You are on page 1of 36

Powered By Advertising

የአዘጋጇ
መልዕክት
ሰላም!

ባሉበት ሰላምታዬ ይድስዎት!

እ.ኤ.አ በ2018 ዓ.ም የተደረገ አንድ ጥናት እንዳመለከተው አንድ ኢትዮጵያዊ ሰው በዓመት 6 ገፅ ብቻ ፅሁፍ ያነባል
ሲል አስደንጋጭ የሆነ መረጃን አስፍሯል፡፡ ይህ መረጃ የአብዛኞቻችንን የንባብ ባህል ጥያቄ ውስጥ የሚከት ነው፡፡ አንድ
ሰው መረጃዎችን እና እውቀቶችን ሊያኝ የሚችልበት ዋነኛው መንገድ ንባብ መሆን እንዳለበት ሁላችንም የሚያስማማ
ጉዳይ ነው፡፡ ማንበብ መረጃን ከማግኘት ባለፈ አመክንዮአዊ ብቃታችንን በማዳበር ረገድ የሚኖረው ጥቅም ሳይታለም
የተፈታ ነው፡፡ ታድያ በዓመት 6 ገፅ ያነበበ ሰው እውቀትን እና አመክንዮን ከየት ያገኝ ይሆን?

ውድ አንባቢ ሆይ እርስዎም በአካባቢዎት ያሉትን ሰዎች የንባብ ባህላቸውን ያዳብሩ ዘንድ በማበረታታት የበኩሎን
አስተዋፅኦ እንዲወጡ እንማፀናለን፡፡ ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል ሲባል ያለምክንያት አይደለም እና በጀንበር ንባብ
ሙሉ ሰው መሆን ባይቻል እንኳን ወደ ሙሉነት የምናደርገውን ጉዞ ዛሬ ‘ሀ’ ብለን እንጀምር እላለሁ፡፡

ከቀሪዎቹ መልካም74 ካነሳቻቸው ጉዳዮች ጋር መልካም ንባብን ተመኘሁ!

ቤተልሄም አምባቸው Cover Photo By: Samuel Adamu


ዋና አዘጋጅ

ዋና አዘጋጅ የመፅሄት ዲዛይን ፎቶግራፍ


ቤተልሄም አምባቸው በጭምዴሳ እምሩ በሳሙኤል አዳሙ
+251 911 921 477 +251 917 071 427 +251 946 637 372
betty.melkam74@gmail.com chimdesadebela@gmail.com samueladamu1986@gmail.com
Bethlehem Ambachew Chimdesa E Debela Shalom Sami

04 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
ሽክ እንዴት?

05 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
ሽክ እንዴት?

06 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
ሽክ እንዴት?

07 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
ስለ ጤና እናውራ

የማህፀን በር ጫፍ
ካንሰር
ቤተልሄም አምባቸው

ካንሰር በሰውነት ውስጥ ያሉ ህዋሳት ከቁጥጥር ውጪ የፓፕ ፣ የኤች.ፒ.ቪ. አልያም ሁለቱንም ምርመራዎች
በሆነ ሁኔታ በፍጥነት እንዲራቡ የሚያደርግ በሽታ ነው:: ሊያደርግ ይችላል፡፡
ምንም እንኳን ካንሰር ከቆይታ ወደ የተለያዩ የሰውነት የፓፕ ምርመራ በማህፀን በር ላይ የተከሰቱ የህዋስ
ክፍሎች የመዛመድ ባህሪ ቢኖረውም ስሙን የሚያገኘው ለውጦችን ወይንም ቅድመ ካንሰር ምልክቶችን ለመለየት
ግን በሽታው ከሚጀምርበት ቦታ ነው፡፡ ካንሰር በማህፀን የሚረዳ ሲሆን በዚህም ደግሞ በሽታው ከመከሰቱ በፊት
በር ጫፍ ላይ በሚጀምርበት ግዜም የማህፀን በር ጫፍ እርምጃዎችን ለመውሰድ ያግዛል፡፡ በሽታው ምናልባት
ካንሰር በመባል ይጠራል፡፡ የማህፀን በር ማለት የማህፀን ተከስቶ እንኳን ቢሆን ቀድሞ ለማወቅ የሚረዳ የምርመራ
ጠባቡ እና የታችኛው ክፍል ማለት ነው፡፡ አይነተ ነው፡፡

ይህ አይነት ካንሰር ካሉት ሌሎች የካንሰር አይነቶች ሁሉ በሌላ በኩል ደግሞ የኤች.ፒ.ቪ. ምርመራ ኤች.ፒ.ቪ.
በቀላሉ በቅድመ ምርመራ መለየት የሚቸል አይነት ቫይረስን ማለትም የማፀን በር ጫፍ ካንሰርን
ሲሆን በቅድመ ምርመራ ወቅት የሚታዩ ምልክቶችንም የሚያመጣውን ቫይረስ ለመለየት የሚረደ ምርመራ ነው፡፡
በመከተል ካንሰሩ እድገቱን ሳይጀምር በቀላሉ መቆጣጠር በማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ማን ሊጠቃ ይችላል?
ይቻላል፡፡ አንዲት በዚህ ካንሰር የመጠቃት ምልክት ያሳየች
ሴትም ብትሆን በሽታው ቀድሞ ከታወቀ በህክምና ሙሉ ምንም እንኳን በአብዛኛው እድሜያቸው ከ30 ዓመት በላይ
ለሙሉ የመዳን እድል ይኖራታል፡፡ ባሉ ሴቶች ላይ ችግሩ ጎልቶ ቢታይም የትኛዋም ሴት ግን
በዚህ ካንሰር ልትጠቃ ትችላለች፡፡ በአሁኑ ግዜ በአለማችን
የማህፀን በር ጫፍ ካንሰርን ቀድሞ በአመት ቁጥራቸው አምስት መቶ ሰባ ሺህ የሚደርስ ሴቶች
ለመለየት የሚያስችሉ ምርመራዎች በዚህ በሽታ ሲጠቁ በሀገራችን ደግሞ ቁጥራቸው በርከት
ይኖሩ ይሆን? ያሉ ሴቶች የዚህ በሽታ ሰለባ እየሆኑ ይገኛሉ፡፡
የማህፀን በር ጫፍ ካንሰርን ቀድሞ ለመከላከል አልያም ሂዩማን ፓፒሎማ ቫይረስ የዚህ ካንሰር ዋነኛ መንስኤ
በሽታው ገና የመጀመርያ ደረጃው ላይ እያለ ለመለየት ነው፡፡ ይህ ቫይረስ በግብረስጋ ግንኙነት ግዜ ከአንድ ሰው
የሚረዱ ሁለት አይነት ምርመራዎች አሉ፡፡ ወደ ሌላው ይተላለፋል፡፡ ሆኖም ግን የተወሰኑ ሴቶች ብቻ
እንደ ታካሚዋ እድሜ በማየት አንድ የህክምና ባለሙያ የካንሰሩ ተጠቂ ይሆናሉ፡፡

08 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
ስለ ጤና እናውራ

የበሽታው ምልክቶች ምንድን ናቸው? የጀመረች ሴት አልያም ከብዙ ሰዎች ጋር ግንኙነት


የምትፈፅም ሴት ከሌላው ሰው በበለጠ በዚህ ቫይረስ
የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር በመጀመርያዎቹ ደረጃዎቹ የመያዝ እድል ይኖራታል፡፡ አብዛኛው የኤች.ፒ.ቪ ቫይረስ
ላይ ምንም አይነት ምልክት ላያሳይ ይችላል፡፡ ነገር ግን አይነት በግዜ ሂደት ራሱ የሚጠፋ ነው፡፡ ሆኖም ግን ይህ
በሽታው እየበረታ ሲሄድ የደም መፍሰስ አልያም የተለያዩ ቫይረስ ሳይጠፋ በሰውነት ውስጥ የሚቆይ ከሆነ ግን ወደ
ከማህፀን የሚወጡ ፈሳሾች እንደ ምልክት ሊወሰዱ ካንሰርነት ሊቀየር ይችላል፡፡
ይችላሉ፡፡ አንዲት ሴት እንደዚህ አይነት ያልተለመዱ አይነት ከቫይረሱ በዘለለም እነዚህ ነገሮቸች ለማህፀን በር ጫፍ
ምልክቶችን በምታይ ግዜ በፍጥነት የሀኪም እርዳታን ካንሰር ያለን ተጋላጭነት ሊጨምሩ ይችላሉ፡-
መሻት እንደሚያስፈልጋት ይመከራል፡፡ • ሲጋራ ማጨስ
ምርመራውን መቼ ማድረግ ይቻላል? • የኤች.አይ.ቪ ቫይረስ ተጠቂ መሆን
የፓፕ የቅድመ ካንሰር ምርመራ አይነት በጣም ውጤታማ • ከአምስት አመታት በላይ የወሊድ መቆጣጠርያ
እና ታማኝ የምርመራ አይነት ነው፡፡ ይህም ምርመራ እንክብሎችን መውሰድ
እድሜያቸው ከ21- 29 ያሉ ሴቶች ይህንን ምርመራ • ከሶስት በላይ ልጆችን መውለድ
ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡ የመጀመርያው ምርመራ ምንም
አይነት የቅድመ ካንሰር ምልክት የማያሳይ ከሆነ አንዲት የማህፀን በር ጫፍ ካንሰርን እንዴት
ሴት ለሚቀጥሉት 2 እና 3 ዓመታት ተጨማሪ ምርመራ መከላከል ይቻላል?
ማድረግ ላይኖርባት ይችላል፡፡
እድሜያቸው ከ30 ዓመት በላይ ያሉ ሴቶች ደግሞ • ተደጋጋሚ እና ያልተቋረጠ የቅድመ ካንሰር ምርመራ
የፓፕ ፣ የኤች.ፒ.ቪ አልያም ሁለቱንም ምርመራዎች ማድረግ
በጣምራ ሊያደርጉ ይችላሉ ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡ የአንዲት • ቅድመ ካንሰር ምልክቶች ከታዩ በህክምና ባሙያዎች
ሴት የመጀመርያው የምርመራ ውጤት ጤናማ የሚሰጡ ምክሮችን መተግበር
ከሆነ በሚቀጥሉት የተወሰኑ ዓመታት ውስጥ ቅድመ • የኤች.ፒ.ቪ ቫይረስ መድሀኒቶችን መውሰድ
ካንሰር ምልክቶችን የማሳየት እድሏ ዝቅተኛ ይሆናል፡ • ሲጋራ ከማጨስ መቆጠብ
፡ ከምርመራው ቀጣይ ላሉት 4-5 ዓመታትም ተጨማሪ • በግንኙነት ወቅት ኮንዶምን በትክክል መጠቀም
ምርመራ ማድረግ ላያስፈልግ ይችላል፡፡ • ከብዙ ሰዎች ጋር ግንኙነትን ከመፈፀም መቆጠብ
ነገር ግን እድሜያቸው ከ21 -65 ዓመት ያሉ ሴቶች ሁሉ
የሀኪሞቻቸውን ምክሮች በመከተል ተከታታይ እና ቋሚ የቅድመ ካንሰር ምርመራዎችን የት
የሆነ የቅድመ ካንሰር ምርመራ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡ ማድረግ እችላለሁ?

የአንዲትን ሴት በማህፀን በር ጫፍ ካንሰር የመያዝ እድል በአሁኑ ሰዓት በሀገራችን ያሉ የተለያዩ የመንግስት እና የግል
ምን ሊጨምር ይችላል? የጤና ተቋማት ይህንን የቅድመ ካንሰር ምርመራ እየሰጡ
የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ኤች.ፒ.ቪ በተባለው ቫይረስ ይገኛሉ፡፡ አብዛኞቹም ተቋማት ምርመራውን ከክፍያ ነፃ
አይነት የሚከሰት ነው፡፡ ማንኛዋም የግብረስጋ ግንኙነት ይሰጡታል፡፡ ስለዚህ ማንኛዋም እድሜዋ ከ21 ዓመት በላይ
ማድረግ የጀመረች ሴት ይህ ቫይረስ ሰውነቷ ውስጥ ያለች ሴት ይህንን ምርመራ እንድታደርግ እና ራሷን ከዚህ
ይኖራል፡፡ ሆኖም ግን በትንሽ እድሜዋ ግንኙነት መፈፀም አይነት በሽታ እንድትከላከል ባለሙያዎች ይመክራሉ፡፡

09 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
አይ ሄት ፖለቲካ
በአዱኛ

የወጉን ርዕስ በእንግሊዝኛ ያደረኩት ስድስት ወር ሙሉ አሜሪካ ስለነበርኩ አማርኛ ጠፍቶብኝ ሊመስላቹ
ይችላል ወይም ደግሞ አማርኛ የስራ ቋንቋ መሆን የለበትም ብዬ ለመቃወም አስቤ እንደሆነም ልታስቡ
ትችላላቹ፤ ግን አይደለም!! ዝም ብላችሁ ነገር ባትበሉና ያላሰብኩትን እያሳሰባችሁ ባትዘባርቁ የተሻለ
ይመስለኛል...

ይሄን ስል ይሄ ሰውዬ ወግ ሊያወጋን ነው ወይስስ ሊወጋን ነው ሃሳቡ ምትሉም ትኖራላቹ፤ ግን እንደዛ


አይደለም ፍቅርና ልምምጥ ለኛ ሰው እንደማይበጅ ስለማምን ነው። አየኋችሁ... ልምምጥ አቶዱም
እዝሎ ከሚያንሸራሽራቹ መሪ ይልቅ አስሮ የሚሸመሽማችሁን መሪ እንደምታከብሩ ታዝቤያለሁ፤ ይሄን
ወግ ቆጣ ቆጣ ባሉ ቃላት ያዋቀርኩትም ለዚ ነው!!

ከቅርብ አመታት በፊት የቅርብ ጓደኛዬ በከፍተኛ ወንጀል ተጠርጥሮ በመታሰር ስምንት አመት ተፈርዶበት
ነበር። ባለፈው ግን ምንም አላጠፋህም ተብሎ ካሳ ተከፍሎት ከእስር ቤት ተፈታ። የታሰረው የግራ እጅ
ክንዱ ላይ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ የሚል ፅሁፍ ተነቅሶ ተይዞ መሃከል ላይ ለምን ሰማያዊ ኮከብ የሚል ፅሁፍ
አልጨመርክበትም በሚል ምክንያት ነበር... ዛሬ ግን ማንም አይናገረውም ደረቱን ነፍቶ በጃፖኒ ይዞራል!!!

የቴሌቭዥን ጣቢያዎች መዋሸት አቁመዋል፣ ኢንተርኔት አይዘጋብንም፣ አጭበርባሪ ባለስልጣናት የበሏትን


እየተፉ ከርቸሌ እየተወረወሩ ነው፣ በጥቅሉ ከመብራት ክፍያ በዘለለ ሁሉ ነገር ጥሩ ሁኔታ ላይ ያለ
ይመስለኛል!! በእንቁላል አቅም እንኳን ዋጋው ባይቀንስም መጠኑ ተልቋል ይህ የሚያሳየው የቀድሞው
ስርአት የዶሮዎች ማህፀን ላይ እንኳ ጫናው የከፋ እንደነበር ነው... እኛ ግን ፈላብን ለቀቅ ስንደረግ ያለፈ
ታሪክ እያነሳን እንደውሻ መነካከስ ጀመርን። ከዛም ከዚም የሚናፈሱ ወሬዎችን እየሰማን ተመረዝን...

10 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
ፀባዩ የሚቀያየር ሰው እስስት ሲባል አውቃለሁ፤ ብሄሩ የሚቀያየር ሰው ግን ምን ሊባል እንደሚችል እንጃ!!!
አንድ ክፉ የፌስቡክ ጓደኛ ነበረኝ ሰኞ ሰኞ ኦሮሞ ነው። ከጠዋት ጀምሮ ፊንፊኔ ኬኛ ምናምን የሚሉ ፅሁፎቹን
በፎስቡክ ገፁ ላይ ሲለጥፍ ይውላል፤ አመሻሽ ላይ አማራ ሁኖ እስከ ንጋት ድረስ ንቃ አማራ መደራጀት ነው
ሚሻለን እያለ ሲዘባርቅ ያነጋል፤ ማክሰኞ ጠዋት ከንቅልፌ ስነቃ ጉራጌ ሆኖ አገኘዋለሁ!! ወደ ፌስ ቡክ ገፄ
ስገባ... እቺን ሃገር እኛ ጉራጌዎች ብንመራት ኢትዮጵያ እንደቻይና በልፅጋ አለምን ባስደመመች ነበር የሚል
ልጥፉ ከፊቴ መቶ ግምጭር ይላል... ማምሻውን ወደ ትግሬነት ተለውጦ... ትግስት ፍራቻ አይደለም፤ ትግራይ
እኔን ጨምሮ መለስን፣ ይኋንስን ያፈራች የጀግና አገር ናት ምናምን የሚሉ ፅሁፎችን ይፅፍብናል...

እኔ ዘረኞችን ንቆ የማለፍ እንጂ መልስ የመስጠት ልማድ የለኝም ግን በዚህ ልጥፉ ላይ ምላሽ ፅፌለታለሁ...
አትሊስት በራስ አሉላ ተመካ የሚል... እሱ ግን ለኔ መልስ ለመመለስ ጊዜ አልነበረውም። እንዳልኳችሁ በቀን
ሁለቴ ብሄሩን እየቀያየረ በእልህና በክፋት እኛን በመናጥ ስራው ተጠምዷል!!

አንዳንድ ደራሲዎችና አክቲቪስቶችም ጭራሹን የኢትዮጵያን መረጋጋት የሚሹ አይመስልም አንባቢና


አድማጭ እንዳያጡ በመስጋት ነገር ሲጭሩ ነው የሚስተዋለው... ለምን... ሁሉም ነገር ባንድ ቀን ካልሆነ
ብለን እንጮሃለን?!! አህያን በአንድ ቀን እስክስታ ማስተማር ይቻላል??? በርግጥ ቆንጣጭ ያጣ ልጅ አልጋ
ላይ መሽናቱን አይተውም... ስለዚ እንሽና... አልጋችን ሸቶ ስህተታችን እስኪገማን ድረስ እንሽና!!

አንድ አሳ አስጋሪ ነበር... አሶቹን በሚገባ ይንከባከባቸዋል፣ እየመጣ ተረት ያወራላቸዋል፣ ፍርፋሪ መኖ እየቀለበ
ያንደላቅቃቸዋል... ታድያ ይሄ አሳ አስጋሪ የአሳ ሃብቱ በጣም በመጨመሩ ምክንያት እሱን የሚያግዘውና
አገልጋዩ ሆኖ የሚሰራ ገበሬ ይቀጥራል። ገበሬው ስለ አሶቹ ሁኔታ ምንም አያውቅም እሱ የነበረበት ክፍለሃገር
JOIN OUR TELEGRAM CHANNEL CLICK HERE

የእርሻ መሬት እንጂ የአሳ እርባታ ያልነበረ በመሆኑ አሶቹን እንዴት መንከባከብ እንዳለበት ባለማወቁ እግሩን
በአሶቹ መዋኛ ውስጥ እየታጠበ ውሃቸውን ያደፈርስባቸው ጀመር። አሶቹ ሸሹ አንደኛ አሳ አስጋሪው በየቀኑ
አየመጣ የሚነግራቸው ተረት ናፈቃቸው ሁለተኛ እነሱን ለመንከባከብ የተቀጠረው ገበሬ የአሶቹን ህይወት
ባለማወቁ ምክንያት ውሃቸውን ስለሚያደፈርስባቸው አሶቹ አመፁ የሚጣለው መረብ ውስጥ የሚገባ
አንድም አሳ በመጥፋቱ አሳ አስጋሪው ከሰረ ተመልሶ መቶ የድሮ ተራቱን ቢተርትም አሶቹ አልሰሙም መረቡ
ውስጥ አልገባ ብለው አመፁ...

እኔ ፖለቲካ አሎድም... ግን አሳ አስጋሪው አሶቹን ወደቀድሞ ሰላማቸው መመለስ ከፈለገ አሶቹን ለመጠበቅ
የቀጠረውን ገበሬ ወደ እርሻው መልሶ የደፈረሰውን ውሃ ማፅዳት ያለበት ይመስለኛል!!!

11 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
ሔዋን

ቤተልሄም አምባቸው

እጅ የሚያስቆረጥም የቃቄ ውርድወት ፣ ድገሙኝ የስራ እድል ተመቻችቶላቸዋል፡፡ ምንም እንኳን ቀዳሚ
የሚያስብል ጣይቱ ፍርፍር ፣ ባለሙያ የከሸነችው የላጤዋ እድሉ ለእንደዚህ አይነት ሴቶች ቢመቻችም የኢኮኖሚ
ሽሮ የት እንደሚያኙ ያውቃሉ? እንግዲያውስ ሳር ቤት ጥያቄ ያለባት ማንኛዋም ኢትዮጵያዊት ሴት የስራ ቦታ
ወደሚገኘው “ተምሳሌት ኪችን” ልውሰዳችሁ እና ምግብ እስካለ ድረስ በተምሳሌት ውስጥ የመስራት አጋጣሚው
ቤቱን ላስቃኛችሁ፡፡ ይኖራታል፡፡

“ተምሳሌት ኪችን” የዛሬ 4 ዓመት ገደማ ሳምራዊት በማህበረሰቡ ውስጥ ማንኛውንም የቤት ውስጥ ስራ
ጴጥሮስ ፣ ፍትህ አስራት እና ማስረሻ አየለ በተባሉ ሴቶች ማከናወን በሴት ጫንቃ ላይ የተጣለ ማብቂያ የሌለው
ላይ አተኩረው መስራትን ባለሙ ሶስት ሴት ጓደኛሞች ሀላፊነት ነው፡፡ ምንም እንኳን ይህ የቤት ውስት ስራ የገንዘብ
ሲመሰረት አያሌ አላማዎችን ሰንቆ ነበር፡፡ ሴቶች በህብተሰቡ ተመን አልያም የምስጋና ቃል ባይሰጠውም ሴቶቻችን
ውስጥ ያለባቸው የኢኮኖሚ ጥገኝነት መፈታት እንዳለበት ለዘመናት ሲከውኑት ኖረዋል፡፡ ይህንን የተረዳው ተምሳሌት
እና ራሳቸውን የማስተዳደር የገንዘብ አቅም ሊኖራቸው ኪችንም ሴቶቹ በዚህ ምግብ ቤት ውስጥ ስራ ፍለጋ
እንደሚገባ ያመኑት እነዚህ ጓደኛሞች ይህንን ምግብ ቤት ሲመጡ የቀደመው የቤት ውስጥ የስራ እንቅስቃሴያቸውን
መሰረቱ፡፡ ይህ ምግብ ቤት የተለያዩ ሴቶችን በተለይም በቂ በቂ የስራ ልምድ አድርጎ ይወስዳል፡፡ ይህንን ልምድም
የሆነ የትምህርት ዝግጅት የሌላቸውን እና የስራ ልምድ ከዘመናዊው የምግብ ቤት ስነ-ምግባር ጋር ያዋድዱትም
ያላካበቱትን ወደ ተለያየ ቦታ ስራ ፍለጋ በሚሰማሩበት ግዜ ዘንድ ስራ ከመጀመራቸው በፊት በቂ የሆነ ስልጠና
ከሚደርስባቸው እንግልት እና እንግልቱም ከሚፈጥረው እንዲያገኙ ይደረጋል፡፡ ስልጠናውም በምግብ ቤቱ ውስጥ
ተስፋ መቁረጥ ለመታደግ ያለመም ነው፡፡ በምግብ ቤቱ ላላቸው ቆይታ ብቻ ሳይሆን ከምግብ ቤቱ ውጪም ቢሆን
ውስጥ ልጆቻቸውን ብቻቸውን የሚያሳድጉ እናቶች ፣ ለሚኖራቸው ቀሪ የስራ ግዜ እና ተጨማሪ የስራ እድሎች
ከትምህርት ገበታቸው የተፈናቀሉ ሴቶች እና ወደ አበይት ግብዓት ይሆናል፡፡ ስልጠናው በአብዛኛው በተግባር
አረብ ሀገራት ለመሄድ በመሰናዳት ላይ ያሉት ቀዳሚ ላይ ያተኮረ እንዲሆን የሚደረግ ሲሆን ይህም ደግሞ ሴቶቹ
12 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
ሔዋን

ስልጠናው ባለቀበት ሰዓት ወዲያውኑ ያለምንም ተጨማሪ የተነሳ ድርጅት እንደመሆኑ መጠን እስከ አሁን የገጠሙትን
ግዜ ማጥፋት ስራውን እንዲቀላቀሉ ይረዳል፡፡ የንግድ አልያም ሌሎች ፈተናዎች በራሱ ሲፈታ ቆይቷል፡፡
JOIN OUR TELEGRAM CHANNEL CLICK HERE

በተምሳሌት ውስጥ ያሉ ሴቶች የሚያገኙት የስራ ስልጠና አሁንም ቢሆን ይህንን የመቀጠል አላማ አለው፡፡ ነገር ግን
ብቻም አይደለም፡፡ በሌላ ዘርፍ ያለ የትምህርት እድልም ከድርጅቱ አላማ ጋር የኛም ሀሳብ ይዋደዳል የሚል አካል
ይመቻችላቸዋል፡፡ ምግብ ቤቱ ከሰነቃቸው አላማዎች ካለ ከተምሳሌት ጋር ጥምረት የመፍጠር በር ሊከፈትለት
መካከል አንዱ ሴቶችን በኢኮኖሚ ማብቃት ነው እና እንደሚችል ለመገንዘብ ችለናል፡፡
ማንኛዋም የምግብ ቤቱ ሰራተኛ ለነገዋ የሚሆንን ተጨማሪ ተምሳሌት በዋናነት ሴቶችን በኢኮኖሚ ማበልፀግ ላይ
ችሎታ እና እውቀት ይዛ እንድትወጣ ይፈለጋል፡፡ በዚህም አተኩሮ ቢሰራም አብዛኞች በተሳሳተ መልኩ እንደሚረዱት
ፍላጎት ውስጥ ታድያ ሰራተኞች ራሳቸውን በትምህርት ግን የእርዳታ ድርጅት አይደለም፡፡ ይልቁንም ማህበረሰብ
እንዲያዳብሩ የሚችሉበት መንገድ ተመቻችቷል፡፡ ተኮረ የሆነ የንግድ ድርጅት እንጂ፡፡ ይህ ማህበረሰብ ተኮር
በተምሳሌት ውስጥ ያለች ሴት የመማር ፍላጎት ካላት የሆነ ድርጅት ለመሰል ድርጅቶች አልያም በዚህ አይነት
ምግብ ቤቱ ሙሉ የትምህርት ወጪን እስከመሸፈን የንግድ ዘርፍ ለመሰማራት ለሚያስቡ ሁሉ ከተሞክሮው
የሚደርስን ድጋፍ ሊያደርግላት ይችላል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ምክርን ሳያካፍል አላለፈም፡፡ የድርጅቱ ኦፕሬሽናል ማናጀር
ተምሳሌት በስሩ 23 የሙሉ ግዜ ሰራተኞች ሲኖሩት ከዚህ የሆነችው ትዕግስት ወርቅነህ እንዲህ ስትል ምክሯን
በተጨማሪም 6 የአስተዳደር ሰራተኞች አሉት፡፡ ከሌላው ታካፍላለች “በመጀመርያ አንድ ሰው ወይንም ድርጅት
ድርጅት ለየት ባለ ሁኔታም ሁሉም የአስተዳደር ሰራተኞች በእንደዚህ አይነት የንግድ ዘርፍ ለመሰማራት ሲያስብ
ምንም አይነት ክፍያ ከተምሳሌት ሳያገኙ በበጎ ፈቃደኝነት ይህንን አይነት ስራ መስራት መፈለጉን እርግጠኛ መሆን
የሚያገለግሉ ናቸው፡፡ አለበት፡፡ ሁለተኛ ነገር ደግሞ የሚያጋጥሙትን ችግሮች
ተምሳሌት ሴቶችን በኢኮኖሚ ከማብቃት በዘለለ ሁሉ ለመጋፈጥ ሙሉ ፈቃድ ሊኖረው ይገባል፡፡ አለበለዚያ
ጠቅላላውን የማህበረሰብ ክፍል የሚነኩ ጉዳዮችም ላይ ብዙ ርቀር መጓዝ ሊከብደው ይችላል፡፡ ተምሳሌት አራት
በማተኮር ይታወቃል፡፡ በተለያዩ ርዕሶች ዙርያ በየወሩ አመት ይህንን ስራ ሳያቋርጥ መስራት የቻለው ከላይ
የሚዘጋጀው “ዘ ስታንድ” የተሰኘውን የውይይት መድረክ ያልኩሽ ቁርጠኝነት ውስጣችን ስላለ ነው፡፡ “
ለዓብነት ማንሳት ይቻላል፡፡ በዚህ ወርሀዊ መድረክ ላይ ድርጅቱ በምግብ ቤት ብቻ ሳይገደብ ለወደፊቱ የተለያዩ
ማንኛውም ሰው መሳተፍ የሚችል ሲሆን በሚነሱት ስራዎች ላይ የመሰማራት ሀሳብ ሲኖረው ከእነዚህም
ዘርፈ ብዙ ርዕሶችም ላይ ሙያዊ አስተያየቶችን ጨምሮ መካከል አንደኛው የህፃናት መዋያ በመክፈት በተለይም
የፕሮግራሙ ተሳታፊዎችም ሀሳባቸውን እንዲያጋሩ ልጆቻቸውን በሚጠብቅላቸው ሰው እጦት ምክንያት
ይደረጋል፡፡ ከወርሀዊ መድረኩ በዘለለም ለልዩ ልዩ ስራቸውን ማከናወን ያልቻሉ ሴቶችን ማገዝ እና ወደ ስራ
ከተምሳሌት አላማ ጋር ኩታ ገጠም ለሆኑ ዝግጅቶች ገበታቸው እንዲመለሱ መርዳት ነው፡፡
ሬስቶራንቱ ቦታ ያመቻቻል፡፡ ማንኛውም ውይይቶችን እና እኔም በቦታው ተገኝቴ ከታደምኩት የቤቱ እጅ
ህብረተሰብ ተኮር የሆኑ ዝግጅቶችን አልያም ትርኢቶችን እና የሚያስቆረጥም ምግብ እና መንፈስን ከሚያድሰው
የጥበብ ምሽቶችን ማዘጋጀት የሚፈልግ ግለሰብ ወይንም የምግብ ቤቱ ድንቅ ድባብ እርስዎም ይካፈሉ ስል
ድርጅት የሚዘጋጀው ዝግጅት ተምሳሌት የተነሳበትን አላማ በመልካም74 ስም ግብዣዬን አስተላልፋለሁ፡፡
የሚደግፍ ከሆነ በምግብ ቤቱ አዳራሽ ውስጥ ዝግጅቱን
የማድረግ አጋጣሚው ሊፈጠርለት ይችላል፡፡ አድራሻ፡ ሳር ቤት ከአዳምስ ፓቪሊዮን አለፍ ብሎ ኮይካ
ተምሳሴት በራስ ሰርቶ ራስን ማበልፀግ የሚል ሀሳብን ይዞ ህንፃ ስር
13 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
ከጀርባ ማን ነበር ?

ከእንጦጦ
ቤተ-ዕደጥበባት
ጀርባ ማን ነበር?
ከእንጦጦ ተራራ ስሙን ያገኘው እንጦጦ ቤተ-ዕደ ጥበባት ትረቱን የኤች.አይ.ቪ. ቫይረስ በደማቸው ውስጥ ያሉ
ሴቶችን በኢኮኖሚ ራሳቸው እንዲችሉ ማድረግ ላይ አድርጎ የሚሰራ ድርጅት ነው፡፡ ድርጅቱ ለእንደዚህ አይነት
ሴቶች የስራ እድል ከመፍጠር ባለፈ የሚሰሩትን የእጅ ስራ ውጤቶች በሙሉ ለውጪ ገበያ በማቅረብ የሀገራችን
የራስ ምታት የሆነውን የውጪ ምንዛሬ ችግር ለመቅረፍ አበክሮ ይሰራል፡፡ ከዚህ ውጤታማ ከሆነ ድርጅት ጀርባ
ካለችው እና የድርጅቱ መስራች ከሆነችው ከቤተልሄም ብርሃነ ጋር ቆይታ አድርገን ነበር፡፡ መልካም ንባብ!

መልካም74፡ ቤቲ ብዙ የሚድያ ሰው አይደለሽም፡፡ ብዙም አልፈልገውም::


ብዙ ሚድያዎች ላይ አናይሽም ሆኖም ግን ይህንን ቃለ-
መጠይቅ ለመልካም74 ለመስጠት ፈቃደኛ ስለሆንሽ ወደ ጥያቄሽ ስመጣ ፤ እንጦጦ በመጀመርያ ስሙን
በአንባቢዎቼ ስም በጣም አመሰግናለሁ፡፡ ያገኘው ከእንጦጦ ተራራ ነው፡፡ በተራራው ላይ
በመጀመርያ ስለ እንጦጦ ቤተ-ዕደ ጥበባት ንገሪኝ:: ከተለያዩ ቦታዎች ተራራው ላይ ካለ ቤተክርስቲያን
ድርጅቱ ምንን መሰረት አድርጎ ነው የተቋቋመው? ጠበል ሊጠጡ መጥተው ነገር ግን ፈውስን
እንጦጦ የሚለውን ስም የመረጣችሁበት የተለየ ባለማግኘታቸው የተነሳ እዛው የቀሩ በጣም
ምክንያት አለ? ብዙ ሴቶች አሉ፡፡ አነዚህ ሴቶች ከህብረተሰቡ
ጋር ተቀላቅለው እንዳይሰሩ አንደኛ የስራ ችሎታ
ቤተልሄም፡ እኔም በጣም አመሰግናለሁ ቃለ- የላቸውም፡፡ ወደ ሀገራቸው እንዳይመለሱ ደግሞ
መጠይቅ ልታደርጉኝ ስለመጣችሁ፡፡ እንዳልሽው እኔ በሽታ አለባቸው ተብሎ ስለሚታሰብ ህብረተሰቡ
ብዙ ሚድያ ላይ መውጣት አልወድም፡፡ ምክንያቴ ያገላቸዋል፡፡ በዚህም የተነሳ መሄጃ አጥተው እዛው
ደግሞ አንደኛ ሚድያ ላይ የሚያስወጣ ነገር ተራራው ላይ በጣም በከፍተኛ ችግር ላይ የሚገኙ
ሰርቻለሁ ብዬ አላምንም፡፡ ሁለተኛ ደግሞ “ሎው ብዙ አሉ እና እንጦጦ ቤተ-ዕደጥበባትም በዋነኛነት
ፕሮፋይል” የሆነ ነገር ይመቸኛል፡፡ ለዛ ሚድያን እነዚህን ሴቶች ራሳቸውን በኢኮኖሚ እንዲችሉ
14 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
ከጀርባ ማን ነበር ?

ብሎም ሀገራቸውን መጥቀም እንዲችሉ ለማድረግ መልካም74፡ ወደዚህ አይነት ስራ እንዴት ልትገቢ ቻልሽ?
በማሰብ በዋነኛነት እነዚህን ሴቶች ሙያ በማስተማር ምን አይነት አጋጣሚ ነው ወደዚህ ስራ የሳበሽ?
የተለያዩ ለወጪ ንግድ የሚቀርቡ ጌጣ ጌጦችን እንዲያመርቱ
እናደርጋለን ማለት ነው፡፡ ቤተልሄም፡ እንግዲህ እኔ ከኮሌጅ ማርኬቲንግ ተምሬ
እንደወጣሁ የኢትዮጵያ ቱሪስት ትሬዲንግ ውስጥ ባለ
መልካም74፡ እንጦጦ አተኩሮ እየሰራ ያለው ኤች.አይ.ቪ አንድ ሱቅ ላይ በሴልስ ፐርሰንነት ተቀጠርኩ፡፡ ነገር ግን
ቫይረስ በደማቸው ውስጥ ያሉ ሴቶች ላይ ነው፡፡ እነዚህን ሴቶች እዛ ያሉትን እቃዎች ሳያቸው አያምሩም፡፡ እኛ ደግሞ
መምረጥ ያስፈለገበት ምክንያት ምንድን ነው? የምንመርጠው እቃ የሚያብረቀርቅ ወይንም የሆነ አይነት
የውጪ ስሜት ያለው ነው እንጂ የራሳችን የባህላችን
ቤተልሄም፡ እንጦጦ በዋነኛነት እንደ ድርጅት እኩል የሆነ የሆኑት እቃዎች ብዙም አይስቡንም፡፡
የሀብት ክፍፍል በህብረተሰብ ውስጥ መኖር እንዳለበት እዛ እየሰራሁ እራሴን አንድ ነገር ጠየኩት፡፡ ማነኝ ፣ምንድን
ያምናል፡፡ በዚህም የተነሳ እነዚህን ሴቶች ስናያቸው ብዙም ነኝ ፣ ወዴት ነው የምሄደው ፣ ምንድን ነው የምፈልገው፣
ትኩረት ያልተሰጣቸው እና በህብረተሰቡ የተገፉ ስለሆኑ ለምንድን ነው ወደዚህ ምድር የመጣሁት የሚለውን ጥያቄ
ስራ የማግኘት እና ራሳቸውን የመደገፍ እድላቸው በጣም ራሴን ጠየኩ፡፡ በሰዓቱ 22 ዓመቴ አካባቢ ነበር፡፡ ከዛ ደግሞ
ዝቅተኛ ነው፡፡ ለዚህም ነው እንደ ድርጅት እነዚህ ሴቶች ዲግሪ መማር ነበረብኝ፡፡ አካውንቲንግ ልማር? ቤተሰብ
ላይ አተኩረን መስራት የፈለግነው፡፡ ደግሞ መርዳት ነበረብኝ ፤ በዛ ሁሉ መሀል ራሴን ፈልጌ
አገኘሁት ማለት ነው፡፡ እኔ አካውንቲንግ መማር አልችልም፡፡
መልካም74፡ ሌላው ደግሞ ምንድን ነው እቃዎቹን ቢሮ ውስጥ ቁጭ ብዬ መስራት ሳይሆን የምችለው እኔ
ለማምረት የምትጠቀሙባቸው እቃዎች ጌጣጌጦችን ለማምረት ሴልስ መሆን ነው የምችለው ብዬ ለራሴ ወሰንኩ፡፡ ከዛ
ይጠቅማሉ ተብለው የሚታሰቡ አይነት አይደሉም፡፡ ከቡና ደግሞ የራሴን ስራ ስሰራ የምወደውን ስራ መስራት አለብኝ
የተሰራ የአንገት ጌጥ አይቻለሁ:: ከጥይቅ ቀለሀ የተሰራ አለ፡ ብዬ አሰብኩኝ፡፡ የምሰራበት ቦታ ያሉትን እቃዎች ደግሞ
፡ ከወዳደቁ ብረቶች ጌጦችን ትሰራላችሁ እና እንደዚህ አይነት ሳስተውላቸው የራሳችን ወግ እና ልማድ የሚገለጥበት
እቃዎችን የመረጣችሁበት ምክንያት ምንድን ነው? የእኛው የሆነ ነገር እንደሆነ ገባኝ፡፡ ማንኛውንም ነገር
ስንጀምር ደግሞ በቅርብ ካለው መሆን አለበት እና እንደነሱ
ቤተልሄም፡ በነገራችን ላይ እነዚህ ጌጦች እኮ አዲስ አይነት እቃዎችን መሸጡ ላይ ለማተኮር ወሰንኩ፡፡ በግዜ
የፈጠርናቸው አይደሉም፡፡ ወሎ ብትሄዱ ወይንም ሂደት ደግሞ እቃዎቹን በጣም እየወደድኳቸሁ መጣሁ፡፡
ወደ ጎጃም ብትሄዱ እነዚህን ጌጦች የአካባቢው ሰዎች ለኔ በፊት የነበርኩበት የስራ ቦታዬ በጣም ብዙ ትምህርት
በስፋት ሲጠቀሙባቸው ታያላችሁ፡፡ እኛ ምንድን ነው ያገኘሁበት ነው፡፡ እዛ ለነበሩ ሰዎች ሁሉ ፣ ላገኘኃቸው ሰዎች
ያደረግነው ባህላዊ የሆኑትን ጌጦች ዘመናዊ መልክ ፣ ለመንግስት ትልቅ ምስጋና እና አክብሮት አለኝ፡፡
እንዲይዙ አደረግናቸው፡፡ እነዚህን ጌጦች እኛ አይደለንም
የፈጠርናቸው፡፡ ቡናውንም ፣ ብረቱንም ምኑንም ወደ መልካም74፡ እዚህ ቤት የሚሰሩት ስራዎች የዕደ-ጥበባት
ጌጥነት ቀይሮ በቀላሉ መስራት ይቻላል፡፡ ስራዎች ናቸው፡፡ ይህ አይነተ ስራ ደግሞ በባህሪው የሆነ አይነት
ችሎታን ወይንም ሙያን የሚጠይቅ ነው፡፡ አንቺ ከዚህ በፊት
መልካም74፡ እንጦጦ እየሰራ ያለው ነገር ፤ እየደረሰ ያለውም ለሙያው የመጋለጥ አጋጣሚ ነበረሽ ወይስ ሙያውን ተምረሽው
የሰው ቁጥር በጣም ሰፊ ነው፡፡ የዚህን ድርጅት ስራ ያየ ወይም ነው ይህንን ስራ የመረጥሽው?
የሰማ ሁሉ ደግሞ ከድርጅቱ ጀርባ ያለችው ማናት ብሎ መጠየቁ
አይቀሬ ነው፡፡ ማን ብለን እንንገራቸው? ቤተልሄም ብርሀነ ቤተልሄም፡ እኔ ቅድም እንዳልኩሽ ዲዛይነር አይደለሁም፡፡
ማናት? እዚህ ላይ እውነቱን ነው መናገር የሚያስፈልገው፡፡
ለዲዛይነሮች ትልቅ አክብሮት አለኝ ግን ዲዛይነር
ቤተልሄም፡ ቤተልሄም ብርሃነ የ40 ዓመት ሴት:: ባለትዳር እና አይደለሁም፡፡ ነገር ግን የሆኑ ነገሮች የሆነ ቦታ ማድረግ
የሁለት ልጆች እናት ፤ በዛም ላይ ደግሞ ኢትዮጵያዊት ናት፡፡ እችላለሁ፡፡ ለምሳሌ እኔ ዲዛይን ያደረኳቸው ቦርሳዎች
15 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
ከጀርባ ማን ነበር ?

፣ ያንገት ጌጦች እዚህ ቤት ታገኛለሽ፡፡ የዚህንም ሱቅ መድሀኒት እያቀበለ ነው ማለት ነው፡፡ በዚህም የተነሳ ከመንግስት
ኢንቲሪየር ዲዛይን እኔ በሰፊው ተሳትፌበታለሁ፡፡ ስለዚህ የተለየ ድጋፍ እና አትኩሮት ሊሰጠው ይገባል ባይ ነኝ፡፡ ነገር ግን
ይሄ ነገር የኔ የውስጥ ፍላጎት ወይንም ደግሞ ፓሽኔ ነው:: እውነታውን የምታውቂው አንቺ ነሽ እና ከመንግስት በኩል
አንዳንዱ ነገር ባይሸጥ እንኳን እንደዚሁ ተሰርቶ ሲቀመጥ ያለው ትኩረት በተለይም ለወጪ ንግድ እንቅስቃሴ ምን
እና ሳየው ደስ ይለኛል፡፡ አንዳንድ ነው የእውነት ዲዛይነር ይመስላል? በምን ተደግፋችኃል በምን ደግሞ ችላ ተብላችኃል?
JOIN OUR TELEGRAM CHANNEL CLICK HERE

ነው፡፡ አንዳንድ ሰው ደግሞ ሰው የሚፈልገውን ያውቃል፡


፡ እኔ ሰው የሚፈልገውን አውቃለሁ ወይም ደግሞ ምን ቤተልሄም፡ እንጦጦ መደገፍ ባለበት መጠን አልተደገፈም፡፡
ከምን ጋር እንደሚሄድ በመጠኑ አውቃለሁ፡፡ እንጦጦ ፕሮጀክት ነው፡፡ የእኔ ነው ወይንም ደግሞ
የቤተሰቤ ነው ብዬ አላስብም፡፡ እውነቴን ነው የምልሽ
መልካም74፡ ስለዚህ ዲዛይነርነት ሳይሆን የውስጥ ፍለጉት እንጦጦ የሀገር ነው ብዬ ነው የማስበው፡፡ ከመንግስት
ነው አንቺ ጋር ያለው ብለን ማለት እንችላለን? ድጋፍ በማጣቱ የተነሳ ደግሞ የተገደበ ምስኪን ድርጅት
ነው፡፡ እኔ ውስጤን ሞልቶ የሚፈስ ራዕይ አለኝ፡፡ እንግዲሀ
ቤተልሄም፡ አዎን፡፡ ምናልባት ይሄ ነገ በትምህርት ቢደገፍ ካለኝ ምንም ማድግ አይቻልም፡፡ ነገር ግን ብዙ ማነቆዎች
ዲዛይነር ወደሚለው የሚያሳድገኝ ይመስለኛል አንዳንዴ አሉብን፡፡ አንዱ እና ዋነኛው የመስሪያ ቦታ ችግር ነው፡፡
ሳስበው፡፡ ግን ደግሞ እንደሱም ለመድፈር እቸገራለሁ፡፡ አሁን ገና የመስሪያ ቦታ አዲስ ከተገነቡት የመስሪያ ቦታዎች
ላይ ሁለት “ፍሎር” ተሰጠን፡፡
መልካም74፡ አንቺ ዲዛይነር አይደለሁም ትይኛለሽ እኔ እኛ ወደ ሀገራችን ዶላር እናመጣለን ነገር ግን የቦርሳ
ግን ምን ሰማሁ ያንቺ የሆነ ስራን ሚሼል ኦባማ የማድደግ ፊኒሺንግ ብረቶችን እና የጌጣጌጥ መስሪያዎችን ለማምጣት
አጋጣሚው ነበራት፡፡ ቪክቶሪያ ቤካምም እንዲሁ እንጦጦ በማለት ያመጣነውን ዶላር መልሰን ወደ ቱርክ እና ቻይና
መጥታ ስራው ላይ የተሳተፈችበት አጋጣሚ ነበር፡፡ ስለ እሱ እንወስደዋለን፡፡ ፋሽኑ የሚጠይቀውን አይነት ምርት
እስቲ አጫውቺኝ፡፡ ለማምረት ያንን ማድረግ ግድ ነው፡፡ አለበለዚያ
አይፈልጉትም ስለዚህ ከውጭ የምናመጣቸውን
ቤተልሄም፡ ሚሼል ያደረገችውን ጌጥ እኔ እልነበርኩም እቃዎች መተካት ላይ ነው አተኩረን መስራት ያለብን፡፡
የወሰድኩት፡፡ “ቴን ታውዘንድ ቪሌጅስ” የሚባል አንድ በዚህ ብቻ ነው በትክክል የሀገርን ኢኮኖሚ መደገፍ
የ”ፌር ትሬድ” አባል የሆነ ድርጅት ውስጥ የምትሰራ የምንችለው፡ ፡ ጌጦቹን ለመስራት የሚያስፈልጉትን ሁሉ
ሴት ጌጡን ከኛ ይዛው ትሄዳች እኛም የፌር ትሬድ አባል ግብዓቶች መንግስት ቢደግፈን እዚሁ ማምረት እንችል
ስለሆንን ማለት ነው፡፡ በዚህ ግዜ ሚሼል የአፍሪካን ወጣቶች ነበር፡፡ ነገረ ግን የሚደረገው ድጋፍ የሚያስፈልገውን
ለማናገር ደቡብ አፍሪካ በመጣች ግዜ ጌጡን አይታ በጣም ያህል አይደለም፡፡ በዚህም ድጋፍ ማጣት ምክንያት
ስለወደደችው ወሰደችው ማለት ነው፡፡ ቪክቶሪያ ቤካምም ከፈረንሳይ እና ከአሜሪካ ያገኘናቸውን ከፍተኛ የገበያ
እንደዚሁ የዩ.ኤስ ኤይድስ የሴቶች አምባሳደር በነበረችበት ዕድሎች አጥተናል፡፡
ግዜ ኢትዮጵያ መጥታ ነበር እና እንጦጦንም ጎብኝታ ነበር፡፡ በእርግጥ የማልክደው ነገር አሁን የተወሰነ ቦታ
በዚህ ግዜ አንድ የእጅ ጌጥ ዲዛይን አድርጋ ሄደች፡፡ ዲዛይኑን ተሰጥቶናል በዛውም ላይ ከቀረጥ ነፃ ተጠቃሚዎች ነን
እኛ ቤካ በለነው ነበር እሷ ግን ቪክቶሪያ በሉስ ስላለችኝ ሆኖም ግን ድጋፉ ይበቃል ማለት አይደለም፡፡
ቪክቶሪያ ብለን ሰይመነው አሁንም ድረስ ጌጡ በሱቆ
ቻችን ይገኛል ማለት ነው፡፡ እና እነዚህ ነበሩ አጋጣሚዎቹ፡፡ መልካም74፡ በውጪው አለም አንድ የተለመደ
ነገር አለ፡፡ እሱም ምንድን ነው በተለይ እናንተ
መልካም74፡ እንግዲህ ባለንበት ነባራዊ ሁኔታ የሀገራችን የምትሰሯቸውን አይነት የተለዩ ምርቶችን የሚያቀርቡ
ራስ ምታት የሆነው ዋነኛው ነገር የውጭ ምንዛሬ እጥረት ነው፡ ድርጅቶች ስራዎቻቸውን በተለያዩ ሰፊ የመደብር
፡ እንጦጦ ደግሞ እንደ ድርጅት በወጪ ንግድ ላይ አተኩሮ ሰንሰለት ባላቸው ቦታዎች ላይ የማስቀመጥ እና
የሚሰራ ነው፡፡ ይህ ማለት የሀገራችንን ራስ ምታት ለማከም የማሸጥ ነገር አለ፡፡ ለምሳሌ ታርጌት ፣ ወይም ሜይሲስ
16 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
ከጀርባ ማን ነበር ?

የተባሉ አይነት ሱቆች እንደዚህ የማድረግ ልምድ


አላቸው፡፡ እናንተስ ምርቶቻችሁን እንደነዚህ ባሉ ሰፊ መልካም74፡ አሁን ምን ያህል ሱቅ አላችሁ ማለት ነው እዚህ
ተደራሽነት ባላቸው መደብሮች ውስጥ የማስቀመጥ ሀገር ላይ?
አጋጣሚው ነበራችሁ? ቤተልሄም፡ እዚህ ሀገር ላይ ኤርፖርት ትልቅ ሱቅ
አለን፡፡ የኛ ብቻ ሳይሆን ሌሎችም የዕደ-ጥበባት
ቤተልሄም፡ ችግሩ ምን መሰለሽ ደሀ ስትሆኚ ውጤቶች የሚሸጡበት፡፡ እዚሀ ለምሳሌ ከ26 በላይ
ትበዘበዣለሽ፡፡ በዘመናዊ መንገድ በደንብ ነው የሆኑ ዕደ-ጥበብ ውጤት አምራቾች ስራቸውን
የምትበዘበዥው፡፡ ፈረንጆቹ በዝባዦች ናቸው፡፡ ይሸጣሉ፡፡ ለምሳሌ ከአክሱም ፣ ከባህር ዳር እንዲሁም
ከእኛ 2 ዶላር ይገዛሉ እነሱ 90 ዶላር ይሸጡታል፡፡ እዚሁ አዲስ አበባ ውስጥም ያሉ የተለያዩ ድርጅቶች
እኛ በዋጋችን ላይ አንድ ሳንቲም እንጨምር ብንል እና ማህበራት እዚህ ሱቅ ውስጥ ስራዎቻቸውን
ጦርነት ነው፡፡ ስለዚህ እኛ ይሄ ዘመናዊ ብዝበዛ ሰለቸን፡፡ ያስቀምጣሉ፡፡ ይሸጥላቸዋል ማለት ነው፡፡ ስለዚህ
JOIN OUR TELEGRAM CHANNEL CLICK HERE

ሁሉም ማት ቢከብድም እንኳን አብዛኞቹ እንደዛ እኛ የራሳችንን ምርት ብቻ ሳይሆን ባሉን ሱቆች ሁሉ
ናቸው፡፡ ስለዚህ እኛ በፈረነጆቹ ፌብሩዋሪ ላይ እንጦጦ የሌሎች አምራቾችንም ምርቶች እንሸጣለን፡፡ አሁን
ኤል.ኤል.ሲ ሚኒአፖሊስ ላይ መሰረትን፡፡ ስለዚህ አራት ሱቆች ናቸው ያሉን 6 ኪሎ ፣ አትላስ አካባቢ
ስራዎቻችንን በራሳችን ሱቅ ለመሸጥ እንቅስቃሴ ላይ ፣ ኤርፖርት ውስጥ እና ሂልተን ሆቴል፡፡ አሁን ደግሞ
ነን፡፡ የምናደርገውም ያንን ነው፡፡ ስካይ ላይት ሆቴል ውስጥ ልንከፍት ነው፡፡

መልካም74፡ ውጪ ከሚወጡት እቃዎች በተጨማሪ ሀገር መልካም74፡ ምን ያህል ሰራተኞች አሉ በስራችሁ አሁን?
ውስጥ ካሉ የተለያዩ አምራቾች ጋርስ ያለው የገበያ ትስስር ምን ቤተልሄም፡ እንድዲህ አሁን ኮንስትራክሽን ውስጥም
የመስላል? በምን መልኩ ነው አብራችሁ እየሰራችሁ ያላችሁት? ገብተናል፡፡ ስለዚህ ወደ 250 አካባቢ ሰራኛ ይኖረናል፡፡
ያው በተለያየ ቦታ ላይ ስለሆነ ሰራተኞቻችን ያሉት
ቤተልሄም፡ የገበያ ትስስር የተፈጠረልን የተለያየ ክልል ይህን ያህል ብሎ ትክክለኛ ቁጥር መስጠቱ ይከብደኝ
ላይ ካሉ አምራቾች ነው፡፡ ለምሳሌ የተለያዩ የስፌት ይሆናል፡፡
ስራዎችን ከ ባህር ዳር እና አክሱም እናመጣለን ፣
ጌጦችን ከወሎ እና ከጎጃም እናመጣለን ፣ ደቡብ ላይ መልካም74፡ የማምረት አቅሙስ ምን ላይ ደርሷል፡፡ በጅምላ
ማር እና ቡና የሚያቀርቡልን አሉ ፣ በተለይም ደግሞ መግዛት የሚፈልጉ ሰዎች ካሉ ያንን ፍላጎት የማሟላት አቅም
ካዌ ከተባለው ድርጅት ጋር - እነ ወ/ሮ ንግስት ማለት አላችሁ?
ነው ከእነሱም ጋር እንሰራለን፡፡ ለኔ ወ/ሮ ንግስት ማለት ቤተልሄም፡ እኛ ትልቁ ችግራችን የመስሪያ ቦታ እጥረት
ከእናቴ ቀጥላ አስተማሪዬ ናት፡፡ ክብር የሚገባት ሴት ነው፡፡ ከዛ ውጪ በጅምላ አንድ እና ሁለት መቶ ሺ
ናት፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ መሬት የወረደ ስራ ስትሰራ ስራዎችን በአንድ ሲዝን የሚያዝ ሰው ቢመጣ ያንን
ያየኃት እኔ እሷን ነው፡፡ እንግዲህ ይህንን ይመስላል ፍላጎት ለሁለት አመታት ማሟላት የሚችል ጥሬ እቃ
ያለን ትስስር፡፡ እጃችን ላይ አለ፡፡ ግን መስሪያ ቦታ የለንም፡፡

17 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
ከጀርባ ማን ነበር ?

መልካም74፡ እስከዛሬ ድረስ ብዙ ስራዎችን ሰርተሻል እና ማህበራዊ ሀላፊነት ላይ ማተኮር በጣም የምፈልገው
በእኔ እይታ ስኬታማ ነሽ ብዬ አስባለሁ፡፡ አንቺስ ስኬታማ ነኝ እና የምታገልለለትም ጉዳይ ነው፡፡ ድርጅቶች
ብለሽ ታስቢያሽ? ስኬትስ ላንቺ ምንድን ነው? ማህበራዊ ሀላፊነታቸውን በተወጡ ቁጥር የሀብት
ክፍፍሉ ፍትሀዊ እየሆነ ይመጣል፡፡ ይህ ደግሞ አሁን
ቤተልሄም፡ እኔ ስኬታማ ነኝ ማለት ይከብደኛል፡ የምናያቸውን ችግሮች ሁሉ የሚቀርፍልን ነው፡፡
፡ አይደለሁም ማለትም በጣም ይከብደኛል፡፡ የእኛን አሁን ሀገራችን ውስጥ ያሉ ችግሮችን ሁሉ የፈጠረው
ሴቶች ሳስብ እንዴት እድለኛ ነኝ እላለሁ፡፡ ትልቁ ፍትሀዊ የሆነ የሀብት ክፍፍል አለመኖር ነው፡፡ እኔ
አላማዬ ኢኮኖሚውን መቆጣጠር ነው፡፡ ያልተወሰነ እየበላሁ ፣ ልጆቼን ጥሩ ትምህርት ቤት ስያስተማርኩ
የገነዘብ ሀብት ውስጥ መግባት ነው ህልሜ፡፡ ይህ ግን ሌላው ግን የሚበላው አንኳን አጥቶ እያየሁ ዝም ብዬ
JOIN OUR TELEGRAM CHANNEL CLICK HERE

የቅንጦት ህይወትን ለመምራት አይደለም፡፡ አለም ላይ ማለፍ አልፈልግም፡፡ ያንን ለማድረግ የሚደፍር ሰው
ስትኖሩ ገንዘብ አቅም ነው፡፡ ተቀባይነትን የምታገኙት ራሱ ምን አይነት ህሊና እንዳለው አላውቅም፡፡ ለዚህ
በምታወጡት ገንዘብ ልክ ነው፡፡ ነው በተለይ ማበራዊ ሀላፊነትን መወጣት እና ፍትሀዊ
የሆነ የሀብት ክፍፍል ማስፈን ላይ ማተኮር የፈለኩት፡፡
መልካም74፡ እንጦጦ በዋናነት ማበረሰባዊ ሀላፊነቱን ሌሎች ድርጅቶችም ይህንን ተግባር እንዲከተሉ እና
መወጣት ላይ አተኩሮ ነው እየሰራ ያለው፡፡ ይህን ነገር ደግሞ የበኩላቸውን እንዲያደርጉ እመክራለሁ፡፡
አብዛኛው ድርጅት ሲተገብረው አላየንም፡፡ በዛም ላይ ደግሞ
ተጨማሪ ወጪዎችን ስለሚጠይቅ ድረጅቶች በአብዛኛው መልካም74፡ እኔ እግዲህ ያለኝን ጥያቄ ጨርሻለሁ፡፡
ሲሸሹት ይስተዋላል፡፡ ለመሰል ድርጅቶች ማበራዊ ሀላፊነትን ቤቲ ግዜሽን ሰጥተሸኝ ይህንን ቃለ-መጠይቅ
ከመወጣት አንፃር ምን ቢያደርጉ ብለሽ ትመክሪያለሽ? ከእንጦጦ ስለሰጠሸኝ እጅግ በጣም አመሰግናለሁ፡፡
ምን ይማሩ? ቤተልሄም፡ እኔም እዚህ ድረስ መጥታችሁ
ስላደራችሁልኝ ቃለ መጠይቅ እጅግ በጣም
ቤተልሄም፡ ማህበራዊ ሀላፊነትን የተመለከተው አመሰግናለሁ፡፡
ጉዳይ እኔ በበኩሌ ሙሉ ቃለ መጠይቁ ቢሆን
እንኳን ደስ የሚለኝ ጉዳይ ነው፡፡ በስነ-ምግባር እና

18 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
JOIN OUR TELEGRAM CHANNEL CLICK HERE

እኩል አይበርደንም
በሰይፈ ተማም

የአየሩ ጠባይ ብርድ ቢሆን ጭጋግ


ዝናብ ቢሆን ንፋስ የደመና ጭፍግግ
ሰው ነኝ የሚለው ህዝብ ለኑሮ ሲመረግ
ምን ቁሩ ቢጠና አንጀት ቢያላውስም
በአንድ አየር እያለን እኩል ግን አይበርድም
JOIN OUR TELEGRAM CHANNEL CLICK HERE

በአንድ ጥላ ገብተን እኩል አይጠልልም


አንድ ያልሆን አንድ ነን እኩል የተሰጠን እኩል አይ ደርሰንም
ገሚሱ በተስፋ ፀሐይ ይጠብቃል
ገሚሱ በምሬት በብርዱ ተቃጥሏል
ገሚሱ ብርዱም ላይ ውዱም ላይ ደርቧል
ባጋደለች ኑሮ በተንቋረረ አየር በጨፈገ ሰማይ
ባልገጠመ ዞሮ በጨቀየ አፈር በጠቆረ አተያይ
የሚያነጥስ እንጂ የታል ይማርህ ባይ

ጀምበሯም አልወጣች አሁንም ብርድ ነው


ጀላቲ ነው እንዴ መስከረም የጠባው
መስኩም አደይ የለው ልቤም እንደራደ
የብቻዬ ክረምት መች ተገባደደ
እትት በረደኝ በብርዱ ተቀጣሁ
የሚይዘኝ ሞልቶ የሚያቅፈኝ እጅ አጣሁ
እንዲህ ስንዘፈዘፍ የሞቀው ሰው ባይም
(አለፍኩት እያልኩኝ)
በአንድ አየር እያለን እኩል ግን አይበርድም
በምንተፋ ኑሮ ሁሉም በሆነበት እራሱን ዘራፊ
መሃል ተሰይሞ ላለ ተንሳፋፊ
በጁም በእግሩ ሮጦ ካልተንቀሳቀሰ
እንዴት ይሞቀዋል ብርድ እየለበሰ

ደሞ ፀሐይ መጥታ ሙቀት ሲሆን ሃሩር


ንዳድ ሲሆን ወበቅ የቀትር ላይ ጥሩር
ሰው ነኝ የሚለው ህዝብ ለኑሮ ሲነጠር
ምን ሙቁ ቢከርር አናትን ቢያፈርስም
በአንድ አየር እያለን እኩል ግን አይበርድም
በአንድ ጥላ ገብተን እኩል አይጠልልም
አንድ ያልሆን አንድ ነን እኩል የተሰጠን እኩል አይደርሰንም
አረንጓዴ

ያልተቃኘ ድምፅ
ብርሀኑ

የአለም የጤና ድርጅተ 466 ሚሊየን ሰዎች የመስማት ፡ መርፍ ወድቃ ከምታሰማው እስከ መድፍ ተኩስ ድምፅ
ችግር እንዳለባቸው ገልጿል፡፡ እንዲሁም በአውሮፓውያኑ ድረስ የራሱ የሆነ የራሱ የሆነ ልኬት አለው፡፡ ይህም ልኬት
አቆጣጠር በ2050 የመስማት ችግር ያለባቸው ሰዎች ቁጥር ዴሲብል በመባል ይታወቃል፡፡ ጆሮ የተመጠነ የድምፅ
በእጥፍ ሊጨምር እንደሚችል ተገልጿል፡፡ መጠን ከ90 ዴሲብል ያነሰ እንደሆነ ይታመና፡፡ ማንኛውም
በአለማችን ብሎም በሀገራችን የመስማት ቀን ተበሎ ሰው በንግግር ወቅት ድምፁ 60 ዴሲብል የሚያክል
ይከበራ፡፡ ይሁን እንጂ የመስማት ቀንን ከማክበር በዘለለ ጥንካሬ አለው፡፡ አንዳንድ ድምፆች 120 ዴሲብል ሲደርስ
የምንሰማውን ድምፅ ለጆሯችን መጥነን ስንጠው ጆሮን ያሳምማል፡፡
አይስተዋልም፡፡ ተፈጥሮ መርቃ የሰጠችውን የመስማት በአካባቢያችን ከተለመዱ ድምፆች መካከል
ችሎን እድሜ እየገፋ ሲሄድ እየተዳከመ መሄዱ የማይቀር የተወሰኑት ልኬታቸው እንደሚከተለው ነው፡፡
ሀቅ ነው፡፡ አብዛኛውን ግዜ ሰዎች የመስማት ችሎታቸውን
የሚያጡት በእርጅና ምክንያት ብቻ ሳይሆን ጫጫታ • የባቡር እንቅስቃሴ - 100 ዴሲብል
የሚባባቸው ስራዎች ፣ ከፍተኛ ድምፅ የሚሰማባቸው • የመኪናዎች እንቅስቃሴ - 80 ዴሲብል
ስፍራዎች የሚያስከትሉት ጉዳት አንድ ላይ ሲደመር • የኤሌክትሪክ መጋዝ - 110 ዴሲብል
የመስማት ችሎታ ያዳክማል፡፡ ታድያ ዛሬ በሀገራችን ፣ • አውሮፕላን ሰያልፍ - 120 ዴሲብል
በአካባቢያችን ፣በቤታችን ያሉ ተንቀሳቃሽ ስልኮቻችን • የጠመንጃ ድምፅ - 140 ዴሲብል
የሚያሰሟቸው ድምፆች ተመጥነው ይሆን?
ጎዳናዎች ከሚርመሰመሱ መኪናዎች ፣ አውቶቡሶች አዘውትረን ከማንሰማቸው ድምፆች ደግሞ
እና ከባድ የጭነት መኪናዎቸ እንዲሁም በስራ ቦታዎች • ስንተነፍስ - 10 ዴሲብል
ከሚገኙ መሳርያዎች የሚወጡ ከፍተኛ ድምፆች ጎዳናችን • ስናሾካሹክ - 20 ዴሲብል
ሲበጠበጥ ይውላል፡፡ ማኛውም ድምፅ የራሱ ልኬት አለው፡ • ንግግር - 60 ዴሲብል

20 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
አረንጓዴ

ለመሆኑ ድምፅን እንዴት እንሰማለን? ስለሚችል ሊድን የማይችል የጆሮ ጉዳተ ያደርሳል፡፡ እነዚህ
ህብረ ህዋሳት አንድ ግዙ ከተጎዱ እንደገና ሊድኑ አይችሉም፡
ጆሮ የውጨኛው ፣ የመካከለኛው እና የውስጠኛው ፡ በዚህ ምክንያት የጆሮ መጮህ ችግር ሊያጋጥም ይችላል፡፡
ተብለው የሚጠሩ ሶስት ክፍሎች አሉት፡፡ ውጫዊው የመስማት ችሎታን ማራዘም
የጆሮ ክፍል በአይን የሚታየው ሲሆን ወደ ጆሮ ታምቡር ሰዎች በፈጥሮ የሚያገኙት የመስማት ክህሎት አንድ ግዜ
የሚገባውን ድምፅ የሚመጥን በመሆኑ መጣ ገባ እና ብቻ በመሆኑ ከተጎዳ ወደ መጀመርያው መመለስ በጣም
ጠመዝማዛ ቅርፅ ይዞ ተፈጥሯል፡፡ በውጫዊ የጆሮ ክፍል አስቸጋሪ ስለሆነ በየግዜው የጆሮዎቻቸውን ጤንነት
የገባው የተመጠነው ድምፅ ደግሞ በመካከለኛው የጆሮ መከታተል ግድ ይላቸዋል፡፡ ስለዚህ የመስማት ክህሎት
ክፍል ውስጥ ይስተናገዳል፡፡ በመካከለኛው የጆሮ ክፍል እድሜ ለማራዘም የሚከተሉትን ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡
ውስጥ ሶስት ጥቃቅን አጥንቶች ይኖራሉ፡፡ እነዚህ አጥንቶች • የምናዳምጠው ሙዚቃ በኢርሴት ከሆነ የድምፁን
ከውጫዊ የጆሮ ክፍል የገቡ የጆሮ ድምፆች የጆሮ ታምቡር መጠን መቀነስ እ በዙያችን ያለውን ድምፅ መስማት
ንዝረት እንዲፈጥር ያደርጉታል፡ በውስጠናው የጆሮ ክፍል በሚያስችለን መልክ ዝቅ ማድረግ
የሚገኙ ጥቃቅን ፀጉሮች ከድምፅ ሞገዱ ጋር በሚፈጥሩት • ጫጫታ በበዛበት አካባቢ የድመምፅ መከላከያ
ግንኙነት መገዶቹ ወደ ፈሳሽ መልክ አስተላላፊነት ማድረግ
ይቀየራሉ፡፡ በዚህ አማካኝነት ጥቃቅን ፀጉሮች በፈሳሽ • ከፍተኛ የድምፅ ሞገዶች የሚበዙበት ስፍራን
የድምፅ ነርቮች ተሸካነት መልዕክቱን ወደ አንጎል ይልኩና አለማዘወተር
ድምፅ ሆነው ይሰማሉ፡፡ • ጆሮዎች በጆሮ ማፅጃዎች ማፅዳት
ከፍተኛ ድምፅ (በካይ ድምፅ) በውጫዊው ጆሮ • አካባቢ የሚረብሹ ነገሮችን ማወቅ
በኩል ሳይመጠኑ የገቡት ሣይመጠኑ የገቡት ድምፆች • ለማህበረሰቡ በቂ እውቀት መስጠት
በውስጠኛው የጀሮ ክፍል ላይ በሚገኙ በቀለሉ ሊጎዱ የሚሉ ከሁሉም በላይ በየመንገዳችን የመኪናዎች ድምፅ የሚበዛ
ፀጉር መሰል ህዋሳት ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ከፍተኛ ነው፡ በመሆኑ አሽከርካሪዎች ያለ በዚ ምክንያት የመኪናውን
፡ በድንገት የሚባርቅ ድምፅ የውስጠኛውን ጆሮ ህብረ ጥሩንባ እንዲያሰሙ የተቻለንን ማድረግ ከጆሮዎች ዋስትና
ህዋሰትን ሊደን እና ሊድን የማይችል ጠባሳ ሊያስቀር ከፍተኛ ነው፡፡

21 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
የኛ

ኢትዮጵያዊው ልዑል በባዕድ ሀገር


ቤተልሄም አምባቸው

በ1860 ዓ.ም አፄ ቴዎድሮስ ከእንግሊዞች ጋር ባደረጉት አቀላጥፎ መናገሩ ነበር፡፡ በተጨማሪም አለቃ ዝርዓት እና
ጦርነት ልጃቸው ልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ ወደ እንግሊዝ አቶ ገብረመድህን የተባሉ ሁለት ኢትዮጵዊያን ሞዚቶች እና
ሀገር ተወስዶ ነበር፡፡ በዛሬው የኛ አምዳችንም የዚህን ልዑል አጫዋቾች¬ ተመረጡለት፡፡
ባዕድ ሀገር ኑሮ ልናስቃኛችሁ ወደድን፡፡ አለማየሁ ከጠባቂው ስፒዲ ጋር ፌሬዝ በተባለችው መርከብ
ልዑል አለማየሁ ሚያዚያ 5 ቀን 1853 ዓ.ም በደብተረ ተሳፍሮ በ1860 ዓ.ም. ወደ እንግሊዝ አቀና፡፡ በመርከቢቱ
ታቦር ከተማ ነበር ውልደቱ፡፡ በልዑሉ ውልደት የተደሰቱት ላይ በነበራቸውም ቆይታ ስፒዲ እና አለማሁ እጅግ የጠበቀ
አፄ ቴዎድሮስም በእለቱ መድፍ ያስተኮሱ ሲሆን 500 ወዳጅነትን መስርተው ነበር፡፡ ስፒዲ በሄደበት ቦታ ሁሉ
ያህል እስረኞችንም ፈትተዋል፡፡ ከልዑሉ ጋር ሲጫወቱ አለማየሁን ማስከተል ያዘወትር ነበር፡፡ ይህንን የሁለቱን
መዋል አፄውን እጅግ የሚያስደስት ነገር ነበር፡፡ ተናደው እና ፍቅር ያየው ጀነራል ናፒየርም ኢትዮጵያውያን ሞግዚቶቹ
ተበሳጭተው ከነበር እንኳን አለማየሁን ታቅፈው ሲስሙ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ይልቁንም የአለማየሁን
ንዴታቸው ይበርድ ነበር ይባላል፡፡ ሀላፊነት ሙሉ በሙሉ ካፕቴን ስፒዲ እንዲረከብ ስለወሰነ
ልዑል አለማየሁ እንግሊዞች እጅ ከገባ ቡሀላ ከእድሜው ሁለቱ ሞግዚቶች ጉዞው ተጠናቆ እንግሊዝ ሀገር ሳይደርሱ
ለጋነት የተነሳ የሚጠብቀው እና የሚንከባከበው ሰው ከስዊዝ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ተደረገ፡፡ ምንም
ሊኖር ግድ ነበር፡፡ ይህንን የተረዳው ጀነራል ናፔር ካፕቴን እንኳን የእንግሊዛውያኑ የታሪክ ድርሳናት ይህንን ቢሉም
ስፒዲ የተባለን ሰው የአለማየሁ ጠባቂ እንዲሆን መደበው፡ ልዑሉ ኢትዮጵያውያን ሞግዚቶቹን በተባለው መጠን
፡ ምክንያቱ ደግሞ ካፕቴኑ የአማርኛ ቋንቋን አምርሮ ይጠላቸው እና ባያቸውም ቁጥር በብስጭት
22 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
የኛ

ያለቅስ እንደነበር ማረጋገጫ የለንም፡፡ ከተማ አዛዥ ሆኖ ስለተሾመ የ8 ዓመቱን አለማየሁን እና


ከሶስት ወራት የመክረብ ላይ ጉዞ በኃላ አለማየሁ እንግሊዝ ሚስቱን ይዞ ወደዛው አቀና፡፡ በሄዱበት ሀገርም አለማየሁ
ሀገር ደረሰ፡፡ እዛ አንደደረሰም የወቅቱ የእንግሊዝ ንግስት ትምህርቱን መከታተሉን ቀጥሎ የነበረ ሲሆን ከመደበኛው
ከነበረችው ንግስት ቪክቶሪያ ጋር ተገናኘ፡፡ ንግስቲቱም ትምህርት በዘለለም ፈረስ ግልቢያ እና ሌሎች ስፖርቶችንም
ልዑሉ የፈለገው እና ያሻው ይደረግለት ዘንድ ቀጭን ያዘወትር ነበር፡፡
ትዕዛዝ አስተላለፈች፡፡ ልዑሉ በመቀደላ የነበረውን ልዑሉ በዚህ አይነት ከቆየ በኃላ ቻንስለር ሮበርት ሉዊ ልዑሉ
እልቂት በመጠኑም ቢሆን በማየቱ እና የአባቱ እና የእናቱ የቀለም ትምህርት ላይ ከሚያዘወትር ይልቅ የወታደር
ተከታታይ ሞትም በልጅ አዕምሮው ሊቀበለው ከሚችው ትምህርት ቤት ገብቶ የፈረስ ውትድርናን እንዲማር
በላይ ስለነበር እጅግ ታውኮ እንደነበር በተደጋጋሚ ተፅፎ መደረግ አለበት ሲሉ ያቀረቡት ሀሳብ የልዑሉን ህይወት
እናገኛለን፡፡ አንድ እንግሊዝ ሀገር ውስጥ በሚገኝ ሙዚየም እስከወዲያኛው የለወጠ ነበር፡፡ ይህም ሀሳብ ተቀባይነትን
ውስጥ ባለ የንግስት ቪክቶሪያ የእለት ማስወሻ ላይም ስላገኘ አለማየሁን ከስፒዲ ነጥሎ በመንግስት ቁጥጥር
ንግስቲቱ፡ “ምስኪኑ ልጅ አሁንም ፍርሀቱ አለቀቀውም፡፡ ስር ለማድረግ እና የውትድርና ትምህርቱን እንዲከታተል
መቅደላ የነበረው እልቂት እና የአባቱን ሞት ስላየ ያ ነገር ተወሰነ፡፡ ይህ ውሳኔ ግን ለአለማየሁም ሆነ ለስፒዲ ከባድ
በአዕምሮው ይመጣበታል፡፡ “ የሚል ቃል ፅፋ እናገኛለን፡፡ ግዜ ነበር፡፡ ስፒዲ እና ሚስቱ አለማየሁን ላለመስጠት
ልዑሉ እንግሊዝ ሀገር ከደረሰ በኃላ ጠባቂው የነበረው ከባድ ትግልን አደረጉ፡፡ ነገር ግን ትግላቸው ውጤትን
ካፕቴን ስፒዲ የእንግሊዘኛ ቋንቋን ያስተምረው ጀመር፡ አላስገኘላቸውም፡፡ ይልቁኑም አለማየሁ ወደ እንግሊዝ
፡ ንግስቲቱም የልዑሉን ሁኔታ በቅርበት ትከታተል ነበር፡፡ ሀገር እንዲመለስ ተወሰነ፡፡
ስፒዲ ልጁን እንዳይጎዳው በማሰብም በስፒዲ ላይ የልዑሉን ስፒዲም አለማየሁን ይዞ ወደ እንግሊዝ መጣ፡፡ የአለማየሁ
ጉዳይ በቅርበት የሚከታተል ተቆጣጣሪ አስቀምጠውበት አዲሱ አስተማሪ እና ጠባቂ እንዲሁኑ የተመረጡትም
ነበር ይባላል፡፡ በአስተማሪነታቸው የተመሰከረላቸው እና በደግነታቸው
አንድ ግዜ ንግስት ቪክቶሪያ ስለ ልዑሉ በእለት ውሎ የታወቁት ቄስ ብሌክ ነበሩ፡፡ ንግስት ቪክቶሪያም
መመዝገቢያዋ ላይ ከመዘገበችው መሀል “ልጁ ጨዋ የአለማየሁን እና የስፒዲን ፍቅር ያውቁ ስለነበር ሁለቱን
እና ውብ ልጅ ነው፡፡ ኬክ መብላት ደግሞ ይወዳል፡ ቶሎ መነጣጠል አልፈለጉም፡፡ ይልቁኑም አለማየሁ ከቄስ
፡ የሰጠሁትንም ኬክ ሁሉ ጨርሶ በላ፡፡” የሚል አረፍተ ብሌክ ጋር እስኪላመድ ድረስ ስፒዲ አብሮት ይቆይ ስትል
ነገር ተፅፎ እናገኛለን፡፡ ንግስቲቱ በተደጋጋሚ ለዚህ እናት ፈቀደች፡፡
ለሌለው ልጅ እናቱ እኔ ነኝ ስትል ትደመጣለች፡፡ ለልዑሉም አዲሶቹ የአለማየሁ ጠባቂዎች አለማየሁ ስራ እንዲሰራ
የተለየ አክብሮት እና ፍቅር ፤ ልዩ ትኩረትም እንደነበራት ወሰኑ፡፡ በወጣለትም ፈረቃ መሰረት በሳምንት ለ 31 ሰዓት
ድርሳናት ዘግበውታል፡፡ ተኩል ያህል ማንኛውንም አይነት ስራ እንዲሰራ ተወሰነ፡
ምንም እንኳን ከንግስቲቱ ጋር የነበራቸው ወዳጅነት ፡ የስፒዲ ሚስትም ይህንን በመቃወም ጠባቂው ለነበሩት
ከግዜ ወደ ግዜ እየበረታ ቢመጣም ከሀገሩ ሲወጣ አብሮት በቢዶልፍ ደብዳቤ ላከች፡፡ ቢዶልፍም ለሉዊ አለማየሁ
የነበረውን ካፕቴን ስፒዲን ግን ለአፍታም አልዘነጋውም አንዳንድ ግዜ እየሄደ ከስፒዲ ሚስት ጋር ግዜ እንዲያሳልፍ
ነበር፡፡ በየትኘውም ስፍራ ሲሄድ ስፒዲ አብሮት እንዲሆን ሲሉ ትዕዛዝ አስተላለፉ፡፡ በትዕዛዙም መሰረት የስፒዲ
ይፈልጋል፡፡ ግብዣም ሲሄድ ሆነ ከልዑላን ልጆች ጋር ሚስት ከአለማየሁ ጋር እንድትውል ተፈቀደላት፡፡ ሚስቱም
እንዲጫወት ሲጋበዝ ስፒዲን ትቶ መሄድ አይሆንለትም፡ አብራ ውላ ያየችውን እንዲህ ስትል በደብዳቤ ገልጣለች፡
፡ ቤተ-መንግስት ሲገባ እንኳን ስፒዲን አስከትሎ ነው፡፡ “ማደጉን ቁመቱ አድጓል፡፡ መልኩ ግን ገርጥቷል፡፡ አካላቱም
ስፒዲ እና አለማየሁ አብረው ይበላሉ አብረውም ደግሞ ከስቷል፡፡ ዝምተኛ እና ጭምትም ሆኗል፡፡ ከወንዶች ልጆች
ይተኛሉ፡፡ አለማየሁን ለብቻው ማሳደግ የከበደው ስፒዲ ጋር እንዳይገናኝ እና ከእኩዮቹም ጋር እንዳይገናኝ ተደርጓል፡
ልጁን በማሳደግ ትረዳው ዘንድ ሚስት ለማግባት ወሰነ፡፡ ፡ ውጪ እየወጣም እንዳይዘል ታግዷል፡፡ እየደጋገመም
ከዛም ወ/ሮ ኮታንን አገኘ እና አገባት፡፡ አለማየሁ እና ወ/ሮ ‘አብረውኝ የሚጫወቱ ልጆች አጣሁ፡፡ ቅዳሜ እና እሁድ
ኮታንም ለመዋደድ ግዜ አልወሰደባቸውም ነበር፡፡ ብቻ ከሁለት ልጆች ጋር አንድጫወት ይፈቀድልኛል፡፡
በ1861 ዓ.ም ስፒዲ ህንድ ሀገር በምትገኝ አንዲት ሊያጫውቱኝ የሚመጡትም እነዚህ ልጆች ሁልግዜ እነሱ
23 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
የኛ

ብቻ በመሆናቸው ተሰላችተናል፡፡ በሌላ ቀን ግን የሌሎች አመት ሚስተር ድራፐር ቤት እንዲኖር ተደረገ፡፡ ቄስ


ልጆችን እጅ አንኳን ጨብጬ አላውቅም’ ብሎኛል፡ ብሌክም ካዩት የልዑሉ ባህሪ በመነሳት ልዑሉ ወታደርነት
፡ ይህንን የመሰሉት ነገሮች ያበሳጩታል፡፡ እኔም ብሆን ላይ ቢያተኩር የበለጠ ውጤታማ እንደሚሆን ተናገሩ፡፡
ይህን የሚበሳጭበትን ጉዳይ ለማስተው ጓደኛ ልፈጥርለት በዚህም ንግግር መሰረት የወታደር ትምህርት ቤት እንዲገባ
አልቻልኩም፡፡ እየደጋገመ የነገረኝም ‘ወንዶች ልጆች ተደረገ፡፡
እፈልጋለሁ፡፡ የበለጠ እንድንዛመድም እፈልጋለሁ’ እያለ በአንድ ወቅት አለማየሁ ወደ ሊድስ በመሄድ በሰር ራምሰን
ነው፡፡ በምግብ አበላሉ በኩልስ እንዴት ነህ ብዬ ብጠይቀው ቤት ተቀምጦ በነበረበት ወቅት ታመመ፡፡ ምንም አይነት
‘ምግብ አሁን አይበላልኝም፡፡ ምክንያቱም ውጪ ወጥቼ ህክምና ቢደረግለትም ህመሙ እየጠናበት ሄደ፡፡ በሽታውም
ስለማልዛለል እና ስለማልጫወት አይርበኝም፡፡ የምበላው ምግብ እንዳይበላ ብሎም መድሀኒት እንዳይወስድም
በትንሹ ነው’ ብሎ መለሰልኝ፡፡ እኔ እንደማስበው አለማየሁ ከለከለው፡፡ ታዋቂ የነበሩ ሀኪሞችም ተመድበውለት
ደስተኛ እና በሚደረግለት የረካ ልጅ አይደለም፡፡” ነበር፡፡ የበሽታው ፅናት ግን አለማየሁን ህዳር 5 ቀን 1872
የስፒዲ ሚስት የፃፈችው ይህ ደብዳቤ ከንግስት ቪክቶሪያ ዓ.ም ከጠዋቱ በ3 ሰዓት ከሩብ በተወለደ በ19 ዓመቱ
ዘንድ ደረሰ፡፡ ንግስቲቱም ትንሹ ልዑል አብሮአቸው ከዚህ አለም እንዲሰናት አደረገው፡፡ አስከሬኑም ዊንድሶር
ሊጫወት የሚችሉ ጓደኞች እንዲፈለጉለት አዘዘች፡፡ ባለው የነገስታት መቀበርያ በክብር አረፈ፡፡ በመቃብሩም
እንደተባለውም ተደረገ፡፡ ላይ “የሀበሻው ልዑል አለማየሁ” የሚል ፅሁፍ ሰፍሮበት
1867 ዓ.ም አለማየሁ ወደ ራግቢ ትምህርት ቤት ተዛወረ፡ እስካሁን በእንግሊዝ ሀገር ይገኛል፡፡
፡ በዚህም ከቄስ ብሌክ ቤት ወጥቶ ወደ ሊው ዋርነር ቤት ምንጭ፡ ጳውሎስ ኞኖ ፤ አጤ ቴዎድሮስ
እንዲገባ ተደረገ፡፡ በዚህ ግን ደስተኛ ስላልነበር በቀጣዩ

24

መ ል ካ ም7 4 |
ፌብሩወሪ 1,2019

እኛ አቢሲኒያዎች ነን !
የጥንት ስልጣኔ ባለቤት ፣ ሀገራችንን በፊት ወደንነበረችበት ሀያልነት ፣ አንድነት
24
፣ መ ል ካሆና
ተወዳጅነት እና ተሰሚነት ለመመለስ እንሰራለን ። ሀገራችን ከፊት
24 መ ል ካ ም7
4 | ፌብሩወሪ
ም7ሳናያት
4 | ፌብ ሩዋሪ
1,2019
1,2019
አንተኛም ። ማንኛውም ሀገሩን ለመቀየር የተነሳ ግለሰብም ሆነ ድርጅት የኛን ራእይ
መጋራት ይችላል ።
እናመሰግናለን!
ቻናሉን ለመጎብኘት እዚህ ይጫኑ
24
24 ም744| ሜ
መልልካካም7
መ | ማ
ይር 1ች, 210, 21 09 1 9
በልዑል ሀይሌ
ፓንዲ
ክፍል ፩
“ዛሬ የምንማማረው ስለ ኢትዮጵያ ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ ነው” ይላል አጠር ያለው መላጣ ጂኦግራፊ አስተማሪያችን
“ዛሬ የምማረው ስለ ፓንዶራ ጥልቅ ዓይኖችና የሰውነት አቀማመጥ ነው”(እኔ) አቤት ፓንድዬንኮ ስወዳት ለጉድ ነው፡፡
ይኸው ስለምወዳትምኮ ነው ሁሉም የክፍላችን ተማሪዎች(እሷን ጨምሮ) ስለ ኢትዮጵያ ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ
ሲማሩ እኔ ስለ እሷ አቀማመጥ በተመስጦ የምማረው…
“ኢትዮጵያ የምትገኘው በምስራቃዊው የአፍሪካ ቀንድ ሲሆን በሰሜን ኤርትራ ፤ በምስራቅ ጅቡቲና ሶማሊያ ፤ በምዕራብ
ሱዳን፤ በደቡብ ደሞ ኬንያ ያዋስኗታል” (አጭሩ ጂኦግራፊ አስተማሪያችን) “ፓንዶራ የምትገኘው በክፍላችን ሁለተኛው
መደዳ አራተኛው ወንበር ነው፡፡ ከፊት እነ ጀሚላና ቶማስ፤ ከኋላ እነ ሳምሶንና ትዕግስት፤ በግራዋ
በኩል ከድር በቀኟ ደሞ እኔ አፍቃሪዋ እናዋስናታለን” (እኔ) የሌሎቹን ባላውቅም እኔ ግን የሷ አዋሳኝ በመሆኔ ትልቅ ኩራት
ይሰማኛል፡፡ በርግጥ አንድም ቀን እንደምወዳት ነግሬያት ወይም በሰፊው አጫውቻት ባላውቅም እንደዚሁ ሳያት መዋሉ
በራሱ በደስታ
ያንሳፍፈኛል፡፡ ከፓንዲ ጋር እንድቀመጥ የረዳኝ ይሄ ደግሞ ጂኦግራፊ አስተማሪያችን ስለሆነ ውለታውን ለመመለስ
በሚል የኔን የፍቅር ውሎ
ከሱ ትምህርት ጋር እያዛመድኩኝ ቀኑን ሙሉ አሰላስላለሁ፡፡ በዚህም ጂኦግራፊ ትምህርቴን ሁሌም እንደደፈንኩኝ ነው፡
፡ምክንያቱም ሳጠና ከፓንዲ ጋር እያዛመድኩኝ ስለሆነ መቼም አልረሳውም….እንዴት ብዬ?….ጂኦግራፊን ከፓንዲ ጋር
አዛምጄ ….ፓንዲ እንዴት ትረሳለች?..ኧረ በጭራሽ!! ፓንዲን እርሳት ከምትሉኝ ራስህን እርሳ ብትሉኝ ይቀለኛል፡፡
ለነገሩ ራሴንማ ከረሳሁት ቆየሁኝ…..ምግብ ዘግቶኝ እኛ ቤት ያለወትሮው እንጀራ መሻገት ጀምሯል፡፡ (እኔ ነበር
የማወድመው ለካ!) ልብስም ከሰፈራችን አንደኛ ለባሽ የነበርኩት ልጅ አሁን ግን ከዩኒፎርሜ ውጪ ምንም አይነት ልብስ
መልበስ አስጠልቶኛል፡፡ ምክንያቱም ፓንዲን ያገናኘኝ ይሄ ዩኒፎርም ስለሆነ አልቀይረውም፡፡ ፓንዲን
ልቀይራት?!..አይደረግም!! …..ደሞም ልብስ ሆኖ የሚያሞቀኝ ምትሃታዊ ፍቅሯ ወዴት ሄዶ?!....ደብተሮቼን እንዳለ
ብታዩዋቸው በተወጉ የልብ ቅርፆች ያሸበረቁ ናቸው፡፡ ሁሉም አስተማሪዎቻችን የየራሳቸውን ትምህርት በፅሁፍ
ሲያስገለብጡን ‘P’ የሚለውን ፊደል በተለየ ውበት ተለቅ አድርጌ
በጥንቃቄ ነው የምፅፈው….ብቻ ምን ልበላችሁ እንቅስቃሴዬ ሁሉ በፓንዶራ ዙሪያ ነው፡፡…….በዚህ ሃሳብ መሀል
እያለሁ የሆነ ነገር ሲነካኝ ተሰማኝና ብንን አልኩኝ(ጂኦግራፊ አስተማሪያችን ነበር ተጣርቶ አልሰማ ስለው በቾክ ወርውሮ
ከገባሁበት ጣፋጭ ህልም የቀሰቀሰኝ)
“በል እንጂ መልስ!!”…..በድንጋጤ የማደርገው ነገር ሲጠፋኝ የክላሳችን ተማሪዎች በሙሉ ሳቁብኝ…..ድዳቸው ለሙቅ…..
ለነገሩ እነዚህ ሙቅም ሙድም አይገባቸውም……ግልፍጥ ሁላ ጥርሱን
መክፈቻ ያድርገኝ?…. “አንተንኮ ነው!!... በዓለም በቆዳ ስፋት ትንሿ ሃገር ማናት?”
ሲለኝ ወዲያው በድንጋጤ ከአፌ የመጣልኝ የምወደው ቃል አሟለጨኝ
25 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
“ፓንዶራ!....” አልኩና የክላሱ ተማሪ ሲያፈጥብኝ “ፓንዶራ የምትባል ሃገር” ስል መምህሩ የሹፈት ሳቅ ሳቀና “ፓንዶራ
የት ነው የምትገኘው? …” ሲለኝ ካጠገቤ ልለው አሰብኩኝና መልሼ ዋጥኩት “እዚህ (በአፌ ወደ ፓንዶራ አቅጣጫ
እያመለከትኩኝ) ምዕራብ አፍሪካ” ስል መምህሩ በንዴት በሱ ክላስ እንዳልገባ አስጠንቅቆ ወደ ውጪ አስወጣኝ፡፡ ቆይቼ
ስሰማ ፓንዶራ ሳይሆን አንዶራ የምትባል ሃገር አውሮፓ ውስጥ እንደምትገኝ አወቅኩኝ፡፡እኔ ታዲያ መች አወቅኩኝ
የኔዋ ፓንዲን እንጂ ሀገሪቷን ከየት አመጣታለሁ ምን አይነት ክፉ አጋጣሚ ነው? …… ከፓንዲ ጋር ያቆራኘሁት ጂኦግራፊ
አለመማር ማለት ወፌ ላላ ተሰቅሎ 400 ጅራፍ መገረፍ ማለት ነው፡፡ ….ለነገሩ ፓንዲ እንደሆነች ሁሌም
ከጎኔ አለች ስለዚህ ከሌላ ትምህርት ጋር ለምን አላቆራኛትም አልኩና ከባይሎጂ ትምህርት ጋር ማቆራኘት ጀመርኩኝ…
ቻው ቻው ጂኦግራፊ!!....አንተ መላጣ አስተማሪ ምን ይዋጥህ?…ምንም!!..ባይሎጂ አስተማሪያችን እንደ ጂኦግራፊ
አስተማሪያችን መላጣ አይደለም፡፡ ደስ ሲል!!... ሴት ነች ፀጉሯ ወርዶ ወርዶ ሲቆጨው መሰለኝ ተመልሶ ወጥቶ ከጆሮዋ
በላይ ተሰንቅሯል፡፡
መምህርታችን ጋዋኗን አውልቃው አታውቅም …እስከዛሬ በሌላ ልብስ
አይቻት አላውቅም፡፡ ወይ ማን ያውቃል እንደኔ ጋሽ ፎንቃ ሰፍሮባት ይሆናላ!!....በኔም ስለደረሰ አልፈርድባትም ታፍቅር…..
ብቻ ግን ያንን
የፓንዲን ስም ያቀለለውን ጂኦግራፊ አስተማሪያችንን አፍቅራ እንዳይሆንና ፊልድ እንዳልቀይር!!...ለነገሩ ምኑ
ይፈቀራል!...በቴሌስኮፕ ካላየችው
ለዓይኗም አይሞላ!!....ቴሌስኮፕ ደሞ እኛ ትምህርት ቤት የለም ደስ ሲል!!...ምን ይዋጥህ ጂኦግራፊ አስተማሪያችን
….ምንም!..... “ዛሬ የምንማማረው ስለ ሴክሹዋል ሪፕሮዳክሽን” ስትል ‘ቱ! ቲቸር ምን አይነት ባለጌ ነች?’ እያሉ በሳቅ
በመጎሻሸም በእፍረት ያዩዋታል
ከፊታችን የተቀመጡት እነ ቶማስ… .ግማሹ የክላሱ ተማሪዎች ደሞ
በጉጉት ሲጠብቁት የነበረው ምዕራፍ በመድረሱ ዓይናቸው ተጎልጉሎ ሊወጣ ምንም አልቀረውም “ሴክሹዋል ሪፕሮዳክሽን
ማለት ዘርን ለመቀጠል ስለሚረዱ የመራቢያ አካላት የሚያጠና ነው፡፡ ለምሳሌ በሰው ልጅ ስናየው ሴቷም ወንዱም
የየራሳቸው የመራቢያ አካላት አሏቸው፡፡ እስቲ ከወንዱ የመራቢያ አካል እንጀምር!!...” ስትል ክፍላችን በተቃውሞ
ሹክሹክታ ታመሰ “ምንድነው ሚያንሾካሹካችሁ?” ….የክፍላችን ደፋር ተናጋሪ ቢኒያም ተነስቶ ፀጉሩን እየጠቀለለ “አይ
ቲቸርዬ!..ማለት ቅድሚያ ለሴቶች በሚለው ህግ መሰረት ከሴቶች ቢጀመር አሪፍ ነው!!” ሲላት ባይሎጂ አስተማሪያችን
በንዴት “ና ውጣ!!..ከዚህ በኋላ በኔ ክላስ እንዳላይህ!...” ቢኒያም ከወጣ በኋላ ቀጠል አድርጋ “የወንድ የመራቢያ ክፍል
ዘር ሲያዘጋጅ ሴቷ ደሞ እንቁላሉን ታዘጋጃለች ማለት ነው፡፡….የወንዱ የመራቢያ አካል (ባይሎጂ መፅሀፍ ገለጥ ገለጥ
አደረገችና) ከፍ
አድርጋ ወደኛ አዙራ መለመላውን ስታሳየን ሴቶች በኩራት ሲሳለቁብን እኛ ወንዶች በመሸማቀቅ አጀብናት፡፡ “ለነገሩ
ፎቶ አስነስቶ ያዋረደንኮ በየሰፈሩ ቱቦ በጠራራ ፀሐይ የሚሸናው ወንድ ነው ምናለ ምች ባጣመመለት!!...መዘዝ አድርጎ
ሲያወጣውኮ ሻሞላ የመዘዘ ጀግና የሆነ ነው ሚመስለው” ይላል የክፍላችን ሰቃይ ተማሪ ከድር ከጎኔ
ስለሆነ ሹክሹክታውም ይሰማል፡፡
በዚህ ሁሉ ሁኔታ ውስጥ የክፍላችን አብዛኞቹ ሴቶች የኛን በማየታቸው
ተደስተው ይሁን ምን ይሁን ሲገለፍጡ ፓንዲ ግን ምንም እንዳልተፈጠረ ዝም ብላ ትከታተላለች….አይ ፓንዲ! ጨዋ!!
የጨዋ ልጅ!! የጨዋ የልጅ ልጅ ልጅ!!....ለዚህ እኮነው የምወዳት
ጨዋነቷ!...

(ይቀጥላል......)

26 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
ስራ ፈጠራ

ሀሜክ ዲዛይን
ቤተልሄም አምባቸው
ወጣት ሀይማኖት ሆነልኝ በትምህርቷ የማኔጅመንት ምሩቅ ዲዛይንን መሰረተች፡፡ ሀሜክ ማለት ሀይማኖት የሚለውን
ናት፡፡ የከፍተኛ ደረጃ ትምህርቷን ጨርሳ እንደወጣችም ስም በማቆላመጥ የተገኘ የቁልምጫ ጥሪ ነው፡፡
በተማረችበት የሙያ መስክ ለመስራት በማሰብ የስራውን ሀይማኖት ስራዋን ስትጀምር በጆሮ ጌጥ ምርቶች ብቻ ነበር፡
አለም ተቀላቅላ ነበር፡፡ ለሁለት ዓመታትም ያህል በተለያዩ ፡ የተለያዩ የአፍሪካ ጨርቆችን በመጠቀም በመጠናቸው
ድርጅቶች ውስጥ ሰርታለች፡፡ ነገር ግን የምትሰራው ስራ ገዘፍ ያሉ እና በቀለማቸው ደመቅ ያሉ ጆሮ ጌጦችን ትሰራ
የነፍሷ ጥሪ እንዳልነበር ለመረዳት ግዜ አልወሰደባትም፡፡ ነበር፡፡ ይህም ስራ የሀሜክ ዲዛይን መለያ ነው፡፡ በጊዜ
በድርጅቶች ውስጥ መስራትን እርግፍ አድርጋ ትታ በቤቷ ሂደትም የአንገት እና የእጅ ጌጦችን በመጨመር ስራዋን
ውስጥ በእጅ የተሰሩ የጆሮ ጌጦችን ማምረት ጀመረች፡፡ አሰፋች፡፡ በዚህ ብቻ ያልተገደበችው ወጣት ሀይማኖት
ይህንን ስራ ስትጀምር ምንም አይነት ትምህርትን ተምራ በአሁኑ ሰዓት የመብራት ጌጦችን ፣ እቃ ማስቀመጫ
ሳይሆን በግል ካላት ፍላጎት የተነሳ እና ለራሷ አየሰራች ሳጥኖችን ፣ የማስታወሻ ደብተሮችን እንዲሁም የሶፋ
ከምትጠቀምባቸው የጌጣጌጥ ስራዎች በቀሰመችው ልምድ ትራሶችን እነዚህኑ የአፍሪካ ህትመት ያለባቸውን ጨርቆች
ብቻ ነበር፡፡ የምትሰራቸውንም ስራዎች እያዩ የወደዱላት በመጠቀም ትሰራለች፡፡
ሰዎች በሚሰጧት መልካም አስተያየት የተነሳ ምርቷንም የሀሜክ ዲዛይን ምርቶች ሁሉ በእጅ የተሰሩ እና ምንም
ለመጠቀም የሚፈልጉ ሰዎች ቁጥራቸው እያየለ ሲመጣ አይነት ማሽን ያልነካቸው ናቸው፡፡ በውጪው አለም
ይህንን ስራ በንግድ መልክ ለመጀመር በማሰብ ሀሜክ ለእንደዚህ አይነት ምርቶች ከፍተኛ ቦታ እና አክብሮት

27 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
ስራ ፈጠራ

ሲሰጥ እናስተውላለን፡፡ በሀረጋችን ግን ያለው እውነታ የመሰማራትን ህልም ሰንቃለች፡፡ በቅርብ ግዜያት ማምረስ
ከዚህ የራቀ መሆኑ ስራውን ፈታኝ እንዳደረገባት ሀይማኖት ጀመረቻቸውን የሶፋ ትራሶች እማስ በማስፋት የቤት
ትናገራለች፡፡ በዚህም ያለመረዳት ችግር ምክንያት ውስጥ እና የቢሮ መገልገያ የእንጨት ውጤቶች ምርት
አብዛኞቹ የሀሜክ ዲዛይን ደንበኞች ኢትዮጵያ ውስጥ ላይ የመሰማራት እቅድ እንዳላት ሀይማኖት ነግናለች፡
የሚኖሩ የውጪ ሀገር ዜጎች እና በውጪው አለም በነዋሪነት ፡ በተጨማሪም ሀሜክ ዲዛይን ልብሶችን በማምረት
የሰነበቱ ኢትዮጵያውያን ብቻ እንዲሆኑ አድርጎታል፡፡ ነገር ለተጠቃሚ የማድረስ ህልምም አለው፡፡ ሁሉም ምርቶች
ግን ሌላውም ኢትዮጵያዊ በእጅ ለተሰሩ ምርቶች ያለውን ታድያ የሀሜክ መለያ የሆኑትን የደመቁ የአፍሪካ ጨርቆችን
ክብር ቢጨምር በዚህ ኢንደስትሪ ላይ ያሉ ወጣቶችን የሚጠቀሙ ይሆናሉ፡፡
በማበረታታት የኢንደስትሪውን አለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነት ለመሰል ስራ ፈጣሪ ወጣቶች ደግሞ ይህንን መልዕክት
መጨመር ይቻላል፡፡ አስለታልፋለች
ከንቃት በለለ ያለው ችግር የጥሬ እቃ አቅርቦት እንደሆነ “ማንኛውም ሰው መጀመርያ ማድግ የሚፈልገውን ነገር
ሀይማኖ አፅንኦት ሰጥታ እገልፃለች፡፡ የሀገራችን የገበያ ማወቅ አለበት፡፡ ራሱ ማድረግ የሚችለው እና የሚፈልገው
ሁኔታ ከሌላው አለም እጅግ የተገለለ ከመሆኑ እና ነው እንጂ ጓደኛ ያደረገውን አይደለም ማድረግ ያለበት፡፡
የኦንላይን ግብይትን ካለመፍቀዱ ጋር ተያይዞ ለስራዎቹ ይህንነ ካወቀ ውሳኔን ወስነ ወደ ስራ መግባት ይቻላል፡፡
ግብዓት የሚሆኑትን ምርቶች ለማግኘት እጅግ አሰልቺ በእርግጥ ቀላል አይሆንም ነገር ግን ሁሉንም ነገር በመሞክ
ረጅም ጉዞን መጓዝ ለወጣቷ የግድ ሆኖባታል፡፡ እቃዎቹ ነው እና የምናገኘው ከመሞከር ወደ ኃላ አንበል፡፡ ሌላው
ሲገኙ ደግሞ እቃዎቹን ለማኘት በሚደረገው ሂደት መሀል በስራ ፈጣሪ ወጣቶች ዙርያ ያሉ ሰዎች ያንን ሰው በደንብ
ዋጋቸው እጅግ እየናረ የተጠቃዎች ቁጥር መጨመር ላይ ሊደግፉት ይገባል፡፡ የሚሰራው ስራ ባይገባቸው እንኳን
ጋሬጣ ሆኗል፡፡ ሞራሉን ቢጠብቁ እላለሁ፡፡ መንግስትም ስራ ፈጠራ ላይ
ሆኖም ግን ዛሬም ወጣት ሀይማኖት እነዚህን የተዋቡ የራሱ ድርሻ ይኖረዋል፡፡ ሁኑታዎችን ከማመቻቸት ጀምሮ
የእጅ ስራ ውጤቶች በመስራት ለፈላጊው ማቅረቡን በዚህ ዙርያ ከፍተኛ ጥኩረት ሰጥቶ ሊሰራ ይገባል እላለሁ፡
ተያይዛዋለች፡፡ ወጣቷ ዛሬ ከምትሰራቸው መገልገያዎች ፡”
በዘለለ ለወደፊቱ ትልቅ እና ሰፊ በሆነው የኢንደስትሪ መስክ

28 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
ዘመንኛ
ዘመንኛ

በሞባይል ስልካችን ላይ ከሚፈጸም የመረጃ ጠለፋ (hacking)


እንዴት ጥንቃቄ ማድረግ ይቻላል?
ሚኪ ማክ

ዛሬ ዛሬ በሞባይል ስልካችን የምንፈጽማቸው ጉዳዮች ሰላምታ ከመለዋወጥ እና መልእክት ከመላላክ አልፈዋል:: ምስልና
ድምጽ ቀርጸን ከማስቀመጥ ጀምሮ የተለያዩ መተግበሪያዎችን (Mobile Applications) በመጠቀም ረቀቅ ያሉ
ተግባራትን በስልካችን ላይ መፈጸም የምችልበት ጊዜ ላይ ደርሰናል::ታዲያ የእነዚህ የሞባይል መተግበሪያዎች መጎልበትና
የአይነታቸውን መብዛት ያክል ይኸው የዲጂታሉ አለም አይነተ ብዙ ተግዳሮቶችንም ፈጥሮልናል:: ከእነዚህ ተግዳሮቶች
ውስጥ ታዲያ የመረጃ ጠላፊዎች (hackers)መፈጠር አንዱና ዋነኛው ነው::የመረጃ ጠለፋ ከፍቃዳችን ውጪ በስልካችን
ወይም ኮምፒውተራችን ላይ የሚደረግ የመረጃ ስርቆት ወይም ኮምፒውተር ነክ እቃዎቻችን በመጠቀም የሚደረግ
የዲጂታሉ አለም ስውር ስለላ ነው:: ለመሆኑ የሞባይል ስልካችን ለመረጃ ጠለፋ መጋለጡን አልያም በስልካችን አማካኝነት
ስለላ እየተካሄደብን እንደሆነ በምን ልናውቅ እንችላለን?

1 የስልካችን ፍጥነት ከወትሮው


በተለየ ዝግ ማለት ወይም 3 ከወትሮው በተለየ የስልካችን
ባትሪ ቶሎ ቶሎ ማለቅ ከጀመረና
መንቀርፈፍ ከጀመረ እና ያልተለመደ ግለት ካሳየ
ምንም እንኳን ስልካችንን የተለያዩ ተግባራትን ለመፈጸም ብዙ ጊዜ የመረጃ ጠላፊዎች በተለይም ስለላ ላይ የተሰማሩ
የሚያስፈልገውን ፍጥነት የሚወስኑት የተለያዩ ምክንያቶች የደህንነት መስሪያ ቤቶች እና የመንግስት ተቋማት
ሊኖሩ ቢችሉም ነገር ግን ሳንጠቀምበት ወይም ከኋላ እየሰሩ ፖለቲካ ውስጥ ልዩ ተሳትፎ ያላቸውን ሰዎች ለመከታተል
ያሉ መተግበሪያዎች (Background running applica- ፣ ወንጀለኞችን ለማደን እና ለሌሎችም በርካቶች
tions) ሳይኖሩ እንደ መደወል ወይም የጽሁፍ መልእክት ለማይስማሙባቸው ምክንያቶች የስልካችንን ካሜራና
መላክ ላሉ ብዙም ፍጥነት የማይጠይቁ ተግባራትን ማይክራፎን በመጥለፍ ስለላ (cyber spying) ሊያከናውኑ
ለመከወን ስንሞክር ከወትሮው የተለየ ዝግ የማለት ሁኔታ ይችላሉ:: ታዲያ እንዲህ ላለው የመረጃ ጠለፋ ተጋልጠን
ካስተዋልን ምናልባትም ስልካችን ለመረጃ ጠላፊዎች ከሆነ የስልካችን ካሜራና ማይክራፎን ከእኛ እውቅና ውጪ
ለመጋለጡ አንድ ጠቋሚ ምልክት ሊሆን ይችላል:: ዘወትር ስራ ላይ ስለሚሆን እና ይህም ስልካችን ከፍተኛ
ሃይል እንዲጠቀም ስለሚያደርገው ከወትሮው የተለየ
እንግዳ መተግበሪያዎች
2 ስልካችን ላይ ተጭነው ከተገኙ
የባትሪ ፍጆታ ወይም የሙቀት መጨመር ሊያስከትል
ይችላል::

ምክንያታዊ ያልሆነ የኢንተርኔት


ከዚህ ቀደም ያላየናቸው ወይም እኛ ያልጫንናቸው
መተግበሪያዎች (applications) ስልካችን ላይ ተጭነው
4 ዳታ ፍጆታ
ካገኘን ይህም የመረጃ ጠላፊዎች ሰለባ መሆናችንን
የኢንተርኔት መረጃ ጠለፋ ብዙውን ጊዜ የሚከወነው
ማሳያ ሊሆን ይችላል:: ስውር መተግበሪያዎችን ስልካችን
ኢንተርኔትን በመጠቀም እንደመሆኑና ካለእኛ እውቅና
ላይ በድብቅ መጫን የመረጃ ጠላፊዎች ለስለላና እንደ
በድብቅ የተጫኑ መተግበሪያዎች (Applications)
አድራሻ ፣ የስልክ መልእክት ልውውጥ እና የምስልና ቪዲዮ
ስልካችን ላይ ያስቀመጥነውን ወይም በዙሪያችን ያለን
መረጃዎቻችንን ለመመንተፍ የሚጠቀሙበት አንደኛው
ዲጂታል መረጃ ለመመንተፍም ሆነ ስውር የስለላ
መንገድ ነው::
30 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
ዘመንኛ

ስራቸውን ለመከወን የኢንተርኔት ግንኙነታችንን


የድህረ ገጾች ያልተለመደ
ስለሚጠቀሙ የገዛነው ካርድ ወይም የኢንተርኔት ጥቅል
አገልግሎት ሳንጠቀምበት ቶሎ ቶሎ የሚያልቅ ከሆነ ይህም
7 ድንገተኛ ገጽታ ወይም ውስን
አንዱ የመረጃ ምንተፋ እየተደረገብን ለመሆኑ አመላካች ይዘት መቀየር
ሊሆን ይችላል::
ብዙም የተለመደ ባይሆንም አልፎ አልፎ የኢንተርኔት

ስልካችን ላይ ያልተለመዱ መፈለጊያዎችን ተጠቅመን የምናገኛቸው ድህረ ገጾች


5 ባህርያትን ማስተዋል
ወይም አዘውትረን የምከታተላቸው ጦማሮች ከተለመደው
ውጪ የሆነ ባህርይ ሊያሳዩን ይችላሉ:: ከነዚህ ያልተለመዱ
ባህርያት ውስጥ ደግሞ ይህን ድህረ ገጽ መጎብኘት
አንዳንድ ጊዜ ጠረጴዛ ላይ የተውነው ወይም ኪሳችን አይችሉም ወይም ለመቀጠል ከታች የሚታየው ምስል
ውስጥ ያለ ስልክ መልእክት ሲላክልን ወይም እንደ ፌስቡክ ወይም ጽሁፍ ላይ ክሊክ ያድርጉ ሊሆን ይችላል:: ይህ
ያሉ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ notifications ሲደርሰን የሚሆነውም የኢንተርኔት መረጃ ጠላፊዎች በስልካችን
የሚያሰማውን ድምጽ አሰምቶን ወይም ስክሪኑ በርቶ እና በኢንተርኔት ግንኙነቱ መካከል ያለውን ዲጂታል
ሲጠፋ ተመልክተን ስንከፍተው ምንም አይነት የnotifi- የኢንተርኔት አድራሻችንን IP adress በመመንተፍ
cation banners ማሳያም ሆነ መልእክት ከሌለ ይህም ለስለላቸው ሲያመቻቹን ነው::
ስልካችን ላይ ያስቀመጥነው መረጃችን እየተበረበረ
ለመሆኑ አንዱ ምልክት ነውና መጠርጠሩ አይከፋም::

6 የመተግበሪያዎች ድንገቴ ስራ
ማቆም
8 መተግበሪያዎችን ወይም
ኢንተርኔትን ተከትለው ብቅ
JOIN OUR TELEGRAM CHANNEL CLICK HERE

የሚሉ ሳጥኖች ( pop ups )


እንደ Facebook, Messenger, Instagram,
WhatsApp, Telegram ያሉ ወይም ሌሎች አዘውትረን ኢንተርኔት ለመጠቀም ስንሞክር ወይም መተግበሪያዎችን
የምንጠቀምባቸው መተግበሪያዎች በድንገት መስራት ስንከፍት ድንገት ብቅ የሚሉ (pop up) ሳጥኖች
ካቆሙና ያልተለመደ ባህርይ ማሳየት ከጀመሩ በጠላፊዎች አስቸግረውን ከሆነ ይህም ለመረጃ ምንተፋ የመጋለጣችን
ተሰናክለው ወይም ለመረጃ ምንተፋ malwares አንዱ ምልክት ሊሆን ስለሚችል እነዚህን Pop up ሳጥኖች
ተጋልጠው ሊሆን ይችላል:: መክፈት ወይም መጫን አደጋ ሊኖረው ይችላል::

31 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
ዘመንኛ

ታዲያ እነዚህን ከላይ ያሉትን ለመረጃ ምንተፋ የመጋለጥ


ምልክቶች በስልካችን ላይ አስተውለን ከሆነ ወይም ለወደፊት
ከሚከሰት የመረጃ ንጥቂያ ለመራቅና ለጥንቃቄ ምን ማድረግ
ይኖርብናል?

1. በስልካችን ላይ ያሉ የማናውቃቸው ወይም ከዚህ በፊት አስተውለናቸው የማናውቅ እኛ


ያልጫንናቸው መተግበሪያዎችን ማጥፋት (delete)ማድረግ
2. Settings ውስጥ በመግባት factory data reset የሚለውን ማስተካከያ
በመጠቀም የስልካችንን ይዘት ሙሉ በሙሉ መቀየር ወይም reset ማድረግ
* ይህኛው መንገድ ስልካችን ላይ ያስቀመጥናቸውን ፎቶዎች፣ቪዲዮዎች፣መተግበሪያዎች፣የስልክ
ቁጥሮች ፣ የመልእክት ልውውጥ እና ሌሎችንም ጠቃሚ መረጃዎችንም አብሮ ሊያጠፋ
ስለሚችል backup መያዝ ያስፈልጋል::
3. የመረጃ ጠላፊዎች ከኢንተርኔት በተጨማሪ የተለያዩ ምስሎች፣ ቪዲዮዎች እና ሌሎች ፋይሎች
ውስጥ malware የሚባሉትን አደገኛ ስውር ፕሮግራሞች በመደበቅ ስለላ ሊያካሂዱብን ወይም
ስልካችን ላይ ያሉንን መረጃዎች ሊበረብሩብን ስለሚችሉ ምንጫቸው ያልታወቁና በተለይም
ደህንነታቸው ካልተረጋገጠ ድህረ ገጾች ላይ ዳውን ሎድ የተደረጉ ምስልና ቪዲዮዎች ወይም
ሌሎች መሰል ፋይሎችን በብሉቱዝ ወይም ዋይፋይ ከመላላክ መቆጠብም ሌላው መንገድ ነው::
4. እንደ ሾፒንግ ሞል ፣ ባዛር ፣ ትምህርት ቤቶች እና ሌሎችም መሰል ቦታዎች የሚገኙ ብዙ
ተጠቃሚዎች የሚበዙባቸውን የዋይ ፋይ (WiFi)ኔትዎርኮች ከመጠቀም መቆጠብ አልያም
የVPN እና Active anti-malware ፕሮግራሞችን መጠቀም 5. ስልካችን ላይ ያሉትን WiFi,
Bluetooth እና Cellular data ተጠቅመን ስንጨርስ የመዝጋት ልምድን ማዳበር
5. በተለይም የአንድሮይድ ስልክ ተጠቃሚ ከሆንን ስልካችንን ቻርጅ ለማድረግ ኢንተርኔት
ግንኙነት ያለው ኮምፒውተር ላይ መሰካት የመረጃ መንታፊዎችን ስራ ምቹና ቀላል ስለሚያደርግ
ይህንንም አለማድረጉ ይመከራል::
6. የትምህርት መረጃዎች፣ ሚስጥራዊ ሰነዶች እንዲሁም ሌሎች እንዲያዩብን የማንፈልጋቸውን
ምስልና ቪዲዮዎች ወይም ሌሎች መረጃዎች ስልካችን ላይ አለማስቀመጥ
7. የመግዛት አቅሙ ካለን እንደ አይፎን ያሉ ጠበቅ ያለ የመረጃ ጥበቃ ሲስተም ያላቸውን ስልኮች
መጠቀምም ከመረጃ ምንተፋ ወይም ስውር የሞባይል ስልክ ስለላ ለመዳን አይነተኛ መፍትሄ
ሊሆን ይችላል::

32 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
ከስፖርት ማህደር
የኋላው ከሌለ…
በዮናስ ድንቁ

ታሪክ በታሪከኞች ሲሰራ የጸሃፊው ድርሻ የሚሆነው ይህ ግብጽ እነ ባዳዊ አብደል ፈታህን በመሳሰሉ በዛን ጊዜ
ታሪክ ከጊዜ በላይ ሆኖ ከፍ ብሎ እንዲታይ ማድረግ የአጉሪቱ ምርጥ በሚባሉ ተጫዋቾቿ ታግዛ ሌላ የአፍሪካ
ነውና እኛም ይህን ብለን በዚህ ወር የስፖርት ማህደራችን ቡድን አንዴም እንኳን ዋንጫውን ለማንሳት ዕድሉን
በኢትዮጵያ የእግርኳስ ታሪክ ትልቅ ቦታ ስላለው አንድ ቀን ሳያገኝ ለሶስተኛ ጊዜ ሻምፒዮን ለመሆን ወደሜዳ ትገባለች።
ልናወራቹ ወደድን። መልካም ንባብም ተመኘን። ኢትዮጵያ በበኩሏ በ1949 ዓ.ምበተመሳሳይ ሁኔታ በግብጽ
ጥር 13፣1954 ዓ.ም, አዲስ አበባ, ኢትዮጵያ። ቀዳማዊ 4 ለ 0 ተሸንፋ ያጣችውን ዋንጫ የቫሳሎ ወንድማማቾችን
ሃይለስላሴ ስታድየም መፈናፈኛ እስኪታጣ ድረስ ከ መንግስቱ ወርቁ ጋር ባጣመረ ቡድኗ በዚህ አመት
እግርኳስን በተጠሙ ከ25,000 በላይ በሚሆኑ ደጋፊዎች ለማሳካት ቋምጣለች።
ተሞልቷል። ጨዋታው ደግሞ ኢትዮጵያን ከግብጽ የዕለቱ የመሃል ዳኛ የነበሩት ኡጋንዳዊው ኢንስትራክተር
ያፋጠጠውየ3ተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ። ጆን ብሩክስ በፊሽካቸው የጨዋታውን መጀመር
ወደ ውድድሩ ግብጽ የቀድሞው የዋንጫ ባለቤት በመሆኗ አበሰሩ።ደጋፊውም ዝማሬውን በድምቀት ቀጥሎ የኳሷን
ኢትዮጵያ ደግሞ አዘጋጅ ስለነበረች ያለማጣሪያ በቀጥታ አቅጣጫ ተከትሎ ያፈጥ ገባ። ደቂቃዎች አለፉ። 35ኛው
መግባት ሲችሉ በማጣሪያ ውድድሩን የተቀላቀሉትን ደቂቃ ላይ ባዳዊ ግብጽን ቀዳሚ ያደረገችውን ጎል ከመረብ
ቱኒዚያንና ኡጋናዳን በማሸነፍም ነው ለፍጻሜው ያለፉት። አሳረፈ። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ደጋፊዎች ዝም አሉ፣
የጨዋታው መጀመሪያ ሰአት ተቃርቧል። በሃገሪቱ ሰንደቅ ሁሉም ተደናገጠ፣ ጨዋታውም ቀጠለ።
አላማ ቀለም ያሸበረቁ ደጋፊዎች፣ በአሸናፊነት ተስፋ አሁን ኢትዮጵያውኑ ተጭነው መጫወት ጀመሩ። የውጤት
የተሞሉ ልቦች በዝማሬ ለቦታው ልዩ ድምቀት ሰጥተውታል። ለውጥ ግን አልነበረም። የመጀመሪያው አጋማሽም በግብጽ
የመጀመሪያውንና ሁለተኛውን ዋንጫ ማንሳት የቻለችው መሪነት ተጠናቀቀ።ሁለተኛው አጋማሽ ላይ ተሽለው

34 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
ከስፖርት ማህደር

የቀረቡት ኢትዮጵውያኑ በ74ተኛው ደቂቃ በግርማ ተክሌ 4 ለ 2 በሆነ ውጤት በኢትዮጵያ አሸናፊነት ተጠናቀቀ።
የአቻነቷን ጎል አስቆጠሩ። ደጋፊው እንደአዲስ ተስፋው የቡድኑ አንበል የነበረው ሉቺያኖ ቫሳሎም ከቀዳማዊ
አንሰራርቶ ሳይጨርስ ግን ባዳዊ ለግብጽ 2ኛውን ጎል ሃይለስላሴ እጅ ዋንጫውን ተቀበለ።ሌሊቱን ሙሉ ደስታና
በሰከንዶች ልዩነት ውስጥ አስቆጥሮ ዋንጫው ወደግብጽ ሀሴት እጅና እግር አውጥተው በከተማው ላይ በድምቀት
ምድር መሄዱ እርግጥ መሰለ። ታዩ። ቀኑም በታሪክ መዛግብት ላይ ትልቅ አሻራውን ጽፎ
የኢትዮጵያ የእግርኳስ ታሪክ ካያቸው ድንቅ ተጫዋቾች አለፈ።
መካከል አንዱ የሆነው መንግስቱ ወርቁ በ85ኛው ደቂቃ ይህ ስብስብ ኢትዮጵያ በእግርኳስ ብሎምበስፖርት ታሪኳ
ላይ ከማዕዘን ምት የተሻገረለትን ኳስ በግንባሩ በመግጨት ካየችው ስብስብ ውስጥ ምርጡ ነው ቢባል ብዙዎችን
አስቆጥሮ ውጤቱን ወደ 2 ለ 2 ቀየረው። በዚህም መሃል የሚያከራክር አይሆንም።
የግብጹ ግብ ጠባቂ ኳሷን ስቶ በስህተት የመንግስቱን ግራ አሁን ላይ ግን ሀገራችን ኢትዮጵያ ለዋንጫ ከመፎካከር
ዓይን በቡጢ መትቶታል። በኋላም መንግስቱስለዚህ ጉዳይ ይልቅ ውድድሩ ውስጥ ለመግባት የሚደረገውን ማጣሪያ
ተጠይቆ ሲመልስ በቀልድ መልክ እንዲህ ብሎ ነበር። እንኳን ማለፍ ተስኗት እናያለን።
ታዲያ ኋላችን እንዲህ እያማረ አሸብርቆ ሲታይ አሁናችን
ላይ ምን ተፈጠረ? ፊታችንስ ከኛ ምን ይጠብቃል?
አባቴ የሞተው ለኢትዮጵያ ክብር በሁሉም የኢትዮጵያ የእግር ኳስ ቤተሰብ ውስጥ ሊመላለሱ
ጣልያንን ሲዋጋ ነው። ስለዚህ የሚገቡ የሚመለከተው አካል ደግሞ ምላሽ ሊሰጥባቸው
ለኢትዮጵያ አንድ ቡጢ መቅመስ ለኔ የሚያስፈልጉ ጥያቄዎች ናቸው። አበቃሁ።
ያን ያህል ከባድ አልነበረም።
#ተጨማሪ
መደበኛው 90 ደቂቃ ተጠናቆ አሸናፊውን ለመለየት • በወቅቱ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ያሰለጥኑ
30 ተጨማሪ ደቂቃዎች ጨዋታውን መቀጠል አስፈላጊ የነበሩት ዩጎስላቪያዊ አሰልጣኝ ስላቭኮ ሚሎሴቪች
ነበር። በስታዲየሙ ውስጥም ከፍተኛ ውጥረት ነገሰ። በውድድሩ ወቅት አገሪቱ ውስጥ ስላልነበሩ እሳቸውንን
ነገር ግን በ101ኛው ደቂቃ ላይ በግብጽ ተጫዋቾች በመተካት አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ቡድኑን ለዋንጫ
በተፈጠረ ስተት ኢታሎ ቫሳሎ ኢትዮጵያን መሪ ማድረግ አብቅተውታል።
ቻለ።የኢትዮጵያውያን ፊት በብርሀን ተሞላ። • በውድድሩ ታሪክ በዋንጫም ሆነ በሜዳልያ ብዛት
117ኛው ደቂቃ ላይ አፍሪካ እስካሁን ድረስ በሙሉ አፏ ግብጽን የሚስተካከላት የለም።
የምታወራለት ግብ ከመረብ ላይ አረፈ። መንግስቱ ወርቁ • የ2019 አፍሪካ ዋንጫ በቶታል ስፖንሰርነት እንደ
በአስደናቂ ብቃት 4 የግብጽ ተጫዋቾችን አታሎ በማለፍ ኢትዮጵያን አቆጣጠር ከሰኔ 14 እስከ ሀምሌ 12 2011
4ኛውን የኢትዮጵያን ጎል ከመረብ አሳረፈ። ስታድየሙ ዓ.ም ይካሄዳል።
በአንድ እግሩ ቆመ፣ አዲስ አበባ ጮቤ ረገጠች።ጨዋታው

35 መ ል ካ ም7 4 | ሜ ይ 1 , 2 0 1 9
*805*ፍቅር#
በልዑል ሀይሌ

*805*............
ጎዶሎ ጎን መሙያ
ያልተፋቀውን ካርድ ዕጣ ስትሞላበት
እሷን ነው?...’ሌላ’ን ነው?
በፍቅር ህይወቴ ስሟን ያኖርክበት
.
አላውቅም!
.
*805*...............
.
ይሄን ቁጥር ፅፌ
ሄዋን እየሞላሁ ደውዬም አውቃለሁ
ያገለገለ ካርድ እየተባለብኝ
ካርዴን የሚሞላ ኔትውርክ አጥቻለሁ
.
ይሁን!
.
*805*.................
እናም አሁንም
.
ካርዴ ውስጥ ያለሽው አንቺ ትሆኚ እንደው
ከኮከብ ቀጥለሽ ተፅፈሽ ገብተሻል
እስከመቼ አትበዪኝ
መሰላሉን ስጫን ኔትወርክ ይነግርሻል
.
*805*.................
.
ስማኝ ፈጣሪዬ...
በሙከራ ብዛት ቻርጅ ከሚያልቅብኝ
በተሞሉ ካርዶች ጊዜ ከሚያልፍብኝ
..
የፃፍካትን ስጠኝ
ከኮከብ ቀጥዬ የሷን ስም ልፃፈው
መሰላል ተጭኜ በሞላኸው ቤቴ
አንተው ጋ ደውዬ በምስጋና እንዳልፈው
*805*ፍቅር#

You might also like