You are on page 1of 4

የመተማ ወረዳ ትም/ት ጽ/ቤት

መግቢያ

መንግስት የህብረተሰቡንና የሲቪል ሰርቫንቱን ኖሩ ለማሻሻል በኪራይ ሰብሳቢነት ዙሪያ በርካታ ስራወችን
ከክልል እስከ ዞን ከዞን እስከ ወረዳና ከወረዳ እስከ ቀበሌ ድረስ በርካታ ስራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል፡፡

በዚህ መሰረት የመ/ወ/ትም/ት ጽ/ቤት ተቋሙ ካልዉ ራዕይና ተልዕኮ አካያ ተቋሙ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ
በተቋሙ ዋና ዋና የኪራይ መስብሰቢያ አዝማሚ ናቸዉ ከሚባሉት የመንግስት ስራ ሰዓት
አለማክበር፣ቅጥር፣ዝዉዉር፣የደረጃ እድገት፣ የዲስፕሊን ክስ ላይ የሚገባዉን ዉሳኔ ካለመስጠት፤ የት/ቤት
አመራሮች በጀትን ለልታለመለት አላማ ማዋል፤ ወ.ዘ.ተ የመሳሰሉት የሚታዩ የኪራይ ሰብሳቢነት
አዝማሚያዉች ሲሆኑ እነዚህን ተግባራት ከመታገል አንፃር በርካታ ስራዎችን አከናዉኗል፡፡ ይህን ችግር
በዘላቂነት በመቅረፍ የት/ቤቱን አገልግሎት ፈልገዉ ለሚመጡ ደንበኞች ፈጣንና ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥ
በመዘርጋት በተቋሙ ላይ የተሻለ አመኔታ እንዲኖራቸዉ የማድረግ ስራ ተሰርቷል፡፡

ስለዚህ በ 2010 ዓ.ም የፀረ-ኪራይ ሰብሳቢነት ማድረቂያ እቅድ ስናዘጋጅ በ 2009 ዓ.ም የታዩ ጉድለቶችን
በማስዉግድ የነበሩትን ጠንካራ ተግባራት ደግሞ የበለጠ አጠናክረን ለማስቀጠል ይህን መነሻ እቅድ
አዘጋጅተናል፡፡

/
የመተማ ወረዳ ትምህርት ጽ ቤት ተልዕኮ፣ ራዕይና እሴቶች

ተልዕኮ
 በትምህርትና ስልጠና ውጤታማና ብቁ ዜጋ ማፍራት፤

2010 ዓ.ም የፀረ ኪራይ ሰብሳቢነት ማድረቂያ እቅድ Page 1


የመተማ ወረዳ ትም/ት ጽ/ቤት

ራዕይ 2012

 ትምህርትና ስልጠናን በስፋት በማዳረስ ስብዕናው የተሟላ የስራ ባህልን ያሳደገ ብቁ ዜጋ ተፈጥሮ ማየት፤

እሴቶች
 ለዉጥ ናፋቂና አራማጅ እንሆናለን፣
 የስራ ፍቅር፣ ከበሬታና መልካም ስነ-ምግባር መለያችን ይሆናል፣
 ከተገልጋዮች/ዜጎች ፍላጎት ቅድሚያ መስጠት የመፈጠራችን ምክንያት መሆኑን
እንረዳለን፣
 ግልጽነትና ተጠያቂነትን እናሰፍናለን፣
 ሁሌም ተማሪና አስተማሪ መሆን እንደሚገባ እንገነዘባለን፣
 ቅልጥፍናና ዉጤታማነትን ማረጋገጥ የጥረታችን ሁሉ መቋጫ መሆኑን እናምናለን፣

 ፍትሃዊነትን ማስፈን የመልካም አስተዳደር ገጽታችን ዋነኛ አካል መሆኑን


እንገነዘባለን፣

ዓላማ

 የፀረ-ኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና አዝማሚያ ተግባርን በመታግል በሰነ- ምግባሩ የታነፀ ሙያተኛ
፣ደንበኛና ማህበረሰብ በመፈጠር ኪራይ ሰብሳቢነትን የሚፀየፍና የሚጠላ የህብረተሰብ ክፍል
ማፈራት ነዉ፡፡

የሁኔታ ትንተና
በጥንካሬ
 የፀ-ኪራይ ሰብሳቢነት ማትጊያ መድረኮችን ፈጥሮ በማታገል የተሻለ መሆኑ፤
 ሙያተኛዉ እና የት/ቤት መርሱወች በየዓመቱ ራሱን በሚያሳይ ሁኔታ 2 ጊዜና ሲቀጥልም
እንደአስፈላጊነቱ ሂስና ግለ-ሂስ ማድረጉና ችግሮችን እየለየ ማሻሻል መቻሉ፤
 በመሰረታዊነት የሚታዩ ችግሮችን ከተገልጋዮች ጋርና በጽ/ቤቱ አደረጃጀቶች እንዲፈቱ ጅምር
ተግባር መኖሩ፤
 ኪራይ ሰብሳቢነት አዝማሚያ ያላቸዉን ባለሙያዎች በመለየት በህግና በሲ/ሰ መመሪያ እንዲጠየቁ
መደረጉ፤
በድክመት
 ሙያተኛዉ እና መርሱወች የሚያሳዩቸዉ የትግል ሁኔታ ከአድርባይነት የተላቀቀ አለመሆኑ፤

2010 ዓ.ም የፀረ ኪራይ ሰብሳቢነት ማድረቂያ እቅድ Page 2


የመተማ ወረዳ ትም/ት ጽ/ቤት

 በሂስና ግለ-ሂስ ወቅት ከተወሰኑ ባለሙያዎች ዉጭ ሂስን ከመቀበል ይልቅ የማኩረፍ ሁኔታ መኖሩ፤
 በሂስና ግለ-ሂስ ወቅት ሁሉም ባለሙያ በምን አለብኝነት ዝምታን የመምረጥ ሁኔታ መኖሩ፤
የኪራይ መሰብሰቢያ ምንጭች
1. ሙያተኛዉ እና መርሱወች የመንግስትን የመዉጫና የመግቢያ የስራ ስዓት በትክክል አለመጠቀም
2. በመርሱ ቅጥር ወቅት ከተፈታኞች የማይገባ ጥቅም መፈለግ፤
3. በቅጥር ወቅት ተፈታኞችን በኩል እይታ ያለማየት ችግር ማለትም ተፈታኝ ዘመድ ካለ ለዘመድና
ለሚያዉቁት ማዳላት እና የት/ቤት ምደባም ያለአግባብ መስራት፤
4. የት/ቤት ት/ቤት ዝዉዉር ሲሰራ ከደንብና መመሪያ ዉጭ መፈፀም፤
5. በዲስፕሊን ክስ ወቅት በተከሳሾች ላይ ያላግባብ መመስከር፣ ያላጠፋዉን ጥፋት እንደ ጥፋተኛ ነጥብ
ይዞ መቅረብ፤ መጠየቅ ያለበትን መርሱ ደግሞ አደፋፍኖ ማለፍ እና ከጥፋቱ ጋር ያልተመጣጠነ ዉሳኔ
መወሰን፤
6. ባልተሰራ ስራ ላይ አበል መጠየቅ፤
7. የት/ቤት አመራሮች የት/ቤት በጀትን ለግል ጥቅም የማዋል አዝማሚያወች፤
8. በጽ/ቤቱ ዉስጥ የምንጠቀምባቸዉን እስክብሪቶ፣ወረቀትና ማቴሪያሎችን በአግባቡ አለመጠቀም
ወ.ዘ.ተ የመሳሰሉት ዋና ዋና የኪራይ መሰብሰቢያ ምንጮች ናቸዉ፡፡

ኪራይ ሰብሳቢነትን የማደረቂያ ስልቶች

 በሙያተኞች እና መርሱወች ላይ የሚታዩትን የክህሎት፣አመለካከት፣የእዉቀትና የግንዛቤ ችግሮችን


በተገቢዉ መንገድ እየገመገሙ እንዲሰተካከል ማድረግ፤
 የልማት ቡድና የ 1 ለ 5 ዉይይቶችን በመጠቀም በጽ/ቤታችን እና በት/ቤቶች የሚታዩ ዋና ዋና
ችግሮችን እየለየን መፍታት
 በመረጃ አያያዝ፣በአገልግሎት አሠጣጥ የሲ/ሰርቪሱን ሪፎርሞች በመጠቀምና በማስተግበር የላቀ ሚና
እንዲኖር ማደረግ
 ቅጥር፣ዝዉዉር፣ዲስፕሊን፣የስራ ልምድ ወ.ዘ.ተ የመሳሰሉትን ተግባራት ደንበኞች ሲጠይቁ
በመመሪያዉ መሰረት ስራዎችን በማከናዉን ከአድሎአዊ፣ከዘረኝነት ፣ከዝምድና፣ከኪራይ ሠብሳቢነት
በፀዳ መልኩ በፍትሐዊነትና በታማኝነት ስራዎች እንዲከናዉኑ ማድረግ
 የት/ቤት ር/መ/ራን የት/ቤት ፋይናንስን በአግባቡ እንዲመሩ ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ፤
 በጠነከረ ድጋፍና ክትትል የት/ት ተቋማት የሲ/ሰርቪሱን ሪፎርሞች እንዲተገብሩ በማድረግና ኪራይ
ሰብሳቢነትን እንዲታገሉ ማድረግ
ዋና ዋና ግቦች
 ግብ 1፡- በቅጥር እና ዝዉዉር ወቅት የፍትሀዊነት አስራርን መፍጠር፤

2010 ዓ.ም የፀረ ኪራይ ሰብሳቢነት ማድረቂያ እቅድ Page 3


የመተማ ወረዳ ትም/ት ጽ/ቤት

 ግብ 2፡- በአገልግሎት አሰጣጣችን ከአድሎ የጸዳና ደንበኞችን በስታንዳርድ መሰረት አገልግሎት


እንዲያገኙ ማስቻል፤
 ግብ 3፡- ደንበኞች የተለያዩ መመሪያዎችን እንዲያዉቋቸዉ ማድረግና በመመሪያዉ መሰረት
ጥያቄ/ሞጋች የህብረተሰብ መፍጠር፤
 ግብ 4፡- ማንኛዉም መርሱ በሲ/ሰርቪስ ሪፎርሞች እንዲተዳደር ማድረግ መቻል፤
 ግብ 5፡- ማንኛዉንም ደንበኛ በፋገግታ መቀበል ፣በቅንነትና ፣በታማኝነት ሳይጉላሉ ወቅቱን በጠበቀ
ሁኔታ ማስተናገድ ማስቻል፤
 ግብ 6፡- በእያንዳንዱ የመንግስት ተቋም የሚፈፀሙበት የልማትና የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ
ከኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰብና ተግባር የፀዱ መሆኑን ማረጋገጥ፣ ህዝባችንን በለዉጡ ተሳታፊና
ተጠቃሚ እንዲሆን ማድረግና ማንኛዉም የህብረተሰብ ክፍል ከራሱ ጀምሮ ኪራይ ሰብሳቢነትን
ተፀያፊ እንዲሆን ማስቻል፡፡

ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮች


 በሚደረገዉ ማንኛዉ ግምገማ ላይ ሙያተኛዉ እና መርሱወች ዝምታን የመምረጥና የአድረባይነት
ችግር መኖር፤
 የኪራይ ሠብሳቢነት አዝማሚያ በሙተኞች እና በመርሱወች ላይ ሲታይ የሰላ ትግል ያለማድረግ
ችግር፤
 የአጋር አካላት ግንኙነት የላላ መሆኑና ትኩረት ያለመስጠት ችግር መኖር፤
መፍትሔወች
 ተከታታይነት ያለዉ ዉይይት በማድረግ የጽ/ቤት ሙያተኛዉ እና የት/ቤት መ/ራን፤ ር/መ/ራን እና ሱ/ሮች
በአመለካከት ፣በእዉቀትና፣ በክህሎት ያሉባቸዉን ችግሮች እንዲቀርፍ እና በኪራይ ሰብሳቢነት ላይ ትግል
እንዲያደርጉ ማድረግ፤
 ለት/ት ተቋማት የሚደረገዉ የድጋፍና ክትትል ስርዓት ችግር ፍች እንዲሆን በማድረግ፣ ት/ቤቶች የኪራይ
ሰብሳቢነት ምንጭ መሆናቸዉ ቀርቶ የወረዳችን ተማሪወች ጥራት ያለዉ ት/ት እንዲያገኙ የእዉቀት
ምንጭ ማድረግ፤
 አጋር አካላትን መለየት፣ ማጠናከርና የስራ ድርሻዉን ማሳወቅ፤

2010 ዓ.ም የፀረ ኪራይ ሰብሳቢነት ማድረቂያ እቅድ Page 4

You might also like

  • 2012
    2012
    Document25 pages
    2012
    Lij Dani
    No ratings yet
  • 2012 e
    2012 e
    Document5 pages
    2012 e
    Lij Dani
    No ratings yet
  • 2011
    2011
    Document9 pages
    2011
    Lij Dani
    No ratings yet
  • 2011 e
    2011 e
    Document5 pages
    2011 e
    Lij Dani
    No ratings yet
  • 2011 1 5
    2011 1 5
    Document5 pages
    2011 1 5
    Lij Dani
    100% (1)
  • 2011
    2011
    Document9 pages
    2011
    Lij Dani
    No ratings yet
  • 2010
    2010
    Document12 pages
    2010
    Lij Dani
    No ratings yet
  • 2011
    2011
    Document6 pages
    2011
    Lij Dani
    No ratings yet
  • 2010
    2010
    Document4 pages
    2010
    Lij Dani
    No ratings yet
  • 2009
    2009
    Document4 pages
    2009
    Lij Dani
    100% (2)
  • 2009 .
    2009 .
    Document36 pages
    2009 .
    Lij Dani
    No ratings yet
  • 2009
    2009
    Document10 pages
    2009
    Lij Dani
    No ratings yet
  • 2009 1 5
    2009 1 5
    Document10 pages
    2009 1 5
    Lij Dani
    No ratings yet
  • 2009
    2009
    Document10 pages
    2009
    Lij Dani
    100% (1)