Professional Documents
Culture Documents
የገንዘብ_ቁጠባና_ብድር_ኅብረት_ሥራ_ማህበራት_ዩኒየን_መተዳደሪያ_ደንብ
የገንዘብ_ቁጠባና_ብድር_ኅብረት_ሥራ_ማህበራት_ዩኒየን_መተዳደሪያ_ደንብ
ሥራ ማህበራት ዩኒየን
መተዳደሪያ ደንብ
(ሞዴል)
የ ኃ/የተወሰነ ገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየን
መተዳደሪያ ደንብ
1. የኅብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየን ስምና አድራሻ
1.1. የኅብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየኑ ስም
2. አድራሻ
2.1. ክልል/ከተማ አስተዳደር
2.2. ዞን/ክፍለ ከተማ
2.3. ወረዳ
2.4. ቀበሌ
2.5. ስልክ ቁጥር
2.6. ፋክስ ቁጥር
2.7. ፖ.ስ.ቁ
2.8. ድረ ገጽ
2.9. ኢሜይል
3. የስራ ክልል
3.1. የስራ ክልሉ
4.2. ማህተም
4.2.1.
፣
5. ትርጉም
በኅብረት ሥራ ማህበራት አዋጅ ቁጥር 985/2009የተቀመጠው ትርጓሜ እንዳለ ሆኖ የቃሉ አገባብ በህግ ሌላ
ትርጉም የማያሰጥ ካልሆነ በስተቀር በዚህ መተዳደሪያ ደንብ ውስጥ፡-
5.1. “ግለሰብ”፡-ማለት በህግ መብት የተሰጠው የተፈጥሮ ሰው ማለት ሲሆን ይህም የወንድን ወይም የሴትን ጾታ
የሚያካትት ነው፡፡
5.2. “ሸሪዓ” ማለት የእስልምና ተከታዮች የሚመሩበት ከፈጣሪ የወረደ ትዕዛዝ ነው፡፡
1
5.3. “መደበኛ ቁጠባ” ማለት የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበሩ በሚወሰነው የጊዜ ገደብ እና ዝቅተኛ የገንዘብ
መጠን መሰረት በማድረግ አባሉበግሉ የወሰነውን የቁጠባ መጠን በተከታታይነት ያለማቋረጥ የሚቆጠበው ቁጠባ
ነው፡፡
5.4. “የፍላጎት ቁጠባ” ማለት አባሉ በፍላጎቱ ከመደበኛው ቁጠባ በተጨማሪ በተለያዩ የቁጠባ አይነት የሚቆጠበው ቁጠባ
ነው፡፡
5.5. “የልጆች ቁጠባ” ማለት እድሜያቸው ከ18 አመት በታች የሆኑና በኅብረት ሥራ ማህበሩ የስራ ክልል የሚኖሩ ልጆች
በቤተሰቦቻቸው በኩል የሚቆጥቡት የአደራ ቁጠባ አይነት ነው፡፡
5.6. “ብድር” ማለት አባላት ለተለያዩ ጉዳዮች ማስፈጸሚያ የሚሆን ከገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ወይም
ከፋይናንስ ተቋማት በሚደረግ ስምምነት መሰረት በተወሰነ ጊዜ ቆይታ ተመላሽ የሚሆን እና ወለድ የሚያስከፍል
ወይም ወለድ የማያስከፍል ገንዘብ ነው፡፡
5.7. “ወለድ” ማለት ግለሰቦች ወይም ተቋማት ለቆጠቡት ገንዘብ የሚከፈላቸው ወይም ለተበደሩት ገንዘብ የሚከፍሉት ዋጋ
ነው፡፡
5.8. “ወለድ የሚያስገኝ የፋይናንስ አገልግሎት” ማለት የቁጠባ እና የብድር የፋይናንስ አገልግሎት ሆኖቆጣቢዎች ወለድን
የሚያገኙበት ወይም ተበዳሪዎች ወለድ የሚከፍሉበት አገልግሎት ነው፡፤
5.9. “ወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎት” በሸሪዓ መሰረት በሚሰጡ የቁጠባና የብድር አገልግሎቶች ወለድ መቀበልና
መክፈልን በጥብቅ የሚከለክል አገልግሎት ማለት ነው፡፡
5.10. “ተካፉል አገልግሎት” ማለት በሸሪያ መሰረት የሚሰጥ የአነስተኛ መድን ዋስትና አገልግሎት ነው፡፡
5.11. “አረቦን” ማለት ለአነስተኛ መድን ዋስትና ወይም ተካፉል አገልግሎትን ለመስጠትእንዲቻል ከተበዳሪ የሚሰበሰብ
ገንዘብ ነው፡፡
5.12. “ተጨማሪ እጣ” ማለት የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ለተለያዩ ኢንቨስትመንት ስራዎች ለማከናወን
ለአባላት የሚሸጠው እጣ ነው፡፡
5.13. “መነሻ እጣዎች” ማለት አንድ ገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር የዩኒየን አባል መሆን ሲፈልግ ሙሉ አባል
ለመሆን የሚገዛው እጣ ነው፡፡
5.14. “የአባላት ካፒታል” ማለት አንድ አባል የመደበኛውን ቁጠባ ደህንነት ለመጠበቅ በሚያስችል ምጥጥን ተሰልቶ አባሉ
የሚያስቀምጠው ገንዘብ ነው፡፡
5.15. “የፋይናንስ አገልግሎት አካታችነት” ማለትአባል የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት የፋይናንስ
አገልግሎቶችን በጥራትና በተደራሽነት መጠቀም ሲችሉ ነው፡፡
6. የዩኒየኑ አላማ፣
6.1. የአባላትን ፍላጎት መሰረት ያደረገ መደበኛ እና የፍላጎት ቁጠባናየተለያዩ የብድር አገልግሎቶች በመስጠት፣
የኢንቨስትመንት አቅም በማጎልበት ጠንካራ የፋይናንስ ተቋም መፍጠር ነው፡፡
6.2. የወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎት ስርዓት በመዘርጋት አባላትን መሰረት ያደረገ የፋይናንስ አገልግሎት በመስጠት
የኢንቨስትመንት አቅም ማጎልበት፣
6.3. የአነስተኛ መድን ዋስትና ወይም የተካፉል አገልግሎት በመስጠት የአባላትን ቁጠባና የኅብረት ሥራ ማህበሩ
ያሰራጨው ብድር ደህንነቱ የጠበቀ እንዲሆንናየሚከሰተውን ማህበራዊ ቀውስን ማስወገድ፣
6.4. የፋይናንስ አገልግሎት አካታችነትን በማሳደግ፣ የኅብረተሰቡን የፋይናንስ ክህሎትናየቁጠባ ባህልን በማዳበር
2
የአባላትን በራስ የመተማመን አቅም ማጎልበት፣
6.5. የፋይናንስ ተቋማት እና ኅብረት ሥራ ማህበራት የፋይናንስ ትስስር በመፍጠር የሚከሰተውን የፋይናንስ እጥረትና
ክምችት ችግርን መፍታት፣
7. ኅብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየን ተግባራት
7.1. የተለያዩ የቁጠባና ብድር አሰራር በመዘርጋት ከአባላት ቁጠባ መሰብሰብና የብድር አገልግሎት መስጠትና ማስመለስ፣
7.2. አባላት ገንዘባቸውን አዋጭነት ባለው ስራ እንዲያውሉ የምክር አገልግሎት መስጠት፣
7.3. የአደራ ገንዘብ ተረክቦ ያስቀምጣል፣የሀዋላ ወይም የገንዘብ መላላክ አገልግሎት መስጠት፣
7.4. ተዘዋዋሪ ብድሮችን ተረክቦ ያስተዳደራል፣
7.5. የወለድ አልባ የፋይናንስ አግልገሎት በአባሉ ሙሉ ፍላጎትና ጥያቄ መሰረት ራሱን በቻለ አደረጃጃት አገልግሎት
መስጠት፣
7.6. የአነስተኛ መድን ዋስትና ወይም ተካፉል አገልግሎት ከአባል ኅብረት ሥራ ማህበራት ጋር በጋራ በመሆን ለአባሉ
ይሰጣል፣
7.7. ዘመናዊ የሂሳብ አሰራር ስርዓት መዘርጋት፣
7.8. ለአባላት፣ ለአመራር አካላት፣ ቅጥር ሰራተኞች አስፈላጊው ትምህርት፣ ስልጠና መስጠት፣
7.9. የተለያዩ የፋይናንስ አገልግሎቶችን በመስጠት የዩኒየኑን ካፒታል ማሳደግ፣
7.10. ዘመናዊ የመረጃ ቴክኖሎጂ ስርዓት መዘርጋት ዩኒየኑን እና አባላት የኮር ባንኪንግ ስርዓት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ፣
7.11. አግባብ ያለው ባለስልጣን በሚፈቅደው መሰረት ለመሰረታዊ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር ኦዲት
አገልግሎት መስጠት፣
7.12. ለስራው አጋዥ የሚሆኑ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረት ማፍራትና ማስተዳደር
7.13. ከተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት ጋር ትስስር መፍጠር፣
7.14. በዩኒየኑ የስራ ክልል አባል ያልሆኑ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት አባል እንዲሆኑ ያደርጋል፣
7.15. ከሌሎች መሰል የገንዘብ ቁጠባ ብድር ኅብረት ሥራ ማህበራት ጋር በመሆን የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ
ማህበራት ፌዴሬሽን ማቋቋም፣
7.16. ሌሎች በጠቅላላ ጉባኤ የሚሰጡ ተግባራትን ይፈጽማል፣
8. የኅብረት ሥራ መርሆች
8.1. አባልነት በፈቃደኝነትና በፍላጎት ላይ የተመሰረተ እና ለሁሉም ክፍት ማድረግ፣
8.2. ዲሞክራሲያዊ አሰራና አመራር ማስፈን፣
8.3. አባላት ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ማስቻል፣
8.4. ራስ አገዝና ራስን በራስ ማስተዳደር፣
8.5. ለአባላት፣ለአመራር አካላትና ለቅጥር ሰራተኞች ተከታታይ ትምህርት ፣ስልጠናና መረጃ መስጠት፣
8.6. ከሌሎች አቻ ኅብረት ሥራ ማህበራት ጋር ኅብረት መፍጠር ፣
8.7. በአካባቢ ልማት መሳተፍ፣
9. የኅብረት ሥራ እሴቶች፣
9.1. ራስን በራስ መርዳት፣
9.2. የግል ኃላፊነትን መወጣት፣
3
9.3. የዲሞክራሲ ባህል ማስፋፋት፣
9.4. እኩልነት፣
9.5. ፍትሃዊነት፣
9.6. ወንድማማችነት፣
10. የአባላት የስነ-ምግባር ዕሴቶች፣
10.1. ታማኝነት፣
10.2. ግልጽነት፣
10.3. ተጠያቂነት
10.4. አሳታፊነት
10.5. ማህበራዊ ኃላፊነት፣
10.6. ለሌሎች ማሰብ ናቸው፣
11. አባል ለመሆን የሚያበቁ ሁኔታዎች፣
የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟላ መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበር የኅብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየኑ አባል መሆን
ይችላል፣
11.1. በኅብረት ሥራ ማህበራት ማቋቋሚያ አዋጅ መሰረት አግባብነት ባለው ባለስልጣን ተመዝግቦ የህጋዊ ሰውነት
ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት ያገኘ እና ወቅቱን ጠብቆ ያሳደሰ መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበር፣
11.2. በሌላ ተመሳሳይ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት ዩኒየን አባል ያልሆነ፣
11.3. የዩኒየኑን መተዳደሪያ ደንብ፣ ውስጠ ደንብ፣ ዩኒየኑ ያወጣቸው የተለያዩ የውስጥ የስራ መመሪያዎች፣ የጠቅላላ ጉባኤ
ውሳኔዎችን የተቀበለና ግዴታውን ለመወጣት ፈቃደኛ የሆነ፣
11.4. በመተዳደሪያ ደንቡ የተቀመጠውን መመዝገቢያና የአባልነት መነሻ ዕጣ ለመግዛት የተስማማ፣
11.5. በመተዳደሪያ ደንቡ የተቀመጠውን መነሻ መደበኛ ቁጠባ ለመቆጠብ ፈቃደኛ የሆነ፣
11.6. በህግ ችሎታ ያለውና ተቀባይነት ያገኘ፣
11.7. አባል ለመሆን የመሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበሩ ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ ማቅረብ የሚችል፣
11.8. አባል ለመሆን የሚፈልግ የመሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበሩ የፋይናንስ ሪፖርት ማቅረብ የሚችል፣
12. ለኅብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየን አባልነት ስለሚቀርብ ማመልከቻ፣
12.1. አባል ለመሆን የሚፈልግ ኅብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየኑ ለዚህ ተግባር ያዘጋጀውን የአባልነት ማመልከቻ ቅጽ ተሞልቶ
በስራ አመራሩ ፊርማ ለኅብረት ሥራ ዩኒየን የስራ አመራር ቦርድ ያቀርባል፣ ከማመልከቻው ጋር የሚከተሉት ተያይዘው
መቅረብ አለባቸው፣
12.1.1. የመሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ
12.1.2. አግባብ ባለው አካል መመዝገቡን የሚያረጋግጥና የታደሰ ሰርተፊኬት፣
12.1.3. የፋይናንስ አቋሙን የሚያሳይ የፋይናንስ ሪፖርት፣
12.1.4. የመሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበር አመራር አካላት ስም ዝርዝር፣ አድራሻና ፊርማ፣
12.2. የዩኒየኑ ቦርድ አመራር የቀረበለትን የአባልነት ማመልከቻ መርምሮ በ ቀናት ውስጥ አባልነት
ለጠየቀው መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበር አባልነቱን ስለመቀበሉ በጽሁፍ መልስ ይሰጣል፣ አስፈላጊውን ፎርማሊቲ
4
አሟልቶ አባል ይሆናል፣
12.3. አባልነቱን ያልተቀበለው ስለመሆኑ ያልተቀበለበትን ምክንያት በጽሁፉ ይመልስለታል፣
12.4. የዩኒየኑ ቦርድ አመራር አባል የሆነውን መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበር አባል ስለመሆኑ ለጠቅላላ ጉባኤ ሪፖርት
ያደርጋል፣
12.5. አመልካቹ በውሳኔው ቅሬታ ካለው ለዩኒየኑ ጠቅላላ ጉባኤ በጽሁፍ ይግባኝ ሊጠይቅ ይችላል፣
12.6. በድጋሚ አባል ለመሆን የሚፈልግ አመልካች በተመሳሳይ ሁኔታ ማመልከቻውን ሞልቶ ማቅረብ ይኖርበታል፣
12.7. የአባልነት ማመልከቻ ዩኒየኑ ያዘጋጃል፣
13. ስለ አባላት ምዝገባ፣
ኅብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየን ከዚህ በታች በተጠቀሱት ነጥቦች መሰረት የአባላት መዝገብ አዘጋጅቶ መዝግቦ
ይይዛል፣
13.1. የአባልነት መለያ ቁጥር
13.2. የአባል ኅብረት ሥራ ማህበሩ ስም፣ ዓይነት፣ አድራሻ፣ የተቋቋመበት ዓ/ም
13.3. በህግ የተመዘገበበት ቁጥርና ዓ/ም
13.4. አባል ሲሆን ያሉ አባላት በጾታ፣
13.5. አባል የሆነበት ቀን፣ ወር እና ዓ/ም
13.6. የገዛው እጣ መጠን እና የተከፈለ መመዝገቢያ፣
13.7. አባልነት ያቋረጠበት ቀን፣ ወርና ዓ/ም
13.8. ያቋረጠበት ምክንያት፣
14. የአባላት መብት
14.1. ስለ ዩኒየኑ እንቅስቃሴ የሚፈልገውን መረጃ ጠይቆ የማግኘት መብት፣
14.2. በወኪሎቹ አማካኝነት የዩኒየኑ ጉባኤ ላይ መሳተፍ፣ ሃሳብን በነጻ የመግለጽ፣ ድምጽ የመስጠት፣
14.3. አመራሮችን የመምረጥና የማሰናበት፣ እንዲሁም በአመራርነት የመመረጥ፣
14.4. ዩኒየኑ የሚሰጠውን አገልግሎትና ጥቅም የማግኘት፣
14.5. ዩኒየኑን በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ ማንኛውንም ጥያቄ፣ ቅሬታ፣ አስተያየት ማቅረብና መልስ የማግኘት፣
14.6. ጥቅሞቹ ተከብረውለት በጥያቄው መሰረት የመሰናበት፣
15. የአባላት ግዴታዎች
በኅብረት ሥራ ማህበራት አዋጅና መመሪያ መሰረት እያንዳንዱ የዩኒየኑ አባል መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበር
የሚከተለውን የመፈጸም ግዴታ አለበት፣
15.1. የመመዝገቢያ፣ ዝቅተኛውን የአባልነት እጣ ዋጋ የመክፈል እና ዝቅተኛውን መደበኛ ቁጠባ በወቅቱ የመቆጠብ፣
15.2. የዩኒየኑን መተዳደሪያ ደንብ፣ የውስጥ አሰራር መመሪያዎች፣ ውስጠ ደንቦችና ውሳኔዎች የማክበር እና የመፈጸም፣
15.3. በዩኒየኑ ጉባኤ ላይ መገኘት፣
15.4. በዚህ መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ 50.6.1. ከተቀመጠው በላይ ያለ የዩኒየኑን ኪሳራ በጋራ የመካፈል፣
15.5. የዩኒየኑን የጋራ ንብረት መንከባከብ፣
15.6. አባሉ በገባው ውል መሰረት የወሰደውን ብድር በወቅቱ የመክፈል
5
በአነስተኛ መድን ዋስትና በተገባ ውል መሰረት መረጃን የማጠናቀር እና ከግለሰብ አባላት አረቦን ሰብስቦ ገቢ ማድረግ
15.7.
፣
16. የመመዝገቢያ ክፍያ
16.1. ማንኛውም መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበር የዩኒየኑ አባል እንዲሆን ሲፈቀድለት የመመዝገቢያ ብር (
) ይከፍላል፣
16.3. የመመዝገቢያ ክፍያ ለዩኒየኑ የሚያስፈልጉ ሰነድ ማዘጋጃና ማደራጃ እንዲሁም ስራ ማስኬጃነት ይውላል፣
16.4. አንድ አባል ከዩኒየኑ ከተሰናበተ በኋላ እንደገና አባል እንዲሆን ከተፈቀደለት እንደ አዲስ አባል የመመዝገቢያ ክፍያ
ይከፍላል፣
17.1. አባል እንዲሆን የተፈቀደለት መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበር ዩኒየኑ ካዘጋጀው እጣዎች ውስጥ የእጣ ድርሻ ይኖረዋል፡፡
17.3. ዩኒየኑ የተለያዩ ኢንቨስትመንት ስራዎችን ለማከናወን ሲፈልግ እጣዎችን በጠቅላላ ጉባኤ ወስኖ መሸጥ ይችላል፣
ሆኖም ተጨማሪው እጣ ሽያጭ በተወሰነው የጊዜ ገደብ ውስጥ ተሸጦ መጠናቀቅ ይኖርበታል፣
17.4. እያንዳንዱ አባል በየጊዜው ከመደበኛ ቁጠባ እድገት ጋር የተጣጣመ የካፒታል መጠን እንዲኖረው የመደበኛው
ቁጠባውን ያላነሰ ዋጋ ያለው ገንዘብ በካፒታል መልክ በዩኒየኑ በየጊዜው እየለየ
ያስቀምጣል፣
17.5. በአንቀጽ 17.4 መሰረት የካፒታል ገንዘብ ከመደበኛ ቁጠባ ጋር አብሮ ይሰበሰባል፣ የእጣና የአባላት ካፒታል ተለይቶ
ሂሳቡ መመዝገብ ይኖርበታል
17.6. የዩኒየኑ አባል እንዲሆን የተፈቀደለት አመልካች ከተፈቀደለት ቀን አንስቶ በ ጊዜ ውስጥ አባል ለመሆን
የሚያስችለውን የመነሻ እጣ መጠን ከፍሎ ማጠናቀቅ አለበት፣
17.8. በየጊዜው ከቁጠባ ሂሳብ ጋር የሚሰበሰበው የአባለት ካፒታል በአባሉ የቁጠባ ደብተር ላይ ተመዝግቦ መያዝ አለበት፣
6
17.9. ከዩንየኑ ዕጣ ለገዛ ለማንኛውም አባል ኅብረት ሥራ ማህበራት ዕጣ ስለመግዛታቸው የሚያስረዳ የዕጣ ሰርተፍኬት
አዘጋጅቶ መስጠት አለበት፡፡
17.10. ከመደበኛ ቁጠባ ጋር የሚሰበሰብ የአባላት ካፒታል የመደበኛ ቁጠባ ደህንነት የሚጠብቅ በመሆኑ ገቢ በማያስገኙና
በረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት ላይ አይውልም፣ የአባላት ካፒታል አጠቃቀም አስመልክቶ በፋይናንስ አስተዳደር መመሪያ
መሰረት የሚከናወን ይሆናል፣
18.2. ዩኒየኑ ወለድ አልባ እና ወለድ የሚያስገኝ መደበኛ ቁጠባ ከአባላት ይሰብስባል፣
18.3. እያንዳንዱ አባል መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበር ቢያንስ ብር የሚሆነውን ዝቅተኛ መደበኛ
ቁጠባ ገንዘብ ለዩኒየኑ በ ጊዜ ገደብ ገቢ ያደርጋል፣ ሆኖም እያንዳንዱ አባል መሰረታዊ ኅብረት ሥራ
ማህበር ከዝቅተኛ ቁጠባ መጠን በላይ መቆጠብ ከፈለገ በማመልከቻ ጠይቆ በመደበኛነት መቆጠብ ይችላል፣
18.4. እያንዳንዱ አባል መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበር ዩኒየኑ በሚያዘጋጀው ማመልከቻ መሰረት መቆጠብ የሚፈልገውን
ወለድ አልባ ወይም ወለድ የሚያስገኝ ቁጠባን ለይቶ ለዩኒየኑ በማመልከቻ መጠየቅ ይኖርበታል፣
18.5. አባሉ በወለድ አልባ ወይም ወለድ በሚያስገኝ የመደበኛ ቁጠባ መጠንን ለመለወጥ ቢፈልግ ዩኒየኑ በሚያዘጋጀው
ማመልከቻ መጠየቅ ይችላል፣ ሆኖም ጥያቄው ተቀባይነት የሚኖረው የስራ አመራር ቦርድ ሲወስን ነው፣ መጠኑ
በአንቀጽ 18.3. ከተቀመጠው ዝቅተኛ መደበኛ ቁጠባ መጠን ማነስ የለበትም፣
18.6. የመደበኛ ቁጠባ ተቀማጭ ገንዘብ የብድር መጠንን ለመወሰን እና ለብድር ጥያቄ ዋስትና በመሆን ሊያገለግል
ይችላል፣
18.7. አባሉ ከዩኒየኑ እስካልተሰናበተ ድረስ ወለድ በሚያስገኝም ሆነ በወለድ አልባ የተቀመጠ መደበኛ ቁጠባ በማንኛውም
ጊዜ ለአባሉ ወጪ ሆኖ አይከፈለውም፣
18.8. ዩኒየኑ ከመደበኛ ቁጠባ ውጪ ያሉ የቁጠባ አገልግሎቶች መስጠት የሚችለው ቁጠባውን የመጠቀም አቅሙ ከፍተኛ
ሲሆን ብቻ ነው፣
18.9. ወለድ አልባ ወይም ወለድ በሚያስገኝ የፍላጎት ቁጠባ አገልግሎት መጠቀም የሚፈልጉ አባላት ጥያቄዎቻቸውን ዩኒየኑ
ባዘጋጀው ማመልከቻ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፣
18.10. ዩኒየኑ ከአባሉ ጋር በሚያደርገው ስምምነት መሰረት ወለድ በሚያስገኝ እና ወለድ አልባ የጊዜ ገደብ ቁጠባ አገልግሎት
ይሰጣል፣ ሆኖም የጊዜ ገደብ ቁጠባ አገልግሎት ከ ወራት ማነስ የለበትም፣
18.11. አባላት በፍላጎታቸው የቆጠቡት ገንዘብ በገቡት ውል መሰረት ታይቶ ማውጣት ይችላሉ፣ ሆኖም ግን የቆጠቡትን ገንዘብ
ማውጣት የሚችሉት ገንዘቡ በብድር ዋስትናነት ካልተያዘ ብቻ ነው፣
18.12. ዩኒየኑ የቁጠባ መሰብሰቢያና ማውጫ እለታዊ የባንክ አገልግሎት ይሰጣል፣ ሆኖም ለወለድ አልባ አገልግሎት ራሱን
በቻለ ልዩ መስኮትና የሰው ኃይል መሆን አለበት፣
18.13. ዩኒየኑ ገንዘብና ንብረትን በአደራ የማስቀመጥ አገልግሎቶች ይሰጣል፣
18.14. የተሰበሰበ የቁጠባ ገንዘብ በሙሉ ህጋዊ በሆነ የፋይናንስ ተቋማት መቀመጥ ይኖርበታል፣
7
18.15. ዩኒየኑ ለወለድ አልባ ሆነ ወለድ ለሚያስገኙ የቁጠባ አገልግሎቶችን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችሉ የተለያዩ የሂሳብ
ሰነዶች፣ መዛግብቶች፣ ካዝናዎች፣ የክፍያ መስኮቶች ያዘጋጃል፣ ይህንን ስራ ማከናወን የሚያስችል የሰው ሀይል
እንዲኖረው ያደርጋል፣
18.16. ዩኒየኑ የቁጠባ መጠን ለማሳደግና እና ለማበረታት ሲባል ለአባላት የተለያዩ ማበረታቻዎችን አዘጋጅቶ መስጠት
ይቻላል፣
18.17. ዩኒየኑ ከአባል መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበራት ጋር በመሆን የፋይናንስ ተጠቃሚ ያልሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎችን
እንደየ አካባቢው ሁኔታ ተስማሚ የሆኑ የቁጠባ አይነቶች በማዘጋጃት ተጠቃሚና ተደራሽ እንዲሆን ያደርጋል፣
18.18. ዩኒየኑ ከላይ ከተገለፀው በተጨማሪ በጠቅላላ ጉባኤ በሚወስነው መሰረት ወለድ የሚያስገኝ እና ወለድ የማያስገኝ
ቁጠባ አገልገሎቶች አሰጣጥ ሊከተል የሚገው ከዚህ በታች የተጠቀሱት ይሆናሉ፤
18.18.1. ወለድ አልባ ቁጠባ ዓይነቶች
1) የሸሪዓ ህግን መሰረት ያደረገ መደበኛ ወዲዓ የድ ደማን ቁጠባ ከአባላቱ ይሰበስባል፣
2) ዩኒየኑ ከመደበኛ ቁጠባ ውጭ በአባሉ ሙሉ ፍላጎት ወለድ አልባ የሆነ የፍላጎት ቁጠባ አገልግሎት
ይሰጣል፤ እነዚህ የወለድ አልባ የቁጠባ አገልግሎቶች ቀርድ ሀሰን፣ ወዲዓ የድ ደማን የመሳሰሉትን
የወለድ አልባ አገልግሎቶች ይሰጣል፣
3) በወለድ አልባ ለተቀመጠ ቁጠባ ወለድ አይጠየቅበትም ወይም ጥቅም አይገኝበትም፣
4) በወለድ አልባ የተሰበሰበ ቁጠባ በፋይናንስ ተቋማት ሲቀመጥ በወለድ አልባ ሂሳብ ውስጥ መሆን
ይኖርበታል፣
5) የወለድ አልባ ቁጠባ አገልግሎት ሲሰጥ ስራውን ለማከናወን የሸሪያ ህግን ጠንቅቀው በሚያውቁ
ባለሙያዎችና ራሱን በቻለ የሂሳብ አሰራር መሆን አለበት፣
6) አባል ኅብረት ሥራ ማህበራት በአንቀጽ 18.3 የተቀመጠ መደበኛ ቁጠባ ውስጥ የወለድ አልባ ቁጠባ
ለይተው ወደ ዩኒየኑ ገቢ ያደርጋሉ፣
13
29.11. የዩኒየኑ የስራ አመራር ቦርድ አባል ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ከደረሰበትና በገዛ ፈቃዱ ለመልቀቅ ከፈለገ የስራ
አመራር ቦርድ መደበኛው ስብሰባ ከመካሄዱ ከ ቀን በፊት በጽሁፍ ማሳወቅ ይኖርበታል፣
29.12. የዩኒየኑ ሊቀ መንበር የአገልግሎት ጊዜውን ሳይጨርስ በገዛ ፈቃዱ አባልነቱን ቢተው የስራ አመራር ቦርድ አባላት
መካከል መርጦ እሰከ ቀጣይ ጠቅላላ ጉባኤ ድረስ መተካት ይችላል፣
29.13. የዩኒየኑ የስራ አመራር ቦርድ ቋሚ መደበኛ ስብሰባ ጊዜ ይኖረዋል፣ ዝርዝሩ በስራ አመራር ቦርድ ውስጠ ደንብ ውስጥ
የሚጠቀስ ይሆናል፣
29.14. የዩኒየኑ የቦርድ አመራር በማናቸውም ሁኔታ ስራቸውን ሲለቁ በስራ በነበሩበት ወቅት ሲሰሩበት የነበረውን ማንኛወንም
ዶክመንት የማስመርምር ግዴታ አለባቸው፣
29.15. በማንኛውም ጊዜ የሚደረግ መደበኛ የስራ አመራር ቦርድ ስብሰባ ከግማሽ በላይ የሆኑ አባላት ከተገኙ ስብሰባው
ሊካሄድ ይችላል፣
29.16. የዩኒየኑ የስራ አመራር ቦርድ የዩኒየኑን የስራ ኃላፊነት በጋራ ይወጣሉ፣
29.17. የስራ አመራር ቦርድ አባላት መካከል ከተመረጡበት ቀጣይ አመት በኋላ አንድ ሶስተኛው የቦርዱ አባላት በአዲስ
አመራር መተካት አለባቸው፣
29.18. የዩኒየኑ የስራ አመራር ቦርድ በአዋጅ፣በመተዳደሪያ ደንብ፣ በጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ ከተሰጠው ስልጣንና ኃላፊነት ውጭ
በሚሰሩት ስራ ምክንያት በዩኒየኑ ላይ በሚደርሰው ኪሳራ ወይም ጥፋት ወይም ጉድለት በጋራ ወይም በግል ተጠያቅ
ይሆናሉ፣
30. የስራ አመራር ቦርድ ስልጣንና ተግባር፣
30.1. የዩኒየኑን ሀብትና እዳ መግለጫ፣ እቅድና በጀት በማዘጋጀት በጠቅላላ ጉባኤ እንዲጸድቅ ያደርጋል፣ ይተገብራል፣
30.2. የዩኒየኑን መተዳደሪያ እና የአሰራርና የአስተዳደር ውስጠ ደንቦችን ያዘጋጃል፣ በጠቅላላ ጉባኤ ያጸድቃል ተግባራዊ
ያደርጋል፣
30.3. የወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎቶች፣ አሰራሮችና የሂሳብ መዛግብቶች ተለይተው እንዲያዙና በአግባቡ እየተከናወኑ
ስለመሆኑ ያረጋግጣል፣
30.4. ግዥን እና ሽያጭን መሰረት ያደረጉ ብድሮች ተግባራዊ እንዲሆኑ አስፈላጊ የሆኑ አሰራሮችን ተግባራዊ
ያደርጋል፣ አፈጻጸሙን ክትትል ያደርጋል፣
30.5. የዩኒየኑ ሂሳብ አያያዝ ዘመናዊ የሂሳብ አያያዝ የተከተለ እንዲሆን አስፈላጊውን ሁሉ ያሟላል፣ አፈጻጸሙን ክትትል
ያደርጋል፣
30.6. አመታዊ የስራ ሪፖርት ያዘጋጃል፣ ለጠቅላላ ጉባኤ ያቀርባል፣ አዳዲስ የቁጠባና ብድር አሰራሮችን ይነድፋል ለጠቅላላ
ጉባኤ አቅርቦ ያስወስናል፣ ተግባራዊ ያደርጋል፣
30.7. ዘመናዊ የሆነ የብድር መረጃ አያያዝ ስርዓት ይዘረጋል፣ የብድር አሰጣጥና አመላለስ ተግባራዊነቱን ይከታተላል፣
30.8. የወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ አሰራሮችን ይቀይሳል፣ በሰውኃይል፣ በአሰራር እና በቁሳቁስ
ያደራጃል፣ አገልግሎት አሰጣጡ ሸሪዓን የተከተለ መሆኑን ያረጋግጣል፣
30.9. የመመዝገቢያ ክፍያ ይሰበስባል፣ እጣን ይሸጣል፣ ቁጠባን ይሰበስባል፣ ተጨማሪ እጣ መሸጥ በሚያስፈግበት ወቅት
በጠቅላላ ጉባኤ አስወስኖ ይሸጣል፣
30.10. የዩኒየኑ የቁጠባና የብድር አስተዳደር መመሪያ ያዘጋጃል፣ ወለድ አልባ አሰራርን ባካተተ ሁኔታ እና ሁሉንም አባላት
14
ተጠቃሚ ሊያደርግ በሚችል መልኩ ያዘጋጃል፣ ያሻሽላል፣ በጠቅላላ ጉባዔ ያጸድቃል፣
30.11. የዩኒየኑን እዳ/ቁጠባ ከካፒታል መሸከም አቅም ጋር የተጣጣመ ስለመሆኑ ያረጋግጣል፣ ክፍተት ካለ የማስተካከያ
እርምጃ ይወስዳል፣
30.12. የገንዘብ እጥረት ሲያጋጥመው በተፈቀደለት እስከ ተፈቀደለት የብድር ጣሪያ ድረስ ከፋይናንስ ተቋማት ብድር
ይበደራል፣ ወቅቱን ጠብቆ ይመልሳል፣
30.13. የወለድ መጠንን ይወስናል፣ በተወሰነው መሰረት ወለድ ይከፍላል፣ ይሰበስባል፣ በብሄራዊ ባንክ የሚደረጉ የወለድ
ለውጥን መሰረት ያደረገ የወለድ ምጣኔ ማስተካከያ ያደርጋል፣
30.14. የአባላት የቁጠባ አቅም እንዲጎለብት የተለያዩ የቁጠባ አይነቶችን ያስፋፋል፣ ማበረታቻዎችን በማዘጋጀት አባላት
እንዲበረታቱ ያደርጋል፣
30.15. የዩኒየኑን የሰው ሀይል አስተዳደር መመሪያ በማዘጋጀት በጠቅላላ ጉባኤ ያጸድቃል፣ የዩኒየኑን አደረጃጀት መዋቅር እና
የሰው ሀይል ብዛት እንዲሁም የክፍያ ሁኔታ ያዘጋጃል፣ በየጊዜው ወቅቱ በሚጠይቀው ሁኔታ ያሻሽላል፣ የጠቅላላ ጉባኤ
ውሳኔ ሲያገኝ ተግባራዊ ያደርጋል፣
30.16. የዩኒየኑ የመረጃ አያያዝ በዘመናዊ የመረጃ አያያዝ ቴክኖሎጂ እንዲደገፍ ያደርጋል፣ ከአባል መሰረታዊ ኅብረት ሥራ
ማኅበራት ጋር በመረጃ መረብ በመገናኘት ዘመናዊ የመረጃ አያያዝ ስርዓት ያደርጋል፣
30.17. የዩኒየኑን ሥራ አስኪያጅ ቅጥር ለጠቅላላ ጉባኤ አቅርቦ ያፀድቃል
30.18. በዩኒየኑ መተዳደሪያ ደንብ መሰረት እና የቁጠባና ብድር መመሪያ መሰረት ይበደራል፣ ያበድራል፣
30.19. በዩኒየኑ እና በአባላት መካከል በሚከሰት አለመግባባት ሲኖር ወደ ሽምግልና ዳኝነት ከመሄዱ በፊት
የሚያግባባ የመፍትሄ ሀሳብ ያፈላልጋል፣
30.20. የተካፉልን ወይም አነስተኛ የመድን ዋስትና አሰራር በዩኒየኑ ውስጥ ተግባራዊ ያደርጋል፣ ለዚህ የሚሆን
መመሪያ ያዘጋጃል፣ በጠቅላላ ጉባኤ ሲጸድቅ ተግባራዊ ያደርጋል፣
30.21. የዩኑየኑን ስብሰባዎች ቃለ ጉባኤ በጽሁፍ ይይዛል፣ መደበኛ እና አስቸኳይ ስብሰባዎን ይጠራል፣ ስብሰባዎችን
ይመራል፣
30.22. የአባልነት ማመልከቻ መርምሮ ውሳኔ ይሰጣል፣ በአባሉ ፈቃድ ከአባልነት የሚሰናበት መሰረታዊ ኅብረት ሥራ
ማህበር ጥያቄ ተቀብሎ ያሰናብታል፣ ግዴታውን ባለመወጣት እና በጥፋት የሚሰናበት አባል መሰረታዊ
ኅብረት ሥራ ማህበር ውሳኔ እንዲሰጥበት ለጠቅላላ ጉባኤ ያቀርባል፣
30.23. የግዥና ሽያጭ አሰራርን ለማከናወን የሚያስችል አሰራር ስርዓት ይቀርጻል፣ ተግባራዊነቱን ይከታተላል፣
30.24. በማንኛውም ጊዜ ዩኒየኑን በሚመለከቱ ጉዳዮች ወክሎ ይቆማል፣ ውሎችን ይዋዋላል፣
30.25. የማይመለስ ብድርን በመለየትና መመለስ የማይቻል መሆኑን በማረጋገጥ ውሳኔ እንዲሰጥበት ለጠቅላላ
ጉባኤ ያቀርባል፣
30.26. በየአመቱ ለማይመለሱ ብድሮች መጠባበቂያ የሚሆን በጀት እንዲመደብ ያደርጋል፣
30.27. ማንኛውም የዩኒየኑን ገቢዎች በዩኒየኑ ደረሰኝ ይሰበስባል፣ አወጣጡ በዩኒየኑ ወጪ ማዘዣ መሆኑን
ይከታተላል፣
30.28. የዩኒየኑ የስራ አመራር ቦርድ አባል ጥፋት አጥፍቶ ሲገኝ ለጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ እንዲሰጥበት ያቀርባል፣
15
የተሻሻለ መተዳደሪያ ደንብ እና የብድር መመሪያ እንዲመዘገብ አግባብ ላለው ባለስልጣን በማቅረብ
30.29.
ያስመዘግባል፣
30.30. በመተዳደሪያ ደንብ እና በሌሎች ውስጠ ደንቦች የተዘረዘሩ ተግባራትንና የጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔዎች
ያስፈጽማል፣
31. የስራ አመራር ቦርድ አባላት ስልጣንና ተግባር
የዩኒየኑ ሊቀመንበር በዩኒየን ጠቅላላ ጉባኤ የሚመረጥ ሆኖ የሚከተሉት ስልጣንና ተግባራት ይኖሩታል፣
31.1.1. የዩኒየኑን የጠቅላላ ጉባኤውንና የስራ አመራር የቦርዱን ስብሰባ ይመራል፣
31.1.3. ለኅብረት
ሥራ ዩኒየኑ አገልግሎት የሚውሉ የብድር እና ሌሎች ውሎችን ከአገር ውስጥና ከውጪ ሀገር
ተቋማት ጋር ይፈራረማል፤
31.1.4. ስለ ኅብረት ሥራ እንቅስቃሴ መግለጫ ይሰጣል፣ ዩንየኑን ይወክላል፤
31.1.7. የዩኒየን ስራ አስኪያጅ ብድርን ለማጽደቅ ከተሰጠው ስልጣን በላይ የሆነውን ብድር ያጸድቃል፣
31.1.8. ለዩኒየኑ ስራ አስኪያጅ እንዲዋዋል ከተሰጠው ኃላፊነት በላይ የሆነውን የውል ስምምነት ይዋዋላል፣
31.1.9. የዩኒየኑ ስራ አስኪያጅ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ እየተወጣ ስለመሆኑ ግምገማ እና ቁጥጥር
ያደርጋል፣
31.1.10. ፍትሃዊ የሰራተኞች አስተዳደር ስርዓት እንዲኖር ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠር ያደርጋል፣ በስራ አስኪያጅና
በቅጥር ሰራተኞች መካከል ያለውን አለመግባባት በሰው ኃይል መመሪያ መሰረት ይፈታል፣
31.1.11. የኅብረት ሥራ ዩኒየኑ ወርሃዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት በሥራ አስኪያጅ በኩል ለሥራ አመራር ቦርድ
እንዲያቀርብ ያደርጋል፡፡
31.1.12. K?KA‹ ›eðLÑ> ¾J’< የኅብረት ሥራ ዩኒየኑን Y^ ‹ ÁŸ“¨“M፡፡
31.2.1. የቦርዱ ም/ሊቀምንበር በጠቅላላ ጉባኤ የሚመረጥ ሲሆን የሊቀመንበሩ ረዳት ሆኖ ያገለግላል፡፡
16
32.5. የቁጥጥር ኮሚቴ ተጠሪነቱ ለጠቅላላ ጉባኤ ነው፣
32.6. ከኮሚቴ አባላት መካከል ስራውን ቢያቆም ከኮሚቴ አባላት መካከል ተክቶ ያሰራል፣
32.7. ከሁለተኛው ምርጫ አመት ጀምሮ አንድ ሶስተኛው የቁጥጥር ኮሚቴ አባላት በአዲስ አባል ተመራጭ በየጊዜው
መተካት አለበት፣
33. የቁጥጥር ኮሚቴ ስልጣንና ተግባር፣
33.1. የቁጥጥር ኮሚቴ በማንኛውም ጊዜ የዩኒየኑ አሰራርና የተለያዩ የሂሳብ ሰነዶችና መዛግብቶችን ይመረምራል፣
ይቆጣጠራል፣
33.2. የዩኒየኑ የቁጠባና ብድር አሰራር በዩኒየኑ መተዳደሪያ ደንብና የውስጥ የቁጠበና ብድር መመሪያ መሰረት መከናወኑን
ያረጋግጣል፣
33.3. የወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎት በአግባቡ እየተሰጠ ስለመሆኑ ያረጋግጣል፣
33.4. ዩኒየኑ የሰው ሀይል አመራር በሰው ሀይል አስተዳደር መመሪያ መሰረት እየተከናወነ ስለመሆኑ ያረጋግጣል፣
33.5. የውስጥ ቁጥጥር አሰራርን ተግባራዊ ያደርጋል፣ ለስራው የሚያስፈልገውን የሰው ሀይልና በጀት በጠቅላላ ጉባኤ
አስወስኖ ተግባራዊ ያደርጋል፣
33.6. የፋይናንስ አፈጻጸም መለኪያዎች ተግባራዊ እንዲሆን ከስራ አመራር ቦርድ ጋር በመሆን ይሰራል፣ ዩኒየኑ ያለበትን ደረጃ
ገምግሞ ለጠቅላላ ጉባኤ ያቀርባል፣
33.7. ከስራ አመራር ቦርድ ጋር በመሆን ኦዲት እንዲደረግ ያደርጋል፣ የኦዲት ግኝቶችና የተሰጡ አስተያየቶች ተግባራዊ
ስለመሆናቸው ክትትል ያደርጋል፣
33.8. በስራ አመራር ቦርድ ስብሰባ ላይ በድምጽ አልባነት ይገኛል፣ የቦርዱ ስብሰባ ህግን በተከተለና ዲሞክራሲያዊ በሆነ
መልኩ መከናወኑን ይታዘባል፣ ውሳኔዎች ተግባራዊ መሆናቸውን ያረጋግጣል፣ በስራ ምክንያት የተከሰቱ ችግሮች
እንዲታረሙ ለቦርዱ አስተያየት ይሰጣል፣
33.9. የጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔዎች ተግባራዊ መሆናቸውን ይከታተላል፣
33.10. የቁጥጥር ኮሚቴ የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ለጠቅላላ ጉባኤ ያቀርባል፣ የስራ እቅድና በጀት አዘጋጅቶ ለጠቅላላ ጉባኤ
ያቀርባል፣ ሲፈቀድለት ተግባራዊ ያድርጋል፣
33.11. የዩኒየኑ ቅጥር ሰራተኞች ኃለፊነታቸውን በአግባቡ ስለመወጣታቸው ክትትል ያደርጋል፣ የተከሰቱ ግድፈቶች እንዲታረሙ
ለስራ አመራር ቦርድ ሪፖርት ያደርጋል፣
33.12. ሌሎች በጠቅላላ ጉባኤ የሚወሰኑ ውሳኔዎች ተግባራዊ ያደርጋል፣
34. ሌሎች ንዑሳን ኮሚቴዎች በተመለከተ፣
34.1. የስራ አመራር ቦርድ ለስራው አስፈላጊ የሆኑ የተለያዩ ንዑሳን ኮሚቴዎችን ይሰይማል፣ዩኒየኑ የሚከተሉት ኮሚቴዎች
እንዳስፈላጊነቱ ይኖሩታል፣
34.1.1. የብድር ኮሚቴ
34.1.2. የወለድ አልባ የፋይናንስ አገልግሎት ክትትል ኮሚቴ
34.1.3. የግዥ ኮሚቴ
34.1.4. የንብረት አስተዳደርና የሽያጭ ኮሚቴ
34.1.5. የቁጠባ፣ የትምህርት እና ቅስቀሳ ኮሚቴ
34.2. ኮሚቴዎቹ ከሶስት ያላነሱ አባላት ይኖራቸዋል፣ የየራሳቸው ሰብሳቢ፣ ጸሀፊና አባል ይኖራቸዋል፣
17
34.3. ኮሚቴዎቹ ተጠሪነታቸው ለስራ አመራር ቦርድ ነው፣ የስራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን እንዲሁም እቅድና በጀት ለስራ
አመራር ቦርድ ያቀርባሉ፣ ያጸድቃሉ፣ ተግባራዊ ያደርጋሉ፣
34.4. ዝርዝር ተግባር አፈጻጸማቸው ዩኒየኑ በሚያዘጋጀው የውስጥ አሰራር ደንብ ውስጥ የሚገለጽ ይሆናል፣
34.5. የኮሚቴዎቹ የስራ ዘመን የስራ አመራሩ ቦርድ የስራ ዘመን ይሆናል፣
35. የዩኒየን ቅጥር ሰራተኞች
35.1. ዩኒየኑ የሰው ሀይል አስተዳደር መመሪያ እና በጠቅላላ ጉባኤ የጸደቀ አደረጃጀት እና መዋቅር ይኖረዋል፣
35.2. ዩኒየኑ የዕለት ተዕለት ስራውን የሚያከናውኑለት ቅጥር ሰራተኞች ይኖሩታል፣
35.3. ቅጥር ሰራተኞች በዩኒየኑ ሰው ሀይል አስተዳደር መመሪያና አግባብ ባለው አካል በሚያወጣው መመሪያ መሰረት
የሚተዳደሩ ይሆናል፣
35.4. የቅጥር ሰራተኞችን የሚመራና ዩኒየኑን በኃላፊነት የሚያስተዳድር ስራ አስኪያጅ ይኖረዋል፣
35.5. የዩኒየኑ ስራ አስኪያጅ ወይም ቅጥር ሰራተኛ ሲቀጠር አግባብ ባለው ባለስልጣን በሚያወጣው የሀብት ማስመዝገቢያ
ቅጽ መሰረት የተቀጣሪው የግል ንብረት እና ሀብት መረጃ መዝግቦ አስፈርሞ ይይዛል፣
36. የዩኒየኑ ሥራ አስኪያጅ ተግባርና ኃላፊነት
ዪኒየኑ ተጠሪነቱም ለስራ አመራር ቦርድ የሆነ ስራ አስኪያጅ ይኖረዋል፣ሥራ አስኪያጁ የሚከተሉት ተግባርና ኃላፊነት ይኖሩታል፣
36.1. የዩንየኑን የዕለት ተዕለት የሥራ እንቅስቃሴ በኃላፊነት ይመራል፣
36.2. የዩንየኑን ዓመታዊ የሥራ ዕቅድ እና በጀት በማዘጋጀት ለሥራ አመራር ቦርዱ ያቀርባል ሲፈቀድም ተግባራዊ ያደርጋል፣
36.3. የዩኒየኑ ተቀጣሪ ሰራተኞች በሰው ሀይል አደረጃጃትና አስተዳደር መመሪያ እና አግባብ ባለው አካል በሚያወጣው
መመሪያ መሰረት ይቀጥራል፣ ያስተዳድራል፣
36.4. ለሰራተኞች የሥራ ዝርዝር ያዘጋጃል፤የሥራ አፈፃጸማቸውን ይገመግማል፤የሰራተኛ ቅጥርና ስንብት ሀሳብ በማዘጋጀት
ለውሳኔ ለስራ አመራር ቦርድ ያቀርባል፡፡ ሲፀድቅለትም ተግባራዊ ያደርጋል፡፡
36.5. በዩኒየኑ ሥራ አመራር ቦርድ ሊቀመንበር የሚፀድቁ የብድር ውሎችን በማረጋገጥና በሰነዶች ላይ በመፈረም
ወጪዎችን ያፀድቃል፤ ክፍያ እንዲፈፅምም ለሂሳብ ክፍል በደብዳቤ ትዕዛዝ ይሰጣል፤
36.6. እስከ ብር የሆኑ የሂሳብ ወጪዎችን ከፋይናንስ ሃላፊና ከገንዘብ ያዥ ጋር በመሆን በጣምራ በቼክ ላይ
ይፈርማል፡፡ ሂሳቡን ያጸድቃል፣
36.7. እስከ ብር ለአባላት የሚሰጡ ብድሮችን በፊርማ ያፀድቃል፡፡ አመላለሱን ይከታተላል፣
36.8. እስከ ብር የሆኑ የሥራ ማስኪያጃ ወጪዎችን ይፈቅዳል፤ ያጸድቃል፣
36.9. እስከ ብር የሚደርሱ ውሎችን በስራ አመራሩ ቦርድ ሲፈቀድለት ይዋዋላል፣ አፈጻጸሙን
ይከታተላል፣ ሪፖርት ለቦርድ ያቀርባል፣
36.10. በዩንየኑ የሥራ አመራር ቦርድ ስብሰባዎች ላይ ይገኛል፤ወቅታዊ ሪፖርት ያቀርባል፤አስተያየት እና መረጃ ይሰጣል፣
ድምፅ አይሰጥም፣
36.11. የዩኒየኑን የጠቅላላ ጉባኤ እና የሥራ አመራር ቦርድ ስብሰባ ቃለ ጉባኤ ይይዛል፤
36.12. የዩኒየኑን የስብሰባዎች ጊዜ ለጠቅላላ ጉባኤ እና ለቦርዱ አባላት በወቅቱ ያሳውቃል፤
36.13. የጠቅላላ ጉባኤ እና የስራ አመራር ቦርድ አጀንዳዎችን ከሊቀመንበሩ ወይም ምክትል ሊቀ መንበር ጋር በመሆን
ያዘጋጃል፣
36.14. የዩኒየኑን ጽህፈት ቤት ያደረጃል፣ ዘመናዊ የመረጃ አያያዝ እንዲፈጠር ያደርጋል፣
18
36.15. ቢሮዎች ለስራ ምቹ እንዲሆኑ ያደርጋል፣ የገቢና የወጪ ደብዳቤዎችን አሰራርን ስርዓት ይዘረጋል፣
36.16. የአባላትን መረጃዎችና ፋይሎች በተገቢው ሁኔታ በማደራጀት ይይዛል፤
36.17. ሌሎች ከሥራ አመራር ቦርድ እና ቁጥጥር ኮሚቴ የሚሰጡትን ተግባራት ያከናውናል፤
36.18. ሸሪዓ መር የቁጠባና ብድር አገልግሎቶች እንዲሁም የመድን ዋስትና ወይም ተካፉል አገልግሎቶችን ይተገብራል፡፡
37. ዩኒየኑ የስብሰባ ሥነሥርዓት፣
37.1. ዩኒየኑ መደበኛ ወይም አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ይኖሩታል፣
37.2. የዩኒየኑ ጠቅላላ ጉባኤ በአመት ሁለት ጊዜ ይደረጋል፣ ስብሰባውም በሚከተሉት ወቅቶች የጠቅላላ ጉባኤ ይደርጋል፣
37.2.1. የመጀመሪያው ጠቅላላ ጉባኤ ይደረጋል፣
37.2.2. ሁለተኛው ጠቅላላ ጉባኤ ይደረጋል፣
37.3. የዩኒየኑ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ከመካሄዱ በፊት ቢያንስ በ ቀናት ጊዜ ውስጥ የመወያያ ርዕስ፣
የስብሰባ ቀን፣ ቦታና ሰዓት በጥሪ ደብዳቤው ላይ ተጠቅሶ ለሁሉም አባላት የስብሰባ ጥሪው እንዲደርሳቸው ይደርጋል፣
ሆኖም የጥሪ ጉባኤው ከመካሄዱ በፊት ባሉ 15 ቀናት ውስጥ ለአባላት መድረስ አለበት፣
37.4. የዩኒየኑ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ካሉት አባላት ውስጥ ከግማሽ በላይ ሲገኙ ምልዓተ ጉባኤ ይሆናል፣
37.5. መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቶ ምልዓተ ጉባኤ ካልተሟላ ቀናት ውስጥ ሁለተኛ ጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ
ይደረጋል፣
37.6. ለሁለተኛ ጊዜ የተጠራው መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ምልዓተ ጉባኤው ካልተሟላ በእለቱ በተገኙ አባላት መደበኛ ጠቅላላ
ጉባኤ ሊካሄድ ይችላል፣
37.7. በአንቀጽ 37.6 መሰረተ ምልዓት ጉባኤው ሳይሟላ የተካሄደ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የሚያሳልፋቸው ውሳኔዎች ሁሉም
የጉባኤው አባላት በተገኙበት እንደተላለፈ ሆኖ ይቆጠራል፣
37.8. የዩኒየኑ ስራ አመራር ቦርድ ወይም የቁጥጥር ኮሚቴ ወይም ከጠቅላላ አባላት ውስጥ ከአንድ ሶስተኛ ያላነሱ አባላት
አስቸኳይ ስብሰባ እንዲጠራላቸው ሲጠይቁ የኅብረት ሥራ ዩኒየኑ ስራ አመራር ቦርድ በ
ቀናት ውስጥ ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ ያደርጋል፣
37.9. ለሁለተኛ ጊዜ የተጠራው አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ምልዓተ ጉባኤ ካልተሟላ የስራ አመራር ቦርድ አግባብ ላለው
ባለስልጣን በሪፖርት ያሳውቃል፣
37.10. የስራ አመራር ቦርድ በቀረበለት ጥያቄ መሰረት አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤው ካልጠራ የዩኒየኑ አባላት ወይም የቁጥጥር
ኮሚቴ አግባብ ባለው ባለስልጣን አስቸኳይ የጠቅላላ ጉባኤ እንዲጠራላቸው መጠየቅ ይችላሉ፣
37.11. ከጠቅላላ አባላት ውስጥ ሁለት ሶስተኛ አባላት የተገኙበት አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ምልዓተ ጉባኤ ይሆናል፣
37.12. የስራ አመራር ቦርድና የቁጥጥር ኮሚቴ የራሳቸው መደበኛና አስቸኳይ ስብሰባ ይኖራቸዋል፣ ዝርዝር አሰራሩ በስራ
አመራር ቦርድ ወይም ቁጥጥር ኮሚቴ ውስጠ ደንብ የሚገለጽ ነው፣
38. የኮሚቴ አባላት እገዳና ስንብት
38.1. የዩኒኑ የስራ አመራር ቦርድ፣ የቁጥጥር እና ሌሎች ንዑሳን ኮሚቴ አባል የሆነ ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ሲያጋጥመው
ከአመራርነት ለመሰናበት ከፈለገ ለስራ አመራር ቦርድ ወይም ለቁጥጥር ኮሚቴ ማመልከቻ ማቅረብ ይኖርበታል፣
38.2. የስራ አመራር ቦርድ ወይም የቁጥጥር ኮሚቴ ጥያቄው በቀረበ በ ¬¬¬¬¬¬ቀናት ውስጥ በጽሁፍ መልስ መስጠት
ይኖርበታል፣
38.3. የስራ አመራር ቦርድ ወይም የቁጥጥር ኮሚቴ ተመራጭ ከዩኒየኑ ደንብና ህግን የሚጻረር ድርጊት ከፈጸመ ተጠሪ
19
በሆነበት የስራ አመራር ቦርድ ወይም ቁጥጥር ኮሚቴ አማካኝነት ከስራው ይታገዳል፣
38.4. የታገደው አመራር የታገደበት ምክንያት በጽሁፍ እንዲያውቀው በማድረግ ለጠቅላላ ጉባኤ ቀርቦ ውሳኔ እንዲሰጠው
ይደረጋል፣
38.5. አንድ አመራር ለ ተከታታይ የዩኒየኑ ስራዎችና ስብሰባዎች እንዲገኝ ጥሪ ተደርጎለት ያለበቂ ምክንያት
ካልተገኘ ከአመራርነቱ እንዲሰናበት ተደርጎ ለጠቅላላ ጉባኤ እንዲወሰንበት ይቀርባል፣
39. ድርሻና ጥቅምን ስለማስከበር፣ ስለማቻቻልና ስለማስተላለፍ፣
39.1. አንድ አባል መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበር በአንቀጽ 21.1፣ 21.16 እና 21.17 የዩኒየኑ አባልነት የሚሰናበት ከሆነ
በዩኒየኑ የሚኖረውን ድርሻና ጥቅም የሚከፈለው በዩኒየኑ ያለበት እዳ ከተቀነሰ በኋላ የሚቀረው ብቻ ነው፣
39.2. አንድ አባል ዩኒየኑ ውስጥ ያለው ጥቅሙ ወይም ድርሻ ከዩኒየኑ ውጭ ላለበት እዳ ወይም ተጠያቂነት ሊከበር፣ ሊያዝ፣
ሊሸጥ አይችልም፣
39.3. ዩኒየኑ ከአባሉ ላይ ለሚፈልገው እዳ የአባሉን ድርሻ እና ሌሎች ጥቅሞች ወይም ካለው የቁጠባ ገንዘብ ላይ በመቀነስ
እዳውን ያቻችላል፣
39.4. የአባሉ እዳ ከሚቻቻለው የእጣ እና ጥቅም ወይም ቁጠባ በላይ የበለጠ ከሆነ በስራ አመራር ቦርድ አማካኝነት
ለጠቅላላ ጉባኤ ቀርቦ ውሳኔ ይሰጥበታል፣
39.5. ዩኒየኑ አባል ኅብረት ሥራ ማህበራት ድርሻና ጥቅም የማስተላለፍ ስራ አይሰራም፣
ለማካካስ እንዲቻል ዩኒየኑ በውል የተመሰረተ ስምምነት ከኅብረት ሥራ ማህበር በማድረግ አነስተኛ የመድን
ዋስትና ወይም ተካፉል አገልግሎት ይሰጣል፣
43.3. የአነስተኛ መድን ዋስትና አገልግሎት ወለድ ለሚሰጣቸው አባላት የሚሰጥ ሲሆን የተካፉል አገልግሎት
ይቀመጣል፣
43.7. ለአረቦን ከተሰበሰበ ገንዘብ ውስጥ የካሳ ክፍያ ተከፍሎ ከቀረው ገንዘብ ውስጥ
መመሪያ መሰረት ተግባራዊ ይሆናል፤ ቀሪው ገንዘብ በገቢነት ተይዞ ወደ ትርፍ ክፍፍል ይሄዳል፣
43.9. ሁሉም የዩኒየኑ አባላት ለአባሎቻቸው ብድር የሚሰጡ ከሆነ አባሎች መድን ዋስትና መግባት ይኖርባቸዋል፣
43.10. ከተካፉል አገልገሎት ተጠቃሚዎች የሚሰበሰብ ገንዘብ የጉዳት ማካካሻ ተከፍሎ የሚቀረው ገንዘብ
44.1. ዩኒየኑ ንብረቱን ከተለያየ አደጋ ለመጠበቅ እንዲችል የመድን ዋስትና ሊገባ ይችላል፡፡
46.1. አዋጅን፣ ደንብን ፣ መመሪያንና የጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔን ያላከበረ አባል ቅጣት ይቀጣል፣ የሥራ አመራር
ቦርዱም የጥፋቱን ክብደትና ቅለት በመመርመር የቅጣት ውሳኔ ይሰጣል፣ በውሳኔው ያልተስማማ አባል
ጉዳዩ በእርቅ ወይም በሽምግልና ዳኝነት እንዲታይ ማድረግ ይችላል፣
46.2. ከተቀጣ አባል የሚሰበሰብ ገቢ ለአባላት የማይከፋፈል ወይም ሌላ ጥቅም የማይገኝበት ሲሆን ለኅብረት
ሥራ ማህበራት ዩኒየኑ ስራ ማስኬጃነት ይውላል፡፡
46.3. የኅብረት ሥራ ዩኒየኑ ለሚሰጠው ልዩ ልዩ አገልግሎት በኅብረት ሥራ ዩኒየኑ ውስጠ ደንብ መሰረት አገልግሎት ክፍያ
ሊሰበስብ ይችላል፣
47. የአበልና ሌሎች ክፍያዎች
47.1. ለስራ አመራር ቦርድና ሌሎች የኮሚቴ አመራሮች እንዲሁም ለቅጥር ሰራተኞች የሚከፈል አበል በፋይናንስ አስተዳደር
ውስጠ መመሪያ መሰረት ይሆናል፣
47.2. የአበልና ሌሎች ክፍያዎች ተመን የጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ ማግኘት ያስፈልጋል፣
48. የዩኒየኑ መዛግብትና የሂሳብ ሰነዶች፣
48.1. ዩኒየኑ ለስራ አስፈላጊ የሆኑ መዛግብቶችና ሰነዶች ይኖሩታል፣ ዝርዝሩ በውስጠ ደንብ እና በፋይናንስ አስተዳደር
መመሪያ ይቀመጣል፣
49. የዩኒየኑ የገንዘብ ምንጭ፣
23
49.1. የመመዝገቢያ ክፍያ፣
49.2. ከአባላት የሚሰበሰብ ዕጣ ክፍያ
49.3. ከትርፍ ላይ ተቀንሶ የሚቀመጥ መጠባበቂያ
49.4. ከተለያዩ አካላት የሚሰጡ ስጦታዎች፣
49.5. ከአባሉ የሚሰበሰብ ቁጠባ
49.6. ከውጭ አካላት የሚገኙ የተለያዩ ብድሮች
49.7. ከጥቃቅን ሽያጭ የሚገኝ ገቢ
49.8. ከወለድ የሚገኝ ገቢ
49.9. ከቅጣት የሚገኝ ገቢ፣
49.10. ሌሎች ገቢዎችን ያካትታል፣
50. የተጣራ ትርፍ ክፍፍል፣
50.1. ከዩኒየኑ የተጣራ ትርፍ ውስጥ 30 በመቶ እየተቀነሰ የካፒታሉን 30 በመቶ እስከሚደርስ ድረስ ዩኒየኑ በሚከፍተው
ቁጠባ ሂሳብ ተቀማጭ ይሆናል፣
50.2. የዩኒየኑ መጠባበቂያ ካፒታል የሚፈለገውን መጠን ከደረሰ በኋላ የተጣራ ትርፍ ሙሉ በሙሉ ለትርፍ ክፍፍል ይውላል፣
ሆኖም ህግ በሚያዘው መሰረት ለኅብረት ሥራ ፈንድ የሚሆን ገንዘብ ተቀናሽ መሆን ይኖርበታል፣
50.3. የዩኒየኑ መጠባበቂያ ሂሳብ በሚፈለገው ደረጃ መገኘቱን ትርፍ ክፍፍል ከመደረጉ በፊት በኦዲተር መረጋገጥ
ይኖርበታል፣ ሆኖም የመጠባበቂያው ሂሳብ በአንቀጽ 50.1 ከተጠቀሰው በታች ከሆነ የመጠባበቂያ ሂሳቡ በሚፈለገው
ደረጃ እስከሚደርስ ድረስ ከትርፉ እየቀነሰ በመጠባበቂያ ሂሳብ ውስጥ ያስቀምጣል፣
50.4. በአንቀጽ 50.1 የተጠቀሰው ሂሳብ ከተቀነሰ በኋላ ቀሪው 70 በመቶ ትርፍ በየአመቱ በጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ የሚደለደል
ሆኖ የትርፍ ክፍፍል ድልድሉም እንደሚከተለው በመቶኛ ይሆናል፣
50.4.1. ለእጣና አባላት ካፒታል
50.4.2. ለአባላት ቁጠባ
50.4.3. ለብድር አመላለስ
50.4.4. ለትምህርትና ስልጠና
50.4.5. ለማህበራዊ አገልግሎት
50.4.6. ለኅብረት ሥራ ፈንድ ተከፋይ
50.4.7. ለተለያዩ ማበረታቻዎች
50.5. አባላት ካገኙት ዓመታዊ ትርፍ ክፍፍል ተጨማሪ እጣ ሊገዙ ይችላሉ፣
50.6. የመጠባበቂያ ገንዘብ ወጪ የሚሆነው፣
50.6.1. ዩኒየኑ ኪሳራ በሚደርስበት ጊዜ ለኪሳራ ማካካሻ ለማዋል፣
50.6.2. ዩኒየኑ የፋይናንስ እጥረት ሲያጋጥመው አግባብ ያለው ባለስልጣን በማስፈቀድ ለአጭር ጊዜ ለሆኑ ስራዎች
ማዋል ይቻላል፣
51. ስለማይከፋፈል የዩኒየኑ የጋራ ንብረቶች፣
51.1. በአንቀጽ 50.1 የተገለጸው የመጠባበቂያ ገንዘብ ለአባላት አይከፋፈልም፣
51.2. ዩኒየኑ በስጦታ፣ በሽልማት ያገኛቸው ንብረቶች የዩኒየኑ የወል ንብረት ይሆናል፣
24
51.3. ለመጠባበቂያ የተመደበው ሂሳብ ለብድር አገልግሎት እና ለብድር ዋስትና አይውሉም፣
58.1. በዩኒየኑ ውስጥ ለሚነሱ አለመግባባት በስራ አመራር ቦርድ ወይም በጠቅላላ ጉባኤ ታይቶ ውሳኔ ሊያገኝ
ይችላል ፡፡
58.2. በዚህ መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ 58.1 ውሳኔ ያላገኘ አለመግባባት በዕርቅ ወይም በሽምግልና ዳኝነት ማለቅ
ይችላል፣በዕርቅ ወይም በሽምግልና ዳኝነት የሚታዩ አለመግባባት በአዋጁ መሰረት ተፈጻሚ ይሆናሉ፣
59. ስለ ኅብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየኑ መፍረስ፣
59.4. በሂሳብ ምርመራ ውጤት መሰረት ዩኒየኑ የከሰረና የኪሳራው መጠን ህልውናን የሚያሰጣ መሆኑን አግባብ
60.1. የዩኒየኑ እንዲፈርስ ሲወሰን አግባብ ያለው ባለስልጣን በዩኒየኑ ወጪ ሂሳብ አጣሪ ይመድባል፣
60.3. የገንዘብ ጠያቂዎች መብት መጠበቁ ከተረጋገጠ በኋላ የዩኒየኑ ቀሪ ንብረት ለአባላት ባላቸው ዕጣ መሰረት
ይከፋፈላል፣
60.4. ለዩኒየኑ የተሰጠውን የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምዝገባ ምስክር ወረቀት አግባብ ላለው ባለስልጣን
ተመላሽ ያደርጋል፣ የምዝገባ ምስክር ወረቀት ከተመለሰበት ቀን ጀምሮ የዩኒየኑ ህጋዊ ሰውነት አይኖረውም፣
ቆጣቢ በሆነ መንገድ የዩኒየኑን ዕድገት ማምጣት እስከቻሉ ድረስ ላከናወኑት ተግባር ከዓመቱ ትርፍ ማትጊያ
በጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ መሠረት ሊከፈላቸው ይችላል፡፡
61.2. ዩኒየኑ አመራር አባላትና የቅጥር ሠራተኞች የመልካም ሥራ ውጤት ማትጊያ የሚፈጸመው አግባብ ያለው
27
አካል በሚያወጠው መመሪያ እና በዩኒየኑ የሰው ኃይል አስተዳደር መመሪያ መሰረት የሚፈጸም ይሆናል፣
62. የውስጥ ደንብ ስለማውጣት፣
62.1. የሥራ አመራር ቦርድና የቁጥጥር ኮሚቴ በዚህ መተዳዳሪያ ደንብ መሰረት የውስጥ ደንብ አዘጋጅተው
በጠቅላላ ጉባኤ ፀድቆ ለ ክልል ኅብረት ሥራ ልማት ኤጀንሲ ቀርቦ ከተመዘገበና የክልሉ
የኤጀንሲው ማህተም ተደርጎ ከተላከ በኋላ ሥራ ላይ ያውላሉ፣
63. ስለ ደንብ ትርጓሜ፣
63.1. በዚህ መተዳደሪያ ደንብ ውስጥ አሻሚ የሆኑ ወይም ማብራሪያ የሚፈልጉ ወይም ክርክር የሚያስነሱ ቃላቶች
ከተፈጠሩ በጠቅላላ ጉባኤ የሚሰጠው ትርጓሜ የመጨረሻ ይሆናል፣
64. ልዩ ውሳኔ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች፣
64.1. በአባላቱ ላይ አስገዳጅነት እንዲኖረው የሚያስፈልገው ልዩ ውሳኔ ከኅብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየኑ ጠቅላላ
65.2. በመተዳደሪያ ደንቡ ላይ የተደረገ መሻሻልና የዩኒየኑ ጠቅላላ ጉባኤ የተላለፈ ውሳኔ በሶስት ኮፒ ተዘጋጅቶ
ውሳኔ ከተላለፈበት ጊዜ በ30 ቀን ውስጥ ለ……………….ክልል ኅብረት ሥራ ልማት ኤጀንሲ ቀርቦ
ከተገመገመ በኋላ ተመዝግቦ የክልሉ ሕጋዊ ማህተም ተደርጎ ከተላከ በኋላ ሥራ ላይ ይውላል፡፡
66.1. ይህ መተዳደሪያ ደንብ በኅብረት ሥራ ማህበራት ዩኒየኑ ጠቅላላ ጉባኤ ፀድቆ አግባብ ባለው አካል ቀርቦ
ከተመዝገበበት ቀን ዓ/ም ጀምሮ የፀናይሆናል፡፡
28