Professional Documents
Culture Documents
222222222222
222222222222
አዲስ አበባ
መግቢያ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በከተማው ውስጥ የሚስተዋለውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ የተለያዩ
የቤት ልማት አማራጮችን በመንደፍ በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረገ የሚገኝ ሲሆን በቀጣይም የመንግሥት
ሠራተኛውን ከተቀረጹት የቤት ልማት ፕሮግራሞች መካከል አንዱ በሆነው የመኖሪያ ቤት የኅብረት ሥራ
ማኅበር በማደራጀት የመኖሪያ ቤት ችግራቸውን እንዲቀርፉ የሚያስችል ግልጽ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት
በማስፈለጉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ሠራተኞችን የጋራ ህንጻ መኖሪያ ቤት የህብረት ሥራ
ስለሆነም የአዲስ አበባ ከተማ የህብረት ስራ ማህበራት ኤጄንሲ በደንብ ቁጥር 129/2014 አንቀጽ 28 ላይ
በተሰጠው ስልጣን፣ ኃላፊነትና ተግባር መሰረት ይህን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ሠራተኞች
የጋራ ህንጻ መኖሪያ ቤት የህብረት ስራ ማህበር የአደረጃጀትና የአፈጻጸም መመሪያ አውጥቷል፡፡ የከተማ
አስተዳደሩ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ነዋሪ በሆኑ የመንግስት ሠራተኞች በግልጽ ከሚታይባቸው የመኖሪያ
ቤት ችግር በመነሳት የመንግስት ሠራተኛው ከቀረቡለት የቤት አማራጮች በፍላጎቱ መሰረት የቤት ባለቤት
የሚሆንበትን እድል ለማስፋት እንዲሁም ሠራተኛው በከተማ አስተዳደሩ በሚሰራባቸው ተቋማት ውጤታማ
አገልግሎት እንዲሰጥ ለማስቻል የሠራተኛውን የመኖሪያ ቤት ፍላጎት ለማሟላት ይረዳ ዘንድ ይህ ዝርዝር
የአፈጻጸም መመሪያ ተዘጋጅቷል፡፡
ክፍል አንድ
ጠቅላላ
1. አጭር ርዕስ
ይህ መመሪያ "የአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር የመንግሥት ሠራተኞች የጋራ ሕንፃ መኖሪያ ቤት የህብረት ሥራ
8. “የመንግስት ሠራተኛ” ማለት በከተማው ውስጥ ነዋሪ ሆኖ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ የመንግስት
መስሪያ ቤቶች በቋሚነት ተቀጥሮ በማገልገል ላይ የሚገኝ እና በአዲስ አበባ ከተማ ስር ባሉ የመንግሥት ልማት ድርጅቶች
ውስጥ በቋሚነት ተቀጥሮ የሚሰራ ወይም ተቀማጭነታቸው በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በሆኑ የኦሮሚያና የፌዴራል
መንግስት መስሪያ ቤቶች ውስጥ በቋሚነት ተቀጥሮ በማገልገል ላይ የሚገኝ ሰራተኛ ነው፤
10. "ዝግ ሂሳብ" ማለት በፕሮግራሙ ተጠቃሚ ለመሆን በኅብረት ሥራ ማኅበሩ ስም ቅድሚያ
የሚጠበቅበትን የቤቱን ግንባታ ወጪ በባንክ ለማስቀመጥ የሚከፈት የማይንቀሳቀስ የቁጠባ ሂሳብ ነው፤
11. "የቤት ልማት ፕሮግራም" ማለት በአስተዳደሩ አስተባባሪነት የመኖሪያ ቤት ችግርን ለመቅረፍ
የሚያካትት ነው፤
12. "ባንክ" ማለት የኅብረት ስራ ማኅበራቱ ገንዘባቸዉን በማይንቀሳቀስ የቁጠባ ሂሳብ ለማስቀመጥ
13. "የለማ መሬት" ማለት መሠረተ ልማት የተሟላለት እና ከማንኛውም የይገባኛል ጥያቄ ነጻ የሆነ
መሬት ነው፤
14. “ሰው’’ ማለት የተፈጥሮ ሰው ወይም በህግ የሰውነት መብት የተሰጠው አካል ነው፤
15. “አደራጅ” ማለት የአዲስ አበባ ከተማ የኅብረት ሥራ ማኅበራት ኤጀንሲ ሲሆን እስከ ክፍለ ከተማ ያለውን መዋቅር
ይጨምራል፤
16. “የስራ አመራር ኮሚቴ” ማለት በጠቅላላ ጉባኤ ተመርጦ የአንድን ኅብረት ስራ ማህበር ስራዎችን
እንዲመራ ኃላፊነት የተሰጠው አካል ነው፤
17. “መሰረተ-ልማት” ማለት ከመሬት በላይ ወይም ከመሬት በታች ያለ መንገድ፣ የባቡር ሃዲድ፣
የአውራፕላን ማረፊያ፣ የቴሌኮሚዩኒኬሽን፣ የኤሌክትሪክ ኃይል፣ የመስኖ፣ የውሃ መስመር ወይም
የፍሳሽ ማስወገጃ መስመር ሲሆን ሌሎች ተያያዥ ግንባታዎችንም ይጨምራል፤
18. “ሊዝ” ማለት በጊዜ በተገደበ ውል መሰረት የከተማ ቦታ የመጠቀም መብት የሚገኝበት የመሬት ይዞታ
ስሪት ነው፣
19. “ወቅታዊ የአካባቢ የገበያ ዋጋ” ማለት ማንኛውንም ንብረት በሚነሳበት ጊዜ ንብረቱ በሚገኝበት
አካባቢ ባለው ገበያ ሊያወጣ ወይም ሊያስከፍል የሚችለው ዋጋ ነው፣
20. “ተወካይ” ማለት አወካከሉ በህብረት ስራ ማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ በሚወሰነው መሰረት ሆኖ
በመንግስት ሰራተኛ የጋራ ህንጻ መኖሪያ ቤት ህብረት ስራ ማህበር በግለሰብ አባላት ተወክሎ በጠቅላላ
ጉባኤ ድምጽ የሚሰጥ ግለሰብ ነው፣
3. የፆታ አገላለጽ
4. የተፈጻሚነት ወሰን
ይህ መመሪያ በከተማ አስተዳደሩ ውስጥ ነዋሪ በሆኑ የመንግሥት ሠራተኞች ማለትም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
ስር በሚገኙ የመንግስት መስሪያቤቶች እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር ባሉ የመንግስት የልማት ድርጅቶች
ውስጥ ወይም ተቀማጭነታቸው በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በሆኑ የኦሮሚያና የፌዴራል መንግስት መስሪያቤቶች
ውስጥ በቋሚነት ተቀጥሮ በማገልገል ላይ የሚገኝ ሠራተኛ በጋራ ሕንፃ መኖሪያ ቤት የኅብረት ሥራ ማኅበር
5. መርሆዎች
በደንብ ቁጥር 129/2014 የተቀመጡት የህብረት ስራ ማህበራት መርሆዎች እንደተጠበቁ ሆነው መመሪያው የሚከተሉት
መርሆዎች ይኖሩታል፡-
6. ዓላማ
የዚህ መመሪያ ዋና ዓላማ የከተማ አስተዳደሩ ካቀረባቸው የቤት ልማት ፕሮግራም አማራጮች የመንግሥት
ሠራተኞች በጋራ ሕንፃ መኖሪያ ቤት ህብረት ስራ ማህበራት ተደራጅተው ገንዘባቸውን፣ ዕውቀታቸውን፣ ጉልበታቸውንና
ጊዜያቸውን በማቀናጀት የመኖሪያ ቤት ችግሮቻቸውን በጋራ ጥረት ሊፈቱ የሚችሉበትን መንገድ መፍጠር ነው፤
6.1. የመንግስት ሰራተኛው በግልና በተናጠል ሊፈታ ያልቻለውን የመኖሪያ ቤት ችግር በማህበር ተደራጅቶ
እንዲፈታ ለማስቻል፣
6.2. ግልጽና ፍትሐዊ የሆነ የምዝገባና የአደረጃጀት ስርዓት ለመዘርጋት፤
6.3. የመሬት አቅርቦትንና አስፈላጊ የሆኑ የከተማ አስተደዳሩን ድጋፎች በግልጽ ተግባራዊ እንዲሆኑ ለማድረግ፣
ክፍል ሁለት
7. የምዝገባ መስፈርት
ማንኛውም የህብረት ስራ ማህበር ተመዝጋቢ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር የመንግስት ሠራተኞች የጋራ ሕንፃ መኖሪያ
ቤት ህብረት ስራ ማህበር አደረጃጀትና አፈጻጸም ደንብ ቁጥር 129/2014 አንቀጽ 7 ላይ የተመለከተው የአባልነት ምዝገባ
መስፈርት እንደተጠበቀ ሆኖ ለዚህ መመሪያ አፈጻጸም ሲባል የሚከተሉት መስፈርቶችን ማሟላት ይኖርበታል፡-
1. የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ መሆኑን የሚያረጋግጥ የታደሰ የነዋሪነት መታወቂያ ማቅረብ የሚችል፣
2. በመንግሥት ሠራተኝነት በቋሚነት ተቀጥሮ እያገለገለ ያለ ስለመሆኑ ከሚሰራበት ተቋም ለኤጄንሲው ማስረጃ
ማቅረብ የሚችል፣
3. ከ 2005 ዓ/ም ወዲህ በከተማ አስተዳደሩ ውስጥ በራሱም ሆነ በትዳር ጓደኛው ስም የመኖሪያ ቤትም ሆነ የመኖሪያ
ቤት መሥሪያ ቦታ የሌለው ወይም ኖሮት ለሶስተኛ ወገን ያላስተላለፈ፣
4. ቢሮው በሚያወጣው ወቅታዊ የመኖሪያ ቤት ዋጋ መሠረት የቤቱን የግንባታ ጠቅላላ ወጪ 10-15 በመቶ ቅድመ ክፍያ
በባንክ በዝግ ቁጠባ ሂሳብ በማህበሩ ስም ማስገባት የሚችል እና ቀሪውን የግንባታ ወጪ ከባንክ ጋር በሚፈጠር የብድር
ስምምነት መሠረት ውል ለመግባት ፈቃደኛ የሆነ፤
5. በዚህ መመሪያ አንቀጽ ሰባት ንዑስ አንቀጽ ከተራ ቁጥር 1 እስከ 5 ድረስ ያለው ቅድመ ሁኔታ እንደተጠበቀ ሆኖ
የመመዝገቢያ ጊዜ ኤጄንሲው በሚያወጣው ማስታወቂያ መሰረት ይሆናል፣
6. የማህበሩ አባል ሆኖ ቅድመ ሁኔታዎችን አሟልቶ የተመዘገበ ሠራተኛ ለባለ አንድ መኝታ ቤት፣ ለባለ ሁለት መኝታ ቤት
እና ለባለ ሶስት መኝታ ቤት በሚል እንደ መኝታ ቤቱ ዓይነት ለመደራጀት ፈቃደኛ የሆነ፤
7. ቢሮው ለኤጀንሲው በሚያቀርበው የቤቶች ዲዛይን መሰረት ማንኛውም በኅብረት ሥራ ማኅበር የሚደራጅ
ተደራጅ በአደራጁ አማካይነት በዕጣ የሚደለደል መሆኑን የሚቀበል፤
8. የህብረት ሥራ ማኀበሩ ሕገ-ወጥነትንና ያልተገባ ተጠቃሚነትን ለመከላከል ይቻል ዘንድ አባላቱን ማስመዝገብና የአባላቱን
አሻራ ለመውሰድ በሚወጣው ፕሮግራም መሠረት ቀርቦ አሻራ መስጠት የሚችል፤
9. ከላይ በአንቀጽ 7 ንዑስ አንቀጽ 8 ላይ የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በዚህ መመሪያ የተገለጸውን የማህበር
አባላት ቁጥር አሟልቶ የሚገኝ የአንድ ተቋም ሠራተኞች በፈቃደኝነታቸው መሰረት በአንድ ወይም ከዚያ በላይ
ማህበር ሆነው መደራጀት ይችላሉ፡፡
8. ተጠቃሚዎችን ስለመለየት
ኤጀንሲው የጋራ መኖሪያ ቤት ሕንፃ ማኀበር ለመደራጀት የሚፈልጉትን በዚህ መመሪያ አንቀጽ 7 ከንዑስ አንቀጽ 1
እሰከ 10 ድረስ በተመላከተው ዝርዝር መስፈርት መሰረት ተጠቃሚዎችን የመለየት ሥራ ያከናውናል፡፡
9. የአደረጃጀት ሂደት
1. በአንድ የጋራ መኖሪያ ቤት ሕንጻ ማህበር የሚደራጁ የአባላት ቁጥር የሚወሰነው ቢሮው በሚልከው ዲዛይን አንድ የመኖሪያ ቤት
ሕንጻ መያዝ በሚችለው የአባላት ብዛት እና የቤት ዓይነት ስብጥር መሰረት ይሆናል፡፡
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 መሰረት የቤት አይነት ምርጫ ያከናወነ የማህበር አባል በአቅራቢያው
እንዲተላለፍ ያደርጋል፤
መ) የሥራ አመራር ኮሚቴና የቁጥጥር ኮሚቴ አካላትን እንዲሁም ንዑስ ኮሚቴዎችን ይመርጣል፤
ሠ) የምስረታ ቃለ-ጉባዔ በማዘጋጀት አስመራጭ ኮሚቴና የተመረጡ አካላት በእያንዳንዱ ገጽ ላይ እንዲፈርሙ ተደርጎ
6. ማህበሩ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (5) መሰረት ከቤት ፍላጎት ምዝገባ ቅጻቅጾች በተጨማሪ በደንቡ አንቀጽ (14)
ንዑስ አንቀጽ (3) የተዘረዘሩትን እና ከተለያዩ ተቋማት ጋር ማህበሩን ወክለው ግንኙነት የሚያደርጉ የስራ አመራር
ኮሚቴ አካላትን ውክልና ጭምር የያዘ ሰነድ ለአደራጅ አካል ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
7. የክፍለ ከተማው ጽህፈት ቤት ማህበሩ ለቅድመ ምዝገባ የሚያስፈልጉ ሁኔታዎችን አሟልቶ ሲገኝ ለባንክ በአባላቱ ስም
ዝርዝር መሠረት በማህበሩ ስም ዝግ ሂሳብ እንዲከፈት ደብዳቤ ይጽፋል፣
8. ማንኛውም ሰው በማህበር ሲደራጅ የቤቱን የግንባታ ወጪ ቅድመ ክፍያ ለባንክ በማህበሩ ስም በተከፈተ ዝግ ሂሳብ ገቢ
ያደርጋል፤ ገቢ ያደረገበትንም ማስረጃ በማህበሩ አማካኝነት ለክፍለ ከተማው ጽህፈት ቤት ያቀርባል፤
9. በባንክና በአደራጁ መካከል በሚደረግ ስምምነት መሠረት በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀፅ (8) የተመለከተው ቅድመ ክፍያ
የተቀበለው ባንክ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀፅ (7) መሰረት የተፃፉለትን ደብዳቤ ቁጥር፣ ገቢ የተደረገውን
የገንዘብ መጠን፣ ገንዘቡን ገቢ ያደረገበትን የገንዘብ መቀቢያ ሰነድ ቁጥር እና ቀን ጠቅሶ ለክፍለ ከተማው
ጽህፈት ቤት ገንዘቡ ገቢ ስለመሆኑ ደብዳቤ ይጽፋል፤ ይህም መረጃ በቀጣይ በዘመናዊ ኢንፎርሜሽን
ይሰጣል፡፡
ክፍል ሶስት
2. ከላይ በአንቀጽ (10) ንዑስ አንቀጽ (1) ላይ የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ የህንጻው ከፍታ የሚወሰነው በከተማ
አስተዳደሩ የማስተር ፕላንና የከተማው የግንባታ ፍቃድና ቁጥጥር መመሪያን በማይጻረር መልኩ ይሆናል፤
3. የቤት ስፋት አማካይ ባለ አንድ መኝታ ቤት 60 ካ.ሜ፣ ባለ ሁለት መኝታ ቤት 75 ካ.ሜ እና ባለ ሦስት
ሀ. G+4፡ 40 አባላት
ለ. G+5- 70 አባላት
ለ. G+7፡ 75 አባላት
ሐ. G+9፡ 90 አባላት
መ. G+12፡ 110 አባላት
ሠ. G+15፡ 140 አባላት
3. በአንቀጽ 12 ንዑስ አንቀፅ 2 በፊደል ተራ ሀ ፣ለ ፣ሐ ፣መ እና ሠ ዜሮ ወለል ለተለያዩ
አገልግሎቶች ማዋል ይቻላል ፡፡
13. ስለቤቶች አሰራር
ልማትና የከተማውን መዋቅራዊ ኘላን እንዲሁም የከተማ ህንፃ ጥግግትና ከፍታ መሠረት ያደረገ
ይሆናል፤
2. ቢሮው የከተማዉን መዋቅራዊና የአካባቢ ልማት ፕላን መሠረት አድርጎ የሕንፃ ዲዛይን ያዘጋጃል
ክፍል አራት
ግዴታና ኃላፊነቶች
4. ማንኛውም ተመዝጋቢ የማህበር አባል በአደረጃጀትና በአመዘጋገብ ሂደት የተከሰቱና ከዚህ መመሪያ
5. ማንኛውም የማህበሩ አባል በተመረጠው የቤት ዲዛይን አማካኝነት የቤቱን ወጪ በዚህ መመሪያ
በአንቀጽ 7 ንዑስ አንቀጽ (5) መሠረት በማህበሩ ስም በተከፈተው ባንክ በዝግ ቁጠባ ሂሳብ ገቢ
የማድረግ፤
ለማህበሩ የማቅረብ፤
7. የማህበሩ አባላት የቤቶችን ግንባታ በቅርብ በመከታተል በዕውቀት፣ በጉልበት እና በተለያዩ መንገዶች
የመደገፍ፤
8. በማህበር የሚደራጅ አባል መብቱን በሽያጭም ሆነ በስጦታ ለሦስተኛ ወገን ማስተላለፍ የሚችለው
9. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (8) የተጠቀሰው ቢኖርም አባል በሞት ምክንያት ሲለይ በህግ አግባብ
ተረጋግጦ ለሚቀርበው ወራሽ የህንጻ ግንባታው 100% ከመድረሱ በፊት ማስተላለፍ የሚችል
መሆኑን፤
10. የህብረት ስራ ማህበሩ አባል የቤቶቹ ግንባታ ሲጠናቀቅ በጋራ ህንጻ መኖሪያ ቤት ማኅበር
አስተባባሪነት በቦታው በአካል በመገኘት ወይም በህጋዊ ወኪል በዕጣ የሚደርሰውን ቤት የመረከብ፤
11. ከአበዳሪ ባንክ ጋር በሚደረገው የብድር ውል መሠረት ቀሪ ክፍያውን ወቅቱን ጠብቆ የመከፍል ግዴታ የሚቀበል፤
12. በዚህ መመሪያ አንቀጽ 14 ንዑስ አንቀጽ (9) የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ የማህበሩ አባል
በራሱ ፍላጎት፣ በዲሲፕሊን እና በፍርድ ቤት ውሳኔ ከማህበሩ አባልነት ሊሰረዝ ይችላል፤
13. አባሉ ሕገ-ወጥነትንና ያልተገባ ተጠቃሚነትን ለመከላከል ይቻል ዘንድ አሻራ ለመውሰድ በሚወጣው ፕሮግራም
መሠረት ቀርቦ አሻራ የመስጠት፡፡
1. የመመስረቻ ቃለ-ጉባኤ፣ የመተዳደሪያ ደንብና በደንብ ቁጥር 129/2014 በአንቀጽ 14 ንዑስ አንቀጽ 3 ላይ
6. የአባላትን እና የማህበሩን መብትና ጥቅም ለማስከበር ከኤጀንሲው እና ሌሎች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ
ተባብሮ የመስራት፤
7. ከባንክ ጋር ስለሚኖረው የብድር ውልና አመላለስ፣ ህንጻውን ለገነባው አካል ስለሚከፈል አከፋፈል እና ሌሎች ተያያዥ
ጉዳዮችን ማህበሩን ወክሎ የማስፈጸም፤
8. በአባላት ስነ-ምግባር ዙሪያ በጠቅላላ ጉባኤ የሚተላለፉ ውሳኔዎችን ለአደራጁ ጽ/ቤት አቅርቦ ሲጸድቅ ብቻ ተግባራዊ
የማድረግ፤
9. በዚህ መመሪያ አንቀጽ 14 ንዑስ አንቀጽ (12) በተጠቀሰው መሰረት ከማህበሩ አባልነት ስለሚሰናበት
የማህበር አባል አጀንዳውን ለጠቅላላ ጉባኤ አቅርቦ የተደረሰበትን የውሳኔ ሃሳብ ለአደራጁ አካል
በ 10 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የመጨረሻ ውሳኔ እንዲሰጥበት የማቅረብ፤
10. ከእጣ ክፍፍል በኋላ በአዋጅ ቁጥር 370/95 መሰረት የጋራ ህንጻ ነዋሪዎች ህብረት ስራ ማህበር እንዲደራጅ በማመቻቸት
ለአደራጅ ጽ/ቤት ጥያቄ የማቅረብ፡፡
16. የኤጀንሲው ኃላፊነት
ኤጀንሲው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈፃሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 74/2014
የተሰጡት ስልጣንና ተግባር እንደተጠበቀ ሆኖ ለዚህ መመሪያ አፈጻጸም የሚከተሉት ኃላፊነት ይኖረዋል፡-
1. በጋራ ህንጻ መኖሪያ ቤት ህብረት ስራ ማህበር ለመደራጀት የሚላኩ የየተቋማት ሰራተኞች ዝርዝር መረጃ
አጣርቶ ለአደራጅ ክፍለ ከተማ ህብረት ስራ ጽ/ቤት የማስተላለፍ፤
2. የመንግስት ሰራተኞች የጋራ ህንጻ መኖሪያ ቤት የህብረት ስራ ማህበራት አመዘጋገብ፣ አደረጃጀት፣ ይዘትና አስፈላጊነት ላይ
የምዝገባ፣ የመስራች ቃለ-ጉባኤ እንዲሁም ሌሎች በዚህ መመሪያ የተገለጹትን አስፈላጊ ቅጻቅጾችና
9. በዚህ መመሪያ መሰረት የሚደራጅ ማህበር ለምዝገባ ብቁ ሆኖ በአካል እስከቀረበ ድረስ ተረጋግጦ
10. በማኅበሩ ሥም ፋይል ስለመከፈቱ፣ በአባላት የተሞሉት ቅፃቅፆች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ
11. ማህበራት ቅድመ ሁኔታውን አሟልተው ሲቀርቡ የተለያዩ የትብብርና የድጋፍ ደብዳቤዎችን
13. ለተደራጆች የምዝገባ ጊዜ ገደብን በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች የምዝገባ ጥሪን ያስተላልፋል፤
14. በዚህ መመሪያ በአንቀጽ 14 በንዑስ አንቀጽ 12 ላይ በተመላከተው መሰረት ከህብረት ስራ ማህበሩ
በለቀቁ አባላት ምትክ ተተኪ አባልን ከተጠባባቂ ተመዝጋቢዎች ተክቶ መረጃውን ለቢሮ በጽሑፍ
የማሳወቅ፤
1. የተደራጁትን የመንግስት ሰራተኞች የጋራ ህንጻ የመኖሪያ ቤት የህብረት ማህበራት መረጃን ከኤጄንሲው የመረከብ፤
2. ለኅብረት ሥራ ማኅበር አገልግሎት የሚውል የለማ መሬት ከመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ጠይቆ የመረከብ፤
3. በህብረት ስራ ማህበራት የሚገነቡ የጋራ መኖሪያ ቤት ህንጻዎች የከተማውን መሪ ፕላን መሠረት ያደረገ መሆኑን
የማረጋገጥ፤
4. ደረጃቸውን የጠበቁ የህንፃ ዲዛይኖችን የማዘጋጀትና የኅብረት ሥራ ማህበራትን በማወያየት ለምርጫ የማቅረብና
የማስወሰን፤
5. በህብረት ስራ ማህበሩ የሚገነቡ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በቴክኖሎጂ የታገዙ እንዲሆኑ ምክረ ሃሳብ የማቅረብ፣
6. የዲዛይንና የሱፐርቪዥን ድጋፎችን ማድረግ እንዲሁም ሌሎች ከግንባታ ጋር የተያያዙ የምክር አገልግሎት የመስጠት፤
7. በጋራ መኖሪያ ሕንፃ ኅብረት ሥራ ማህበር በመደራጀት ቤት ለመገንባት ለሚንቀሳቀሱ የኅብረት ሥራ ማህበራት
አመራሮች ስለኮንስትራክሽን ማኔጅመንት የአቅም ግንባታ ሥልጠና የመስጠትና ተያያዥ ድጋፎችን የማድረግ፤
8. በህብረት ስራ ማህበራት የሚቀርቡ የስራ ተቋራጮችና አማካሪ ድርጅቶች መስፈርቱን ማሟላታቸውን የማረጋገጥ፤
9. በዚህ አንቀጽ 17 ንዑስ አንቀጽ 8 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ ለህብረት ስራ ማህበር የጋራ ቤቶች ግንባታ ስራ የስራ
ተቋራጭ፣ አማካሪ ድርጅት እና ከቤት ግንባታ ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ተግባራት የሚያከናውኑ የጥቃቅንና አነስተኛ
10. በዝግ የባንክ ሂሳብ የተቀመጠውን ገንዘብ ለማስለቀቅ እንዲቻል ግንባታው የደረሰበትን ደረጃና በየደረጃው
የሚያስፈልገውን የገንዘብ መጠን እንዲለቀቅ ለኤጄንሲው የማሳወቅ፤
11. የግንባታዎቹን ሂደት የሚከታተል ባለሙያ የመመደብ፣ የመከታተልና ግንባታው የደረሰበትን ደረጃ ለኤጄንሲው
የማሳወቅ፤
12. የኅብረት ሥራ ማኅበራቱ በተደራጁበት ዓላማ መሠረት ግንባታ እንዲያከናውኑ ክትትልና ድጋፍ የማድረግ፤
13. ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተውና ትስስር ፈጥረው ለመኖሪያ ቤት ህብረት ስራ ማህበራት አስፈላጊውን የመሰረተ
ልማት እንዲቀርብ የማመቻቸትና ክትትል የማድረግ፤
14. ለህብረት ስራ ማህበራት የጋራ መኖሪያ ቤት ህንጻ ግንባታ የሚቀርቡ የግንባታ ግብዓቶች እንዲሟላ የማመቻቸት፣
ክትትልና ድጋፍ የማድረግ፤
15. ለዚህ ፕሮግራም የሚያግዝ የፋይናንስ አማራጭ ፕሮፖዛል አዘጋጅቶ ለባንኮችና ሌሎች በመንግስት እውቅና
ለተሰጣቸው የፋይናንስ ተቋማት የማቅረብ፤
16. በዚህ አንቀጽ 17 ከንዑስ አንቀጽ 1 እስከ 15 ላይ የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ መመሪያውን በተገቢው ለማስፈጸም
ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብርና በመቀናጀት የመስራት፤