You are on page 1of 5

የ 2015 ዓ.

ም የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የአስተዳደርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ዲን ጽ/ቤት ሪፖርት

መግቢያ

የአስተዳደርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ዲን ጽ/ቤት በ 2015 ዓ.ም የአስተዳደር፤ የፋይናንስ፤ የልማትና ማህበረሰብ
አገልገሎት ተግባራትን ለማከናወን ሰፊ ዕቅድ በማቀድ እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል፡፡ ከዕቅዶቹም መካከል በዋናነት
የኮሌጁ ማህበረሰብ የዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ የማድረግ፤ ለትምህርትና ስልጠና የሚያስፈልጉ
ግብአቶች በጥራትና በወቅቱ እንዲቀርቡ የማድረግ፤ የቤተመጻህት፤ የሳይንስ ቤተሙከራዎች፤ የአይሲቲ ላቦራቶሪዎች፤
የአይ አር ሲ እና የማባዣና ፎቶ ኮፒ ክፍሎች ተገቢዉን አገልግሎት ቀልጣፋና በቂ በሆነ ሁኔታ እንዲሰጡ የማመቻቸት፤
የኮሌጁን የፋይናንስ ፍሰት መመሪያን ጠብቆ እንዲሄድ መከታተልና መደገፍ፤ ድጋፍ ለሚስፈለጋቸዉ የኮሌጅ ዉስጥና
ለዉጭ ማህበረሰብ ድጋችን ማድረግ እንዲሁም የካፒታል ፕሮጀክቶችን የመከታተልና ሌሎችንም በርካታ ሥራዎች
መስራት ይጠበቅበታል፡፡

በ 2015 ዓ.ም በመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዉስጥ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት እንደሚከተለዉ ቀርበዋል፡፡

1. የትምህርትና ሥልጠና ግብአት አቅርቦትና ሥርጭትን በማሻሻል የሠልጣኞችን ውጤታማነትና ተጠቃሚነትን


ከማሳደግ አንጻር
 በ 2015 ዓ.ም አዲስ ለሚገቡ ሰልጣኞች በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች የ 1 ኛ ሴምስተር ኮርስ ሞጁሎችን
ከአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ በማምጣት በማባዛትና በመጠረዝ ለንባብ ዝግጁ ሆነዉ በቤተመጻህፍት ሰርኩለሽን
እንዲቀመጡ ተደርጓል፡፡
 የኮሌጁ ቤተመጻህፍት ዕድሳት ተደርጎና ለንባብ ምቹ በሚሆን መልክ ተደራጅቶ መገልግሎት መስጠት
እንዲጀምር ተደርጓል፡፡
 ለአዲሱ የድግሪ መርሐ ግብር ፕሮግራም ኮርሶች የማጣቀሻ መጽሀፍትን ከትምህርት ክፍሎች ጋር በመናበብ
የመለየት ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡
 በቤተመጻህፍት ተከማችተዉ ያሉና የአገልግሎት ጊዜያቸዉ ያለፉ ሞጁሎችን የመለየትና በህጋዊ መንገድ
በሽያጭ እንዲወገዱ ተደርጓል፡፡
 ተጨማሪ አንድ የአይ ሲቲ ክፍል በማደራጀትና የአይ ሲቲ ላቦራቶሪዎች በበቂ የቴክኖሎጂ ቁሳቁስና 1 ለ 2
የተማሪ ኮምፒዉተር ጥምርታ የማደራጀት ስራ ተከናዉኗል፡፡
 አይ አር ሲ ለተማሪዎች ተገቢዉን አገልግሎት መስጠት እንዲችል የማዘጋጀት ስራ ተሰርቷል፡፡
 ግዥ የሚያስፈጋቸዉን ግብዓቶች የመለየት ስራ ተሰርቷል፡፡
2. የቅድመ ስራ ስልጠና ከመስጠት አንጻር ስልጠናዉን ዉጤታማ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት

 ተማሪዎች የሚገቡበትን መማሪያ ክፍሎች ወንበርና ሰሌዳ በመሟላት የማዘጋጀት ስራ ተሰርቷል፡፡

 ለተማሪዎች ስለ ቤተመጻህፍት አጠቃቀምና በሌሎች ጉዳዮች ኦረንተሸን ተሰጥቷል፡፡


 በትምህርት መርጃ መሳሪያዎች ማዕከል ለተማሪዎች አስፈላጊዉን ቁሳቁስ በማሟላት መርጃ መሳሪያ
እንዲያመርቱና እንዲጠቀሙ የማመቻቸት ስራ ተሰርቷል፡፡
1
 ቤተመጻህፍት ለመምህራንና ከዉጭ ለሚመጡ ባለጉዳዮች የማስነበብና የዉሰት አገልግሎት እንዲሰጥ
ተደርጓል፡፡
 ለመምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞች ተገቢዉን የስራ ቁሳቁስ ስርጭት ተደርጓል፡፡
 በመምህራን ኢንቴርነት ክፍል ለመምህራን ተገቢዉን አገልግሎት የመስጠት ስራ ተሰርቷል፡፡
3. አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማስረጽ አሠራርን በማቀላጠፍ የደንበኞችን ፍላጎ ማርካትን በተመለከተ
 በኮሌጁ ግቢ በየትኛዉም አከባቢና በሁሉም የስራ ክፍሎች ባለገመድና ገመድ አልባ እንዲሁም በመምህራን
መኖሪያ ቤትና የእንቴርነት አገልግሎት የመስጠት ስራ ተሰርቷል፡፡
 የአይሲቲ ዳታ ሰንተር ተገቢዉን አገልግሎቱ እንዲሰጥና እንዳይቋረጥ ተደርጓል፡፡
 ለኮሌጁ የሰዉ ሐብት መረጃ አያያዝንና አጠቃቀምን የሚያዘምን ICSIMS ቴክኖሎጂ የማቅረብና ለሰራተኞችም ስልጠና
የመስጠት ስራ ተሰርቷል፡፡ እንዲሁም የሰራተኞችን መረጃ ወደ ስስተሙ የማስገባት ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡

4. የሚበላሹ የቴክኖሎጂ መሣሪያዎችን በመጠገንና ሰርቪስ በማድረግ ሥራን በተመለከተ


 ጥገና የሚያስፈልጋቸዉን ኮምፒዉተሮች ፤የፎቶ ኮፒ ማሽኖችን እንዲሁም ሌሎችንም የትምህርትና ሥልጠና
ግብአቶችን በዉስጥ ባለሞያዎች የማስጠገን ስራ ተሰርቷል፡፡

 ጥገና የሚያስፈልጋቸዉን መማሪያ ክፍሎችንና የቢሮ ዕቃዎችን በዉስጥ ባለሞያዎች የማስጠገን ስራ


ተሰርቷል፡፡
 ጥገና የሚያስፈልጋቸዉን ኤሌክትሮኒክሶችንና የማባዣና የፎቶ ኮፒ ማሽኖችን እንዲሁም ሌሎችንም
የትምህርትና ሥልጠና ግብአቶችን የመለየት ስራ ተሰርቷል፡፡
 የተበላሹ መጻሕፍትንና ሞጁሎችን የመጠገን ስራ ተሰርቷል፡፡
5. የፋይናስና ግዥ ስራዎችን በተመለከተ
 የሚፈጸሙ ግዥዎች በመመሪያ ደንብ መሰረት መሆናቸዉን የመከታተል ስራ ተሰርቷል፡፡
 ለቅድሜ ዝግጅትና ለተለያዩ የጥገና ስራዎች የሚያገለግሉ ቁሳቁሶች ማለትም ስምንቶ፤ ተራዞ፤ ሳር፤ ኮንዲት፤
የግድግዳ ቀለሞች፤ የቧንቧ ዕቃዎች፤ ቆርቆሮ፤ ቁልፍ፤ አሸዋና ጠጠር፤ለሎችም የግንባታ መሳሪዎች ግዥ
ተፈጽሟል፡፡

6. የማህብረሰብ አገልግሎት በተመለከተ የተሰሩ የድጋፍ ስራዎች


 ዝቅተኛ ደመወዝ ተከፋይ ለሆኑ የኮሌጃችን ሰራተኛ ልጆች በብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ) ብር ወጪ
ተደርጎ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል፡፡
 በጋሞ ዞን በድርቅ በተጎዱ አከባቢ ለሚገኙ ተማሪዎች በብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ) ብር ወጪ ተደርጎ
የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል፡፡
 በዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ወቅት ለአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ወንበር በትብብር የመስጠት ስራ ተሰርቷል፡፡

2
 በዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ምክንያት ከአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ወደ ዉጭ እንዲወጡ ለተደረጉ ተማሪዎች
በኮሌጃችን ግቢ ማደሪያ ቦታ በማዘጋጀት የማስጠለል ስራ ተሰርቷል፡፡
7. የመሰረተ-ልማት ስራዎች

 የተቋረጠዉን የ G+2 መማሪ ህንጻ ግንባታ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ እንዲጠናቀቅ ተደርጓል፡፡

 የ G+2 ላቦራቶሪ ህንጻ ግንባታ ክትትልና ድጋፍ ተደርጓል፡፡


 የመማሪያ ክፍል ጥገና ስራን የመከታተልና የመደገፍ ስራ ተሰርቷል፡፡
 የኮሌጁ አረንጋዴ መናፈሻ ግንባታን የመከታተልና የመደገፍ ስራ ተሰርቷል፡፡
 የጉድጓድ ዉሃ ቀሪ ስራዎችን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ዝግጁ እንዲሆን የማድረግ ስራ ተሰርቷል፡፡
 ለግቢ መግቢያ በር ሎጎ ስፔስፊከሽን የማዘጋጀት ስራ ተሰርቷል፡፡
 የኮሌጁ መሰብሰቢያ አዳራሽ የማስጠገን ስራ ተሰርቷል፡፡

8. ሌሎች የአስተዳደራዊ ስራዎች

1.1 ከተለያዩ አከባቢዎች ለሚመጡ ባለጉዳዮች ተገቢዉ አገልግሎት ተሰጥቷል፡፡

1.2 ኮሌጁን በመወከል መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ አካላትና መዋቅር ጋር አስፈላጊዉ ግንኙነት

ተደርጓል፡፡
1.3 የአገልግሎት ክፊያዎች (የቴሌ፤ መብራትና፤ ዉሃ፤ የጋዜጣና መጽሔት) በወቅቱ እንዲከፈሉ ተደርጓል፡፡
1.4 የዉስጥ ገቢ ማስገኛ ስራዎችን በተመለከተ የመመረቂያ ገዋን በማከራዬት ገቢ የማስገኘት ስራ ተሰርቷል፡፡
1.5 በማኔጅመንት ጉዳዮች ላይ መሳተፍ አስፈላጊዉን አስተያዬትና ዉሳኔ የመስጠት ስራ ተሰርቷል፡፡
1.6 ዕቅድና ሪፖርት ዝግጅት በተመለከተ
 በስራ ሂደቱ ስር የሚገኙ ሁሉም ፈጻሚዎች ሳምንታዊ ዕቅድ አዘጋጅተዉ በዕቅዱ መሰረት እየተገበሩ
ይገኛሉ፡፡
 የ 2015 ዓ.ም እቅድ ለሚመለከተዉ አካል በወቅቱ ቀርቧል፡፡
 የ 2014 ዓ.ም እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ለሚመለከተዉ አካል በወቅቱ ቀርቧል፡፡

3
9. የትምህርትና ሥልጠና ግብአት አቅርቦትና ሥርጭትን በማሻሻል የሠልጣኞችን ውጤታማነትና ተጠቃሚነትን
ከማሳደግ አንጻር
 በ 2013 ዓ.ም በተደራጀ መልኩ አዳዲስ ሞጁሎችን ማዘጋጀት ፤ ክለሳ የሚያስፈልጋቸዉን መከለስ ፤በወቅቱ
ሞጁሎችን መጠረዝና ማደራጀት እንዲሁም ጥምርታን በማሻሻል 1 ለ 1 ለተማሪዎች ለማሰራጨት
ዝግጅት ተደርጓል፡፡ የጎደሉ እና የተበላሹ ሞጁሎችን እንደገና የማባዛትና የጥረዛ፣ ለቀማ ሥራም ተከናዉኗል፡፡
 በግዥ የሚቀርቡ ግዓቶችን በተመለከተ የኮቪድ መከላከያ ቁሳቁሶች ግዥ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ
ተከናዉኗል፡፡
 የአይ ሲቲ ላቦራቶሪዎችን በበቂ የቴክኖሎጂ ቁሳቁስና 1 ለ 2 የተማሪ ኮምፒዉተር ጥምርታ የማደራጀት ስራ
ተከናዉኗል፡፡
1.2 የቅድመ ስራ ስልጠና ከመስጠት አንጻር የተከናወኑ የግብአት አቅርቦት ስራዎችና ስልጠናዉን ዉጤታማ ለማድረግ
የተከናወኑ ተግባራት
 የተማሪዎች መረጃን መሰረት በማድረግ ሞጁሎችን የማዘጋጀት፤ የማባዛት ስራ ተሰርቷል፡፡

 የኮሌጁን ቤተመጻህፍትን ለንባብ ምቹና ላብራቶሪዎችን የማደራጀት ስራ ተሰርቷል፡፡

10. አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማስረጽ አሠራርን በማቀላጠፍ የደንበኞችን ፍላጎ ማርካትን በተመለከተ
 በኮሌጁ ግቢ በየትኛዉም አከባቢና በሁሉም የስራ ክፍሎች ባለገመድና የገመድ አልባ የኢንተርኔት አገልግሎት
በተለያዩ ቦታዎች የመስጠት ስራ ታቅዶ ተከናዉኗል፡፡
 የኮሌጁን የኢንተርነት አቅም ከ 30 ሜጋ ባይት ወደ 50 ሜጋ ባይት የማሳደግ ስራ ተሰርቷል፡፡
 በአይሲቲ ዳታ ሰንተር በጊዜያዊነት ባለሙያ በመመደብ አገልግሎቱ እንዳይቋረጥ ተደርጓል፡፡

4
 ቀላል የኤሌክትሮኒክስ ጥገናዎች በኮሌጁ የ ICT ባለሙያዎች ለተለያዩ የራ ክፍሎች
የመስጠት ስራ ተሰርቷል፡፡
 ለመምህራን የኢንተርነት ክፍል እንዲደራጅ ተደርጓል፡፡
 በኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ግዥ የሚያገለግሉ ስፔስፊከሽን ስራ ተሰርቷል፡፡

11. የሚበላሹ የቴክኖሎጂ መሣሪያዎችን በመጠገንና ሰርቪስ በማድረግ ሥራን በተመለከተ


 ጥገና የሚያስፈልጋቸዉን ኤሌክትሮኒክሶችን የማባዣና የፎቶ ኮፒ ማሽኖችን እንዲሁም ሌሎችንም
የትምህርትና ሥልጠና ግብአቶችን በመለየት የማስጠገን ስራ ተሰርቷል፡፡
 የተበላሹ መጻሕፍትንና ሞጁሎችን የመጠገን ስራ ተሰርቷል፡፡
12. የመሰረተ-ልማት ስራዎች

 የተቋረጠዉን የ G+2 መማሪ ህንጻ ግንባታ በተመለከተ ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር በድጋሚ በመወያዬትና
አቅጣጫ በማስቀመጥ ግንባታዉ እንድቀጥል የማድረግና የመከታተል ስራ ተሰርቷል፡፡
 አስቀድሞ አዲስ የ G+2 ላቦራቶሪ ህንጻ ዲዛይን ተሰርቶና በጀት ተፈቅዶ የነበረዉን ወደ ግንባታ የማስገባትና
የመከታተል ስራ ተሰርቷል፡፡
13. ሌሎች የአስተዳደራዊ ስራዎች

1.7 የድስፕልን ጥሰት በታየባቸዉ የስራ መደቦች ግለሰቦቹ በድስፕልን እንዲጠየቁ የማድረግ ስራ ተሰርቷል፡፡

1.8 የመልካም አስተዳደር ስራዎች አፈጻጸም በተመለከተ፡ በትምህርት መሳሪያዎች አቅርቦት ስርጭትና
የቴክኖሎጅ ስርፀት ዋና ስራ ሂደት የመልካም አስተዳደር ችግር በዋናነት በሚታይባቸው የስራ ክፍሎችና
አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ዉይይት ተደርጎ ወደ ስራ ተገብቷል፡፡
1.9 ሌሎች በስራ ክፍሉ የተከናወኑ ተግባራትን በተመለከተ

ሀ) በማኔጅመንት ጉዳዮች ላይ መሳተፍ በተመለከተ አንደ አንድ ዋና የስራ ሂደት የማኔጅመንት ዉሳኔ ለሚፈልጉ ጉዳዮች
በማኔጅመንት ዉይይቶች በመሳተፍ አስፈላጊዉን አስተያዬትና ዉሳኔ የመስጠት ስራ ተሰርቷል፡፡

ለ) ዕቅድና ሪፖርት ዝግጅት በተመለከተ

 ከሁሉም ስራ ክፍል ፈጻሚዎች ጋር የክልሉን ዕቅድ መነሻ በማድረግ የግብ ስምምነት በመፈራረም ወደ

ስራ ተገብቷል፡፡

 በስራ ሂደቱ ስር የሚገኙ ሁሉም ፈጻሚዎች ሳምንታዊ ዕቅድ አዘጋጅተዉ በዕቅዱ መሰረት እየተገበሩ
ይገኛሉ፡፡
 የ 2012 ዓ.ም እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ለሚመለከተዉ አካል በወቅቱ ቀርቧል፡፡

You might also like