Professional Documents
Culture Documents
8 Module
8 Module
ሱር ታክስ ማለት በአንድ ሀገር ውስጥ የመንግሥት የፋይናንስ ድጋፍ የሚሹ ጉዳዮች ሲከሰቱ በተወሰኑ
ሸቀጦች ወይም የኅብረተሰብ ክፍሎች ላይ በጊዜያዊነት የሚጣል ታክስ ዓይነት ነው፡፡ መንግሥት ሱር
ታክስን ለመጣል ከሚገደድባቸው ሁኔታዎች መካከል የሀገር ሉአላዊነት አደጋ ላይ ሲወድቅ፣ የተፈጥሮና
ሰው ሰራሽ አደጋዎች ሲከሰቱ፣ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኘው የኅብረተሰብ ክፍል የመንግሥትን
ቀጥተኛ ድጎማ የሚፈልግበት ሁኔታ ሲከሰት እና ለመሳሰሉት ወጪ መሸፈኛ የሚሆን ገንዘብ
ለማሰባሰብና በሀገር የሚመረቱ ዕቃዎችን በሀገር ውስጥ የበለጠ ተወዳዳሪ የሚሆኑበትን ሁኔታ ለመፍጠር
እና የመሳሰሉት ይገኙበታል ፡፡
በሀገራችን ሱር ታክስ ከጥር ወር 1993 ዓ.ም. እንዲሁም በመቀጠል ከውጭ ዕቃዎች ቀረጥና ታክስ /ቡና
የነበረው የቡና ቀረጥና ታክስ በዓለም የቡና ገበያ መውደቅ ምክንያት ከ 1994 በጀት ዓመት ጀምሮ
ላልተወሰነ ጊዜ ተነስቶ ነበር ፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ታክሱ በአሁኑ ጊዜ ግን ወደ ሀገር በሚገቡ ዕቃዎች ላይ ስለተጣለ ተጨማሪ ቀረጥ
የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 133/1999 ዓ.ም በተደነገገው መሠረት ታክሱ እየተሰበሰበ
የሚገኝ ሲሆን ስለዚህ ታክስ አስተዳደር ሥርዓት የታክስ ከፋይም ሆኑ ሌሎች የማህበረሰብ አባላት
ግንዘቤ ለማስያዝ ይቻል ዘንድ ይህ ሰነድ ተዘጋጅቶ ቀርቧል ፡፡
1
ክፍል አንድ
አጠቃላይ
1.1 ዓላማ
ዋና ዓለማ
የተጨማሪ ቀረጥ ወይም ሱር ታክስ ደንብ ቁጥር 133/1999 ዓ.ም የአሠራር ሥርዓት ላይ አገልግሎት
ሰጪውም ሆነ ተቀባዩ ስለ የሱር ታክስን ምንነት እና ስለታክሱ አስተዳደር ሥርዓት ላይ የጋራ ዕውቀትና
መግባባት በመያዝ ታክሱ እንደሚከፈል እንዲያውቁት ነው ፡፡
ዝርዝር ዓላማዎቹ
ሠልጣኞች ፡
የሱር ታክስ ቀረጥ ጽንሰ ሃሳብን ይረዳሉ ፡፡
የሱር ታክስ የሚከፈልባቸውን እና ከታክሱ ነጻ የሆኑትን የገቢ ዕቃዎች በመለየት ግዴታቸውን
ይወጣሉ ፡፡
የሱር ታክስ የሥሌት መሰረትና መጣኔውን ይረዳሉ ፡፡
1.2. ውጤት
ተገልጋዮች የሱር ታክስ የህግ ድንጋጌዎችን ላይ ግንዘቤ ፈጥሮ ታክሱን አስልቶ ይከፍላሉ፡፡
1.3.ወሰን
1.3.1. ሽፋን
ስለሱር ታክስ / ተጨማሪ ቀረጥ ለማስከፈል የወጣ የሚኒስተሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 133/ 1999 እና
በተዋሀዶ የሸቀጦች አሰያየምና አመዳደብ ሥርዓት ዓለም አቀፍ ኮንቬሽን ማፅደቂያ አዋጅ ቁጥር
ታክስ ከፋዮች ፤ የንግድ ድርጅቶች የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እና ሌሎች ተገልጋዮች ይሆናሉ ፡፡
2
2.1. ሱር ታክስ ማስከፈያ ልክ ( መጣኔ )
ለሚከፈለው ሱር ታክስ ( ተጨማሪ ቀረጥ) የስሌት መሰረት የገቢ ዕቃው ዋጋ፣ የመድን አረቦን እና
የማስጫኛ ወጪ (Cost , Insurance and Transport) እንዲሁም በዕቃው ላይ ሊከፈል የሚገባው
የጉምሩክ ቀረጥ የኤክሣይዝ ታክስ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ ድምር ውጤት ይሆናል፡፡ ይህም ማለት
የገቢው ዕቃ የጉምሩክ ዋጋ ሲደመር የዕቃው የጉምሩክ ቀረጥ ሲደመር የዕቃው ኤክሳይሰዝ ታክስ
ሲደመር የተጨማሪ እሴት ታክስ ጠቅላላ ድምር ሲበዛ 10 % (አስር በመቶ) ይሆናል በእቃው ላይ
የሚከፈል ሱር ታክስ ይሆናል ማለት ነው ፡፡
የሙከራ ጥያቄዎች ፤
በሕግ ያ ወይም መንግሥት ባደረገው ስምምነት ከጉምሩክ ቀረጥ ነጻ የተደረጉ ሰዎች እና ድርጅቶች
የሚያስመጧቸው ዕቃዎች ሲሆኑ የሚከተሉትን ይጨምራል፤
የመሬት ማዳበሪያዎች፣
የካፒታል (የኢንቨስትመንት) ዕቃዎች ሲሆን የገንዘብ ሚኒስቴር በደንቡ ከተጨማሪ ቀረጥ ነጻ ሆነው
ወደ አገር እንዲገቡ የተፈቀደውን ዕቃዎች ዝርዝር ሊጨምር ወይም ሊቀንስ እንዲሁም ለዚህ
ደንብ አፈጻፀም የሚያግዙ መመሪያዎችን ሊያወጣ ይችላል
3
የሙከራ ጥያቄ
ማጣቀሻ ፡
ወደ ሀገር በሚገቡ ዕቃዎች ላይ ስለተጣለ ተጨማሪ ቀረጥ የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር
133/1999 ዓ.ም እና ሌሎች ሁለተኛ ደረጃ የመረጃ ምንጮች