጥ ብዙ ጊዜ
ተጽፎ ሊገኝ ችሏል።

በክርስቲያን ግሪክኛ ቅዱሳን ጽሑፎች ወይም “በአዲስ ኪዳን” ውስጥ ግን ሁኔታው ከዚህ
የተለየ ነው። በራእይ መጽሐፍ (የመጨረሻው የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ) የእጅ ጽሑፍ
ቅጂ ውስጥ የአምላክ ስም “ያህ” በሚለው ምህጻረ ቃል (“ሃሌ ሉያ” በሚለው ቃል ውስጥ)
ተጽፎ ይገኛል። ከዚህ በቀር በአሁኑ ጊዜ በእጃችን በሚገኙት ከማቴዎስ እስከ ራእይ
በሚገኙት የጥንት ግሪክኛ የእጅ ጽሑፍ ቅጂዎች ውስጥ የአምላክ ስም ተጽፎ አይገኝም።
ታዲያ የአምላክ ስም በክርስትና ግሪክኛ ቅዱሳን ጽሑፎች ውስጥ መኖር የለበትም ማለት
ነውን? እንዲህ ቢሆን ነገሩ ግራ ያጋባ ነበር። ምክንያቱም የኢየሱስ ተከታዮች የአምላክ
ስም ያለውን ከፍተኛ ቦታ ይገነዘቡ ነበር፤ ኢየሱስም ስለ አምላክ ስም መቀደስ እንድንጸልይ
አስተምሮናል። ታዲያ የአምላክ ስም ከክርስቲያን ግሪክኛ ቅዱሳን ጽሑፎች የጠፋው
ለምንድን ነው?

ይህንን ለመረዳት በአሁኑ ጊዜ ያሉን ጥንታዊ ግሪክኛ የክርስቲያን ቅዱሳን ጽሑፎች


ቅጂዎች በኩረ ጽሑፎች አለመሆናቸውን ማስታወስ ይገባናል። ማቴዎስ፣ ሉቃስና ሌሎቹ
የመጽሐፍ ቅዱስ ጸሐፊዎች በራሳቸው እጅ የጻፏቸው መጻሕፍት በአገልግሎት ብዛት
አርጅተው ጠፍተዋል። በዚህም ምክንያት እነዚህን መጻሕፍት መገልበጥ አስፈላጊ ሆኗል።
ግልባጮቹ በሚያረጁበት ጊዜ ደግሞ ሌሎች ግልባጮች ከግልባጮቹ ተገልብጠዋል።
የሚገለበጡት ቅጂዎች አገልግሎት ላይ የሚውሉ እንጂ በአንድ ቦታ ተጠብቀው
የማይቀመጡ በመሆናቸው እንዲህ መደረጉ የሚጠበቅ ነገር ነው።

በአሁኑ ጊዜ በሺህ የሚቆጠሩ ግሪክኛ የክርስቲያን ጽሑፎች ጥንታዊ የእጅ ግልባጮች


ይገኛል፤ ይሁን እንጂ ከእነዚህ መካከል አብዛኞቹ የተገለበጡት በአራተኛው መቶ ዘመን
እንደ ዘመናችን አቆጣጠር ወይም ከዚያ በኋላ ነው። ይህ ደግሞ ከአራተኛው መቶ
ዘመን በፊት የአምላክ ስም ከግሪክኛ የክርስቲያን ጽሑፎች ውስጥ እንዲወጣ ያደረገ ነገር
ተፈጽሞ ይሆንን? የሚል ጥርጣሬ ያሳድርብናል። በእርግጥም የተፈጸመ ነገር መኖሩን
እውነታዎቹ ያሳያሉ።

መለኮታዊው ስም ይገኝ ነበር


ሐዋርያው ማቴዎስ የአምላክን ስም በወንጌሉ ውስጥ አስገብቶ እንደነበረ እርግጠኞች
ልንሆን እንችላለን። ለምን? ወንጌሉን በመጀመሪያ የጻፈው በዕብራይስጥ ስለነበረ ነው።
በአራተኛው መቶ ዘመን የላቲን ቩልጌት ን የተረጎመው ዤሮም እንዲህ ሲል ጽፏል:- “ሌዊ
ይባል የነበረውና ከቀረጥ ሰብሳቢነት ሐዋርያ የሆነው ማቴዎስ በመጀመሪያ በይሁዳ ምድር
በዕብራይስጥ ቋንቋ የክርስቶስን ወንጌል አጠናቀረ። . . . ከዚያ በኋላ ወደ ግሪክኛ
የተረጎመው ማን እንደሆነ በውል አይታወቅም። የዕብራይስጡ ቅጂ ግን እስከ ዛሬ ድረስ
በቂሣርያ በሚገኝ ቤተ መጻሕፍት ውስጥ ይገኛል።”

ማቴዎስ የጻፈው በዕብራይስጥ ቋንቋ በመሆኑ በተለይ ‘ከብሉይ ኪዳን’ ጠቅሶ በሚጽፍበት
ጊዜ በአምላክ ስም አልተጠቀመም ማለት ፈጽሞ የማይታሰብ ነገር ነው። ይሁን እንጂ
ሁለተኛውን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የጻፉት ሌሎች ጸሐፊዎች መጽሐፎቻቸውን የጻፉት
ለዓለም አቀፍ አንባቢዎች ስለነበረ የጻፉበት ቋንቋ በዘመኑ ዓለም አቀፍ ቋንቋ የነበረው
ግሪክኛ ነበር። በዚህም ምክንያት ከ“ብሉይ ኪዳን” በሚጠቅሱበት ጊዜ ከዕብራይስጡ በኩረ
ጽሑፎች ሳይሆን ከግሪክኛው ሰፕቱጀንት ትርጉም ይጠቅሱ ነበር። የማቴዎስ ወንጌልም
ቢሆን ከጊዜ በኋላ ወደ ግሪክኛ ተተርጉሟል። በእነዚህ የግሪክኛ ጽሑፎች ውስጥ የአምላክ
ስም ይገኝ ነበርን?

በኢየሱስ ዘመን ከነበረው የሰፕቱጀንት ትርጉም እስከ ዘመናችን ድረስ ተጠብቀው የቆዩ
በጣም ያረጁ ብጥስጣሾች ይገኛሉ፤ በእነዚህ ቅዳጆች ላይ የአምላክ ስም ተጽፎ መገኘቱም
ከፍተኛ ግምት ሊሰጠው የሚገባ ነገር ነው። ዘ ኒው ኢንተርናሽናል ዲክሽነሪ ኦቭ ኒው
ተስታመንት ቲኦሎጂ (ጥራዝ 2፣ ገጽ 512) እንዲህ ይላል:- “በቅርቡ በተገኙ የጽሑፍ
ማስረጃዎች ምክንያት የሰፕቱጀንት አጠናቃሪዎች የሐወሐ የሚለውን
ቴትራግራማተን ኪሪዮስ እያሉ ተርጉመዋል የሚለው አስተሳሰብ እውነት መሆኑ በጣም
አጠራጣሪ ሆኗል። በአሁኑ ጊዜ በሚገኙት እጅግ ጥንታዊ የሆኑ የሰፕቱጀንት ቅጂ ቅዳጆች
ላይ በግሪክኛው ጽሑፍ መካከል ቴትራግራማተኑ በዕብራይስጥ ፊደላት ተጽፎ ይታያል።
በመጀመሪያው መቶ ዘመን የነበሩ አይሁዳውያን የብሉይ ኪዳን ተርጓሚዎችም ይህንኑ
ልማድ ይከተሉ ነበር።” ስለዚህ ኢየሱስም ሆነ ደቀ መዛሙርቱ የሚያነቡት ቅዱስ ጽሑፍ
ዕብራይስጥ ወይም ግሪክኛ ቢሆን መለኮታዊውን ስም ማግኘታቸው አይቀርም ነበር።

በዚህ ምክንያት በአሜሪካ አገር የሚገኘው የጆርጂያ ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰር የሆኑት ጆርጅ
ሐዋርድ የሚከተለውን አስተያየት ሰጥተዋል:- “የአዲስ ኪዳኑ ቤተ ክርስቲያን
ይጠቀምበትና ይጠቅሰው በነበረው በሰፕቱጀንት ትርጉም ውስጥ መለኮታዊው ስም
በዕብራይስጥ ፊደላት ተጽፎ ይገኝ በነበረበት ጊዜ ሁሉ የአዲስ ኪዳን ጸሐፊዎች
ቴትራግራማተንን በጥቅሶቻቸው ውስጥ ይጽፉ እንደነበረ አያጠራጥርም።” (ቢብ ሊካል
አርኪዮሎጂ ሪቪው፣ መጋቢት 1978፣ ገጽ 14) ከዚህ የተለየ ነገር ለማድረግ ምን ሥልጣን
ሊኖራቸው ይችላል?

የአምላክ ስም በግሪክኛ የ“ብሉይ ኪዳን” ትርጉም ውስጥ ለጥቂት ጊዜ ቆይቷል።


በሁለተኛው መቶ ዘመን እዘአ የመጀመሪያ አጋማሽ ወደ አይሁድ እምነት ገብቶ የነበረው
አቂላ የዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሑፎችን ወደ ግሪክኛ ሲተረጉም የአምላክን ስም
የሚወክለውን ቴትራግራማተን በጥንታዊው የዕብራይስጥ ፊደል ጽፏል። በሦስተኛው
መቶ ዘመን ደግሞ አሪገን እንዲህ ሲል ጽፏል:- “በጣም ትክክለኛ በሆኑት የእጅ ጽሑፍ
ቅጂዎች ውስጥ ስሙ በዛሬው ሳይሆን በጣም ጥንታዊ በሆነው የዕብራይስጥ ፈደል ተጽፎ
ይገኛል።”

በአራተኛው መቶ ዘመን እንኳ ዤሮም ለመጽሐፈ ሳሙኤልና ለመጽሐፈ ነገሥት በጻፈው


መቅድም ላይ እንዲህ ብሏል:- “የአምላክን ስም ማለትም ቴትራግራማተንን [‫]יהוה‬
እስከዚህ ዘመን ድረስ እንኳን በአንዳንድ የግሪክኛ ጥራዞች ውስጥ በጥንታዊ ፊደላት ተጽፎ
እናገኛለን።”

የመለኮታዊው ስም መወገድ

ይሁን እንጂ በዚህ ጊዜ ኢየሱስ ይመጣል ሲል የተነበየለት ክህደት መከሰት ጀምሮ ስለነበር
የአምላክም ስም በጽሑፎች ላይ ተጽፎ የሚገኝ ቢሆንም ቀስ በቀስ ከአገልግሎት ውጭ
እየሆነ መጣ። (ማቴዎስ 13:24–30፤ ሥራ 20:29, 30) እንዲያውም ከጊዜ በኋላ ብዙ
አንባቢዎች የቴትራግራማተንን ምንነት እንኳን ፈጽመው የማያውቁ ሆኑ። ዤሮም
በዘመኑ “አንዳንድ ደንቆሮዎች [ቴትራግራማተንን] በግሪክኛ መጻሕፍት ውስጥ
በሚያገኙበት ጊዜ ከፊደሎቹ መመሳሰል የተነሣ ΠΙΠΙ (የግሪክኛ ፊደላት ሲሆኑ “ፒፒ”
ተብለው ይነበባሉ) ብለው ያነቡ ነበር” ብሏል።

በኋለኞቹ ዘመናት በተጻፉት የሰፕቱጀንት ቅጂዎች ውስጥ የአምላክ ስም ተወግዶ እንደ


“አምላክ” (ቴኦስ ) እና “ጌታ” (ኪሪዮስ ) ያሉ ቃላት ተተክተዋል። ይህን ለማለት
የምንችለው የአምላክ ስም የተጻፈበት ቀደም ያለ የሰፕቱጀንት መጽሐፍ ቅዱስ ብጣሽና
የአምላክ ስም የማይገኝበት ከዚሁ ብጣሽ ጋር አንድ የሆነ በኋለኞቹ ዘመናት የተገለበጠ
ብጣሽ ስለምናገኝ ነው።

“በአዲስ ኪዳን” ወይም በክርስቲያን ግሪክኛ ቅዱሳን ጽሑፎች ላይም ተመሳሳይ ድርጊት
ተፈጽሟል። ፕሮፌሰር ጆርጅ ሐዋርድ በመቀጠል እንዲህ ብለዋል:- “በዕብራይስጥ ሆሄያት
ይጻፍ የነበረው የአምላክ ስም በሰፕቱጀንት ውስጥ በግሪክኛ ቃላት መተካት ሲጀመር
በአዲስ ኪዳን ውስጥ ከሚገኙ የሰፕቱጀንት ጥቅሶችም ተወገደ። . . . ብዙም ሳይቆይ
መለኮታዊው ስም በአንዳንድ ቃላት ላይ ተለጣፊ ሆኖ ከመግባቱና በአንዳንድ ምሁራን
ዘንድ ከመታወቁ በስተቀር ከአሕዛብ ቤተ ክርስቲያን እይታ ፈጽሞ ተወገደ።”

ስለዚህ አይሁዳውያን የአምላክን ስም ለመጥራት እምቢተኞች ሲሆኑ የከሐዲዋ ክርስትና


ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ከሁለቱም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች የግሪክኛና የሌሎች ቋንቋዎች
ትርጉሞች ፈጽማ አስወጥታለች።

የስሙ አስፈላጊነት

ከጊዜ በኋላ ግን ቀደም ስንል እንደተመለከትነው መለኮታዊው ስም በብዙዎቹ የዕብራይስጥ


ቅዱሳን ጽሑፎች ትርጉሞች ውስጥ ተመልሶ ሊገባ ችሏል። በግሪክኛ ቅዱሳን ጽሑፎችስ
ውስጥስ? የመጽሐፍ ቅዱስ ተርጓሚዎችና አጥኚዎች የአምላክ ስም ካልተጨመረባቸው
ለመረዳት የሚያስቸግሩ አንዳንድ የግሪክኛ ቅዱሳን ጽሑፎች ክፍሎች እንዳሉ ተገነዘቡ።
የስሙ ወደ ቦታው መመለስ በመንፈስ አነሣሽነት ለተጻፈው ለዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል
ግልጽነትና ትክክለኛ ግንዛቤ መጨመር ከፍተኛ እርዳታ አበርክቷል።

ለምሳሌ ጳውሎስ ለሮማውያን የጻፈውን ቃል በኦቶራይዝድ ቨርሽን ተጽፎ እንደሚገኘው


እናንብብ:- “የጌታን ስም የሚጠራ ማንኛውም ሰው ይድናልና” ይላል። (ሮሜ 10:13)
ለመዳን የምንጠራው የማንን ስም ነው? ኢየሱስ ብዙ ጊዜ “ጌታ” ተብሎ ስለተጠራና
እንዲያውም አንድ ጥቅስ “በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እመን . . . ትድናላችሁ” ስለሚል
ጳውሎስ እዚህ ላይ የሚናገረው ስለ ኢየሱስ ነው ብለን መደምደም ይገባናልን? — ሥራ
16:31

የለም፣ እንዲህ ማለት አንችልም። በኦቶራይዝድ ቨርሽን በሮሜ 10:13 አንጻር የገባው
የህዳግ ማጣቀሻ በዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሑፎች ውስጥ የሚገኘውን ኢዩኤል 2:
32 ን ይጠቅሳል። ይህን ጥቅስ አውጥተህ ብትመለከት ጳውሎስ ለሮማውያን በጻፈው
ደብዳቤ ላይ የኢዩኤልን ቃል በቀጥታ ጠቅሶ እንደጻፈ መገንዘብ ትችላለህ። ኢዩኤል ደግሞ
በዕብራይስጡ በኩረ ጽሑፍ ያለው “የይሖዋን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል” ነው። (አዲሲቱ
ዓለም ትርጉም ) አዎን፣ ጳውሎስ የይሖዋን ስም መጥራት እንደሚገባን መናገሩ ነበር።
ስለዚህ በኢየሱስ ማመን ቢኖርብንም መዳናችን ግን ለአምላክ ስም ካለን አድናቆትና
ግንዛቤ ጋር በቅርብ የተሳሰረ ነው።
ይህ ምሳሌ የአምላክ ስም ከግሪክኛ ቅዱሳን ጽሑፎች በመወገዱ ምክንያት ብዙ ሰዎች ስለ
ይሖዋና ስለ ኢየሱስ ማንነት እንዴት ግራ ሊጋቡ እንደቻሉ ያሳያል። ለሥላሴ መሠረተ
ትምህርት መፈጠር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳደረገ አያጠራጥርም!

መለኮታዊው ስም ወደ ቦታው መመለስ ይኖርበታልን?

አንድ ተርጓሚ መለኮታዊውን ስም፣ በተለይ በአሁኑ ጊዜ በሚገኙት ጥንታዊ ጽሑፎች


ውስጥ የማይገኝ ሆኖ እያለ፣ በትርጉሙ ውስጥ ለማስገባት መብት ሊኖረው ይችላልን?
አዎን፣ ይኖረዋል። አብዛኞቹ የግሪክኛ መዝገበ ቃላት አዘጋጆች “ጌታ” የሚለው ቃል
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይሖዋን እንደሚያመለክት ይገነዘባሉ። ለምሳሌ ያህል በሮቢንሰን
የተዘጋጀው ኤ ግሪክ ኤንድ ኢንግሊሽ ሌክሲከን ኦቭ ዘ ኒው ተስታመንት (በ 1859
የታተመ) ኪርዮስ (“ጌታ”) በሚለው ቃል ሥር “የሁሉ የበላይ የሆነ ጌታ እና የአጽናፈ
ዓለሙ ሉዓላዊ ገዥ፣ በሰፕቱጀንት ትርጉም ውስጥ በዕብራይስጥ ‫ יהוה‬ይሖዋ ተብሎ
የሚጻፈው” ማለት እንደሆነ ይገልጻል። ስለዚህ የክርስቲያን ግሪክኛ ቅዱሳን ጽሑፎች
ጸሐፊዎች ከዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሑፎች በሚጠቅሱባቸው ቦታዎች
ተርጓሚው ኪርዮስ የሚለውን ቃል መለኮታዊው ስም በበኩረ ጽሑፉ ላይ ይገኝባቸው
በነበሩ ቦታዎች ሁሉ “ይሖዋ” ብሎ ለመተርጎም መብት አለው።

ብዙ ተርጓሚዎችም እንዲሁ አድርገዋል። ቢያንስ ከ 14 ኛው መቶ ዘመን ጀምሮ ግሪክኛ


የክርስቲያን ቅዱሳን ጽሑፎች ብዙ ጊዜ ወደ ዕብራይስጥ ተተርጉመዋል። ታዲያ
ተርጓሚዎቹ የአምላክ ስም የሚገኝባቸው “የብሉይ ኪዳን” ክፍሎች ‘በአዲስ ኪዳን’ ውስጥ
ተጠቅሶ ሲያገኙ ምን አድርገዋል? አብዛኛውን ጊዜ የአምላክን ስም ጨምረው
ለመተርጎም ተገድደዋል። በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ወደ ዕብራይስጥ ቋንቋ በተተረጎሙ
የክርስቲያን ግሪክኛ ቅዱሳን ጽሑፎች ውስጥ የአምላክ ስም ይገኛል።

በዘመናዊ ቋንቋ የተተረጐሙ በርካታ ትርጉሞችም፣ በተለይ ሚስዮናውያን ይገለገሉባቸው


የነበሩ ትርጉሞች የእነዚህን ተርጓሚዎች ምሳሌ ተከትለዋል። በዚህም ምክንያት በብዙ
የአፍሪካ፣ የእስያ፣ የአሜሪካና የፓስፊክ ደሴቶች ቋንቋዎች በተተረጎሙ የግሪክኛ ቅዱሳን
ጽሑፎች ውስጥ ይሖዋ የሚለው ስም በብዙ ቦታዎች ስለሚገኝ አንባቢዎች
በእውነተኛው አምላክና በሐሰተኞቹ አማልክት መካከል ያለውን ልዩነት በግልጽ ሊገነዘቡ
ችለዋል። ስሙ በአንዳንድ የአውሮፓ ቋንቋዎች ትርጉሞችም ላይ ገብቷል።

የአምላክን ስም በጥሩ መረጃዎች በመደገፍ ቀድሞ ወደነበረው ቦታ በድፍረት ከመለሱት


ትርጉሞች አንዱ ግሪክኛ የክርስቲያን ቅዱሳን ጽሑፎች የአዲሲቱ ዓለም ትርጉም ነው።
ይህ በአሁኑ ጊዜ እንግሊዝኛን ጨምሮ በ 13 የተለያዩ ቋንቋዎች የተዘጋጀው ትርጉም
የአምላክ ስም የሚገኝባቸው የዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሑፎች በተጠቀሱባቸው የግሪክኛ
ቅዱሳን ጽሑፎች ክፍሎች ሁሉ የአምላክን ስም አስገብቷል። በዚህ የግሪክኛ ቅዱሳን
ጽሑፎች ትርጉም ውስጥ የአምላክ ስም በጠቅላላው 237 ጊዜ ተጠቅሷል።

በስሙ ላይ የተነሣ ተቃውሞ

ብዙ ተርጓሚዎች የአምላክን ስም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለማስገባት ብርቱ ጥረት


ቢያደርጉም ይህን ስም ለማስወጣት ሃይማኖታዊ ግፊት መደረጉ አላቆመም።
አይሁዳውያን ከመጽሐፍ ቅዱሳቸው ውስጥ ባያስወጡትም በአፋቸው ለመጥራት
አሻፈረን ብለዋል። የሁለተኛውና የሦስተኛው መቶ ዘመን ከሃዲ ክርስቲያኖች የግሪክኛ
መጽሐፍ ቅዱስ ቅጂዎችን በሚገለብጡበት ጊዜ ስሙን ከማስወጣታቸውም በላይ
መጽሐፍ ቅዱስን ወደ ሌሎች ቋንቋዎች በሚተረጉሙበት ጊዜ አስወጥተውታል። ዘመናዊ
ተርጓሚዎችም ቢሆኑ ትርጉማቸው የአምላክ ስም ወደ 7,000 ጊዜ ያህል በሚገኝበት
በዕብራይስጡ በኩረ ጽሑፍ ላይ የተመሠረተ ቢሆንም መለኮታዊውን ስም ከትርጉማቸው
አውጥተዋል። (በአዲሲቱ ዓለም የቅዱሳን ጽሑፎች ትርጉም የ 1984 እትም ላይ
በዕብራይስጥ ጽሑፎች ውስጥ 6,973 ጊዜ ተጠቅሷል።)

ታዲያ ይሖዋ ስሙን ከመጽሐፍ ቅዱስ የሚያስወጡትን ሰዎች እንዴት ያያቸዋል? አንተ
ደራሲ ብትሆንና አንድ ሰው ሆን ብሎ ስምህን አንተ ከደረስከው መጽሐፍ ውስጥ ጨርሶ
ቢያጠፋ ስለዚያ ሰው ምን ይሰማሃል? በአጠራር ችግር በማሳበብም ሆነ የአይሁዳውያንን
ወግ በመከተል የአምላክን ስም ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚያስወጡ ተርጓሚዎች
ኢየሱስ “ትንኝን የምታጠሩ ግመልንም የምትውጡ” ያላቸውን ሰዎች ይመስላሉ።
(ማቴዎስ 23:24) በእነዚህ ትናንሽ ችግሮች ተሰናክለው የመላው ጽንፈ ዓለም የበላይ
የሆነውን አምላክ ስም ራሱ ካዘጋጀው መጽሐፍ ውስጥ በማስወጣታቸው በጣም ከባድ
የሆነ ችግር ፈጥረዋል።

መዝሙራዊው “አቤቱ [አምላክ ሆይ] ጠላት እስከ መቼ ይሳደባል? ጠላት ስምህን ሁልጊዜ
ያቃልላልን?” ብሏል። — መዝሙር 74:10 አዓት

[በገጽ 25 ላይ የሚገኝ ሣጥን]

“ጌታ” የሚለው “ይሖዋ” ከሚለው ስም ጋር አንድ ነውን?


አምላክ ተለይቶ የሚታወቅበትን የተጸውኦ ስም ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አስወጥቶ እንደ
“ጌታ” ወይም “አምላክ” ባሉት የማዕረግ ስሞች መተካት የጽሑፉን ኃይል ከማዳከሙም
በላይ በብዙ መንገዶች ጎደሎ ያደርገዋል። ለምሳሌ ያህል ትርጉም የለሽ የቃላት ድግግሞሽ
ሊያስከትል ይችላል። ዘ ጀሩሳሌም ባይብል በመቅድሙ ላይ እንዲህ ይላል:- “‘ያህዌህ
አምላክ ነው’ ማለት ግልጽ ትርጉም ያለው አባባል ሲሆን ‘ጌታ አምላክ ነው’ ማለት ግን
ትርጉም የሌለውና አስፈላጊ ያልሆነ የቃላት ድግግሞሽ ነው።”

ከዚህም በላይ ይህ ዓይነቱ መለኮታዊውን ስም በማዕረግ ስም የመተካት ተግባር ለአንዳንድ


ግራ የሚያጋቡ ሐረጎች መፈጠር ምክንያት ሊሆን ይችላል። ለምሳሌ መዝሙር 8:
9 በኦቶራይዝድ ትርጉም እንዲህ ይነበባል:- “አቤቱ ጌታ ጌታችን ሆይ፣ ስምህ ምንኛ
በመላው ምድር ግሩም ነው!” እንዲህ ባለው ጥቅስ ላይ ይሖዋ የሚለው ስም ሲጨመር
የጥቅሱ ትርጉም ምን ያህል ግልጽ እንደሚሆን ማስተዋል ይቻላል። ያንግስ ሊተራል
ትራንስሌሽን ኦቭ ዘ ሆሊ ባይብል “ጌታችን ይሖዋ ሆይ፣ ስምህ በመላው ምድር ላይ ምን
ያህል የተከበረ ነው!” ይላል።

በተጨማሪም ስሙን ማውጣት ግራ መጋባት ሊያስከትል ይችላል። መዝሙር 110:1 “ጌታ


ጌታዬን፣ ጠላቶችህን ለእግርህ መቀመጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው”
ይላል። (ኦቶራይዝድ ቨርሽን ) እዚህ ላይ ተናጋሪው ማነው? የሚናገረውስ ለማነው?
“ይሖዋ ለጌታዬ የተናገረው ቃል ‘ጠላቶችህን የእግርህ መቀመጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ
ተቀመጥ ይላል’ ” ተብሎ ሲተረጎም ትርጉሙ ምን ያህል ግልጽ እንደሚሆን ማስተዋል
ይቻላል።— የአዲሲቱ ዓለም ትርጉም

በተጨማሪም “ይሖዋ” የሚለውን ስም በ“ጌታ” መተካት አንድ በጣም ወሳኝ የሆነ ነገር
ከመጽሐፍ ቅዱስ እንዲወገድ ምክንያት ይሆናል። እርሱም የአምላክ የተጸውኦ ስም
ነው። ዘ ኢላስተረትድ ባይብል ዲክሽነሪ (ጥራዝ 1፣ ገጽ 572) “እንደ እውነቱ ከሆነ
ብቸኛው የአምላክ ‘ስም’ ያህዌህ ነው” ይላል።

ዘ ኢምፐሪያል ባይብል ዲክሽነሪ (ጥራዝ 1፣ ገጽ 856) “በአምላክ” (ኤሎሂም ) እና


“ይሖዋ” በሚለው መጠሪያ መካከል ያለውን ልዩነት እንዲህ ሲል ይገልጻል:- “[ይሖዋ]
በየትም ቦታ የእውነተኛው አምላክ የእርሱ ብቻ የግል መታወቂያ፣ የተጸውኦ ስም ሲሆን
ኤሎሂም ግን ይበልጥ የወል ስምነት ባሕርይ ያለው የግዴታ ወይም ሁልጊዜ ባይሆንም
አብዛኛውን ጊዜ ከሁሉ በላይ የሆነውን አምላክ የሚያመለክት ቃል ነው።”
እንግሊዝ አገር ያለው የትሪኒቲ ኮሌጅ ርዕሰ መምህር የሆኑት ጄ ኤ ሞትየር እንዲህ
በማለት ይጨምራሉ:- “በምትክነት ከሚገቡት [ጌታ ወይም አምላክ] ቃላት አልፈን
የአምላክን የግልና የተጸውኦ ስም ለመመልከት ብንረሳ ከመጽሐፍ ቅዱስ ንባባችን ማግኘት
የሚገባንን ብዙ ጥቅም ሳናገኝ እንቀራለን። አምላክ ስሙን ለሕዝቦቹ ያስታወቃቸው
ውስጣዊ ባሕርዩን ሊገልጻላቸው ስለፈለገ ነው።”— ኤርድማንስ ሃንድቡክ ቱ ዘ
ባይብል ገጽ 157

አምላክ ተለይቶ የሚታወቅበትን የተጸውኦ ስም ተራ በሆነ የማዕረግ ስም መለወጥ ፈጽሞ


አይቻልም። ማንኛውም የማዕረግ ስም የመጀመሪያው የአምላክ ስም የሚያስተላልፈውን
የተሟላና የበለጸገ ትርጉም ሊያስተላልፍ አይችልም።

[በገጽ 26 ላይ የሚገኝ ሣጥን/ሥዕል]

ይህ በመጀመሪያው መቶ ዘመን እዘአ የተጻፈ ነው ተብሎ የሚታሰበው ዘካርያስ 8:19–21


እና 8:23 እስከ 9:4 የሚገኝበት የሰፕቱጀንት ትርጉም ቅዳጅ (በስተቀኝ) በኢየሩሳሌም
በእስራኤል ቤተ መዘክር ይገኛል። የአምላክ ስም በአራት ቦታዎች ላይ የሚገኝበት ቅዳጅ
ሲሆን ሦስቱ በሥዕሉ ላይ ተመልክተዋል። ከ 400 ዓመት በኋላ በተጻፈው አለክሳንድሪን
ማኑስክሪፕት በተባለው የሰፕቱጀንት ግልባጭ ላይ ግን (በስተግራ) በእነዚሁ ቁጥሮች ላይ
የሚገኘው የአምላክ ስም ኪሪዮስ (“ጌታ”) የተባለው የግሪክኛ ቃል ምህጻረ ቃል
በሆነው KY እና KC ተተክቷል

[በገጽ 27 ላይ የሚገኝ ሣጥን]

ጆን ደብልዩ ዴቪስ የተባለ በ 19 ኛው መቶ ዘመን በቻይና ይኖር የነበረ ሚስዮናዊ የአምላክ


ስም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ መግባት ይኖርበታል ብሎ የሚያምንበትን ምክንያት እንዲህ
በማለት ገልጿል:- “መንፈስ ቅዱስ በማንኛውም ሥፍራ ላይ በዕብራይስጥ ይሖዋ ካለ
ተርጓሚው በእንግሊዝኛም ይሁን በቻይንኛ ይሖዋ የማይልበት ምን ምክንያት አለ? በዚህ
ቦታ ይሖዋ የሚለውን አጠራር እጠቀማለሁ፣ በዚያኛው ቦታ ላይ ደግሞ ምትክ በሚሆን
ሌላ ቃል እጠቀማለሁ የሚልበት ምን መብት አለው? . . . ይሖዋ በሚለው ስም መጠቀም
ስህተት የሚሆንባቸው ቦታዎች አሉ የሚል ሰው ካለ ምክንያቱን ያሳየን። ማስረጃ
የማቅረቡ ግዴታ የሚያርፈው በእርሱ ላይ ነው። ይህም ቀላል ሥራ አይሆንለትም፤
ምክንያቱም በትርጉሞች ውስጥ ይሖዋ በሚለው ስም መጠቀም ስህተት የሚሆንበት
አንድ ቦታ እንኳን ከኖረ በኩረ ጽሑፉን በመንፈስ አነሣሽነት የጻፈው ሰው ለምን በዚህ
ስም ተጠቀመ? ለሚለው ቀላል ጥያቄ መልስ መስጠት ይኖርበታል።”
የአምላክ ስም — ትርጉሙና አነባበቡ
የአምላክ ስም—ትርጉሙና አነባበቡ

ከመጽሐፍ ቅዱስ ጸሐፊዎች አንዱ እንደሚከተለው በማለት ጠይቆ ነበር:- “ነፋስንስ በእጁ
የጨበጠ ማን ነው? ውኃንስ በልብሱ የቋጠረ ማን ነው? የምድርን ዳርቻ ሁሉ ያጸና ማን
ነው? ይህን ታውቅ እንደ ሆንህ፣ ስሙ ማን የልጁስ ስም ማን ነው?” (ፊደላቱን ጋደል
አድርገን የጻፍናቸው እኛ ነን።) (ምሳሌ 30:4) እኛስ የአምላክ ስም ማን እንደሆነ ልናውቅ
የምንችለው እንዴት ነው? ይህ በጣም አስፈላጊ የሆነ ጥያቄ ነው። ፍጥረት አምላክ
ለመኖሩ ጠንካራ ማረጋገጫ የሚሰጠን ቢሆንም ስሙን ግን አይነግረንም። (ሮሜ
1:20) ፈጣሪ ራሱ ባይነግረን ኖሮ የአምላክ ስም ማን እንደሆነ ለማወቅ አንችልም ነበር።
የራሱ መጽሐፍ በሆነው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስሙን ገልጦልናል።

በአንድ ታላቅ ታሪካዊ ወቅት አምላክ ሙሴ እያዳመጠው የራሱን ስም ደጋግሞ ጠርቷል።


ሙሴ በዚያ ጊዜ የሆነውን ነገር ጽፎ ያቆየልን ሲሆን ይህም ታሪክ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ
ይገኛል። (ዘጸአት 34:5) እንዲያውም አምላክ የገዛ ስሙን በራሱ “ጣት” ጽፏል። አምላክ
በአሁኑ ጊዜ አሥርቱ ትእዛዛት ብለን የምንጠራቸውን ሕግጋት ለሙሴ የሰጠው ራሱ
በተአምር ጽፎ ነው። ታሪኩ እንዲህ ይላል:- “እግዚአብሔርም ከሙሴ ጋር በሲና ተራራ
የተናገረውን በፈጸመ ጊዜ በእግዚአብሔር ጣት የተጻፈባቸውን ከድንጋይ የሆኑ ሁለቱን
የምስክር ጽላቶች ሰጠው።” (ዘጸአት 31:18) የአምላክ ስም በመጀመሪያው አሥርቱ
ትእዛዛት ውስጥ ስምንት ጊዜ ተጠቅሷል። (ዘጸአት 20:1–17) ስለዚህ አምላክ ራሱ የገዛ
ስሙን በቃልም ሆነ በጽሑፍ ለሰዎች ገልጧል። ታዲያ ይህ ስም ማን ነው?

ስሙ በዕብራይስጥ ቋንቋ ‫ יהוה‬ተብሎ ይጻፋል። እነዚህ ቴትራግራማተን ተብለው


የሚጠሩት አራት ፊደላት በዕብራይስጥ የሚነበቡት ከቀኝ ወደ ግራ ሲሆን በብዙዎች
የዘመናችን ቋንቋዎች የሐወሐ ወይም ጀሐቨሐ በሚሉት ሆሄያት ሊወከሉ ይችላሉ።
በእነዚህ አራት ተነባቢ ሆሄያት የሚወከለው የአምላክ ስም በመጀመሪያው የ“ብሉይ ኪዳን”
ቅጂ ወይም የዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሑፎች ውስጥ ወደ 7, 000 ጊዜ ያህል ይገኛል።

ስሙ ሐዋሕ (‫ )הוה‬ከተባለው “መሆን” የሚል ትርጉም ካለው የዕብራይስጥ ግሥ በእርባታ


የተገኘ ሲሆን “ይሆናል” ማለት ነው።* ስለዚህ የአምላክ ስም አምላክ የገባውን ቃል ደረጃ
በደረጃ የሚፈጽም መሆኑንና ዓላማውን ከመፈጸም የሚያግደው ምንም ነገር የሌለ
መሆኑን ያመለክታል። ከአምላክ በቀር ማንም እንዲህ ያለ ከፍተኛ ትርጉም ያለው ስም
ሊኖረው አይችልም።ቀደም ባለው ክፍል (በገጽ 5 ላይ) የአምላክ ስም በመዝሙር
83:18 ላይ እንዴት ባለ የተለያየ መንገድ እንደተጻፈ ታስታውሳለህን? ሁለቱ ትርጉሞች
የአምላክ ስም ምትክ አድርገው ያሰፈሩት የማዕረግ ስሞችን (“ጌታ”፣ “ዘላለማዊው”)
ነው። በሁለቱ ትርጉሞች ላይ በሰፈሩት ይሖዋ እና ያህዌህ ግን የአምላክን ስም
የሚወክሉት አራቱ ፊደሎች እንደሚገኙ ማስተዋል ይቻላል። ይሁን እንጂ የስሙ አጠራር
ወይም አነባበብ የተለያየ ነው። ይህ የሆነው ለምንድን ነው?

የአምላክ ስም የሚነበበው እንዴት ነው?

እንደ እውነቱ ከሆነ የመጀመሪያውን የአምላክ ስም አጠራር ወይም አነባበብ አስረግጦ


የሚያውቅ ሰው የለም። ለምን? ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈበት የመጀመሪያ
ቋንቋ ዕብራይስጥ ሲሆን የዕብራይስጥ ቋንቋ በሚጻፍበት ጊዜ ጸሐፊው የሚጽፈው አናባቢ
ሆሄያትን እየጨመረ ሳይሆን ተነባቢ ሆሄያትን ብቻ ነበር። በዚህም ምክንያት መጽሐፍ
ቅዱስን በመንፈስ ቅዱስ አነሣሽነት የጻፉትም ሰዎች የአምላክን ስም በሚጽፉበት ጊዜ
የጻፉት ስሙን የሚወክሉትን ተነባቢ ሆሄያት ብቻ ነው።

የዕብራይስጥ ቋንቋ በየዕለቱ የሚሠራበት የመነጋገሪያ ቋንቋ በነበረበት የጥንት ዘመን ይህ


አጻጻፍ ምንም ችግር አላስከተለም ነበር። የአምላክ ስም አጠራር በእስራኤላውያን ዘንድ
በሚገባ የታወቀ ስለነበረ ማንኛውም አንባቢ አናባቢዎቹን ፊደል ራሱ ጨምሮ
ያለችግር ሊያነብ ይችል ነበር። (አንድ አማርኛ አንባቢ “ዓ.ም.” ወይም “ወ/ሮ” የሚሉትን
አሕጽሮተ ቃላት ሲመለከት “ዓመተ ምህረት” ወይም “ወይዘሮ” ብሎ እንደሚያነበው
ማለት ነው።)

ይህ ሁኔታ እንዲለወጥ ምክንያት የሆኑ ሁለት ነገሮች ተፈጽመዋል። የመጀመሪያው


በአይሁዳውያን መካከል የአምላክን ስም ጮክ ብሎ መጥራት ትክክል አይደለም የሚል
አጉል እምነት መስፋፋቱና መጽሐፍ ቅዱስን በሚያነቡበት ጊዜ የአምላክ ስም በተጻፈበት
ቦታ ላይ ሲደርሱ የአምላክን ስም ከመጥራት ይልቅ አዶናይ (“ሉዓላዊ ጌታ”) ብለው
ማንበባቸው ነው። ከዚህም በላይ ዘመናት እያለፉ ሲሄዱ የጥንቱ የዕብራይስጥ ቋንቋ
የዕለት ተዕለት መነጋገሪያ መሆኑ እየቀረ በመምጣቱ የመጀመሪያው የአምላክ ስም አነባበብ
ወይም አጠራር እየተረሳ ሄደ።

በሁለተኛው ሺህ አጋማሽ እዘአ ይኖሩ የነበሩ የዕብራይስጥ ቋንቋ ምሁራን የዕብራይስጥ


ቋንቋ አነባበብ ጠፍቶ እንዳይቀር በማሰብ በጽሑፎች ላይ መጨመር የሚኖርባቸውን
አናባቢ ሆሄያት የሚያመለክቱበት ሥርዓተ ነጥብ ፈለሰፉ፤ እነዚህንም ነጥቦች በዕብራይስጥ
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በሚገኙት ተነባቢ ሆሄያት ላይ ጨምረዋል። በዚህ መንገድ
ተነባቢዎቹ ሆሄያትም ሆኑ አናባቢዎቹ ተጽፈው ስለቆዩልን በዘመኑ የነበረው አነባበብ
ተጠብቆ ሊተላለፍ ችሏል።

አምላክ ስም ላይ ሲደርሱ ግን በተነባቢዎቹ ሆሄያት ላይ ትክክለኞቹን አናባቢዎች


ከመጨመር ይልቅ አብዛኛውን ጊዜ አንባቢው አዶናይ ብሎ እንዲያነብ የሚያሳስቡ ሌሎች
አናባቢ ምልክቶችን ጽፈዋል። ኢሁዋህ የሚለው አነባበብ የመጣው በዚህ ምክንያት ሲሆን
ከጊዜ በኋላ ጅሆቫ የሚለው የመለኮታዊ ስም አጠራር በእንግሊዝኛ ቋንቋ ሰፊ ተቀባይነት
አግኝቷል። በዚህ አነባበብ ወይም አጠራር ውስጥ የመጀመሪያው ዕብራይስጥ መሠረታዊ
ድምፆች ይገኛሉ።

በየትኛው አነባበብ ወይም አጠራር ትጠቀማለህ?

ታዲያ እንደ ያህዌህ ያሉት አጠራሮች የመጡት ከየት ነው? የመጀመሪያውን የአምላክ
ስም አጠራር ለማወቅ ሙከራ ያደረጉ ዘመናዊ ምሁራን የተሻሉ ናቸው ያሏቸው
አጠራሮች ናቸው። ሁሉም ሳይሆኑ አንዳንድ ምሁራን ከኢየሱስ ዘመን በፊት የነበሩት
አይሁዳውያን የአምላክን ስም ያህዌህ ብለው ሳይጠሩ አይቀሩም ብለው ያስባሉ። ይሁን
እንጂ በእርግጠኛነት ሊናገር የሚችል ሰው የለም። በዚህ ዓይነት አጠራር ሊጠቀሙም
ላይጠቀሙም ይችላሉ።

ያም ሆነ ይህ ብዙዎች ይሖዋ የሚለውን አጠራር ይመርጣሉ። ለምን? ምክንያቱም


ያህዌህ ከሚለው አጠራር የበለጠ የተለመደና በሰፊው የሚሠራበት ስለሆነ ነው። ታዲያ
ከመጀመሪያው አጠራር ጋር ሊቀራረብ በሚችል አጠራር መጠቀሙ የተሻለ አይሆንም?
በመጽሐፍ ቅዱስ ስሞች ረገድ ይህን የመሰለ ልማድ ስለማንከተል እንደዚህ ለማለት
አይቻልም።

በዚህ ረገድ በዋነኛነት ሊጠቀስ የሚችለውን የኢየሱስ ስም እንደ ምሳሌ


እንውሰድ። አንተ ኢየሱስ በልጅነቱ ይኖር በነበረበት የናዝሬት ከተማ ቤተሰቦቹና ጓደኞቹ
ዕለት ተዕለት ሲያነጋግሩት ምን ብለው ይጠሩት እንደነበረ ታውቃለህ? የሹዋ (ምናልባትም
የሆሹዋ) ብለው ሳይጠሩት እንደማይቀር ቢታሰብም ማንም ሰው በእርግጠኝነት ለመናገር
አይችልም። ኢየሱስ ወይም ጂሰስ ተብሎ ይጠራ እንዳልነበረ ግን የተረጋገጠ ነው።

የኢየሱስ ሕይወት ታሪክ በግሪክኛ ቋንቋ በተጻፈበት ጊዜ ግን በመንፈስ አነሣሽነት የጻፉት


ጸሐፊዎች የመጀመሪያውን የዕብራይስጥ አጠራር እንዳለ ለማስቀመጥ አልሞከሩም።
ከዚህ ይልቅ ወደ ግሪክኛው አጠራር በመለወጥ ኢየሱስ ብለውታል። ዛሬም የስሙ አጠራር
መጽሐፍ ቅዱስ እንደተተረጎመበት ቋንቋ ይለያያል። የስፓንኛ መጽሐፍ ቅዱስ
አንባቢዎች ሄሱስ ብለው ያነባሉ። ጣሊያናውያን ጀይዙ ይሉታል። ጀርመናውያን ደግሞ
የሱስ ብለው ይጠሩታል።

አብዛኞቻችን፣ እንዲያውም ሁላችንም ለማለት ይቻላል፣ የመጀመሪያውን የኢየሱስ ስም


አጠራር ስለማናውቅ በኢየሱስ ስም መጠቀማችንን ማቆም ይገባናልን? እስከ ዛሬ ድረስ
እንዲህ መደረግ አለበት ያለ አንድም የመጽሐፍ ቅዱስ ተርጓሚ የለም። ለእኛ ሲል ደሙን
ያፈሰሰው ውድ የአምላክ ልጅ ተለይቶ የሚታወቅበት ስም ስለሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ
በሚለው ስም መጠቀም ያስደስተናል። የኢየሱስን ስም ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሙሉ
በሙሉ አውጥተን “መምህር” ወይም “መካከለኛ” እንደሚሉት ባሉት የማዕረግ ስሞች
ብንተካ ኢየሱስን ማክበር ይሆናልን? በፍጹም አይሆንም! ኢየሱስን በቋንቋችን
በተለመደው አጠራር ስንጠራ ከእርሱ ጋር የመቀራረብ ስሜት ሊያድርብን ይችላል።

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለምናነባቸው ስሞች በሙሉ ተመሳሳይ ሐሳብ መስጠት


ይቻላል። ስሞቹን በቋንቋችን በተለመደው አጠራር እንጠራለን እንጂ የመጀመሪያውን
አጠራር ለመኮረጅ አንሞክርም። “ኤርምያስ” እንላለን እንጂ ይርምያሁ አንልም።
በተመሳሳይም ኢሳይያስን በዘመኑ የሸያሁ ተብሎ ሳይጠራ አይቀርም ተብሎ የሚታሰብ
ቢሆንም ኢሳይያስ እንለዋለን። የእነዚህን ስሞች ጥንታዊ አጠራር የሚያውቁ ምሁራን
እንኳን ስለ ሰዎቹ ሲናገሩ የዘመኑን አጠራር እንጂ የጥንቱን አጠራር አይጠቀሙም።

የይሖዋ ስምም ቢሆን ከዚህ የተለየ አይደለም። በዘመናችን የተለመደው ይሖዋ ወይም
ጅሆቫ የተባለው አጠራር ከመጀመሪያው የጥንት አጠራር ጋር አንድ ዓይነት ላይሆን
ቢችልም የስሙን አስፈላጊነት በምንም ዓይነት መንገድ አይቀንሰውም። ኢየሱስ
“በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ፣ ስምህ ይቀደስ” ያለው ፈጣሪ፣ ሕያው የሆነው
አምላክና የሁሉ የበላይ የሆነው ልዑል ተለይቶ የሚታወቅበት ስም ነው።—ማቴዎስ 6:9

‘በሌላ ሊተካ አይችልም’

ብዙ ተርጓሚዎች ያህዌህ የሚለውን አጠራር ቢመርጡም የአዲሲቱ ዓለም


ትርጉምና አንዳንድ ሌሎች ትርጉሞች ይሖዋ የሚለው ለበርካታ መቶ ዘመናት
የተለመደ አጠራር በመሆኑ ምክንያት በዚሁ አጠራር ለመጠቀም መርጠዋል። ከዚህም
በላይ የሐወሐ (“YHWH”) ወይም ጀሐቨሐ (“JHVH”)* የሚሉት የቴትራግራማተን
ሆሄዮች ከሌሎች አጠራር ባላነሰ መጠን ተካትተዋል።

ከዚህ ቀደም ብሎ ጀርመናዊው ፕሮፌሰር ጉስታቭ ፍሬድሪክ ኦህለር ከዚህ እምብዛም


ባልተለየ ምክንያት ተመሳሳይ ውሳኔ አድርገዋል። ስለተለያዩ አነባበቦች ካብራሩ በኋላ
እንዲህ በማለት ደምድመዋል:- “ይሖዋ የሚለው ስም በሥነ ቃላታችን ውስጥ በጣም
የተለመደና የታወቀ በመሆኑና በማንኛውም ሌላ ዓይነት አጠራር ሊተካ የማይችል በመሆኑ
ከዚህ በኋላ ይሖዋ የሚለውን ቃል እጠቀማለሁ።” — ቲኦሎጊ ደስ አልተን
ተሰታመንትስ (የብሉይ ኪዳን ሃይማኖት) ሁለተኛ እትም፣ በ 1882 የታተመው፣ ገጽ 143

ፖውል ዡዋን የተባሉት ኢየሱሳዊ ምሁርም በተመሳሳይ ግራምየር ደ ለብሩ


ቢብሊክ (የመጽሐፍ ቅዱስ ዕብራይስጥ ሰዋስው) በተባለው መጽሐፍ በ 1923 እትም፣
በገጽ 49 የግርጌ ማስታወሻ ላይ እንዲህ ብለዋል:- “በትርጉሞቻችን ውስጥ የመላምት
ውጤት ከሆነው ያህዌህ ይልቅ በፈረንሣይኛ ሥነ ጽሑፍ ውስጥ ሰፊ ተቀባይነት
ባገኘው ዢሆቫ የሚል አጠራር ተጠቅመናል።” ሌሎች ብዙ ቋንቋዎችም በገጽ 8 ላይ ባለው
ሠንጠረዥ ውስጥ እንደተመለከተው ከዚህ ጋር በሚመሳሰል አጠራር ይጠቀማሉ።

ታዲያ እንዲህ ሲባል ያህዌህ ከሚለው አጠራር ጋር በሚመሳሰል አጠራር መጠቀም ስህተት
ነው ማለት ነውን? በፍጹም አይደለም። ይሖዋ የሚለው አጠራር “በብዙ ቋንቋዎች ጆሮ
የተለመደ” አጠራር በመሆኑ ምክንያት በአንባቢዎች ዘንድ የተሻለ ተቀባይነት ስለሚያገኝ
ብቻ ነው። ዋናው ነገር በስሙ መጠቀማችንና ስሙን ለሌሎች ማሳወቃችን ነው።
“ሕዝቦች ሁሉ ይሖዋን አመስግኑ! ስሙንም ጥሩ። ሥራዎቹን ለሕዝቦች ሁሉ አሳታውቁ።
ስሙ ከፍ ያለ መሆኑን ተናገሩ።”—ኢሳይያስ 12:4 አዓት

የአምላክ አገልጋዮች ባለፉት መቶ ዘመናት ይህን ትእዛዝ ለመፈጸም ያደረጓቸውን ነገሮች


እንመልከት።

[የግርጌ ማስታወሻዎች]

^ አን.5 በአዲሲቱ ዓለም የቅዱሳን ጽሑፎች ትርጉም ፣ 1984 እትም ላይ ተጨማሪ ክፍል
(አፔንዲክስ) 1A ተመልከት።

^ አን.22 በአዲሲቱ ዓለም የቅዱሳን ጽሑፎች ትርጉም የ 1984 እትም ተጨማሪ ክፍል
(አፔንዲክስ) 1A ተመልከት።

[በገጽ 7 ላይ የሚገኝ ሣጥን]

(የሐወሐ) ‘YHWH’ ስለሚለው ስም የመጀመሪያ አነባበብ የተለያዩ ምሁራን የተለያየ


ሐሳብ ሰጥተዋል።
ዶክተር ኤም ራይዘል ዘ ሚስቲርየስ ኔም ኦቭ Y.H.W.H. በተባለው መጽሐፍ በገጽ 74
ላይ የቴትራግራማተን የመጀመሪያ አጠራር “ዬሁዋህ ወይም ያሁዋህ መሆን ይኖርበታል”
ብለዋል።

የካምብሪጁ ካኖን ዲ ዲ ዊሊያምስ “የቴትራግራማተን እውነተኛ አጠራር ጃህዌህ


እንዳልሆነ የሚያመለክት፣ እንዲያውም የሚያረጋግጥ ለማለት ይቻላል ማስረጃ አለ። . . .
ትክክለኛ ስሙ ጃህኦህ ሳይሆን አይቀርም” ብለዋል። —ሳይትእሽክሪፍት ፊውር ዲ
አልቴስታሜንትልሼ ቪሴንእሽካፍት (የብሉይ ኪዳን እውቀት መጽሔት) 1936፣ ጥራዝ
54፣ ገጽ 269

‘ሪቫይዝድ ሴጐንድ ቨርሽን’ በተባለው የፈረንሳይኛ መጽሐፍ ቅዱስ የቃላት መፍቻ በገጽ 9
ላይ የሚከተለው አሳብ ተሰጥቷል:- “አንዳንድ የቅርብ ጊዜ ትርጉሞች
የተጠቀሙበት ያህቬ የሚለው አጠራር በማያጠራጥር ሁኔታ የተረጋገጠ ሳይሆን በአንዳንድ
የጥንት መረጃዎች ላይ የተመሠረተ ነው። እንደ ኤልያስ (ኤልያሁ) ያሉትን መለኮታዊው
ስም ተካትቶ የሚገኝባቸውን የተጸውኦ ስሞች ከተመለከትን የአምላክ ስም
አጠራር ያሆ ወይም ያሁ ሊሆን ይችላል።”

በ 1749 ቴለር የሚባለው ጀርመናዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ምሁር ስላነበባቸው የተለያዩ


የአምላክ ስም አነባበቦች እንዲህ ብሏል:- “የሲሲሊው ዳዮዶሩስ፣ ማክሮቢዩስ፣ ክሌሜንስ
አሌክስንድሪነስ፣ ቅዱስ ዤሮምና ኦሪገን ጃኦ ፤ ሳምራውያን፣ ኤፒፋንዩስ፣
ቴዎዶሬቱስ፣ ጃሔ ወይም ጃቬ ፤ ሉድዊግ ካፕል ጃቮ፤ ዱሩሲዩስ ጃቪ፤ ሖቲንገር ጀህቫ፤
መሪሴሩስ ጅሆቫ፤ ካስቲሊዩ ጃህቫ እና ሊ ክሊርክ ጃዎህ ወይም ጃቮህ ብለው ጽፈዋል።”

በዚህ ዓይነት የመጀመሪያው የአምላክ ስም አነባበብ በአሁኑ ጊዜ እንደማይታወቅ ግልጽ


ነው። ደግሞ መታወቁም ያን ያህል አስፈላጊ አይደለም። በጣም አስፈላጊ ቢሆን ኖሮ
አምላክ ራሱ ትክክለኛው አነባበብ ተጠብቆ እንዲቆይና እኛ እንድንጠቀምበት ያደርግ
ነበር። በጣም አስፈላጊው ነገር በራሳችን ቋንቋ በተለመደው አጠራር ወይም አነባበብ
በአምላክ ስም መጠቀም ነው።

[በገጽ 8 ላይ የሚገኝ ሣጥን]

ጅሆቫ የሚለው አጠራር በብዙ ብሔራት ተቀባይነት እንዳገኘ የሚያሳዩ የመለኮታዊው


ስም የተለያዩ ቋንቋዎች አጻጻፍ

አማርኛ – ይሖዋ
አዋባካልኛ – የሖዋ

ቡጎቱኛ – ጂሆቫ

ካንትንኛ – የህወዋህ

ዳንሽኛ– ጅሆቫ

ዳችኛ – ጅሆቫ

ኤፊክኛ – ጅሆቫ

እንግሊዝኛ ጅሆቫ

ፍጅያንኛ – ጅዮቫ

ፍንሽኛ – ጅሆቫ

ፈረንሳይኛ – ዢሆቫ

ፍቱናኛ – እሆቫ

ጀርመንኛ –ይሖቫ

ሀንጋሪያንኛ – ጅሆቫ

እግቦኛ – ጅሆቫ

ጣሊያንኛ – ጅኦቫ

ጃፓንኛ – ኢሆባ

ማውሪኛ – እሆዋ

ሞቱኛ – ኢየሆቫ

ሟላ ሟሉኛ – ጅሆቫ

ናሪንያሪኛ – ጅሆቫ
ኔምቤኛ –ጅሆቫ

ፔታትስኛ – ጅሁቫ

ፖላንድኛ –ጅሁቫ

ፖርቱጋልኛ – ጅኦቫ

ሮማኒያንኛ – ኢየሆቫ

ሳሞአንኛ –ኢየወቫ

ሶቶኛ –ጅሆቫ

ስፓንኛ – ጅሆቫ

ስዋሒሊኛ – የሖቫ

ስዊድንኛ – ጅሆቫ

ታሂቲያንኛ – ኢየሆቫ

ታጋሎግኛ – ጅሆቫ

ቶንጋንኛ – ጅሆቫ

ቤንጃኛ – ይሖቫ

ቆሳኛ – ኡይሆቫ

የሩባኛ – ጅሆፋህ

ዙሉኛ – ኡጅሆቫ

[በገጽ 11 ላይ የሚገኝ ሣጥን]

“ይሖዋ” የአምላክ ስም እንደሆነ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ ባሉ ጽሑፎች ላይ እንኳ በሰፊው


የታወቀ ሆኗል።
በዮሐን ላዲስላቭ ፒርከር የተደረሰውን “ዘ ኦልማይቲነስ” የተባለውን የዜማ ግጥም
በሙዚቃ ያቀናበረው ፍራንዝ ሹበርት ሲሆን በዚህ የዜማ ግጥም ውስጥ ይሖዋ የሚለው
ስም ሁለት ጊዜ ተጠቅሷል። በተጨማሪም “ናቡኮ” በተባለው የቬርዲ ኦፔራ ውስጥ
በመጨረሻው ትዕይንት ላይ ተጠቅሷል።

በተጨማሪም በፈረንሳዊው የሙዚቃ አቀነባባሪ በአርተር ሆኔገር የተደረሰው “ኪንግ ዴቪድ”


የተባለው ዝማሬ ይሖዋ ለሚለው ስም ከፍተኛ ቦታ ሰጥቷል። ቪክቶር ሁጎ የተባለውም
እውቅ ፈረንሳዊ ደራሲ ከ 30 በሚበልጡ የሥነ ጽሑፍ ሥራዎቹ ውስጥ “ይሖዋ” በሚለው
ስም ተጠቅሟል።

የጀርመን ፌደራል ባንክ በ 1967 አሳትሞ ባወጣው ዶቸ ታለር (የጀርመን ገንዘብ) የተባለ
መጽሐፍ ውስጥ የ“ይሖዋ” ስም የሚገኝበት እጅግ ጥንታዊ ከሆኑት ሳንቲሞች አንዱ
የሆነውና ከሲሌሲያው ግዛት የተገኘው የ 1634 ራይኽታለር ሥዕል ወጥቷል። መጽሐፉ
በሳንቲሙ ጀርባ ላይ ስላለው ሥዕል እንዲህ ብሏል።:- “የብርሃን ነጸብራቅ ከሚወጣበት
ጅሆቫ ከሚለው ስም ግርጌ ከዳመና ውስጥ የሚወጣና አክሊል የደፋ የሲሌስያ ካባ
ይታያል።”

በምሥራቅ ጀርመን በሩዶልፍሽታት በሚገኝ ቤተ መዘክር ውስጥ በ 17 ኛው መቶ ዘመን


የስዊድን ንጉሥ የነበረው ዳግማዊ ጉስታፈስ አዶልፍ ይለብሰው በነበረው የጦር ልብስ
ኮሌታ ላይ ጅሆቫ የሚለው ስም በትላልቅ ፊደላት ተጽፎ ማየት ይቻላል።

ስለዚህ ለበርካታ መቶ ዘመናት ዓለም አቀፍ ተቀባይነት አግኝቶ የቆየው የአምላክ ስም


አጠራር ጅሆቫ የሚለው ነው። ይህንን ስም የሚሰሙ ሰዎችም ስለማን እንደተነገረ
ወዲያው ይገነዘባሉ። ፕሮፌሰር ኦህለር እንዳሉት “ይህ ስም በሥነ ቃላታችን ውስጥ በጣም
የተለመደ ስለሆነ በማንም ሌላ አጠራር ሊተካ አይችልም።”— ቲኦሎጊ ደስ አልተን
ተስታመንትስ (የብሉይ ኪዳን ሃይማኖት)
[በገጽ 6 ላይ የሚገኝ ሥዕል]

በቫቲካን በቅዱስ ጴጥሮስ ቤተ ክርስቲያን በሚገኘው የሊቀ ጳጳስ ክሌመንት 13 ኛ


መቃብር ላይ በሚገኘው የመልአክ ቅርጽ ላይ ያለው የአምላክ ስም ጐላ ብሎ ሲታይ

[በገጽ 7 ላይ የሚገኝ ሥዕል]

የአምላክን ስም የያዙ ብዙ ሳንቲሞች ተሠርተው ነበር። ይህ ሳንቲም በ 1661 ጀርመን


አገር ኑረምበርግ ከተማ የተገኘ ነው። የላቲኑ ጽሑፍ ሲነበብ “በክንፎችህ ጥላ ሥር” ይላል
[በገጽ 9 ላይ የሚገኙ ሥዕሎች]

በቀደሙት ዘመናት በቴትራግራማተን የተጻፈው የአምላክ ስም የብዙ ሃይማኖታዊ


ሕንጻዎች ማስጌጫ ሆኖ ነበር

ፉርቭዬ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን፣ ሊዮንስ፣ ፈረንሳይ

የቡርዥ ካቴድራል፣ ፈረንሳይ

ላ ሴሌ ዱኗ የሚገኝ ቤተ ክርስቲያን፣ ፈረንሳይ

በደቡብ ፈረንሳይ በዲኝ የሚገኝ ቤተ ክርስቲያን

ሳኦ ፖሎ፣ ብራዚል የሚገኝ ቤተ ክርስቲያን

ስትራትስበርግ ካቴድራል፣ ፈረንሳይ

የቅዱስ ማርቆስ ካቴድራል፣ ቬነስ፣ ጣሊያን

[በገጽ 10 ላይ የሚገኙ ሥዕሎች]

ቦርደሾልም፣ ጀርመን በሚገኝ ገዳም የይሖዋ ስም እንዲህ ተጽፎ ይታያል

በ 1635 በተሠራ የጀርመን ሳንቲም ላይ

በፌህማርን ቤተ ክርስቲያን መዝጊያ ላይ፣ ጀርመን

You might also like