You are on page 1of 4

የመተማ ወረዳ ት/ት ጽ/ቤት

የማኔጅመንት ኮሚቴ የ 2010 ዓ.ም የእቅድ መነሻ

መግቢያ፡-

የሀገራችንን ህዳሴ ለማረጋገጥ መንግስት የ 5 ዓመት የእድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በመንድፍ በርካታ ተግባራት
በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ስለሆነም የልማት ፣ የመልካም አስተዳደርና የመ /ስ/ግንባታ ተግባራትን በቀጣይነትና በዘላቂነት
ለመተግበር የተደራጀ የልማት ሰራዊት ፈጥሮ መገንባት አማራጭ የሌለዉ ጉዳይ ነዉ፡፡ በመሆኑም የጥራት ያለው
ትምህርት አለመስጥ፣ በት/ቤቶች ስታንዳርዱን የጠበቀ ክፍል፣ወንበርና ሌሎች የትምህርት መሳሪያዎች አለመኖር
ከስር መሰረቱ ለመፍታት ትምህርት ሙያተኛውና የመረሱ የልማት ሰራዊት አደረጃጀት በማዋቀር ተግባራትን
መፈጸም ከተጀመረ ዉሎ አድሯል ፡፡

በመሆኑም ከማኔጅመንት ኮሚቴ እስከ 1 ለ 5 አደረጃጀት በማደራጀትና ወደ ስራ በማስገባት ባለፈዉ ዓመት የተሻለ
ጅምር ስራ ተሰርቷል ፡፡ በዚህ በጀት ዓመትም ሁሉን የጽ/ቤት ተግባራት በኃላፊነት ለመፈፀም ያመች ዘንድ ይህን
የማኔጅመንት ኮሚቴ እቅድ ተዘጋጅቷል ፡፡

የዕቅዱ ዋና ዓላማ

 የተደራጀ የልማት ሰራዊት መገንባት


 የለውጥ መሳሪያ ከሆኑት አደረጃጀቶች አንዱ ማኔጅመንት በመሆኑ ይህን አደረጃጀት የለውጥ መሳሪያ
አድርጎ ለመጠቀም

የእቅዱ አስፈላጊነት

ግንባታ ማዕከል ያደረገ ሳምንታዊ የስራ አፈፃፀም ግምገማ በማድረግ ጠንካራ ጎኖቻችንን ማጎልበትና ከደክመቶቻችን
ፈጥነን እንድንወጣ የሚያስችል የማስተካከያ ስራ በመስራት ደረጃ በመለየት እዉቅና በመፍጠር ማኔጅመንቱን የስራዊት
ቁመና በማላበስ ትምህርት ሙያተኛውና የመረሱ የልማት ሰራዊት ለመፍጠርና ለመገንባት ነው፡፡

ግብ 1
የኪራይ ሰብሳቢነት ፖለቲካል ኢኮኖሚን አምሮው የሚፀየፍ የልማታዊ ፖለቲካል ኢኮኖሚ በመስሪያ ቤታችን እንዲገነባ
አልሞ የሚሰራ የለዉጥ ሀዋሪያ የሆነ ሰራተኛ መፍጠር

የሚከናወኑት ተግባራት

የ 2010 ዓ.ም የማኔጂመንት ዕቅድ Page 1


የመተማ ወረዳ ት/ት ጽ/ቤት

ሁሉን የስራ ሂደት አስተባባሪዎች እና ባለሙያዎች ከእቅድ ዝግጅት እስከ ማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ ተግባራትን በበላይነት
እንዲፈፅሙና የሀላፊነት መንፈስ እንዲላበሱ ማድረግ
ሳምንታዊ የስራ አፈፃፀም ግምገማ በተከታታይ ለማድረግ ሰራተኛዉን ደረጃ መለየት
የእለት ግምገማ በማድረግ በየቀኑ ሞዴል ሰራተኛ መፍጠር
በየሳምንቱ በየወሩ ኮከብ ሰራተኞችን መለየትና ማበረታታት
አጫጭር ስልጠናዎች በማዘጋጀት በጽ/ቤቱ ያሉ የአመለካከት፣ የክህሎት፣የአስ /አደረጃጀት ችግሮችን በየጊዜዉ መፍታት
፡፡
የጽ/ቤታችን የሚከሰቱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለቅሞ በመለየት ራሱን የቻለ ዕቅድ በማዘጋጀት ችግሮች
መፍታትና መላዉ ሰራተኛ አገልግሎት አሰጣጡን በከፍተኛ ደረጃ ማሻሻል ፡፡
ምርጥ ተሞከክሮችዎችን መቀመርና ማስፋፋት

ግብ 2

ለተቋማችን የጋራ አስተሳሰብ /Hegemony/ እና የቡድን መንፈስ/Team sprit/ በመግንባት በሁሉም ሙያተኞች
የተቀራረበ የአመለካከት አንድነት መፍጠር

የሚከናወኑ ተግባራት
`በስድስቱም ሂደት ተግባርን ማዕከል ያደረገ የአስተሳሰብ አንድነት እንዲፈጠር ማድረግ
ስራን በመደባዊ ትግል በመምራት ፀረ-ኪራይ ሰብሳቢነት አቋም ያለዉ ሙያተኛ መፍጠር

ግብ 3

በተግባራቸዉ የተሻለ አፈፃፀም ያላቸዉ ሞዴል ሰራተኞችን በመለየትና በማፍራት የመሪነት ሚና እንዲያስቀጥሉ
ማድረግ
በየጊዜዉ በሚካሄዱ ግምገማዎች የሞዴል ሰራተኞች ልየታ ተግባርን ማዕከል ያደረገ እንዲሆን ማስቻል
በየወሩ ጠንካራ አፈፃፀም ያላቸዉን የስራ ሂደቶች መለየትና እወቅና መስጠት
ልዩ ልዩ ስልጠና ነክ የግምገማ መድረኮችን ማዘጋጀት
በሁሉም የስራ ሂደት ባሉ ባለሙያዎች በመማማር ዕድገት ፕሮግራም የተቀራረበ እዉቀት በመፍጠር
የሰራተኛዉን አቅም ማመጣጠን መቻል ፡፡

ግብ 4 በስድስቱም የስራ ሂደቶች ያሉትን አደረጃጀቶች በጥብቅ በመፈተሸና አቅም በመገንባት የልማት ሰራዊት
ማፍሪያ ማዕከል ማድረግ ፡፡
የ 1 ለ 5 ዕለታዊ ዉይይት በዕቅዱ መሰረት እየገመገሙ አፈፃፀሙን ለዉጤት በሚበቃ ሁኔታ መምራት
የስራ ቡድን አደረጃጀት በሳምንቱ የተሰሩ ስራዎችን በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫዎችን ማስቀመጥ
በስራ ሂደቱ ባሉ ባለሙያዎች ተቀራራቢ እውቀትና ክህሎት ለመማማርና እድገት ፕሮግራም ወደ ተቀራረበ
አፈጻጸም እንዲኖራቸው ማድረግ

የ 2010 ዓ.ም የማኔጂመንት ዕቅድ Page 2


የመተማ ወረዳ ት/ት ጽ/ቤት

በሁሉም የስራ ሂደቶች ተግባራትን በልማት ሰራዊት ግንባታ ስራዎች እንዲፈጸሙ ማድረግ

ማኔጅመንት ኮሚቴ ዋና ዋና የአሰራር ስልቶች


የማኔጅመንት ኮሚቴው የየሳምንቱ ተግባራትን መሰረት ያደረገ የስራ ግምገማ ሰኞ ሰኞ ዉይይት በጽ /ቤት ኃላፊው
በዋነኝነት ሚካሄድ ሲሆን ጽ/ቤት ኃላፊ በሌለበት በጽ/ቤት ተወካይ እንዲመራ ይደረጋል ፡፡
አካሄድን በሚመለከት
ሁሉም ስራ ሂደት ከቁልፍና አበይት ተግባራት አንጻር አጭር ሪፖርት በማቅረብ የስራ ግምገማ እንዲካሄድ ማድረግና
የቀጣይ ሳምንት የትኩረት አቅጣጫ ወይም ቸክሊስት ለሂደቶች እንዲደርሱ ማድረግ ፡፡
በሁሉም የስራ ሂደቶች ያሉ ሁሉም ባለሙያዎች በተገኙበት ጥቅል የሴክተር አፈጻጸምን በወር አንድ ቀን ይገመግማል ፡፡
የማኔጀመንት ኮሚቴው በወር መጨረሻ ለእቅድ ዝግጅት በሲ/ሰርቪስ የለውጥ ኮሚቴ የሚወጣ ደረጃ መሰረት በማድረስ
ያፀድቃል፡፡
የሁሉም የስራ ሂደት በየሩብ ዓመቱ ተግባርን መሰረት ያደረገ የስራ አፈጻጸም ሂስና ግለሂስ በማካሄድ ፈጻሚውን ክፍተት
መሙላት፡፡
የክትትል ድጋፍ ሪፖርት ስርዓት
የሁሉም የስራ ሂደቶች አባላት የተገመገመ የስራ ሂደት ሪፖርት ለማኔጅመንት በማቅረብ ይገመግማል
ሁሉም የስራ ሂደት አስተባባሪ የሁለት ሳምንት ሪፖርት ለግምገማ ያቀርባል ግብረ መልስ ይሰጣል፡፡
የሳምንቱ ኮከብ ሰራተኛ ይመርጣል በማስታወቂያ ሰሌዳ እንዲለጠፍ ያደርጋል ፡፡
በየወሩ ኮከብ የስራ ሂደት በማናጅመንት ኮሚቴ ይገመገማል ያሳውቃል፡፡

የማኔጅመንት አባላት በተመለከተ


1. አቶ አባይነህ ወረታ --------------------- የጽ/ቤቱ ኃላፊ --------------------------- ሰብሳቢ
2. -------------------------------------- የጽ/ቤቱ ም/ኃላፊና መርሱ አስተባባሪ ------------ ም/ሰብሳቢ
3. ------------------------------------------------የጽ/ቤቱ አ/ም/ኃላፊ -------------------------አባል
4. አቶ ገንብራቸው ጫኔ------------------ የት/ኢ/ጥ/ማረጋገጫ የስራ ሂደት---------------- አባል
5. አቶ ስዩም ታደሰ ---------------- የስ/ት/መ/ማ/ትግበራ የስራ ሂደት------------------ አባል
6. አቶ ታያቸው ገ/ስላሴ ------------ የት/መ/ስ/እ/ዝ/ሃ/ማ/ማፈ/የስራ ሂደት----------አባልና ፀሀፊ
7. አቶ ወልዴ ገብሬ ----------------------የሙያ ፍቃድ እድሳት የስራ ሂደት--------------------- አባል

የ 2010 ዓ.ም የማኔጂመንት ዕቅድ Page 3


የመተማ ወረዳ ት/ት ጽ/ቤት

የሚያጋጥሙ ችግሮች እና መፍትሄዎቻቸው


የጽ/ቤት ኃላፊዎች ተረጋግተው አለመቀመጥና የማናጅመንት ስብሰባ ወቅቱን አለመጠበቅ
በየሳምንት ኮከብ ሰራተኛ አለማሳወቅ
መፍትሄ
የጽ/ቤት ኃላፊዎች በሌሉበት የተተኪ ስርዓት በመፍጠር ስራን እንዳይቆም ክትትል ማድረግ ፡፡
የሰራተኞች ግምገማ ተግባራትን አፈጻጸም መሰረት በማድረግ ለቁርጠኝነትና በተነሳሽነት መንፈስ ለማወዳደር
ለሁሉም ሰራኞች ግልጸኝነትንና ተነሳሽነት የሚፈጥር እንዲሆኑ ማድረግ አለበት ፡፡

የ 2010 ዓ.ም የማኔጂመንት ዕቅድ Page 4

You might also like