Professional Documents
Culture Documents
5-2006
5-2006
ባህር ዳር
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኢንዱስትሪ እና ከተማ ልማት ቢሮ የከተማ ቦታን ለአጭር ጊዜ በሊዝ ወይም
በኪራይ ውል ለተጠቃሚዎች ለመፍቀድ ተሻሽሎ የወጣ የአፈፃፀም መመሪያ
0
በዝቅተኛ ካፒታል የንግድ እንቅስቃሴ በማድረግ ራሳቸውን ለመቻል የሚጥሩ ዜጎችን መሬት የማግኘት ዕድል
በማስፋት ከህገ-ወጥ አሰራር ወጥተው ወደ ህጋዊ ስርዓት በመምጣት ለኢኮኖሚው ማደግ የበኩላቸውን
አስተዋጽኦ ማበርከት እንዲችሉ በማገዝ በከተሞች ውስጥ የተንሰራፋውን ድህነት መዋጋት በማስፈለጉ፤
በክልላችን ከተሞች ለሚኖሩ ዜጐች ሰፊ የስራ ዕድል በመፍጠር የህዝባችንን ገቢ በማሻሻል ድህነትን በመቀነስ
ተወዳዳሪና ቀጣይነት ያለው ፈጣን ልማት ለማስመዝገብና ከመሬት የሚገኘውን ሀብት ማሳደግ በማስፈለጉ፤
ከተሞች በአስተዳደር ወሰናቸው ውስጥ ያለውን ክፍት ቦታ በቋሚነት ልማት ላይ እስኪውል ድረስ በጊዜያዊ የሊዝ
ወይም የኪራይ ውል ለተጠቃሚዎች ተሰጥቶ ጥቅም ላይ እንዲውልና አገልግሎት እንዲሰጥ ማድረግ በብዙ መልኩ
የተሻለ ጠቀሜታ እንዳለው በመታመኑ፤
የሊዝ አዋጅ ቁጥር 721/2004 እና የክልሉን የሊዝ ደንብ ቁጥር 103/2004 በተሟላ መልኩ ተግባራዊ ለማድረግ እና
በሥራ ላይ የቆየውን የአጭር ጊዜ ቦታ አሰጣጥ የአፈፃፀም መመሪያ በማሻሻል ከከተሞች ነባራዊ ሁኔታ አኳያ
ቦታዎችን በጊዜዊነት ለመጠቀም ከነዋሪዎች የሚቀርቡ ጥያቄዎችን ማስተናገድ የሚያስችል መመሪያ ማውጣት
በማስፈለጉ፣
የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት አስፈጻሚ አካላት እንደገና ማቋቋሚያና ስልጣንና ተግባራት መወሰኛ አዋጅ ቁጥር 176/2003
አንቀጽ 11 ንዑስ አንቀጽ 1 ፊደል /ሠ/ እንዲሁም የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በወጣዉ አዋጅ ቁጥር
721/2004 አንቀጽ 33 ንዑስ አንቀጽ 2፣ እና የከተማ ቦታን በሊዝ ለማስተዳደር የክልሉ ደንብ ቁጥር 103/2004
አንቀጽ 57 ንዑስ አንቀጽ 2 በተሰጠዉ ስልጣን መሰረት የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ኢንዱስትሪና ከተማ
ልማት ቢሮ ይህንን የአፈፃፀም መመሪያ አውጥቷል፡፡
ክፍል-- አንድ
ጠቅላላ
1. አጭር ርዕስ
ይህ መመሪያ የከተማ ቦታን ለአጭር ጊዜ በሊዝ ወይም በኪራ ይ ውል ለተጠቃሚዎች ለመፍቀድ የወጣ
የአፈፃፀም መመሪያ ቁጥር 5/2006 ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡
2. . ትርጓሜ
3. የቃሉ አግባብ ሌላ ትርጉም የሚያሠጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ መመሪያ ውስጥ ፡-
1
1. “አዋጅ” ማለት የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ የወጣው አዋጅ ቁጥር 721/2004 ዓ.ም ነው፤
2. “ደንብ” ማለት የከተማ ቦታን በሊዝ ለማስተዳደር እንደገና ተሻሽሎ የወጣ የክልል መስተዳደር ደንብ ቁጥር
103/2004 ነው፤
3. “ሊዝ” ማለት በጊዜ በተገደበ ዉል መሰረት የከተማ ቦታ የመጠቀም መብት የሚገኝበት የመሬት ይዞታ
ስሪት ነው፤
4. “የአጭር ጊዜ ኪራይ ውል” ማለት ወደ ሊዝ ስሪት ባልገቡ ከተሞች በጊዜ በተገደበ ውል ቦታ ለአጭር
ጊዜ የሚሰጥበት አግባብ ነው፤
5. “የቦታ ምደባ” ማለት በጨረታ ሊስተናገዱ ለማይችሉ ተቋማት የከተማ ቦታ በሊዝ ወይም ኪራይ ውል
የሚፈቀድበት ስልት ነው፤
6. “ለአጭር ጊዜ በሊዝ ወይም ኪራይ የሚፈቀድ ቦታ” ማለት ለከተማ ግብርና እስከ አስራ አምስት
ዓመት እንዲሁም ለሌሎች የአጭር ጊዜ የቦታ አገልግሎት ለአምስት ዓመትና ከዚያ በታች ለማምረቻ
፣ለማከማቻ ፣ለመሸጫ ፣ ለአገልግሎት ማቅረቢያ ወይም ለሌሎች አገልግሎቶች እንዲዉል በጊዜያዊ
ዉል የሚሰጥ ቦታ ነው፤
7. “ጊዜያዊ የሊዝ ወይም የኪራይ ክፍያ” ማለት በጊዜ ተወስኖ ለአጭር ጊዜ መጠቀሚያ ለተፈቀደ
የከተማ ቦታ በኪራይ ተመን ወይም በሊዝ ዋጋ መሠረት የሚከፈል ዓመታዊ ክፍያ ነው፤
8. “ክላስተር” ማለት በአንድ አካባቢ ተሰባስበው ብዛት ያላቸውንና ተመጋጋቢ የሆኑ የተለያዩ ምርቶችና
አገልግሎቶችን የሚያቀርቡና ተመሳሳይ ስጋትና መልካም አጋጣሚውንም የሚጋሩ ተቋማት ስብስብ
ነው፤
9. ”ጥቃቅን ኢንተርፕራይዝ”ማለት ከፖሊሲና ስትራቴጅ መሻሻል ጋር የሚኖር የትርጓሜ ለውጥ
እንደተጠበቀ ሆኖ የኢንተርፕራይዙን ባለቤት፤ የቤተሰብ አባላትና ተቀጣሪ ሰራተኞች ጨምሮ እስከ
አምስት ሰዎች ቀጥሮ የሚያሰማራና የጠቅላላ ካፒታሉ መጠን ህንፃን ሳይጨምር በአገልግሎት ዘርፍ
ከብር 50,000 (ሃምሳ ሺህ) ወይም በኢንዱስትሪ ዘርፍ ከብር 100,000 (አንድ መቶ ሺህ) ያልበለጠ
ኢንተርፕራይዝ ነው፤
10. ”አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ” ማለት ከፖሊሲና ስትራቴጅ መሻሻል ጋር የሚኖር የትርጓሜ ለውጥ
እንደተጠበቀ ሆኖ የኢንተርፕራይዙን ባለቤት፤ የቤተሰብ አባላትና ተቀጣሪ ሰራተኞችን ጨምሮ
ከስድስት እስከ ሰላሳ ሰዎች የሚያሰማራና የጠቅላላ ካፒታሉ መጠን ህንፃን ሳይጨምር በአገልግሎት
ዘርፍ ከብር 50,001 (ሃምሳ ሺህ አንድ) እስከ 500,000 (አምስት መቶ ሺህ) ወይም በኢንዱስትሪ
ዘርፍ ከብር 100,001 (አንድ መቶ ሺህ አንድ) እስከ 1,500,000 (አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺ)
ያልበለጠ ኢንተርፕራይዝ ነው፤
2
11. “ሼድ” ማለት እንደየአካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ በተዘጋጀው ዲዛይን መሰረት የሚሰራና በቋሚነት
ወይም ለተወሰነ ጊዜ ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ምርት ማምረቻና መሸጫ የሚያገለግል
ግንባታ ነው፤
12. #ጊዚያዊ ግንባታ; ማለት የጊዜ ገደብ ተቀምጦለት የሚገነባ እና የተሰጠው የጊዜ ገደብ ሲጠናቀቅ በቀላሉ
የሚነሳ ግንባታ ነው፤
13. “አግባብ ያለው አካል’’ ማለት የከተማ መሬትን ለማስተዳደር እና ለማልማት በህግ ስልጣን የተሰጠው አካል
ነዉ፤
14. “ከተማ” ማለት ማዘጋጃ ቤት የተቋቋመበት ወይም ሁለት ሺህ ወይም ከዚያ በላይ የህዝብ ቁጥር
ያለውና ከዚህ ውስጥ ሃምሳ በመቶ (50%) በላይ የሚሆነው ነዋሪ ከግብርና ውጭ በሆነ ሥራ ላይ
የተሰማራ ሆኖ የሚገኝበት አካባቢ ነው፤
15. “የከተማ ቦታ” ማለት በከተማ የአስተዳደራዊ ወሰን ክልል ውስጥ የሚገኝ መሬት ነው፤
16. “ቢሮ” ማለት የኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ቢሮ ማለት ነው፤
17. ማንኛውም በወንድ ጾታ የተገለጸው የሴትንም ይጨምራል፡፡
3. የተፈጻሚነት ወሰን
ይህ መመሪያ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ውስጥ በሚገኙ ከተሞች በአዋጁ አንቀፅ 18 ንዑስ አንቀጽ 2
ፊደል ተራ /ለ/ እንዲሁም በደንቡ አንቀፅ 25 በተጠቀሰው መሰረት በአጭር ጊዜ ውስጥ በቋሚነት ጥቅም ላይ
በማይውሉ የከተማ ቦታዎች ላይ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
3
4. ለአጭር ጊዜ ሊዝ ወይም ኪራይ የሚሰጡ ቦታዎች የስራ ዕድል ፈጠራን ትኩረት ባደረገ፣ በጥቃቅንና
አነስተኛ ተደራጅተው ለሚቀርቡ ስራ ፈላጊዎች ወይም በግል ለሚቀርቡ እና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ
ያሉ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረገ መሆን አለበት፡፡
5. በአጭር ጊዜ ውል የሚሠጡ የከተማ ቦታዎች በተቻለ መጠን መሰረተ ልማት የተሟላላቸው ወይም
በቅርበት የሚገኝባቸው ቦታዎች መሆን አለባቸው፡፡
6. ለአጭር ጊዜ ውል በሚሰጥ ቦታ ላይ የሚያርፍ ግንባታ ወይም ንብረት ወይም የሚሰጥ አገልግሎት
የከተማውን የትራፊክ እንቅስቃሴ በማያውክ መልኩ መሆን ይኖርበታል፡፡
7. በአጭር ጊዜ ውል ለተጠቃሚ በጊዜያዊነት የተላለፈ ቦታ/ሸድ ከውርስ በስተቀር በማንኛውም መንገድ
ለሶስተኛ ወገን ማስተላለፍ ወይም በዋስትና ማስያዝ አይቻልም፣
ክፍል ሁለት
4
መ. መዉጫና መግቢያን በመዝጋት የትራፊክ ዕንቅፋት የሚፈጥሩ ቦታዎች፣
ሠ. በከተማዉ ወይም በአካባቢዉ ነዋሪ ለአረንጓዴ ልማት (Greenery
areas)የተከለሉ ቦታዎች፣
ረ. ታሪካዊና ጥብቅ ቦታዎች/hisorical and reserved areas/ እና ሌሎች ተመሳሳይ ቦታዎች፣
7. በአጭር ጊዜ ውል በሚሰጡ የከተማ ቦታዎች ላይ የሚፈቀዱ የአገልግሎት አይነቶች፣
1. በዚህ መመሪያ አንቀጽ 5 የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ ለአጭር ጊዜ የሚሠጡ ቦታዎች በአካባቢው
ካለው እንቅስቃሴና አገልግሎት ጋር የተጣጣመ እና በአካባቢው ላይ የብክለትም ሆነ ሌላ ተጽዕኖ
የማያሳድር መሆኑ እየተጠረጋገጠ የሚከተሉትን የኘሮጀክት/አገልግሎት አይነቶች ያካተተ ሊሆን
ይችላል፡፡
ተ. ለጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት ለተለያዩ አገልግሎቶች ማቅረቢያ/መሸጫ እና ማምረቻ ቦታዎች ሊሆኑ ይችላል፡፡
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 ከ/ሀ/ እስከ /ተ/ የተዘረዘሩ የአገልግሎት አይነቶች እንደተጠበቁ ሆኖ አግባብ
ያለው አካል ለአጭር ጊዜ በሊዝ ወይም ኪራይ ውል ሊሰጡ ይገባል ብሎ የሚያምንባቸውን ሌሎች
ተመሳሳይ ዓላማ ያላቸው የአገልግሎት አይነቶች ሊሰጥ ይችላል::
5
8. የከተማ ቦታን በአጭር ጊዜ ውል ለመጠቀም የሚቀርብ ጥያቄ አቀራረብ እና
ለተጠቃሚዎች የሚተላለፍበት አግባብ
1. የቦታ ጥያቄዉ በግል ወይም በማህበር የሚቀርብ ከሆነ ቦታዉን ለምን አገልግሎት እንደፈለገዉ፣
በቦታዉ ላይ ሊከናወን የተፈለገዉ አገልግሎት ጠቀሜታ፣ ለአገልግሎቱ የሚውለው ጊዜያዊ የግንባታ
ስትራክቸርና የሚጠቀምበትን የጊዜያዊ ግንባታ ቁስ ዓይነት፣ የመጀመሪያ ደረጃ ንድፍ፣ ስራዉ
የሚጠይቀዉን የቦታ ስፋት፣ ቦታው የሚገኝበትን አድራሻ፣ ቀንና ዓ.ም የተጠቀሰበት የጽሁፍ
ማመልከቻ አግባብ ላለው አካል ያቀርባል፡፡
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 የተመለከተዉ እንደተጠበቀ ሆኖ የቦታ ጥያቄዉ በአነስተኛና ጥቃቅን
ከተደራጁ ማህበራት የቀረበ ሲሆን የማህበራቱ አደረጃጀት፤ የህጋዊነቱ አግባብ እና ጥያቄዉ
ተቀባይነት ማግኘቱ ማህበራቱን በሚያደራጀዉ በከተማው ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች
ልማት ጽ/ቤት በኩል እየተረጋገጠ አግባብ ላለው አካል መቅረብ ይኖርበታል፡፡
3. ለከተማ ግብርና እና ለማዕድን ማውጫ በጊዜያዊነት ለሚሰጡ ቦታዎች የሚቀርቡ ፕሮጀክቶችን
በተመለከተ የቀረበው ፕሮጀክት ዘርፉን በሚመራው ተቋም በኩል ግምገማና ሙያዊ አስተያየት
መሰጠት ይኖርበታል፡፡
4. ከተማው በተመረጡ የእድገት ተኮር የልማት ዘርፎች ላይ መሰማራት ለሚፈልጉ ስራ አጦችና
በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ወጣቶች፣ሴቶችና አካል ጉዳተኞች በጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዝ ጽ/ቤቱ በኩል በግል ተመልምለው ሲቀርቡ ማስተናገድ ይችላል፡፡
5. በዚህ አንቀጽ በተገለፀው አግባብ በጊዜያዊነት ለሚሰጡ ቦታዎች የሚቀርብ የቦታ ጥያቄ በከተማው
ከንቲባ ኮሚቴ ወይም ማዘጋጃ ቤት ማኔጅመንት ኮሚቴ በኩል እየተወሰነ በምደባ ለተጠቃሚዎች
የሚተላለፍ ይሆናል፡፡
6
ለ. ከሶስተኛ ወገን ሙሉ በሙሉ ነፃ ያደርጋል፣
ሐ. ጊዜያዊ ሳይት ኘላን ያዘጋጃል፣
መ. ለእያንዳንዱ ቁራሽ መሬት መለያ ቁጥር በመስጠት የወሰን ድንጋይ በመትከል ቁጥር እንዲሠጣቸው
ያደርጋል፡፡
2. ከተማው ጊዜያዊ ሸድና ክላስተር በመገንባት ወይም ቦታን በማዘጋጀት በአጭር ጊዜ ሊዝ/ኪራይ አግባብ
ለተጠቃሚዎች እንዲተላለፍ ያደርጋል፡፡
3. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 2 በተገለፀው መሰረት የከተማው ኢንዱስትሪ ልማትና ከተማ
አገልግሎት/መምሪያ/ ጽ/ቤት ወይም ማዘጋጃ ቤት ተመርጦ በተዘጋጀ ቦታ ላይ የሸድና ክላስተር ግንባታ
ያከናውናል፡፡
4. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 3 በተገለፀው መሰረት ከተማው ኢንዱስትሪ ልማትና ከተማ
አገልግሎት/መምሪያ/ ጽ/ቤት ወይም ማዘጋጃ ቤት የተገነባውን ጊዜያዊ ሸድ ለከተማው ጥቃቅንና
አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት ያስረክባል፡፡
5. የከተማው ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት የተገነቡ ክላስተርና ሸዶች በጊዜያዊ ውል
ለተጠቃሚዎች ያስተላልፋል፡፡
6. በዚህ አንቀጽ 5 የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ የከተማው ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ልማት
ጽ/ቤት በውሉ መሰረት ሸድና ክላስተር ይዞታዎችን አጠቃቀም እና ክፍያ አፈፃፀም ይከታተላል፡፡
7. የከተማው ማዘጋጃ ቤት ወይም ኢንዱስትሪ ልማትና ከተማ አገልግሎት/መምሪያ/ ጽ/ቤት ወይም ማዘጋጃ
ቤት ቦታውን በቋሚነት ማልማት ሲፈለግ ከተጠቃሚዎች ጋር የተያዘው የሊዝ/ኪራይ ውል
እንዲቋረጥ ከስድስት ወር በፊት ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት በደብዳቤ
ያሳውቃል፡፡
8. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 2 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ ከተማው በአጭር ጊዜ ሊዝ/ኪራይ አግባብ
ጊዜያዊ ቦታን በግል ወይም በማህበር ለሚቀርቡ ተጠቃሚዎች እንዲተላለፍ ያደርጋል፡፡
ሀ. በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት በኩል ተመልምለውና ተደራጅተው ለከተማው
ማ/ቤት ወይም ኢንዱስትሪ ልማትና ከተማ አገልግሎት/መምሪያ/ ጽ/ቤት ወይም ማዘጋጃ ቤት
ጊዜያዊ ቦታ እንዲያገኙ ጥያቄው በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት ሲቀርብ
በተገለፀው የቦታ መጠንና የአገልግሎት ዘርፍ መሰረት በቅደም ተከተል ቦታ ይሰጣቸዋል፡፡
ለ. የጊዜያዊ ውሉ በተዘጋጀው የውል ፎርም መሰረት በከተማው ማዘጋጃ ቤት ወይም ኢንዱስትሪ
ልማትና ከተማ አገልግሎት/መምሪያ/ ጽ/ቤት በኩል የሚያዝ ይሆናል፡፡
ሐ. የቦታ አጠቃቀሙና የክፍያ አፈፃጸሙ በከተማው ኢንዱስትሪ ልማትና ከተማ አገልግሎት/መምሪያ/
ጽ/ቤት ወይም ማዘጋጃ ቤት በኩል ክትትል ይደረግበታል፡፡እንደአስፈላጊነቱ የጊዜያዊ ውል እደሳት
የሚደረግ ይሆናል፡፡
7
መ. በተናጥል በጊዜያዊነት የሚሰጡ አገልግሎቶች ለምሳሌ ለግንባታ ጊዜ ቁሳቁስ ማስቀመጫ
፣ለማስታዎቂያ መትከያ ወዘተ አገልግሎቶች ሆነው ለሚቀርቡ ጊዜያዊ የቦታ ጥያቄዎች አግባብ
ያለው አካል እንደአስፈላጊነቱ በጊዜያዊ ውል ቦታ የሚፈቅድ ይሆናል፡፡
ክፍል ሶስት
ሀ. በከተማው በኩል በጊዜያዊነት በተሰጡ ቦታዎች ላይ በህገወጥ መንገድ የግንባታ ፈቃድ በመውሰድ
ቋሚ ግንባታ የገነቡ እና ቦታውን እየተጠቀሙ ያሉ ግለሰቦች ቋሚ ግንባታውን በማፍረስ ቦታው
ወደ መሬት ባንክ እንዲገባ ተደርጎ ችግሩን የፈጠረው አካልም አግባብ ባለው ህግ ተጠያቂ
ይሆናል፡፡
8
በተሰጠው ጊዜ የማያፈርስና የማያነሳ ከሆነ ከተማው የህገ-ወጥ ግንባታዎችን
በሚያስተናግድበት አግባብ ተፈፃሚ የሚያደርግ ይሆናል፡፡
መ. የከተማ ቦታን በጊዜያዊነት አገልግሎት ላይ ለማዋል አግባብ ካለው አካል ወስደው የአገልግሎት
ለውጥ ያደረጉ ተጠቃሚዎች የአመታዊ የሊዝ/ኪራይ ክፍያውን 3% ቅጣት በማስከፈል
መጀመሪያ ለተፈቀደው የአግልግሎት አይነት እንዲጠቀሙ ይደረጋል፡፡
3. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 2 ፊደል ተራ /ሠ/ እና /ረ/ በተገለፀው አግባብ ቀደም ሲል
በጊዜያዊነት የወሰዱ እና አሁን እንዲጠቀሙበት የተፈቀደላቸው ባለይዞታዎች ውዝፍ የቦታ
ሊዝ/ኪራይ ክፍያ በአንድ ጊዜ አጠቃለው እንዲከፍሉ ይደረጋል፡፡
4. በህጋዊ መንገድ ቦታ በጊዜያዊነት ለማልማት ወስደው ለተፈቀደላቸው አገልግሎ እየተጠቀሙ
የሚገኙ ሆነው በተለያየ ምክንያት ውል ያልያዙ፣ውል ይዘው ያላሳደሱ እና የቦታ ኪራይ/ሊዝ
ክፍያ ያልከፈሉ ተጠቃሚዎች ከተማው ቦታውን ለተለየ ልማት እስካልፈለገው ድረስ ቦታውን
ከተረከቡበት ጊዜ ጀምሮ ውል እንዲይዙ በማድረግ በውሉ መሰረት ውዝፍ የኪራይ/ሊዝ ክፍያ
እንዲከፈሉ ይደረጋል፡፡
6. ከዚህ ቀደም በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት በጊዜያዊነት የተገነቡ ሆነው
ለተጠቃሚዎች የተላለፉ ሸዶችን መረጃ በዝርዝር ተለይተው ተገቢውን የሰነድና ማስረጃ ርክክብ
9
በመፈጸም የማስተዳደር እና ክፍያ አፈፃፀሙን የመከታተል ስራ በከተማው ኢን/ል/ከተማ
አገል/መምሪያ/ጽ/ቤት/ማ/ቤት በኩል የሚከናወን ይሆናል፡፡
10
1. አንድ ዓመትና በታች ለሆነ ጊዜ በጊዜዊነት የሚፈቀዱ ቦታዎች በየወሩ ወይም
እንደአስፈላጊነቱ ውል ሰጭና ውል ተቀባይ በውል ስምምነታቸው በሚያስቀምጡት ጊዜ
መሰረት የሚከፈል ይሆናል፡፡
2. ለአጭር ጊዜ የተፈቀደው ቦታ ውሉ ከአንድ ዓመት በላይ ከሆነ ክፍያው በየዓመቱ የሚፈፀም
ይሆናል፡፡በጊዜያዊነት ለአጭር ጊዜ የሚሰጡ ቦታዎች ዓመታዊ የክፍያ መጠን በካ/ሜትር እና
በአገልግሎት ዓይነት በዚህ መመሪያ አባሪ 4 ላይ ይመልከቱ፡፡
3. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 ላይ የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በአጭር ጊዜ ውል የተሰጠ
ማንኛውም ቦታ ውል ከተያዘበት ጊዜ ጀምሮ በየአመቱ ዓመታዊ የሊዝ/ኪራይ ክፍያ የሚከፈል
ይሆናል፡፡ ከአንድ አመት በላይ ውል ላላቸው ቦታዎች አመታዊ ክፍያውን ከሶስት ወርና በላይ ሳይከፍሉ
ከዘገዩ ለሚዘገይበት እያንዳንዱ ወር የአመታዊ ክፍያውን 3 በመቶ ቅጣት የሚከፍሉ ይሆናል፡፡
4. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 3 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ ከሶስት አመት በላይ ውል ለያዙ
ተጠቃሚዎች የሶስት አመት ውዝፍ ካለባቸው ውዝፍ ክፍያውን በማስከፈል ቦታውን እንዲነጠቁ
ይደረጋል፡፡
5. የውል ጊዜው ተጠናቆ አዲስ ውል የሚፈረም ከሆነ እና አዲስ የተደረጉ የዋጋ ማስተካከያዎች ካሉ
ውሉ በተስተካከለው ዋጋ መሰረት ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
6. በከተማ አስተዳደሮች በዚህ መመሪያ አባሪ 4 ላይ የተቀመጠውን ዋጋ ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ
ከተሞች ጥናቱን አከናውነው ለቢሮ በማቅረብ አስፈላጊው ግምገማ አስተያየት ተሰጥቶበት
እንዲፀድቅ ይደረጋል፡፡
7. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 6 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ በማዘጋጃ ቤት እና ታዳጊ ከተሞች
በጊዜያዊነት የሚሰጡ ቦታዎች ሊዝ/ኪራይ ዋጋ ማሻሻያ ጥናት በዞን ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት
መምሪያዎች በኩል ተጠንቶ ጥናቱ ለቢሮው በማቅረብ ሲፀድቅ ተግባራዊ የሚደረግ ይሆናል፡፡
ክፍል አራት
11
1. የከተማዉ ኢንዱስትሪ ልማትና ከተማ አገልግሎት/መምሪያ/ ጽ/ቤት ወይም ማዘጋጃ ቤት ወይም
ታዳጊ ከተማ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ዋና የስራ ሂደት የተሰጠዉን ዉሳኔ ቃለ ጉባኤ መሰረት
በማድረግ በተዘጋጀው የዉሉ ቅጽ/ፎርም መሰረት ከውል ተቀባይ ጋር ይዋዋላል፡፡
2. የዉሉ ይዘት ቃለ ጉባኤዉን መነሻ የሚያደርግ እና የዉል ተቀባይ እና ዉል ሰጪን መብት እና ግዴታ
ያካተተ ይሆናል፡፡
3. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 እና 2 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ የከተማ ቦታ የአጭር ጊዜ ሊዝ
ወይም ከራይ የውል አፈፃፀም ዝርዝር ሁኔታ የያዘ ፎርም በቢሮው በኩል የሚዘጋጅ ይሆናል፡፡
4. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 2 የተመለከተዉ እንደተጠበቀ ሆኖ ለድንጋይ ማዕድን ማዉጫነት ለሚዉል
ቦታ የሚፈጸመዉ ዉል ቦታዉን በነበረበት ሁኔታ አፈር በመሙላት እና በማስተካከል መመለስን
የሚያካትት ይሆናል፡፡
5. በዚህ መመሪያ በአባሪነት የተያያዘው ፎርም የመመሪያው አካል ሆኖ ዉል ተቀባይ የከተማዉ የመሬት
ልማትና ማኔጅመንት ዋና የስራ ሂደት ጋር ዉል እንደተፈራረመ ቦታዉን ለተጠቀሰዉ ጊዜ መጠቀም
የሚያስችለዉ ጊዜያዊ የምስክር ወረቀት/ሰርትፊኬት ለተፈቀደው የውል ዘመን የሚሰጠዉ ይሆናል፡፡
ሆኖም በጊዜያዊነት ለአጭር ጊዜ ተገንብተው ለተጠቃሚዎች ለሚተላለፉ የክላስተርና ሸድ ቤት
ተከራዮች ጊዜያዊ የምስክር ወረቀት የሚሰጥ አይሆንም፡፡
6. ለክትትል ይረዳ ዘንድ የከተማዉ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ዋና የስራ ሂደት ከከተማው ጥቃቅንና
አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ሰነዶቹን መነሻ በማድረግ የጊዜያዊ
ሊዝ/ኪራይ ይዞታዎች መረጃ በማህደር የሚያደራጅ ይሆናል፡፡
7. የከተማው መሬት ልማትና ማኔጅመንት ዋና የስራ ሂደት በጊዜያዊነት የተላለፈዉ መሬት በዉሉ
መሰረት በአግባቡ ጥቅም ላይ ስለመዋሉ እና ከዉል ተቀባዩ ዉጪ ለሌላ አካልም ያልተላለፈ መሆኑን
ክትትል ያደርጋል፤ በዉሉ መሰረት ካልተፈጸመም ቦታዉን መልሶ ይረከበዋል፡
8. ከተማው ጊዜያዊ ሸድ ገንብቶ ለጥቃቅን በሚያስረክብበት ጊዜ ከተጠቃሚዎች ጋር የሚያዘው የኪራይ
ውልና ክፍያ አፈፃፀም ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት በኩል ክትትል የሚደረግ
ይሆናል፡፡
12
2. እንደአስፈላጊነቱ ጊዜያዊ የውል እድሳት የሚደረግ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በጥቃቅንና አነስተኛ
ለተደራጁ ግለሰቦች ወይም ማህበራት ለከተማ ግብርና አገልግሎት የሚሰጥ ቦታ የውል ዘመን ለ 5 ዓመት
ይሆናል፡፡
3. ውል ተቀባይ ቦታዉን ለሌላ ተጨማሪ አመት መጠቀም ከፈለገ የዉል ዘመኑ ለመጠናቀቅ ከአንድ አመት
እስከ ስድስት ወር ሲቀረዉ የውል እድሳት ጥያቄውን ለከተማዉ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ዋና
የስራ ሂደት በደብዳቤ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
4. በዚህ አንቀጽ /3/ በተገለፀው መሰረት ዉል ሰጭ በጊዜያዊ የቦታ ውል ዕድሳት ማመልከቻ ደብዳቤ
መሰረት ጥያቄውን ከደንብና መመሪያ አኳያ አጣርቶ ቦታውን በቋሚነት ለሌላ ልማት የማይውል
መሆኑን በማረጋገጥ ለሚመለከተው አካል በማቅረብ ሲወሰን የሚታደስለት ይሆናል፡፡ የጊዜያዊ ውል
እድሳቱ ለውል ተቀባይ ሲገለጽለት ቀድሞ የነበረዉን ጊዜያዊ የምስክር ወረቀት ተመላሽ እንዲያደርግ
እና የዉል እድሳት በመፈጸም አዲስ የመጠቀሚያ ጊዜያዊ ምስክር ወረቀት እንዲሰጠዉ ይደረጋል፡፡
5. በከተማው በኩል በጊዜያዊነት ተገንብተው ለከተማው ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ልማት
ጽ/ቤት የተላለፉ ጊዜያዊ ሸዶች ጽ/ቤቱ የውል ዕድሳቱን አስፈላጊነት በደብዳቤ ሲያሳዉቅና ቦታዉ ለሌላ
ልማት የማይፈለግ መሆኑ ሲረጋገጥ የሚታደስለት ይሆናል፡፡
6. በጊዜያዊነት ለአጭር ጊዜ የተሰጠ የከተማ ቦታ ውል ሊታደስ የሚችለው ቀደም ሲል ለተሠጠው
አገልግሎት ሲሆን የአገልግሎት ለውጥ ጥያቄ ከቀረበ በሚመለከተው አካል ሲታመንበት ሊስተናገድ
ይችላል፡፡
7. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 3 እና 4 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ በጥቃቅንና አነስተኛ ለተደራጁ ከተማ
ግብርና አገልግሎት የተሰጠ እና በውሉ መሰረት ጥቅም ላይ እየዋለ ከሚገኝ ቦታ በስተቀር ከአንድ ጊዜ
በላይ ውል እድሳት ማድረግ አይቻልም ፡፡
8. የዉል ዘመኑ የተጠናቀቀ እና ዉል ተቀባይ እድሳት ጥያቄ ያላቀረበ ወይም ውል ሰጭ እድሳቱን ያላመነበት
ከሆነ ቦታዉን ዉሉ በተጠናቀቀ በሶስት ወር ጊዜ ዉስጥ ዉል ተቀባይ እንዲያስረክብ ይደረጋል፡፡ የውል
ተቀባይ የአጭር ጊዜ ይዞታ ባለቤትነት እና የጊዜያዊ መጠቀሚያ የምስክር ወረቀት እንዲሠረዝ ተደርጎ
ቦታዉም በመሬት መረጃ ባንክ ላይ በማንም ያልተያዘ በሚል ተመዝግቦ እንዲያዝ ይደረጋል፡፡
9. ለአጭር ጊዜ የተሰጠ ቦታ የውል ጊዜው ከመጠናቀቁ በፊት ለልማት ሲፈለግ ለውል ተቀባይ ንብረቱን
ለማንሳት የሚያበቃ ግምት ይሰጠዋል፡፡ እንደአስፈላጊነቱ እየታየ ለቀሪው የውል ጊዜ መጠቀሚያ
የሚሆን ምትክ ቦታ ሊሰጥ ይችላል፡፡
10. ከላይ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 7 የተገለጸው ቢኖርም ከከተማው ፕላን ጋር በተጣጣመ፣ የትራፊክ
እንቅስቃሴን በማያውክ፣ የመሰረተ ልማት አውታሮችን በማያደናቅፍ፣ ህንጻዎችንና ሰው ሰራሽ
የተፈጥሮ ቅርሶችን በማይከልልና በማያውክ ሁኔታ መሆኑ እየተረጋገጠ ለመንግስታዊ ተቋማት፣
13
ለኢምባሲዎች እና በተመሳሳይ ለሌሎች በልዩ ሁኔታ መታየት ላለባቸዉ ተቋማት ለማስታወቂያ ሰሌዳ
መትከያ የሚፈቀዱ ቦታዎች በየጊዜዉ ሊታደስላቸዉ ይችላል፡፡
ክፍል አምስት
ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
17. ስለተጠያቂነት
14
በዚህ መመሪያ የተጣለበትን ግዴታ ያልተወጣና ለሊዝ/ኪራይ ውል ተቀባዮች የተሰጠውን መብት በአግባቡ
ያላከበረ አካል በአዋጁ አንቀጽ 35 የተጠቀሰው እንደጠበቀ ሆኖ ወንጀል ህጉ ተግባራዊ የሚደረግ ይሆናል::
ይህ መመሪያ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ቢሮ ፀድቆ ከወጣበት ግንቦት
15/2006 ጀምሮ የጸና ይሆናል፡፡
15
ተ.ቁ የህንፃው አገልግሎት ጠ/ወለል የቦታዉ ምርመራ
ስፋት(በካ/ሜ) ስፋት(በካ/ሜ)
1 ጨርቃጨርቅና አልባሳት
16
3 የደሮ እርባታ
እድሜ)፣ታዳጊ(9-12 ሳምንት
እድሜ)፣እናት ወይም
አዉራደሮ
4 አሳማ እርባታ
ታዳጊ
4 ማድለብ
አባሪ 4፡- ዓመታዊ የአንድ ሜትር ካሬ ኪራይ ክፍያ በአገልግሎት ዓይነትና ቦታ ደረጃ
17
2 25 15 18 6 35 18 1.00 8
3 20 12 15 6 30 16 0.75 6
4 10 10 12 5 25 10 0.50 4
5 8 8 10 5 20 8 0.25 2
2 2 1 20 15 18 5 30 16 1.50 1
2 20 12 15 5 25 10 1.00 8
3 15 10 12 4 20 8 0.75 6
4 8 8 10 3 15 6 0.50 4
5 5 7 8 3 10 4 0.25 2
3 3 1 15 12 15 4 20 10 1.00 6
2 10 10 12 4 15 8 0,75 4
3 8 8 10 3 10 6 0.50 2
4 6 6 8 2 8 3 0.25 1
5 3 4 6 2 5 2 0.15 0.5
4 4 1 8 8 10 3 10 3 0.75 4
2 6 6 8 3 8 2 0.50 2
3 3 4 6 2 6 1 0.25 1
4 2 2 4 1 4 0.50 0.15 0.5
5 5 1 6 6 8 2 8 2 0.50 2
2 3 3 6 1 5 1 0.25 1
3 2 1 2 0.5 2 0.50 0.15 0.5
6 6 1 2 2 3 1 2 0.50 0.25 1
2 1 0.50 1 0.25 1 0.25 0.15 0.25
የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በወጣው አዋጅ ቁጥር 721/2004 እና በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት
ምክር ቤት የከተማ ቦታን በሊዝ ለማስተዳደር በወጣው ደንብ ቁጥር 103/2004 መሠረት ተፈጻሚ የሚሆን
ውል፡-
18
1.ውል ሰጪ የ--------------------- ከተማ ኢንዱስትሪ ልማትና ከተማ አገልግሎት/መምሪያ ጽ/ቤት ወይም
ማዘጋጃ ቤት
2. ውል ተቀባይ፡-ሙሉ ስም--------------------------------------
አድራሻ፡-ዞን------------ወረዳ-----------ከተማ-----------ቀበሌ----------------------የቤት
ቁጥር-------------------ስልክ ቁጥር-----------------------------
3. ውል ስለመፈረም
በዚህ ውል የተጠቀሰውን የከተማ ቦታ/ሸድ ውል ተቀባይ ለአጭር ጊዜ በሊዝ /በኪራይ ውል
ለ------------------አገልግሎት ብቻ ለመጠቀም ከዛሬ ----------------ቀን--------------- ወር----------------
ዓ.ም ጀምሮ ከዚህ በኋላ ውል ሰጭ እየተባለ በሚጠራው የ-------------- ከተማ ኢንዱስትሪ ልማትና
ከተማ አገልግሎት/መምሪያ ጽ/ቤት ወይም ማዘጋጃ ቤት እና ውል ተቀባይ እየተባለ በሚጠራው
በአቶ/ወ/ሮ/ወሪ/ት/ድርጅት/ተቋም------------------መካከል ተፈርሟል፡፡
4. በአጭር ጊዜ የሊዝ/በኪራይ ውል የሚያዘው ቦታ/ሸድ ዝርዝር ሁኔታ፡-
ቦታው/ሸዱ የሚገኝበት አድራሻ፡-
ዞን--------------------ወረዳ------------------ከተማ-----------------ቀበሌ---------------ቦታው/ሸዱ የሚገኝበት
አካባቢያዊ ልዩ ስም------
የቦታው/ሸዱ አዋሳኝ፡-
በሰሜን ----------------------
በደቡብ ----------------------
በምስራቅ---------------------
በምዕራብ --------------------
19
የቦታው የሊዝ/ኪራይ ውል ዘመን---------------------ዓመት ነው፡፡
በሊዝ ወይም በኪራይ የሚያዘው ቦታ ደረጃ -------------የንዑስ የቦታ ደረጃ----------ነው፡
ተከራይ የተገለፀውን የማምረቻና የማሳያ ማዕከላት ወይም ሕንፃ በካሬ ሜትር ……. ብር ሂሳብ
በጠቅላላ ---------------------------- በካሬ ሜትር ብር -------------------------------------- ኪራይ በወር
ለመክፈል ተስማምቷል፡፡
በየወሩ ኪራይ የሚከፈለው በአካባቢው የሚገኘው የገቢዎች ጽ/ቤት ድረስ በመሄድ ነው፡፡ ተከራይ
የተጠቀመበትን የኪራይ ክፍያ እስከ 3 ወር ካልከፈለ በየወሩ የወርሃዊ ክፍያውን 10% ጨምሮ መቀጫ
ይከፍላል፡፡ የቅጣቱን ክፍያም ለገቢዎች ጽ/ቤት ይከፍላል፡፡
ተከራይ በተከታታይ እስከ ሶስት ወር ድረስ ያለውን ኪራይ ከነመቀጫው ካልከፈለ አከራይ ውሉ
እንዲቋረጥ በማድረግ ቀሪውን ገንዘብ ለማስከፈል በሕግ ይጠይቃል፡፡ ውሉ ከተቋረጠ በኃላ በሕንፃው
ውስጥ ለሚገኝ ንብረት ተጠያቂነት አይኖርበትም፡፡
20
በግንባታ ቁሳቁስ ጉድለት በእርጅና እንዲሁም ከአቅም በላይ በሆኑ ነገሮች በሕንፃው ላይ ጉዳት ቢደርስ ሕንፃውን
አከራይ ይጠግናል፡፡
7. የውል ተቀባይ መብትና ግዴታ
ውል ተቀባይ ሕንፃውን ወይም ቦታውን መልቀቅ ሲፈልግ የተረከበውን ማንኛውንም ንብረት ሲረከብ
በነበረበት ሁኔታ ለአከራይ የመመለስ ግዴታ አለበት፡፡
8. የውል ሰጪግዴታና የመቆጣጠር ስልጣን
21
ለውል ተቀባዩ ጊዜያዊ የምስክር ወረቀት የመስጠት ግዴታ አለበት፡፡
በጊዜያዊነት የተፈቀደው ቦታ/ሸድ በአግባቡ ጥቅም ላይ እየዋለ መሆኑ እና በየዓመቱ የሚከፈለው
ክፍያ ወቅቱን ጠብቆ እየተከፈለ መሆኑን መከታተልና ማረጋገጥ አለበት፡፡
የሊዝ/ኪራይ ውሉ ከመፈረሙ በፊት ስለ ውሉ ይዘት ማሳወቅ አለበት፡፡
ቦታው/ሸዱ ለተፈቀደለት አገልግሎት መዋሉን እና መልማት ባለበት አግባብ እለማ መሆኑን
ይቆጣጠራል፡፡
9. የውል መቋረጥ
ይህ ውል ተቀባይ አና ውል ሰጪው ከዚህ በላይ በዝርዝር የተገለፀውን የውል ስምምነት አንብበው እና ተስማምተው
በፊርማቸው አጽድቀው በአራት ኮፒ በማዘጋጀት አንድ ኮፒ ለውል ተቀባይ ፣አንድ ኮፒ ለማይንቀሳቀስ ንብርት ምዝገባ
ተቋም፣አንድ ኮፒ ለግንባታ ፈቃድ ሰጭ ተቋም እና አንድ ኮፒ የውል ተቀባይ ማህደር ውስጥ ተያይዞ ይቀመጣል፡፡
22
አባሪ--6 ፡- ጊዜያዊ የከተማ ቦታ መጠቀሚያ የምስክር ወረቀት
የቦታው አቀማመጥ
አዋሳኝ:-
በሰሜን -----------------------
በደቡብ ----------------------
ሰ
በምስራቅ----------------------
በምዕራብ ---------------------
23
አባሪ--7፡- በጊዜያዊነት የተሰጡ ቦታዎች መረጃ ማሰባሰቢያ ፎርም/ቅፅ/
ይዞታው የሚገኝበት የቦታ የቦታ የሚሰ የኘ በየአመ የቦታው የሊዝ/ የሊዝ/ የፕላን
አድራሻ ው ው ጠው ሎት ቱ ጠቅላላ ኪራይ ኪራይ ውሉ ምደባ
ደረ ስፋት አገልግ ቁጥ የሚከፈ የሊዝ/ኪራይ ዘመን የሚጠናቀቅ ኮድ
ጃ ሎት ር ለው ክፍያ በት ጊዜ ቁጥር
የሊዝ
ኪራይ
ክፍያ
ዞን ወረዳ ከተማ ቀበሌ/
ልዩ ስም
24