You are on page 1of 39

‫كشف الشبهات‬

ከሽፉ ሹቡሐት
(ማመሳሰያዎችን ማጋለጥ)

‫لإلمام حممد بن عبد الوهاب رمحه اهلل‬


ትርጉም፡ አቡዓብዲልዓዚዝ/ዩሱፍ አሕመድ
1/37

ክፍል አንድ

የመልእክተኞች ዋና ዓላማ አምልኳዊ የተውሂድ ክፍልን ማረጋገጥ መሆኑ የሚብራራበት ክፍል

እወቅ -አላህ ይዘንልህ-

ተውሒድ እርሱ፡ አላህን በአምልኮ ብቸኛ ማድረግ ነው፡፡ እርሱ አላህ መልእክተኞችን ወደባሮቹ
የላከበት እምነት ነው፡፡

የመጀመሪያቸው ኑህ ነው፡፡ በደጋግ ባሮቹ ላይ ድንበር በተላለፉ ጊዜ እርሱን ወደ ህዝቦቹ


አላህ ላከው፡፡ እነርሱም ፡ ወድ ፣ ሱዋዕ ፣ የጉስ ፣ የዑቅ እና ነስር ናቸው፡፡

የመልእክተኞች መጨረሻ ሙሐመድ ‫ ﷺ‬ናቸው፡፡ እርሱ የእነዚያን ደጋጎች ሐውልቶች


የሰባበረ ነው፡፡

የሚያመልኩ ፣ ሐጅ የሚያደርጉ ፣ የሚሶድቁ ፣ አላህን የሚዘክሩ ወደሆኑ ሰዎች አላህ


ላከው፡፡ ነገር ግን በእነርሱ እና በአላህ መካከል አንዳንድ ፍጡራኖችን አማካኝ ያደርጋሉ፡፡ “እኛ
ከእነርሱ የምንፈልገው ወደአላህ መቃረብን ነው” ፤ “ከእርሱ ዘንድ ምልጃቸውን እንፈልጋለን”
ይላሉ፡፡ ለምሳሌ፡ መላኢካዎችን ፣ ኢሳን ፣ መርየምን እና ከእነርሱ ውጭ የሚገኙ ደጋግ
ባሮችን፡፡፡

ለእነርሱ ሐይማኖታቸውን -የአባታቸውን የኢብራሂምን እምነት- እንዲያድስላቸው እና


ይህ መቃረብ -ለሌላ ለአንድም አካል የማይስማማ ጥርት ያለ የአላህ ሐቅ መሆኑንም ሊነግራቸው
ሙሐመድን ወደነርሱ አላህ ላከ- ለቅርብ መላኢካም ይሁን ፣ ለተላከ ነብይ ፣ እንኳን ከሁለቱ
ውጭ!
2/37
ካለበለዚያ እነዚህ አጋሪዎች፡ አላህ እርሱ -ለእርሱ ሸሪካ የሌለው- ፈጣሪ እንደሆነ ፣ ከእርሱ
በቀር የሚመግብ እንደሌለ ፣ ከእርሱ በቀር ህያው የሚያደርግና የሚገድል እንደሌለ ፣ ነገርን
ከእርሱ በቀር የሚያስተናብር እንደሌለ ይመሰክሩ ነበር፡፡ እንደዚሁ ፣ በአጠቃላይ ሰባቱ ሰማያት
በውስጣቸው የሚገኙትም ፣ ሰባቱ ምድሮችም በውስጣቸው የሚገኙትም ፣ በአጠቃላይ የእርሱ
አገልጋይ መሆናቸውን ፣ በእርሱ ማንቀሳቀስ እና ሀይል ስር መሆኑን ይመሰክሩ ነበር፡፡

ክፍል ሁለት
የአላህ መልእክተኛ የተጋደሏቸው አጋሪዎች የጌትነት የተውሂድ ክፍልን ማረጋገጣቸውና ይህም
በአምልኮ ከማጋራት እንደማያወጣቸው (ሙስሊም እንደማያደርጋቸው) የቀረቡ ማስረጀዎች
የሚብራራበት ክፍል

እነዚያ -የአላህ መልእክተኛ የተጋደሏቸው- አጋሪዎች በዚህ የሚመሰክሩ ለመሆናቸው ማስረጃ


ከፈለግክ በእርሱ ላይ የሚከተለውን የአላህ ቃል አንብብለት፡
ْ َ َّ َ ْ ُ ْ ُ َ َ َ َ ْ َ َ ْ َّ ُ ْ َ َّ َ ْ َ َ َ َّ َ ُ ُ َ ُْ
ِّ ِّ ‫﴿قل من يَ ْر ُزقكم مِّن السماء واألر ِّض أمن يملِّك السمع واألبصار ومن ُي ِّرج الَح مِّن المي‬
‫ت‬ َ
َ ُ َّ َ َ َ َ ْ ُ َ ُ َ ُ ُ َ َ َ َ ْ َ ُ َ ُ َ َ َ ْ َ َ َّ َ ْ ُ ْ ُ َ
﴾‫َح ومن يدبِّر األمر فسيقولون اّلل فقل أفال تتقون‬ ِّ ‫ويخ ِّرج الميت مِّن ال‬
“ከሰማይና ከምድር ሲሳይን የሚሰጣችሁ ማን ነው? መስሚያዎችንና ማያዎችንስ የፈጠረ ማን ነው?
ከሙትም ሕያውን የሚያወጣ ፣ ከሕያውም ሙትን የሚያወጣስ ማን ነው? ነገሩን ሁሉ የሚያስተናብርስ
ማን ነው?” በላቸው፡፡ “በእርግጥም አላህ ነው” ይሉሃል፡፡ “ታዲያ (ለምን ታጋራላችሁ?)
አትፈሩትምን?” በላቸው፡፡” (ዩኑስ፡ 31)

የሚከተለውንም የአላህ ቃል (አንብብለት፡-


ُّ‫ون۞قُ ْل َمن َّرب‬ َ ُ َّ َ َ َ َ َ ْ ُ َّ َ ُ ُ َ َ َ ُ َ ْ َ ْ ُ ُ َ َ َ ُ َْْ َ ُ
‫﴿قل ل ِّم ِّن األرض ومن فِّيها إِّن كنتم تعلمون۞سيقولون ِّّللِّ قل أفال تذكر‬
ُ ُ ُ َ َ َ َ ْ ُ َ ُ َّ َ َ َ َ ْ ُ َّ َ ُ ُ َ َ َ ْ‫السبْعِّ َو َر ُّب الْ َع ْر ِّش ال‬
َّ ‫ات‬ َّ
َ ‫الس َم‬
‫ك‬
ِّ ‫وت‬ ‫ك‬ ‫ل‬ ‫م‬ ِّ ‫ه‬‫د‬ِّ ‫ي‬ِّ ‫ب‬ ‫ن‬ ‫م‬ ‫ل‬ ‫ق‬ ۞‫ون‬ ‫ق‬ ‫ت‬ ‫ت‬ ‫ال‬‫ف‬ ‫أ‬ ‫ل‬ ‫ق‬ ِّ ‫ّلل‬
ِّ ‫ون‬‫ول‬‫ق‬ ‫ي‬ ‫س‬۞‫م‬ِّ ‫ي‬ ‫ظ‬
ِّ ‫ع‬ ِّ ‫او‬
َ ُ َ ْ ُ َّ َ َ ْ ُ َّ َ ُ ُ َ َ َ ُ َ ْ َ ْ ُ ُ َ ُ َُ ََ ُ ُ َُ َ ْ َ
﴾‫ار َعليْهِّ إِّن كنتم تعلمون۞سيقولون ِّّللِّ قل فأَّن تسحرون‬ ‫ُيري وَل ُي‬ ِّ ‫َش ٍء وهو‬
3/37
“ምድርና በውስጧ ያለው ሁሉ የማን ነው? የምታውቁ ብትሆኑ (ንገሩኝ)” በላቸው፡፡ “በእርግጥ የአላህ
ነው” ይሉሃል፡፡ “ታዲያ አትገሰጹምን?” በላቸው፡፡ “የሰባቱ ሰማያት ጌታና የታላቁ ዐርሽ ጌታ ማን
ነው?” በላቸው፡፡ “በእርግጥ አላህ ነው” ይሉሃል፡፡ “እንግዲያ አትፈሩትምን?” በላቸው፡፡ “የነገሩ ሁሉ
ግዛት በእጁ የሆነ ፣ እርሱ የሚጠብቅ ፣ በእርሱ ላይ የማይጠበቅ ማን ነው? የምታውቁ እንደሆናችሁ
(መልሱልኝ)” በላቸው፡፡ ይልቁንም እውነትን አመጣንላቸው፡፡ እነርሱም (በመካዳቸው) ውሸታሞች
ናቸው፡፡” (አል’ሙእሚኑን፡ 84-89)

ከዚህም ውጭ ያሉ አንቀጾችን (አንብብለት፡

እነርሱ በዚህ አረጋጋጭ መሆናቸውን ካረጋገጥክ ፡ እርሱ ፣ የአላህ መልእክተኛ ‫ ﷺ‬ወደርሱ


ጥሪ ያደረጉበት ወደሆነው ተውሂድ ያላስገባቸው መሆኑን ፣ እነርሱ ያስተባበሉት ተውሂድ ፣
“ተውሂደል ዒባዳ” (አላህን በብቸኛነት የማምለክ ተውሂድ) መሆኑን አወቅክ- ያ በዘመናችን
የሚገኙ ሙሽሪኮቸ “ኢዕቲቃድ” (እምነት) ብለው የሚጠሩት (የሆነውን ነው ያስተባበሉት)፡፡

ሌሊትና ቀን አላህን ይማጸኑ ነበር ፡ ከእነርሱ መካከል ለደግነታቸው ፣ ወደአላህ ቅርብ


ለመሆናቸው ለእነርሱ (ወደአላህ) እንዲያማልዷቸው መላኢካዎችን የሚማጸኑ ነበሩ ወይም
ደጋጎችን የሚማጸኑ ነበሩ ለምሳሌ፡ ላት ወይም ነብይን (የሚማጸኑ ነበሩ) -ለምሳሌ፡ ኢሳ ፡፡

የአላህ መልእክተኛ ‫ ﷺ‬በዚህ ሽርክ ላይ የተጋደሏቸው መሆኑን ፣ አምልኮን ለአላህ ብቻ


እንዲያጠሩ የጠሯቸው መሆኑን ካወቅክ፡፡ አላህ በሚከተለው ቁርኣን እንደተናገረው፡
ً َ َ َّ َ َ ُ ْ َ َ َ َّ َ َ َ ْ َّ َ َ
﴾‫جد ِّّللِّ فال تدعوا مع اّللِّ أحدا‬
ِّ ‫﴿وأن المسا‬

“እነሆ መስጊዶችም (አጠቃላይ ምድርም) የአላህ (ማምለኪያ) ብቻ ናቸው፡፡ (በውስጣቸው) ከአላህ


ጋር አንድንም አትገዙ፡፡” (አል’ጅን፡ 18)

አላህ እንደተናገረው፡
َُ ْ َ َّ َ َ َّ ْ َ ِّ ‫ون ل َ ُهم ب‬
َ ُ َ َْ َ ُ َ ُ ْ َ َ َّ َ َ ْ ُ َ ْ َ ُ َ
‫َش ٍء إَِّل ك َبا ِّس ِّط كفيْهِّ إَِّل ال َماء ِِّلَبْلغ‬ ‫جيب‬
ِّ ‫ت‬ ‫س‬ ‫ي‬ ‫َل‬ ِّ ‫ه‬ ِّ ‫ن‬ ‫و‬ ‫د‬ ‫ِّن‬
‫م‬ ‫ون‬ ‫﴿َل دعوة اْل ِّق واَّلِّين يدع‬
َ َ َّ َ َْ ُ ُ َ
﴾‫ين إَِّل ِِّف ضال ٍل‬ ‫فاهُ َو َما ه َو ب ِّ َبال ِّ ِّغهِّ َو َما د ََعء الَكف ِِّّر‬
4/37
“ለእርሱ (ለአላህ) የእውነት መጥሪያ አለው፡፡ እነዚያም ከእርሱ ሌላ የሚግገዟቸው (ጣዖታት)
ለእነርሱ በምንም አይመልሱላቸውም” (አር’ረዕድ፡ 14)

ዱዓ በአጠቃላይ ለአላህ ፣ እርድ በአጠቃላይ ለአላህ ፣ ስለት በአጠቃላይ ለአላህ ፣ ተማጽኖ


በአጠቃላይ ለአላህ ፣ የአምልኮ አይነቶች በአጠቃላይ ለአላህ እንዲሆን ዘንድ የአላህ መልክተኛ
የተጋደሏቸው መሆኑን ካረጋገጥክ፡፡

በሩቡብያ የተውሂድ ክፍል ማረጋገጣቸው በእስልምና ውስጥ ያላስገባቸው መሆኑን ካወቅክ፡፡


ደማቸውንና ገንዘባቸውን የተፈቀደ ያደረገው እርሱ ያ ምልጃቸውን በመፈለግ ፣ በእርሱም
ወደአላህ መቃረብን በመፈለግ መላኢካዎችን ወይም ነብያትን ወይም ወልዮችን መደገፊያ
ማድረግ መሆኑን ካወቅክ፡፡ የዚህ ጊዜ ተውሂድ -መልእክተኞች ወደርሱ የተጣሩበት ፣ በእርሱ
አጋሪዎች ከማረጋገጥ እምቢ ያሉት- መሆኑን አወቅክ፡፡ ይህ ተውሂድ (ላኢላሃ ኢልለላህ)
የሚለው ንግግርህ ትርጉም ነው፡፡

ክፍል ሶስት
ተውሂደል ዒባዳ የ “ላኢላሃ ኢልለሏህ” ትርጉም መሆኑና

በረሡል ዘመን የነበሩት ከሀዲዎች ሙስሊም ነን ብለው ከሚሞግቱት በበለጠ ሁኔታ ትርጉሟን
እንደሚያውቁ የሚብራራበት ክፍል

“ኢላህ” የሚለው ከእነርሱ ዘንድ ለእነዚህ ነገሮች የሚታሰብ ነው -መላኢካም ይሁን ወይም
ነብይ ወይም ወልይ ወይም ዛፍ ወይም ቀብር ወይም ጅን፡፡ “ኢላህ” በሚለው ፈጣሪ ፣ መጋቢ
እና አስተናባሪ የሚለውን አልፈለጉበትም፡፡ ከዚህ በፊት እንዳስቀደምኩልህ እነርሱ ይህ ለአላህ
ብቻ መሆኑን ያውቃሉ፡፡ “ኢላህ” ሲባል የፈለጉት “ሰይ̕ይድ” በሚል የዘመናችን አጋሪዎች
የፈለጉበትን ነው፡፡ ነብዩ ‫ ﷺ‬ወደተውሂድ ቃል ሊጠሯቸው መጡ፡፡ እርሷም (ላኢላሃ ኢልለሏህ)
ናት፡፡
5/37

ከዚህች ቃል የተፈለገው ቃሏ ሳይሆን ትርጉሟ ነው፡፡ በዚህች ቃል የነብዩ ‫ ﷺ‬ፍላጎት በእምነት


አላህን ብቸኛ ማድረግ ፣ ከእርሱ ውጭ በሚመለኩ ነገሮች መካድ ፣ ከእርሱም (ከማጋራት)
መራቅ መሆኑን በጣም ጃሂል የሆኑት ከሀዲዎች ያውቃሉ፡፡

እንሆ “ላኢላሃ ኢልለሏህ” በሉ ባላቸው ጊዜ ለእርሱ የሚከተለውን አሉ፡


ٌ َ ُ ٌ ْ َ َ َ َ َّ ً َ ً َ َ َ ْ َ َ َ َ
﴾‫حدا إِّن هذا لَشء عجاب‬ ِّ ‫﴿أجعل اْلل ِّهة إِّلها وا‬
“አማልክቶቹን አንድ አምላክ አደረጋቸውን? ይህ አስደናቂ ነገር ነው” (አሉ) (ሷድ፡ 5)

በጣም ጃሂል የሆኑት ከሀዲዎች ይህን (የላኢላሃ ኢልለሏህን ትርጉም) የሚያውቁ


መሆናቸውን ካወቅክ ፣ በጣም የሚያስገርመው በጣም ጃሂል የሆኑት ከሐዲዎች ያወቁትን
የዚህችን ቃል ትርጉም ሙስሊም ነኝ የሚለው አለማወቁ ነው፡፡

እንዴውም እርሱ ይህ (መመስከር) አንዳች ከትርጉሟ በልብ ምንም አይነት እምነት ሳይኖር
በሀርፎቿ ብቻ መናገር ነው ብሎ ይገምታል፡፡ ከእነርሱ ዘንድ ጥልቅ እውቀት ያለው የእርሷ
ትርጉም ፡ “ፈጣሪ የለም ፣ መጋቢ የለም ፣ ነገርን የሚያስተናብር የለም አላህ እንጅ” ብሎ
ይገምታል (ላኢላሃ ኢልለሏህ ያለውን በተውሂደ ሩቡብያ ብቻ ይፈስረዋል) ፡፡ በ“ላኢሃ
ኢልለሏህ” ትርጉም በጣም ማህይም የሆኑት ከሀዲዎች በእውቀት የበለጡት ሰው ከእርሱ ዘንድ
ምንም መልካም የለውም!

ክፍል አራት
በእርሱ ላይ አላህ ተውሒድን ማጎናጸፉ በእርሱ መደሰትን እና እርሱን ከመንነጠቅ መፍራትን
የሚያመጣ መሆኑን ሙእሚን ማወቅ እንዳለበት የሚያረጋግጥ ክፍል

ለአንተ የነገርኩህን ከልብህ ከተገነዘብክ ፣ በአላህ ማጋራትንም ካወቅህ ፣ ያ ስለርሱ -“አላህ


በእርሱ ማጋራትን በፍጹም አይምርም፡፡”- ያለውን ካወቅክ (አን’ኒሳእ፡ 48)
6/37
ከመጀመሪያቸው እስከመጨረሻቸው መልእክተኞችን በእርሱ የላከበትን -ከእርሱ ውጭ
አንድንም አላህ የማይቀበልበት የሆነውን- የአላህን ዲን ካወቅክ ፤ በዚህም አብዛኛው ሰው
ማህይም መሆኑን ከተገነዘብክ ሁለት ፋይዳዎችን ያስጠቅምሃል፡
አንደኛ፡- በአላህ ችሮታና እዝነት መደሰት አላህ እንደተናገረው፡-
َ َْ ٌ ْ ‫ْحتِّهِّ فَب َذل َِّك فَلْ َي ْف َر ُحوا ْ ُه َو َخ‬
﴾‫ري م َِّّما ُي َم ُعون‬ َ ْ ‫ضل اّللِّ َوب َر‬ ْ َ ُْ
ِّ ِّ ِّ ‫﴿قل بِّف‬
“በአላህ ችሮታና በእዝነቱ (ይደሰቱ)፡፡ በዚህም ምክንያት ይደሰቱ፡፡ እርሱ ከሚሰበስቡት ሀብት በላጭ
ነው፡፡ በላቸው፡፡” (ዩኑስ፡ 58)

በተጨማሪ የሚከተለውን ያስጠቅምሀል፡

ታላቅ የሆነ ፍርሀት፡ የሰው ልጅ ከምላሱ በምትወጣ ቃል እንደሚከፍር ካወቅክ ፣ አንዳንዴ -


(1)
እርሱ አላዋቂ ሆኖ- (ቃሏን) ይላታል፡፡ ባለማወቁ ምክንያት አይሰጠውም፡፡ አንዳንዴ እርሷ
ወደአላህ ታቃርበዋለች ብሎ በመገመት (ቃሏን) ይላታል- አጋሪዎች እንደሚገምቱት፡፡

(1). ሸይኽ ሙሐመድ ብን ሷሊህ አልዑሰይሚን “ከሽፍ ሹቡሀ” የተባለውን የሸይኽ ሙሐመድ ብን አብዱልወሀብ
መጽሐፍ ትንታኔ ከሰጡበት ኪታባቸው ገጽ 46 ላይ የሚከተለውን ተናግረዋል፡
በዚህ የመጽሐፉ አዘጋጅ ንግግር ላይ የምንሰጠው ማብራሪያ የሚከተለው ነው፡
ሸይኽ ለአለማወቅ ምክንያት አይሰጥም የሚል አቋም አላቸው የሚል ጥርጣሬ የለኝም፡፡ ነገር ግን ትምህርትን
በመተው ሟጓደል ካልኖረ በቀር፡፡ ለምሳሌ፡ ሀቅን ይሰማል ወደርሱ ፊቱን አያዞርም ፣ አይማርም፡፡ ይህ ባለማወቁ
ምክንያት አይስሰጠውም፡፡ ይህን ጉዳይ ከሸይኽ የማልጠረጥርበት ምክንያት ባለማወቅ ምክንያት መስጠቱን የሚጠቁም
የእርሱ ሌላ ንግግር ስላለው ነው፡፡
ሸይኹ -በእርሱ ላይ ስለሚጋደሉበት ነገር ፣ እንዲሁም በእርሱ ላይ ግለሰብን ስለሚያከፍሩበት ነገር ተጠየቀ
የሚከተለውንም ምላሽ ሰጠ፡-
የኢስላም መሰረቶች አምስት ናቸው፡፡ የመጀመሪያዋ ሁለቱ ምስክሮች ናቸው፡፡ ከዚያም አራቱ ማዕዘናቶች ናቸው፡፡
አራቱን አረጋግጦ በቸልተኝነት ቢተዋት በተግባሯ ላይ ብንጋደለውም በመተው አናከፍረውም፡፡ ያለምንም ማስተባበል
በቸልተኛነት ቢተዋቸው ይከፍራል አይከፍርም በሚለው ዑለሞች ተለያይተዋል፡፡ ሁሉም ዑለሞች በተስማሙበት እንጅ
አናከፍርም፡፡ እርሱም ሁለቱ የምስክር ቃሎች ናቸው፡፡ ካሳወቅነው በኋላ አውቆ ከተቃወመ እናከፍረዋለን፡፡…
‫وصلى هللا على محمد وآله وصحبه وسلم‬
7/37
በተለይም የሙሳ ህዝቦች ደጋግ ፣ አዋቂ ከመሆናቸው ጋር የሚከተለውን ተናጋሪ ሆነው
ወደርሱ እንደመጡት አላህ በቁርኣኑ የተረከውን ካሳወቀህ
ٌ َ َ ً َ َ َّ َ ْ
﴾‫ـها ك َما ل ُه ْم آل َِّهة‬ ‫﴿اجعل َّلا إِّل‬

“ሙሳ ሆይ፡- ለእነርሱ (ለሰዎቹ) አማልክት እንዳላቸው ለእኛም አምላክን አድርግልን” (አል’አዕራፍ፡
138)

በዚህ ጊዜ ከዚህ (ውስብሰብ ችግር) እና ከመሰሎቹ ከሚያጸዳህ ነገር ፍርሀትህ እና ጉጉትህ


ከፍ ይላል፡፡

ክፍል አምስት
ለነብያቶቹ እንዲሁም ለወልዮቹ ከሰውም ይሁን ከጅን ጠላቶችን ማድረግ የአላህ ጥበቡ ማስፈረዱ
የሚብራራበት ክፍል

እወቅ፡ ከአላህ ጥበብ መከከል አንድን ነብይ በዚህ ተውሂድ ላይ አላከም ለእርሱ ጠላትን ያደረገ
ቢሆን እንጅ፡፡ አላህ እንደተናገረው፡
ْ َْ َ ُ ْ ُ ْ َ َ ْ ُ ُ َْ ُ ْ َ َ َ َ ًّ ُ َ ُ َْ َ َ َ َ َ َ
ِّ ‫اْل ِّن ي‬
‫وِح بعضهم إَِّل بع ٍض زخرف القو ِّل‬ ِّ ‫نس و‬
ِّ ‫اإل‬ ِّ ‫﴿وكذل ِّك جعلنا ل‬
ِّ ‫ِّك ن ِّ ٍِّب عدوا شيا ِّطني‬
﴾‫ورا‬ ً ‫ُغ ُر‬

“እንደዚሁም ለነብያት ሁሉ ከሰውና ከጋኔን የሆኑን ሰይጣናት ጠላት አደረግን፡፡ ከፊላቸው ወደ ከፊሉ
ለማታለል ልብስብስን ቃል ይጥላሉ፡፡” (አል’አንዓም፡ 112)

አንዳንዴ ለተውሂድ ጠላቶች በርካታ እውቀቶች ፣ መጽሐፎች እና ማስረጃዎች ሊኖራቸው


ይችላል፡፡ አላህ እንደተናገረው፡
ْ ْ َ ُ َ َ ُ َ َ َ ْ ُ ُ ُ ُ ْ ُ ْ َ َّ َ َ
﴾‫ات ف ِّرحوا بِّما عِّندهم مِّن العِّل ِّم‬
ِّ ‫﴿فلما جاءتهم رسلهم بِّاْليِّن‬
“መልእክተኞቻቸውም ተዓምራቶችን በመጡላቸው ጊዜ ከእነርሱ ዘንድ ባለው ዕውቀት ተደሰቱ፡፡” (ጋፊር፡
83)
8/37
ይህን ካወቅህ ፣ እንዲሁ ወደአላህ የሚወስደው መንገድ የግድ በእርሱ ላይ ተቀማጭ
የሆኑየንግግር ችሎታ ፣ እውቀት እና ማስረጃዎች ያላቸው ጠላቶች ያለበት መሆኑን ካወቅህ ፣
ለአላህ ዲን ስትል እነዚያን ሰይጣናት የምትጋደልበት መሳሪያ የሚያስፈልግህ መሆኑን ማወቅ
በአንተ ላይ ግዴታ አለብህ- የእነርሱ ተቀዳሚያቸውና መሪያቸው ለጌታህ (የሚከተለውን)
ተናገረ፡
ْ‫يم۞ ُث َّم ْلت َِّي َّن ُهم مِّن بَ ْني َأي ْ ِّديه ْم َوم ِّْن َخلْفِّه ْم َو َعن‬ َ َ َ ْ ُ َ َّ َ ُ ْ َ
َ ِّ‫ك ال ْ ُم ْس َتق‬ ‫ِصاط‬ َ ْ َ ْ َ َ َ َ َ
ِّ ‫﴿قال فبِّما أغويت ِِّن ألقعدن لهم‬
ِّ ِّ ِّ
َ َ ْ ُ ََ ْ َ ُ َ َ َ ْ َ َ َ َ ْ ََْ
﴾‫َتد أكَثهم شاك ِِّّرين‬ ِّ ‫أيمان ِّ ِّهم وعن شمآئِّل ِّ ِّهم وَل‬

“ስለአጠመምከኝም ለእነርሱ በቀጥተኛው መንገድ ላይ በእርግጥ እቀመጥባቸዋለሁ” አለ፡፡ “ከዚያም


ከስተፊቶቻቸው ከኋላቸውም ከቀኞቻቸውም ከግራዎቻቸውም በእርግጥ እመጣባቸዋለሁ፡፡
አብዛኞቻቸውም አመስጋኞች ሆነው አታገኛቸውም” (አለ)፡፡ (አል’አዕራፍ፡ 16-17)

ነገር ግን ወደአላህ ከዞርክ ፣ ወደአላህ ማስረጃዎች እና አስረጅዎቹ ጆሮ ከሰጠህ ፣ አትፍራ ፣


አትዘን፡፡
ً َ َ َ
﴾‫ان َكن ضعِّيفا‬ َ ْ َّ َ ْ َ َّ
ِّ ‫﴿إِّن كيد الشيط‬
“የሰይጣን ተንኮል ደካማ ነውና፡፡” (አን’ኒሳእ፡ 76)

ከተወሂድ ሰዎች ተራው ሰው ፣ ከእነዚያ አጋሪዎች አሊሞች አንድ ሽውን ያሸንፋል፡፡ አላህ
እንደተናገረው፡
َ َ ْ َ َ َ ُ َّ
﴾‫ندنا ل ُه ُم الغاْلِّ ُون‬ ‫﴿ِإَون ج‬
“ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡” (አስ’ሷፋት፡ 173)

የአላህ ሰራዊቶች በሰይፍ እና በጦር አሸናፊዎች እንደሆኑ ሁሉ በማስረጃ ፣ በአንደበትም


አሸናፊዎች ናቸው፡፡

በተውሂድ ሰው ላይ ስጋቱ ከእርሱ ጋር መሳሪያ ሳይኖር መንገድን የሚጓዘው ነው፡፡ (ለሁሉም ነገር
አብራሪ ፣ መሪም…) ያደረገውን መጽሐፍ አላህ በእኛ ላይ ለግሷል፡
9/37
َ ْ ُ ْ َ ْ ُ َ ًَْ َ َ ً ُ َ ْ َ ُ ً َْ
﴾‫ِّك َش ٍء وهدى ورْحة وبْشى ل ِّلمسل ِّ ِّمني‬ ِّ ‫﴿ت ِّبيانا ل‬
“ለሁሉም ነገር አብራሪ ፤ መሪም ፤ እዝነትም ፤ ለሙስሊሞችም አብሳሪ ሆኖ በአንተ ላይ አወረድነው”
(አን’ነህል፡ 89)

የጥመት ባለቤት በማስረጃ አይመጣም ፡ እርሷን የሚያፈርሳት ፣ ጥመቷን ግልጽ የሚያደርጋት


በቁርኣን ውስጥ የሚገኝ ቢሆን እንጅ፡፡
አላህ እንደተናገረው፡
ً ْ َ َ َ ْ َ َ َْ َ َ ْ َّ َ َ َ َ ُ ْ َ َ َ
﴾‫سريا‬ ِّ ‫﴿وَل يأتونك بِّمث ٍل إَِّل‬
ِّ ‫جئناك بِّاْل ِّق وأحسن تف‬
“በጥያቄም አይመጡብህም እውነተኛውን (መልስ) መልካምን ፍችም የምናመጣልህ ብንሆን እንጅ”
(አል’ፉርቃን፡ 33)

አንዳንድ ተንታኞች (የሚከተለውን) ተናገረዋል፡-

“ይህች አንቀጽ እስከ ቂያማ ቀን ድረስ በእርሷ ማስረጃ ይዞ ለሚያመጣ ማንኛውም የጥመት
ባለቤት ሁሉ (ምላሽ) የምትሆን ነች”

ክፍል ሰባት
ጥቅልም ይሁነ ዝርዝር በጥመት ባለቤቶች ላይ የተሰጠው ምላሽ የሚብራራበት ክፍል

እኔ በዘመናችን አጋሪዎች በእኛ ላይ ማስረጃ አድርገው ላቀረቡት ምላሽ አላህ በመጽሐፉ


ካወሳው አንዳንድ ነገሮችን ለአንተ አወሳልሀለሁ፡፡

እንላለን፡ ለጥመት ባለቤቶች የሚሰጠው ምላሽ በሁለት መንገዶች ነው፡ ጥቅል እና ዝርዝር፡፡

(ጥቅሉ)፡ እርሱ ለሚገነዘበው ሰው ታላቅ ነገር ፤ ከፍ ያለ ፋይዳ አለው፡፡ እርሱም የሚከተለው


የእርሱ ቃል ነው፡
َ َّ َّ َ َ ٌ َ َ َ ُ ُ َ ُ َ َ ْ ُّ ُ َّ ُ ٌ َ َ ْ ُّ ٌ َ ُ ْ َ َ ْ َ ْ َ َ َ َ َ َ َّ َ ُ
‫اَّلين ِف‬
ِّ ‫اب وأخر متشابِّهات فأما‬ ِّ ‫﴿هو اَّلِّي أنزل عليك الكِّتاب مِّنه آيات ُّمكمات هن أم الكِّت‬
َ ُ َّ َ ُ َّ ُ َ ْ َ ُ َ ْ َ َ َ ْ َ َ ْ َ ْ ْ َ ْ ُ ْ َ َ َ َ َ َ ُ َّ َ ٌ ْ َ ْ ُ ُ
‫قلوب ِّ ِّهم زيغ ف َيتبِّعون ما تشابه مِّنه ابتِّغاء الفِّتنةِّ َوابتِّغاء تأوِّيلِّهِّ وما يعلم تأوِّيله إَِّل اّلل والرا ِّسخون‬
10/37
َ ْ ْ ُ ْ ُ َّ ُ َّ َّ َ َ َ َ َ ْ ٌّ ُ َّ َ َ ُ َُ ْ ْ
﴾‫اب‬
ِّ ‫ِِّف العِّل ِّم يقولون آمنا بِّهِّ ك مِّن عِّن ِّد ربِّنا وما يذكر إَِّل أولوا األْل‬
“እርሱ ያ በአንተ ላይ መጽሐፉን ያወረደ ነው ፤ ከእርሱ (ከመጽሐፉ) ግልጽ የሆኑ አንቀጾች
አሉ፡፡ እነሱ የመጽሐፉ መሰረቶች ናቸው፡፡ ሌሎችም ተመሳሳዮች አልሉ፡፡ እነዚያማ
በልቦቻቸው ውስጥ ጥመት ያለባቸው ሰዎች ማሳሳትን ለመፈለግና ትችቱን ለመፈለግ ከርሱ
የተመሳሰለውን ይከታተላሉ፡፡ (ትክክለኛ) ትችቱንም አላህ ብቻ እንጅ ሌላ አያውቀውም፡፡
በእውቀትም የጠለቁት “በርሱ አምነናል ፤ ሁሉም ከጌታችን ዘንድ ነው” ይላሉ፡፡ የአእምሮ
ባለቤቶችም እንጅ (ሌላው) አይገሰጽም፡፡” (አል’ዒምራን፡ 7)
የአላህ መልእክተኛ ‫ ﷺ‬የሚከተለውን እንደተናገሩ በሐዲስ ተረጋግጧል፡

‫"إذا رأيتم الذين يتبعون المتشابه ويتركون المحكم فأولئك الذين سمى هللا في كتابه‬
"‫فاحذروهم‬

“ተመሳሳዩን የሚከተሉ ፣ ግልጹን የሚተው ከተመለከታችሁ እነርሱ በመጽሐፉ አላህ የሰየማቸው


ናቸውና ተጠንቀቋቸው፡፡” (ቡኻሪ፡ 4547, ሙስሊም፡ 2665)

ለዚህ ምሳሌ፡ ከአጋሪዎች አንዱ ለአንተ (የሚከተለውን) ቢልህ፡


َ ََُْ ْ ُ َ َ ْ َْ َ ٌْ َ َ ْ َ َّ َ
َ
﴾‫﴿أَل إِّن أو ِِّلاء اّللِّ َل خوف علي ِّهم وَل هم َيزنون‬

“ንቁ! የአላህ ወዳጆች በእነሱ ላይ ፍርሃት የለባቸውም ፤ እነሱም አያዝኑም፡፡” (ዩኑሱ፡ 62)

ወይም ምልጃ ሀቅ ነው ወይም ነብያቶች ከአላህ ዘንድ ልቅና አላቸው ወይም በአንድ ነገር ላይ
ለጥመቱ ማስረጃ ይሆነው ዘንድ ከነብዩ ‫ ﷺ‬ንግግር ቢያዋሳ - እርሱ ያወሳውን ንግግር ትርጉሙን
አንተ የማትገነዘበው ብትሆን፡፡ በሚከተለው ንግግርህ ምላሽ ስጠው፡

እነዚያ በልባቸው ውስጥ ጥመት ያለባቸው ሰዎች ግልጽ የሆነውን እንደሚተው ተመሳሳዩን
እንደሚከተሉ አላህ አውስቷል፡፡

አጋሪዎች ፈጣሪነቱን እንደሚያረጋግጡ ፤ በመላኢካዎች ፣ በነብያቶች ፣ በወልዮች


11/37
በማመናቸው ከሐዲ እንዳላቸው አላህ የተናገረበትን ለአንተ ያወሳሁልህ የሚከተለውን
ከማለታቸው ጋር ነው፡
ُ َ َ ُ
َ ‫اؤنَا ع‬ ُ َ َ ُ ُ
﴾ِّ‫ِّند اّلل‬ ‫﴿ َو َيقولون هـؤَلء شفع‬

“እነዚህም አላህ ዘንድ አማላጆቻችን ናቸው” ይላሉ (ዩኑስ፡ 18)

ይህ ትርጉሙን አንድም አካል መቀየር የማይችለው የተብራራ ግልጽ ነገር ነው፡፡ አንተ አጋሪ
ሆይ! ከቁርኣን ወይም ከረሡል ‫ ﷺ‬ንግግር ለእኔ ያወሳህልኝ ትርጉሙን አላውቀውም፡፡ ነገር ግን
በቁርጠኝነት የምነግርህ የአላህ ንግግር እርስ በርስ የማይጋጭ ፣ የነብዩ ‫ ﷺ‬ንግግር ከአላህ ንግግር
ጋር የማይጋጭ መሆኑን ነው፡፡

ይህ መልካምና ቀጥ ያለ ምላሽ ነው፡፡ ነገር ግን አላህ የገጠመው ካልሆነ በቀር የሚገነዘበው


የለም ፣ እርሱን አታቅልለው፡፡ እንሆ እርሱ አላህ እንደተናገረው ነው፡
َ َ ُ َّ َ َّ َ ُ َ َ ُ َ َ َ َّ َّ َ َّ َ ُ َ َ
﴾‫يم‬
ٍ ‫﴿وما يلقاها إَِّل اَّلِّين صَبوا وما يلقاها إَِّل ذو ح ٍظ ع ِّظ‬

“(ይህችንም ጠባይ) እነዚያ የታገሱት እንጅ ሌላው አያገኛትም ፤ የትልቅም ዕድል ባለቤት
እንጅ ማንም አይገጠማትም፡፡” (ፉሲለት፡ 35)

(ዝርዝሩ ምላሸ) ፡ የአላህ ጠላቶች ሰዎችን ከእርሱ የሚያግዱበት በአላህ መልእክተኞች


እምነት ላይ በርካታ ተቃውሞዎች አሏቸው፡፡

ከእርሷ መካከል የሚከተለው ንግግራቸው ነው፡ እኛ አንድም በአላህ ላይ አናጋራም፡፡ ይልቁንም


የሚፈጥር ፣ የሚመግብ ፣ የሚጠቅም የሚጎዳ -ብቸኛውና ምንም አጋር የሌለው- ከአላህ በቀር
አንድም የሌለ መሆኑን ፣ ሙሐመድም ለነፍሱ መጥቀምም ይሁን መጉዳት እንደማይችል
እንመሰክራለን -እንኳን ዓብዱልቃድር እና ሌሎች ይቅርና፡፡ ነገር ግን እኔ ወንጀለኛ ነኝ፡፡ ደጋግ
የአላሀ ባሮች ደግሞ ከአላህ ዘንድ ለእነርሱ ልቅና አላቸው፡፡ በእነርሱ አማካኝነት ከአላህ
እፈልጋለሁ፡፡
12/37

ከዚህ በፊት ባሳለፍነው ምላሽ ስጠው፡ የአላህ መልእክተኛ ‫ ﷺ‬የተጋደሏቸው ለእኔ ያወሳሀቸውን
ነገሮች ያረጋግጡ ነበር -አንተ ጠማማ ሆይ! ጣዖቶቻቸው አንድም ነገር ማስተናበር
እንደማይችሉ ያረጋግጡ ነበር፡፡ ከእነርሱ የፈለጉት ልቅናቸውን እና ምልጃን ነው፡፡ አላህ
በመጽሐፉ ያወሳውን እና ግልጽ ያደረገውን አንብብለት፡፡

የሚከተለውን ከተናገረ፡ እነዚህ አንቀጾች የወረዱት ጣዖታትን በሚገዙ አካላት ላይ ነው፡፡


ደጋጎችን እንዴት እንደጣዖታት ዓይነት ታደርጓቸዋላችሁʔ! ወይም ነብያቶችን ጣዖታት እንዴት
ታደርጓቸዋላችሁʔ! ከዚህ በፊት ባሳለፍነው መልስለት፡

እንሆ ከሀዲዎች ሩቡብያን በአጠቃላይ ለአላህ የሚመሰክሩ ፣ እነርሱ አላማ ካደረጓቸው


አካላት ምልጃን እንጅ ሌላን ያልፈለጉ መሆናቸውን የሚመሰክሩ መሆናቸውን ካረጋገጠ ፣ ነገር
ግን እርሱ ባወሳው በእነርሱ ተግባር እና በእርሱ ተግባር መካከል መለየትን ፈለገ፡፡

ለእርሱ አውሳለት፡ ከከሀዲዎቸ መካከል ጣዖታትን የሚማጸኑ ፣ ከነርሱ መካከል ወልዮችን


የሚማጸኑ ነበሩ፡፡
እነርሱን አስመልክቶ አላህ የሚከተለውን ተናግሯል፡-
ُ َ ْ َ ْ ُ ُّ َ َ َ َ ْ ُ َ َ َ ُ َ ْ َ َ ُ ْ َ َ َّ َ َ ُ
﴾‫﴿أولـئِّك اَّلِّين يدعون يبتغون إَِّل رب ِّ ِّهم الو ِّسيلة أيهم أقرب‬

“እነዚያ እነርሱ የሚግገዟቸው ማንኛቸውም (ወደአላህ) በጣም ቀራቢያቸው ወደ ጌታቸው መቃረቢያን


(ስራ) ይፈልጋሉ፡፡” (አል’ኢስራእ፡ 57)

ኢሳ ኢብን መርየምን እና እናቱን ይጣራሉ፡፡ አላህ በእርግጥ የሚከተለውን ተናግሯል ፡


ُ َ َ َّ َ ُ ْ َ َ َ ٌ َ ُ ُّ ُ َ ُ ُ ُّ َْ ْ َ َ َْ ٌ َّ َ ْ ُ ‫س‬ ْ َّ
ْ‫انظر‬ ‫ص ِّديقة َكنا يأكال ِّن الطعام‬ ِّ ‫يح اب ُن م ْر َي َم إَِّل َر ُسول قد خلت مِّن قبلِّهِّ الرسل وأمه‬ ِّ ‫﴿ما ال َم‬
ُ َ ُ ْ َ َ َ
ًّ‫ك ْم ََضا‬ ُ َ ُ ُ ْ َ َ ْ ُ َ ُ َ ْ ُ َّ َ ْ ُ َّ ُ َ ُ ُ َ ُ َ ُ َ ْ َ
‫ون اّللِّ ما َل يملِّك ل‬
ِّ ‫ات ثم انظر أَّن يؤفكون۞قل أتعبدون مِّن د‬ ِّ ‫كيف نب ِّني لهم اْلي‬
ُ َ ْ ُ َّ َ ُ ُ َ ً ْ َ َ َ
﴾‫وَل نفعا واّلل هو الس ِّميع العلِّيم‬

“የመሬም ልጅ አልመሲህ ከበፊቱ መልእክተኞች በእርግጥ ያለፉ የሆነ መልእክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
13/37
እናቱም በጣም እውነተኛ ናት፡፡ (ሁለቱም) ምግብን የሚበሉ ነበሩ ፤ አንቀጾችን ለነርሱ (ለከሀዲዎች)
እንዴት እንደምናብራራ ተመልከት ከዚያም (ከእውነት) እንዴት እንደሚመለሱ ተመልከት፡፡ ከአላህ
ሌላ ለእናንተ መጉዳትንና መጥቀምን የማይችል ትገዛላችሁን? በላቸው፡፡ አላህም እርሱ ሰሚው ዐዋቂ
ነው፡፡” (አል’ማኢዳ፡ 75-76)

የሚከተለውን የአላህ ቃል አውሳለት፡


َ َ‫ك أ‬
َ‫نت َو ِّ ُِّلنا‬ َ َ َ ْ ُ ُ َ َ ُ ُ ْ َ ُ َ ْ ُ َّ َ ُ َ َ َ َ َ ْ ُ ُ َ َّ ُ ً َ ْ ُ ُ ُ ْ َ َ ْ َ َ
‫﴿ويوم َيْشهم َجِّيعا ثم يقول ل ِّلمالئِّكةِّ أهؤَلء إِّياكم َكنوا يعبدون۞قالوا سبحان‬
َ ُ ْ ُّ ُ ُ َ ْ َ َّ ْ َ ُ ُ ْ َ ُ َ ْ َ ُ
﴾‫اْلن أكَثهم ب ِّ ِّهم مؤمِّنون‬ ِّ ‫مِّن دون ِّ ِّهم بل َكنوا يعبدون‬

“ሁሉንም በሚሰበስባቸው እና ከዚያም ለመላእክቶቹ “እነዚህ እናንተን ይግገዙ ነበሩን?” በሚላቸው


ቀን (የሚሆነውን አስታውስ)፡፡ (መላእክቶቹም) “ጥራት ይገባህ ከእነርሱ ሌላ ረዳታችን አንተ ብቻ
ነህ፡፡ (እንደሚሉት) አይደለም ይልቁንም ጅንን ይግገዙ ነበሩ፡፡ አብዛኞቻቸው በእነርሱ አማኞች ናቸው”
ይላሉ፡፡ (ሰበእ፡ 40-41)

የአላህን ቃል (አውሳለት)፡
َ َ ُ َْ َ َ َُ ُ َّ َّ َ ُ َ ََ َ َ ْ َ َ ْ َ ُ ‫﴿ِإَوذْ قَ َال‬
َ‫اّلل ي‬
‫ون اّللِّ قال‬ِّ ‫د‬ ‫ِّن‬‫م‬ ‫ني‬
ِّ ‫ـه‬ ‫ل‬ِّ ‫إ‬ ‫ّم‬
ِّ ‫أ‬‫و‬ ‫وِن‬
ِّ ‫ذ‬ ِّ ‫اَّت‬ ِّ
‫اس‬ ‫ِّلن‬ ‫ل‬ ‫لت‬ ‫ق‬ ‫نت‬ ‫أ‬ ‫أ‬ ‫م‬ ‫ي‬‫ر‬ ‫م‬ ‫ن‬ ‫اب‬ ‫ِّيَس‬
‫ع‬ ‫ا‬
َ َ َْ َ ُ َ ْ َ ُ َْ َ ْ َ َ ُ ُْ ُ ُ ُ َ َ ْ َ َ َ َُ ْ َ ُ ُ َ َ َ َ َ ْ ُ
‫سبحانك ما يكون َِّل أن أقول ما ليس َِّل ِِّب ٍق إِّن كنت قلته فقد علِّمته تعلم ما ِِّف نف َِّس وَل‬
ُ ُ ْ ُ َّ َ َ َ َ َّ َ ْ َ َ ُ َْ َ
﴾‫وب‬
ِّ ‫سك إِّنك أنت عالم الغي‬ ِّ ‫أعلم ما ِِّف نف‬

“አላህም፡- “የመሬም ልጅ ኢሳ ሆይ! አንተ ለሰዎቹ፡- እኔንና እናቴን ከአላህ ሌላ ሁለት አምላኮች
አድርጋችሁ ያዙ ብለሃልን” በሚለው ጊዜ (አስታውስ)፡፡ “ጥራት ይገባህ ፤ ለእኔ ተገቢዬ ያልሆነን ነገር
ማለት ለኔ አይገባኝም፡፡ ብዬው እንደሆነም በእርግጥ አውቀኸዋል፡፡ በነፍሴ ውስጥ ያለውን ሁሉ
ታውቃለህ፡፡ ግን ከአንተ ነፍስ ያለውን አላውቅም፡፡ አንተ ሩቆችን ሁሉ በጣም ዐዋቂ አንተ ብቻ ነህና”
ይላል፡፡ (አል’ማኢዳ፡ 116)

ለእርሱ ንገረው፡ ጣዖትን አላማ ያደረገን ሰው አላህ በከሐዲነት እንደፈረጀው አውቀሀል ፤


እንዲሁም ደጋጎችን አላማ ያደረገን በከሐዲነት የፈረጀ መሆኑን ፣ የአላህ መልእክተኛ ‫ﷺ‬
የተጋደሏቸው መሆኑንም አውቀሀል፡፡
14/37
እርሱም ካለ፡ ከሀዲዎች ከእነርሱ ይፈልጋሉ ፤ እኔ ግን አላህ ጠቃሚ ፣ ጎጅ እንዲሁም አስተናባሪ
መሆኑን እመሰክራለሁ፡፡ ከእርሱ እንጅ አልፈልግም፡፡ ደጋጎች ለእነርሱ አንዳች ነገር (መብቱ)
የላቸውም፡፡ ነገር ግን እነርሱን አላማ ያደረግኩኝ የእነርሱን ምልጃ ከአላህ ዘንድ ተስፋ
ስለማደርግ ነው፡፡
መልሱ፡ ይህ እኩል በእኩል የከሐዲዎች ንግግር ነው፡፡

የሚከተለውን የአላህ ቃል በእርሱ ላይ አንብብ፡


َ ْ ُ َّ َ َ ُ َ ُ َّ ْ ُ ُ ُ ْ َ َ َ ْ َ ُ ُ َ َّ َ َّ َ
﴾‫ِّين اَّتذوا مِّن دونِّهِّ أو ِِّلاء ما نعبدهم إَِّل ِِّلق ِّربونا إَِّل اّللِّ زلف‬
‫﴿واَّل‬

“እነዚያም ከእርሱ ሌላ (ጣኦታትን) ረዳቶች የያዙት “ወደአላህ ማቃረብን እንዲያቃርቡን እንጅ ለሌላ
አንገዛቸውም” (ይላሉ) (አዝ’ዙመር፡ 3)

የሚከተለውንም የአላህ ቃል (አንብብ)፡


ُ َ َ ُ
َ ‫اؤنَا ع‬ ُ َ َ ُ ُ
﴾ِّ‫ِّند اّلل‬ ‫﴿ َو َيقولون هـؤَلء شفع‬

“እነዚህም አላህ ዘንድ አማላጆቻችን ናቸው” ይላሉ፡፡ (ዩኑስ፡ 18)

እነዚህ ሶስት ማስመሰያዎች ከእነርሱ ዘንድ ትልቆቹ መሆናቸውን እወቅ፡፡ አላህ በቁርኣኑ ግልጽ
ያደረገ መሆኑን ካወቅክ ፣ በደንብ እርሷን መገንዘብን ከተገነዘብክ ከእርሷ በኋላ ያለው በጣም
ቀላል ነው፡፡
ክፍል ስምንት
ዱዓ አምልኮ አይደለም ባሉ አካላት ለይ የተሰጠው ምላሽ የሚብራራበት ክፍል

የሚከተለውን ከተናገረ፡ እኔ አላህን እንጅ ሌላን አልገዛም፡፡ ይህ ወደነርሱ መጠጋቱ ፣ እነርሱን


መጥራቱ አምልኮ አይደለም፡፡

ለእርሱ የሚከተለውን ንገረው፡ አምልኮን ማጥራት አላህ በአንተ ላይ ግዴታ ያደረገው በአንተ ላይ
የእርሱ ሐቁ መሆኑን ታረጋግጣለህ?
15/37
የሚከተለውን ካለ፡ አዎ

ለእርሱ የሚከተለውን ንገረው፡ አላህ በአንተ ላይ ግዴታ ያደረገውን ለእኔ አብራራልኝ፡፡ እርሱም
አምልኮን ማጥራት ነው፡፡ እርሱም በአንተ ላይ የእርሱ ሀቅ ነው፡፡ እንሆ እርሱም አምልኮንና
አይነቶቿንም አያውቅም፡፡
ለእርሱ በሚከተለው ንግግርህ አብራራለት፡ አላህ የሚከተለውን ተናግሯል፡
َ ‫ب ال ْ ُم ْع َت ِّد‬
﴾‫ين‬
َ ُ َّ ً َ ْ ُ َ ً ُّ َ َ ْ ُ َّ َ ْ ُ ْ
ُّ ِّ‫َل َُي‬ ‫﴿ادعوا ربكم تَضَع وخفية إِّنه‬

“ጌታችሁን ተዋርዳችሁ በድብቅም ለምኑት፡፡ እርሱ ወሰን አላፊዎችን አይወድምና፡፡”


(አል’አዕራፍ፡ 55)

በዚህ ካሳወቅከው ለእርሱ የሚከተለውን በለው፡ እርሱ (ዱዓ) ለአላህ አምልኮ ነውን? –
“አዎ! ዱዓ ከአምልኮ ነው” ማለቱ የማይቀር ነው፡፡

ለእርሱ የሚከተለውን ንገረው፡ እንሆ እርሷ አምልኮ መሆኗን ካረጋገጥክ ፣ ሌሊት እና ቀንን
አላህን ፈርተህና ተስፋ አድርገህ ከጠራህ ከዚያም በዚያ ጉዳይ ላይ ነብይን ወይም ሌላን ከጠራህ
በአላህ አምልኮ ሌላን አላጋራህምን?

“አዎ!” ማለቱ የማይቀር ነው፡፡


ለእርሱ የሚከተለውን ንገረው፡ አላህ የሚከተለውን ተናግሯል፡
ْ َ َ
﴾‫﴿ف َص ِّل ل َِّربِّك َواْنَ ْر‬

“ስለዚህ ለጌታህ ስገድ ፤ (በስሙ) ሰዋም፡፡” (አል’ከውሰር፡ 2)

አላህን ከታዘዝክ ፣ ለእርሱ ካረድክ ፣ ይህ አምልኮ ነውን?

“አዎ!” ማለቱ የማይቀር ነው፡፡

ለእርሱ የሚከተለውን ንገረው፡ ለፍጡር ካረድክ ፡ ነብይ ወይም ጅን ወይም ከሁለቱ ሌላ - በዚህ
አምልኮ ከአላህ ውጭ አጋራህን?
16/37
“አዎ!” ማለቱ የማይቀር ነው፡፡

በተጨማሪ ለእርሱ የሚከተለውን ንገረው ፡ ቁርኣን በእነርሱ ላይ የወረደባቸው አጋሪዎች


መላኢካን ፣ ደጋጎችን ፣ ላትን እና ሌሎችን አካላት ይገዙ ነበርን?

አዎ! ማለቱ የማይቀር ነው፡፡

ለእርሱ የሚከተለውን ንገረው፡ በዱዓ ፣ በእርድ ፣ ወደነርሱ በመጠጋት እና በመሳሰሉት እንጅ


እነርሱን ማምለካቸው በሌላ ነበርንʔ

ካለበለዚያ እነርሱ እርሱን ተገዥዎች ፣ በአላህ ቁጥጥር ስር መሆናቸውን ፣ ነገሮችን


የሚያስተናብር አላህ መሆኑን አረጋጋጮች ናቸው፡፡ ነገር ግን ለልቅና እና ለምልጃ ሲሉ እነርሱን
ጠሯቸው፡፡ ይህ በጣም ግልጽ ነው፡፡

ክፍል ዘጠኝ

በሸሪዓዊው ምልጃ እና ሽርክ በሆነው ምልጃ መካከል ያለው ልዩነት የሚብራራበት ክፍል

የሚከተለውን ከተናገረ፡ የአላህን መልእክተኛ ምልጃ ትቃወማላችሁንʔ ፣ ከእርሷ እራሳችሁን


ንጹህ ታደርጋላችሁንʔ

ለእርሱ ንገረው፡ አልቃወማትም፡፡ ከእርሷም ራሴን ንጹህ አላደርግም፡፡ ይልቁንም እርሱ ‫ﷺ‬
አማላጅ ፣ ምልጃው ተቀባይነት ያለው ነው፡፡ የእርሱን ምልጃ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ነገር ግን ምልጃ
በአጠቃላይ የአላህ ነች፡፡

አላህ እንደተናገረው፡
ً ‫اع ُة ََج‬
﴾‫ِّيعا‬
َّ َّ ُ
َ ‫الش َف‬
ِّ‫﴿قل ِّّلل‬

“ምልጃ ሁሉም የአላህ ብቻ ነው፡፡” (አዝ’ዙመር፡ 44)

አላህ እንደተናገረው ከአላህ ፈቃድ በኋላ እንጅ አትሆንም፡፡


17/37
ْ َّ ُ َ ْ ُ َ ْ َ َّ َ َ
﴾ِّ‫﴿من ذا اَّلِّي يشفع عِّنده إَِّل بِّإِّذنِّه‬

“ያ እርሱ ዘንድ በፈቃዱ ቢሆን እንጅ የሚያማልድ ማነውʔ” (አል’በቀራህ፡ 255)

አላህ እንደተናገረው አላህ ከፈቀደ በኋላ እንጅ ለአንድም ሰው አያማልድም፡፡


َ َ ْ َ َّ َ ُ َ ْ َ َ َ
﴾‫ارتض‬ ‫﴿وَل يشفعون إَِّل ل ِّم ِّن‬

“ለወደደውም ሰው እንጅ ለሌላው አያማልዱም” (አል’አንቢያእ፡ 28)

አላህ እንደተናገረው እርሱ ተውሂድን እንጅ አይወድም፡፡


ْ َ ْ َ َ ً ِّ َ ْ َ ْ َ َ ْ َ َ َ
﴾‫ِّينا فلن ُيق َبل مِّن ُه‬ ِّ ‫﴿ومن يبتغِّ غري‬
‫اإلسالم د‬

“ከኢስላም ሌላ ሃይማኖትን የሚፈልግ ሰው ፈጽሞ ከርሱ ተቀባይ የለውም፡፡” (አል’ዒምራን፡ 85)

ምልጃ ሁሏም ለአላህ ከሆነች ፣ ከእርሱ ፈቃድ በኋላ እንጅ የማትሆን ከሆነ ፣ አላህ በእርሱ
ካልፈቀደ በቀር ነብዩም ይሁኑ ሌሎች አካላት ለአንድም ማማለድ የማይችሉ ከሆነ ፣ ለተውሂድ
ባለቤቶች እንጅ የማይፈቅድ ከሆነ ምልጃ በአጠቃላይ ለአላህ መሆኑ ግልጽ ሆነ ፤ ከእርሱም
እፈልጋታለሁ ፤ “አላህ ሆይ! የእርሱን ምልጃ አትከልክለኝ ፤ አላህ ሆይ! ስለኔ አማላጅ
አድርገው ፣ እና የመሳሰሉትን” እላለሁ፡፡

የሚከተለውን ከተናገረ፡ ነብዩ ምልጃ ተሰጧቸዋል ፣ እኔ ደግሞ አላህ ከሰጠው አካል


እፈልጋታለሁʔ

መልሱ፡ አላህ ምልጃን ሰጦታል ፣ ከዚህ (ከረሡል ‫ ﷺ‬ከመፈለግ) ከልክሎሀል ፣


አላህ የሚከተለውን ተናግሯል፡
ً َ َ َّ َ َ ُ ْ َ َ َ َّ َ َ َ ْ َّ َ َ
﴾‫جد ِّّللِّ فال تدعوا مع اّللِّ أحدا‬
ِّ ‫﴿وأن المسا‬
“እንሆ መስጊዶችም (ምድር በአጠቃላይ) የአላህ (አምልኮ መፈጸሚያ) ብቻ ናቸው፡፡” (ጅን፡ 18)

የእርሱን ነብይ ምልጃ ከአላህ መፈለግህ አምልኮ ነው፡፡ በዚህ አምልኮ አንድንም አካል ማጋራትን
18/37
አላህ ከልክሎሀል፡፡ የእርሱን ነብይ ለአንተ አማላጅ እንዲያደርገው አላህን የምትማጸን ከሆነ
ባሳለፍነው ንግግሩ እርሱን ታዘዘው፡፡
“እንሆ መስጊዶችም (ምድር በአጠቃላይ) የአላህ (አምልኮ መፈጸሚያ) ብቻ ናቸው፡፡” (ጅን ፡ 18)

በተጨማሪ፡ ምልጃን ከነብዩ ‫ ﷺ‬ውጭ ሰጧታል፡፡ መላኢካዎች እንደሚያማልዱ ፣ ህጻናቶች


እንደሚያማልዱ ፣ ወልዮች እንደሚያማልዱ በትክክለኛ ሐዲስ ተረጋግጧል፡፡

“አላህ ምልጃን ሰጧቸዋልና ከእነዚህ እፈልጋለሁ፡፡” ትላለህን?

የምትል ከሆነ ፡ አላህ በቁርኣኑ ያወሳት የሆነችን - ወደደጋጎች አምልኮ ተመለስክ፡፡

የምትል ከሆነ፡ “በፍጹም!” ፡ (የሚከተለው) ንግግርህ ተበላሸ - “አላህ ምልጃን ሰጧቸዋል፡፡


እኔ ደግሞ አላህ ከሰጠው አካል እፈልጋታለሁ፡፡”

ክፍል አስር
ወደደጋጎች መጠጋት ሽርክ መሆኑን ማረጋገጥና

ይህን የተቃወመን አካል እርሱን (ሽርክ መሆኑን) እንዲመሰክር ማስገደድ

የሚከተለውን ከተናገረ፡ “እኔ በአላህ አንድም አላጋራም፡፡ ነፍሴን አጠራለሁ ፣ ተከልከል! ነገር
ግን ወደደጋጎች መጠጋት ማጋራት አይደለም፡፡”

ለእርሱ የሚከተለውን ንገረው፡ አላህ ከዝሙት ሀራምነት በከበደ ሁኔታ ማጋራትን እርም አድርጓል
ብለህ የምታረጋግጥ ከሆነ ፣ አላህ ፍጹም የማይምረው መሆኑን የምታረጋግጥ ከሆነ ፣ ይህ አላህ
ሀራም ያደረገው ነገር ምንድን ነው ፣ አልምረውም ብሎ የተናገረው ምንድን ነው? እንሆ እርሱ
አያውቅም፡፡

ለእርሱ የሚከተለውን ንገረው፡ እንዴት ነፍስህን ከማጋራት ነጻ ታደርጋለህ? - አንተ እርሱን


ሳታውቅ?
19/37
ይህንን በአንተ ላይ አላህ እንዴት ሀራም ያደርጋል? እንደማይምረው እንዴት ያወሳል? አንተ
ከእርሱ የማትጠይቅ ስትሆን ፣ አንተ እርሱን የማታውቅ ስትሆን? አላህ ሀራም ያደረገውን ለእኛ
አያብራራውም ብለህ ትገምታለህʔ!

እርሱ የሚከተለውን ከተናገረ፡ “ማጋራት ማለት ጣዖታትን መገዛት ማለት ነው ፤ እኛ ደግሞ


ጣዖታትን አንገዛም፡፡”

ለእርሱም ንገረው፡ የጣዖት አምልኮ ትርጉሙ ምንድን ነውʔ እነርሱ ፣ ዲንጋዮች ፣ እንጨቶች
ለጠራቸው ሰው ይፈጥራሉ ፣ ይመግባሉ ፣ ነገርን ያስተናብራሉ የሚል እምነት አላቸው ብለህ
ትጠረጥራለህንʔ ይህን ደግሞ ቁርኣን ያስተባብለዋል፡፡

የሚከተለውን ከተናገረ፡ እርሱ እንጨትን ወይም ዲንጋይን ፣ ወይም ከቀብር ለይ የተገነባን ግንባታ
ወይም ሌላን አላማ የሚያደርግ ፣ እርሱንም የሚማጸን ፣ ለእርሱ የሚያርድ “ወደአላህ
ማቃረብን ያቃርበኛል ፣ በእርሱ በረከት ከእኛ ላይ አላህ ይከላከላል ፣ በእርሱ በረከት ይሰጠናል”
የሚል ነው፡፡

ለእርሱ ንገረው፡ እውነትክን ነው፡፡ ይህ ከዲንጋዮች ዘንድ ፣ ከመቃብሮች እና ከሌሎች


ግንባታዎች ዘንድ የእናንተ ተግባራችሁ ነው፡፡ ይህ ተግባራቸው እርሱ የጣዖት አምልኮ እንደሆነ
አረጋገጠ፡፡ እርሱም ተፈላጊ ነው፡፡

እንደዚሁ ለእርሱ ይንነገረዋል፡ “ማጋራት የጣዖት አምልኮ ነው” የሚለው ንግግርህ ፤ ማጋራት
በዚህ ብቻ የተለየ ነው የሚል ነው ፍላጎትህ? ወደደጋጎች መጠጋት ፣ እነርሱን መማጸን በዚህ
ውስጥ አይገባም የሚል ነው ፍላጎትህ?

ይህን ደግሞ በመላኢካ ወይም በኢሳ ወይም በደጋጎች (ልቦናው) የተያያዘ (የተጠጋ) ክህደት
መሆኑን አላህ በመጽሐፉ ያወሳው ይመልሰዋል፡፡

“በአላህ አምልኮ ከደጋጎች አንድንም አካል ያጋራ ፣ እርሱ በቁርኣን የተወሳው ማጋራት ነው”
20/37
በማለት ማረጋገጡ አይቀርም፡፡ ይህ ደግሞ ተፈላጊ ነው፡፡

የዚህ ጉዳይ ሚስጢሩ፡ “እንሆ እኔ በአላህ አላጋራም” ካለ፡፡

ለእርሱ የሚከተለውን ንገረው፡ “በአላህ ማጋራት ምንድን ነው? ፣ ለእኔ አብራራልኝ”

የሚከተለውን ከተናገረ፡ “እርሱ የጣዖት አምልኮ ነው፡፡”

ለእርሱ ንገረው፡ “የጣዖት አምልኮ ምንድን ነው? ለእኔ አብራራልኝ”

የሚከተለውን ከተናገረ፡ “እኔ አላህን እንጅ አልገዛም”

ለእርሱ በለው፡ “ለእርሱ ሸሪካ የሌለው በብቸኛነት አላህን መገዛት ትርጉሙ ምንድን ነው? ለእኔ
አብራራልኝ”

በቁርኣን አላህ እንዳብራራው አድርጎ ከተነተነልህ እርሱ ተፈላጊ ነው፡፡ የማያውቀው ከሆነ ፣
እንዴት እርሱ በማያውቀው ነገር ይሞግታል?

ያለትርጉሙ ካብራራው፡ በአላህ ማጋራት ፣ በቀጥታ በዚህ ዘመን የሚሰሩት የሆነውን የጣዖት
አምልኮ ትርጉም ግልጽ በሆኑ አንቀጾች ለእርሱ ታብራራለታለህ፡፡ በእርሱ ምንም ሳያጋሩ
በብቸኛነት አላህን ማምለክ በእኛ ላይ የሚቃወሙን እርሱን ነው፡፡ ወንድሞቻቸው እንደጮሁት
የሚጮሁበት እርሱ ነው፡፡

እነርሱ ባሉ ጊዜ፡
ٌ َ ُ ٌ ْ َ َ َ َ َّ ً َ ً َ َ َ ْ َ َ َ َ
﴾‫حدا إِّن هذا لَشء عجاب‬ِّ ‫﴿أجعل اْلل ِّهة إِّلها وا‬
“አማላክቶቹን አንድ አምላክ አደረጋቸውንʔ ይህ አስደናቂ ነገር ነው” (አሉ) (ሷድ፡ 5)

እርሱ የሚከተለውን ከተናገረ፡ “እነርሱ መላኢካዎችን ፣ ነብያቶችን በመጣራታቸው አልካዱም


፣ የካዱት “መላኢካዎች የአላህ ሴት ልጆች ናቸው” ብለው በተናገሩ ጊዜ ነው፡፡ እኛ
ዓብዱልቃድር እና ሌሎችም የአላህ ወንድ ልጆች ናቸው አላልንም”
21/37
መልሱ፡ ልጅን ወደአላህ ማስጠጋት እራሱን የቻለ ክህደት ነው፡፡
አላህ የሚከተለውን ተናግሯል፡
ُ َ َّ ُ َّ ٌ َ َ ُ َّ ُ ْ ُ
﴾‫﴿قل ه َو اّلل أحد۞اّلل الصمد‬
“በል “እርሱ አላህ አንድ ነው፡፡ “አላህ (የሁሉ) መጠጊያ ነው፡፡” (አል’ኢኽላስ፡ 1-2)

“አልአሀዱ” ፡ ለእርሱ ሸሪካ የሌለው ማለት ነው፡፡ “አስሶመድ” ፡ ለሐጃዎች ሁሉ ወደርሱ


የሚጠጉበት ማለት ነው፡፡ ይህን ያስተባበለ በእርግጥ ካደ ፤ የምዕራፉን መጨረሻ ባያስተባብልም
(አልወለደም አልተወለደም… የሚለውን አንቀጽ)፡፡
አላህ የሚከተለውን ተናግሯል፡
َ ْ َُ َ َ َ ََ ََ ُ َّ َ َ َّ َ
﴾‫َل وما َكن معه مِّن إ ِّ ٍَل‬
ٍ ‫﴿ما اَّتذ اّلل مِّن و‬
“አላህ ምንም ልጅን አልያዘም (አልወለደም)፡፡ ከእርሱም ጋር አንድ አምላክ የለም” (አል’ሙእሚኑን፡ 91)

በሁለቱ ዓይነቶች ለይየ፡፡ እያንዳንዳቸውን ራሳቸውን የቻሉ ክህደት አደረጋቸው፡፡


አላህ የሚከተለውን ተናግሯል፡-
ْ َْ َ َ َ َ َ ُ َ ْ ُ َ َ َ ْ ُ َ َ َ َ َّ ْ ََ ُ ْ َُ َ َ
﴾‫ري عِّل ٍم‬ ‫غ‬
ِّ ِّ ‫ب‬ ‫ات‬
ٍ ‫ن‬ ‫ب‬ ‫و‬ ‫ني‬ِّ ‫ن‬ ‫ب‬ ‫َل‬ ‫وا‬‫ق‬‫ر‬ ‫خ‬ ‫و‬ ‫م‬ ‫ه‬ ‫ق‬ ‫ل‬ ‫خ‬‫و‬ ‫ن‬ ‫اْل‬
ِّ ‫ء‬‫َك‬ ‫ُش‬ ِّ ‫ّلل‬
ِّ ‫﴿وجعلوا‬

“ለአላህም አጋንንትን የፈጠራቸው ሲሆን (በመታዘዝ) ተጋሪዎች አደረጉ፡፡ ወንዶች ልጆችንና ሴቶች
ልጆችንም ያለ እውቀት ለእርሱ ቀጠፉ፡፡” (አል’አንዓም፡ 100)

በሁለቱ ክህደት መካከል ለይየ

በዚህ ላይ ማስረጃው በተጨማሪ -ላትን በመጣራት ከሀዲ የሆኑት- ደግ ሰው ከመሆኑ ጋር-


የአላህ ልጅ አላደረጉትም፡፡

እንደዚሁ ዑለሞች -በተጨማሪ- ፡ አጠቃላይ አራቱ መዝሀቦች “ባቡ ሁክሙል ሙርተድ”


በሚለው ምዕራፍ ውስጥ አንድ ሙስሊም ለአላህ ልጅ አለው ብሎ ካለ ሙርተድ (ከኢስላም
የወጣ) መሆኑን ያወሳሉ፡፡ በአላህ ካጋራ እርሱ ሙርተድ ነው፡፡ በሁለቱ መካከል ያለውን
ይለያሉ፡፡ ይህ በጣም ግልጽ የሆነ ነው፡፡
22/37
አላህ ተናግሯል፡
َ ََُْ ْ ُ َ َ ْ َْ َ ٌْ َ َ ْ َ َّ َ
َ
﴾‫﴿أَل إِّن أو ِِّلاء اّللِّ َل خوف علي ِّهم وَل هم َيزنون‬

“ንቁ! የአላህ ወዳጆች በእነሱ ላይ ፍርሃት የለባቸውም ፤ እነሱም አያዝኑም፡፡” (ዩኑስ፡ 62)

(አንተም ለእርሱ የሚከተለውን) ተናገር፡ ይህ እርሱ ሀቅ ነው (“ፍርሀት የለባቸውም እነሱም


አያዝኑም” የሚለው)፡፡ ነገር ግን እነርሱ አይመለኩም፡፡ ከአላህ ጋር መመለኩን ፣ ከእርሱ ጋር
መጋራቱን እንጅ እኛ አንቃወምም፡፡ ካለበለዚያ በአንተ ለይ ግዴታው እነርሱን መውደድ ፤
እነርሱን መከተል ነው፡፡ ከራማቸውን ማረጋገጥ ነው፡፡ የወልዮችን ከራማ የሚቃወም የለም
የቢድዓ እና የጥመት ባለቤት ቢሆን እንጅ፡፡

የአላህ ዲን በሁለት ጽንፎች መካከል ነው፡፡ በሁለት ጥመት መካከል ያለ ቅን ጎዳና ነው፡፡ በሁለት
ብልሹዎች መካከል ያለ ሐቅ ነው፡፡

ክፍል አስራ አንድ


የመጀመሪያዎቹ ህዝቦች ማጋራት ፣ ከዘመናችን ህዝቦች ማጋራት በሁለት ነገሮች ቀለል ያለ
መሆኑን የሚያረጋግጥ ክፍል

ካወቅህ፡ በዘመናችን የሚገኙ አጋሪዎች “ከቢረል ኢዕቲቃድ” (ትልቁ እምነት) ብለው


የሚጠሩት እርሱ ቁርኣን የወረደበት ማጋራት ነው፡፡ በእርሱ ላይ የአላህ መልእክተኛ ‫ﷺ‬ሰዎችን
የተጋደሉበት ነው፡፡

የመጀመሪያዎቹ (ትውልዶች) ማጋራት ከወቅታችን ሰዎች ማጋራት በሁለት ነገሮች ቀላል መሆኑን
እወቅ

አንደኛው፡ የመጀመሪያዎቹ አያጋሩም ፣ ከአላህ ጋር መላኢካን ወይም ወልይን ወይም ጣዖቶችን


አይማጸኑም በደስታ ጊዜ እንጅ፡፡ በብርቱ ችግር ጊዜ ሀይማኖትን ለአላህ ብቻ ያጠራሉ፡፡
23/37
አላህ በቁርኣን እንደተናገረው፡
َ ُ ْ ُ ْ ُ َ َ ْ َ ْ ُ َّ َ َّ َ َ َ ُ َ َ ْ ُ َ َّ ُ َ َ ْ ُ ْ ُ ‫﴿فَإ َذا َرك‬
﴾‫ْشكون‬
ِّ ‫ي‬ ‫م‬ ‫ه‬ ‫ا‬‫ذ‬ِّ ‫إ‬ ‫َب‬
ِّ ‫ال‬ ‫َل‬ِّ ‫إ‬ ‫م‬ ‫اه‬‫َن‬ ‫ا‬‫م‬ ‫ل‬ ‫ف‬ ‫ِّين‬
‫اَل‬ ‫َل‬ ‫ني‬ ‫ص‬
ِّ ِّ ‫ل‬ ‫ُم‬ ‫اّلل‬ ‫ا‬‫و‬‫ع‬ ‫د‬ ‫ك‬
ِّ ‫ل‬ ‫ف‬ ‫ال‬ ‫ِف‬
ِّ ‫وا‬‫ِّب‬ ِّ
“በመርከቦች ውስጥ በተሳፈሩ ጊዜም አላህን መገዛትን ለእርሱ ብቻ ያጠሩ ሆነው ይጠሩታል፡፡ ወደየብስ
(በማውጣት) ባዳናቸው ጊዜ ወዲያውኑ እነርሱ (ጣኦትን) ያጋራሉ፡፡” (አል’አንከቡት፡ 65)
ُ َ ْ َ َ َ ْ ُ ْ َ ْ َ َ ْ َ ْ ُ َّ َ َّ َ َ ُ َّ َّ َ ُ ْ َ َ َّ َ ْ َ ْ ُّ ُّ ْ ‫ك ُم ال‬
ُ َّ َ َ ﴿
‫اإلنسان‬
ِّ ‫ن‬ ‫َك‬ ‫و‬ ‫م‬ ‫ت‬ ‫ض‬‫ر‬ ‫ع‬ ‫أ‬ ‫َب‬
ِّ ‫ال‬ ‫َل‬ِّ ‫إ‬ ‫م‬ ‫اك‬‫َن‬ ‫ا‬‫م‬ ‫ل‬ ‫ف‬ ‫اه‬‫ي‬ ‫إ‬ ‫َل‬
ِّ ِّ ‫إ‬ ‫ون‬‫ع‬ ‫د‬‫ت‬ ‫ن‬ ‫م‬ ‫ل‬ ‫ض‬ ‫ر‬
ِّ ‫ح‬ ‫اْل‬ ‫ِف‬
ِّ ‫َض‬ ‫ِإَوذا مس‬
ً َُ
﴾‫كفورا‬

“በባህሩም ውስጥ ጉዳት ባገኛችሁ ጊዜ የምትጠሯቸው (አማልክት) ሁሉ ከእርሱ (ከአላህ) በቀር


ይጠፋሉ፡፡ ወደየብስም በማድረስ ባዳናችሁ ጊዜ (እምነትን) ትተዋላችሁ፡፡ ሰውም በጣም ከሀዲ ነው፡፡”
(አል’ኢስራእ፡ 67)
َْ َ َ ْ ُ ُ َ ُ َْ َ ْ َ َ ُ َ َّ ُ ُ ْ َ َ ْ َ ُ َ َ ْ ُ ََ ْ ُ ُْ َََ ْ ُ
‫﴿قل أرأيتكم إِّن أتاكم عذاب اّللِّ أو أتتكم الساعة أغري اّللِّ تدعون إِّن كنتم صادِّق ِّني۞بل‬
َ ُ ْ ُ َ َ ْ َ َ َ َ ْ ْ َ َ ُ ْ َ َ ُ ْ َ َ َ ُ ْ َ ُ َّ
﴾‫ْشكون‬ ِّ ‫شف ما تدعون إِِّلهِّ إِّن شاء وتنسون ما ت‬ ِّ ‫إِّياه تدعون فيك‬

“የአላህ ቅጣት ቢመጣባችሁ ወይም ሰዓቲቱ (ትንሳኤ) ብትመጣባችሁ ከአላህ ሌላን ትጠራላችሁን?
እውነተኞች እንደሆናችሁ ንገሩኝ በላቸው፡፡ አይደለም እርሱን ብቻ ትጠራላችሁ ቢሻም ወደርሱ
የምትጠሩበትን ነገር ያስወግዳል፡፡ የምታጋሩትንም ነገር ትተዋላችሁ (በላቸው)” (አል’አንዓም፡ 40-41)
َُْ ْ َ ُ ْ َ َ َ َ َ َ ُ ْ ً َ ْ ُ َ َّ َ َ َّ ُ ْ َ ً ُ ُ َّ َ َ َ ٌّ ُ َ َ ْ َّ َ َ
‫اإلنسان َض دَع ربه منِّيبا إِِّلهِّ ثم إِّذا خوَل ن ِّعمة مِّنه ن َِّس ما َكن يدعو إِِّلهِّ مِّن قبل‬ ِّ ‫﴿ِإَوذا مس‬
َّ َ ْ َ ْ َ َّ ً َ َ ْ ُ ْ َّ َ َ ْ ُ َ َ َّ ُ ً َ َ َّ َ َ َ َ
﴾ِّ‫اب اَّلار‬
ِّ ‫ضل عن سبِّيلِّهِّ قل تمتع بِّكف ِّرك قلِّيال إِّنك مِّن أصح‬ ِّ ‫وجعل ِّّللِّ أندادا ِِّل‬

“ሰውንም ጉዳት ባገኘው ጊዜ ጌታውን ወደርሱ ተመላሽ ሆኖ ይጠራል፡፡ ከዚያም ከእርሱ ዘንድ ጸጋን
በሰጠው ጊዜ ያንን ከዚያ በፊት ወደርሱ ይማጸንበት የነበረውን (መከራ) ይረሳል፡፡ ከመንገዱ
ለመሳሳትም ለአላህ ባላንጣዎችን ያደርጋል፡፡ “በክህደትህ ጥቂትን ተጣቀም፡፡ አንተ በእርግጥ ከእሳት
ጓዶች ነህ” በለው፡፡ (አዝ’ዙመር፡ 8)
َ ‫ني َ َُل اَل‬
﴾‫ِّين‬ ِّ َ َّ ‫لظلَل َد َع ُوا‬
َ ‫اّلل ُُمْلِّص‬ ُّ َ ٌ ْ َّ ُ َ َ َ
‫شيهم موج َك‬ ِّ ‫﴿ِإَوذا غ‬
ِّ
“እንደጥላዎችም የሆነ ማእበል በሸፈናቸው ጊዜ አላህን ሐይማኖትን ለእርሱ ብቻ ያጠሩ ሆነው
ይጠሩታል፡፡” (ሉቅማን፡ 32)
24/37

አላህ በቁርአኑ ግልጽ ያደረገውን ይህን ጉዳይ የተገነዘበ ፣ እርሱም -የአላህ መልእክተኛ ‫ﷺ‬
የተጋደሏቸው አጋሪዎች- በደስታ ጊዜ አላህን እና ሌላን እንደሚጠሩ ፤ በብርቱ ችግር ጊዜ ከሆነ
ደግሞ አላህን ብቻ እንጅ ሌላን እንደማይጠሩ ፤ አለቆቻቸውንም እንደሚረሱ (የተገነዘበ) ፣
በዘመናችን ያለውን ሽርክ እና የመጀመሪያዎቹ ሽርክ ልዩነቱ ለእርሱ ግልጽ ይሆንለታል፡፡ ነገር ግን
ይህን ጉዳይ ልቡ ጥልቅ በሆነ ግንዛቤ የሚገነዘብ የታለ? እገዛን ከአላህ እንፈልጋለን፡፡

ሁለተኛው ጉዳይ፡ የመጀመሪያዎቹ ከአላህ ዘንድ ሙቀረብ የሆኑትን ሰዎች ከአላህ ጋር ይጠራሉ
- ነብይ ወይም ወልይ ወይም መላኢካ ወይም ለአላህ ታዛዥ ሊሆን ይችላል፡፡ ወይም ወንጀለኛ
ያልሆኑትን ዲንጋይን ፣ ዛፍን ይጠራሉ፡፡

የዘመናችን ሰዎች ከአላህ ጋር ከሰዎች በጣም አመጸኛ የሆኑትን ይማጸናሉ፡፡ እነዚያ


የሚጠሯቸው ዝሙት ፣ ስርቆት ፣ ሶላትን መተው እና ሌላም ስለነርሱ የአመፅ ተግባሮች
የሚያወሩላቸው ናቸው፡፡

በደጋጎች የሚያምን ፣ ምንም ወንጀል የማይፈጽሙ ነገሮችን -ለምሳሌ፡ እንጨትን ፣ ዲንጋይን


(የሚያመልኩት)- ቀላል ነው ፣ አመጹ እና መበላሸቱ በግልጽ የሚታይበትን ፣ በእርሱም
የሚመሰከርበትን አካል (ከሚያመልኩት)

ክፍል አስራ ሁለት


በዲኑ ውስጥ የተወሰኑ ግዴታዎችን የፈጸመ ፣ የተውሂድን ተቃራኒ ቢፈጽምም ከሀዲ አይሆንም
ብለው ለሚሞግቱ አካላት ማስረጃው እስከ ዝርዝሩ

የአላህ መልእክተኛ ‫ ﷺ‬የተጋደሏቸው አጋሪዎች ከእነዚህ ይበልጥ ዓቅሎቻቸው ጤናማ ፤


ሽርካቸው በጣም የቀለለ መሆኑ ከተረጋገጠ ፣ ባወሳናቸው ጉዳዮች ላይ እነርሱ የሚያቀርቧቸው
ማመሳሰያዎች እንዳሏቸው እወቅ፡፡ እነርሱም ከታላላቅ ማመሳሰያዎች ናቸው፡፡ ለመልሷ ጀሮህን
ስጥ፡
25/37
እነርሱ የሚከተለውን ይናገራሉ፡ እነዚያ ቁርኣን በእነርሱ ላይ የወረደላቸው አካላት “ላኢላሃ
ኢልለሏህ” ብለው አይመሰክሩም ፤ የአላህን መልእክተኛ ‫ ﷺ‬ያስተባብላሉ ፤ ሞቶ መቀስቀስን
ይቃወማሉ ፤ ቁርኣንን ያስተባብላሉ ፤ (ቁርኣንን) ድግምት ያደርጉታል፡፡
እኛ “ላኢላሃ ኢልለሏህ ፣ ሙሐመድ ረሱሉሏህ” ብለን እንመሰክራለን ፣ ቁርኣንን እውነት
እንላለን ፣ ሞቶ በመቀስቀስ እናምናለን ፣ እንሰግዳለን ፣ እንጾማለን ፣ እንደነዚያ እንዴት
ታደርጉናላችሁ?

መልሱ፡ አንድ ሰው በአንድ ነገር ረሡልን ‫ ﷺ‬እውነት ብሎ ፣ በሆነ ነገር ካስተባበለው ከሐዲ
እንደሚሆን ፣ ወደኢስላም እንደማይገባ በሁሉም ዑለሞች መካከል ልዩነት የለም፡፡ በቁርኣን
በተወሰነው አምኖ በተወሰነው ካስተባበለም ልክ እንደዚሁ ነው፡፡ ልክ በተውሒድ አረጋግጦ
በሶላት ግዴታነት እንዳስተባበለ ነው ወይም በተውሂድ ፣ በሶለት አረጋግጦ በዘካ ግዴታነት
እንዳስተባበለ ነው፡፡ ወይም በዚህ ሁሉ አረጋግጦ በጾም ግዴታነት እንዳስተባበለ ነው፡፡ ወይም
በዚህ ሁሉ አረጋግጦ የሐጅን ግዴታነት እንዳስተባበለ ነው፡፡

በነብዩ ‫ ﷺ‬ዘመን ለሐጅ ህግ ታዛዥ ባለመሆናቸው እነርሱን አስመልክቶ አላህ የሚከተለውን


ቁርኣን አወረደ፡
َ ‫ِن َعن الْ َعالَم‬
ٌّ ‫ك َف َر فَإ ِّ َّن اّلل َغ‬
َ ً َ ْ َ َ َ َ ْ َ ْ َ ْ ُّ
َ ‫يال َو‬ ََ
﴾‫ني‬ ِّ ِّ ِّ ‫ن‬ ‫م‬ ِّ ‫ب‬‫س‬ ِّ ‫ه‬‫ِل‬ِّ ‫إ‬ ‫اع‬‫ط‬‫ت‬ ‫اس‬ ‫ن‬
ِّ ‫م‬ ‫ت‬
ِّ ‫ي‬ ‫اْل‬ ‫ِّج‬
‫ح‬ ِّ
‫اس‬ َّ‫لَع اَّل‬ ِّ ‫﴿ َو ِّّلل‬

“ለአላህም በሰዎች ላይ ወደርሱ መሄድን በቻለ ሁሉ ላይ ቤቱን መጎብኘት ግዴታ አለባቸው፡፡ የካደም
ሰው አላህ ከዓለማት ሁሉ የተብቃቃ ነው፡፡” (አል’ዒምራን፡ 97)

በዚህ ሁሉ ያረጋገጠ ፣ ሞቶ መቀስቀስን ያስተባበለ ከሀዲ እንደሚሆን ፣ ደሙም ገንዘቡም


የተፈቀደ እንደሆነ የዑለሞች ስምምነት ነው፡፡
አላህ እንደተናገረው፡
ْ ُْ َ ْ ُْ َ ُ ُ
‫ني اّلل ِّ َو ُر ُسلِّهِّ َويقولون نؤم ُِّن ب ِّ َبع ٍض َونكف ُر ب ِّ َبع ٍض‬ َ ْ َ‫ون أَن ُي َفرقُوا ْ ب‬
َ ُ َُ ُُ َ َ ُ ُ ْ َ َ َّ َّ
ِّ ‫يد‬ ‫ر‬
ِّ ‫ي‬ ‫و‬ ِّ ‫ه‬ِّ ‫ل‬ ‫س‬‫ر‬ ‫و‬ ِّ ‫اّلل‬ِّ ‫﴿إِّن اَّلِّين يكفر‬
‫ب‬ ‫ون‬
ً ‫ين َع َذابًا ُّمه‬
﴾‫ينا‬ َ ‫ون َح ًّقا َوأ َ ْع َت ْدنَا ل ِّلْ ََكف ِّر‬
َ ُ َ ْ ُ ُ َ َ ْ ُ ً َ َ َ َ ْ َ ْ ُ َّ َ َ َ ُ ُ َ
‫خذوا بني ذل ِّك سبِّيال۞أولـئِّك هم الَكف ِّر‬ ِّ ‫وي ِّريدون أن يت‬
ِّ ِّ
26/37
“እነዚያ በአላህና በመልእክተኞቹ የሚክዱ ፣ በአላህና በመልክተኞቹም መካከል መለየትን የሚፈልጉ ፣
“በከፊሉም እናምናለን በከፊሉም እንክዳለን” የሚሉ ፤ በዚህም መካከል መንገድን ሊይዙ የሚፈልጉ ፤
እነዚያ በውነት ከሐዲዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡ ለከሀዲዎችም አዋራጅን ቅጣት አዘጋጅተናል፡፡” (አን’ኒሳእ፡
150-151)

በከፊሉ ያመነ ፣ በከፊሉ የካደ በእውነት ከሀዲ መሆኑን አላህ በመጽሐፉ ግልጽ ካደረገ ፣ ይህ
ብዥታ ተወገደ፡፡ ይህን ነው አንዳንድ የ “አህሳእ” ሰዎች ወደኛ በላኩት ደብዳቤ ያወሱት፡፡

አሁንም ይባላል፡ ረሡልን ‫ ﷺ‬በአንድ ነገር እውነት ብሎ የሶላትን ግዴታነት ካስተባበለ እርሱ
ከሀዲ ፣ ደሙም ፣ ገንዘቡም የተፈቀደ መሆኑ የዑለሞች ስምምነት መሆኑን የምታረጋግጥ ከሆነ
፣ እንደዚሁ በሁሉም ነገር አረጋግጦ ሞቶ መቀስቀስን ያስተባበለ ፣ ልክ እንደዚሁ የረመዷንን
ጾም ግዴታነት ያስተባበለ ፣ በዚህ ሁሉ እውነት ያለ ፣ በዚህ ዙሪያ (ከሐዲ እንደሚሆን)
መዝሀቦች አይለያዩም - ከዚህ በፊት እንዳስቀደምነው - ቁርኣኑም በዚህ ተናግሯል፡፡

ተውሂድ ነብዩ ‫ ﷺ‬በእርሷ ከመጡበት ሁሉ ትልቁ መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ እርሱም ከሶላት ፣
ከዘካ ፣ ከጾም እና ከሐጅ የበለጠ ነው፡፡ ረሡል ‫ﷺ‬በመጡበት ሁሉ ቢተገብር አንድ ሰው
ከእነዚህ ነገሮች አንዱን ያስተባበለ ከሀዲ ከሆነ ፣ የመልእክተኞች ሁሉ እምነት የሆነውን
ተውሒድ ያስተባበለ እንዴት ከሀዲ አይሆን?! አላህ ጥራት ይገባው!! ይህንን ድንቁርና ምን
አስደናቂ አደረገው!!

እንደዚሁ በተጨማሪ ይባላል፡ እነዚያ የአላህ መልእክተኛ ‫ ﷺ‬ባልደረቦች በኒ ሀኒፋዎችን


ተጋድለዋል ፣ ከነብዩ ‫ﷺ‬ጋር ኢስላምን የተቀበሉ ናቸው፡፡ “ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ
የለም ፤ ሙሀመድ የአላህ አገልጋይና መልእክተኛ ነው” ብለው ይመሰክራሉ ፣ አዛን ያደርጋሉ
ይሰግዳሉ፡፡
እርሱ ቢናገር፡ እነርሱ ሙሰይሊማ ነብይ መሆኑን ይመሰክራሉ

እኛ እንናገራለን፡ ይህ ተፈላጊ ነው፡፡ አንድን ግለሰብ ወደነብይነት ደረጃ ከፍ ያደረገ ከሀዲ ከሆነ ፣
27/37

ሁለቱ የምስክርነት ቃሎች ካልጠቀሙት ፤ ሶላትም እንዲሁ ፣ “ሸምሳንን” ፣ ወይም “ዩሱፍ”


ወይም “ሶሃባን” ወይም “ነብይን” በሰማያት እና በምድር ጌታ ደረጃ ከፍ ያደረገ እንዴት ሊሆን
ነው? ጥራት ይገባው! ሁኔታውን ምን ትልቅ አደረገው!
َ َ َ َ َّ ُ ُ َ َ ُ َّ ُ َ ْ َ َ َ َ
﴾‫ِّين َل َي ْعل ُمون‬ ِّ ‫﴿كذل ِّك يطبع اّلل لَع قل‬
‫وب اَّل‬

“እንደዚሁ አላህ በእነዚያ በማያውቁት ሰዎች ልቦች ላይ ያትማል” (አር’ሩም፡ 59)

እንደዚሁ ይባላል፡- ዓልይ ብን አቢጧሊብ ያቃጠላቸው ሁሉም ኢስላምን ይሞግታሉ፡፡ እነርሱ


ለዓልይ ባልደረቦች ናቸው፡፡ እውቀትን የወሰዱት ከሶሃቦች ነው፡፡ ነገር ግን ልክ በ “ዩሱፍ” ፣ በ
“ሸምሳን” እና በመሰሎች እንዳመኑት በአልይም አመኑ፡፡ እነርሱ በመገደላቸው ፣ ከሀዲ
በመሆናቸው ሶሃቦች እንዴት ተስማሙ? ሶሃቦች ሙስሊምን በከሐዲነት የሚፈርጁ ናቸው ብለህ
ትገምታለህ? ወይስ በ “ታጅ” እና በመሰሎቹ ማመን የማይጎዳ ፣ በዓልይ ብን አቢጧሊብ ማመን
የሚያከፍር ነው ብለህ ትገምታለህ?

አሁንም ይባላል፡ በኑ ዑበይድ አልቀዳህ -በበኒ አልአባስ ዘመን ሞሮኮን እና ግብጽን


የተቆጣጠሩ- ሁሉም “ላኢላሃ ኢልለሏህ ሙሐመድ ረሡሉሏህ” ብለው ይመሰክራሉ፡፡
ኢስላምን ይሞግታሉ፡፡ ጁሙዓን ፣ ጀማዓን ይሰግዳሉ፡፡ በአንዳንድ -አሁን ካለንበት (ችግር)
በታች በሆነ- ሸሪዓን የሚቃረን ነገር ይፋ ባደረጉ ጊዜ ፣ እነርሱ ከሀዲ በመሆናቸው ፣
በመገደላቸው ዑለሞች ተስማሙ፡፡ አገራቸው የጦርነት አገር ሆነች፡፡ ከሙስሊም አገሮች
በእጃቸው የተቆጣጠሩትን ነጻ እስከሚያደርጉ ድረስ ሙስሊሞች ዘመቱባቸው፡፡

አሁንም ይባላል፡ የመጀመሪያዎች ከሀዲ አልሆኑም ፣ ሽርክ (በመፈጸማቸው) ፣ ሩሡሎችን


በማስተባበላቸው ፣ ቁርኣንን ፣ ሙቶ መቀስቀስን እና ሌሎችንም መቃወምን በመሰብሰባቸው
እንጅ፡፡ በሁሉም መዝሐብ ዑለሞች “ባቡ ሁክሚል ሙርተድ” በማለት የከፈቱት ምዕራፍ
ትርጉሙ ምንድን ነው? እርሱ ከእስልምናው በኋላ ከሀዲ የሚሆን ሙስሊም ነው፡፡
28/37

ከዚያም በርካታ አይነቶችን አወሱ፡፡ ከእርሷ እያንዳንዷ አይነት የሚያከፍር ፤ የግለሰቡን ገንዘብ
እና ደሙን የተፈቀደ የሚያደርግ፡፡ ከሚሰራት ሰው ዘንድ ቀላል የሆኑ ነገሮችን ሳይቀር
አውስተዋል፡፡ ለምሳሌ ከልቡ ሳይሆን በምላሱ የሚናገራት ቃል ወይም በጨዋታ እና በቀልድ
መልኩ የሚያወሳት ቃል?!
በተጨማሪ ይባላል፡ ስለነርሱ አላህ የተናገረላቸው
ْ َ ْ َ ْ َ ْ ُ َ ََ ْ ُ ْ َ َ َ ْ ُ َ ْ َََ ْ ُ َ َ َ ُ َْ
﴾‫﴿َيلِّفون بِّاّللِّ ما قالوا ولقد قالوا َكِّمة الكف ِّر وكفروا بعد إِّسال ِّم ِّهم‬

“ምንም ያላሉ ለመሆናቸው ይምላሉ፡፡ የክህደትንም ቃል በእርግጥ አሉ፡፡ ከእስልምናቸውም በኋላ


ካዱ፡፡” (አት’ተውባ፡ 74)

በነብዩ ‫ ﷺ‬ዘመን ከእርሳቸው ጋር የሚታገሉ፣ ከእርሳቸው ጋር የሚሰግዱ ፣ ዘካ የሚያወጡ ፣


ሀጅ የሚያደርጉ ፣ አላህን (በአምልኮ) ብቸኛ ያደረጉ ከመሆናቸው ጋር ፣ በአንድ ቃለ
ምክንያት አላህ በከሀዲነት የፈረጃቸው መኖራቸውን አልሰማህምን?
እንደዚሁ አላህ ስለነርሱ የተናገረላቸው፡
ْ ُ َ َ ْ َ ُ ْ َ َ ْ َ ْ ُ َ ْ َ ‫َل‬َ َ ُ َْ َْ ُْ ُ ُ َ َ َ َ َ ُْ
﴾‫وَلِّ كنتم تسته ِّزئون۞ تعت ِّذروا قد كفرتم بعد إِّيمان ِّكم‬
ِّ ‫﴿قل أبِّاّللِّ وآياتِّهِّ ورس‬

“በእርግጥ ብትጠይቃቸው “እኛ የምንዘባርቅና የምንጫወት ብቻ ነበርን” ይላሉ፡፡ “በአላህና በአንቀጾቹ


፣ በመልእክተኛውም ታላግጡ ነበራችሁን?” በላቸው፡፡ አታመካኙ ፤ ከእምነታችሁ በኋላ በእርግጥ
ካዳችሁ፡፡ ከእናንተ አንዷን ጭፍራ ብንምር (ሌላዋን) ጭፍራ እነሱ ሐጢአተኞች በመሆናቸው
እንቀጣለን፡፡” (አት’ተውባ፡ 65-66)

እነዚያ እነርሱ በቀልድ መልክ ቃልን በመናገራቸው ካመኑ በኋላ የካዱ መሆናቸውን አላህ ግልጽ
ያደረገባቸው -በተቡክ ዘመቻ ከረሡል ‫ ﷺ‬ጋር የዘመቱ ነበሩ-

ይህን ማመሳሰያ አስተውል! እርሷም “ላኢላሃ ኢልለሏህ ብለው የሚሰግዱ ፣ የሚጾሙ


ሙስሊሞችን ታከፍራላችሁ?” የሚለው ቃላቸው ነው፡፡ ከዚያም መልሷን አስተውል፡፡ እንሆ
እርሱ በእነዚህ ወረቀቶች (በዚህች መጽሐፍ) ውስጥ ከሚገኙት ነገሮች በጣም ጠቃሚው ነው፡፡
29/37
በዚህ ላይ -ተጨማሪ- ማስረጃው ስለበኒ ኢስራኢሎች አላህ የተናገረው ነው፡፡ ሙስሊም
ከመሆናቸው ፣ ከእውቀታቸው ፣ ደጋግ የአላህ ባሪያ ከመሆናቸው ጋር ለሙሳ የሚከተለውን
አሉት፡
ٌ َ ْ ُ َ َ َ ً َ َ َّ َ ْ
﴾‫﴿اجعل َّلا إِّلـها كما لهم آل ِّهة‬

“ሙሳ ሆይ! ለእነርሱ (ለሰዎቹ) አማልክት እንዳሏቸው ለእኛም አምላክን አድርግልን” (አል’አዕራፍ፡
138)

ከሶሃቦች የተወሰኑ ሰዎች “የአላህ መልእክተኘ ሆይ! የማንጠልጠያ ባለቤት አድርግልን”


የሚለው ንግግር ነው፡፡ የአላህ መልእክተኛ “ይህ “ለእኛም አምላክ አድርግልን” እንደሚለው የበኒ
ኢስራኢሎች አይነት ንግግር ነው፡፡” በማለት ምለው ተናገሩ፡፡ (አህመድ፡ 21897, ቲርሚዚይ፡ 2180)

ክፍል አስራ ሶስት


በማህይምነት ምክንያት ከሽርክ አይነቶች ወድቆ ከእርሱ የቶበተ ሙስሊም ብይን

ነገር ግን ለአጋሪዎች በዚህ ታሪክ የሚያቀርቡት ማመሳሰያ አላቸው፡፡ እርሷም፡ “በኒ ኢስራኢሎች
በዚህ ከሀዲ አልሆኑም” ይላሉ፡፡

“እንደዚሁ ለእነርሱ የማንጠልጠያ ባለቤት እንዲኖራቸው ነብዩን የጠየቁት አልካዱም” ይላሉ፡፡

መልሱ፡ (የሚከተለውን) ማለትህ ነው፡ በኒኢስራኢሎች አልሰሩትም፡፡ ልክ እንደዚሁ ነብዩንም


‫ ﷺ‬የጠየቁት አልሰሩትም፡፡ በኒ ኢስራኢሎች ቢሰሩት ኖሮ እንደሚክዱ ምንም ልዩነት የለም፡፡
እንደዚሁ ነብዩ ‫ ﷺ‬የከለከሏቸው ሰዎች ባይታዘዟቸውና ከከለከሏቸው በኋላ የማንጠልጠያ
ባለቤትን ቢይዙ ኖሩ በመክፈራቸው ልዩነት አይኖርም፡፡ ይህ እርሱ ተፈላጊ ነው፡፡

ነገር ግን ይህ ታሪክ፡ አንድ ሙስሊም -ይልቁንም ዓሊም- ከእርሷ ሳያውቅ ከሽርክ አይነቶች
አንዳንዴ ሊወድቅ እንደሚችል ያስጠቅመናል፡፡
ትምህርትን ፣ ጥንቃቄን (ያስጠቅመናል) እንዲሁም “ተውሂድን ተገንዝበናል” የሚለው የጃሂል
30/37
ንግግር ትልቁ ጅህልና ፣ የሰይጣን ሴራ መሆኑን ማወቃችንን ያስጠቅመናል፡፡

በተጨማሪ- (ሐቅን ለማወቅ) የሚታገል ሙስሊም የክህደት ንግግር በተናገረ ጊዜ -እርሱ


ሳያውቅ- በዚህ ላይ እንዲነቃ ከተደረገ ፤ በዚያው ሰዓት ከቶበተ ፣ እንሆ እርሱ የማይከፍር
መሆኑን ያስጠቅመናል- በኒ ኢስራኢሎች እና የአላህን መልእክተኛ የጠየቁት ሰዎች (ሶሃቦች)
እንደሰሩት፡፡

በተጨማሪ ያስጠቅመናል፡ እርሱ ባይከፍር እንኳ የአላህ መልእክተኛ ‫ ﷺ‬እንደሰሩት ብርቱ እና


ከበድ ያለ ንግግር ይነገረዋል፡፡
ክፍል አስራ አራት
የሚያፈርሳትን ቢፈጽም እንኳ “ላኢላሃ ኢልለሏሀ” የምትለው ቃል ለተውሂድ በቂ ነች ለሚሉ
ሰዎች ምላሽ

ሌላም ማመሳሰያ አላቸው፡፡ “ላኢላሃ ኢለላህ” የሚለውን ቃል የተናገረውን ሰው ኡሳማ


በመግደሉ ረሡል ‫ ﷺ‬አውግዘውታል፡፡ “ላኢላሃ ኢልለሏህ” ካለ በኋላ ትገድለዋለህ? ብለውታል
ይላሉ፡፡ ልክ እንደዚሁ፡ “ላኢላሃ ኢልለሏህ” የሚለውን ቃል እስከሚሉ ሰዎችን ልጋደል
ታዝዣለሁ” የሚለው ንግግራቸው ነው፡፡

እንደዚሁ እርሷን ከተናገረ ሰው ላይ (እርምጃ ከመውሰድ) መቆጠብ እንደሚገባ የሚናገሩ


ሌሎች ሐዲሶች ናቸው፡፡

የእነዚህ ጃሂሎች ፍላጎት፡ “እርሷን የተናገረ አይከፍርም ፣ -የሰራውን ቢሰራ- አይገደልም”


የሚል ነው፡፡

ለእነዚህ ጃሂል ሙሽሪኮች ይባላሉ፡ “ላኢላሃ ኢለሏህ” እያሉ ረሡል ‫ ﷺ‬አይሁዶችን


እንደተጋደሉና እንደማረኳቸው ይታወቃል፡፡
የአላህ መልእክተኛ ‫ ﷺ‬ባልደረቦች በኒ ሀኒፋዎች “ላኢላሃ ኢልለሏህ ሙሀመድ ረሱሉሏህ”
31/37
እያሉ ፣ ሶላት እየሰገዱ ፣ ኢስላምን እየሞገቱ ተጋድለዋቸዋል፡፡

ልክ እንደዚሁ አልይ ብን አቢጧሊብ በእሳት አቃጥሏቸዋል፡፡

እነዚህ ጃሂሎች ሞቶ መቀስቀስን የተቃወመ “ላኢላሃ ኢልለሏህ” ቢልም እንደሚገደልና ከሀዲ


እንደሚሆን ያረጋግጣሉ፡፡ ከቅርንጫፎች የተወሰነ በማስተባበሉ ካልጠቀመችው ፣ የሩሡሎች ዲን
መሰረት እና ቅንጭላቱ የሆነውን ተውሂድን አስተባብሎ እንዴት ይጠቅመዋል?

ነገር ግን የዲን ጠላቶች የሀዲሶችን ትርጉም አልተገነዘቡም፡፡

የኦሳማ ሐዲስን በተመለከተ፡ ደሙን እና ገንዘቡን ፈርቶ እንጅ ኢስላምን አልሞገተም በሚል
ጥርጣሬ አንድን ግለሰብ ኢስላምን እየሞገተ ገደለው፡፡ አንድ ግለሰብ ኢስላምን ይፋ ካደረገ
ከእርሱ መቆጠብ ግድ ነው -ያንን የሚቃረን ነገር ግልጽ እስከሚሆን ድረስ፡፡ በዚህ ዙሪያ አላህ
ቁርኣን አወረደ፡
ْ ُ َّ َ َ َ َ ْ ُ ْ َ َ َ ْ ُ َ َ َّ َ ُّ َ َ
﴾‫يل اّللِّ فتبينوا‬
ِّ ِّ ‫﴿يا أيها اَّلِّين آمنوا إِّذا َضبتم ِِّف سب‬
“እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በአላህ መንገድ (ለመጋደል) በተጓዛችሁ ጊዜ አስረግጡ፡፡” (አን’ኒሳእ፡ 94)

“አረጋግጡ” ማለት ነው ፡ አንቀጹ የሚጠቁመው ከእርሱ መቆጠቡ እና ማረጋገጡ ግድ


እንደሆነ ነው፡፡ ከዚያ በኋላ ኢስላምን የሚቃረን ነገር ከእርሱ ላይ ግልጽ ከሆነ ይገደላል-
“አስረግጡ” በማለቱ፡፡ እርሷን የተናገረ ጊዜ ፣ የማይገደል ቢሆን ኖሮ “አስረግጡ” ያለው
ትርጉም ፋይዳ አይኖረውም ነበር፡፡

ልክ እንደዚሁ ሌሎችም ሐዲሶችና መሰሎቻቸው ትርጉሙ ያወሳሁት ነው፡፡ ኢስላምን እንዲሁም


ተውሂድን ይፋ ያደረገ ከእርሱ መቆጠብ ግድ ነው - ያንን የሚቃረን ነገር ግልጽ ካልሆነ በቀር፡፡

ለዚህ ማስረጃው የአላህ መልእክተኛ ‫ﷺ‬፡ “ላኢላሃ ኢልለሏህ” ካለ በኋላ ገደልከውን?” ፤


“ሰዎችን ልጋደል ታዝዣለሁ ላኢላሃ ኢልለሏህ እስከሚሉ” በማለት የተናገሩት ነው፡፡ በአምልኮ
፣ ላኢላሃ ኢልለሏህ የሚለውን ቃል በብዛት ተግባራዊ ከማድረጋቸው ጋር (የአላህ መልእክተኛ)
32/37
ስለኸዋሪጆች የሚከተለውን ተናግረዋል፡ “ባገኛችኋቸው ቦታ ሁሉ ግደሏቸው ፤ ባገኛቸው የአድ
ህዝቦች አገዳደል እገድላቸው ነበር” ፣ ሶሃቦች ከእነርሱ ዘንድ ሶላታቸውን ይንቁ ነበር፡፡ እነርሱ
ደግሞ ከሶሃቦች ነው የተማሩት፡፡ የሸሪዓ ተቃርኖ በእነርሱ ላይ ይፋ በሆነ ጊዜ “ላኢላሃ
ኢልለሏህ” ፣ እንዲሁም የአምልኮት ብዛቱ ፣ ሙስሊም ነን ብለው መሞገታቸው
አልጠቀማቸውም፡፡ አይሁዶችን መጋደሉ ፣ ሶሀቦች በኒ ሀኒፋዎችን መጋደላቸው ልክ እንደዚሁ
ነው፡፡
አንድ ግለሰብ ዘካ ከለከሉ ብሎ ለነብዩ ‫ ﷺ‬የተናገረ ጊዜ ነብዩ ወደበኒ ሙስጦለቆች ለመዝመት
ማሰባቸውም እንደዚሁ ነው፡፡ አላህ የሚከተለውን የቁርኣን አንቀጽ እስከሚያወርድ፡
َ َ ُ ْ ُ َ َ َ َ ً ْ َ ُ ُ َ ُ َّ َ َ َ َ َ ٌ َ ْ ُ
ْ‫لَع َما َف َعلْ ُتم‬ َ ُ َ َ َّ َ ُّ َ َ
‫﴿يا أيها اَّلِّين آمنوا إِّن جاءكم فا ِّسق بِّنبأ ٍ فتبينوا أن ت ِّصيبوا قوما ِِّبهال ٍة فتصبِّحوا‬
َ ‫نَادِّم‬
﴾‫ِّني‬

“እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ነገረኛ ወሬን ቢያመጣላችሁ በስህተት ላይ ሆናችሁ ህዝቦችን እንዳትጎዱና
በሰራችሁት ነገር ላይ ተጸጻቾች እንዳትሆኑ አረጋግጡ፡፡” (አል’ሑጁራት፡ 6)

ግለሰቡ በእነርሱ ላይ ዋሽቶባቸው ነበር፡፡

ይህ ሁሉ የሚጠቁመው ፣ እነርሱ በእርሷ ማስረጃ የሚያደርጉባት የረሱል ሀዲሶች ሁሉ የነብዩ


ፍላጎት ከዚህ በፊት ያወሳነው መሆኑ ነው፡፡

ክፍል አስራ አምስት


በአካል በተገኘ ህያው ሰው በእርሱ ላይ በሚችለው ነገር እገዛ መፈለግን እና በሌላ እገዛ መፈለግ
ያለው ልዩነት

ሌላም ማመሳሰያ አላቸው፡ እርሷም ነብዩ ‫ ﷺ‬ያወሱት ሰዎች የቂያማ ቀን በአደም ፣ ከዚያም
በኑህ ፣ከዚያም በሙሳ፣ከዚያም በኢሳ እርዳታ እንደሚፈልጉ ከዚያም ወደአላህ መልእክተኛ ‫ﷺ‬
እስከሚደርሱ ድረስ ሁሉም ምክንያት እንደሚያቀርቡ ነብዩ ‫ ﷺ‬የተናገሩት ሐዲስ ነው፡፡
33/37
እነርሱ አሉ ፡ ይህ የሚጠቁመው ከአላህ ውጭ እርዳታ መፈለግ ሽርክ ላለመሆኑ ነው፡፡

መልሱ የሚከተለውን ማለትህ ነው፡ በጠላቶቹ ልቦና ላይ ያተመ (ጌታ) ጥራት ይገባው! በእርሱ
ላይ በሚችለው በፍጡር እርዳታ መፈለግ አንቃወማትም፡፡ በሙሳ ታሪክ አላህ እንደተናገረው፡
ُ َ ْ َّ َ َ َ َّ ُ َ َ َ ْ َ
﴾ِّ ‫﴿فاستغاثه اَّلِّي مِّن ِّشيعتِّهِّ لَع اَّلِّي مِّن عدوِّه‬
“ያም ከወገኑ የሆነው ሰው በዚያ ከጠላቱ ከሆነው ሰው ላይ እርዳታን ጠየቀው፡፡” (አል’ቀሶስ፡ 15)

ፍጡር በእርሱ ላይ በሚችላቸው ነገሮች አንድ ሰው በጦርነትም ይሁን በሌላ እርዳታ


እንደሚፈልገው፡፡ እኛ የተቃወምነው ከወልዮች ቀብሮች ፣ ወይም በእርሷ ላይ አላህ እንጅ ማንም
በማይችለው አንዳንድ ነገር በሩቅ ያሉትን አካላት የአምልኮ የሆነውን እርዳታ መጠየቅን ነው፡፡

ይህ ከተረጋገጠ፡ የቂያማ ቀን በነብያቶች ኢስቲጋሳ ማድረግ ከእነርሱ የፈለጉት ሰዎችን ሂሳብ


እንዲያደርግ ፣ የጀነት ሰው ከመውቂፉ ጭንቀት እረፍት ያገኙ ዘንድ አላህን እንዲማጸኑላቸው
ነው፡፡ ይህ በዱንያም በአኼራም የተፈቀደ ነው፡፡ ወደአንድ ግለሰብ ሄደህ ንግግርህን እንዲሰማ
ዘንድ ከእርሱ ጋር ትቀመጣለህ ፣ ከዚያም ለእርሱ የሚከተለውን ትለዋለህ፡ “ለእኔ ዱዓ
አድርግልኝ” ፣ ልክ የረሡል ‫ ﷺ‬ሶሃቦች በህይዎት እያሉ እንደሚጠይቁት፡፡

ከሞቱ በኋላማ እነርሱ ከቀብራቸው ዘንድ ይህንን ጠየቁ ማለት የጠሩ ናቸው ፣ ተከልከል
(እነርሱ ጠይቀዋል ከማለት)፡፡ ከእርሱ ቀብር ዘንድ አላህን ለመማጸን ማሰብን ሰለፎች
አውግዘዋል፡፡ እናቴም አባቴም ለእርሳቸው መስዋእት ይሁኑና እንዴት ነፍሳቸውን (ራሳቸውን)
ይማጸናሉ፡፡

ሌላም ማመሳሰያ አላቸው፡ እርሷም የኢብራሂም ታሪክ ነች፡፡ እሳት በተጣለ ጊዜ በአየር ላይ
ጅብሪል ለእርሱ አቀረበለት፡ አለውም፡ ሀጃ አለህን?

ኢብራሂምም፡ ወደአንተ ከሆነ የለኝም፡፡ እነርሱም የሚከተለውን አሉ ፡ በጅብሪል እርዳታን


መጠየቅ ሽርክ ቢሆን ኖሮ ወደኢብራሂም ባላቀረባት ነበር፡፡
34/37
መልሱ፡ ይህ የመጀመሪያው አይነት ማመሳሰያ አይነት ነው፡፡ ጅብሪል እርሱ በሚችለው
ለመጥቀም በእርሱ ላይ አቀረበ፡፡ እንሆ እርሱን አስመልክቶ አላህ እንደተናገረው፡-
ُْ ُ َ
﴾‫يد الق َوى‬ ‫﴿ش ِّد‬

“(ሀይሎቹ ብርቱው (መላኢካ)” (አን’ነጅም፡ 5)

የኢብራሂምን እሳት እና በዙሪያው ያለውን ምድር ፣ ተራራ እንዲይዝ እና ወደምስራቅና


ወደምዕራብ እንዲጥለው አላህ ቢያዘው ይሰራዋል፡፡ ኢብራሂምን ሩቅ ቦታ እንዲያኖረው አላህ
ቢያዘው ይሰራው ነበር፡፡ ወደሰማይ ከፍ እንዲያደርገው ቢያዘው ይሰራው ነበር፡፡

ይህ ልክ እንደ አንድ ሀብታም ሰው ማለት ነው -ብዙ ገንዘብ እንዳለው፡፡ አንድ ፈላጊ (ችግረኛ)
የሆነን አካል እንደሚመለከትና ሊያበድረው ፣ ወይም ሀጃውን ለመፈጸም በስጦታ መልክ
ሊሰጠው ሀሳብ እንዳቀረበ ሀብታም ምሳሌ ነው፡፡ ይህ ፈላጊ (ችግረኛ) ከእርሱ ከመቀበል እምቢ
እንደለና አላህ ሲሳይ እስከሚያመጣለት አንድም ሰው በእርሱ እንዳይመጻደቅበት መታገስን
እንደፈለገ ሰው ምሳሌ ነው፡፡ ከአምልኮ እና ከሽርክ እስቲጋሳ ጋር ይህ የት ነው ያለው? ቢገነዘቡ
ኖሮ!

ክፍል አስራ ስድስት


ተውሂድን በልብ ፣ በምላስ እና በአካል ተግባራዊ ማድረግ ግዴታ ነው፡፡ ሸሪዓዊ ለሆነ ምክንያት
ካልሆነ በቀር

ያሳለፍነውን እንድንገነዘብ የሚያደርግ ታላቅና አንገብጋቢ የሆነን አንቀጽ በማውሳት ይህን ኪታብ
እናጠናቅ፡፡ ነገር ግን ሁኔታዋ ትልቅ ፣ በእርሷ ዙሪያ ስህተቶችም ስለሚበዙ ንግግርን ለብቻ
እናድርግላት፡፡

የሚከተለውን እንናገራለን፡ ተውሂድ የግድ በልብ ፣ በአንደበት እና በተግባር መሆኑ ምንም ዓይነት
ልዩነት የለም፡፡ ከዚህ መካከል አንዱ ከጎደለ ግለሰቡ ሙስሊም ሊሆን አይችልም፡፡
35/37
ተውሂድን ቢያውቅና በእርሱ ባይሰራ እርሱ ከሀዲና አመጸኛ ነው -ልክ እንደፊርአውን ፣
ኢብሊስ እና እንደመሰሎቻቸው፡፡

ይህን ጉዳይ በርካታው ሰው ይሳሳትበታል፡፡ የሚከተለውን ይላሉ፡ “ይህ ሐቅ ነው ፣ ይህን


እንገነዘበዋለን ፣ ሐቅ መሆኑንም እንመሰክራለን ፣ ነገር ግን ልንሰራው አንችልም ፣ ከአገራችን
ሰዎች ዘንድ እነርሱን የተስማማ ካልሆነ በቀር አይፈቀድም” ከዚህም ውጭ ምክንያቶችን
(ይደረድራሉ)

ይህ ምስኪን አላወቀም፡ አብዛኞች የክህደት መሪዎች ሀቅን ያውቃሉ ፤ ለሆነ ምክንያት እንጅ
አልተውትም፡፡

አላህ እንደተናገረው፡
َ ْ ََ ْ
﴾‫ات اّللِّ ث َم ًنا‬
ِّ َ‫َت ْوا بِّآي‬ ‫﴿اش‬

“በአላህ አንቀጾች ጥቂትን ዋጋ ገዙ፡፡” (አት’ተውባ፡ 9)

ከዚህም ውጭ ሌሎች አንቀጾች አሉ፡


የሚከተለው የአላህ ቃል ይመስል፡
ْ ُ َ ْ َ َ ُ ْ َ َ َ ُ َ ُ ْ َ َ َ ْ ُ ُ َ ْ َ َ َّ
﴾‫﴿اَّلِّين آتيناهم الكِّتاب يع ِّرفونه كما يع ِّرفون أبناءهم‬

“እነዚያ መጽሐፍን የሰጠናቸው ወንዶች ልጆቻቸውን እንደሚያውቁ (ሙሐመድን) ያውቁታል፡፡”


(አል’በቀራህ፡ 146)

በግልጽ በተውሂድ ስራ ቢሰራ -እርሱ አይገነዘበውም ፣ በልቡም አያምንበትም -እርሱ ሙናፊቅ


ነው ፤ እርሱ ጥርት ካለው ከሀዲ የከፋ ነው፡፡
አላህ እንደተናገረው፡
َ َْ َ
َّ ‫ني ِف‬ َ ُ ْ َّ
﴾ِّ‫اَل ْركِّ األسف ِّل مِّن اَّلار‬
َّ َ
ِّ ِّ‫﴿إِّن المنافِّق‬
“መናፍቃን በእርግጥ ከእሳት በታችኛው አዘቅት ውስጥ ናቸው፡፡” (አን’ኒሳእ፡ 145)
36/37
ይህ ጉዳይ ረጅም ነው፡፡ በሰዎች አንደበት ካስተዋልካት ለአንተ ግልጽ ታደርግልሀለች፡፡ ሀቅን
የሚያውቅ ፣ ዱንያው ፣ ስልጣኑ እና ንግስናው ይቀንስብኛል ብሎ በመፍራት በእርሱ መስራትን
የሚተው ትመለከታለህ፡፡
በስውር ሳይሆን በግልጽ ስራ የሚሰራን ትመለከታለህ፡፡ በልቡ የሚያምንበትን ነገር ከጠየከው
እርሱ ያንጊዜ አያውቀውም፡፡

ነገር ግን ከአላህ መጽሐፍ ሁለት አንቀጾችን መገንዘብ ይኖርብሀል፡

የመጀመሪያው ፡ ከዚህ በፊት ያሳለፍነው ነው፡፡ እርሱም የሚከተለው ንግግሩ ነው፡


ُ َ ََْ ُْ َ َ َْ ْ ُ ََْ َ
﴾‫يمان ِّك ْم‬ِّ ‫﴿َل تعت ِّذروا قد كفرتم بعد إ‬
“አታመካኙ ካመናችሁ በኋላ ካዳችሁ” (አት’ተውባህ፡ 66)

ከአላህ መልእክተኛ ‫ ﷺ‬ጋር ወደሮማ የዘመቱ አንዳንድ ሶሃቦች በቀልድ መልክ የተናገሯት
በሆነች አንዲት ቃል ምክንያት መካዳቸውን ካረጋገጥክ ፤ ገንዘቡ ፣ ስልጣኑ ይጎድልብኛል ወይም
ከሆነ አካል ጋር ለመተዳደር ብሎ የክህደት ንግግር የተናገረ ወይም በእርሱ የሰራ በቀልድ መልክ
ከተናገረው የከበደ መሆኑ ለአንተ ግልጽ ይሆናልሃል፡፡

ሁለተኛው አንቀጽ፡ የአላህ ቃል ነው፡


ْ ُ ْ َ َ َ َّ ََ َ ٌّ َ ْ ُ ُ ُ ْ َ َ َ ْ ُ ْ َ َّ َ َْ َََ َ
‫كن من ُشح بِّالكف ِّر‬ ِّ ‫ان ولـ‬ ِّ ِّ ‫﴿من كفر بِّاّللِّ مِّن بع ِّد إيمانِّهِّ إَِّل من أك ِّره وقلبه مطمئِّن ب‬
ِّ ‫اإليم‬
َِّ ‫خرة‬ َ َ َ ْ ُّ ْ َ َ َ ْ ْ ُّ َ َ ْ ُ ُ َّ َ َ َ ٌ َ ٌ َ َ ْ ُ َ َ َ ٌ َ َ ْ َََْ ً ْ َ
ِّ ‫صدرا فعلي ِّهم غضب مِّن اّللِّ ولهم عذاب ع ِّظيم۞ذل ِّك بِّأنهم استحبوا اْلياة اَلنيا لَع اْل‬
َ َ ْ َْ َْ ْ َ َ َ َّ َ َ
﴾‫وأن اّلل َل يه ِّدي القوم الَكف ِِّّرين‬

“ከእምነቱ በኋላ በአላህ የካደ ሰው (ብርቱ ቅጣት አልለው)፡፡ ልቡ በእምነት የረጋ ሆኖ (በክህደት ቃል
በመናገር) የተገደደ ሰው ብቻ ሲቀር፡፡ ግን ልባቸውን በክህደት የከፈቱ ሰዎች በነሱ ላይ ከአላህ ቁጣ
አለባቸው፡፡ ለእነሱም ታላቅ ቅጣት አልላቸው፡፡ ይህ (ቅጣት) እነሱ ቅርቢቱን ህይወት ከመጨረሻይቱ
በመምረጣቸው ምክንያትና አላህም ከሀዲዎችን ህዝቦች የማያቀና በመሆኑ ነው፡፡” (አን’ነህል፡ 106-107)
37/37
ልቡ በእምነት የተረጋጋ ከመሆኑ ጋር የተገደደ ሰው ሲቀር አላህ ለእነዚህ ሰዎች ምንም
አይነት ምክንያት አላደረገም፡፡ ከዚህ ውጭ ከእምነቱ በኋላ ካደ፡፡ የተገደደ ሰው ሲቀር ፈርቶም
ይስራው ፣ ወይም ተስፋ አድርጎ ፣ ወይም ከሆነ አካል ጋር መተዳደር ብሎ ወይም አገሩን ወይም
ቤተሰቡን ወይም ዘመዶቹን ወይም ገንዘቡን ወዶ (ሳስቶ) ወይም በቀልድ መልክ ሰራው ወይም
ከዚህ ውጭ ላለ አላማ ሰራው እኩል ነው (አላህ ምንም ዓይነት ምክንያት አይሰጠውም)፡፡

አንቀጹ በዚህ ላይ የሚጠቁመው ሁለት አቅጣጫዎችን ነው፡

አንደኛው፡ “የተገደደ ሰው ሲቀር” የሚለው ንግግሩ ነው፡፡ የተገደደን ሰው እንጅ ነጥሎ


አላወጣም፡፡ የሰው ልጅ በተግባር እና በንግግር እንጅ ሊገደድ እንደማይችል የታወቀ ነው፡፡ የልብ
እምነት ከሆነ አንድም ሰው በእርሷ ላይ አይገደድም፡፡

ሁለተኛው፡ የሚከተለው ቃሉ ነው

“ይህ (ቅጣት) እነሱ ቅርቢቱን ህይወት ከመጨረሻይቱ በመምረጣቸው ምክንያትና አላህም ከሀዲዎችን
ህዝቦች የማያቀና በመሆኑ ነው፡፡” (አን’ነህል፡ 107)

ይህ ክህደት እና ቅጣት በእምነት ወይም በጀህል ወይም ዲንን በመጥላት ወይም ክህደትን
በመውደድ ምክንያት እንዳልነበረ ግልጽ አደረገ፡፡ ምክንያቱ ለእርሱ ከዱንያ ድርሻዎች የሆነ
ድርሻ እንደነበረውና እርሱንም ከዲን አብልጦ በመምረጡ ነው፡፡ ወሏሁ አዕለም

‫ وصلى هللا على محمد وآله وصحبه أجمعين‬،‫والحمد هلل رب العالمين‬

‫هــ‬1213 ‫تمت بعون هللا وتوفيقه سنة‬


ባህር ዳር በሚገኙ የአህለሱና መሻይኾች የተቀሩ ጠቃሚ ኪታቦች፣ ከሀገር
ውስጥና ከውጭ በሚመጡ መሻይኾች የተሰጡ ኮርሶች፣ ሙሓዶራዎች፣
የጁመዓ ኹጥባ፣ በትክክለኛ ማስረጃ የተደገፉ የተለያዩ ኢስላማዊ መጣጥፎችን
የሚከተለውን የቴሌግራም ሊንክ ጆይን በማድረግ መከታተል ይችላሉ
http://t.me/alateriqilhaq

You might also like