You are on page 1of 52

የአዘጋጆች መልዕክት

Masqala YOO! YOO! Daanaw daana!

YOO! YOO! Daanaw daana!

በጎፋ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ፆሊንቶ መጽሔት በየዓመቱ እየተዘጋጀ የሚቀርብ ሲሆን የዘንድሮው ቁጥር-2
መጽሔት የጎፋ ጋዜ ማስቃላን መሰረት አድርጎ የተዘጋጀ ነው፡፡ የመጽሔቱ ይዜት በአራት ክፍሎች የተዋቀረ በመሆኑ
ክፍል አንድ የተለያዩ አካላት ያስተላለፉት መልዕክት፤ ክፍል ሁለት የጎፋና ኦይዳ ህዝቦች ታሪክ፤ ክፍል ሶስት የባህል አምድ
ሆኖ በውስጡ የተለያዩ የባህላዊ ክዋነና ስርዓት ያካተተ ነው፡፡ የመጨረሻው ክፍል ደግሞ ኢኮኖሚያዊ አምድ ሆኖ የዞኑን
ኢኮኖሚያዊ አቅሞች በተመጠነ መልኩ ያካተተ በመሆኑ ለአንባብያን መልዕክት ያስተላልፋሉ ተብሎ ይታመናል፡፡

በመጨረሻም በመጽሔቱ አዘገጃጀት ላይ አንባብያን የሚሰጡትን አስተያየት ለመቀበልና በቀጣይ ዝግጅታችን ለማካተት
ጠቃሚ በመሆኑ ማንኛውንም አወንታዊም ሆነ አሉታዊ ጎን አስተያየት ከአንባቢያን እንጠብቃለን፡፡

Masqala YOO! YOO! Daanaw daana!

Albba Zumaaddan daana! Kinitti Shaluwadan Daana! Mithadan shuchadan Daana!

አዘጋጆች

1. አቶ ድንበሩ ድርቤ ዲላ - የመምሪያው ኃላፊ


2. መ/ር ዘለቀ ዶሳ ሞርጋሞ - ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ
3. አቶ አረካ አደም አሻንቃ - የመምሪያው ባህል፤ታሪክ እና ቅርስ ጥናት ባለሙያ
4. አቶ ጣሊያን ጣሰው ጻባላ - የመምሪያው ፕሮሞሽን ባለሙያ
5. ዮሐንስ ኢትዮጵያ ቶጫ - የመምሪያው የቅርስ ጥናትና ልማት ባለሙያ
6. ኢስያስ አዋሼ አጻ - የጎፋ ልማት ማህበር ፕሮግራም ማናጄር
7. ምህረቱ ቶይሎ ቶጋ - የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ባለሙያ

ምስጋና
ለዚህ መጽሔት ዝግጅት ፕሮግራሞችን በማዘጋጀት፤ መረጃዎችን በመስጠት፤ የእርማት ሥራዎችን በመሥራትና
በጽሑፍ ሥራ ላገዙን ሁሉ የላቀ ምስጋና እናቀርባለን፡፡ በተለይ ደግሞ የጎፋ ዞን ዋና አስተዳደርና የዞኑ ባህልና ቱርዝም
መምሪያ ከሚመለከታቸው የመንግስት ኃላፊዎች ጋር በመሆን አስፈለጊውን በጀት በመመደብና ትኩረት በመስጠት
ላደረጉልን አስተዋጽዖ ከልብ እናመሰግናለን፡፡
መልካም ንባብ

ክፍል አንድ
መልዕክቶች
የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ጌትነት በጋሻው መልዕክት

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 1


ውድ የዞናችን ሕዝቦችና በሀገራችን በተለያዩ ክልል ከተሞች እንዲሁም ከሀገር ውጭ የምትኖሩ የጎፋ እና የኦይዳ
ብሔረሰብ ተወላጆች መላው የዞናችን ህዝቦች በሙሉ በቅድሚያ እንኳን ለ 2015 ዓ.ም. ለጎፋ እና ኦይዳ ብሔረሰብ
የዘመን መለወጫ በዓል ለሆነው "ጋዜ ማስቃላ" እና " ዮኦ ማስቃላ" ክብረ-በዓል በሠላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን ለማለት
እወዳለሁ። መጪው አዲሱ ዓመታችን የሠላም፣የጤና፣ የፍቅር፣የደስታ፣የመቻቻል፣የአንድነትናየአብሮነት እንዲሁም
ኢትዮጵያዊ ወንድማማችነትን በማጠናከር በሀገር ደረጃ የተጀመረውን የለውጥና የብልጽግና ራዕይ እውን ለማድረግ
ሁላችንም እጅ ለእጅ ተያይዘን ለመስራት ቃል የምንገባበት ጊዜ እንዲሆን ልባዊ ምኞቴን ለመግለጽ እወዳለሁ።

ውድ የዞናችን ሕዝቦች ባለፉት አራት ዓመታት በተለይም ከ 2013 ዓ.ም ጀምሮ የውስጥም ሆኔ የውጭ ታሪካዊ
ጠላቶቻችን የተጀመረውን የለውጥና ብልጽግና ጉዞ ራዕይ ለማደናቀፍና ኢትዮጵያን የማፈራረስ ዕቅድ ይዘው
የተንቀሳቀሱበት ጊዜ ቢሆንም ኢትዮጵያውያን አንድነታቸውን በማጠናከር የጠላቶቻችን እኩይ ሴራ በማክሸፍ
ኢትዮጵያ በአሸናፊነት እንድትቀጥል የራሳችሁን የማይተካ ሚና በሀገር ደረጃ መክፈላችሁ ሁሌም ሲታዎስ ይኖራል፡፡

የዘንድሮው የጎፋ ጋዜና የኦይዳ ዮኦ ማስቃላን በዓልን ልዩ የሚያደርገው ነገር ብኖር፤ በዞናችን የወቅቱን የአየር ንብረት
ለውጥ ተከትሎ በተከሰተው ድርቅና የመሬት መንሸራተት አደጋዎች ያስከተሉት ከፍተኛ ተጽዕኖዎችን በመቋቋም
በሀገራችን ኢትዮጵያ በአሸባርው የህይዋት ቡድን የተደቀነውን የ 3 ኛ ጊዜ ጦርነት ለመመከት ህዝባችን የራሳቸውን
ፈታኝ ችግሮችን ወደ ጎን በመተው ሀገርን በማስቀደም ለጀግናው የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊት እንደከዚህ ቀደሙ
ጽኑ ደጄንነቱን እያሳዬ በሚገኝበት ወቅት ላይ ማክበር መቻላችን ነው፡፡

ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ በይፋ የተደራጀው እንዲሁም ከለውጡ ትሩፋቶች መካከል አንዱ የሆነው የጎፋ ዞን መደራጀቱን
ተከትሎ የለውጡ መንግሥት በሰጠው ዕድል ሕዝባችን ለዘመናት ሲያነሷቸው የነበሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር
ጥያቄዎች ምላሽ አግኝተዋል። በሀገራችን ብሎም በአካባቢያችን ሁለንተናዊ ለውጥ፣ልማትና እድገት ማምጣት
የሚቻለው ሁላችንም ልዩነቶቻችንን ወደ ጎን ትተን የዞናችን አነድነት በማስጠበቅ የአከባቢውን እምቅ አቅም
በማጎልበት በ 2015 ዓ.ም በሁሉም የልማት ዘርፎች ተወዳዳርና ብቁ ሆነው እንድገኙ በዚህ አጋጣም መልዕክተን
ለማስተላለፍ እወዳለው፡፡

በድጋሚ እንኳን የጎፋ እና እና ኦይዳ ብሔረሰቦች የዘመን መለወጫ የሆነው ጋዜ ማስቃላ እና ዮኦ ማስቃላ በዓል በሠላም
አደረሳችሁ እያልኩኝ፣አዲሱ ዓመት የሠላም፣የፍቅር፣የስኬት፣የልማትና የብልጽግና፣የበጎነትና የመተሳሰብ ዓመት
እንዲሆንልን ልባዊ ምኞቴን እገልጻለው።

አመሠግናለሁ! ጋዜ ማስቃላ ዮ…ዮ..! " ዮኦ ማስቃላ!"

ዶ/ር ጌትነት በጋሻው:- የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ

አቶ ድንበሩ ድርቤ ዲላ

የጎፋ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ መልዕክት


ኢትዮጵያ ከሰማንያ በላይ የሚሆኑ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እንዲሁም የተለያዩ የሐይማኖት ተከታዮች
ለዘመናት እርስበርሳቸው ተቻችለው፣ተዋደውና ተፋቅረው በአንድነት የሚኖሩባትና ህብረብሔራዊ አንድነትና
ወንድማማችነት ጎልቶ የሚታይባት ሀገር ናት። በሀገራችን ኢትዮጵያ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በቅርቡ የራሳቸውን
ችለው የተዋቀሩት ሲዳማ እና የምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልሎችን ጨምሮ በአጠቃላይ አሥራ አንድ /11/ ክልሎች
መካከል የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት አንዱ ነው። በክልላችን ስር ከሚገኙ ዞኖች መካከል
የጎፋ ዞን አንዱ ነው። ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ የተደራጀው የጎፋ ዞን ሁለት ብሔረሰቦችን ማለትም የጎፋ እና ኦይዳ
ብሔረሰቦች የሚገኙ ሲሆን በሰባት ወረዳዎችና በአራት የከተማ አስተዳደር መዋቅሮች የተደራጀ ነው። እነዚህ

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 2


ብሔረሰቦች ለዘመናት ጠብቀው ያቆያቸው ባህላዊ እሴቶች፣ ታሪክና ቋንቋ እንዲሁም የበርካታ ተፈጥሮ መስህቦች
ባለቤቶች ናቸው።

በሁለቱ ብሔረሰቦች ዘንድ በየዓመቱ በወርሃ መስከረም የሚከበረው የጎፋ ብሔረሰብ "ጋዜ ማስቃላ" እና የኦይዳ
ብሔረሰብ "ዮኦ ማስቃላ ክብረ በዓል አንዱ ሲሆን በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት ይከበራል። በጎፋ እና እና ኦይዳ
ብሔረሰቦች ዘንድ በየዓመቱ በደማቅ ባህላዊ ስነስርዓት የሚከበረው የመስቀል በዓል አከባበር በአለምአቀፍ ደረጃ እውቅና
እንዲያገኝና በማይዳሰሱ ቅርሶች እንዲመዘገብ መምሪያው ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል። በመግቢያው
እንደገለጽኩት የጎፋ እና ኦይዳ ሕዝቦች የራሳቸው የሆነ ባህላዊ እሴቶች፣ ታሪክ፣ ቋንቋና የበርካታ ተፈጥሮ መስህቦች
ባለቤቶች ቢሆኑም ብሔረሰቦች ለዘመናት ጠብቀው ያቆያቸው የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶች የመስቀል በዓል
አከባበርን ጨምሮ በአግባቡ ያልተጠኑና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ሳይሰጡ መቆየታቸው ይታወቃል።

በመሆኑም ቱሪዝም ለአንድ ሀገር ምጣኔ ሀብታዊ እድገት የሚያበረክተውን ፋይዳ በመገንዘብ መምሪያው የተሰጠውን
ሥልጣንና ኃላፊነት በአግባቡ በመጠቀም በቀጣይም በዞኑ የሚገኙ የተለያዩ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎችን በማልማትና
በማስተዋወቅ የተቋሙን ራዕይ እውን ለማድረግና ተልዕኮውን ለማሳካት ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ
ለመግለጽ እወዳለሁ። በተለይም የዞናችን መቀመጫ የሆነችው ሳውላ ከተማን ጨምሮ በሁሉም ከተማ አስተዳደሮች
የሚስተዋለውን የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እጥረት ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ከዞኑ መንግሥትና
ከባለሀብቶች ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን እገልፃለሁ።

ዞናችን የበርካታ ባህላዊና ተፈጥሮአዊ መስህቦች ባለቤት መሆኑን ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት የአካባቢው ማህበረሰብ
በየአካባቢያቸው የሚገኙ ተፈጥሮአዊና ባህላዊ ቅርሶችን በመጠበቅና በመንከባከብ ከዘርፉ ልገኙ የሚችሉ ጥቅሞችን
በማሳደግ እና አከባቢውን ይበልጥ እንድያስተዋወቁ በዚህ አጋጣሚ አሳስባለሁ። በመጨረሻም የዞናችን ነዋሪዎች፣ በሀገር
ውስጥ በተለያዩ ከልሎች እንዲሁም ከሀገር ውጭ የምትኖሩ የጎፋ እና ኦይዳ ብሔረሰብ ተወላጆች እንኳን ለጎፋ
ብሔረሰብ "ጋዜ ማስቃላ" እና ኦይዳ ብሔረሰብ "ዮኦ ማስቃላ" በዓል በሠላም አደረሳችሁ፣ አደረሰን ለማለት
እወዳለሁ።

አመሠግናለሁ! Masqala YOO! YOO! Daanaw daana!

መግቢያ
በደቡብ ብሔር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ክልል ከሚገኙ 13 ዞኖች አንዱ የጎፋ ዞን ነው ፡፡ የጎፋ ዞን እንደ ሀገር
ለውጡ ከወለዳቸዉ የለውጡ ፍሬ ከሚባሉ እንዱ ስሆን የዞኑ አጠቃላይ ቆዳ ስፋቷም 4551 ስኩዋር ኪሎ
ሜትር ነው ፡፡ የዞኑ ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ 5'54N - 6'44N ላቲትዩድ እና 36'20 E-37' 20 E ሎንግቲውድ
ነው ፡፡ በሰሜን ከዳውሮ ዞንና ኮንታ ልዩ ወረዳ በደቡብ ከደቡብ ኦሞ ዞንና ጋሞ ዞን በምስራቅ ከዳውሮ ዞንና
ከጋሞ ዞን በምዕራብ ከደቡብ ኦሞ ዞንና ከባስከቶ ልዩ ወረዳ ጋር ይዋሰናል ፡፡ የዞኑ ዋና ከተማ ሣውላ ሲሆን
ከአድስ አበባ በስተደቡብ ምዕራብ አቅጣጫ በ 516 ኪሎ፤ ከክልሉ ርዕሰ ከተማ ሐዋሳ 296 ኪሎ ሜተር ርቀት
ላይ ይገኛል፡፡ በዞኑ ሁለት ነባር ብሔረሰቦች ጎፋና ኦይዳን ጨምሮ ሌሎች የሀገርቱ ወንድምና እህት ከሆኑ
ህዝቦች መጥተው በጎፋ ዞን ተጋብተዉ ተዋልደው በማይነጣጠል አንድነት ተጋምደው በሠላምና በፍቅር ሰዎች
የምኖሩባት ትንሹዋ ኢትትዮጵያ ብንል ማጋነን አይሆንም፡፡

የዞኑ ሕዝብ ብዛት ከ 1.5 ሚሊየን በላይ ሲሆን የአከባቢው ህዝብ ኑሮ በአብዛኛዉ በሚባል ደረጃ በግብርና ሥራ
ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ የዞኑ የአየር ንብረት በሦስት ተከፍሎ 20.92% ደጋ፣ 31.12% ወይና ደጋ 47.96% ቆላማ
የአየር ፀባይ ያለው ነው፡፡ የዞኑ የመሬት አቀማመጥ ከባህር ጠለል በላይ በአማካይ 1976 ሜትር ከፊታ ያለዉ
ሲሆን በከፍታቸው የታወቁ በመሎ ኮዛ ወረዳ 3439 ሜትር ከፍታ ያለው የዳሞታ ተራራ እና በኡባ ደብረፀሐይ
ወረዳ 3421 ሜትር ከፍታ ያለው የሀገር ማሰዲዚ ተራራ እና በደምባ ጎፋ 3400 የፃንጋ አልባ ዙማ ባለሻኛው
የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 3
ተራራ ይገኙበታል፡፡ የዞኑ አማካይ ዓመታዊ የዝናብ መጠን 170.5 ሚ.ሜትር ነው፡፡ የጎፋ ዞን ለአስተዳዳራዊ
አመችነት በ 7 ወረዳዎችና በ 4 የከተማ አስተዳደሮች እንድሁም በ 196 የገጠርና ከተማ ቀበሌዎች የተከፋፈሉ
ነው፡፡

የዞኑ የአየር ንብረትና የመሬት አቀማመጥ ለሰዉ ልጅ ኑሮ ተስማሚ፤ መልካዓምድር አቀማመጥ በጣም
ማራኪና መሬቱ ለእርሻ ሥራ፣ለኢንቨስቲመንት እና ለቱሪዝም ክፍለ ኢኮኖሚ ተመራጭ እና ሠላሟ በህዝቦቿ
የተረጋገጠ ከመሆኑ የተነሳ ወደ ዞኑ በመምጣት አዋጭ በሆኑ የሥራ ዘርፍ ላይ ኢንቨስት በማድረግ ዳጎስ ያለ
ትርፍ በማግኘት ለመበልፀግ ለሚፈልጉ ባለ ሀብቶችና ድያስፖራዎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት
በሩ ክፍት ሙኑን በዚሁ አጋጣሚ የጎፋ ዞን አስተዳደር ጥሪውን ያቀርባል፡፡

ክፍል ሁለት
የታሪክ አምድ
2.1 የጎፋ ብሔረሰብ ታሪክ

መግቢያ

“To be ignorant of what occurred before you were born is to remain always a child”

CICERO (First Century B.C.)

የጎፋ ብሄረሰብ ታሪክን በአጭሩ ለመጽሄት መሙያ አድርጎ ማዘጋጀት ከግምት በላይ ነው፡፡ በመሆኑም የጎፋ
ብሄረሰብ ሙሉ ታሪክ ሳንል የታሪክ ቅንጭብጭብ (Demo) ብለን ብንመለከተው ጥሩ ይሆናል፡፡ ምክንያቱም
የጎፋ ብሄረሰብ ታሪክ እናወሳለን ካልን በፖለቲካ ታሪኩ ራሱን ከማስተዳደር አልፎ በሀገር አቀፍ ደረጃ ያገኘው
ዕውቅና፤በኢኮኖሚውና ማህበራዊው ዘርፍ ብንሄድ የማህበራዊ ትስስርን ለኢኮኖሚያዊው ጠቀመታ ያዋለበት
ጥበብ፤ በትምህርትና ዕውቀት ብንመለከት የጎፋ ብሄረሰብ በቋንቋ፤በሥነ-ቃል፤በሙዝቃ፤በአርት እና በተለያዩ
የጥበብ ሥራዎች፤በዘመን አቆጣጠሮች፤እጅግ ብዙ ፈርጅ ያለው የታሪክ ሰንሰለት በመሆኑ በዚህ ክፍል በትንሹ
ከየዓይነቱ ቀንጨብ ቀንጨብ ተደርጎ ለጎፋ ጋዜ ማስቃላ መጽሄት እንደመነሻ ሆኖ ቀርቧል፡፡

ታሪክን መሥራት እንደ ታሪክ መማር፤ማስተማርና መጻፍ ቀላል አይሆንም፤ሆኖም ግን ታሪክን መጻፍና
ማስተማር የራሱ የሆነ ከፍ ያለ አስተዋጥኦ አለው፡፡ ታሪክ ለሰው ልጆች ምን ያህል ጥቅም እንደሚሰጥ ወይም
ስለአስፈላግነቱ በዓለማችን ዕውቅ የሆኑ መሪዎችና ምሁራን ተጠቅመውበታል፤መልሰውም ተንትነውበታል፡፡
የዛሬዋን የጎፋ ብሄረሰብ ታሪክ የሚሰሙም ሆኑ የሚያሰሙ ለትውልዳቸው የሚሆን ትልቅ ታሪክ እየሰሩ ነው፡፡
ከዓለማችን መሪዎች የአሜርካው ፕርዝዳንት ተወዳጁ አብራሃም ሊኒኬን ስለታሪክ ተቀመታ ያሉትን
የእንግልዘኛውን ሀሳብ በቀጥታ አስቀምጠን ትርጉሙን ቀለል ባለ ማብራሪያ እንመለከተዋለን፡፡

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 4


"Human nature will not change. In any future great national trial, compared with the men of this, we
shall have as weak and as strong, as silly and as wise, as bad and as good. Let us therefore study the
incidents in this as philosophy to learn wisdom from and none of them as wrongs to be avenged."

Abraham Lincoln (in the context of The American Civil War of 1861 to 1865)

እንደምታወቀው ይህ ፕርዝዳንት በአሜርካ ታሪክ ለነጮችም ሆነ ለጥቁሮች እኩል ቦታ በመስጠቱና


የተከተላቸው የመርነት ጥበቦች በብዙ ትውልዶች መካከል እንድታወስ አድርገውታል፡፡ ከላይ ያሉትን
ሲንመለከት ሃሳቡን ብቻ፤

…የሰው ልጅ ተፈጥሮ አሁን ካለው ወደፊት በብዙ ትውልድን በምፈትኑ ነገሮች ብያልፉም እምብዛም
አይለወጥም፤ ግን … ደካማ እንዳለ ሁሉ ጠንካራ ፤እንድሁም ሞኝም እንዳለ ሁሉ ብልህም፤ መጥፎም እንዳለ
ሁሉ ጥሩም እየሆነ ይቀጥላል፡፡ ስለዚህ ማጥናት ያለብን በታርክ ከተፈጸሙት እንደ አንድ መሰረታዊ ነገር
(principles) ጥበብን (wisdom) እንማራለን፤ ይህን ብናደርግ እምብዛም አያስኮንንም… ይላሉ፡፡

ስለዚህ በመግቢያየ እዳስቀመጥኩ እውቁ ሲስሮ (Ceciro) ከክርስቶስ ልደት በፊት ታሪክን ያለማጥናት፤
ያለማወቅና ያለማሳወቅ ሳያድጉ ልጅ ሆኖ መቅረት ነው ካሉት ለማሚለጥ፤እንደ ፕርዝዳንት አብራሃም
ሊኒከን ምክር ከትውልዶች ታሪክ ጥበብን ለመማር እንድሁም በዚህ ዘመን ያለው የታሪክ ሺሚያውና ማጥፊያ
ዘዴው እኛ ከሚንገምተው በላይ በመሆኑ የጎፋ ብሄረሰብ ታሪክ ለማዳን ተባብሮ ጽፎ ለትውልድ ማቆዬቱ
መልካም በማለት አቅርበናል፡፡ ይህንንም ትውልድ ተሻጋር ሥራ የሚከውኑ ሁሉ አስተዋዮች ናቸው፡፡

በዚህ ላይ አንድ ጸሐፊ ደራስና ጋዜጠኛ የሆኑት ተጓዡ ጋዜጠኛ ሄኖክ ስዩም በቅርቡ ገበያ ላይ ባዋሉት “ሀገረ“
በምለው መጽሐፋቸው ከገትኔት እንየው እውቀትን ፍለጋ ከተሰኘው መጽሐፍ ለምክር የሚሆን አንድ ግጥም
መሣይ ስለማንነትና ማንነትን ፈልጎ ስለማግኘት ያስቀመጡትን አይተን እናበቃለን፤

ነው ሲኖሩ “…ከራስ ጋር ታዋዶ ከራስ ጋር ታርቆ

“እኔ ማነኘ?” ብሎ፤ራስን ጠይቆ

መኖር እንጂ ፍቺው፤ማንነትን አውቆ

ጊዜማ ይሄዳል ጊዜውን ጠብቆ”

(ሄኖክ ስዩም 2013፤159)

2.1.1 የጎፋ ብሔረሰብ - ታሪክ መነሻ

የጎፋ ብሄረሰብ ምናልባትም የሰው ዘር ከተፈጠረበት ጊዜ አንስቶ በብዙ ጥናት ተዳስሶ ወጥተው ቀደምት
አከባብ፤ ብሄረሰብ፤ የሰው ዘር መገኛ ተብሎ ከሚታወቁ አከባቢዎች አንዱ ይሆናል ሚል እምነትና ግምት
አለኝ፡፡ ለዚህ በዋናነት ምክንያት የሚጠቀሰው በአንዳነድ የሚርምር ውጤቶችና የቋንቋ ጥናቶች
እንደተመለከተው የጎፋ ብሄረሰብ በጥነታዊነቱ በታወቀው በኦሞትክ ህዝቦች ውስጥ መገኘት ብቻ ሳይሆን
በጂኦግራፋዊ አቀማመጡም ማዕከላዊ በመሆኑም ጭምር ነው፡፡ አንዳንድ ታሪክ ጻሀፍዎች የዖሞትክ ህዝቦች
በድሮ ከጥንት ዘመን ጀምረው ከደቡብ ሸዋ ፈልሰው የኦሞ ወንዝ ተከትለው የሰፈሩ ህዝቦች ናቸው ስለሚሉ

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 5


የጎፋ ህዝብም የዚህ ታሪክ ባለበት ነው፡፡ በለላ በኩልለሎችና ምናልባትም የሚበዙት ግን የጎፋ ብሄረሰብ ከጥንት
ዘመን ጀምረው በላኛው የኦሞ ወንዝ ጫፍ አከባብ ሰፍረው ለረጅም ጊዜ የኖሩና ከዚያ እየሰፉና
እየበዙ፤ግዛታቸውን በማስፋት አሁን የያዙበትን አልፈው የቆዩና ከለላ ቦታ ፈልሰው ያልመጡ ናቸው ይላሉ፡፡

በተጨማርም በዓለማችን በተደረጉ የቋንቋ ጥናቶች፤የሥኔ- አጽም ምርመራ ያስገኘው ውጤት የተለያዩ
ቅርቴ አካሎችና የጥንታዊ ሰዎች መገልገያ መሳሪያዎች በተለይ በቅርቡ እየተደረገ ባለው ጥናት ከሉሲ ቀጥሎ
ከፍተኛ ዕድሜ ያለው ሰው መሰል አጽም (Homo erectus) የተገኘው በምሥራቅ አፍርካ ሲሆን የተገኘበት
የቱርካና ሐይቅ አከባብ መሆኑ እና ለቱርካና ሐይቅ ዋነኛ መጋቢው “ዑማ“ ወንዝ መሆኑ ነው፡፡ ከዚህ ስንነሳ
በከንያና በኢትዮጵያ ድንበር አከባቢ የተደረገው ጥናት የዑማን ወንዝ ተከትሎ ከፍ ቢል የበለጠ ማስረጃ ሊገኝ
ይችላል የሚል ግምት ምሁራን ያስቀምጣሉ፡፡

እንደገናም የጥንቷ ኢትዮጵያ ተብሎ በኢትዮጵያ ካርታዎች ድርጅት ተዘጋጅቶ ለታሪክ ከተረፈው ካርታ ላይ
ከተሰጡት ማብራርያዎች ታሪካዊ ሥፍራ (Historical Sites) ተብለው ከተለዩት አንዱ የኦሞ ሸለቆ
ከመሆኑም በላይ ከ 1.8 እስከ 3 ሚልዮን ዓመት እነዳስቆጠረ ጥንታዊነቱን ቁልጭ አድረግዎት አሳይቶናል፡፡
በዚህ ላይ ተጨማር መረጃዎችን ለላ ጊዜ፡፡ በመጨረሻም አንዳንድ በብሔረሰቡ ሚከናወኑ ባህላዊ ሥርዓቶችና
ክዋነዎች እንደ “ጎሜ“ ዓይነቶች በአሁኑ ሰዓት ሥልጣነ ጣራ በነካው በረቀቀው ቴክኖሎጅ ወቅት የሌሉ
መሆናቸው እውነትም ከለላ ቦታ ፈልሰው የመጡናቸው የሚለውን ለመቀበል ያስቸግራል፡፡

2.1.2 የጥንቱን ዳሰሳ በከፍል

1. ጎፋ - ከማዜ ወንዝ እስከ ከፋ


ኢትዮጵያ ሀገራችን አብሲኒያ ተብላ ስትጠራ የግዛት ወሰኗ ከግብጽ ጀምሮ በሱዳን እስከ የመን ይደርሳል
ተብሎ ይነገራል፡፡ እንደዚሁ በጎፋ ብሄረሰብ ታሪክም የጎፋ ንጉሦች (ካዎዎች) አንድ ወቅት የኦሞ/ዑማ ወንዝ
ተሻግረው እሰከ ከፋ ባሉት ሥፍራዎች እንዳስተዳደሩ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡ ኤክ ሀቤርላንድ የተባለው
ከባህር ማዶ ጻፍዎች መሃል የሆኑት የደቡብና ደቡብ ምዕራብ ህዝቦች ታሪክ ስጽፍ የጎፋ ብሄረሰብ ታሪክን
እነድህ በማለት ገልጸዋል፡፡ የጎፋ ብሄረሰብ ከጥንት ጀምሮ የተደራጀና አንድ ወቅት ጎፋን ሲያስተዳድር
የነበረው የጎፋ ነጉስ (ካዎ) ጎቤ የሚባለው ለግዛት መስፋፋት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየተዋጋና ነጻ መሬቶችን
በራስ ግዛት ውስጥ እያጠቃሌለ እንደሚቆጣጠርና እንደምያስተዳድር ገልፅወታል፡፡ (በላይነህ አሰጉ 2009፤38)

አክለውም ከጥቅት ኒሎ ሳሄራውያንናከዳውሮ ጋር በቋንቋና በባህል የሚመሳሰሉ ጎሳዎች የሰፈሩበት ሲቀር


ሌላውን ባዶ መሬት በሙሉ ያዘ፡፡ በጥቅት ዓመታት ውስጥ በርካታ የዳውሮ ግዛቶችን በመያዙ የአከባቢው
ገዥም ወደእሱ ገባ ይለናል፡፡ በዚህ ምክንያት የጎፋ ግዛት እስከ ከፋ ዘልቆ የጅማ ጎረበት ልሆን በቅቶ ነበር፡፡
(ሀበርላንድ 28፤ በላይነህ አሰጉ 2009፤38 እንደጻፈው)

በሌላ በኩል የጥንቷ ኢትዮጵያ ተብሎ በኢትዮጵያ ካርታዎች ድርጅት ተዘጋጅቶ ለታሪክ የተላሌፈውን የጥንት
ኢትዮጵያ ከ 2800 ዓመተ ዓለም እስከ 1270 አመተ ምህረት ካርታ ላይ ስንመለከት ያነ እንኳን በሙላት
የኢትዮጵያ ቅርጽ ባልወጣበት ኦሞትክ ህዝቦች ተብልው የሚጠሩት ከጉራጌ በታች፤ ሀድያና ሲዳማን ወደ
ምስራቅና ደቡብ ጎን በመተው እንደሚታወቁ ተገልጿል፡፡ በዚህ ላይ የኦሞ ወንዝ ተከትለው በተሰየመው
ማህበረሰብ ውስት ወንዙን “ዑማ“ እያለ በዋናነት ከቦ በመኖር የሚታወቀው የጎፋ ብሄረሰብ መሆኑን
ጂኦግራፊካል ሎኬሽን የተለዬ ዕድል መስጠቱን ያሰያል፡፡ በዚህም ማዕከላዊ ቦታ ከመያዙ የተነሳ በሚያስገርም
ሁኔታ ከሁሉም ለሎች አጎራባቾች ጋር ከፍተኛ የሆነ የቋንቋ መወራረስ መኖሩን ደራሲው መምህር በላይነህ

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 6


አሰጉ ጎፋ ባህሉና ታሪኩ በሚለው መጽሐፋቸው ያስቀመጡትን ተመልክተናል፡፡ (በላይነህ አሰጉ 2009፤21፤
ፕሮፈሰር ላጵሶ ጌ. ደለቦ 1983፤13)

ስለ ጥንታዊነቱ በተጨማረትም ኢትዮጵያ የታሪክ መነሻ በሚለው በኢትዮጵያ ትምህርት ሚንስትር


ትምሀረርት መሣሪያዎች ማሚረቻና ማከፋፈያ ድርጅት በፕሮፈሰር ላጵሶ ጌ. ደለቦ በእንግልዘኛ ተጽፎ በአቶ
ተርፋሳ ድጋ ወደ አማረኛ በተተረጎመው ላይ ስለ ኦሞ ማህበረሰብ እንድህ ብለው መስክረውታል፡፡

“… በአስራ አራተኛው መዕተ ዓመት በኢትዮጵያ የአፄ ማዕከላዊ መንግሥትግዛት ውስጥ ከመቀላቀላቸው
አስቀድሞ የሀርላ፤ ሸዋ፤ ይፋት፤ አርጎባ፤ወርጅ፤ አዳል፤ ሀዲያ፤ ሲዳሞ፤ ደዋሮ፤ ፈጠጋር፤ አራባቢኒ፤
ሻርክ፤ ባሌ፤ ዳራ፤ ወጅ፤ ጉራጌ፤ ዳሞት፤ ገንዝና ኦሞ ልዩ ልዩ ማህበረሰቦች እስከ 1000 ዓ.ም. ድረስ
የራሳቸው አስተዳዳራዊ ሥርዓት ፈጥረው ይኖሩ እንደነበር ይገመታል…፡፡“

(ፕ. ላጵሶ ጌ. ደለቦ 1983፤16)

በዚህ ላይ ዋና ዋናዎቹ ዑማውያን ብለው ቼሩል የተሰኘው ባህር ማዶ ጸሀፍ ካስቀመጣቸው አንዱ ጎፋ
መሆኑን ገልጸውታል፡፡ (በላነህ አሰጉ እንደጻፈው፤Cerulli, 1956, p 96)፡፡ ከመሳፍንት በኋላ ጎፋ በጠቅላይ ግዛት
በመደራጀት ለመጀመሪያ ጊዜ ከማዕከላዊ መንግሥት ቀጥታ ተጠርነቱ ወደ ታች ዝቅ ያለበትና በኋላ ወደ
አውራጃ ግዛትነት ተቀይሮም በኢትዮጵያ ካሉት 12 አውራጃዎች አንዱ እንደሆነ ታሪክ ያስረደናል፡፡ በቀዳማዊ
ኀ/ሥላሴ ዘመን የነበረውን የጎፋ ብሄረሰብ ከብረት የጠነከረውን ታሪክ በዚህች አጭር ጽሁፍ ለማቅረብ
ይከብዳል፡፡ (ቀዳማዊ ኀ/ሥላሴ 2 ኛ መጽሐፍ 328)

2. የጀግንነት መለኪያው በምኒልክ በቴመንግስት - ጎፋ

የጎፋን ብሄረሰብ ታሪክ ሲናጠና ከምኒልክ ዘመነ መንግሥት ቀደም ብሎ ያለና የተደራጄ፤ ማእከላዊነቱን የተበቀ
አስተዳደር መዋቅር ያለበት መሆኑን ከብዙ መረጃዎች አረጋግጠናል፡፡ ለምሳሌ ፕሮፌሰር ላጵሶ ጌ. ደሌቦ
ከ 1600 ዓ.ም.እስከ 1855 ዓ.ም. የነበረውን ታሪክ ዳስሰው በኢትዮጵያ ታሪክ መነሻ መጽሐፋቸው
ያስቀመጡት ከምኒልክ ዩኒፊኬሽን በፊት የተጠናከረ መንግስት ያለበት መሆኑን በግልጽ አስቀምጠዋል፡፡

እንድህ ብለው ጽፈው ነበር፤

“… በሌላ በኩል ከ 1696 እስከ 1855 ዓ.ም.ባለው ጊዜ በደቡብ የተጠናከረና ማዕከላዊነቱን የጠበቀ የሸዋ ንዑስ
ግዛት ተመስርቷል፡፡ በምዕራብ ክልል ጃንጀሮ፤ ሊሙ ኢናሪያ፤ ቦሻ፤ ጅማ፤ጎማ፤ጌራ፤ ከፋ፤ ኩሎ፤ ኮንታ፤ ሞቻ
የተሰኙና በደቡብ ምዕራብ ወላይታ፤ ጋሞ፤ ጎፋና ጎንሶ፤ በምስራቅ የሐረር ንዑስ ግዛት ከተማና የአውሳ
ሡልጣናዊ ንዑስ ግዛት፤ በሩቅ ሰሜን የትግሬ ቤጃዎች ወይም ቤኒአምር ግዛት፤ በሩቅ ምዕራብ ቤኒሻንጉል
ሡልጣናዊ ግዛት የነበረው የባል ጀብለዊ ንዑስ ግዛቶች የተፈጠሩ ሲሆን በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ልዩ ልዩ ንዑስ
አከባብ ግዛቶች በየአቅጣጫው የተፈጠሩበት ወቅት ነበር…“

(ፕ. ላጵሶ ጌ. ደለቦ 1983፤37)

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 7


በአጠቃላይ በታሪክ ምሁሩ አገላለጽ በአስራ ዘጠነኛው ምዕተ ዓመት አጋማሽ ላይ ከስድሳ በላይ የአከባባዊ
ንዑስ ግዛቶችና ልዩ ልዩ ማህበረሰቦች ነበሩ ካላቸው ውስጥ ጎፋ አንደኛው እንደነበረ ተገልጿል፡፡

3. አይበገረው የጎፋው ንጉሥ ካማ ዳዳ

አይበገረው የጎፋው ንጉሥ ካማ ዳዳ በሠራቸው የጀግንነት ገድሉ የጎፋው አፄ ቴዎደሮስ በሚል ታሪኩ
እነደሚወሳ ሁሉም የጎፋ ትውልድ ይስማማል፡፡ በተረጋጋው የንግስና ዘመናቸው በምወዱ ህዝቦች መሀል
ረጅም ጊዜ ከኖሩ በኋላ የምኒልክ ጦር አከባቢውን ተቆጣጥሮ ለመግዛት ይመጣል፡፡ በወቅቱ በቂ መረጃ
ከየአቅጣጫው ያገኘ ቢሆንም በተለዬ መልክ ከጅማው ንጉሥ አባጅፋርና ከዳውሮው ንጉሥ ሀላላ እንድህ
የሚል መልዕክት መጥቶለት ነበር፤ “አንቴ ጀግና እንደሆንክ እናውቃለን…’ጀግንነትና ጦርነት ሁሌ አይቀናም’፤
ራስህንና ህዝብህን ትጎዳለህ እባክህ እጅህን ስጥና ግብር ትከፋላለህ“ የሚል ነበር፡፡ አይበገረው ካማ ዳዳ ስለ
መልዕክቱ አመስግአቸው እንድህ የሚል መልስ ላከላቸው “ወንድ ለወንድ እንደት እጅ ይሰጣል እጄን በሰማይ
ላለው ለእግዝአብሔር እሰጣለው“ ደግሞስ “እኔም በሀገረ ንጉሥ ነኝና እንደት ለእርሱ እገብራለው?“
እንግድህ እኔ ለሱ “kana kaaca kasttole girana“ ሲለው በጣም ቅኔንና ንቀትን የተሞላ ሁለት ትረጉም የያዘ
አንድ ዐረፍተ ነገር ነበር የተናገረው፡፡ ትርጓመውም የመጀመሪያው ሰሙን “ውሻ፤ ጦር እና ቁንጫን እገብራለው“
የሚለው ጦር እገብራለው ማለቱ በጦር እዎጋዋለው ማለቱ ሲሆን፤ ወርቁ ደግሞ “የሀገረ ሰው የውሻ ራስ ጥሪ ቁንጫ
ነው የሉታልና ቁንጫን እገብራለው እንጅ እውነተኛ ግብር አልገብርም ማለቱ ነው“ እንደሆነ ይነገራል፡፡

አይቀረው የፈተናው እሳት መጣ ተዘጋጅቶ ሲጠባበቅ ነበረና የፃንጋውን አልባ ዙማ ምሽግና የውርጪውን
ምሽግ ሁለቱን ትቶ የመጀመሪያውን የፊት የወይደዎችን ምሽግ ይዞ በወይደ ዛፋ ዴሌ ዑማ/ ኦሞ ወንዝ
ወርደው በዳውሮ ተሻግሮ የመጣውን የሸዋውን ጦር ገጠመው፡፡ በቂ ዝግጅት በማድረጉ የምኒልክ ጦር
በሚመጣበት ወቅት ከፍተኛ መከላከል በማድረጉ በራስ ወልደጊዮርጊስ የተመራው በመጀመሪያ ዙር ተሸንፎ
ተመልሶ በሁለተኛ ጊዜ እንደገና ተጠናክሮ ብመጣም እንደገና ተሸንፎ ወደ ኋላ መመለሱን ታሪክ የስረዳል፡፡
በመሆኑም የምኒልክ ጦር በከፍተኛ ዝግጅት ተጠናክሮና ለሎችን ከባባዊ ሥልቶችን በመጠቀም በከባድ
መስዋዕትነት ጦሩን ለሦስተኛ ጊዜ በማምጣት ሲዋጋ የጎፋ ንጉሥ ካማ ዳዳም ከነ ጦራቸው እጅ ባለመስጠት
ስፋለሙ ቆይተው በመጨራሻም በመስዋዕትነት ደማቁን የጎፋን ታሪክ ጽፌው አልፈዋል፡፡

በውግያው ፊልሚያውም ድሎችን ብያስመዘግብም በመጨረሻውቃሉን ጠብቆ ለጎፋ ህዝብ ስምና ክብር
በማለት “ውርጪ ጭልዣ“ በሚባል በጎፋ ዞን ደምባ ጎፋ ወረዳ የሚገኝ እጅግ በታወቀው የጦር አውድማ
ወይም ግምባር ከነአጋሮቻቸው ጋር አብረው የጎፋ ጀግኖች የምኒልክንም ጦር በአይበገርነትም ተዋግተው፤
ለራሳቸውም በዚው የጎፋን ታሪክ በደማቅ የደም ቀለማቸው በመጻፍ በመስዋዕትነት ዘግተዋል፡፡ ትውልድ ግን
ከታሪክ ማህደር ስያስታውስና ስዘክር የኖራል፡፡

ለድሉም ምክንያት ከሆኑት ነገሮች ዋና ዋናዎቹ የጎፋ ካዎ ካማ ዳዳ አስቀድሞከአከባቢ ሽማግለዎችና ታዋቅ


ሰዎች እየመከረ እንደነበረ፤ በምዕራብ ኢትዮጵያ ከገነነው ከጅማው ነጉሥ አባ ጅፋር በመልዕክተኛ በቂ መረጃ
ይዞ፤ ከዎላይታው አንጋፋና ጦረኛ መሪ ከንጉሥ ጦና ጋር ስለሁኔታው ገና የምኒልክ ጦር በምዕራብና
በደቡባዊው ሸዋ እያለ ሰምቶና ሀሳብ ተለዋውጦ በመኖሩ፤ እንድሁም ከዳውሮ ንጉሥ የአማች በቴሰብ ከመሆኑ
የተነሳ በቂ መረጃ በማግኘቱ ጦሩን ለመመከከትና እጅ ላሌመስጠት የጦር ሥልት፤ የመሳሪያ ሁኔታ የውጊያ
ፈረሶችን ጨምሮ፤ሠራዊት ምልመላ፤ የኋላ ደጀን ጦርም ጭምር አዘጋጅቶ በመግጠሙ ድልን ማግኘት
ችለዋል፡፡ በመጨረሻም በተደጋጋሚው ጦርነት እጅ ሳይሰጥ ተፋልመው ከሁሉም ሠራዊቱና ለሎች አዝማች
እራሻዎች ጋር በመስዋዕትነት በማለቃቸው ወንድነቱንና ጄግንነቱን እንድሁም አብረው የተሰለፈው ጦር
ጀግንነትና አለመካካዳቸውን ከጦርነቱ በኋላ የሸዋ ጦር የካዎ/ንጉሥ ካማ ዳዳን ዝናን ወደ ምኒልክ በቴ-

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 8


መንግስት ወስዶ እንድያናኘው ምክንያት ሆኗል፡፡ እስከ ዛሬ ድረስ ትውልድ አልፎ ትውልድ ሲተካ ይህ ድነቅ
ጀግንነት እየተወሳ መጥቷል ነገም ይኖራል፤ ይወሳል፡፡ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ጎፋ የሚለው ስም በምኒልክ
በቴመንግሥት ታውቆ ቀረ፡፡

4. ጎፋ በምኒልክ በቴ - መንግሥት ሶስተኛው ወንበር እስከ መያዝ

ጎፋ በማዕከላዊው መንግሥት እጅግ የሚታወቅና ተጽዕኖ ፈጣርነቱን ከጎፋው ንጉሥ ካማ ዳዳ ምስትም ማየት
እንችላለን፡፡ ካማ ዳዳ በመስዋዕትነት የጎፋ ህዝብ ታሪክ በጀግንነት ህያው አድርጎ ሲያልፍ ታሪኩም ህያው ሆኖ
በዚያው እጅግ ናኝቶ ወደ አዲስ አበባ የንጉሥ በቴ- መንግስት ሰተት ብሎ ገባ፡፡ የሸዋው ጦር ጎፋና ለሎች
የኢትዮጵያ ግዛቶችን ከተቆጣጠረ በኋላ በ 1908 በምኒልክ በቴመንግሥት የዙፋኑ አማካሪዎች (ካውንስል)
ሲያቋቁም ከተሰዩሙ ሚኒስቴሮችና ዋና ዋና ከሆኑት ያነ ተስፋፊ ጦሩ በሚዘምትበት ወቅት ከፍተኛ ተጋድሎ
ከፈጸሙትና ሰፋፊ ግዛቶች በማምጣት ለሀገረ መንግሥት መረጋጋት አደራጅቶ ነበር፡፡ በዚህን ጊዜ የጎፋ ገኔ
(ንግሥት) አቅለሲያ በሸዋው በቴመንግሥት ቦታ ለመያዝ በቃች፡፡ በወቅቱ ጄግናና ታዋቅ ከነበረው ከነ ወላይታ
ንጉሥ ጦና ጋር በመሆን ወንበር ተጋራች፡፡ ንጉሤ ነገሥቱ ለቆራጥና በደማቸው ጀግንነት ላላቸው ሰዎችና
አከባቢዎች የተለየ ትኩረት የሚሰጥ በመሆኑ የጎፋ ጦር አይበገረትና የጎፋ ገኔ (ንግሥት) አቅለሲያ የነበራትን
አጠቃላይ ሁነታ በማየት ከሚትርባት “ሜላ” ግዛታቸው (በአሁኑ ሰዓት በጎፋ ዞን ዛላ ወረዳ ውስጥ የሚገኝ)
ወደ በቴመንግሥት ወክለው እንድገቡ ተደርገዋል፡፡ በኋም አፄ ምኒልክ ከበቴመንግስታቸው ወጥተው አድዋ
ሲዘምቱ በቴመንግስታቸውንና አዲስ አበባ ከተማን ለአይበገረውና ጀግናው ለወላይታ ካዎ (ንጉሥ) ጦና ሀደራ
ሰጥተው ሄደው ነበር፡፡ ታድያ በዚህ ወቅትም የጎፋ ገኔ (ንግሥት) አቅለሲያ የበቴመንግሥት ሚናዋ እንደቀጠለ
ታሪክ ያወሳል፡፡

ቀደም ብላ ኃይለኛው ንጉሥ ካማ ዳዳ (ባለበቷ) ከተሰዋ በኋላ ከካማ ዳዳ የወለደችውን አንዷን ልጅ አይካን
ይዛ ሜላ ወደ ሚባል ሥፍራ ላይ ግዛት ወስዳ ትኖር እንደነበረ ይነገራል፡፡ በዚያም ብዙ ሥራዎችን እንደሰራችና
ከፍተኛ የሆኑ የመብት ጥያቀዎችን በማንሳት ትሟገት ነበር፡፡ የመጀመሪያ ስሟ ሻሹሬ ሲሆን በኋላ ክርስቲና
ተነሳችና ስሟ አቅለሲያ (ጎፋ ጌኖ አቅለሶ) ተባለ፡፡ በዚህም በክርስትናው ዓለም በግዛቷ ሜላ ብዙ ወጣቶችን
ሰብስባ ከሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል መምህራንን በመቅጠርና ቅስናን በማስተማር በአከባቢው አጠራር ሜላ ቄሴ
በማለት የሚታወቁትን ዛሬ ላይ ትልቅ የሆኑትን የሃይመኖት አባቶችን (ቄሳውስትን) አፍርታም ነበር፡፡

አንድ ወቅት በዚያ “ሜላ” በራስዋ ግዛት እያለች ለምኒልክ አስተዳደር ጥያቄ አቅርባለች፡፡ ንግስት አቅለሲያ
ተሟጋችና ለመብት ቀናዕ እንደሆነች አፄ ምኒልክም ዕውቅና የሰጣት ስለመሆኑ ከታሪክ ማስረጃ መመልክት
እንችላለን፤

“አፄ ምኒልክ ለደጃዝማች ለማ መጋብት 24 ቀን 1900 ዓ.ም በፃፉት ደብዳቤ የጎፋ ገኔ በዛላ
ውስጥ ያለኝ ረዕስት ተወሰደ በደል ደረሰብኝ ብለው ደብዳቤ መጻፋቸውን በመግለጽ
ደጃዝማች ለማን ጎፋ ገኔ አትድረስባት ብለዋቸዋል፡፡”
(በላይነህ አሰጉ 2009፤ 44)

በተጨማርም ዶናልድ ዶሃም የሚለው ጸሐፍ መምህር በላይነህ አሰጉ እንደጠቀሱ ከሹመቷ አኳያ በምኒልክ
በቴመግሥት በመደበኛነት ግብር ከሚጠሩ መኳንንት አንዷ እንደነበረች ተጽፏል፡፡ (ዶናልድ ዶሃም ገጽ 44
በመ/ር በላይነህ አሰጉ፤ 2009፤44-45 እንደተጻፈው)

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 9


በሌላ በኩል ያልታወቀው ምድር ድርሳን ጸሀፊ የሆነው አሳሽ ስቲንጋድ ጎፋ ሲደርስ ወ/ሮ የጎፋ ገኔ (ንግሥት)
አቅለሲያ እንዳገኘ ጽፎ እናያለን፡፡ እንድሁም ስሟ በደስታ ክዳኔ ወልድ አማርኛ መዝገበ ቃላት ጎፋ ገኔ ይልና
የጎፋ ንግሥት ይላታል (ደስታ ክዳኔ ወልድ፤294; በላይነህ አሰጉ 2009፣44፤እና Unknown land through
Abyssinia,285)፡፡ እድሁም ጎፋ ገኔ/ አቅለሲያ በዘውድቱ በቴ-መንግስት የነበራትን ተቀባይነት አስመልክቶ
ደጃዝማች ከበደ ተሰማ የታሪክ ማስታወሻ በሚለው መጽሐፋቸው ውስጥ ከንግሥት ዘውድቱ ጋር በዙፋን
መሶብ ከሚቀመጡት ሶስተኛ ተራ ከተመደቡትና ከንግስትቱ ዙፋን በስተ ቀኝ ከሚቀመጡት አንዷ ወ/ሮ ጎፋ
ገኔ/ አቅለሲያ መሆኗን ጽፈዋል (ከበደ ተሰማ፤ 106)፡፡ በመሆኑም ጎፋ የሚለው ስም በምኒልክ ቤቴ- መንግስት
እንግዳ ያልሆነና ዕውቅና ያተረፈ ሆኖ ቆይቷል፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ ዛሬም ጀግና ነው፡፡ በመጨረሻም አይበገረዋ
የጎፋ ገኔ ዕድመዋን ሙሉ አዲስ አበባ ካሳንቺስ ቶታል አከባቢ ኖራ በ 1926 ዓ.ም ሞታ በዑራኤል በቴክርስቲያን
ተቀበረች፡፡

5. የካማ ዳዳ ፈረስና አሌክሳንደር ቡላቶቪቺ

ነገሩ እንድህ ነው፤የጎፋ ካዎ ካማ ዳዳ ወግ አዋቅ፤ አስተባባሪ፤ጦረኛ፤ብቻም ሣይሆን ሀብትን በመፍጠርም


ለኢኮኖሚ ግምባታ ትኩረት የሚሰጥም ነበር፡፡ በተጨማርም የጎፋ ለሎች ንጉሦችን በማስተባበር የተረጋጋና
ሰላማዊ አከባቢ የመፍጠር ሚናውም ከባድ ነበር፡፡ ለልማት ብቻ ሳይሆን የወሰን ችግሮች እንዳይፈጠሩና ጠላት
ሲመጣና ከማዕከላዊ መንግሥት ጥሪ ሲቀርብ የሚመልሱበት አግባብም እጅግ የተለየ እንደ ነበረ የታሪክ
ምስክሮች ብዙ ናቸው፡፡

በተረጋጋው የንግስና ዘመናቸው በሚወዱ ህዝቦች መሀል ረጅም ጊዜ ከኖሩ በኋላ ለጎፋ ህዝብ ስምና ክብር
“ወንድ ለወንድ እንደት እጅ ይሰጣል እጄን በሰማይ ላለው ለእግዝአብሔር እሰጣለው“ በማለት “ውርጪ
ጭልዣ“ በጎፋ ዞን ደምባ ጎፋ ወረዳ ወስጥ የሚገኝ አከባቢ ወይም የጦር ግምባር ከነአጋሮቻቸው ጋር አብረው
የጎፋ ጀግኖች የምኒልክንም ጦር በአይበገርነት ተፋልመው፤ ለራሳቸውም በዚው የጎፋን ታሪክ በደማቅ የደም
ቀለማቸው በመጻፍ በመስዋዕትነት ዘግተዋል፡፡ ትውልድ ግን ከታሪክ ማህደር ስያስታውስና ስዘክር የኖራል፡፡

ይህን ተከትሎ የአዔ ምኒልክ ሹም የነበሩት ራስ ወ/ጊዮርጊስ አከባቢውን ሲቆጣጠሩ ስለ የጎፋ ንጉሥ ካማ ዳዳ
ፈረስ ወረውን ይሰሙታል፡፡ ይህ ተዓምረኛው ፈረስ በአሁኑ ሰዓት በሰለጠኑ ሀገሮች የሰለጠኑ አነፍናፍ ውሻዎች
ከሚያገለግሉት በላይ የጎፋን ንጉሥ ካማ ዳዳን ሲያገለግል እንደነበረ ይነገራል፡፡ በወቅቱ ይህ ፈረስ
አቅጣቻዎችን ይለያል፤ ስመሽና ከባድ ዝናብ የሚጥልበትን ሁነታ ሲመጣ ምልክትን ማሳየት ይጀምራል፤
ከንጉሡ ውጭ ለሎች እንድቀመጡ ጨርሶ አይወድም ያምጻል፤ ከልክ በላይ የተገራ ፈረስ ከመሆኑም በላይ
እነደ ዘመኑ ባለሥልጣን ጠባቂ (ጋርድ) ከንጉሡ አጠገብ ለመለየት አይፈልግም ነበር ይላሉ የአከባቢው ታሪክ
አዋቅ የዕድሜ ባለጼጎች፡፡ ታሪኩ ያስደንቃል በጎፋ ምድር ሰውም ሆነ እንስሳ ሁሉም ጀግንነት በደማቸው ያለ
የሚያስመስል ነው፡፡ እንግድህ ይህን ተከትለው ራስ ወ/ጊዮርጊስ በሁነታው ተገርመው የራሳቸውን በቅሎ
በመተው የጎፋ ንጉሥ ካማ ዳዳ ፈረስን በራሳቸውን እንደገና በማላመድ በመጨረሻም ይህንን ፈረስ ይጠቀሙ
እንደነበር ይነገራል፡፡ ታሪክ ጸሐፊዎች እንደሚገልጹት ይህ ፈረስ በወርቅና በብር ዕቃዎችም እጅግ ያገጠ
እንደሆነ እንረዳለን፡፡

በመጨረሻም ይህ ፈረስ ሄኖክ ስዩም (ተጓዡ ጋዘጠኛ) አሌክሳንደር ቡላቶቪቺ ከአፄ ምኒልክ ሠራዊት ጋር ብሎ
የፃፋቸውን መጽሐፍ ዶክተር አምባቸው ከበደ ተርጉመውት በአዲስ አበባ ዩኒበርሲቲ አሳትሞ ለንባብ
አብቅተዋል በሚለው መጽሐፋቸው ላይ ይህ እጅግ ውብ የሆነውና ያገጠው ፈረስ ከራስ ወ/ጊዮርጊስ
ለአሌክሳንደር ቡላቶቪቺ በግምቦት 23 ቀን 1892 ዓ.ም. በሥጦታ ተበርክቷል ይላል፡፡ ከዚህ የተነሳ በሁሉም

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 10


ሥፍራዎና ጉዳዮች የሸዋው ጦር የጎፋን ብርቱ ተዋግነትና ጀግንነት ሲያደንቁ እንደነበረ ይነገራል፡፡ (ሄኖክ ስዩም
(ተጓዡ ጋዘጠኛ) በ 2013፤)

2.1.3 ደማቁ ታሪክ - ጎፋና የኢትዮጵያ የጦር አውዴ ግምባሮች

በጎፋ ህዝብ ታሪክ ሲታዎሱ የሚኖሩ ዋና ዋና የኢትዮጵያ የጦር አውዴ ግምባሮችን ስናስብ የዚህ ብሄረሰብ
ትልቅነትና ሀገር ወዳድነቱ፤አስተዋይነቱ፤ስልጡንነቱ ፍንትው አድርገው ያሳያሉ፡፡ ምናልባትም የዚህ ሁሉ
መነሻ የጎፋ ህዝብ የማዕከላዊ መንግስት ጥሪ ተቀብለው ፈጣን ምላሽ መስጠትና የኢትዮጵያዊነት ጥግ
በማሳየት እንደ ንብ 516 ኪሎ ሜትር በእግራቸው በመትመማቸው ነው፡፡ በመሆኑም በአዲስ አበባ የጎፋና
አከባቢዋ ልጆች መጥተው እንድሰፍሩ ቦታ/ሰፈር እስከ መሰጠት የደረሰበት ሁነታን ሲንመለከት ነገሩ በምን
ያህል የአስተሳሰብ ልዕልና እንደተፈጸመ ያስገርመናል፡፡ በዛሬይቱ ኢትዮጵያ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
ለጎፋና ኦይዳ ብሔረሰብ ባህል ማዕከል ግምባታ ቦታ የሰጡትን ስንመለከት በተለይ ከጎፋ ብሔረሰብ አኳያ
ታሪክ ራሱን ለ 2 ኛ ጊዜ ጊዜውን ጠብቆ እየደገሜ ያለ እውነተኛ የታሪክ ማስታወሻ ነው ያስብላል፡፡

በአድዋ ጦርነት የጎፋ ጦር በደጃዝማች ባሻህ አቦዬ እየተመሩ ተዋግተዋል፡፡ ከአድዋ ጦርነት በኋላ የጥቁር
ህዝቦች ችቦ ሲለኮስና የአድዋ የድል ብሥራትታላቅ ሰልፍ በንጉሥ ነገሥቱ ፊት በክብር ስበሰር የጎፋ ጦር የሰልፉ
አድማቂ የክብር ባለበት ሆኖ ተሰይሟል (ሄኖክ ስዩም (ተጓዡ ጋዘጠኛ) 2013፤166) በወቅቱ ለጎፋው ጦር
የተሰጠው ዕውቅና እጅግ የሚያስገርምና የሚያስደንቅ ሆኖ አልፏል፡፡ ለሎች ጠለቅ ሉትን በሌላ ጊዜ መመለከት
ይቻላል፡፡

ከአድዋ ጦርነት ውጭም የጎፋ ህዝብ ጀግንነቱንና ሀገር ወዳድነቱን የሚገልጹ ብዙ ለሎች ኢትዮጵያ
ያሳለፈቻቸው ጦርነቶችም አሉ፡፡ ከአነሱም በተለይ ከጦርነቱ በኋላ በአከባቢው ዋና ዋና ከሚነገሩ የጦር
ግምባሮች እነ ማይጨው፤ኦጋደን፤ጎንደር፤ዶጋሌ፤ሰገሌ የሚባሉ ይጠቀሳሉ፡፡ አንዳንድ የጦር አውዴ ግምባሮች
በአከባቢው ቋንቋና ዘዬ በቀጥታ ባለመጠራት ተቀይረው ስጠሩም እንሰማለን፡፡ የእነዚህን ማብራርያ በለላ
ወቅት ተያያጅ ጥናቶችን በማድረግ የሚቀርብ ይሆናል፡፡ ነገር ግን አሁን ጦሩን ወይም አጠቃላይ ከጎፋ
የዘመቱትን የዘማቾች ሁነታና የመሩት የጦር መሪዎች በአጭሩ ስንመለከት በዋናነት የጥቁር ታሪክ በደማቅ
የተጻፈበት ጦርነት የአድዋ ጦርነት በደጃዝማች ባሻህ አቦዬ፤የኦጋዴን ዘመቻ በደጃዝማች አበበ ዳምጠው
እተመሩ ተዋድቀዋል በለሎች ግምባሮች ለአብነት የማይጨው፤የጎንደር፤በዶጋሌ፤ የሳጋሌ ወዘተ በእኔ ማን
እንደሆነ፤ የብሄረሰቡን ለማዕከላዊ መንግስት ምላሽ አሰጣጣቸውና ለሀገራቸው አንድነትና ዳር ድምበር
መከበር መዋደቅ ከብረት የጠነከረ ጀግንነት ያሳዩት ሌላ ብዙ ጥናት ይጠይቃል፡፡ በነገራችን ላይ አያንዳንዱ ጦር
ግምባር በአከባቢው የቋንቋ ልዩነት፤ ዜየና የረጅም ጊዜ ታሪክ ከመሆኑ የተነሳ ዘማቾቹ እየፎከሩና እየመሰከሩ
ኖረው ሰያልፉና በሌላ ትውልድ ሲተካ ወደ እኛ ዘመን የደረሰው አጠራር በትንሹ ስንመለከት ለአብነት፤

ኦጋዴን የሚባለውን “ዑጋዴ/ ውጋዴ ዖላ” ይላሉ ይህ ጦርነት የሶማሊያ ወራርዎች የኢትዮጵያን ድምበር
ጥሰው በገቡበት የተደረገው የቅርቡ ሳይሆን የሁለተኛው ጣሊያን ወረራ ወቅት በ 1936 በጄነራል ሮዶልፎ
ጊራዚያኒ የተመራውን ጦር ለመመከት ነበር የጎፋ አባቶች የተመሙት፡፡ በሚገርም ሁነታ ያኔ አባቶች ዘመቻ

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 11


ሲሄዱና ሲመጡ በአጭሩ በጦርነቱ ወቅት የተወለዱ ልጆች ስም “ውጋዴ” ተብለው በመሰየማቸው ይህ
የመጠሪያ ስም እስከ ዛሬ ድረስ በጎፋ ምድር አለ፡፡

የሰጋሌ ጦርነት ደግሞ “ሳጋሌ ኦላ” እየተባለ ይጠራል፡፤ የታሪክ ፃሀፊዎች ይህ ጦርነት የእርስ በርስ ጦርንትና
ከአድዋ ጦርነት ቀጥሎ የተደራገ ትልቁ ጦርነት ይሉታል፡፡ የጎፋ ብሄረሰብ በዚህ የሳጋለ ጦርነትም ማዕከላዊውን
መንግስት ደግፈው ከጠላት ጋር ተፋልመዋል፡፡ ሳጋሌ ከአዲስ አበባ 40 ማይል ርቀት በስተ ሰሜን በኩል የሚገኝ
ሥፍራ ሲሆን በጥቅምት 27 /1916 ንግሥት ዘውድቱን በመደገፍ በዚህ ጦር ተሳትፈዋል፡፡

የማይጨው ጦርነት በራሱ ‘’ማይጮ ዖላ’’ እተባሌ ይጠራል፡፡ በዚህ ጦርነት ላይም የጎፋ ብሄረሰብ ከፍ ያለውን
መስዋዕትነት ከፍሏል፡፡ በተለይ የዛላ ካዎ ወይም ንጉስ ፊኖ አማዶ ከነሙሉ ጦራቸው ጋር ዘምተው እዚያው
ማይጨው ለውድ ሀገራቸው ኢትዮጵያ እንደተሰው መምህር በላይነህ ገ/ማሪያም በመጽሀፋቸው ጽፈዋል፡፡
የ 1936 ቱ የሁለተኛው ኢትዮ - ኢታልያ ጦርነት በንጉሥ ኃይለ ስላሴ ዘመን ነበር፡፡

በአጭሩ ሲጠቃለል በረጅሙ የኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የጎፋ ብሄረሰብ ሚና እጅግ የጎላ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡
ለሎች ተያያዥ ጀብዶችና ታሪኮች ለሌላ ጊዜ ስንተው ጎፋ የሚለው ስም በምኒልክ በቴመንግሥት የጀግንነት
መለኪያ የሆነው ከእደዚህ ድንቅ ታሪኮች የተነሳ መሆኑን እንገነዘባለን፡

2.1.4 ማጠቃለያ

የጎፋ ብሔረሰብ ከጥንት ጀምሮ ነባር፤ ገናናና ታዋቂ በመሆኑ በራሱ ግዛት ተደላድሎና ሰፍቶ ያለ መሆኑን፤
በኋላም ከምኒልክ ዩኒፍኬሽን ጀምሮ እስከ 1934 ዓ.ም. የጠቅላይ ግዛት ዘመን ድረስ ተጠርነቱ ለማዕከላዊ
መንግሥት በቀጥታ እንደሆነ፤ ከ 1934 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ደርግ መንግሥት ውድቀት ድረስ ደግሞ በአውራጃ
ደረጃ ተደራጅቶ ከፍታውን ሳይለቅ እንደቆየ ውብ የሆነውን የታሪክ ሰንሰለቱን በአጭሩ ለማየት ችለናል፡፡

ከ 1983 ዓ.ም. ከደርግ ውድቀት ተከትሎ ቦታ በያዘውም መንግሥት አደረጃጀቱ ከአውራጃው ጋር የሚመጣጠን
ልሆን የሚችለው ዞን ነውና በዞን ደረጃ ለመደራጀት የመብት ጥያቄዎች በየጊዜው እዳቀረበና እንደታገሌ
ይሄው ረጅሙን 27 ዓመት በትግል አሳልፈዋል፡፡ በቅርቡ የሀገራዊ ለውጥ ተከትለው የመጣው መንግሥት
የቀደመውን የጎፋን ታሪክ ያውቅ ይመስል ይህን የጎፋን በዞን የመደራጀት ዕድል ፈቅዷል፡፡ በመሆኑም የጎፋና
አከባብው ህዝብ ለለውጡ መንግሥት የተለየ ክብር አለው፡፡ ወንድም የሆነውን የኦይዳ ብሔረሰብን ከራሱ ጋር
በመያዝ በዞን ደረጃ ከፍ ብሎ በመደራጀት በየወረዳዎች ተሰራጭተው ለየቅል ስፘፘጡ የነበሩትን የጎፋ
ብሔረሰብ፤ሀብትና ጉልበት እንድሁም ኦይዳን ጨምሮ ወደ አንድ አሀድ ለማሰባሰብ ዕድል በማግኘት የከፍታ
ጉዞውን ገና አሃዱ ብለው ጀምረዋል፡፡ በዚህ ላይ ብዙ ረፈደብን ብንልም አንድ ተስፋ አለን ይህም ታሪክ ሁል
ጊዜ ራሱን ይደግማል ስለምል ምናልባት በቁጭት ጠንክረን ከሠራን /ከሰሩ በአጭር ጊዜ በከፍታው ላይ
መውጣትና የቀደሙ ብዙዎችን ልንደርስ እንችላለን፡፡

(በመ/ር ዘለቀ ዶሳ ሞርጋሞ፤ ጳጉሜ 2014)

2.2 በጎፋ የሴቶች ሚና አጭር ታሪክ


በህዝቡ በቀደምት ግዜያት የራሳቸውን አሻራ ያሳረፉ የተለያዩ ሴቶች በታሪክ ይታወሳሉ፡፡ እነዚህም በዋናነት
በቀደምት አገዛዝ ሥርዓቶች ትልቅ ቦታ የነበራቸው በመሆናቸው በብዙ ቦታዎችና አካባቢዎች ተፅዕኖ ፈጣሪ
ነበሩ፡፡ ተፅዕኖዋቸውም ነገስታቶችን ውሳኔ ከማስቀየር ባለፈ ወገናዊነትና ጠቃሚ አስተሳሰቦችን

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 12


በማመንጨትም ጭምር ይታወቃሉ፡፡ ይህን የሚገልጽ በጎፋ አንድ ብህል አለ ‹‹Maci Maqqin Caarethi
Kanthenna››ይህም ሴቶች የማማከር እውቀትና ብልሃት እንዳላቸው ያሣየናል፡፡ በተጨማሪም ሴቶች
በአንዳንድ አካባብዎች የጠንካራ መንፈስ ባለቤት ናቸዉ፡፡ መገለጫዉንም ስንመለከት በዱሮ ጊዜ በዛላ አካባቢ
እሊሊ በተባለ ስፍራ ንግስት የነበረችዉ የ‹‹እሊሊ ንግስት›› የአስቸጋሪዉ ንጉስ ትዕዛዛትን በጥበብ የመፍታት
አቅም የነበራት እንደሆነና ኃይል በተሰማትም ግዜ ረግማ የማድረስ ጉልበት አላት ይህም በአንድ ወቅት ንጉሱና
ንግስትቱ ተጣልተዉ ስረጋገሙ ንጉሱም

‹‹አንቺ ሰዉ ነሽ ግን በተቀመጥሽበት የድንጋይ አምድ ሁኝ ስላት›› የሽሌ ጋናዜ ሆና እንደቀረች እንድሁም


ንግስትቱ መልሳ እንድህ ስትል ረገመችዉ

‹‹አንተ ሰዉ ነህ ግን ባለህበት የሚያቃጥል ዉሃ ሆነህ ፈልተህ ቅር›› እንዳለችዉ በሄደበት የሚፍለቀለቅ ብልቦ
ፍል ዉሃ ሆኖ እንደተገኘ አፈ-ታሪክ ይናገራል፡፡ በጥንት ጊዜ ‹‹ጋሎ ፃማቶ (Gaalo Xamaato)›› ተብላ
የምትታወቅና ለነገስታት ቀረቤታ የነበራት አንድት የታወቀች ብርቱ ሴት ነበረች ዋና ተግባሯም ጎበዙን በማጀገን
እንድሁም ሰነፉን በንግግሯ ነቁራ በመተቸት ጎፋ ከጠላት ጋር በነበራት ዉጊያ ከነገስታት ጎን በመሆን ከፍተኛ
የማነሳሳት ስራዎችን ስትፈፅም እንደነበረች የታሪኩ አዋቂ አባቶች ይገልፃሉ፡- በአንድ ወቅት ንጉሱ ጠላትን
ለመዋጋት ተዋጊዎችን ለማሰባሰብ ስፈልግ ‹‹ጋሎ ፃማቶ›› እንድህ ስትል ለአዋጅ ነጋሪዉ መልዕክቷን ሰጠች

‹‹ጉፖዋ ጋንፃዳ ጉፒያ ፓራ ቶጋዳ ጉምቦ ቶራ ኦይክዳይሶ ኦላስ ጋጦ ጋጦ›› በማለት ጎበዙን ስታጀግን

ፈሪዉንና ድንጉጡን ደግሞ ‹‹ጉሳዉ ጉቱማጬያዉ ጉቶይ ቃፅን ሳጼያይሶ ሾጭ ዎጣ ኦይቃዳ ሞርናታስ ጌምቦ
ቆፃናዉ ጋጣ ጎቻ›› በዚህ ጊዜ አብዛኞች በቤተ-መንግስት (kawo gadho) ብገኙም ይታወቁ የነበሩ አንዳንዶች
አልተገኙም ነበር፡፡ ‹‹ጋሎ ፃማቶም (Gaalo xamaato)›› ቀጥ ብላ ወደ መጠጥ ቤት ስትሄድ አገኘቻቸውና
ልታናግራቸው ስትፈልግ ድምፅ ያለዉን ፈስ ፈሳችባቸው ተደናግጠውም አንደት ሴት ሆነሽ በወንድ ፊት
ወይም በእኛ ላይ እንድህ ታደርግያለሽ ስሏት

‹‹እናንተማ የምን ወንድ ናችሁ ወንዶች የሆኑማ በዚህን ሰዓት በጦር ሜዳ የጠላትን ብልት ስገፉ

እናንተ በኮማሪት ቅጥ ስር ተጠግታችሁ ፈስ ትጠጣላችሁ››

ይህን ንግግሯን እንደ ሰሙም የያዙትን ጥለዉ ወደ ክተቱ ዘመቻ ተመሙ ይባላል፡፡ በተጨማሪም ይህች ሴት
ጋዜ ማስቃላ ስደርስ ወደ ንጉሱ ቀርባ ንጉስ ሆይ ገዜ ማስቃላን እንዴት የሚወሳ ገድል ሳንጨብጥ እናከብራለን
ብላ አማከረችዉ በዚህም ንጉሱ ጎበዛዝትን ድል እንድያመጡ ይገፋፋቸዉ እንደነበረና አንዳንዶችም ከባባድ
አውረዎችን (አንበሳ፤ዝሆን፤ጎሽ፤ነብር) በመግደል ትኩስ የፊት ገጽታን ስያቀርቡ አንዳንዱም ደግሞ ጠላትን
ገድሎ የተገፈፈ ብልትን በንጉሱ ፊት በማምጣት ከንጉሱ የክብር ስጦታ (yallo yoosha) በመቀበል የሚወሳ
ሁኔታዎችን በመፍጠር አዲሱን ዘመን በሙገሳ እና በደስታ እንድቀበሉ ታደርግ ነበር፡፡

ባለፉት ዘመናት ሴቶች በብዙ ሁኔታ በተመረጠ አኳኃን ለትዳር ይታጫሉ ይህም የሚሆነው በአብዛኛውን
ህዝብ ዘንድ በጋብቻ ትስስር ዝምድናን መፍጠር ዋናው ጉዳይ ሆኖ በትስስሩ ጥንካሬና ብርታትን እንድሁም
የገዘፈ ድጋፍ እንድኖር ያስችላል፡፡ በመሆኑም ጋብቻን መፈፀም በብዙ መልኩ ጥቅም ይኖረዋል፡፡ በብሔረሰቡ
በዋናነት ለትዳር ትጭጭት ወሳኝ የሆኑ ጉዳዮች አሉ፡- እነዚህም በዋናነት የሴቷ ብርታትና ታታሪነት
የተመስከረላት መሆኑ የታወቀ ይሆናል፡፡ ለአብነትም ከትዳር በፊት ታታሪነቷን ማሣያ የሆኑ አልባሣትን
ማዘጋጀት ወሳኝ ነገር ነው፡፡ በመቀጠልም በማህበረሰቧ ትሁት መሆኗ ልነገርላት የተገባ በመሆኑ በብዙ መልኩ
ተፅዕኖ ፈጣሪ ሴቶችን ተመራጭ ያደርጋቸዋል፡፡

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 13


ለላው ደግሞ ሴቶች ለፖለቲካዊና አስተዳደራዊ ሥርዓት ትስስር ወሳኝ ናቸው፡፡ ለአብነትም የዳውሮ ካዎ ሀላላ
ለጎፋ ካዎ ዳዳ ካማ ልጁን ማሌ አቅለሰን በመዳር ከፍተኛ የጋብቻ ዝምድና በመፍጠሩ ከጎፋ ካዎ ድጋፍ
ማግኘት ችሏል አብረው በመሆንም የምኒልክን ተስፋፊ ጦር በመመከትም ይታወቃል፡፡ ማሌ አቅሌሴ ታዋቅው
የጎፋ ንጉስ ዳዳ ካማ ሚስት የነበረች በመሆኗ ከንጉሱ ጋር በመሆን የተለያዩ ውሣኔዎችን በመወሰንና
በአስፈላጊ ጉዳዮች ዙሪያ በማማከርም የታወቀች ናት፡፡ እንደዚሁም ዳዉሮ ንጉሷ ‹‹ካቲ ዳዶ›› ተሰዉቶ
በተስፋፊው ምኒልክ ጦር በምትያዝበት ጊዜ ልጁ በእድሜ የሰባት ዓመት ህፃን ስለነበር የንጉሱ ምስት የሆነችዉ
የዛላ ካዎ ልጅ ‹‹ዳምማዊት ገኒ ሻሾቴ›› ዳዉሮን በእንደራሰነት አስተዳድራ ነበር (በላይነህ አሰጉ፣2009 ዓ/ም)፡፡

እንድሁም እንደ አንዳንድ መረጃ ሰጪዎች ካዎ ካማ ዳዳ ከወራሪው ጦር ጋር እየተዋጋ በውርጭ ላይማ ጦር


ሜዳ ሲሰዋ ወራሪው ሠራዊት አካባቢውን እስከሚቆጣጠር ድረስ ማሌ አቆለስ ወደ ሜላ (ዛላ ወረዳ) በመሄድ
እዚያው በመመሽግና ጠንካራ ጦር በማደራጀት የዛላ ካዎ አባይነህ ፈኖ ጦር አካባቢወን እንዳይቆጣጠር
በመመካት ለዘመናት በጀግንነት የታወቀች መረ ሴት ነበረች፡፡

ለሎችም ደግሞ ተጠቃሽ ሴቶች አሉ፤- ከእነዚህም ውስጥ ማሌ ሻራፌ ተጠቃሽ ናት፡፡ ይህች ሴት የማሎ ካዎ
ማዳ ፆና ዘር እንደሆነች ይነገርላታል፡፡ በመሆኑም ሳውላ ከተማ ኑሮዋን በማድረግ በከተማዋ የታዋቀ ቡና ቤት
በመከፈቷ ስትታወቅ በሆደ ስፈነቷና በእንግዳ ተቀባይነቷ በሁሉም ሰው ስሙዋ የታወቀ ነው፡፡ እንድሁም የባዮ
ካዎ ጉጃ አሻ ሚስት የሆነችው ማሌ/ጎዳተ/ሞርካሜ ቶጋ (የእራ ካዎ ዜማ ቶጋ ልጅ) ሲትሆን ንጉሡን
በማማከርና ከንጉሡ በታች ትዕዛዛትን በመስጠትና በማስፈፀም በጠንካራ አመራር ሰጭነት ትልቅ ሚና እንደ
ነበራት ትወሳለች፡፡

2.2.1 የማዕረግ ስም አሰጣጥና አጠራር

በጎፋ ሴቶች እንደተገኙበት ዘረ ሐረግና በመሰረተችዉ ትዳር የተለያየ የማዕረግ ስም አጠራር ይኖራቸዋል፡፡
በዚህም መሠረት ሴቷ የምትጠራበት አጠራር ከየትኛው ዘር ሐረግ እንደሆነችና በየትኛው ስልጣን ደረጃና
ዓይነት እንደሚትገኝ በሚገባ ይገልፃል፡፡ በዚህ መሠረት የማዕረግ ሥም ማግኘትና በሁሉም ህብረተሰብ ክፍል
በዚህ ስያሜ መጠራት ክብርን ያስገኛል፡፡

ወደ ስያሜና አጠራሩ ስንመለስ ሴቶች ከተወለዱበት ዘር ሐረግ አንፃር ብቻ የሚያገኙት የማዕረግ ስም አለ፡፡
ይህ ስም ማሌ /MaalIe/ ይባላል፡፡ በጎፋ ብሔረሰብ ይህ ሊገኝ የምችለው ''ጎሻና ወይም አይካ'' ዘር ሐረግ ስኖር
ብቻ ነው፡፡ የማዕረግ ስም አጠራሩ በየትኛውም ጋብቻና በየትኛውም የኑሮ ሁኔታ ሊታጣ የማትችለው ማዕረግ
ነው፡፡ በመሆኑም በዘላቅነት እስከ ህይወት ፍፃመዋ ድረስ በዚህ ስም ትጠራላች፡፡ ነገር ግን ሴቷ በምትፈፅመው
ጋብቻ ምክንያት ተጨማሪ የማዕረግ መጠሪያ ስም ሊኖራት ይችላል፡፡ እነዚህም እንደሚከተሉት ተዘርዝሯል፡፡

ጋብቻ ማዕረግ Goshana/Ayka ከሆነች

 የንጉሥ /Kawo/ ምሰት ከሆነች፡፡ Godatte /Maalle/


 የዳና /Daanna/ ምሰት ከሆነች፡፡ Genne /Maalle/
 የእራሻ /Iraasha/ ምሰት ከሆነች፡፡ Mishire /Maalle/
(በአቶ አረካ አደም)
2.3 ጎፋና ጎዝዳ

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 14


ታሪክ ስናገር ጎሻና የጎፋ ካዎዎች ዘር ሀረግ ነው፡፡ ጎሻና የመጣበት ታሪክ ጎሻ (Gooshsha) ከሚባለው የጎፍኛ
ቋንቋ ነው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ የተጎተተ እንደማለት ነው፡፡ አመጣጥ አንድት ሴት ወንዝ ወርዳ ልብሷን
አውልቃ እየታጠበች ሳለ የፀሐይ ጨረር በዚህች ሴት ማህፀን ላይ ያርፋል፡ በዚህም ጽንስ ይፈጠራል፡፡ በጎፋ
ባህል ያለ ጋብቻ መርገዝ ነውር ነው፡፡ “ጎመ“ (Gome) እጅግ በጣም በባህል የሚጠየፍ ተግባር እንደ እርኩሰት
ይታያል፡፡ ከቤተሰብ አንድትገለል ባህሉ ያስገድዳታል፡፡ ስለሆነም ይህች ሴት በፀሓይ ጨረር የፀነሴችው የወልድ
ጊዜዋ ስደርስ ወንድ ልጅ ተወልዳለች፡፡ የወለደችውን ልጅ ቅርጫት አዘጋጅታ ወንዝ ወስዳ ትጥላለች በዚህም
ነው እንግድህ አንድት ሴት ለራሷ እንጨት ለመለቀም ጫካውን ስታቋርጥ በወንዙ ዳርቻ እንጨት ስትለቅም
የህፃን ድምፅ ትሰማለች በዚህም ተደንግጣ ወደ ወንዙ ስትቀርብ በውሃ ላይ ተንሳፎ እያለቀሰ ያለ ልጅ
ታገኛለች፡፡ እንግድህ ከውሃው ማሃል ቅርንጫቱ ጎትታ በማውጣት ነው ህፃኑን ለማሳደግ የወሰደችው ታሪክ
ይናገራል፡፡ በእንድሁ መልክ የተገኘው ልጅ ስያድግ ብርቱና ኃይለኛ ሆነ፡፡ በጎፋ ውርኪ ምድር ቀድሞ ምድር በዳ
የነበረው ጎሻ በብርታቱ አከባቢው እንደቀየረ ይናገራል፡፡ ጎሻ -ጎባን- ጎንታን -ጋሬ - ቡራ - ቡራቃ- ጋሞ- ጎቤ -
ዙለ ካንሳ - ቁስቴ ዳዳ ካማ ኦይካ፡፡

2.3.1 ጎዝዳ ምንድነው


ጎዝዳ የአንድ እንጨት ፍሬ እንደሆነ የጎፋ አከባቢ የሀገር ሽማግለዎች አቂዎች ይናገራሉ፡፡
እንዳንዶች ጎዚዳን የዛጎል ፍሬም ይላሉ፡ ደግሞ በለላ በኩል ጎዝዳ ከዛጎል ፍሬ የሚለይ ክብ እንደሆነ እና
የፍሬው ውስጥ ተበስቶ የሚለበስ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ ጎዝዳ በጎፋ አከባቢ የሚገኝ በጥንካሬ የሚታወቅ
እንደገጥም ሆኖ የሚያገለግል የእንጨት ፍሬ እንደሆነ ነው፡፡ ጎዝዳ የተባለበት ብቀጠቅጡት የማይሰበር
የማይበጠስ እና በቀላሉ ማለያየት የማይቻል ጥንካሬ መሆኑኑን የሚገልጽ ነው፡፡ ጎዝዳ ፍሬውን እንድገኝ
አዘጋጅተው ጎፋዎች ለውቤት (Alleqqo) ለገጣገጥ ይጠቀማሉ፡፡ ይህ ፍሬው በብሔረተሰቡ እጅግ በጣም
ይወደዳል ልዩ ቦታ ይሰጠዋል ልባኖስ የሀገርቱን ባንድራ ዝግባ እንዳደረገችው ሁሉ የጎፋ ብሔረሰብም ጎዝዳን
የብሔረሰቡ መግለጫ አደርጓል ብባል ማጋነን አይሆንም፡፡
ጎዝዳ የጎፋዎች የአይበገርነትና የጥንካሬ መግለጫ ሆኖ እስከ ዛሬ አለ፡፡ ጎፋዎች ጎዚዳዎች ናቸው፡፡ ይህ ማለት
ጎፋዎች እንደ ጎዝዳ ጠንካራዎች ብርቱዎች ቶሎ የማይሸነፉ እጅ የማይሰጡ ላመኑበት ነገር ወደኃላ የማይሉ
ሕዝቦች የመሆናቸው መግለጫ ነው፡፡

ለጎፋዎች፤ ጎዝዳ - ገጣቸው ነው፣ መፎከሪያቸው ነው፣መለያቸው ነው ስለሆነም በሚቀጠለው መልኩ


ይጠቀማሉ፡፡ ታ ጎፋ ና ጎዝዳይ (Ta Gofa Naa Gozida) ብለው ይፎከራሉ፡፡ እኔ የጎፋ ልጅ ጎዝዳው እንደ
ማለት ነው፡፡ ይህ ማለት እንድግህ ጠንካራ እና አይበገረ መሆኑን እየገለፀ ነው፡፡ ብቻም ሳይሆን ማድረግ
እንደሚችል እያሳየ ነው፡፡
 ታ ጎፌ ና ጎዝዳይ (የጎፋ ልጅ ጎዝዳ)
 ሱግ የድን ሱሬ ኤቂያ (ገፍትሬው ብሞክሩ የማይነቃነቅ)
 ኩቶ ማራቄን ኩሼ መጨይ (በዶሮ መረቅ እጅ የምታጠብ)
 ማሄ ሸሻን አይፌ መጨይ (በነብር ሽንት ፍቱን የሚያጥብ) ጠቅልል ስል እኔ የጎፋ ልጅ ጎዝዳ
ብገፈትሩት እንኳን ቀጥ ብዬ መቆም፤ እጄን በዶሮ ወጥ የሚታጠብ በማለት የአከባቢውን ጥጋቢ፤
በነብር ሽንት ፍቱን የታጠበ ሰው ሲል እጅግ ደፋር መሆኑን የሚገልጽ ነው፡፡

ስለሆነም ጎዝዳ ለጎፋ ሕዝብ የብሔረሰቡ መግለጫ ነው፡፡ የጎፋ ብሔረሰብ የሆነ ሁሉ ጎዚዳ እንደ ማለት ነው፡፡
ጎዝዳ ለመሆን በአጭሩ የጎፋ ብሔረሰብ መሆን አለብህ፡፡ በጎፋ ብሔረሰብ ጎዚዳ ለሁሉም የተሰጠ ነው፡፡ ወንድ፣
ሴት፣ ህፃን እና አዋቂ ሁሉም ጎዚዳ ናቸው፡፡ ጎዝዳን ግን ስጠቀሙ በተለያየ መልኩ መመልከት ይቻላል፡፡

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 15


ለምሳሌ የጎፋ ብሔረሰብ ተወላጅ አንዱ አንዱ ጋ እኔ የጎፋው ልጅ ጎዝዳ ብሎ ልል አይችልም፡፡ ይህ ማለት ምን
ማለት ነው; የጎፋ ብሔረሰብ ተወላጅ ሆኖ እርስ በርስ ቢጣላ እንኳን ታ ጎፌ ና ጎዝዳይ ማለት አይችልም ነውር
ነው፡፡

ጎፋ የሆነ ሁሉ ጎዝዳ ነው ማን ማንን ይላል፡፡ ነገር ግን ከሌላ ብሔር ጋር ከላይ በተጠቀሰው መልኩ የሚፈጠር
ነገር ቢኖር ለምሳሌ፡- ለላው ብሔር ጋ ታ ጎፌ ና ጎዝዳይ ልል ይችላል፡፡ ይህ ማለት ምን ማለት ነው; የራሱን
ጥንካሬ አይበገሬነት ለሌላው ልገልጽ ይችላል ማለት ነው፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ ለላ ብሔር የሆነ ሁሉ የጎፋን
ብሔር ተወላጅ በእንድሁ መልክ ልጠራ ልያሞግስ ይችላል፡፡ ለምሳሌ፡- ጎፋ ና ጎዝዳው ፣ጎፋ ና ጎዝዳቴ፣ በማለት
ጠንካራ፣ጎበዚ አይበገሬ መሆናችንን ልገልፅ ይችላል፡፡

የጎፋ ብሔረሰብ ከጥንት ጀምሮ ጎሻ፣ጎባን እንደወለደና እስከዚህ እንደመጣ ከሆነ ጎባ (Gooba) ማለት ኃያል
ጠንካራ አይበገሬ እንደማለት ሲሆን ይህንን ጥንካሪያቸውንና አይበገሬነታቸውን ጎፋዎች በንጉሳቸው ዳዳ ካማ
በጎፋ አከባቢ ጫቆ ቆጴ በሚባል ስፍራ ያስመሰከሩ በማይጨው በሳጋሌ በአዱዋ ያሳዩ ለዚህም ማሳያ በአዲስ
አበባ ጎፋ ሰፈር አዱዋ የዘመቱ የጎፋ አባቶች ማረፍያ ስፍራ የተሰጠው እስከ ዛሬ ታሪክ ሆኖ ለእኛ ለልጅ
ልጃችንን ቆይቷል፡፡ ስጠቃልል ጎዝዳ የጎፋዎች የአበገሬነትና የጥንካሬ መግለጫ በመሆን ሁሉም እሴቱን ልጠበቅ
ይገባል ባልተገባ መንገድ መጠቀም የለበትም፡፡

(በአቶ ድንበሩ ድርቤ ዲላ፤ ጳጉሜ 2014)

2.4 የኦይዳ ሕዝብ ታሪክ

ታሪካዊ ዳራ

የኦይዳ ሕዝብ በደቡብ ኢትዮጵያ በጎፋ ዞን ከሚገኙ ሁለት ነባር ብሔረሰቦች አንዱና የራሱ የሆነ ቋንቋ፣ባህልና
ታሪክ ያለው፤ እስከ መሳፍንት ዘመን ማቢቅያ ድረስ የኦይዳ ብሔረሰብ በራሳቸው ባህላዊ አስተዳደር ሥርዓት
ሲተዳደሩ ቆይተዋል ፡፡ የኦይዳ መልካአ-ምድራዊ አቀማመጡ ፡- በሰሜን የገዜ ጐፋ ወረዳ፣ በደቡብ የዑባ
ደብረ-ፀሐይ ወረዳ፤ በምስራቅ የደንባ ጐፋ ወረዳ፣ በምዕራብ ሰሜን አሪ ወረዳ (የደቡብ ኦሞ ዞን) ያዋስናሉ ፡፡
የኦይዳ ዋና ከተማ ሸፍቴ ከጎፋ ዞን ዋና ከተማ ሣዉላ በ 9 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ የኦይዳ ብሔረሰብ
ሰፍሮ የሚገኝበት የወረዳው የቆዳ ሲፋት 20,000 ሄክታር ሲሆን የወረዳው ስነ-ምህዳር ስንመለከት፡-ደጋ፣
ወይናደጋ እናቆላ ነው፡፡ የኦይዳ መልካአ - ምድር አቀማመጥ ውብ እና ማራኪ ከመሆኑ የተነሳ የተለያዩ
ተፈጥሯዊና ታሪካዊ የቱሪስት መስህቦች መገኛ እንድትሆን ተፈጥሮ አድሏታል ብባል ግነት አይሆንም ፡፡

(የኦይዳ ወረዳ መልካአ ምድራዊና አጠቃላይ ነባራዊ ሁነታ፤ ፆሊንቶ ቁርጥር 1.ጥቅምት፤2014 ዓ/ም፤ 43)

የሕዝቡ አመጣጥና አሰፋፈረ በአከባቢዉ ጥንታዊ ሲሆን ከአንድ ከተወሰነ ቦታ መጥተዉ የሰፈሩ አይደሉም፡፡
የሕዝቡ መጠሪያ ኦይዳ ሲሆን የቃሉ ልዩ ትርጉም ለምለም (ለመለመ) ማለት ነዉ ፡፡ ይህም ማለት ኦይዳ
የሕዝቡና የመሬቱ አጠቃላይ ስያሜ ነዉ ፡፡

(የመረጃ ምንጭ ፡- አቶ እንግዳ እንድርያስ፣አቶ አየለ አሸናፍ ፣ አቶ ደስታ ካሳ ፡ነሔሰ፤2014 ዓ/ም)

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 16


2.4.1 የሕዝቡ መነሻ ታሪክ በአጭሩ

የኦይዳብ ሔረሰብ በደቡብ ኢትዮጵያ በጎፋ ዞን ከሚገኙ ሁለት ነባር ብሔረሰቦች መካከል አንዱ ሲሆን
የብሔረሰቡ ቋንቋ በደቡብ ክልል በአብዛኛው አከባቢ ከምነገር የቋንቋ ቤተሰብ ዘር ግንድ ከሆነው ከኦሞቲክ
የቋንቋ ቤተሰብ እንደመጣ የዘርፉ አጥኝዎች በህትመታቸው ያሰፈሩት መረጃ ያስረዳል ፡፡ የኦይዳ ሕዝብ
የምናገረው ቋንቋ ኦይድኛ፤ ሲሆን የማህበረሰቡ ኑሮ መሠረት ያደረገው በዋናነት በእርሻ ሥራ ላይ ነው፡፡

የማህበረሰቡ አመጣጥና አሰፋፈረ ስንመለከት ኦይዳ “ዞንጋር” ተብሎ ከሚጠራው ወንድና “ጉዳሮ” ተብላ
ከምትጠራ ሴት መነሻ እንደሆነ የሀገር ሽማግሌዎች ያስረዳሉ ፡፡ የሁለቱ ሰዎች መነሻ (መፍለቅያ) ቦታ በኦይዳ
ወረዳ በባልጣ ቀበሌ ከላይኛው ባልጣ “እንዳአክ ምንጭ” አከባቢተነስቶ ወደ ታችኛው ባልጣ ቀበሌ በመውረድ
መኖረያቸውን “ዞባ” በሚባል ንዑስ መኖር ጀምረዉ እዛዉ ዞባ የበኩር ልጃቸዉን ማዳር የተባለዉን ወልደዉ
ሀብት ንብረት አፍርተዉ ተደራጅተዉ በአከባቢዉ እርሻ በማረስ ኑሩዋቸዉን አደረጉ ፡፡ የመጀመሪያ የኦይዳ
ሰዎች የኑሩበት ጥንተዊ አከባቢ ዞባ የምባልበት ስፍራ እንደሆ በስፋት ይነገራል ፡፡ በዚህ በጥንታዊ አከባቢ የዛን
ጊዜ ሰዎች ለምግብነት የምሆኑ ሰብሎችን እና ስራስር እህሎችን በማረስ እንድሁም የተለያዩ ፍራፍረዎችን
በማምረት እየተመገቡ በምቾት እንደምኖሩ የሀገር ሽማግለዎች ያስረዳሉ ፡፡ በኦይዳ በጥንት ጊዜያት ሰዎች
ለምግብነት አዘወትረዉ የምጠቀሙት የእህል ዓይነት መካከል ለአብነት፡-እንሰት፣ ገፍስ፣ ማሽላ፣ ዘንጋዳ፣
በቆሎና ለሎች የእህል ዓይነቶች ይገኛሉ ፡፡

በዞባ እየኖሩ ማዳር የተባለዉን የበኩር ልጃቸውን ወለዱ ፡፡ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተዋለዱ እና የህዝብ ቁጥር
እየጨመረ ስመጣ የሰው ልጆች አሰፋፈረ በተለያዩ የኦይዳ አከባቢዎች ማድረግ እንደተጀመረና እየጨመረ
የመጣው የሰው ልጅ ውልደት ማለትም ማዳር እና ሌሎች ልጆች እየተዋለዱና እየተባዙ ቁጥራቸው
እየጨመረ መምጣቱ በጎሳ ለመከፋፈል ትልቅ አስተዋጽዖ እንዳበረከተ ይነገራል ፡፡ ከየወገናቸው የተለያየ
ስያሜና መጠሪያ ተሰጥቶ እስከአሁን በብሔረሰቡ የሚገኙ 42 (አርባሁለቱ) ጎሳዎችን ስንዘረዝር ፡- ዣዥንቴ፣
ሻራ፣ ጋኮና፣ አጋር፣ አንታል፣ ወርቃ፣ ካታ፣ ዙል፣ ዞባ፣ አማን፣ አይግር፣ ሸፋል፣ አዢ፣ ጋናዝ፣ ጐሀ፣ አሳ፣ አይካ፣
ሳርካ፣ ዛግርሳ፣ ሞያ፣ ዝና፣ ጉዳርቲ፣ ሳውራር፣ ጋርፃ፣ ኦቅ፣ ማንግ፣ ጋንጅሬ፣ ዛካ፣ ጐንት፣ ሶዙም፣ ሃይቦማል፣
ጎሎማል፣ ወርዝ፣ ጋድር፣ ጋውህና፣ ማሽን፣ ጋንሳ፣ አምፋርሲ፣ ዛግን፣ ዛል፣ ማርንት፣ እና አርጋማ ሲሆኑ ደቢ
እና ኦይድ ካፋሼ ከሚት ባልሴት የተወለዱ መንታል ጆች እየተባዙ ሲመጡ ”ደቢና” እና “ኦይዲና” የሚል የጎሳ
ስያሜ ተሰጥቶአቸው የኦይዳ ብሔረሰብ ቁጥር ወደ 44 (አርባአራት) ከፍብሏል፡፡ ኦይዳዎች በሁሉም አቅጣጫ
ከምያዋስኑዋቸው አጎራባች ህዝቦች ጋር በልዩ ልዩ የሰዉ ልጅ የዕለት ተዕለት ኑሮ እና እንቅስቃሰዎች የጋራ
የሆኑ የአብሮነት እሴት የሆነውን ሠላምን በማረጋገጥ በጋብቻ፣ በንግድና በልዩ ልዩ መንገዶች የተጋመዱ ፍቅር
ህዝቦች ናቸው፡፡

2.4.2 (3.3.1) የኦይዳ ማህበረሰብ ባህላዊ አስተዳደር መዋቅር

1. ካቲ (Kaati) ንጉስ
2. ቢታን (Bittan)

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 17


1. ንጉሥ /Kaati/
የኦይዳ ብሔረሰብ ንጉሥ /Kaati/ ከፍተኛ የሥልጣን ባለቤት ሲሆን የራሱን ግዛት እና ሕዝቡን በበላይነት
ይመራል፣ ያስተዳድራል ፡፡ ከእርሱ በታች ባሉ እርከኖች ያልተፈቱ አለመግባባቶች ሲቀርቡ፤ በመመርመር
የመጨረሻ ዉሳኔ ይሰጣል ፡፡ ከአጎራባች አከባቢዎች ጋርም ግጭት ሲፈጠር የወታደራዊ ኃይሉን ይመራል ፡፡
ግጭቱ አልፎ ወደ ፀብ የሚቀየር ከሆነ ጦርነት ያውጃል፤ በባሕላዊ ሐይማኖታዊ ሥርዓቶችም በአካባቢው
ድርቅ ወይንም ወረርሽኝ ሲከሰት ከታችኛው የተዋረድ እርከንኖች ጋር በመሆን የተለያዩ “ውርሶ” /የማንፃት/
ሥራ በመሥራት የመጨረሻ መፍትሔን የሚሰጠዉ ፈጣሪ እንደሆነ በብሔረሰቡ ባሕል ስለሚታመን ፈጣሪን
/Xoozi/ ለሕዝቡ ይማፅናል ፡፡ የእርስ በእርስ ግጭቶችንም ያስቆማል ፡፡ ከነፍስ ግዲያ ጋር የተገናኙ ግጭቶችን
የሟች እና የገዳይ ወገኖችን በማግባባት፤ ገዳዩን ለሟች ወገን የደም ካሣ በማስከፈል እና ለእርቀሠላም
ማረጋገጫነት በሁለቱም ወገን የበግ ግልገል፤ የምግብ እና የመጠጥ /Kuntsts/ ሲያቀርቡ በግዛቱ ዳርቻ ወስደው
የገዳዩን ወገን ከግዛቱ ወሰን ማዶ እና የሟች ወገንን በግዛቱ ክልል ዉስጥ በማቆም ንጉሱ /Kaati/ እና
ከእሳቸው ጋር ካሉት የእርቅ አስፈፃሚዎች ጋር በመሆን የበጎችን ደም በመቀባት ከሁለቱም ወገን የቀረበውን
ምግብ እና መጠጥ በማቅመስ ያስታርቋቸዋል ፡፡ እርቁንም በመሀላ ያፀናዋል ፡፡ እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩ
ተግባራትን ካቲ በዋናነት የሚፈጽማቸው ተግባራትናቸው፡፡

በኦይዳ ብሔረሰብ ባሕላዊ አስተዳደር ካቲ ሆነዉ የነገሡ ግለበሶች፡- 1 ኛ ካቲዣዦ 2 ኛ.ካቲ ዣልሽ 3 ኛ.ካቲ
ጉሳ 4 ኛ.ካቲ ኦይዲ 5 ኛ.ካቲ ድጋ 6 ኛ.ካቲ ቡዴ 7 ኛ.ካቲ አይሎ 8 ኛ.ካቲ ካቺ 9 ኛ.ካቲ ወጋ 10 ኛ.ካቲ ጎድ
11 ኛ.ካቲ ሳዴ 12 ኛ.ካቲ ካማ 13 ኛ.ካቲ አፋ 14 ኛ. ካቲ ግጋናቸው፡፡

2. ቢታን /Bitan/
ቢታን፤- ከካቲ ቀጥሎ የሚገኝ ባሕላዊ የሥልጣን እርከን ሲሆን ከሁለት እስከ አምስት ቀበሌያት የሚመራ
ሆኖ፤ በኦይዳ ብሔረሰብ ቢታን በዋናነት ባሕላዊ የእምነት ሥርዓት ላይ ያተኩራል፤ በራሱ አካባቢ ያሉትን
ሕዝቦች በሚያስተዳድርበት ወቅት ድርቅ እና ወረርሽኝ ሲከሰት የ“ዉርሶ” ሥርዓትን ይፈፅማል ፡፡
አለመግባባቶችንም ያስወግዳል ፡፡ ከካቲው የሚተላለፈውን ትዕዛዝ በተዋረድ ወደ ታችኛው እርከን ያወርዳል
፡፡ ከታችኛው እርከን የሚቀርቡ ጥያቄዎችን እና ሀሳቦችን ተቀብሎ ይፈፅማል ፡፡ ከአቅም በላይ ሲሆን ወደ
ካቲው ያደርሳል ፡፡
3. ጮማች /Comachch/
ጮማች፡-በካቲ አስተዳደር እርከን ከቢታን ቀጥሎ የሚገኝ ባሕላዊ የአስተዳደር እርከን ሲሆን በዘመኑ
አደረጃጀት የቀበሌ መዋቅር ነው፡፡ ጮማች የሚያከናውናቸው ዋና ዋና ተግባራት በድንብር ጉዳይ የሚነሱ
ጥያቄዎችን ያስተዳድራል፡፡ የስድብ እና የማዋረድ አቤቱታዎችን ይመረምራል፣ ውሳኔ ይሰጣል፡፡ የተለያዩ
ባሕላዊ ሀይማታዊ ሥርዓቶችን ያስፈፅማል፡፡ የካቲው እና የቢታን የእርሻ ማሳዎች በወቅቱ እንዲታረሱ
ያስተባብራል፡፡ ግጭቶችን ያስወግዳል፤ ከአቅሙ በላይ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ቢታንን በመጋበዝ ችግሮቹ እንዲፈቱ
ያደርጋል፡፡ በጦርነት እና በአደን ወቅት ታዋቂ የሆኑ ግለሰቦችን ከሕዝቡ ጋር በማዋሄድ ጠንካራ ሥራን
ይሠራል፤ ምክንያቱም በጦርነት ወይም በአደን ወቅት የተላበሰው ጭካኔ ከሆነ ለዓይኑ የገደላቸውን የአውሬ

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 18


መንፈስ ይሰፍርበታል ተብሎ ስለሚታመን የቁጣ /ጭካኔ/ ማብረጃ ተብሎ የሚፈፀም የ“ብርሴ” /birse/
ሥርዓትን ያከናውናል፡፡ የግለሰቦችን ጀግንነትንም ያረጋግጣል፡፡ የልቅሶ ሥነ-ሥርዓት ከቀብር በኋላ
በለቀስተኛው ቤት ተደጋግሞ ለቅሶ እንዳይመጣ (የለቅሶ ማንሻ “ዳሜ” /dame wodhe/” ሥርዓትን
ያስፈፅማል፡፡

4. ጐዲ
ጐዲ፡- ይህየባህላዊ የአስተዳደር እርከን ከጮማች ቀጥሎ የሚገኝ ሲሆን፤እንደ ሌሎች የባሕላዊ መሪዎች
በግልና በቡድን የሚያከናውናቸው ተግባራት አሉት፡፡ ጐዲ በሚገኝበት አከባቢ ባሕላዊ መሪዎች እና ከሕዝቡ
ጋር በመቀናጀት በአካባቢው በዋናነት የሚከሰቱትን ባሕላዊ እና ሀይማኖታዊ ነክ ጉዳዮች ላይ ያተኩራል፡፡
ከሚተግባራቸው ጉዳዮችም ዋና ዋናዎቹ፤ በሚኖርበት አካባቢ ከጐሳዉ ወይም ከቤተሰብ አባላት አቅም በላይ
የሆኑ፤ በአከባቢዉ ሕዝብ እና በብሔረሰቡ ባሕል ዉግዝ የሆኑ ጉዳዮች ሲከሰቱ የወግ እና የባሕል መተላለፍ
ኃጢያትን ወይም ጐሜን /Gome/ የማንፃት ሥርዓትን ያስፈፅማል፡፡ ከላይኛው እርከን በተዋረድ የሚተላለፉ
ትዕዛዛትን ያስፈፅማል፡፡ የካቲ፣ የቢታን እና የጮማች እርሻዎችን /Maddo/ ያሳርሳል፡፡ ከሕዝቡ የሚቀረቡ
ጥያቄዎችን ወደ ላይኛው እርከን ያደርሳል፡፡ በተለያዩ ጉዳዮችም ሕዝቡን ያማክራል፤ መዋጮዎችን
ያሰባስባል:: ለካቲ፣ለቢታን እና ለጮማች የሚሰጥ እህል አሰባስቦ ለሚመለከታቸው ያቀርባል፡፡ በፌሾ /Feesho/
በዋናዉ የልቅሶ ቀን፣በደቦ ዕለት ዝናብ እንዳይዘንብ፤ከሱ ከፍ ላለዉ አካል በዕለቱ ወደ አምላክ
እንዲማፀንላቸዉ መልዕክት ያስተላልፋል ፡፡

5. ቡጫ /Buca/
ቡጫ፡- /Buca/ የመጨረሻ የመዋቅር እርከን ሲሆን አወቃቀሩም ከሕዝቡ በተወጣጡ የሀገርሽማግሌዎች
ስብስብ ነው ፡፡ ይህ መዋቅር እጅግ የሚከበር፤ የሚፈራ እና ተሰሚነት ባላቸው የሀገር ሽማግሌዎች ዳኝነትን
የሚሰጡበት መዋቅር ሲሆን፤በተጨማሪም እንዲያከናውኗቸው፤ የተሠጣቸው ሥልጣንም፤የአስተዳደር
እርከኖችንም የመሾም እና የመሻር ኃላፊነት ተሰቷቸዋል፡፡ በአከባቢያቸው ለሚፈጠሩ ማናቸውም ግጭቶች
እና አለመግባባቶች የመጀመሪያ ደረጃ አጣሪ እና ዉሳኔ ሰጪ አካል ሆኖ ከታች ወደላይኛው እርከን የሚተላለፉ
ጉዳዮችን ከላይኛው እርከን ጋር እየተመካከሩ ዉሳኔ የመስጠት እና በሚሰጡ ዉሳኔዎች በማይስማሙትም ላይ
የመጨረሻ እርምጃ የመውሰድ ሥልጣንም አላቸው፡፡ የእርምጃ ዓይነቶችም ከጎረቤት እሳት እንዳይጭሩ
መከልከል ከብቶቻቸው ከሕዝቡ ከብቶች ጋር በግጦሽ እንዳይሰማሩ የመከልከል፣ ልጆቻቸው ከሕዝቡ ልጆች
ጋር በሜዳ እንዳይጫወቱ መከልከል እና ከማናቸውም የማሕበራዊ ጉዳዮች የማግለል እና ወዘተ… ናቸው፡፡
(መረጃ ሰጪ፡ የብሔረሰቡ ተወላጅ የሆኑት ፤ አቶ አየለ አሸናፊ፣ አቶ እንግዳ እንድርያስ እና አቶ ደስታ ካሰሳ)፡፡

(በአቶ ዮሐንስ ኢትዮጵያ፤ነሔሰ 2014 ዓ/ም)

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 19


ክፍል ሦስት
የባህል አምድ
3.1 በጎፋ ብሔረሰብ የጋዜ ማስቃላ (መስቀል) በዓል አከባበር
የመስቀል በዓል በጎፋ ብሔረሰብ በዓመት አንዴ የሚከበርና በብሔረሰቡ ዘንድ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶት
ከትንሽ እስከ ትልቅ ደሃውም ሆነ ሀብታሙ፣ በሁሉም ማህበረሰብ ያለውም ሆነ የሌለው በመስቀል በዓል አንድ
የሚሆንበት ልዩ በዓል ነው፡፡

3.1.1 የመስቀል በዓል ቅድመ ዝግጅት

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 20


በጎፋ ብሔረሰብ መስከረም ወር ሲገባ ዓመቱ ተጠብቆ የሚመጣውን የመስቀል በዓል ለማክበር የሚደረገው
የቅድመ ዝግጅት እንቅስቃሴ ድንገት እግር ጥሎት ለመጣ ሰው የተለየ ትዝታ የሚጭር ነው፡፡ ለመስቀል በዓል
15 ቀናት ሲቀሩ እንኳን ሰው የቤት እንስሳትም እንዳይራቡ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ዝግጅት ይደረጋሉ፡፡
እያንዳንዱ አባወራ በቤቱ ለ 7 ቀናት የሚበቃ የእንስሳት መኖ እና ውሃ የማቅረብ ሥራ ይሠራል፡፡ ማንኛውም
አባወራ በመስቀል ሣምንት ከቤት የትም ርቆ ስለማይሄድ እቤት በዓሉ እስከሚያልፍ ድረስ በበቂ ሁኔታ
የሚመገቡትን በየድርሻቸው ያዘጋጃሉ፡፡ በተለይም ሴቶች ጤፍ፣ በቆሎ እና ሌሎች ለበዓሉ የሚሆኑ እህሎችን
በመፍጨት ቦርዴ እና የጌሾ ጠላ በመጥመቅ እንዲሁም ወንዶች ደግሞ ሴቶች ለማገዶ እንዳይቸገሩ እንጨት
ፈልጠው በማቅረብ እና ሌሎች ለበዓሉ የሚሆኑ ግንግና (Ginggina) የተባለው ጭራሮ በመለቀም፣ የእርድ
ቢላዋና እርዱ የሚፈፀሚበትን ቦታ በመወሰን የቅድመ ዝግጅት ሥራውን ማራኪ በሆነ መልኩ ያጠናቅቃሉ፡፡

ለመስቀል በዓል ካለው ከበሬታ የተነሳ ገና በዓመቱ እስከ ሚመጣ ታስቦ ቅድመ ዝግጅት ያደርጋሉ፡፡ ለልጆች
ልብስ በዕለቱ የሚዘጋጅ ምግብና መጠጥ በተለይ ለመስቀል ሥጋ ተብሎ ዓመቱን በሙሉ በመቆጠብ በዕድር
ዝግጅት ከመደረጉም ባለፈ ለመስቀል ተብሎ ለሚደረግ ነገር ሁሉ ሳይሰስት ማንም የሚፈጽመው ይሆናል፡፡
ለእርድ የሚሆኑ ሰንጋዎች ተገዝተው ይዘጋጃሉ፣ ለገንፎ የሚሆን በቆሎ ታምሶ ይፈጫል፣ ቡላ ና ቆጮ
እንዲሁም የሃረግ ቦዬ ይዘጋጃል፣ ለቦርዴና ለጌሾ ጠላ የሚሆን ዝግጅት ይደርጋል፣ ለጠጅና ለብርዝ ማር
ይቆረጣል ይጠመቃልም፡፡ አከባቢው አዳይ አበባ ሲደመቅ በብሔረሰቡ አጠራር ቤላ ጭሻ (Bella ciisha)
ጋራው ሸንተራሩ ሲያሽበርቅ አርሶ አደሩ በብሔረሰቡ ዘንድ በስፋት ከሚታወቀው ምርት በዋናነት ጤፍን
በጊዜው ከአረም ነፃ የሚያደርጉበት ሰብሉን አብቦ የሚደምቅበት ነው፡፡ ወረሃ መስከረም መግቢያ የመስቀል
በዓል መድረሻ ለመሆኑ መግለጫ ነው፡፡ ይህ ብቻ አይደለም መስቀል በዓል ሲቃረብ ልጆች በተሠማሩበት የሥራ
መስክ ላይ ሆነው ከብቶችን በመጠበቅ ላይ፣ ለእንጨት ለቀማ፣ ውሃ ለመቅዳት እና ሣር ለማጨ ከአንድ በላይ
ሆነው በሚገኙበት ቦታ ሁሉ ያለማንም ቅስቀሳ ሲያዘሙ ይደመጣሉ፡፡
ሎያ ባይ ሎያ ባይ
ሎያ ማሰቀላ ባይ
ማስቀላ ኡፋይሳ ባይ
ሙሳ ኡሻ ባይ ሲሎ ይዳመጣሉ፡፡
ይህ ማለት መስቀል እንኳን መጣህልን!
የእኛ ደስታ! የእኛ መዝነኛ መስቀል እንኳን መጣልህን! በማለት በጉጉት ስለሚጠባበቁት መስቀል በዓል
ሲያዜሙ ይደመጣሉ፡፡
በጎፋ ብሔረሰብ ለመስቀል በዓል የምግብና መጠጥ አዘገጃጀቱም ሆነ በሌላ የሚሰጠው ትኬረት ካሉት በዓላት
ልዩ የሚያደረገው ሲሆን ለመስቀል ተብሎ የሚወጣው ወጪ የማንን በር የሚያንኳኳ እና ያለውን የሌለውም
አመቱን ሙሉ በመቆጠብ ሳይሳሳ የሚያዘጋጅበት መሆኑ ነው፡፡
በተለያ በመስቀል በዓል ከሁሉም ቅድሚያ የሚሰጠውን የቤትሰብ አባል ሆነው ተለያይተው የቆዩት
የሚገናኑበት ከአከባቢው በተለያዩ ምክንያቶች ርቀው ያሉት በዳመራ ዕለት በመገናኘት ናፍቆታቸውን
የሚወጡበት፣የተጣሉት የሚታረቁበት፣ሀዘን ውስጥ የነበሩ ሀዘኑን የሚረሱበት፣የተነፋፈቁየሚገናኙበት እና
የትዳር ጓደኛ የሚይዙበት ዓይነተኛ ቀንና ጊዜ መሆኑን ልዩ ያደረገዋል፡፡
1. የምግብ ዝግጅት
በጎፋ ብሔረሰብ ለመስቀል በዓል የተለያዩ የምግብ ዓይነቶች የሚዘጋጁ ሲሆን በዋናነት በዳመራው ዕለት
የሚበላው ከበቆሎ የሚዘጋጅ ገንፎ ሲሆን ስያመውም / Masqqala dhote /በመባል ይተወቃል፡፡ አዘጋጃጀቱም
ከሣምንት በፊት ወተት በማጠራቀም ምንም ውሃ ሳይታከልበት ከበቆሎ ዱቄት በተነጠረ ቅቤ፣በአይብና

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 21


በቅመም የሚዘጋጅ ገንፎ ማለትም ነው፡፡ ይህ ገንፎ ከተዘጋጀ በኃላ ቤተሰቡ ሁሉ በአንድነት በመሰባሰብ
እጃቸውን ወደ መሶቡ የሚሰዱበት ሥርዓት ከምንም በላይ ፈጣሪያቸውን የሚያስቡበትና የሚማፀኑበት
ስለሆነ ማስቃላ የ! ዮ! እያሉ በጋራ የሚቀምሱበት፣በፍቅርና በአንድነት የሚበሉበት ሲሆን ከእንሴት ምርት
የሚዘጋጀውን ቡላ /Ittima/ በአይብ፣የሐረግ ቦዬ በአዋዜ / Boyye/ በዋናነት በመስቀል በዓል ዕለት ለምግብነት
የሚዘጋጁ የምግብ ዓይነቶች ናቸው፡፡
ከመጠጥ ዓይነቶች ደግሞ ቦርዴ /Bordde/ ከቦቆሎና ከጤፍ ሙጴ /Muudhe/ ጌሾ ፣ጤላ፣ ብርዝና ጠጅ
የሚዘጋጅ ሆኖ ከዳመራ ዕለት ጀምሮ ስጠጡና ስጨፈሩ ቆይተው በ 2 ኛው ቀን ከወር መስከረም እስከ ነሐሴ
መጨረሻ ድርስ በጋራ በመደራጀት የገዙትን የእርድ በሬ ለመስቀሥነል ሲጋ እርድ ይፈፅማሉ፡፡
2. ከደመራው በፊት የሚደረግ ሥነ -ሥራዓት
ከመስቀል በዓል በፊት በአከባቢው ወይም በቀበሌ ውስጥ ከቤተሰብ ሰው ሞቶባቸው በሀዘን ያሉ ካሉ የቀበሌው
ሽማግሌዎችና አሮጊቶች ወደ ሀዘንተኛው ቤት ድረስ በመሄድ ለሞተው ሰው በማልቀስ ሀዘናቸውን
እንዲያወርዱ ይጠይቃሉሀዘናቸውን ያወርዳሉ፡፡
የተጣሉም ካሉ ይታረቃሉ፡፡ ምክንያቱም ሀዘንተኛው ሀዘኑን ትቶ የተጣሉትም ታርቀው በፍቅርና በሠላም
በጋራ የደስታ ተካፋይ እንዲሆኑ ለማድረግ ተብሎ በብሔርሰቡየሚደረግ ልዩ እና ዓይነተኛ ተግባር ነው፡፡
3. የደመራ ሥነ -ሥራዓት
በጎፋ ብሔረሰብ የመስቀል ዳመራ በውስጡ የተለያዩ መልዕክቶችን ያዘለ ነው፡፡
ከሣምንት በፊት ከቤተሰቡ በአባት ወይም በታላቅ ልጅ ለችቦ የሚሆኑና በራሳቸው ጊዜ የደረቁ ቀጥ ያሉ
ጭራሮ ያዘጋጃል፡፡ የደመራ አዘገጃጀትን በተመለከተ በመጀመሪያ የደመራው እንጨት ቀጥ እያ መሆን
እንዳለበት ይታመናል፡፡ ዓላማውም ዘመኑ መልካም ዘመን እንዲሆን ከበሽታ ከመቅሰፍት እንዲጠበቅ ልጆች
በአስተሳሰብና በአመለካከት ቀና እንዲሆኑ በማሰብ ነው፡፡ስለሆነም በብሔረሰቡም ለቤት መሣሪያ አገልግሎት
በስፋት ከሚጠቀሙት የጨፈቃ ዓይነት ሶልዜ /solize/ ተብሎ የሚጠራው ሲሆን ለዚህ አገልግሎት ይውላል፡፡
የደመራ እንጨት አዘገጃጀቱም ከደረቅ ወደ እርጥብ እንዲሆን ተደርጎ ነው፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት ዘመኑ
የጥጋብና የሠላም እንዲሆን በማለት ነው፡፡ በደመራው እንጨት ጫፍ አደይ አበባው ይታሠራል፣ዓላማውም
ተስፋ ውበትና በአበባ ውስጥ ዘርም ስለመኖሩ የደመራው ሥነ - ሥራዓት ለቀጣይ ትውልድ የማተላለፍ
ሥራዓትን ያመላክታል፡፡ ዘራችንም ይበዛል ይሰፋል ለማለት ታስቦ ሲሆን የችቦ አስተሳሰርና የደመራ አቆራረጥ
የቤተሰብ ቁጥር በዕድሚያቸው መሠረትና መጠን ይወስናል፡፡

ይህም በመካከላቸው መደማመጥና መከባበር እንዲሰፍን ያደርጋል፡፡ የችቦ አለኳኮስን በተመለከተ በመጀመሪያ
ቀኑ ደንገዝገዝ ወይም ለዓይን ያዝ ስል አባወራው በወንድ ቁጥር የታሰረውን ችቦ አጠቃላይ በመያዝ ምሶሶ
ካለበት ጎጆ ቤት ውስጥ ለገንፎ ከተጣደው ድስት ስር ከሚነድ እሳት የሁሉም ችቦ ከለኮሰ በኃላ በቀኝ
በመታጠፍ ምሶሶሰውን በመዞር ምሶሶሰውን የከብቶች ጋጣና በበሩ ላይ በቀኝና በግራ የቆሙትን መሪ
ግድግዳዎችን ማስቃላ ዮ! ዮ! እያሉ በተለከሰው እሳት እየነካካ ከቤት ወደ ደጅ ይወጣል፡፡ አባትም ማስቃላ ዮ!
ዮ! እያለ ችቦን በዕድሜ ደረጃቸው ካካፈለ በኃላ መሃል ላይ ሆኖ በወንዶች ታጅቦ ማስቃላ ዮ! ዮ! ዳናው ዳና
እያሉ በዱቡሻው ስር ወደ ተተከለው ደመራ ደርሰውን ዳመራውን ዞረው አባት በመጀመሪያ ችቦን ሲያስቀምጥ
ሌሎች በዕድሜያቸውመሠረት ያሰቀምጣሉ በህላዊ ጨዋታዎችን ይጫወታሉ ይጨፈራሉ፡፡

ችቦ ሲታሰርና ዳመራው ሲተከል ከወንዶቹ መካከል በዕለቱ መገኘት ያልቻለ ቢኖር የለም ተብሎ ደመራ
ሳይወጣለት አይቀርም፡፡ ለሌሎች የሚደረገው ሁሉ ለእርሱም ይደረግለታል፡፡ በሌላው ልጅ ምትክ የታሰረውን
ችቦና ዳመራ አባት ይይዛል፡፡ ዳመራው ከተለኮሰ በኃላ ማስቃላ ዮ! ዮ! እያለ ወደ ቤት ተመልሶ ከእናት

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 22


ከእህቶቻቸው እና ከባለቤቶቻቸው ማስቃላ ዮ! ዮ! ከተባባሉ እንደገናችቦቻቸውን በመያዝ በባህላዊ መሪ ወደ
ተተከለው ዳመራ ቦታ ያመራሉ፡፡ እዚያው ማስቃላ ዮ! ዮ! እያሉ በባህላዊ መሪው ተመርቀው ወደ የቤታቸው
ይመልሳሉ፡፡ በዋናነት በህላዊ መሪው ቢታ ብታንቴ ነው፡፡ ቢታ ብታንቴ የሚባለው በአካባቢው ባላባት የዚያ
ቀበሌ የመሬት አስተዳደር እና ባህላዊ መሪ እንዲሆን የተመረጠ ወይም የተሾመ ማለት ነው፡፡ ማስቃላ ዮ! ዮ!
(Masqqala Yoo! Yoo!) እያሉ የተለያዩ የበረከት ሀሳቦችን ይለዋወጣሉ፣ (መስቀል እንኳን መጣህልን) ማለት
ነው፡፡ አሰከትለውም እየደጋገሙ ማስቃላ ማስቃላ ዮ! ዮ! ዳናው ዳና አልባ ዙማዳን ዳና (አልባ ዙማ በአከባቢው
የሚገኘው ትልቅ ተራራ ሲሆን እንደሱ እንኖራለን እንደ ማለት ነው፡፡) ክንቲ ሻላዳን ዳና (ክንቲ ሻላ ማለት
በአከባቢው የሚገኘው ትልቅ አለት ሲሆን እንደሱ እንኖራለን እንደማለት ነው፡፡ መርናው ዳና (ለዘለዓለም
እንኖራለን) ማለት ነው፡፡ ሀረይ ካጨ ከሳናዳን (አህያ ቀንድ እሰከ ሚያበቅል ድረስ እንኖራለን በማለት ነው)
ገላኦይ ገል ውራናስ ዳና (ልጃገረዶች አገብተው እስኪያልቁ) ድረስ እንኖራለን፡፡ እንዲህ እያሉ እርስ በርስ
ይሸካከማሉ ይተቃቀፋሉም፡፡
የመሰቀል ጊዜ ወጪ የማንንም በር የሚያንኳኳና ሀብታምና ደሃ የማይል ዓመቱን ሙሉ ተዘጋጅቶናቆጥቦ
በመገኘት አንድ የሚሆኑበት መሆኑ በዓመቱ ውስጥ አንድ በሞት የተለየ ዘመድ አዝማድ ወይም ቤተሰብ ብኖር
የመስቀል ደመራ ከመውጣቱ አስቀድሞ ይለቀስና ለመጨረሻ ጊዜ ከሀዘን የሚወጡበት ሥርዓት መኖሩ ድንገት
በመስቀል ደመራ ዕለት ሰው ሞቶ ቢገኝ በብሔረሰቡ በመስቀል ደመራ እሳት ተበልቷል በሚል የማይለቀሱበት
ሥራዓት መኖሩ፣የመስቀል ጊዜ ዘፈንና ጭፈራ የምግብና የመጠጥ ዝግጅቶች የመስቀል በዓል ደመራን ሥነ-
ሥራዓት ልዩ የሚያደረጉ ናቸው፡፡ በጎፋ ብሔረሰብ የመስቀል ዘፈኖችና የአጨዋወት ሥራዓቶች የተለየ
የሚያደርጋቸው ልዩ ባህሪያት አሉ፡፡

ከእነዚህም ለአብነት
 የመልከአ ምድር አቀማመጥንና የመሬቱን ለምነት መግለጫ የመሆኑ፣
 የብሔረሰቡ ተወላጆች የተለያዩ ሰብሎች አምራችና የሥራ ተነሳሽነታቸው ከፍተኛ መሆኑን
አመላካችነቱ፣
 በግል ከመሠራት ይልቅ ተሰባስበው በጋራ የማምረት ልምድ ያካበቱ መሆናቸውን፣
 የሠላም ማብሰሪያ የደስታና የፍቅር መግለጫ ዋነኛ ድልድይ የመሆኑ፣
 የትዳር ጓደኞችን የመምረጫ ሁነት ስለመሆኑ በዓይነተኝነት ሊጠቀሱ የሚገቡ ናቸው፡፡
የመስቀል ዘፈኖችና አጨዋወት ሥራዓቶች ከባህሪያቸው አንጻር በ 3 የከፈላሉ፡፡
እነዚህም በመስቀል ከጅማረው ቀን እስከ መጨረሻው ወይም እስከ ሽኝት ቀን ድረስ የሚዘፈኑና የሚጫወቱት
የጫዋታ ዓይነቶች ጋዜ ወይም ኢኤ፤ ጋሼ፣ሎያ፣ጋሳሊያን ኦይካ፤ ጊሶሌ እንደ ትንፋሽ መሰብሰቢያ ዘፈኖች
ሲበሉና ሲጠጡ የሚዘፈን ወይም የሁል ጊዜ ዘፈኖች ተብሎው ሊጠቀሱ የሚችሉት ደግሞ ባራንቼ፣ላሌና ሄሎ
ሄራሳ የሚባሉው ናቸው፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ በዋናነት የመስቀል በዓል የመጨረሻው ቀን ለሽኝት (ሞይዞስ) የሚዘፈን በብሔረሰቡ አጠራር
"ሆሴ" (Hosse) ይባላል፡፡ በመሆኑም ከሌሎች በብሄሩ ከሚከበሩ በዓላት ይህ ጋዜ ማስቃላ ይጅግ የተለዬና በብዙ
የጨዋታ ዓይነቶች የታጀበ ነው፡፡ ጋዜ ማስቃላ (መስቀል) በጎፋ ብሔረሰብ ከዳመራው ዕለት ጀምሮ በቀጣዮች
7/ሰባት ቀናት ማለትም እስከ መስቀል ሽኝት ቀን ደረስ ባለው በከፍተኛ ድምቀት የሚከበር ሲሆን በዚህ ጊዜ
አዳዲስ ክስተት ስፈፀም ወይም የሚከናወን ሥራዓት አላቸው፡፡
እንደ አጋጣሚ ሆኖ በሚያከብሩበት አከባቢ በደመራው ዕለት ሰው ቢሞት ቀብርና ሌሎች ሥራዓቶችን
በሟቹ ደጅ ላይ ነዋሪዎች ተሰብስበው ይፈፅሙና የማይለቀስበት በመስቀል እሳት ተበልቷል

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 23


በብሔረሰቡ አባባል ማስቃላ ታማን ሜተትስበማለት ለቀስተኞች ሀዘናቸውን እንዲያወርዱ በማድረግ
ማስቃላ ዮ! ዮ! እያሉ ወደ ተጀመረው የመስቀል በዓል ሥነ-ሥራዓት የሚመለሱበት ሥራዓት አላቸው፡፡
ሌላው ደግሞ የመስቀል ደመራ እሳት ከተሎከሰበት ቀን ጀምሮ 7 ተከታታይ ቀናት በመቁጠር በቤቱ
መጠጥና መብል ያዘጋጀው አባወራ ብኖር ተጫዋቾችን ወደ ራሱ በራፍ በመጋበዝ እዚያው
እንዲጨፈሩ እና እንድጫወቱ የሚደረግ ሲሆን በዋናነት ያለማንም ቅስቀሳ በራሳቸው በጎ ፍቃድ
በሚኖሩበት አከባቢ ባለው አደባባይ ወይም በብሔረሰቡ አገላለፅ ቃኤ (Qaa77e) ላይ ወተው በአንድነት
የሚጫወቱ ይሆናል፡፡ ታዲያ በትልቅ ጉጉትና ጥበቃ የመጣውን መስቀል በዓል ብሔረሰቡ በታላቅ
ክብርና ወግ ሲያከብሩ ቆይተው መስቀል በሚሸኝበት ጊዜ እንደ አቀባበሉ ለሽኝቱም የሚፈፀማቸው
ልዩ ልዩ ተግባራት ያደርጋሉ፡፡
4. የመስቀል ጨዋታዎች በጎፋ
በጎፋ ብሔረሰብ በመስቀል በዓል ወቅት አዘውትረው የሚጫወቱባቸው ጫዋታዎች ከነትርጉማቸው
በማብራሪያ ቀጥለን እንመልከት፡፡
1 ኛ. ጋዜ (እኤ) ጋዜ ማለት ደስታ መልካም በዓል እንደ ማለት ነው፡፡
የጫወታው ሥነ ሥርዓትም በቡድን የሚጨዎቱ ሲሆን በቡድን ውስጥ ወንዶችና ሴቶች ጥንድ ጥንድ
ሆነው ቦታ በመቀያየር ይጫወታሉ በዚህ ጨዋታ በጎፋ ተወላጆች ምርታማ መሆናቸውን ለሥራ
ያላቸውን ተነሳሽነት መልከአ ምድራዊ አቀማመጥ እያነሱ ይዘፍናሉ፡፡ ይህ ጫውታ ገና ለመስቀል ከ 1
ወር በፊት እያለ እንደ ዋዜማ እየተዘፈነ ይቆይና ልክ የደመራው እሳት እንደተሎኮሰ እጅግ እየደመቀ
ይቀጥላል፡፡
2 ኛ. ጋሼ የጨዋታው ሥርዓት
ይህ ጨዋታ በተለይ ኦ ሆያ ጋሼ ማለትም ጎፋ ብሔረሰብ በጤፍ አምራችነቱ የሚታወቅ መሆኑን
የሚገልፅ ሲሆን የጤፍ ነዶ ክምር በኩንታል ያመረተዉን ለሁሉም በማድረስ ባለፀጋ መሆኗን ለመግለፅ
የሚጠቀሙብት የጨዋታ ዓይነት ነዉ፡፡ ሁሉም ጭፈራዎች ትከሻ ለትከሻ ተቃቅፈዉ ክብ ሠርተዉ ኦ
ሆያ ጋሼ እያሉ ያጫወታሉ፡፡
3 ኛ. ጋሶሊያን ኦይካ
ይህ ጨወታ በተለይ መስቀል ከመድረሱ በፊት የቦቆሎ ምርት እያጋዙ የሚጨፈሩ ሲሆን ሥራውን
ለማቀላጠፍ ስሉ ይህን ጭፈራ በመጨፈር የመስቀልን መምጫ በማወደስ ሂደታቸውን ይወጣሉ፡፡
አጨፋፈሩን በተመለከተ አ/አደሩ ደጅፍ በህብሬት ሆኖ እየጨፈሩ ካደመቁ በኃላ በሕብረት ወደ ቆላ
ይመለሳሉ፡፡ በዕለት የተዘጋጀውን ቦረዴ እየጠጡ ይደሰታሉ፡፡
4 ኛ. ግሦሌ (ሆይግሶሌ) የጨዋታው ሥራዓት
ግሦሌ ፅንሰ ሀሳቡ የጥጋብና ብሩህ ዘመን መሆኑን መቀበያ እርቅ ማድረጊያ በአዲስ ዓመት አዲሱን
ጤፍ አስፈጭተው (አሽቶ) ማቡካትን (ጊንዴሳ) በአጠቃላይ የደስታ መግለጫነት ሲሆን በተጨማሪም
(ሎሚ፣የሸንኮራ አገዳ ጥሬ ስጋ ወዘቴ…. እርስ በርስ በማቀባበል የአንድነትና የፍቅር መግለጫ
ያደርጉታል፡፡ ወንድና ሴት ተመራርጠው ከሚወዱት ወይም ከሚትወዱት ጓደኛ ጋር በመሆን ዳሌ
ለዳሌ እያገጫጩ የሚጫወቱት ጨዋታ ሲሆን እጅግ ማራክ እና ውብ ጨዋታ ነው፡፡
5 ኛ. ሄራሳ (ሄሎ ሄራሳ ሥራታ)

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 24


ይህን ጨዋታ ከሁሉም ለየት የሚያደርገው ጨዋታው ለመስቀል ቦርዴ ዝግጅት ላይ በደንቦ (ፖጎሎ)
በመዳጥ በመስቀል ዋዜማ ሴቶች ይጫወቱታል፡፡ ወንዶች ደግሞ ያልተጨመቀውን (ኦርጮ) እየተመገቡ
በጭፈራ ያደምቁታል፡፡ በማግስቱ በልተውና ጠጥተው ሲያበቁ አባቶች ወደ እርድ ሥራዓት ይሄዳሉ፡፡
6 ኛ. ሆሴ (Hosse) የጨዋታው ሥርዓጥ
ይህ ጨዋታ ከመስቀል ዋዜማ አንሥቶ እስከ ማብቀያ (ሽኝት) ጊዜ ድረስ የሚጫወቱት የመስቀል
ጨዋታ ሲሆን መስቀል የሚሸኝበት ጊዜ ከበፊቱ ይልቅ ያለ የሌላ ኃይላቸውን አሟጠው በመጠቀም
ወንዶችም ሴቶችም እየደጋገሙ ይጫወታሉ፣ አጨዋወቱም 5 (በአምስት) ሜትር ልዩነት 2 (በሁለት)
ቡድን ተካፍሎ የሚጫወቱበት ሲሆን ከአንደኛው ቡድን ወንዱ እየጨፈረ ሄዶ ከላለኛው ቡድን
የሚወደውን ጓደኛ እየጨፈረ ይዞ ይመጣል፡፡ እንግዳዋን (ሴቷን) እንደተቀበሏት ጭፈራውን ያደምቃሉ፡፡
በሌላ በኩል ከሌላኛው ቡድን ወንዱ እየጨፈረ መጥቶ ደስ ያለትሴት ልጃገረድ አቅፏት እየጨፈረ
ይዟት ወደ ቡድን ይመጣል፡፡ የተወሰደበት ቡድን ወንዱምላሹን ያችን ልጃገረድ አቅፏት እየጨፈረ
ይመልሳል፡፡ በዚህ ዓይነት ጨዋታው ለመተጫጨትም መነሻ ይሆናል፡፡
7 ኛ. ባራንቼ
ባራንቼ ማለት ሠላም፣ፍቅር ማለት ሲሆን አገልግሎቱም የተጣሉትን ለማስታረቅ፣ ቂም በቀል የለም፣
ቂም ያሰበ ቢሮር እንደመረገም ስለሚቆጠር ጓደኛውን ለማስታረቅ፣ እርስ በርስ መግባባት እንደሚችል
እነዚህ ሁለቱ ጨዋታዎች በጎፋ ብሔረሰብ የጨዋታ ሥርዓት ለመስቀል፣ ለጥምቀትና ለደቦ ሥራ ጊዜ
እየበሉና እየጠጡ ለመዝናናት (ባሎቴሳስ) የሚጫወቱት የጨዋታ ዓይነት ነው፡፡

8 ኛ. ላሌ የላሌ ትርጉሙም
ሀገርን ከሀገር ጋር በማወዳደር ጀግንነት ምርታማነትን ለማሳየትና ለማወዳደር ህብረተሰቡም ሆነ
ግለሰቡ ይሞግሳል፣ ይወደሳል፡፡ የብሔረሰቡ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ይዘትን ለመግለጽም
ያገለግላል፡፡ ጨዋታውን ድምፃዊያን (አውጪዎች) ተራ በተራ ሆኖ ሲያቀነቅኑ ታዳሚዎች ይቀበላሉ፡፡
ወንዶችና ሴቶች ከድምፁ ጋር ዜማንና ምቱን አዋህደው ይጨፍራሉ፡፡
9 ኛ. ሄላሎ (Heelalo)
ሄላሎ ይህ ጨዋታ መስቀልን በደስታ ከተቀበሉ በኃላ ከሦስትና ከአራት ቀን በኃላ የሚጫወቱት ጨዋታ
ነው፡፡ ይህም የሆነበት ዋና ምክንያት በጉጉት ሲጠባበቁ የቆዩትን የመስቀል በዓልን በደማቅ ሁኔታ
ሲቀበሉ በደስታ እየጨፈሩ እየዘለሉ በሁለት እና በሦስት ቀን ናፍቆታቸውን ሲወጡ ይደክማቸዋል፡፡
የሄላሎ ጨዋታ ግን እርስ በርስ በመተቃቀፍ ክብ ሠርተው በእንድነት በተረጋጋ መንፈስ የሚጨፈሩት
በመሆኑ ይመረጣል፡፡
10 ኛ. ወሎ ቦላዶ (Wollo Bolado)
ይህ ጨዋታ ከላይ በተራ ቁጥር ዘጠኝ ላይ ከተጠቀሰው ሄላሎ ከሚባለው ጨዋታ ጋር ተመሳሳይነት
ያለው ሲሆን ዜማውም ሆነ አጨፋፈሩ ከሄላሎ ጭፈራ የመፍጠን ዓይነት ሁኔታ ሲኖረው እጅግ
ማራክና ቆሞ ለሚመለከት ሰው ቀልብ የሚስብ የመስቀል ጊዜ ጨዋታ ነው፡፡
11 ኛ. ሊላ (Liilla)
ሊላ ሆያ ኤራ ሊላ
ሊላ ማስቃላ ማታ

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 25


ማስቃላ ሆምቦጫ ከሰሳ
ሊሊ ሉትሻ ኩታ ሊላ-ሆ-ያ ኤራ ይላሉ ሊላ ማለት ሊላ ናልን እንጂ ማለት ነው፡፡ እንግዲህ እንዲህ
እንዲያ እያሉ በዜማ እያዘሙ ይጨፍራሉ ትርጓሜውም መስቀል እንኳን መጣልን ከሚለው ጋር
የሚመሳሰል ሲሆን የመስቀል ጊዜ ያለው ደስታ የሚበላው የሚጠጣው መጠጥ በተለያዩ ጨዋታዎች
ሀሴት በማድረግ በአጠቃላይ መስቀል ሲቀበሉ በጎፋ ብሔረሰብ ያሉው ደስታ ወደር እንደሌለው
በመግጽ የሚጫወቱት
12 ኛ. ሎያ ባይ ሎያ ባይ
ይህ ማለት ትርጓሜው የመስቀል በዓል ጥሩ ነው እንደ ማለት ነው፡፡ ታዲያ ይህ ጨዋታ የመስቀል
በዓል መድረሻ መባቻ ስለመሆኑ የሚገልጽ ልዩ መልዕክት ያለው ነው፡፡ መስቀል ሲመጣ በዓመቱ በጎፋ
ብሔረሰብ በአከባቢው ሳይጠይቅ የሚናገሩ የተፈጥሮ ምልክቶች አሉ፡፡ ለምሳሌ አዳይ አበባ ያብባል
የመጀመሪያ ጤፍ የተዘራው ያብባል
ሎያ ባይ ሎያ ባይ፣ ሎይ ማስቃላ ባይ፣
ማስቃላይ ኡፋይሳ ባይ፣ ሙሳኔ ኡሻ ባይ ፣
ጋሼይካ ፊልጽምስ፤ አድልኤይካ ጪይስ / ጋሼይ ፊልጽምስ ባይ፤ አድልኤይ ጪይስ ባይ
እያሉ በዜማ እያቀናቀኑ በተሠማሩበት የሥራ መስክ ላይ ባሉ ጊዜ ይመጣሉ፡፡ ታዲያ በዚህ መልኩ
የተጀመረው መስቀልን ተቀብለው እስከ ሽኝት ሲጫወቱ ይቆያሉ፡፡

13 ኛ. ሄሎ ላሎ ሀሳ (Heello laale Hasa)


የመስቀል በዓል ዓመቱን ጠብቆ በሚመጣበት ጊዜ በጎፋ ብሔረሰብ በማህበራዊ ግንኙነት ውስጥ ባህላዊ
ክንዋኔዎች ሲፈፅሙ ከጥንት ጀምሮ ይስተዋላል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ አንደኛውን በሄሎ ላሎ ሀሳ
ጨዋታ የሚንመለከተው ይሆናል፡፡ ለምሳሌ ዓመት ጠብቆ መስቀል ስመጥ ከቤትሰቡ ውስጥ በሞት
የተለየ ሰው ካለ የመስቀል ደመራ ችቦ በሚመጣበት ጊዜ በየቤቱ የሚለቀስበት ሥራዓት አለው፡፡ ታዲያ
ሀዘንተኛ ቤተሰብ እቤቱ ስያለቅስ ሌላው ደግሞ በየቤቱ የመስቃላ ደመራ ከወጣ በኃላ በጋራ ሆነው
በአደባባይ የዳመራ እሳት ለማውጣት ባዘጋጀበት ስፍራ በአንድነት የመስቀል ደመራ ካወጡ በኃላ ወደ
የቤታቸው አይመለሱም ሄ-ሎ-ላሎ ሀሳ እያሉ እየጨፈሩ ወደ ሀዘንተኛ ቤተሰብ በመሄድ በጋር ለአንድና
ለመጨረሻ ጊዜ አልቅሰው ሄሎ ሀሳ ጨፈረው ሀዘናቸውን እንድረሱ ለቅሶየወጣበትን ቤት ሁሉ በመዞር
የሀዘን ማስረሻ ሥራ ይሠራሉ፡፡ ይህ ከሆነ በኃላ ሀዘንተኛው ሀዘኑን ይረሳና ወደ መስቀል ደስታው
የሚቀላቀል ይሆናል ማለት ነው፡፡

14 ኛ. ባዳላይ ሻምባራ ደምባን ባራቶ


ይህ ጭፈራ በቡድን ሆነው ተቃቅፈው በሕብረት የሚጫወቱት ጨዋታ ሲሆን በአከባቢው በስፋት
የሚታወቀውን የቦቆሎ ምርትን አጉልቶ የሚያሳይ ነው ማለት ይቻላል፡፡ መስቀልን በጎፋ በሔረሰብ
ስንመለከተው እጅግ ብዙ መልዕክቶችን በውስጡ የያዘና ለብሔረሰቡ ተወላጂ ልዩ ክብርና አድናቆት
በውስጡ አዝሎ የያዘ ታርካዊ በዓል ነው፡፡
ለምሳሌ የመስቀል ደመራ የሚወጣበት ቀን (Tami ke7iya qamma) በመባል በመጀመሪያ ዕለት
ይጠራል፣ ቀጥሎ ሁለተኛው ቀን (Bido qamma) ተብሎ ይጠራል፣ የተባሉበት ምክንያት
o 1 ኛ የደመራን እሳት ዝናብ የሚያጠፋበት ቀን

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 26


o 2 ኛ እስከ 6 ሰዓት ቆይታ ለቅሶ ያለቤት በራፍን እየዞሩ አልቅሰው ሀዘንን እንዲረሱ
የሚያረጉበት ከ 6 ሰዓት በኃላ ለምግብ ዝግጅት የሚገቡበት ሲሆን ወንዶች የእርድ ሥነ -
ሥራዓት የሚፈጽሙበት ጊዜ በመሆኑ ነው፡፡
o 3 ኛ ማለትም ሦስተኛው ቀን በመስቀል ሣምንት ጶቴ (Dhote qamma) ተብሎ ይጠራል፡፡
ምክንያቱም በዕለቱም አላፊው አግዳሚው ሁሉ ለመጣ እንግዳ በሙሉ ገንፎ ተገንፍቶ
ይሰጣል፡፡ በልቶ ከቤት ስለሚወጣ (Dhote qamma) ተብሎ ተሰይሟል፡፡

5. የመስቀል በዓል ሽኝት ጊዜ


መስቀል በጎፋ በሔረሰብ በሚሸኝቤት ጊዜ ለሽኝቱ ተብለው የሚደረግ የምግብ ዝግጅት ሥራዓት
መኖሩ እና የመስቀሉ ሽኝት ጊዜ ዘፈኖች ተለይተው የሚታወቁ እና ከጨዋታ መነሻ ማንኛውም
የብሔረሰቡ ተወላጅ የሆነ የሽኝት ጊዜ ጨዋታ መሆኑን መናገር መቻሉ ዓይነተኛና ልዩ ያደርገዋል፡፡
የመስቀል ዳመራ ከወጣበት ቀን አንስቶ ለሰባት ተከታታይ ቀናት ተቆጥረዉ የመስቀል ሣምንት ተብሎ
የሚታወቁ በመሆናቸው የመጨረሻው ወይም ሰባተኛው ቀን መስቀል የሚሸኝበት ይሆናል፡፡ በብሔረሰቡ
አንደ ሁኔታው ለመስቀል በዓል ሽኝት ጊዜ የሚዘጋጁ የመብልና የመጠጥ ዓይነቶች አሉ፡፡

ከምግብ ዓይነት እንደ ገንፎ፣ሥጋ፣ቡላ እና ሌሎች ከመጠጥ ዓይነቶች ደግሞ ቦርዴ፣የጌሾ


ጠላ፣ሙዴ፣ማር እና ሌሎች መስቀል በዓል በሚሸኝበት ቀን ከትንሽ እሰከ ትልቅ ቀኑን ጠብቀው /ቤላ
ጪሻ/የአዳይ አበባ በእጃቸው ይዘው ወደ የሚጫወቱበት አደባባይ /ቃኤ/ የሚወጡ ሲሆን ይህም ያለ
ቅስቀሳ የሚፈጽሙትና ምናልባት ቀኑን ያላወቀ እንኳን ቢኖር የመስቀል በዓል ጨዋታውን ሰምቶ
የሽኝት ጊዜ ጨዋታ መሆኑን ያውቃል፡፡

ሆሴ /Hosse/ እና ጋዜ /Gaze/ በተደጋጋሚ በዕለቱ የሚጫወቱት ሲሆን ከሌሎች ቀናት በተለየ መልኩ
በከፍተኛ ስሜትና ደስታ ነው፡፡ በዚህ ጊዜ በተለይ ሆሴ ጨዋታ ተቃቅፈው እየጨፈሩ ፊታቸውን ወደ
ምስራቅ በማዞር 10 ሜትር ያህል ወደ ፊትና ኃላ እየሄዱ ጨዋታውን በድምቀት የሚጫወቱት ሲሆን
ወደ ምሰራቅ የዞሩበት ምክንያት የሠላም፣የፍቅር እና የጥጋብ ዘመን ይሆናል ተብሎ ስለሚታመን ነው፡፡
ታዲያ በዚህ ሽኝት ጊዜ በአከባቢው ታዋቂ የተባሉ ሽማግለዎች ይገኛሉ፡፡ ቢታንቴዎች
የዕድሜ ባለፀጋ የሆኑት በተገኙበት ፊታቸውን ወደ ምስራቅ የደርጉ ተጫዋቶች ወደ ፊት 10
ሜትር እየጨፈሩ ከተጓዙ በኃላ በአንድነት እጃቸውን ከፍ በማድረግ ማስቃላ ዮ ! ዮ! ሳሮ ባዳ
ሳሮ ያ! መስቀል በደህና ሄደ በደህና ተመለስ እያሉ በመካከላቸው የሚገኘውን ቢታንቴን
ተከትለው በእጃቸው የያዙትን የአዳይ አበባ ወደ ምስራቅ ይወረውራሉ፡፡ በብሔረሰቡ አባባል
ሆሴ ማስቃላ ላይታን ሳሮ ያ! መስቀል ደህና ሁን በዓመቱ በደህና ተመለስ እያሉ በድምቀት
እየጨፈሩ ማስቃላ ዮ! ዮ! ሳሮ ባዳ ሳሮ ያ! መስቀል በደህና ሄደ በደህና ተመለስ ብለው ለአንዴና
ለመጨረሻ ጊዜ የሚሸኙበት ሥርዓት አላቸው፡፡ በእንዲህ ዓይነት መስቀል ሽኝት ከተደረገበት
ዕለት ገምሮ እስከ መጪው ድረስ በብሔረሰቡ የመስቀል ነገር አይነሣም፡፡
(በአቶ ድንበሩ ድርቤ ዲላ፤ ጳጉሜ 2014)

3.2 የጎፋ ብሔረሰብ የሚነገሩ ሥነ-ቃሎች

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 27


የጎፋ ብሔረሰብ የማንነት መገለጫ የሆነው ጋዜ ማዝቃላ (Mesqel Festivity of Gofa Society) ከብሔሩ መፈጠር
ጀምሮ የዘመን መለወጫ በዓል ተደርጎ የቆዬ ነባር ባህላዊ በዓል ሲሆን፤ የክርስቲና እምነት ወደ ጎፋ ከደረሰ ጊዜ ጀምሮ
ከመስከረም (16) ጀምሮ የሚከበር ሆኖ ተገኝቷል፡፡

በጎፋ ስለ መስቃላ በዓል ሲነሣ አብሮ የሚነሱ የመስቀል በዓል መገለጫ የሆኑ ሥነ-ቃሎች እንደሚነሱ የጎፋ ዕድሜ
ባለፀጋዎች ይገልፃሉ፡፡ ምክንያቱም ሲያብራሩ ሥነ-ቃል ጎበዙን የበለጠ እንድጎብዝ የምያደርግ ሲሆን ስነፉንም
ከስንፍናዉ እንድወጣና ከጎበዞቹ ተረታ እንዲቆም ያደርጋል የሚል ዕምነት ስላለ ነዉ፡፡ በሌላ መልኩ በመስቀል ወጣቶች
ለጋብቻ የሚመራረጡበትና እርስ በርስ የምዋደዱበት (Mate Selection) የምያደርጉበትና ፍቅር የሚጀምሩበት ጊዜና
ሥፍራ ነዉ የሚል ሀሳብ አላቸዉ፡፡ መስቀል እንደ ዘመን መለወጫ ተወሰደ ላሳለፉት ዓመት ፈጣሪያቸዉን
የምያመሰገኑበትና ለቀጣዩ ዓመት የሚለምኑበት እንድሁም በመስቀል ጥሩ ጥሩ ሰዉነትን የምገነቡ ምግቦች
(Delicious Food) ምበላበትና ዕረፍት የሚወስድበት ጊዜ ስለሆነ የመስቀልን መምጣት በጉጉት በመጠባበቅ በተለያዩ
ሥነ-ቃሎች ይገልፁታል፡፡

ከእነዚህ ሥነ-ቃሎች በጥቅቱ ለመግለጽ ያህል፤

1 ኛ ማዝቃላይ ማልኦ ሙዜስ (Mazzeqqalay Mal7o Muzes) ከላይ እንደተገለፀዉ መስቀል ጥሩ ጥሩ ምግብ ያበላል
የሚል መልዕክት ያስተላል፤ ስለዚህ መስቀል ይጠበቃል፡፡

2 ኛ ለላዉ ደግሞ መስቀል በማህበረሰቡ መካከል ልዩነትን በበጎ መልኩ የሚያመጣም ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ ተዘውትሮ በስነ-
ቃል የሚነገረዉ፡- ‹‹ማስቃላይ ዱሪያ ዱሪየስ

ማንቋ ማንቂሴስ ይባላል››

መስቀል በዓመት አንድ ጊዜ የሚመጣ በዓል ስለሆነ ሰፊ ዝግጅት ስለምፈለግ ጠንካራና ጎበዝ የሆኑ ሰዎች በጊዜ ሲዘጋጁ
ሰነፎች በዓሉ ሲደርስ ነው ተፍ ተፍ ማለት የሚጀምሩበት ስለዚህም ገንዘቡን፤ እህሉን፤ ቅቤውንንና በቤቱ የሌላቸዉን
ነገሮች ለመበደር ሀብታም ቤት ለሚሄዱና በእጥፍ ስለሚከፈል ለባለሀብቱ እጥፍ ትርፍ ይገባል፤ ድሀው ግን የበለጠ
ይደሄያልተ ብሎ ይታወቃል፡፡ በመስቀል እርሻ አይታረስም የመብላት የመጠጣትና የመዝናናት ጊዜ ስለሆነ በመስቀል
እርሻ የምያርስ በሥነ-ቃል ይነገርለታል፡፡ ሌለው ደግሞ በመስቀል የተዉሶ ልብስ አይለበስም፡፡ ነገር ግን አንድ
የተዉሶልብስ (ቀምስ) ለብላ ለመስቀል ጫዋታ የሚትሄድ ሴት መንገድ ዳር ማሣ ያለዉን ገበሬ ሲትመለከት ለምኖ
ባመጣው በሬ በመስቀል እርሻ ሲያርስ አግንታ ‹‹ወሴ ቦራ ወሳ ጋሼ ጎየይሶ ጋዴይ ጋኮ›› ትርጓመው ለምነህ ባመጣሄው
በሬ ወደታች እያልክ የምታርስ ማሣው ታርሶ ይለቅልህ!

እሱም ሲመለከታት የትዉሶ ቀሚስ ለብሳ ለመስቀል ጭፍራ መሄዷንአ ግኝቶ (አይቶ) ጋርሳ ቃሚሴያራ ጋዴ ቤሳ ማአዳ
ማስቃላ ጋዛናዉ ቢያሬ አዴ ኤኮ ይላታል ይህ ማለት ለምኖ ለአንድ ቀን እርሻ በመጣ በሬ ወደ ላይ እየተባለ ይታረሳል
እንጅ ወደታች ካለ መልሶ መላልሶ ያረሰበትን ስለሚያርስ ወደ ታች የሚለዉ ሰነፍ ገበሬ መሆኑን ሲያመላክት በመስቀል
ጊዜ ማረሱ ሌላኛዉ የስንፍና ምልክቱ መሆኑን ያመላክታል፡፡ሌላዉ ለመስቀል የተዉሶ ልብስ የሚትለብስ ሴትና አጭር
ልብስ የሚትለብስ ሰነፍ ሴት መሆኑዋን እሱም ጎሼም አድርጓታል ማለትነዉ፡፡

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 28


3 ኛ) ለጦርነት ቀስቃሽ የሆኑ ሥነ-ቃሎች

በጎፋ ሴቶችታ ርክ ዉስጥ Gallo Xammatto (ጋሎ ፃማቶ) የተባለች ሴት ትልቅ ስፍራ ያላት ሴት እንደሆነች
ይናገራሉ:: በአንድ ወቅት መስቀል ሊደርስ ሲል ጦርነት ይነሳል፡፡ ስለዚህም የጎፋ ካዎ ጦርነት ሲያዉጅ እንዲህ ይላል፡፡

Guppiya parra toggadda guppo matha ganxada gumbo toorra oykadda kawo gadho goocha
Guuttoy qaaxin commeysi shoci wodha oyqada ollancha gembo qoxanaw gadha adha!

በዚህ አዋጅ መሠረት በመስቀል ዋዜማ ተዋጊዎቹ ወደ ጦር ሜዳ ሲሄዱ ፈሪዎቹ ለእርሻ ሄደዉ ተመልሰዉ የመስቀል
ጠላ ለመጠጣትበ አንድ ቦታ ተሰብስቦ እያሱ Gallo Xammatto (ጋሎ ፃማቶ) የተባለች ሴት ትመጣና 1 ኛዉን
እግሩዋን ከፊ አድርጋ ፌስ ትለቃለች፡፡ ወንዶቹም በወንድ ላይ የሚትፈሳ ሴት ይህች ሰነፍ ከየት መጣሽ ሲሏት፤ እሷም
መልሳ ወንድ ጦር ሜዳ ወንድን እያገላበጠ የሀገርን ሉዓላዊነት ሲያስከበር ጠላ ተራ የተሰበሰበው እንዴት ዓይነት ሰነፍ
ወንድ ብቻ ነው? በማለት ለጦርነት ትቀሰቅስ ነበርይባላል፡፡

4 ኛ፤ Osso gey uuthi

Oona na7ee gey maathi

በጎፋ ታሪክ ውስጥ እንሰትና ወተት አይነጣጠሉም፡፡ የማንቤት ነው? የሚያስብላዉ እንሰት የማን ልጅ ነው
የሚያስብለው ወተት፤ ይባላል፡፡ እንሰት ድርቅን ከመቋቋም አልፎ በመስቀል ዝግጅት ቡልኦ (ኢቲማ) የሚሠራው
ከእንሰት ነው፡፡ ሌላዉ ህፃናት በጥሩ ጤንነት እንድያድግ ወተት ሰለሚያስፈልግ ነው ይህ የተመስለው፡፡

በመስቀል የተጣላች ሴት መታረቅ አለባት ካልሆነ ሌላ ሚስት የማግባት ዕድሉ የሰፋ ነው፡፡ በዝህ መሠረት የቀድሞ
ምስቱ የሆነች በመስቀል ጊዜ ተጣልታ የተለየች ለመጪዉ መሰቀልም ተለምና እንቢ በማለቷ ተለያይቶ ሌላ አድስ
ሚስት ያገባል፡፡ መስቀል ከመድረሱ በፍት ይህች አድሷ ሚስት እንሰት መፋቅና ዝግጅት ማድረግ ነበረባት፡፡ ነገር ግን
የዱሮ ሚስት አድሷን በአሽሙር ትነካለች እንድህ ስትል Tokkonna Tonchayarre Ittimmay
Uttoo! ሲትል አድሷ ደግሞ

Tokkadda Toylayrre Adde ekka! በማለት ይጎሻሽማሉ፡፡

5 ኛ፤ ሌላዉ በመስቀል ለቅሶና ሐዘን የለም ይባላል ስለዚህ Masqallay Kayo Doggisses መስቀል ሐዘንን ያስረሳል፡፡
በመስቀሉ ዕለት ደግሞ ሰው ከሞተ ማስቃላ ታሚ ሚስ /Mazgalla Tammi Misi/ ይባላል እንጂ አይለቀስለትም፡፡
ሰለዚህ መስቀል የሚደስትቱበትና የሚዝናኑበት እንጂ ሐዘን የለም ይላቸዋል፡፡

6 ኛ፤ በመስቀል ዕለት የተወለደ ልጅ፤ ወንድ ሲሆን ስሙ ማዝቃላ; ሴት ሲትሆን ደግሞ ስሟ ማስቃሎ /Masqallo/
ተብሎ ይሰይማል፡፡ ስለዚህ መስቀል ትልቅ ቦታ ያለውና በብዙ ሥነ-ቃል የሚነገሩ አነጋጋሮችን ያካትታል በመሆኑም የጎፋ
ሕዝብ ቱባ ባህልን አምቆ የያዘ ክብረ በዓል ነው ማለት ይቻላል፡፡

በአቶ ጣሊያን ጣሰው

3.3 የዮኦ ማስቃላ አከባበር ሥነ-ስርዓት በኦይዳ ብሔረሰብ

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 29


የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቀላን ማክበር የጀመረበት ጊዜ በትክክል ቀኑ ባይታወቅም እንደ አከባቢዉ የሀገር
ሽማግለዎች ትውፍት በጥንት ጊዜ የኦይዳ ሰዎች ከሆኑት በዞንጋር አና በጉዳር ዘመን መከበር ሳይጀምር
እንዳልቀረ የሀገር ሽማግለዎች ያስረዳሉ፡፡ ዮኦ ማስቃላ የብሔረሰቡ ዘመን መለወጫ እንደመሆኑ መጠን
በብሔረሰቡ ዘንድ አድስ ዓመት ስመጣ አከባቢው አረንጓዴ ለብሶ፣ ሣርም ድሩ ለዓይን ዕይታ ማራክ ስለምሆን
በኦይዳዎች መስቀል በልዩ ጉጉትና ናፍቆት ከመከበር ባለፌ የብሔረሰቡ ስም ኦይዳ ተብሎ እንድሰየም
የተደረገበት ዋናዉ ምክንያት በኦይድኛ ቋንቋ ኦይዳ ማለት ለመለመ ተመቸ ማለት ሲሆን ዞንጋር ና ጉዳር
(አባትናእናት) የተባሉ ቀደምት ሰዎች በኦይዳ የበኩር ልጃቸዉን ወልደው በምኖሩበት በታችኛ ባልጣ ዞባ
በምባል ንዑስ መንደር በመውረድ አከባቢውን ስመለከቱት ስፍራው ለሰዉ ልጅ ኑሮ ምቹ እንደ ሆኖ ስላገኙ
ኦይዳ በማለት ስያሜ በመስጠት መኖር ጀመሩ፡፡ ኦይዳ የምለዉ የአከባቢዉን ስያሜ ከዛ መነሻ እንደ መጣ እና
በብሔረሰቡ ቋንቋ “ሃና በስታ ኑስ ኦይዳ» ከዛ በኃላ አከባቢው ኦይዳ በመባል መጠራት ተጀመረ፡፡ ሃና በስታ ኑስ
ኦይዳ ማለት ''ይህ ቦታ ለእኛ ተመችቶናል'' ማለትነው፡፡

ህዝቡ በየዓመቱ እንድህ አይነቱ ልምላመ አና ምቾት ይምጣልን እያሉ ዮኦ ኦይዳ ማስቃላ በማለት አድስ
ዓመትን ማክበር እንደ ጀመሩ ይነገራል፡፡ በኦይዳ ብሔረሰብ ዘንድ መስቀል በልዩ ድምቀት የምከበር ታላቅ
ህዝባዊ መሠረት ያለዉ ወካይ ባህል ነው፡፡ የመስቀል በዓልን በኦይዳ ሩቅ ያለ ዘመድ አዝማድ በመጠራራትና
በዕለቱ በየበቱ አቅም በፈቀደ መልኩ እያከበሩ ቤት ያፈራውን ከጎረበት ጋር እና ዘመድ ጠያቅ ከለላቸዉ እና
ጧር ቀባር ከለላቸው አቅመ ደካሞች ጋር አብረው የምያከብሩት በዓልነው፡፡ ይህን ክብረ-በዓል ብዙዎች
በኦይዳ በናፍቆትና በከፍተኛ ጉጉት የምያከብሩት ሲሆን በዮኦ ማስቃላ የተለያዩ በዓል በዓል የምሸቱ ነገሮች
በበዓሉ መቃረብ ወቀት መታየት የምጀምረው ገና ለበዓሉ ሦስተ ወራት ስቀሩት በልዩ ትኩረት የተለያዩ
ቅድመ ዝግጅቶች ያደረጋሉ፡፡ (ነሔሰ 18/2014 ዓ/ም አቶ አየለ አሸናፊ)

3.4.1 ዮኦ ማስቃላ ቅድመ ዝግጅት በኦይዳ ብሔረሰብ

በኦይዳ ብሔረሰብ ዘንድ የመስቀል በዓልን ሁሉም የብሔረሰቡ ተወላጆች በዓመት አንድ ጊዜ በወረሃ
መስከረም ለአንድ ሳምንት ያክል እና ከዚያም በላይ ለሆነ ቀናት እንደ አቅሙ በድምቀት ያከብራል፡፡ ለመስቀል
በዓል በብሔረሰቡ አባላት የቅድመ-ዝግጅት ሥራን ሁሉም በመከፋፈል ዮኦ ማስቃላ ስደርስ ምንም ሳይቸገሩ
በሳቅ በደስታ ማክበር እንድችሉ በቅድምያ ከምሰሩ ሥራዎች መካከል ምግብና መጠጥና ለበዓሉ ማድመቅያ
ለልጆችና ሴቶች የምገዙ ወይም የምደረጉ አልባስ ዝግጅት ይገኙበታል፡፡ በዓልበም መጣበት ጊዜ ዕለቱን
በደመቀና እጅግ ባማረ መልኩ ለማክበት የምፈልግ ሰዉ ገና በዓሉ ሳይደርስ ብር መቆጠብ እና ስለመጭዉ
ዘመን ከወድሁ ማሰብና መጨነቅ የተለመደ ነባር የቁጠባ ባህል ማኒቅያ መንገድ ነው፡፡ ስለዚህ ማንም ሰው
በኦይዳ ቁጠባ ያደርጋል ማለት ነው፡፡

3.4.2 ማስቃላ ዝግጅት የወንዶች ሚና

ዮኦ ማስቃላን ለማክበር በኦይዳ ብሔረሰብ ለአቅመ አዳም የበቃ ትዳር የመሰረተ ወንድ ሰው በየቤቱ ለበአዓሉ
ድምቀት የምሆኑ ነገሮችን የማመቻቸት ኃላፊነት ተጥሎበታል፡፡ በዚህ መሰረት ወንድ ሰው የእርድ በሬ

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 30


እንድገዛ ከአከባቢዉ ለሎች አባወራዎች ጋር በመተባበር በዓሉን ለማክበር ገና ሦስት ወር ስቀረው በቡድን
በመሆን የእርድ በሬ ማዋጮን ያጠናቅቃሉ፡፡ በማህበረሰቡ ዘንድ ለዮኦ ማስቃላ በሬ ለመግዛት ሞልአ በሚባል
ማህበራዊ ህይዎት ይደራጃሉ፡፡ በተደራጁት ማህበር ዓመት ለምከበር በዓል የእርድ በሬ ግዥን ለማከን ገንዜብ
ይቆጥባሉ፤ቤት ዉስጥ ለሴቶች ለበዓሉ የምሆኑ እህሎችን ይሰጣል እንድያዘጋጁ፤በዓሉ እየቀረበ ስመጣ
ለልጆች ልብስ ይገዛል፤ ከልጆቹ ጋር በጋራ በመተባበር ለዮኦ ማስቀላ ክብረ-በዓል እንጨት (ማገዶ) በመልቀም
ና በመፍለጥ ምስቶቻቸዉን በሥራ ያግዛሉ፤ቤት ዉስጥ የደረሰ ታላቅ ልጅ ካለ በማስከተል ወደ ዱር እና ማሳ
በመሄድ ለዳመራ እንጨት ይመርጣሉ፤ዳመራ እንጨት ቆርጠዉ ያመጣሉ፡፡ ለበሬእርድ የምሆን ቢላዋ
ያዘጋጃሉ በጊዜ፤ በበዓሉ ዕለት ወደ እርድ ቦታ በመሄድ ሥጋ ያመጣሉ፤ ያመጡትን ሥጋ ለጥሬ እና ለጥብስ
የምሆነዉን ቆርጠው ለሰቶች ይሰጣሉ፡፡

3.4.3 በዮኦ ማስቃላ ዝግጅት የሴቶች ሚና

በዮኦ ማስቃላ ሴቶች ከፍተኛ የሥራ ጫና ያላቸዉ ሲሆን ከበዓሉ መጀመርያ ቤት ዉስጥ የተለያዩ ተግባራትን
ያከናዉናሉ ቤት ማዘጋጀት (ማስዋብ) በበዓሉ ዕለት ለምበላና ለምጠጣ ምግብ እህል መሰብሰብ እና
መፍጨት፡ሴቶች ልክ እንደ ወንዶች በኦይዳ ለበዓሉ የሤቶች መተባበርያ ማህበር ሁለትና ከሁለት ሴት በላይ
በመሆን በቡድን ይደራጃሉ፡፡ በምደራጁት የበዓል ሥራ ላይ ሴቶች በጋራ በመሆን ለበዓሉ እህል
ይፈጫሉ፤ቅመማ ቅመም ያዘጋጃሉ፡፡ ይህ የሴቶች የሥራ ማህበር ወጋል ተብሎ ይጠራል፡፡ ለበዓሉ የሚፈጩ
እህል ዓነቶች፡- ጤፍ፣ በቆሎ፣ ማሽላ፣ ስንዴ፣ ዘንጋዳ (ቀይማ ማሽላ)፣ ገብስ እና ከቅመማ ቅሜም ዓይነቶች
(አብሽ፣ ተልባ፣ ነጭ አዝሙድ ና ጥቁር አዝሙድ፣ ጅንጅብል፣ ፌርጋ (በርበሬ)፣ በሶብላ፣ ድንብላል፣ ኮሮርማ
(ኦካሼ) እና ፈጦ (ስብካ) በወጋል ሆነው እንደ የግለሰቦች ኢኮኖሚ ደረጃ የወጋል አባላት ከራሳቸዉ ጋር
የምፈጩበትን ወፍጮ ይዘው በመምጣት እየተጫወቱና እየዘፈኑ የዮኦን ማስቃላ እህል በደስታ ይሰራሉ፡፡

3.4.4 በዮኦ ማስቃላ ጊዜ የምበሉ የምግብ ዓነቶች

 በሥጋ የምበላ የቆጮ ቅጣ


 በቀጭኑ የምጋገር የቆጮ ቅጣ (ሎቴ)
 ጱፌ (ሙልሙል)
 ጶቄ (ከታመሰ በቆሎ የምሰራገንፎ/ በቅበና በቅመማ ቅመም ሞቅ ብሎ የሚዘጋጅ)
 የጤፍ እንጀራ
 ጥሬ (ቁርጥሥጋ) ና ጥብስ
 ማር (ሻዳ) በቅጣ የሚበሉ ከብዙ በጥቅቱ ናቸው፡፡
3.4.5 የመጠጥ ዓይነቶች

በኦይዳ ማህበረሰብ በዮኦ ማስቃላ የሚጠጣው ባህላዊ መጠጥ ከገብስ፣ ከጤፍ የሚሰራ ጠላ አለ፡፡ በብሔረሰቡ
የምጠጣው ጠላ ዳና ተብሎ ይጠራል፡፡ ዳና ማለት በኦድኛ ቋንቋ ቦርደ ጠላ ማለት ነው፡፡ በኦዳብ ሔረሰብ
ለዮኦ ማስቃላ ዝግጅት ሦስት ዓነት ቦርደ ጠላዎች በልዩ ጥንቃቀ ይዘጋጃል፡፡ 1 ኛ ባሽንቻ፣2 ኛ ሶንገ በመባል
ይታወቃላ፡፡ ሦስተኛው ጠላ ብዙም ያልጠነከረ ኃይሉ የቀነሰ ጠላ ሲሆን በክብረ-በዓሉ ዕለት ሰው በየፍላጎቱ

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 31


እንደጠጣ ተዘጋጅቶ በባህላዊ የጠላ መጠጫ ቀርቦ ይጠጣል፡፡ የኦይዳ ብሔረሰብ ቦርደ ጠላን በባህላዊ የጠላ
መጠጫ ሃላ ከተባሌ ወይም በጫ ተብሎ በምጠራ ቅልና የቅል ሾርቃ አፍ ለአፍ በማገጣጠም የቀረበውን ጠላ
ወደ አንድ ጎሮሮ እንደምወረድ በማስመሰል ይጠጣሉ፡፡ ይህም የምያመላክተዉ በኦይዳ ብሔረሰብ ዘንድ ከአንድ
ማዕድ አብሮ የተቋደሰ፤ከአንድ የጠላ መጠጫ የተጎነጨ እንደ አንድ ቤተሰቡ እና ቅርብ ወዳጅ ተደርጎ
ይቆጠራል፡፡ ይህ ብቻም ሳይሆን የአብሮነት መገለጫ ማሳያ እና በችግር በደስታ የምጠያየቁ ቅርብ ወዳጆችም
ሆነው ይቀራሉ የምል እምነትም እንዳለ ይነገራል ፡፡

(መረጃዉን የሰጡት የብሔረሰቡተ ወላጆች (አቶ ደስታካሳ፣አቶ ግዳሻዉግዛ፣ ወ/ሮ ታመነች ድንቁእና ለሎች
የብሔረሰቡ ተወላጆች፡ነሔሰ/2014 ዓ/ም)

3.5 በኦይዳ የአመጋገብ ሥርዓት


የኦይዳ ብሔረሰብ የአመጋገብ ወግ በሁለት የተከፈለ ሲሆን አንደኛው በማንኛውም ሰዓት የሚመገቡት
የአመጋግብ ሥርዓት ነዉ፡፡ ለተኛው ለበዓላት እና ለእንግዳ የሚዘጋጅ ምግብና መጠጥ ዓይነቶች ተብሎ
ይታወቃል፡፡ በማንኛውም ሰዓት ማህበረሰቡ የሚያዘውትረው የምግብ ዓይነቶች ከእንሰት ዉጤቶች እንደ
አምቾ፣ ቆጮና ቡላ ከእህል ዘር ከጤፍ፣ ማሽላ፣ ከበቆሎ ዱቄት በቆጮ ተለውሶ የሚዘጋጁ /Dhufe/ ምግቦች
ዋና ዋና ሲሆኑ በተለየ መልኩ ለመስቀል በዓል እና ልዩ ለሆኑ ለክብር እንግዶች የሚዘጋጁ ምግቦች
የጤፍቂጣ፣ገንፎ /Dhoqqe/ እና ከሥጋጋር የሚበላ የቆጮ ቂጣ ማህበረሰቡ ትልቅ ቦታ የሚሰጥ የምግብ
ዓይነቶች ናቸው፡፡ በተጨማሪ ቡና በቅቤ፣ ማር እና የእርጎ ወተት ለእንግዳ ይቀርባሉ፡፡ በኦይዳ የመጠጥ
ዓይነቶች ሶንጌ ዳና /Songee Daana/ የቦርዴ ጠላ ከገብስ፣ ከጤፍ፣ ከበቆሎና ማሽላ የሚዘጋጅ መጠጥ ሲሆን
ከጤፍ ብቻ የሚዘጋጅ “ባሽንቻ ዳና /Baashinicha Daana/” የሚባሉት የብሔረሰቡ ባህላዊ መጠጦች
በዋናነት ይዘወተራሉ፡፡

(መረጃዉን የሰጡ የብሔረሰቡ ተወላጆች (አቶ ደስታካሳ፣አቶ ግዳሻዉ ግዛ፣ ወ/ሮ ታመነች ድንቁ እና
ለየብሔረብ ተወላጆች፡ነሔሰ/2014 ዓ/ም)

3.6 ባህላዊ የግጭት አፈታት ሥርዓት በኦይዳ


ግጭት በሰዎች መካከል የሚከሰት ዘርፈ ብዙ የእምነት እና የሕይወት ዑደት የሚፈጥሯቸው ልዩነቶች
ሲሆኑ፤ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ እና በማሕበራዊ ዘርፎች በተዘረጉ ጉዳዮች እና ግቦችን ለማሳካት
በሚፈጠሩ ልዩነቶች የሚከሰት ኩነት ነው፡፡ በሰው ልጆች የዕለተ ተዕለት ማሕበራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ
በግለሰቦች እና በቡድኖች መካከል የሚነሱ ሀሳብም ሆነ የአስተሳሰብ ልዩነት የተነሳ ግጭቶች የሚፈጠር
መሆኑን የዘርፉ ምሁራን ያስረዳሉ፡፡

ሰዎች በአንዳንድ አከባቢ አብረው በሚኖሩበት ጊዜ በተለያዩ አጋጣሚዎች ማሕበራዊ ግንኙነቶችን


ይፈጥራሉ፡፡ ለምሳሌ በንግድ ልዉዉጥ፣ በጋብቻ መተሳሰር በልቅሶ፣ በሠርግ … ወ.ዘ.ተ.. ሲሆን ሆኖም
ግን አልፎ አልፎ በእነዚህ ማሕበራዊ ግንኙነቶች ዉስጥ አለመግባባቶች እና ግጭቶች ሊከሰቱ ይችላሉ

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 32


፡፡ የብሔረሰቡ ሕዝቦች እርስ በዕርሳቸውም ሆነ ከሌሎች አጎራባች ብሔረሰቦች ጋርም አንዳንዴ
በመካከላቸው ግጭቶች ይከሰታሉ ፡፡ ይሁን እንጂ በባሕላዊ አስተዳደር እና የዳኝነት ሥርዓት፤
በማሕበረሰቡ አባላት መካከል በሚፈጠሩ በግል እና በቡድን የሚነሱ ግጭቶችን በዘለቄታው መፍታት
ነው፡፡

በኦይዳ ብሔረሰብ የግጭት መንስኤዎች ተብለው በዋናነት የሚጠቀሱት፡- የድንበር መተላለፍ፣ የሴት
ልጅ ጠለፋ፣ በግጦሽ መሬት፣ ነፍስ መግደል እና በሌሎችም ወጣቶች መካከል የሚፈጠሩ የሃሳብ
አለመግባባቶች የግጭት መንስኤዎች እንደሆኑ ይታወቃል፡፡ በዚህ መሠረት ኦይዳ ብሔረሰብ ከጥንት
ጀምሮ በባሕላዊ የአስተዳደር ሥርዓቱ እስከ አሁን ድረስ የዘለቀ ነዉ፡፡ በማሕበረሰቡ ግጭቶች እንደየ
ግጭት በዓይነቶች ተለይተዉ በየደረጃው ባሉ ባሕላዊ የአስተዳደር መሪዎች አማካኝነት በተለያዩ ደረጃ
ባሉ /Buca/ ወይም ባሕላዊ የመሰብሰቢያ አደባባይ ግጭቶችን ይፈታሉ፡፡
በፎቶ ( )
ምስል፤- ግጭቶች በተለያዩ ደረጃ ባሉ /Buca/ ወይም ባሕላዊ የመሰብሰቢያ አደባባይ ግጭቶችን ሲይፈቱ

አለመግባባቶች በታችኛው እርከን ባሉ በባሕላዊ የመንደር ሽማግሌዎች አማካኝነት በቡጫ /Buca/


የመሰብሰቢያ ቦታ ታይቶ እልባት የሚሰጠው ሲሆን አልፎ አልፎም እልባት ካላገኘ በጮማች
/Comachi/ እንዲዳኝ የሚደረግበት የመጀመሪያ ደረጃ ባሕላዊ የግጭት አፈታት ሥርዓት ነው፡፡ ጮማች
/Comachi/ የግጭቱን መንስኤ በጥልቀት መርምሮ እና በማስረጃ አስደግፎ የሚሰጠው የብይን ውሳኔ
ሲሆን፤ በዚህ ያልተጠናቀቀ ጉዳይ በቢታን /Bitan/ የሚታይ ይሆናል፡፡ የግጭቱን መነሻ እና በየደረጃው
የተደረጉ ጥረቶች በዝርዝር ከፈተሹ በኋላ እልባት ይሰጣቸዋል፡፡ በሶስቱም እርከኖች በሚሰጠዉ ዳኝነት
ያልረካ አካል ለካቲ ጉዳዩን እንዲያቀርብ ይደረጋል፡፡ በባልጣ ቡጫ /Buca/ ካቲዉ የመጨረሻው ዉሳኔ
ይሰጣል፡፡ የተሰጠውን አልቀበልም የሚል ወገን ካለ ከማንኛውም ማሕበራዊ ተሳትፎ ማለትም ከብቶቹ
ከከብቶች፤ ልጆቹ ከልጆች ጋር እንዳይገናኙ፣ እንዲሁም እሳትና ውሃ ከጎረቤት እንዳይወስድ የሚገለል
ከመሆኑም በላይ በንጉሱ ትዕዛዝ ከአካባቢው እንዲሰደድ ሁሉ ይደረጋል፡፡

በኦይዳ ብሔረሰብ የሰው ነፍስ ያጠፋ ግለሰብ መፀፀቱን ገልፆ ሲቀርብ ካቲዉ ጉዳዩን መርምሮ የሟች
እና የገዳይን ወገኖች በአንድ ላይ በመሰብሰብ ገዳዩን የጦር ጫፍ አስነክሰው በባሕላዊ የአምልኮ እና
ቃለ-መሀላ ሥርዓት በማስፈፀም በቡጫ ላይ ይቅር አባብሏቸው፣ አግባብቷቸው እና ሠላም አውርደው
እንዲኖሩ የሚደረግበት ሥርዓት ነው፡፡ የባሕላዊ እርቀ-ሠላም አወራረድ ሂደቱን በተመለከተ የሟች
ቤተሰብ እና የገዳይ ቤተሰብ አንዳንድ በግ እንዲያቀርቡ ከተደረገ በኋላ ተጨማሪ አንድ በሬ ቀርቦ
ታርዶ ሁለቱንም በጎች አንድ ላይ በማድረግ ደማቸውን እንዲቀላቀል ይደረጋል፡፡ የሁለቱ በጎች
ደማቸውን የመቀላቀል ምሳሌ በደም ተለያይተን በደም አንድ ሆነናል የሚል ነው፡፡ ከዚያ በኋላ የበሬዉ
ቆዳ ተገፎ በእንጨት ክብ ቅርፅ ያለዉ ቀዳዳ ተሰርቶ የሟች እና ገዳይ ቤተሰብ ተወካዮች በቀዳዳው
እንዲያልፉ የሚደረግ ሥርዓት ሲሆን ይህም በኦይደኛ ቋንቋ ቡእንቴ /Bu7intte/ /አደባለቀ/ ማለት ነው፡፡
እንደዚህ የሚያደርጉትም ከዚህ ቀደም በግጭት ምክንያት ተለያይተው የነበሩ ደመኞች ታርቀው አንድ
ሆነዋል፣ ሠላም ተፈጥሯል የሚለውን መግባባት ለመግለጽ ነው፡፡

ከሌሎች አጎራባች ሕዝቦች ጋርም የሚከሰቱ አለመግባባቶች በሚፈቱበት ወቅት መጀመሪያ


በኦጋዴዎችና በሀገር ሽማግሌዎች አማካኝነት ጉዳዩ እንዲፈታ ያደርጋሉ፤ ከዚህ ሥርዓት በኋላ እርቀ-

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 33


ሠላም የሚፈፀመው የሁለቱም ባሕላዊ መሪዎች በጋራ በመሆን በሕዝቦቻቸዉ መካከል በግጭት
ምክንያት ተቋርጦ የነበረው ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነቶችን ለማጠናከር ሁለቱንም ወገኖች
በሚያዋስናቸዉ ወንዝ ላይ በመገናኘት በመካከላቸው ቂም እንዳይዙ ቃለ-መሃላ ያስፈፅማሉ፡፡ በባሕላዊ
ሥርዓት መሠረት እርቅ ሠላሙ በወንዝ ዳር የሚፈፀመዉ የፀቡ መንስዔ ግድያ ከሆነ በወንዙ ግራና
ቀኝ በኩል የሁለቱንም ወገኞች የሚወክሉ ትንንሽ ቤቶችን /ዉልቼ (wulichche) በመሥራት፤
በየአከባቢያቸዉ ደመኞችን በማቆም የእርቀ ሠላሙ ሥርዓት ከተፈፀመ በኃላ ቤቱን /ዉልቼ
(wulichche) ያቃጥሉታል (yijjo michchida) እያሉ ለይስሙላ እየጮኹ ከላይ በተባለው ልክ ታርቀው
ይጨርሳሉ፡፡ ከእርቅ በኋላ በመካከላቸው የተፈጠረው ቂም በዚያ ወንዝ ይሄዳል የሚል እምነት
ስለነበራቸው ነው፡፡

ብሔረሰቡ ከሌሎች አጎራባች ብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ጋር የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን ቡጫ


የሚባል ባሕላዊ የመሰብሰቢያ ሥፍራ ላይ በሠላማዊ መንገድ በሽማግሌዎች አማካኝነት እንዲፈታ
የሚደረግበት ባሕላዊ የሆነ የግጭት አፈታት ሥርዓት አለው ፡፡ በአጠቃላይ በባሕላዊዉ የአስተዳደር
መዋቅር ዉስጥ በየደረጃው የተቀመጡት የባሕላዊ ተሿሚዎች ተግባርን መሠረት ያደረገ የባሕላዊ
አምልኮ ሥርዓት ነው ፡፡ በብሔረሰቡ ዘንድ ባሕላዊ እምነቶች ከፍተኛ ተቀባይነት ስላላቸው በግጭት
አፈታቱ ላይ የጎላ ድርሻም አላቸው፡፡ በኦይዳ ብሔረሰብ የእርስ በዕርስ ግጭቶችም ሆነ ከሌሎች
አጎራባች ብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች መካከል የሚከሰቱ አለመግባባቶች ካቲ ከሌሎች ባሕላዊ
መሪዎች ጋር በመሆን እንደሚፈታ ያመለክታሉ ፡፡ የባሕላዊ እርቅ ሥርዓት የሚመራው በካቲ ሲሆን
በካቲ አደባባይ (ቡጫ) አብረው እርቅ የሚፈጽሙ ጮማች ፣ ብታን ፣ ጎድ እና ቡጫ ጭማ (የሀገር
ሽማግሌ) ናቸው፡፡

በአቶ ዮሐንስ ኢትዮጵያ

3.4 የጎፋ ብሔረሰብ ዘመን አቆጣጠር (Laytha Qoodo)

ጎፋ የሚለዉን የቃሉን ትርጓሜ በተመለከተ የተለያዩ ሰዎች በተለያየ መንገድ ይገልጻሉ፡፡ አንዳንዶች ህዝቡ
ጥንታዊ እንደመሆኑ መጠን ስያሜው ከጥንት ጀምሮ የነበረ እንደሆነ ያስቀምጣሉ፡፡ በዚህ አስተሳሰብ
የሚያምኑ ሰዎች ሁለት የተለያየ አገላለጽ አላቸው፡፡ የህዝቡ የቀድሞ መኖሪያ ከሆነው ከጊቤ ወንዝ መነሻ
አከባቢ የተነሳዉ ህዝብ ጥንትም በዚህ ስም ይጠራ እንደነበረና አዲስ መጥቶ በሰፈረበት በውርኪ አከባቢም
ስያሜውን ይዞ እንደቆየ ይነገራል፡፡ በህዝቡ መነሻ ቦታ የማይስማሙ እና የህዝቡን መነሻ ውርኪ እና ኡባ
ሰንሰለታማ ቦታዎች አድርገዉ የሚገልጹት በነዚህ አከባቢዎች ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ‘ጎፋ’ ጥንታዊ መገለጫ ሆኖ
በሂደት ወደ አከባቢው የመጡትም እየቆዩ በስሙ መጠራት እንደተጀመረ ያምናሉ፡፡

ሁለተኛው አስተሳሰብ ስያሜዉን ከጎፋ ነጋሲ ጎሳ ከሆኑት ከጎሻናዎች አመጣጥ ጋር የሚያገናኝ ነው፡፡ እንደነዚህ
የአገር ሽማግሌዎች የስሙ ምንጭ የጎሻና ጎሳ የዘር ምንጭ የሆነው ‘ጎሻ’ አሳዳጊ የሆነችው ሴት ”ጎፌ”
ከሚትባል ጋር አያይዘው ያስቀምጣሉ፡፡ ጎፌ ጎሻ የሚባል ልጅ አሳዳጊ ስትሆን ልጁ ከትልቅ ውሃ ሰስንፈፍ
የተገኘ በመሆኑ እናቱ ስለማትታወቅ በአሳዳጊዋ የጎፌ ልጅ /Goof naa7a እተባለ ይጠራ ጀመር፡፡ እየቆየ ጎሻ
ታምራትን ማድረግ ስጀምር በአከባቢው ንጉስ እንዲሆን በህዝቡ እንደተመረጠ እና ጎሻ የሚጠራበት ጎፊነኣ
በጊዜ ሂደት የህዝቡ መጠሪያ እንደሆነ ይነገራል፡፡ የህዝቡ መነሻ የሆነው የኦሞ ወንዝ ተፋሰስ ውርኪ አከባቢ

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 34


ይኖር የነበረዉ ህዝብ ጅምር ላይ የጎፌ ልጆች (Goofi Nayta) ይባሉ እንደነበረና በጊዜ ሂደት ጎፋዎች
/Goofata በሚል እንደተቀየረ ይታመናል፡፡

ሌሎች የስሙን አመጣጥ አንድ ወቅት ጎፋን ስገዛ ከነበረ ንጉስ ጎባ ጋር ያገናኙታል፡፡ ካዎ ጎባ ታዋቂና ሀያል የሆነ
ከጎፋ አልፎ ዳውሮንና ኮንታን ወርሮ በመያዝ አንድ ላይ አድርጎ ያስተዳደረ ንጉስ እንደነበረ ይነገርለታል፡፡ ከዚህ
የተነሳ በአጎራባች መንግስታት/ አገሮች በግዛቱ ሥር ይኖሩ የነበሩ ሰዎች (Gooba nayta) “የጎባ አገር ሰዎች"
በሚል ስያሜ ይጠሩ እንደነበረና ቆይቶ በጊዜ ሂደት “ጎባታ/ጎባዎች" ስባል ቆይቶ ዛሬ ላይ ህዝቡ የሚጠራበትን
ስያሜ ይዞ እንደቀረ ይነገራል፡፡

የብሄረሰቡ ስያሜ አመጣጥ በተመለከተ የዕድሜ ባለጸጎችም ሆነ በብሄረሰቡ ታሪክ ጥናት ያደረጉ
ተመራማሪዎች ከላይ እንደተገለጸዉ ሁሉም ያላቸውን የተለያየ እምነት በተለያየ ማስረጃ የሚያረጋግጡ
ሲሆን ብሄረሰቡ የጥንታዊ ስልጣኔ ባለበት ስለመሆናቸው ልዩነት የላቸውም፡፡

ጎፋዎች ከኦሞትክ ቋንቋ ተናጋሪ ህዝቦች ምድብ ስከፈሉ የበርካታ ጥንታዊ ስልጣኔዎች ባለቤት ናቸው፡፡ ህዝቡ
የራሱ የሆነ የአለባበስ፤ ቤት አሠራር፤ የእርሻ አስተራረስ፤ አፈር አጠባበቅ፤ ባህላዊ መድኃኒት ቅመማ
እንዲሁም ዘመን አቆጣጠር ስልት አላቸው፡፡ ከዚህ በላይ ከተገለጹት በተጨማሪ ህዝቡ የአያለ ጥንታዊ
ስልጣነዎች ባለበት መሆኑ ስታወቅሁሉን መዳሰስ የዚህ ጽሁፍ ዓላማ ባለመሆኑ አጠር በማድረግ ጥንታዊ የጎፋ
የዘመን አቆጣጠር ስልት እንደሚከተለው ተዳስሶአል፡፡

የተለያዩ ዘመናዊ የዘመን አቆጣጠር ስልቶች ተዘጋጅተው በአከባቢው ህዝብ ጥቅም ላይ ከመዋሉ በፊት ጥንቱ
ጎፋ የራሱ የሆነ ባህላዊ የዘመን አቆጣጠር ነበረው፡፡ የጎፋ ዘመን አቆጣጠር ቀዳሚ ከሚባሉ የዓለማችን የዘመን
አቆጣጠር ስልቶች አንዱ ቢሆንም በአግባቡ ተጽፎ የተቀመጠ መረጃ ካለመኖሩ እና ለጎፋ ባህላዊ ሳይንስ
ትኩረት ባለመሰጠቱ በቀዳሚነቱ እንደሌሎች አልተወደሰም፡፡ በመሆኑም አዲሱ ትዉልድ ስለ ጎፋ ባህላዊ
የዘመን አቆጣጠር ያለዉ ግንዛቤ አንስተኛ ከመሆኑም ባሻገር ሙሉ በሙሉ እየተረሳ እና እየጠፋ ይገኛል፡፡ ከዚህ
የተነሣ ስለቀደመው ጎፋ ዘመን አቆጣጥር አጠር ያለ ገለጻ በማቅረብ ትዉልዱ የተሻለ እውቀት እንድኖረውና
ለተመራማሪዎች መነሻ የሆነ መረጃ መስጠት የዚህጽሁፍ ዓላማ ነው፡፡

በዓለም ላይ ግብጻዊያን፤ ሮማዊያን፤ ግርኮች፤ ቻይናዊያን፤ ባቢሎናዊያን በጥንታዊ የዘመን አቆጣጠር


ጥበባቸዉ የሚታወቁ ህዝቦች እንደሆኑ ይነገራል፡፡ ከነዚህ ህዝቦች መካከል ለመጀመሪያ ጊዜ የዘመን አቆጣጠር
ስልትን በዓለም ላይ የጀመሩት በቀድሞ ሥልጣኔያቸዉ የሚታወቁት ግብጻዊያን እንደሆነ የታሪክ ጻሐፊዎች
ያትታሉ፡፡ የግብጻዊያን ዘመን አቆጣጠር ዛሬ በዓለማችን ጎልተው የሚታወቁት የጁሊየስና የጎርጎርዮስ የዘመን
አቆጣጠር ስልት ምንጭ እንደሆነም ይነገራል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በዓለም ላይ ከአርባ የሚበልጡ የዘመን አቆጣጠር
ስልቶች በአገልግሎት ላይ እንደሚገኙ ስታወቅ ሁሉም በቅለው ወደ ልዩ ልዩ አቅጣጫ ያዘነበሉት ከግጻዊያን
አቆጣጠር ስልት እንደሆነ አንዳንድ የታርክ ጸሐፊዎች ይገልጻሉ (ማሞ ጎደቦ 2010) ፡፡

በሌላ መልኩ ደግሞ አንዳንድ ጸሐፊዎች ሁሉም የዘመን አቆጣጠር ስልቶች አባታቸዉ ግብጻዉያን እንደሆኑ
አድርጎ ማሰብ ስህተት እንደሆነይገልጻሉ፡፡ የዚህ አስተሳሰብ አራማጆች ሰዎች የዕለት ተዕለት ተግባራቸዉን
በአግባቡ እንድመሩ፤ የተከናወኑትንም ለማስተዋስ እንዲሁም በዓለማችን በተወሰነ ጊዜ ተከስተው ከጠፉ
በኃላ በተወሰነ ጊዜ እንደገና ተመልሰዉ የሚመጡ የተፈጥሮ ክስተቶችን ወቅታቸውን ለማወቅና ምላሽ
ለመስጠት በምደረገው ትግል የዘመን አቆጣጠር ስልት እንደተወለደ ይገልጻሉ፡፡ በዚህ መነሻነት ሁሉም ህዝቦች
የራቸዉ የህይወት ፍልስፍና እና የአኗኗር ዘይቤ ያላቸው በመሆኑ ዘመን አቆጣጠር ባህል ወይም ትውፊት
እንደሆነ ይታመናል፡፡ የሁሉም ዘመን አቆጣጠር ምንጭ በተመለከተ አንድ አይነት አስተሳሰብ ባይኖርም

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 35


የሁሉም ጥንታዊ አቆጣጠር ስልቶች የተመሰረቱት በጨረቃ (Lunar calendar)፤በጸሀይ (Solar calendar) እና
በሁለቱም በጸሀይና ጨረቃ አቆጣጠር ላይ እንደሆነ ተመራማሪዎች ይስማማሉ፡፡

ጎፋ የጨረቃ ዘመን አቆጣጠር (Lunar calendar) ስልት የሚከተል ሲሆን ጨረቃ በየወሩ ስትከሰትና ተመልሳ
ስትጠፋ ጨረቃን ከወር ጋር በማያያዝ ይቆጥራል፡፡ ወሩ የሚቆጠረው በጨረቃ መታየትና መሰወር ሲሆን አንድ
ወር ከአንድ ሙሉ ጨረቃ እስከሚቀጥለው ሙሉ ጨረቃ ድርስ ያለው ጊዜ ነዉ፡፡ በጥናት እንደተረጋገጠው
ጨረቃ መሬትን አንዴ ዞራ ለመመለስ 29.5 ቀናት የሚፈጅባት እንደሆነ ስታወቅ የጎፋ ወር እንደ ዘመናዊ
የአገርቱ አቆጣጠር 30 ቀናት ያሉት ሳይሆን የዕድሜ ባለጸጎች እንዳረጋገጡት ከ 27 እስከ 30 ቀናት ያለው
ነው፡፡ የወራቱ ቀናት ርዝማኔ መለያየትና የጎፋ የዓመቱ ቀናት ብዛት ስንት እንደሆነ ለማወቅ ቀጣይ ጥናት
የሚያስፈልግ መሆኑ ብታመንምበጥናት እንደተረጋገጠው የጨረቃ አቆጣጠር የዓመቱ ቀናት 354 እንደሆነ
ተረጋግጦአል፡፡ በጸሀይ አቆጣጠር በዓመት 365 ቀናት ያለው ሲሆን በሁለቱም አቆጣጠር ስልቶች መካከል
የአስራ አንድ ቀናት ልዩነት አለ፡፡

የቀንና የሌሊት አከፋፈል በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የተለያየ ነው፡፡ ለምሳሌ ቀን በምዕራባውያን አቆጣጠር
እኩለ ሌሊት ስጀምር እስራኤላውያን ከጧቱ አሥራ ሁለት ሰዓት እስከ ምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት ድረስ
በአስራ ሁለት ሰዓታት ከፍለው ይቆጥሩታል (ማሞ ጎደቦ 2010)፡፡ ጎፋ ዕለትን ቃማነ/ሌሊት ጋላስ/ ቀን በማለት
ይከፍላል፡፡ ቀኑ ብርሃን የሚታይበትን የዕለትን ክፍል ስያጠቃል ሌሊቱ ብርሃን የማይታይበት የዕለቱ ክፍል ነው፡፡
ቃማ ሁለት ትርጉም አለው፡፡ አንደኛው ቀን ወይም ቀኑንና ሌሊቱን ሁለቱን የሚያጠቃልል ስያሜ ሲሆን
ሁለተኛዉ ብርሃን የማይታይበት የዕለቱ ክፍል ማለት ነው፡፡

3.3.1 በጎፋ ዘመን አቆጣጠር ውስጥ የሚገኙ አሀዶች

ሰዎች የዕለት ተዕለት ተግባራቸውን ለማከናወን የተከናወኑትንም ዘመን ለማስታወስ የዘመን አቆጣጠር ስልት
(calendar) እንደተቀየስ የታርክ ባለሙያዎች ስያረጋግጡ ጊዜን በቋሚ አሀዶች (units)
በዓመታት፤ወራት፤ሳምንታት፤በቀናት፤ሰዓታት፤ሴኮንዶች በመከፋፈል መቁጠር ለሰው ልጅ እንቅስቃሴ አመቺ
ሁኔታን እንደምፈጥር ይታመናል፡፡ ጎፋም በባህላዊ ተክኖሎጂው የተለያዩ የዘመን አቆጣጠር አሃዶች
በማዘጋጀት ስጠቀም እንደነበረ ስታወቅ ዋና ዋና የዘመን መለኪያ አሀዶችም የሚከተሉት ናቸዉ፡፡

Qiphixeelanashin/issi wol77anthan ሴኮንድ


Salo holida shuchchi simmi yaanas ደቂቃ
Saate ሰዓት
Qamma ቀን/ዕለት
Issi giya ሳምንት
Ageena ወር
Wode ወቅት
Laythi ዓመት
ሠንጠረዥ 1፡ የጎፋየዘመን መለኪያ አሀዶች

3.3.1.1 የሳምንቱ ቀናት

ሣምንት በእንግሊዘኛ ዊክ/week ተብሎ ስጠራ በጎፋ እስ ጊያ ይባላል፡፡ እስ ጊያ ጥሬ ቃሉን ስናይ አንድ ገበያ
ማለት ነው፡፡ ጊያ ሁለት ትርጉም አለዉ፡፡ አንደኛው ገበያ ማለት ሲሆን ሁለተኛው ትርጉም ሳምንት ማለት

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 36


ነው፡፡ ለጎፋ አንድ ገበያ ማለት ስምንት ቀናትን የያዜ ነው፡፡ ይህን በምሳሌ ስናይ፡- ከማክሰኞ እስከ ማክሰኞ
ይቆጠርና አንድ ገበያ/አንድ ሳምንት ይባላል፡፡ የጎፋ ሳምንቱ ቀናት

ዕለታት በጎፍኛ

ተ/ በጎፍኛ በአማርኛ በእንግልዘኛ



1 Laale ሰኞ Monday
2 Kume ማክሰኞ Tuesday
3 Naadde ሮቡዕ Wendsday
4 Bu7e ሐሙስ Thursday
5 Laame ዓርብ Friday
6 Qeera ቅዳሜ Saturday
7 Wogga ዕሁድ Sunday
ሠንጠረዥ 2፡ የሳምንቱ ቀናት በጎፍኛ፤አማርኛ እና በእንግሊዘኛ

እንደ ዕድሜ ባለጸጎች ለጎፋ ስኬታማነትና ውጤት ማጣት ከቀናት ጋር ይያያዛል፡፡ ከዚህ ረገድ ቀናቱን
ገድ/ማጫ ቃማ እና ገደቢስ/አደ ቃማ በማለት በሁለት ይከፍላቸዋል፡፡ ማክሰኞ፤ ሀሙስና ቅዳሜ ገድ ቀናት
ሲሆኑ ሮቡእ/ናዴ አርብ/ላሜ እሁድ/ዎጋ ገደቢስ/ኤቃ ቃማ በመባል ይታወቃሉ፡፡

ዕልተ ሰኞ ግን በሁለቱም ምድቦች ዉስጥ ያልተካተተ በጥንቱ ጎፋ ጦርነት የሚታወጅበት ቀን ስለሆነ ኦላ ቃማ


ይባላል፡፡ ምክንያቱ ምን እንደሆነ ባይታወቅም ሰኞ በአብዛኛው በዓለም ህዝብ ዘንድ የማይወደድ ዕለትእንደሆነ
ይነገራል፡፡ ፈረንጆች ገደቢስ ቀን (black Monday) እያሉ ስጠሩ በአገራችን በሰሜኑ ክፍል ኢትዮጵያ ሰኔና ሰኞ
ተገጣጠሙ ማለት መጥፎ አጋጣሚ የሚል ትርጉም የያዜ ነው፡፡ እንደ ጎፋ ሮቡእ በሰሜን ኢትዮጵያ ህዝቦች
ዘንድም ከገደቢስ ቀናት ውስጥ ይመደባል፡፡ በአማርኛ ሮቡዕ ጦርነት ብጠፋ እንኳን ከባድ አደጋ የሚያስከትል
ዝናብ አይጠፋም የሚለው አባባል ይህን የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ኤቃቃማ/ገደቢስ ቀናት በምባሉት ለፈጣሪ ጸሎት
የሚደረግበት፤የሚጾምብት ቀን ሆኖ አዲስ ነገር በነዚህ ቀናት አይጀመርም ነበር፡፡ ለምሳሌ የዕርቅ ሥነ-ሥርዓት
በገደቢስ ቀን ብፈጸም ዕርቁ አይጸናም ተብሎ ይታሰብ ነበር፡፡ ማጫ/ገዳም ቀናት የእርሻ ስራ
የሚጀመርበት፤ጋብቻ የሚፈጸምበት፤ የዕርቅ ሥራ የሚካሄድበት ነው፡፡ የክርስትና ሀይማኖት ከመስፋፋት ጋር
ተያይዞ ከላይ በተገለጸው መልኩ ቀናትን ከፋፍሎ ማየት ፍልስፍና እየደከመ የመጣ ቢሆንም ፈጽሞ ግን
አልከሰመም፡፡

3.3.1.2 የአመቱ ወራት

ጊዜ መቁጠርን በተመለከተ ለመጀመሪያ ጊዜ የዘመን አቆጣጠር ስልትን በዓለም ላይ የጀመሩት በቀድሞ


ስልጣኔአቸው የሚታወቁት ግብጻውያን እንደሆኑ ይነገራል፡፡ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ 4240 ዓ.ዓ ጥንታውያን
የግብጽ ሰዎች በጸሀይ አቆጣጠር ላይ የተመሰረተ አሥራ ሁለት ወራት በዓመቱ መጨረሻ አምስት ቀናት
በመጨመር ከሌላው ዓለም ተለይተው የታወቁ ቀደምት የዘመን ቁጥር ጀማሪዎች እንደሆኑ የታሪክ
ባለሙያዎች መስክሮላቸዋል (ማሞ ገዴቦ 2010) ግብጻውያን የሌላው ዓለም ህዝቦች ዘመን አቆጣጠር
ጀማሪዎች እንደሆኑ በተለያዩ የታሪክ ጸሐፊዎች የተገለጸ ቢገለጽም ከላይ በመግቢያው እንደተገለጸው ሁሉም
ህዝቦች የራሳቸው የኑሮ ዘይቤ እና የህይወት ፍልስፍና ያላቸዉ በመሆኑ የስልጣኔን ምንጭ ከአንድ አከባቢ ብቻ
አድርጎ መመልከት ጤነኛ አስተሳሰብ አይደለም፡፡
የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 37
በዚህ አስተሳሰብ ውስጥ ሆነን ስናይ የጎፋ ዘመን አቆጣጠርም ከየትም የተቀዳ ሣይሆንጎፋ ከራሱ ኑሮ ዘይቤ
ተፈጥሮአዊ ክስተቶችን በመመልከት የፈጠረው መሆኑን የወራቱ ስያሜ በብሐረሰቡ ቋንቋ የተሰየመ መሆኑ
ማረጋገጫ ነው፡፡ በብሔሩ የዘመን አቆጣጠር ስልት መሠረት ወር የሚቆጠረዉ የጨረቃን መዉጣትና መግባት
መነሻ በማድረግ ሲሆኑ የጎፋ ዘመን ወይም አንድ ዓመት በ 12 ወራት የተከፋፈለ እና አንዱ ወር ከ 27 እስከ 30
ቀናት የያዜ ነው፡፡ አንዳንድ የጎፋ ታሪክ ጸሀፊዎች ኑጮ ከጳጉሜ ጋር በማነጻጸር የጎፋ ዓመቱ ወራት 13
እንደሆኑ የገለጹበት ሁኔታ ቢኖርም ”ኑጮ” ግን የጎፋ ብሔራዊ የአምልኮ ቀን እንደሆነ የዕድሜ ባለጸጎች
ይሞግታሉ፡፡ ኑጮ በዘመናዊው አቆጣጠር በኢትዮጵያ ጳጉሜ አንድ የሚውል ሲሆን በዚህ ቀን የእርሻ ሥራ
የሚያካህድ ጎፋ ትንሽ መሬት ቆርሶ ለኑጮ ምግብ እንድሆን ይከለል ነበር፡፡ ከዚህ የሚንረዳው እንደ ሰሜኑ
ኢትዮጵያ ህዝቦች አቆጣጠር ስልት አይነት ኑጮ ያላት 5/6 ቀናት ሣይሆኑ አንድ ቀን ብቻ መሆኑ ይህች ዕለት
የዓመቱ ወራት ቁጥር ዉስጥ የሚትገባ ሣይሆን የተለየች የአምልኮ ቀን መሆኑዋን የሚያሳይ ነበር፡፡

የጎፋ የዓመቱ ወራት

ተ/ቁ በጎፍኛ በአማርኛ በእንግልዘኛ


1 Gusttama መስከረም September
2 Ciishsha agena/Xiqimayta ጥቅምት October
3 Balibabala ህዳር Noveber
4 Quriquta ታህሣሥ December
5 Guxe ጥር January
6 Wogayza ይካቲት February
7 Lafa መጋቢት March
8 Okola ሚያዝያ April
9 Hiisa ግንቦት May
10 Cooce ሰኔ June
11 Lama ሐምሌ July
12 Galindda ነሐሴ August

1. Gusttama (መስከረም)

መስከረም በጎሪጎሪዮስ የዘመን አቆጣጠር መሠረት የዓመቱ ዘጠነኛ ወር ሲሆን 30 ቀናት አሉት፡፡ መስከረም
የተወሰደዉ ሴፕተም ከሚል ቃል ሲሆን ትርጉሙ ሰባት ማለት ነው፡፡ በቀድሞ አቆጣጠር ሰባተኛ ወር ቢሆንም
አሁን ግን ዘጠነኛ ወር ነው፡፡ በኢትዮጵያ መስከረም የዓመቱ መጀመሪያ ወር ከመሆኑም በተጨማሪ አዲስ
ዓመት የሚጀመርበትና ዘመን የሚንለወጥበት ወር ነው፡፡ መስከረም ምሴተ-ክረምትከሚል ቃል የመጣ ሲሆን
ትርጉሙ ክረምት አለፈ ማለት ነው፡፡ በኢትዮጵያ አዲስ ዓመት የሚከበርበትና ዘመን የሚለወጥበት ዕለት
እንቁጣጣሽ የሚባል ሲሆን የክርስትና እምነት ተከታየች ደግሞ ቅዱስ ዮሐንስ ይሉታል (ማሞ ገደቦ 2010)፡፡

መስከረም ወይም ጉስታማ በጎፋም የራሱ የሆነ የምታወስበት ታርካዊ ክስተት አለው፡፡ ጉስታማ የጎፋ የአመቱ
መጀመሪያ እና ዘመን የሚለወጥበት ወርነው፡፡ የጎፋ ዓመት መለወጫ በዓል ጋዜ የሚከበረው በዚህ ወር ሲሆን
የዘመን መለወጫ በዓሉ እንደ ሰሜን ኢትዮጵያ ህዝቦች የሚከበረው በወሩ መግቢያ ሣይሆን በጉስታማ
አጋማሽ አከባቢ ነው፡፡ ወሩ የጎፋ ብሄራዊ ትልቁ በዓል ጋዜ የሚከበርበት ከመሆኑመም ባሻገር ብርዳመውና

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 38


ዝናባማው የክረምት ወቅት አልፎ ነፋሻማውና በአንራዊነት ሞቃታማ የሆነዉ የጸደይ ወቅት መግቢያ ነው፡፡
ጸደይ በጎፋ የጥጋብ ወቅትና የጎፋ ዓመት መለወጫ በዓል የሚከበርብት በመሆኑ ወሩ የደስታና የጨዋታ
ወር/ጉስታሚ ጉፒያ አገና/ካኢያ አገና/ እየተባለ ይጠራል፡፡

2. Xiqimayta/Ciishsha Ageena (ጥቅምት)

ጥቅምት በጎርጎሪዮስ የዘመን አቆጣጠር መሰረት የዓመቱ አሥረኛ ወር ሲሆን 31 ቀናት አሉት፡፡ ጥቅምት
ኦክቶበር የተወሰደው ኦክቶ ከሚል ቃል ሲሆን ኦክቶ ማለት በግሪክና በላቲን ቋንቋዎች ስምንት ማለት እንደሆነ
የታሪክ ጸሀፊዎች አትተዋል፡፡ ጥቅምት በኢትዮጵያ የዓመቱ ሁለተኛ ወር ሲሆን በአማርኛ ትርጉሙ
የሚጠቅም፤ ጥቅምን የሚሰጥ፤ የሚበጅ፤ የሚያፈራ ወዘተ የሚል ትርጉም የያዜ ነው (ማሞ ገደቦ በ 2010)

ጥቅምት በጎፋ ከገድ ወራት አንዱ ነው፡፡ መስከረምን/ጉስታማን ተከትሎ የሚመጣ ወር ስለሆነ የክረምቱ
ጨለማ እየጠራ የሚሄድበት በቆላና በደጋው አከባቢ የተለያዩ እህሎች የሚደርሱበት ወር ነው፡፡ ጥቅምት/ጭሻ
አገና በደጋው የጎፋ ክፍል የአተር፤ ባቄላ፤ ገብስ የምታረምበትና እሸት በስፋት የሚገኝበት ወቅት ነው፤
በቆላማውም ቢሆን ጤፍ፤ቦየ የተለያዩ ስራስሮች የምደርሱበት በመሆኑ ወሩ በጎፋ ከጥጋብ ወራት አንዱ ነው፡፡
ዝናባማ የሆነዉ ክረምቱ ወቅት አልፎ ብራማው የጸደይ/ጋባ ወቅት አበቦች በየቦታው ፈክተው የሚታዩበት
ስለሆኑ ወሩ የአበቦች ወር/ ጪሻ አገና እየተባለ ይጠራል፡፡

በጥቅምት የተቆረጡ እንጨት ውጤቶች ነቀዝ ስለማይበላው አርሶ አደሩ በጥቅምት ወር ለልዩ ልዩ
አገልግሎቶች የሚውሉትን ከእንጨት የሚዘጋጁ ቁሰሳቁችን የሚያዘጋጀበት ወርም ነው፡፡ በሌላ በኩል ነፋስ
የሚበዛበት ከሌሎች የዓመቱ ወራት ለየት ያለ ቅዝቃዜ የሚስተዋልበት ስለሆነ ጥቅምት ብርድእና ዉርጭ
የሚያይልበት/ቃሬ ጎዥጎዦ አገና በመባል ይታወቃል፡፡ እንደ ዕድሜ ባለጸጎች ቀደምት ጎፋዎች ጥቅምትን
ከሌሎች ወራት ለየት ያለ ብሄራዊ የስኬት ወር ተደርጎ ይታይ ነበር፡፡ ዘመናዊ አስተዳደር በኢትዮጵያ
ከመመሰረቱ በፊት ወሩ የንግስና ሥርዓት የሚፈጸምበት ወር ነበር፡፡ እንደ ዕድሜ ባለጸጎች በጎፋ የመንግስት
ምስረታ የሚካሄደው በጥቅምት ወር ነበር፡፡

3. ህዳር /Balibabala

ኀዳር በእንግሊዘኛ ኖቨምበር ተብሎ ስጠራ በጎሪጎሪዮስ የዘመን አቆጣጠር መሠረት የዓመቱ አስራ አንደኛ ወር
ነው፡፡ ቃሉ ኖቬምብርስ ከሚል ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙ ዘጠነኛ ማለት ነው፡፡ በቀድሞው በሮማውያን
አቆጣጠር ህዳር ዘጠነኛ ወር ነበር፡፡ በቀድሞው አጠራር ዘጠነኛ ወር ቢሆንም በየጊዜው በተደረገው መሻሻል
አሁን አሥራ አንደኛ ወር ሆኖ 30 ቀናትን የያዜ ነው፡፡

ህዳር በኢትዮጵያ ኀደረ ከሚል የግዕዝ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙ አደረማለት ነው፡፡ ወሩ አርሶ አደሩ እህሉን
ለመጠበቅ ዱር የሚያድርበት ስለሆነ ስያሜውን ከዚያ ሳያገኝ እንዳቀረ ምሁራን ያምናሉ፡፡ ህዳር በሰሜኑ
ኢትዮጵያ የጥጋብ ወር ከመሆኑ የተነሳ የእርካታና የጨዋታ ወቅት ነው (ማሞ ገደቦ 2010)፡፡

ህዳር/Balibabaala በጎፋም የጥጋብ ወር ነው፤ ጎፋ አከባቢዎች የአገዳ እህሎችና የተለያዩ ሥራሥር ምግቦች
በተለያዩ የዓየር ክልሎች የምደርስበት ነው፡፡ በደጋው ጤፍ፤ ስንዴ፤ ገብስ የመሳሰሉት እና በቆላማው የጎፋ
ክፍልም ዘንጋዳ፤ቦቆሎ፤ ጤፍ፤ ድንች፤ ቦዬ ያሉ የምግብ አይነቶች ለምግብነት የምደርስበት ወር ነው፡፡ እንደ
ዕድሜ ባለጸጎች በአሁኑ ወቅት በተለይ በጎፋ ቆላማዉ አከባቢዎች በብዛት ለምግብነት እየዋለ ያለው ቦቆሎ
ጎፋ ከመግባቱ በፊት የተለያዩ የማሽላ ዝርያዎች በቆላማው የጎፋ ክፍል የተለመደ የምግብ እህል ነበር፡፡ ዘንጋዳ

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 39


ድርቅን የሚቋቋም የምግብ ዓይነት እንዲሁም ከብቶችን በአጭር ጊዜ የሚያደልብ ስለሆነ ዛሬም ቢሆን
በአከባቢው ከምመረቱ የምግብ አይነቶች አንዱ ነው፡፡ ወሩ ዘንጋዳው የሚያብበት፤ አርሶ አደሩ ክረምቱ
ላይ ያለው የሥራ ጫና ቀለል የምልበት ወቅት ስለሆነ የደረሰውን እህል ከወፎች እየጠበቀ ለመጪው
በጋ ወቅት ዝግጅት የሚያደርግበት ወር ነዉ፡፡ ህዳር ወር ከጥቅምት ቀጥሎ ብርዳማው ወር ስለሆነ
በጎፋ ብርዳማው ወር/ ባጨይ ቦላን ጡቅያ አገና በመባል ይታወቃል፡፡

4. Quriquta (ታህሳስ)

ታህሣሥ በእንግሊዘኛ ዲሴምበር ይባላል፡፡ ታህሣሥ በጎሪጎሪዮስ የዘመን አቆጣጠር መሠረት የዓመቱ አስራ
ሁለተኛ ወር ሲሆን 31 ቀናት አሉት፡፡ ታህሣሥ ዴሴም (Decem) ከሚል ቃል የተወሰደ ሲሆን ትርጉም በላቲን
አሥር ማለት ነው፡፡ አሁን በጎርጎሪዮሳውያን የዘመን አቆጣጠር መሰረት ታህሣስ አሥራ ሁለተኛ ወር ቢሆንም
በቀድሞ አጠራር አስረኛ ነበር፡፡ ታህሣስ በኢትዮጵያ አራተኛ ወር ሲሆን የስሙ ትርጉመም ሐሰሰ ከሚል
ከግዕዝ ሥርወ ቃል የተገኘ እንደሆነ እና ትርጓሜዉ ከጥጋብና አዝመራ በተጨማሪ መረመረ፤ ፈለገ፤ አሰሰ፤ከ
ጀለ፤ ተመኘ ማለት እንደሆነ ማሞ ገደቦ በ 2010 ዕትሙ ዘርዝረዋል፡፡ በታህሣሥ በህዳር ያልደረሱ ሰብሎች
የሚደርሱበት ወር በመሆኑ እንደ ህዳር በአብዛኛው የኢጥዮጵያ ክፍሎች በተለይ በሰሜን ኢትዮጵያ ሰዉ
የማይቸገርበት ወር ነው፡፡ እህል አምራች የሆኑ አርሶ አደሮች ደግሞ ያጨዱትነ አዝመራ በአውድማ
ወቅጠውና ወደ ገበያ አውጥተው በመሸጥ ገንዘብ የሚያገኙበት በታህሣሥ ወር ነዉ (ማሞ 2010)

የታህሣሥ ወር ትርጉም በጎፍኛ ምን እንደሆነ ባይደረስበትም ወቅቱ የበጋዉ መግቢያ ስለሆነ የጸሀይ ወቅት
“አዋ አገና” ተብሎ ይጠራል፡፡ በኢትዮጵያ ታህሣሥ ጥር እና ይካቲት የዝናብ እጥረት ያለባቸው የበጋ ወቅቶች
ቢሆኑም ጎፋ በኢትዮጵያ ዓመቱን ሙሉ ዝናብ ከምያገኙ አከባቢዎች አንዱ በመሆኑከጥር አጋማሽ ጀምሮ
የበልጉ ዝናብ መጣል ይጀምራል፡፡ ከዚህ የተነሳ ከሌሎች ተለይቶ ወሩ ዝናብ የለሌበት ወር /አዋ አገና በሚል
ይታወቅ እንደነበረ መረጃ የሰጡ የዕድሜ ባለጸጎች ይናገራሉ፡፡

ጎፋ ሥራ ሥር ምግቦች በብዛት የሚገኙበት አከባቢ ነው፡፡ ቦዬ፤ ጎደሬ፤ እንሰት፤ ድንች በሰፊው ስመረት ከሥራ
ሥሮች ድንችና ጎደሬ በሰፊው ለምግብነት የሚውልበት ወር ነዉ፡፡ ጎደሬ ለምግብነት ለመድረስ ከአምስት እስከ
ስድስት ወራት የሚፈልግ ሲሆን በክረምቱ የተተከለው ደርሶ አርሶ አደሩ ለምግብነትና ለገበያ የሚያውልበት
ወር ስለሆነ ታህሣስ ወር ከገበያ ጎደሬ ለመግዛት የሚፈልግ ስለ ቦዬው ጥራት/ የሚበስል ወይም የማይበስል
አይነት/ ለምለው ጥያቄ ብዙም ስጋት አይገባበትም፡፡ ከዚህ የተነሣ ወሩ ጎደሬ ለምግብነት የሚዉልበት
ወር/ቦይን ጹሮራ ካጽያ አገና/ ተብሎ ይጠራል፡፡ ታህሣስ የደረቅ ወቅት ስለሆነ በጎፋ አርሶ አደሩ እረፍት
የሚያደርግበት፤ለመጪው አዝመራ ቅድመ ዝግጅት የሚደረግበት፤ትዳር ያልመሰረቱ ጥንዶች ትዳር
የሚመሰረቱበት እንዲሁም ቤት የሚጠገንበትና የሚሰራበት ወር ነው፡፡

5. Guxe/ ጥር

ጥር በእንግሊዘኛ ጃኑዋሪ ይባላል፡፡ ጥር በጎሪጎሪዮስ የዘመን አቆጣጠር መሠረት የዓመቱ የመጀመሪያ ወር ሲሆን
31 ቀናት አሉት፡፡ ጥር ወይም ጃኑዋሪ (Janu + Arius) or (Janus Month) የጃን ወር ከማለት የመጣ ነው፡፡
ጃንስ የሚባለው የሮማዉያን የበር ጠባቂ የመጀመሪያና የመጨረሻ፤ የመግቢያና የመዉጫ አምላክ መጠሪያ
ስም ሲሆን አሪስ (Arius) ደግሞ “የ” ማለት ነው፡፡ ስለዚህ በአንድ ላይ ጃኑዋሪ የጃን ወር ማለት ነው፡፡

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 40


በኢትዮጵያ ጥሪ አምስተኛው ወር ሲሆን በውስጡ ሰላሣ ቀናትንና አራት ሳምንታትን ያቀፈ ነው፡፡ ጥሪ
ትርጉሙ ጠረየ፤ ጥሪት፤ ሀብት የሚሰበሰብበት፤ የድካም ዋጋ የሚገኝበት ወቅት ነው፡፡ ጥር ስመ ጥር፤ ስመ
መልካም፤ ስመ ዝነኛ፤ ስመ ገናና ከሚሉ ቃላት እንደመጣ የታርክ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ በሰሜኑ ኢትዮጵያ
ከጥር እስከ የካቲት ያለው ጊዜ ዘመነ መርዓዊ ወይም የሙሽራ ዘመን ይባላል (ማሞ 2010)፡፡ ጉጼ በጎፍኛ
ትርጉሙ ምን እንደሆነ አይታወቅም፡፡ ከላይ እንደተጠቀሰው የበልጉ ዝናብ ለመምጣት የሚያካፋበት
እንዲሁም አልፎ አልፎ መጠነኛ ዝናብ የሚታይበት ስለሆነ ወሩ የዝናብ መምጫ ምልክት የሚታይበት
ወር/እራ ያናዉ ቆፒያ አገና/ ተብሎ ይጠራል፡፡ ጥር በጎፋ ልክ እንደ ታሕሣስ አርሶ አደሩ እርሻ ሥራ
ስለማይበዛበት ቤት የሚሰራበት እና የሰርግ ወር ነው፡፡

6. Wogayza/ ይካቲት

የካቲት በእንግሊዘኛ ፈብሯሪ (February) ተብሎ ስጠራ በጎሪጎሪዮስ የዘመን አቆጣጠር መሠረት የዓመቱ
ሁለተኛ ወር ነው፡፡ ይካቲት በመደበኛ ዓመታት 28 ቀናት ያሉት ሲሆን በሰገር ዓመታት ደግሞ 29 ቀናት
ይኖሩታል፡፡ በኢትዮጵያ የካቲት የዓመቱ ስድስተኛ ወር ሲሆን በውስጡ ሰላሳ ቀናትና አራት ሳምንታትን ያቀፈ
ወር ነው፡፡ የካቲት ማለት መከር፤ መክተት፤ አዝመራ መሰብሰቢያ፤ ወደ ጎተራ የሚከተትበት የመከር መካተቻ
ጊዜ ነው (ማሞ 2010፡108)

ወጋይዛ ጥሬ የቃሉ ትርጉም ምን ማለት እንደሆነ ባይታወቅም ይካቲት ወጋይዛ የጎፋ ዋናው የእርሻ ወቅት
ነው፡፡ የኢትዮጵያን የዝናብ ሥርጭት ሁኔታ ባለመሙያዎች ዓመቱን ሙሉ ዝናብ የሚያገኙ አከባቢዎች፤
በጸደይ እና በበልግ ዝናብ የሚያገኙ፤ የክረምት ዝናብ አከባቢዎች፤ በበጋ ዝናብ የሚገኙ አከባቢዎች በማለት
በአራት ይከፍላቸዋል፡፡ በዚህም መሰረት ጎፋ ዓመቱን ሙሉ ዝናብ ከሚያገኙ አከባቢዎች የሚመደብ በመሆኑ
ከዚህ ምድብ ዉጭ የሆኑ እንደ ሌሎች አከባቢዎች ሶስቱ የበጋ ወራት (ታህሣሥ ጥርና ይካቲት) ደረቅ ወራት
አይደሉም፡፡ ከላይ እንደተገለጸው ከታህሣሥ ወር ውጪ ቀሪዎቹ ሁሉቱም መጠኑ ይለያይ እንጂ ዝናባማ ወራት
ናቸው፡፡ ጥሪ የበልጉ ዝናብ እያካፋ መምጫው መቃረቡን ምልክት የምሰጥበት ሲሆን ይካቲት ዋናው የበልግ
እርሻ ወቅት ነው፡፡ ከዚህ የተነሣ በጥንቱ ጎፋም ሆነ ዛሬም ወጋይዛ ዋናው የበልግ ወር / ወጋይዝ ዎጋ ቶርቼ/
በመባል ይታወቃል፡፡

7. Lafa (መጋቢት)

መጋቢት በእንግሊዝኛ ማርች ተብሎ ስጠራ በጎርጎሪዮስ የዘመን አቆጣጠር መሠረት የዓመቱ ሶስተኛ ወር
ሆኖ 31 ቀናት አሉት፡፡ ማርች የመጣው ማርስ ከሚባለው ከጥንት የሮማውያን የጦርነት አምላክ በመሆኑ
ትርጉሙም የጦርነት አምላክ የምል ነበር፡፡ ሮማውያን ለጦርነት የሚያቅዱትና የሚነሱት በዚህ ወር ነበር፡፡
መጋቢት ጥንት የሮማውያን የዓመቱ መጀመሪያ ወቅት ነበር (ማሞ ገደቦ 2010)

በኢትዮጵያ መጋቢት የዓመቱ ሰባተኛ ወር ሲሆን በውስጡ ሰላሳ ቀናትንና አራት ሳምንትትን ያቀፈ ነው፡፡
የቃሉ ትርጉም “መገበ” ከሚል ቃል የተገኘ ስም ሲሆን ትርጉሙ በቁሙ የሚመግብ ወይም በጎተራ የተከተተዉ
የሚበላበት ማለት ነው፡፡

ላፋ/መጋቢት በጎፋም ሰባተኛው ወር ሲሆን በላፋ በይካቲት/ወጋይዛ ተጀምሮ የነበረው የበልግ እርሻ
የሚጠናቀቅበት ቀድሞ የተዘራውና የበቀለው እህል የሚኮተኩትበት ወር ነው፡፡ ይህ ወር አብዛኛው አርሶ አደሩ
ቀደም ሲል ያመረተውን ምርት በበጋ ወቅት ስመገብና ስዝናና የእህል ክምችቱ ተማጦ ጎተራ ውስጥ ከቆጠበው
እየተመገበ የበልጉን እርሻ የሚያካህድበት ወር ነው፡፡ ከዚህ የተነሣ መጋቢት በጎፋ የምግብ እጥረት

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 41


ከሚታይባቸው ወራት አንዱ ነው፡፡ የበልጉ ዝናብ በጊዜ ከጀመረ የጓሮ አተክልቶች የሚደርሱበት እንዲሁም በቂ
ዝናብ ከዘነበ የወደፊት የምግብ ዋስትናው የሚረጋገጥበት በመሆኑ አርሶ አደሩ ተስፋው የሚለመልምበት ወር
ስለሆነ መጋቢት በጎፋ የለውጥ ወር/ ላፋይ ላሜስ (lafay laammes) ይባላል፡፡

8. Okola (ሚያዚያ)

ሚያዝያ በእንግሊዘኛ አፕሪል ተብሎ ስጠራ በጎርጎሪዮስ የዘመን አቆጣጠር መሠረት የዓመቱ አራተኛ ወር
ነው፡፡ አፕሪል አፍሮዲት ሞንዝ ከምል ከግሪክ ቃል የተወሰደ ሲሆን አፍሮዲት የግሪክ የውበትና የፍቅር አምላክ
ተብላ የምትመለክ እንስት አምላክ ናት፡፡ በጎርጎሪዮስ የዘመን አቆጣጠር አፕሪል 30 ቀናት አሉት፡፡

በኢትዮጵያ ሚያዝያ የዓመቱ ስምንተኛ ወር ሲሆን በዉስጡ ሠላሣ ቀናትንና አራት ሳምንታትን ያቀፈ ነው፡፡
ሚያዝያ “መሐዘ” ከሚል ከግዕዝ ሥርወ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርሙ ተጎዳኘ፤ ወርሃ- ሠርግ ማለት ነው፡፡
ሚያዝያ እንደ ጥርና እንደ የካቲት ባይደምቅም ከፋስካ በኃላ በሰሜኑ ኢትዮጳያ ክፍል ሠርግ የተለመደ ነው
(ማሞ ገደቦ 2010)፡፡ በጎፋ አቆጣጠርም መያዝያ ስምንተኛ ወር ሲሆን በገጠሩ የጎፋ ክፍል የእህል እጥረት
የሚታይበት ወር ነው፡፡ የበልጉ ምርት ገና ያልደረሰበት የእህል ወቅቶች በማለፋቸዉ የእህል ዋጋ የሚወደድበት
ወር ስለሆነ በጎፋ ገጠር አከባቢ ሚያዝያ ወይም ኦኮላ ለቤት እንስሳት ምቹ ለሰዎች ግን ምቹ ያልሆነ ወር
በመባል ይታወቃል፡፡ ኦኮላ በጎፋ በቂ ዝናብ የሚዘንብበት ወር በመሆኑ ለከብቶች ግጦሽና ውሃ እንደልብ
ይገኛል፡፡ የበልግ ዝናብ ይካቲት ወር ስልምጀምር የተዘሩ ሰብሎች በቅለዉ የበልግ ቡቃያ አምሮ የሚታይበት
ወር ስለሆነ “ኦኮሊ ባዳሊ ኦርዴ ዶሊያ አገና” በመባል ይታወቃል፡፡

9. Hiisa (ግንቦት)

ግንቦት በእንግሊዘኛ ሜይ ተብሎ ስጠራ በጎርጎሪዮስ ዘመን አቆጣጠር መሠረት የአመቱ አምስተኛ ወር ነው፡፡
ግንቦት (ሜይ) ወይም (mayia) ማያ ማለት ታላቅ ማለት ሲሆን የሮማ የጸደይ (spring) እንስት አምላክ
መጠሪያ ስም ነው፡፡ ስለዚህ የማያ ወር ወይም የጸዴይ እንስት አምላክ ማለት ነው፡፡ ሜይ የሚለዉ የግንት ወር
የእንግሊዘኛ ስያሜ ማያ ከሚል ከግርክ ቋንቋ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙ ምግብ የምትሰጥ (መጋቢ) እንደማለት
ነው፡፡ በጎርጎሪዮስ ዘመን አቆጣጠር መሠረት ግንቦት 31 ቀናት አሉት፡፡

በኢትዮጵያ ግንቦት የዓመቱ ዘጠነኛ ወር ሲሆን በውስጡ ሠላሣ ቀናትንና አራት ሳምንታትን ያቀፈ ነዉ፡፡
ግንቦት የሚለው ስያሜ ገነባ፤ ሠራ፤ ከሚለዉ ሥርወ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጉም ጎን፤ ጎድን፤ ወገን፤ ማዕዘን፤
ቅርብ፤ አጠገብ ማለት እንደሆነ አቶ ማሞ በ 2010 ዕትሙ በሰፊዉ አብራርተዋል፡፡

ግንቦት ለጎፋም ዘጠነኛ ወር ሲሆን ወሩ በጎፋ በገደ-ቢስነቱ ይታወቃል፡፡ ህሳ/ግንቦት የበልግ ወቅት የመጨረሻ
ወር በመሆኑ በእጁ ያለዉ እህል እየተሟጠጠ ሄዶ የሚቸገርበት ወር ነው፡፡ ወሩ ከበልግ ወራት አንዱ ቢሆንም
የተዛባ የዝናብ ስርጭት የሚታይበትም ወር ነው፡፡ አንዳንዴ ከመደበኛ በላይ ዝናብ በመምጣት በውሃ ሙላት
አርሶ አደሩ ወደ እርሻውና መገባበያ ሥፍራዎች እንዳይንቀሳቀስ ያደርጋል፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ደግሞ የዝናብ
እጥረት ተከስቶ የበልጉ እርሻ የሚወድምበት ወር ስለሆነ ግንቦት ስዘንብ ሰዉን ከቤት መውጣት ይከለክላል፤
ስጠፋ እህልን ከነድምጥማጡ ስለሚያጠፋ “ህስ አዊኮ ህንቺ ኡዴስ ቡክኮ ሂታን ፐሸስ”ይባላል፡፡

ሂሳ/ግንቦት በጎፋ የምግብ እጥረቱ ጡዘት ከፍተኛዉን ሥፍራ የሚይዝበት ወር ነው፡፡ በግንቦት አብዛኛዉ ሰው
የሚቸገርብት ወር፤ እህል ያለዉም ቢሆን የዓየር ሁኔታው ከተዛባ በምግብ እጥረቱ ልያገኘው ስለምችል
የሁሉም ሰዉ ተስፋ የሚሟጠጥበት ወር ነው፡፡ ከዚህ የተነሣ ጎፋ ህሳ/ግንቦት ሁሉም ሰው ስጋት ዉስጥ

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 42


የሚገባበት፤ተራው ሰው ይቅርና መንግስትም/ንጉሱም በረሀብ ምክንያት ሰውነቱ የሚቀንስበት ወር (Hiis
kawo kushepe worqqey sol77iya ageena) ሲል ይጠራዋል፡፡

ሂሳ /ግንቦት በጎፋ ህዝብ ዘንድ የማይወደድ ወር ነው፡፡ በሂሳ የንግስና ሥነ ሥርዓት አይፈጸምም፤ ጋብቻ
አይመሰረትም፤ብሄራዊ የዕርቅ ሥነ ሥርዓት አይካሄድም፡፡ በቀደምት ጎፋ በሂሳ የአገር መሪ (ንጉሱ) ብሞት
በፈንታ የሚቀመጠው ተተኪ ይሰየምና ሙሉ የንግስና ሥነ ሥርዓት አይፈጸምም፡፡ በዚህ ወር ሥርዓቱ
ብፈጸም ንጉሱ ፍሬያማ አይሆንም፡፡ ህዝቡም ስኬት ይርቀዋል፡፡ የእንስሳትና የሰው በሽታዎች ይበዛሉ፤ እህል
በተፈጥሮ አደጋዎች ይወድማል፤ ከብቶች ይሞታሉ፤ ጦርነት ይበዛል ብሎ ስለምያምን በጥንቱ ጎፋ ነገስታት
የንግስና ሥርዓታቸዉን በግንቦት ወር አይፈጸሙም ነበር፡፡ በአጠቃላይ በሂሳ/ግንቦትአዲስ ኢኮኖሚያዊና
ፖለቲካዊ፤ ሀይማኖታዊ የሆኑ ዕቅዶችን መጀመር ስኬታማነትን እንደምያጎድል ይታመን ነበር፡፡

10. Cooce (ሴነ)

ሰኔ በእንግሊዘኛ ጁን ተብሎ ስጠራ በጎርጎሪዮስ ዘመን አቆጣጠር መሠረት የዓመቱ ስድስተኛ ወር ነው፡፡ ሰኔ
(June) ወይም ጁኖ ከሚለዉ ቃል የመጣ ስም ሲሆን ጁኖ ደግሞ የሮማውያን የአማልክት አምላክ የተባለች
እንስት አምላክ ስም ነው፡፡ ይህች ጣኦት የጋብቻ፤ የሴቶች መልክና ዉበት አምላክ ትባል ነበር፡፡ በጎርጎሪዮስ
ዘመን አቆጣጠር መሠረት ሰኔ 30 ቀናት አሉት፡፡

ሰኔ በኢትዮጵያ ደግሞ አስረኛው ወር ሲሆን ቃሉ ሰነየ ከሚል የግዕዝ ሥርወ ቃል የመጣና ሠናይ ሆነ፤ አማረ፤
ተዋበ የምል ትርጉም የያዜ ነው፡፡ ሰኔ በዋናነት የዘርና የእርሻ ወቅትነው፡፡ በሰሜኑ የአገራችን ክፍል የሰኔና ሰኞ
መገጣጠም እንደ መጥፎ እድል ወይም አጋጣሚ ይፈጠራል ተብሎ ይታመናል፡፡ ሰኔ አንድ ቀን ሰኞ ከዋለ መጥፎ
ሁኔታ ይፈጠራል የሚል አምልኮ ዓይነት ልማድ አለ (ማሞ 2010)፡፡

ለጎፋ ጮጬ/ሰኔ ወር የሂሳ/ግንቦት ረሀብ ወቅት አልፎ እሸት የሚደርስበት ወቅት ነው፡፡ ወሩ የክረምቱ መግቢያ
እና የበልጉ ወቅት ማብቂያ ስለሆነ በበልግ ወቅቱ የተዘሩ እህሎች የሚደርስበት ነው፡፡ ወሩ የክረምቱ መግቢያ
ስለሆነ የዓየሩ ቅዝቃዜ የምጨምርበት አርሶ አደሩም የበልጉ ሰብል ደርሶ የምግብ እጥረቱ ተቃሎ እሸት
የሚበላበት በመሆኑ ጮጨይ ቾንቸስ ይባላል፡፡ ሰኔ በጎፋ ከገድ ወሮች አንዱ ነው፡፡

11. Lama (ሀምሌ)

ሐምሌ በእንግሊዘኛ ጁላይ ተብሎ ስጠራ በጎርጎሪዮስ የዘመን አቆጣጠር መሠረት የዓመቱ ሰባተኛ ወር ሲሆን
31 ቀናት አሉት፡፡

ሐምሌ በኢትዮጵያ የዓመቱ አሥራ አንደኛ ወር ሲሆን በዉስጡ እንደሌሎቹ የዓመቱ ወራት ሰላሣ ቀናትንና
አራት ሳምንታትን ያቀፈ ነው፡፡ ሐምሌ የሚለው ቃል የተወሰደው ሐምል ከሚለው ጥሬ ቃልሲሆን ሐምል፤
ሐመልማል ወይም አመልማል፤ አመልማሎ እየተባለ ይጠራል፡፡

በጎፋም ላማሀምሌ አስራ አንደኛው ወር ሲሆን የክረምሩ ዝናብ የሚበረታበት አርሶ አደሩም የክረምቱን
የእርሻ ሥራ የሚያካህድበት ወር ነው፡፡ የክረምቱ ወራት ለጎፋ ከባድ የእርሻ ወቅት ነዉ፡፡ በክረምት ወቅት
ከምዘሩ የእህል ዓነቶች አንዱ ጤፍ ሲሆን የዘር ወቅት ተጠብቆ ካልተዘራ ጤፍ ምርት አይሰጥም፡፡ ከዚህ የተነሣ
የክረምቱ እርሻ በጥንቃቄና በትጋት ካልተካሄደ ዉጤት እንደማይኖረ ለመግለጽ ስፈልግ “ስል ሼሻስ ብን አቴስ”
በማለት ሌላውን ያስጠነቅቃል፡፡

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 43


12. Galindda (ነሀሴ)

ነሐሴ በእንግሊዘኛ ኦዉገስት ተበሎ ስጠራ በጎሪጎሪዮስ ዘመን አቆጣጠር መሠረት ስድስተኛና 30 ቀናት የያዜ
ነው፡፡ ነሐሴ የመጀመሪያ ስሙ ሴክስቲሊስ (Sextilis) ተብሎ ስታወቅ ትርጉሙም ስድስተኛ ወር ማለት ነበር፡፡
በኃላ ግን በሮማዉ ገናና መሪ በነበረዉ በአውጉስጦስ ስም ለቄሳሩ ክብርና የሥራ መታሰቢያ ሲባል በስሙ
ኦውገስት (August) ተባለ፡፡

ነሐሴ በኢትዮጵያ የዓመቱ አሥራ ሁለተኛ ወር ሲሆን ነሐሴ ቃሉ ከታወቁት የብረት ዓይነቶች አንዱ ከሆነው
ነሐስ የተወሰደ ነው፡፡ ነሐሰ፡- ሠራ፤ገ ነባ፤ የሥራ ወር፤ ሥራ የሚደራረብበት ማለት ነው (ማሞ 2010)፡፡

በጎፋ ነሀሴ ወር ጋሊንዳ ተብሎ ስጠራ ወሩ ጤፍ በምበቅልባቸዉ አከባቢዎች የዘር ወቅት ነው፡፡ በአከባቢው
የአየር መዛባት ምክንያት በአሁኑ ወቅት በቆላውና በደጋማ የዓየር ክልሎች የዘር ወቅት እየተለያየ የመጣ መሆኑ
ቢታወቅም በቀደምት ጎፋ ጋሊንዳ ዋና ጤፍ መዝሪያ ወቅት ነበር፡፡ ከዚህ የተነሳ ወሩ በአከባቢው ነሐሴ የጤፍ
መዝሪያ ወቅት“ጋሊንድ ጋሼ አገና” ይባላል፡፡

3.3.1.3 ወቅቶች/ wode

ወቅት ስንል መሬት በጸሀይ ዙሪያ በምታደርገው ጉዞ ምክንያት የሚፈጠሩ የተወሰኑ ወራትን የያዜ የጊዜ
መፈራረቅ ማለታችን፡፡ በዚህ የጊዜ መፈራረቅ ምክንያት የሚፈጠሩ ወቅቶች ጸደይ፤ በጋ፤ በልግና ክረምት
ናቸው፡፡ እያንዳንዱ ወቅት በውስጡ ሶስት ሶሰት ወራትን እንደምይዝ በዘርፉ ጥናት ያደረጉ ባለሙያዎች
ይገልጻሉ፡፡ ወቅቶች ጎልተው የሚታዩት ወይም ተለይተው የሚታወቁት ከምድር ወገብ ራቅ ብለዉ በሚገኙ
(temprate zone) የሰሜንና የደቡብ ንፍቀ ክበባት አካባቢ ነው፡፡ በምድር ወገብ አከባቢ ጎልተው የሚታወቁት
ሁለት ወቅቶች ሲሆን እነሱም በጋ (የደረቅ ወቅት) እና ክረምት (ዝናባማ ወቅት) ናቸው፡፡

ኢትዮጵያ በምድር ወገብ አጠገብየሚትገኝ አገር ብትሆንም መልካዓ ምድሯ ማለትም የከፍተኛ ተራሮችና
ሰፊ ስምጥ ሸለቆ አገር መሆኗ እንዲሁም የሚትገኝበት አከባቢ ባደረጉላት አስተዋጽኦ ወይም ተጽዕኖ የተለያየ
የዓየር ንብረት እንድኖራት አድረጎአል፡፡ ስለሆነም በኢትዮጵያ የዝናብ አመጣጥና ሥርጭት እንዲሁም የአየር
ሙቀትና ቅዝቃዜ የተለያየ በመሆኑ በግልጽ የሚታወቁ አራት ወቅቶች ተፈጥረዋል፡፡

ጎፋም በኢትዮጵያ ዓመቱን ሙሉ ዝናብ ከሚያገኙ አከባቢዎች አንዱ ሲሆንከተለያዩ የተፈጥሮ ክስተቶችና
ዓየር ሁኔታ የተነሣ አራቱ ወቅቶች ተለይተዉ ይታወቃሉ፡፡ የጎፋ አራቱ ወቅቶች፡-

ተ/ቁ በጎፍኛ በአማርኛ በእንግሊዘኛ


1 Bone በጋ Summer
2 Assura/torchche በልግ Autumun
3 Balggo/Sila ክረምት Winter
4 Gabba ጸደይ Spring

ሀ. ፀደይ

1. Gabba/ ፀደይ

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 44


ጸደይ በጎፋ ጋባ ተብሎ ስጠራ በውስጡ መስከረም፤ ጥቅምትና ህዳር ወራትን ይይዛል፡፡ በጎፋ ዋና የእርሻ
ወቅቶች የሚባሉት በልግና ክረምት ናቸዉ፡፡ አርሶ አደሩ በነዚህ በዋናነት በተለዩ የእርሻ ወቅቶች በቂ ዝናብ
ከጣለ በክረምት ወቅት የተዘራዉን እህል እያረመና እየሰበሰበ በበጋ ወቅት ለምሰሩ ስራዎች ቅድሜ ዝግጅት
የምያደርግበት ወቅት ጋባ ነዉ፡፡ ይሁን እንጅ በበልግና በክረምቱ ወቅት በቂ ዝናብ ሳይገኝ በመቅረቱ የእህል
እጥረት ሲኖር ጋባ /Gabba እንደ ክረምትና በልግ ወቅት የጦፈ የእርሻ ሥራ ይካሄድበታል፡፡ በአጠቃላይ በጎፋ
ጋባ/ፀደይ የክረምት አዝመራ የሚታረመበት ቀደም ስል የተዘሩት የበለግ ሰብሎች ደርሰው ወደ ጎተራ
የሚገቡበት፤ አንዳንድ ጊዜ ሰብሎች የሚሰበሰቡበት ወይም ወይም በእሸትነት የሚገኙበት ወቅት ነው፡፡
ጋባ/ጸደይ በጎፋከረሀብ ነጻ የሆነ የጥጋብ ወቅት ነው፡፡

2. በጋ /Bone

በጋ በጎፋ ቦኔ/bone ይባላል፡፡ በተለምዶ በጋ ታህሣሥ ፤ጥር እና ይካቲትን የሚያካተት ሲሆን ጎፋ በኢትዮጵያ
ዉስጥ ከሞላ ጎደል ዓመቱን ሙሉ ዝናብ ከሚያገኙ አከባቢዎች አንዱ በመሆኑ የበጋዉ ወቅት አጭር ነው፡፡
የበልጉ ዝናብ በይካቲት ወር የሚጀምር በመሆኑ ይካቲት ለጎፋ ከበልግ ወራት አንዱ ነው፡፡ በ ቦኔ /bone ወቅት
አርሶ አደሩ ከእርሻ ሥራ ውጭ ያሉትን ግንባታ ሥራዎችን እያካሄደ፤ከብቶችን እየተንከባከበ ለመጭው በልግ
እርሻ ቅድመ ዝግጅት የሚያደርግበት ወቅት ነው፡፡ አርሶ አደሮች ከጸደይ የተረፈውን አዝመራ በመሰብሰብ
እርሻቸውን በደንብ አለስልሰው በማረስ የሚያመቻቹበት እንዲሁም ማህበራዊ ጉዳዮች ሩቅ ያለ ዘመድ
አዝማድ የሚጠይቅበት ወቅት ነው፡፡ በጋ በጎፋ የሰርግ ወቅት ነው፡፡

3. በልግ /Assura/torchche

በልግ በበጋና በክረምት መካከል የሚገኝ ወቅት ሲሆን በጎፋ በልግ አሱራ ወይም ቶርቼ Assura/torchche ይባላል፡፡
የበልግ ወቅት በጎፋ ከይካቲት እስከ ግንቦት ያለዉን ጊዜ የሚሸፍን ነዉ፡፡ ቶርቼ/አሱራ ለጎፋ በዓመቱ ውስጥ ካሉ
ሶስት የእርሻ ወቅቶች ዋነኛው ነው፡፡ የተለያዩ የሰብል ዓይነቶች የሚዘሩበት ወቅት የተለያየ መሆኑ የታወቀ
ቢሆንም አከባቢው ቦቆሎ በብዛት የሚመረትበት በመሆኑ በልግ ለቦቆሎ እርሻ ምቹ ጊዜ ነው፡፡ ይህን ከጎፋ
ዘወትር ጸሎቱ “ፈጣሪ ሆይ ከበልጉ እርሻ አትለየኝ (torchche assi gadha biyaade tana son peeshopa)”
ከሚለው ምን ያክል የበልጉ እርሻ ወቅት ለጎፋ ወሳኝ መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡ በልግ ለጎፋ የረሀብ ወቅት
ነው፡፡

4. ክረምት/ Balggo/Sila

ክረምት በጎፋ ባልጎ/ስላ (Balggo/Sila) ይባላል፡፡ ሰኔ፤ ሀምሌና ነሐሴ የክረምት ወራት ሲሆኑ ወቅቱ ዝናባማ
እና ከሌሎች ወቅቶች ይልቅ ቀዝቃዛማ ወቅት ነው፡፡ የዝናቡ አሰረጫጨት እንደ በልግ ሁሉን አከባቢዎች
በአንዴ የሚያዳርስ ሣይሆን ከአከባቢ አከባቢ እየለያየ ወይም እየቆራረጠ የሚንዘንብ በመሆኑ አርሶ አደሩ
የዝናቡን የተቆራረጠ ስርጭት ሲገልጽ (sili booras issi kacen bukidi issi kacen bukkona aganaw erees)
ሲል ይገልጻል፡፡ የአባባሉ ጥሬ ትርጉም የክረምት ዝናብ ለምያርሰው በሬ በአንደኛዉ ቀንድ እየጣለ ሌላኛውን
ቀንድ ጥይነካ ይችላል እንደማለት ነው፡፡ ክረምት ከበልግ የእርሻ ወቅት ቀጥሎ ሁለተኛው ለአርሶ አደሩ ወሳኝ
የእርሻ ጊዜ ነው፡፡ አከባቢው በጤፍ ምርትም ታዋቅ ሲሆን ስላ/ክረምት ደግሞ ዋነኛው የጤፍ መዝሪያ ወቅት
ነው፡፡

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 45


የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 46
ክፍል አራት

የኢኮኖሚ አምድ

4.1 የጎፋ ልማት ማህበር

የጎዕብማ ዋና ጽ/ቤት በደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል በጎፋ ዞን በሣዉላ ከተማ የሚገኝ
ሲሆን ማህበሩ በሁሉም የዞኑ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች አሉት፡፡ ከዞኑ
ዉጪ ደግሞ በአዲስ አበባ፤ በአዋሳ፤ አርባምንጭ፤ ወላይታ ሶደ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን ከፍቶ
እየተንቀሳቀሰ ሲገኝ በሀገር ዉስጥና በውጭ ሀገራት 150,000 በላይ አባላት አሉ፡፡

የጎብዕማ አደረጃጀት መዋቅር በተመለከተ፡-

1/ ጠቅላላ ጉባኤ፤

2/ የሥራ አመራር ቦርድ

3/ ኦዲት ኮሚቴ

4/ ዋና ዳይሬክተር እና

5/ የቅጥር ሰራተኞችን በዉስጡ የያዜ ነዉ፡፡

የጎዕብማ የመጀመሪያዉ ጠቅላላ ጉባኤ ተሳታፊዎች 2012 ዓ.ም


የጎዕብማ ሁለተኛ ጠቅላላ ጉባኤ ተሳታፊዎች 2013 ዓ.ም

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 47


4.1.1 ዓላማ
ጎዕብማ ለትርፍ ያልተቋቋመና የዞኑን ህዝብ የኑሮ ዘላቂነት እንድሻሻል ለማድረግ ከአባላት፣ሲቭክ ማህበራት፤ራስ
ገዝ ማህበራትናሌሎች ሲቪል አካላትጋር በመተባበር የሚከተሉትን ዓላማዎች ለማሳካት ይንቀሳቀሳል፡፡
ማህበሩ፤
2.3.1 S ሰረታዊ ¾ƒUI`ƒ ›ÑMÓKAƒ KI´u< እ”Ç=Ç_e TÉ[Ó& K²=IU u›”Å— G<K}—
Å[Í ƒUI`} }Å^i’ƒ“ Ø^ƒ Là ƒŸ<[ƒ SeÖƒ& c?„‹“ ¾%EL k` ›"vu=‹
I퓃¾ƒUI`ƒ }dƒö እ Ç=ÁÉÓ በ TÉ[Ó የራሱንሚናመጫወት'
2.3.2 S ረታዊ ¾Ö?“ ›ÑMÓKAƒ KIw[}cu< ”Ç=Ç[e TÉ[Ó& K²=IU ui ታ” SŸLŸM”
SW[ƒ ÁÅ[Ñ< ¾›"vu=“ ¾ÓM ”êI“ ›Övup' ¾e’-}ªMÊ Ö?““ ¾u?}cw U×’@
›ÑMÓKƒ እ”Ç=eóó TÉ[Ó“ እ”Ç=G<U ¾›?‹.›Ã.y=/›?Ée e`߃ ¾SŸLŸM“
¾Sq×Ö` }Óv^ƒ በ TŸ“¨” የበኩሉን ድርሻመወጣት'
2.3.3 ”ì<I ¾SÖØ ¨<H KQ ብ[}cu< እ”Ç=k`w uTÉ[Ó u}Kà እ“„‹“ I퓃” Ÿ¨<H ¨KÉ
ui ታ‹ SŸLŸM“ u²=I du=Á uc?„‹ LÃ ¾T>ðÖ[¨<” ¾Y^ Ý“ ከ Sk’e አኳያ የበኩሉን
ድርሻ ማበርከት ና
2.3.4 ¾}ðØa Gwƒ MTƒ“ የአካባቢ Øun Y^‹” uØ^ƒ uT[ÒÑØ“ uIw[}cu <Ø[ƒ እ”Ç=eóó
uTÉ[Ó ¾}ðØa Gwƒ T>³” እ”Ç=Öup የበኩሉን አስተዋጽኦ ማበርከት'
2.3.5 K²?Ô‹ ¾Y^ °ÉM“ Ñu= ¾T>ðØ\ }Óv^ƒ” TŸ“¨”&
2.3.6 K¯LT‡ TeðìT>Á ¾T>J” ¾Ñ”²w' ¾‚¡’>¡“ ¾ldle ÉÒõ Ÿ›vLƒ“ ŸKÒj‹ Tcvcw'
¾}KÁ¿ ¾Ñu= TeÑ— ýaÓ^V‹” uT"H@É ¾Ñ”²w ›pS<” TÖ“Ÿ`'
2.3.7 uµ’<“ Ÿµ’< ¨<ß ŸT>”kdkc< ›Ñ^©“ ¯KU ›kó© Ów[-c“à É[Ï„‹“ }Sddà ¯LT
"L†¨< ¾MTƒ É`Ï„‹ Ò` Ó”–<’ƒ uTÉ[Ó ¾MTƒ ›pS<” SÑ”vƒ::
2.3.8 ልዩ ድጋፍ የሚሹ አካባቢዎችን በመለየት ምግብ ዋስትና ችግር ያለባቸው እንዲሁም ተጋላጭ
የህብረተሰብ ክፍሎችን እንደሴቶች፣ ወጣት፣ ህፃናት፣ የአካል ጉዳተኞችን ና ሌሎች የሕብረተሰብ ክፍሎች
ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮግራሞችንና ፕሮጀክቶችን ቀርጾ በመተግበር የበኩሉን ድጋፍ ያደርጋል፡፡
2.3.9 የጎፋ ና ኦይዳ ብሔረሰብ ባህልና ቋንቋ ለማሳደግ አስፈላጊዉን ድጋፍ ማድረግ፤

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 48


2.3.10 የጎፋና ኦይዳ አከባቢ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሻሻል እና የሚመረቱ ምርቶች በገበያ ተመራጭ
እንድሆኑ የግብርና ኤክስቴንሽን ሥረዎችንበ መደገፍ የበኩሉን አስተዋፆ ማበርከት፡፡
4.1.2 የልማት ማህበሩ መሰረታዊ የትኩረት ዘርፎች
1. በትምህርት ዘርፍ
 የአንደኛ ደረጃ ት/ቤት ግንባታዎችን ማካሄድ
 የአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች የትምህርት መርጃ ግብዓቶችን ማሟላት፤
 አካል ጉዳተኞች፤ወላጅ አጥ ህጻናትና ሴቶች የትምህርት ተሳትፎን መደገፍና ማበረታታት
 የጎበዝ ተማሪዎች የልህቀት ማዕከል በመክፈት
 ከፍተኛ የሆነ አካዳማዊ ብቃት እያላቸዉ በግል ኢኮኖሚያዊ ችግር ምክንያት እንዲሁም
በትምህርት ሥርዓቱ ባለዉ የግባኣት እና ሌሎች ተያያዥ ችግሮች የተነሣ ሙሉ
አቅማቸዉን መጠቀም ያልቻሉ ተማሪዎችን በመደገፍ በአገርና በዓለም አቀፍ ደረጃ
ተወዳዳሪ የሆነ ብቁ ዜጋ ማፍራት።
 ከሁሉም የዞኑ አከባቢዎች የተዉጣጡ ከፍተኛ አካዳሚያዊ ብቃት ያላቸዉን የዞኑን ስም
ልያስጠሩ የሚችሉ ተማሪዎችን ደግፎ በማብቃት የዞኑን አንድነት ማጠናከር
 የላቀ ዉጤት ያላቸዉ ነገር ግን በአቅም ዉስንነት ምክንያት የዩኒቨርስቲ ትምህርታቸዉን
መከታተል ያልቻሉ ተማሪዎችን የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግ፤
2. በጤና ልማት ዘርፍ
 አሳታፊና መሰረታዊ የጤና አገልግሎት አሰጣጥን መደገፍ
 ማህበረሰብ አቀፍ የጤና ተቋማትን መገንባትና የህክምና ቁሳቁሶችን ማሟላት
 ዝቅተኛ የኢኮኖሚ አቅም ያላቸዉን ቤተሰቦችን በመረዳት የማህብረሰብ አቀፍ የጤና አገልግሎት
እንድያገኙ ድጋፍ ማድረግ
 የኤቸ አይቪ ኤድስ ሥርጭት ቅድሜ መከላከልና ግንዛቤ ፈጠራ ሥራዎችን ማከናወን
3. በንጹህ ዉሃ አቅርቦት
 ምንጮችን ማጎልበት
 መለስተኛ ጥልቅ የዉሃ ጉድጓድ ቁፋሮና ግንባታ
 የንጹህ መጠጥ ዉሃ ማዕከል ግንባታና መስመር ዝርጋታ
 የግልና የአከባቢ ንጽህና አጠባበቅ ትምህርቶችን መስጠትና ቅድመ ሁኔታዎችን ማሟላት
4. በግብርና እና በምግብ ዋስትና
 ለአርሶ አደሩ ምርጥ ዘር፤ምርጥ የወተትና እርሻ ከብቶች በማቅረብ እንዲሁም ሠርቶ ማሳያዎችን
በማዘጋጀት፤ ዘመናዊ የእርሻ አስተራረስ ስልጠና በማስጠት የምግብ ዋስትና እንድረጋገጥ ማድረግ፤
 ስለመለስተኛ የመስኖ ፕሮጀክቶች ለአርሶ አደሩ ተግባራዊ ስልጠና መስጠት፤
 በመስኖ ልማት ፕሮጀክት የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ
5. በተፈጥሮ ሃብት ጥበቃና በአከባቢ ልማት
 በአከባቢ እንክብካቤ፤አፈርና፤ዉሃ ጥበቃ፤ስለ ደን ልማት ለህብረተሰቡ ስልጠና መስጠት
 በተራቆቱ መሬቶች የደን ተከላ ማካሄድ

4.1.3 የማህበሩ ስኬቶች

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 49


ተ/ቁ ከ 2012-2014 የተከናወኑ ተግባራት የገንዝብ መጠን ምርመራ
ብር ሣ
1 ለመከላከያ ሰራዊት ድጋፍ 10,000
2 ለህዳሴ ግድብ ለቦንድ ግዥ 10,000
3 ለባህል ኪነት ቡድን ድጋፍ 10,000
4 በጤናዉ ዘርፍ (ለጤና ጣቢያ ግንባታ፤ለጤና መድን፤ለጀነሬተር ግዥ …) 502,889
በመንገድ ዘርፍ (ለመንገድ ጥገና፤ለአስፋልት ሥራ) 16,254,670
ለአባላት ንቅናቄ 222,948
ለቢሮ አደረጃጀት 73,000
በግብርናዉ ዘርፍ ለድርቅ ለተጎዱ አከባቢዎች ድጋፍ 1,000,000
ለትምህርት የተደረገ ድጋፍ(ለማጣቀሻ መጽሐፍት ግዥ፤ለኮምፕተር ግዥ፤የላብራቶሪ 6,119,643
ቁሳቁስ…)
ጠቅላላ ድምር 24,203,150

በአቶ እሳያስ ዋሼ

4.2 በኦይዳ የሚገኙ ተፈጥሯዊና ታሪካዊ መስህቦች በጥቂቱ

ኦይዳ የበርካታ ተፈጥሯዊና ታሪካዊ የቱሪስት መስህቦች መገኛ ናት፡፡ እነዚህ የቱሪስት መስህቦች በወረዳዋ
በተለያዩ ቀበልያት መኖራቸዉ በራሱ የኦይዳ ወረዳ የተፈጥሯዊና ታሪካዊ የቱሪስት መስህቦችን የያዘች በጎፋ
ዞን ከምገኙ የቱሪስት መዳረሻ አከባቢዎች ተርታ አሰልፏታል፡፡ መስህቦቹ የምገኙባቸዉ ስፍራዎችን ጎብኚዎች
በእግር፣ በባህላዊ ተራንስፖርት (በበቅሎ) እና በተሸከርካር (በባለ ሁለትና ሦስት እግር ተሽከርካር እንድሁም
በመኪና በመጓዝ እንደለብ ጎብኚቷቸዉ ለመመለስ የአከባቢ ሠላምና ፀጥታ አስተማማኝ ከመሆኑም ባለፈ በየ
ቀየዉ የአርሶ አደሩ እንግዳ አቀባበል ባህሉ ወደ አከባቢዉ እግር ጥሎት ጎራ የምል እንግዳን ተጨማር
የአከባቢዉን ማህበረሰብ ነባር ዕሰት የሆኑትን እግረመንገዳቸውን በጎብኚት ልዩ የጉብኚት ጊዜን እድያሳልፉ
መልካም ዕድልን ይዟል ፡፡ እንድህ ዘና ፈታ በማለት ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ቦታዎችን በኦይዳ ጎብኚቶ ማሳለፍ
በኦይዳ ዛሬ የምጀመር አይደለም ብባል ግነት አይሆንም፡፡

ከጎፋ ዞን ዋና ከተማ ከሆነችዉ ሣውላና ከተለያዩ የሀገርቱ ክፍሎች በየዓመቱ ነሔሰ 27 ቀን በዑባ ደብረ ፀሐይ
ወረዳ ደብረፀሐይ ቀበለ በልዩ ድምቀት ወደ ምከበርበት የግንድ አንሳው መዳኃኒዓለም ዓመታዊ ንግስ ክብረ
በዓልን ለማክበር እና ክብረ በዓሉን ለመታደም ወደ ስፍራዉ ከዛሬ 109 ዓ/ም በፊት ጀምሮ የኦይዳን ወረዳ
አቋርጦ የምያልፍ እንግዳ የማይረሳቸዉ የጉዞ ማስታዎች ለዚሁ እንደጥሩ ማሳያ ተደርገዉ ልወሰዱ ይችላሉ ፡፡
ይሁን እንጅ በኦይዳ ወረዳ የቱሪዝም እምቅ አቅሞች ብኖሩም እነዚህን ስፍራዎች በቀላሉ ጎብኚዎች
በመድረስ በፈለጉበት ጊዜ መጎበኘት እንድችሉ በአከባቢዉ በቅ የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ሥራዎች (መንገድ፤

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 50


ማብራት፣ ንፁሁ የመጠጥ ዉሃን) ጨምሮ ለቱሪዝም ዘርፍ ዕድገት ወሳኝናቸው ከምባሉት መዳረሻ መንገድ፣
ከአከባቢዉ ነባራዊና ተፈጥሯዊ ጋር የምዛመዱ የእንግዳ መቀበያ ሆተሎች፤ የቱሪስት ጋይዲ ማፖች
የምያዉቋቸዉ ሎጆችና የእንግዳ ማረፍያዎች፣ ሀብቶቹ ልሰጡ ከምችሁት ጥቅሞች አንፃር በተገቢዉ
ያለማስተዋወቅ እና ለዘርፉ ልማት በየደረጃዉ ያለዉ አመለካከት ዉስንነትና በኢንቨስትመንት ለመሰማራት
ለምፈልጉ ለግሉ ባለሀብትና ዲያስፖራ ማህበረሰብ ስለኦይዳ አከባቢ በበቅ የማስዋወቅ ሥራ ካለመሰራቱ
እምብዛም ሳይተዋወቅ ኖረዋል፡፡ በዚህ መጽሄት በወረዳዋ ከሚገኙ የቱሪስት መስህቦች መካከል አንዱን ለዚህ
ህትመት ይዘንላችሁ የቀረብነው የሳዓ ጉልዓ ተራራ ነው፡፡

የሳኣ ጉልኣ ተራራ ፡- በፎቶ( )

ምንጭ፡- ነሐሴ/2014 ዓ.ምየጎ/ዞ/ባ/ቱ/መምሪያ

የሳኣ ጉልኣ ተራራ በኦይዳ ወረዳ ከሚገኙ ተፈጥሮአዊ የቱሪስት መስህቦች አንዱነው ፡፡ የመስህቡ ለላኛዉ
መጠርያ ሳኣ ጉልአ (የመሬት እንብርት) ማለት ነዉ ፡፡ ይህ አስደናቂ ተራራ ከወረዳው ዋና ከተማ ሸፊቴ 4
ኪ/ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ ሲሆን 2500-3000 ሜትር ከባህር ጠለለ በላይ ከፍታ አለው ፡፡ ከተራራው አናት
ሲወጡ መላው የከተማውን ክፍልና ሌሎች አከበቢዎችን በቀላሉ ማየት ያስችላል ፡፡ ከዚህም የተነሳ
በአካባቢው ቋንቋ ሳኣ-ጉልኣ የሚል ስያሜ አግኝቷል ፡፡ ትርጉሙም የመሬት እንብርት ማለት ነው፡፡ ሳኣ ጉልኣ
ተራራን በሸፊቴ ከተማ ማሃል ላይ ሆኖ ማየት የሚቻል ከመሆኑም በላይ ቀጥብሎ የቆመ መሆኑ ለየት
ያደርገዋል ፡፡ የሳኣ ጉልኣ ተራራ ሙሉ በሙሉ በምባል ደረጃ በሀገር በቀል ዕጽዋቶችና ተራራዉ በደን በመሸፈኑ
በዉስጡ በርካታ የዱር እንስሳት ዝሪያዎችን፣ የዕጽዋትና የአዕዋፍት ዝሪያዎችን ይዟል፡፡ በዉስጡ ከያዛቸው
ዕጽዋት ዝሪያዎች ጥቅቶቹ ዋርካ፣ ሾላ፣ ወይበታ፣ ትናንሽ ቁጥቋጦ፣ ሰንበለጥና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡
ከእንሳሳት ዝሪያዎች ጦጣ፣ ዝንጀሮ፣ ጅብ እና ከተሳብ እንስሳት እባብና መሰሎችየሚገኙበትነው፡፡

በጥንት ጊዜያት በሳኣ ጉልአ በተራራዉ አናት የባህላዊ እምነት ሐይማኖት መሪዎች(አባቶች) የባህላዊ እምነት
አምልኮት ሥራዓትን እንደምፈጽሙና በተራራዉ አናት ላይ አንድ ምንጭ ዉሃ እንደነበር ፤ ያችን በተራራዉ
አናት ላይ የምትፈልቀዉን ዉሃ ደርሶ የጠጣ ከተላያዩ የስጋ ደዌ ህመም ከመፈወስ ባለፈ ልጅ ያጣ ልጅ
እንድያገኝ፤ሀብት ያጣ ሀብት እንድያገኝ እንደምያደርግ የአከባቢዉ ሀገር ሽመግሌዎች ይናገራሉ ፡፡ በጥንት
ጊዚያት የሰኣ ጉልአ ተራራ በባህናዊ መንገድ እንደምጠበቅና በኦይዳ አከባቢ ያላገቡ ወንዶችና ሴቶች
(ወጣቶች) በተራራዉ አቅራቢያ በመሄድ እንደምዝናኑ ጭምር የአከባቢዉ ተወላጆች ይናገራሉ ፡፡ በአሁኑ
ስዓት ሳኣ ጉልኣ ተራራ በኦይዳ ወረዳ ህዝብ ንቁ የአሬንጓዴ አሻራ ችግኝ ተካላ ለመጭዉ ትዉልድ በአረንጓዴ
የለመለመችውን ሳኣ ጉልኣን ወይም ኦይዳን ለማስወረስ ታቅዶ በተሰራዉ የመስክ ትግበራ ሳኣ ጉልኣን ጥንት
ወደነበረችበት ቁመና ይመልሳታል የምል ተስፋ ተጥሏል ፡፡ በዚህ አስደናቅ ተራራ የተለያዩ የባህል መዳኃኒት
እፅዋት ዓነቶች እንዳሉና ተራራዉ ለጥባለ መዳማ ቦታ ላይ ወደላይ ቀጥብሎ የወጣ የተራራ ሻኛ መሆኑ ልዩ
ማራክ ስፍራ አድርጎታል ፡፡

በአቶ ዮሐንስ ኢትዮጵያ

የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 51


የጎፋ ብሔረሰብ ጋዜ ማስቃላና የኦይዳ ብሔረሰብ ዮኦ ማስቃላ 2014 ዓ.ም. 52

You might also like