You are on page 1of 45

የማሽከርከር ስነ-ባህሪ

ስነ-ባህሪ ማለት ምን ማለት ነው


የተለያዪ ባለሙ ያዎች በተለያየ መልኩ በሁለት አይነት ይገልጱታል
1. ስነ-ባህሪ ፡- የሰዎችና የእንስሳትን ባህሪ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ የሚያጠና ዲሲፒሊን ነው፡፡

2- ስነ-ባህሪ፡- ባህሪን እና የአእምሮ የአስተሳሰብ ሂደት ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ የሚያጠና ዲሲፒሊን ነው፡፡

 ከነዚህ የስነባህሪይ ትርጓሜወች የምንረዳው ሁለት ነገሮችን ነው፤የመጀመሪያው ስነባህሪይ የሚያጠናው ስለ


ባህሪይና የአስተሳሰብ ሂደት መሆኑን ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የስነባህሪይ ባለሙያወች ባህሪንና የአስተሳሰብ
ሂደትን የሚያጠኑት ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ መሆኑን ነው፡፡

3. ባህሪ፡- የሰው አስተሳብ አመለካከትና ድርጊት ውጤት ነው፡፡ ከዚህ በመነሳት በቀጥታ ሊቃኝ ሊመዘገብና
ሊለካ የሚችል ይሆናል፡፡
ተፈጥሮና አካባቢ በባህሪ ላይ ያላቸው ሚና
የሰው ልጅ ባህሪ የውርስ (heredity) እና የአካባቢ ( Environment) የጋራ ውጤት እንደሆነ የተለያዩ
የስነ-ባህሪ ባለሙያዎች ይስማማሉ፡፡
የስነ-ባህሪ ግቦች
 የስነ-ባህሪ ግቦች የሚባሉት
A. ባህሪን መግለፅ
B. የተለያዩ ባህሪያትን መንስኤ ማብራራት
C. ወቅታዊ የባህሪን ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት የወደፊቱን መተበይ
D. ባህሪን ማሻሻል
E. የሰው ልጅ መልካምና መጥፎ ባህሪያን ሊያዳብር ይችላል፡፡ ነገር ግን መልካም ያልሆነው ባህሪ
በተለያዩ የስነ-ባህሪ ዘዴዎች መለወጥ ሌላኛው የስነ-ባህሪ ግብ ነው፡፡

የማሽከርከር ስነ-ባህሪ
 የማሽከርከር ስነ-ባህሪ አሽከርካሪዎች በሚያሽከረክሩበት ወቅት የሚያሳዩትን ባህሪ
የሚያጠና የሥነ-ባህሪ ዘርፍ ነው፡፡
የማሽከርከር ስነ-ባህሪ ጠቀሜታ
 የማሽከርከር ስነ-ባህሪ ዋና አላማው በተሸከርካሪ የሚደርስ አደጋን መቀነስ ነው፡፡ ይህም
ሲባል በዋናነት ሊከናወን የሚችለው አላስፈላጊ የማሽከርከር ባህሪን በማስተካከል ነው፡፡
የግኙነት ክህሎቶች
 ትህትና፡- ለመንገደኞች ትሁት መሆን
 ርህራሄ፡- -ሌሎች መንገድ ተጠቃሚዎችን ስሜት መጠበቅ
 እንደዜጋ ህግንና ደንብን አክባሪ መሆን ፡- ለመንገድ ወይም ለእንቅስቃሴ ህግጋት
ተገዢ መሆን
 ከሌሎች መንገድ ተቃሚዎች ጋር መንፈሳዊ ትስስር መፍጠር
 የፈጠራ የአነዳድ ልምዶችን እና የዘመኑን የሳይንስ ግኝቶችን ማዳበር
 የሌላን መንገድ ተጠቃሚ ስሜት መጋራት ናቸው፡፡
የማሽከርከር ሥነ- ባህሪ ጉዳዮች
 ዝግጁነት
 መነቃቃት
 መረጃ ን የ መስብስብ እና የመተረጎም ሂደት
1.ዝግጁነት፡- የብስለት ፣ የችሎታ ፣ የትምህርትና የመነሳሳት የጋራ
ውጤት ነው፡፡ በመሆኑም የዝግጁነት መገለጫ የሆኑት
ለማሽከርከር ጤነኛ መሆንህን ማረጋገጥ
መፈተሽ ያለብህን ነገር መፈተሽ ( ተሽከርካሪን ለጉዞ ዝግጁ
ማድረግ)
የመንገድ የአየር እና የትራፊክ ሁኔታ በማሽከርከር ሂደት ላይ
የሚፈጥረውን ችግር ቀድሞ መገመት፡፡
2 .
2.መነቃቃት፡- በሰዎች ውስጥ ያለ ሁኔታ ሆኖ ባህሪን ወደ ግብ
የሚያንቀሳቅስ ሂደት ነው፡፡ ከዚህ አንፃር ንቁ ተነሳሽነት ያለው
አሽከርካሪ በማንኛውም የትራፊክ ሁኔታ ውስጥ የሚወስደው ውሳኔና
እርምጃ ፈጣን መሆን እንዳለበት ይረዳል፤ለስራ ዉጤት መነሳሳት
ከፍተኛ ፈላጎት ያለው ሰው የሚገጥሙትን ችግሮች እንደ ፈተና
በመቁጠር ለዉጤቱ የበለጠ ይሰራል፡፡
3. መረጃን የመሰብሰብና የመተርጎም ሂደት
 መገንዘብ
 ትኩረት
 ማስተዋል
 መገንዘብ (- Sensation) ፡- መረጃን ከአካባቢያችን በስሜት
ህዋሳቶቻችን የመቀበል የመለወጥና ወደ አእምሮአችን የመላክ ሂደት
ነው፡፡ ማለትም በስሜት ህዋሶቻችን አማካኝነት ማለትም በማየት
በመስማት በማሽተት በመቅመስና በመዳደስ ነው፡፡
 ከ80-90 ፐርስንት አካባቢን ለማውቅና መርጃ ለመሰብ የሚያስቸለው
ትኩረት (Attention) ፡- በስሜት ህዋሳቶቻችን አማካኝነት
ከሚደርሱን መረጃዎች መካከል ዋናውንና ተፈላጊውን የመምረጥ ሂደት
ነው፡፡ በመሆኑም መረጃ ላይ ትኩረት ማድረግን ሊያዳብሩት የሚገባ
ጉዳይ መሆኑን ማወቅ ይገባል፡፡

ማስተዋል (Perception) ፡- በስሜት ህዋሳቶቻችን አማካኝነት


የመጣን መረጃ የመምረጥ የማቀናበርና ትርጉም የመስጠት ሂደት ነው፡፡
ስለሆነም አሽከርካሪዎች በአጋግባቡ ማስተዋል ውሳኔ የመወሰን ብቃት
ሊያዳብሩ ይገባል፤ሃሳብን መሰብሰብ የማሽከርከር ትልቁና ዋንኛው
የጥንቃቄ መጀመሪያ ነው፡፡
የማሽከርከር ስነባሀሪ ባለሙያወች የአሽከርካሪ መቀመጫ የቀን ህልም
የሚታይበት ቦታ ያለመሆኑን ይገልጻሉ፡፡ስለሆነም የአሽከርካሪ መቀመጫ
ከማሽከርከር ውጭ ሌላ ነገር ለማሰብ ፋታ የማይሰጥ ተግባር በመሆኑና
በየትኛውም ርቀት ላይ ከአደጋ ጋር ልትፋጠጥ እንደምትችል በመገንዘብ
አካባቢህን በንቃት መከታተል፣መረጃን መሰብሰብ፣የሰበሰብከውን መረጃ
ያለህን ዕውቀትና ልምድ በመጠቀም አደጋን ተከላክሎ ለማሽከርከር
ተጠቀምበት፡፡
የባህሪ መለዋወጥ መንስኤዎች
ከቤተሰብ የወረስናቸው ባህሪያትና ያለን አመለካከት
የምንኖርበት አካባቢ፡- በኛ ዙሪያ ባለ እያንዳንዱ ነገር የተሰራ ነው፡፡
አካላዊ ሁኔታ፡- ለባህሪ መለወጥ ምክንያት የሚሆንባቸው
አጋጣሚዎች ይኖራሉ፡፡
ለምሳሌ፡- በሚደክመን ጊዜ እና በህመም ስሜት በሚሰማን ወቅት
የባህሪ ለውጥ ልናሳይ እንችላለን፡፡
ሃይለ ስሜት፡- ውስጣዊ ፍላጎትን ፍቅርን ጥላቻን ሃዘንን ብስጭትን
ወ.ዘ.ተ ያመለክታል፡፡
ስልጠና፡- የተመረጠ አመራርና እቅድ ባለው መንገድ የሚከናወን
ድርጊት ሲሆን የሰውን ልጅ በሚፈልገው አካኃን ለማስተማር ያስቸላል፡፡
የአሽከርካሪዎች ሙያዊ ስነ- ምግባር
ሙያ (Profession) ፡- ሙያ ማለት በህብረተሰብ ውስጥ የተወደደና የተከበረ የስራ
መስክ ሆኖ በተወሰነ የዕውቀት መስክ በትምህርትና ስልጠና የሚገኝ ነው፡፡ ይህ ማለት
ሙያ በትምህርትና ስልጠና የተገኘውን ዕውቀት፣ክህሎትና አስተሳሰብን በመጠቀም
ለህብረተሰቡ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት የሚመመሰችል የስራ መስክ ነው፡፡

ስነ-ምግባር (Ethics) ፡- መልካሙንና መጥፎውን ለመለየት የሚያስችልና


መጥፎውን በመተው መልካሙን እንድንከተል የሚያባረታታ እሴት ነው፡፡
በተጨማሪም ለማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር አብሮ ለመስራትና ለመኖር አስፈላጊ
ነው፡፡

 የሙያ ስነ-ምግባር፡- ማለት ባለሙያው በተሰማራበት ሙያ የሚሰራውን ስራ


ውጤታማ እንዲሆን እንደተሰማራበት የሙያ አይነት አባላቱ በጥብቅ መከተል
የሚገባቸውን መርሆዎች እና ስነ-ስርዓቶችን ያመለክታል፡፡
ሙያዊ ስነ-ምግባራቸው አክብረው የሚያሽከረክሩ አሽከርካሪዎች

ከነዱ አይጠጡም ከጠጡም አይነዱም፤


ያለምንም እረፍት ከአራት ሰዓት በላይ አያሽከረክሩም፤
የእንቅፍ ስሜት በተሰማቸው ጊዜ ሙሉ እረፍት ይወስዳሉ፤
የተሳፋሪው ደህንነት የአሽከርካሪው ሃላፊነት መሆኑን ይገነዘባሉ፤
የመኪናቸውን ጠቅላላ አካል ይጠብቃሉ፤
የፍጥነት ወሰን ገደብን ያከብራሉ፤
ለእግረኛ ቅድሚያ ይሰጣሉ፤
ለትራፊክ መብራት ትዕዛዝ ተገቢውን ምላሽ ይሰጣሉ፤
የመንገድ ስነ-ስርዓት ምልክቶችንና ትዕዛዞችን ያከብራሉ፤
በህክምና ባለሙያ ታዝዞና በስራቸው ላይ ችግር እንደማያደርስ ካልተገለጻቸው
በስተቀር፤ መድሃኒት ወስደው አያሽከረክሩም፤
ስለጉዞዋቸው ዕቅድ ያወጣሉ፣ጊዜ ይቆጥባሉ የችግር መንስኤ እንዳይሆኑ
ይዘጋጃሉ፤
ለማሽከርከር አሽቸጋሪ በሆነ መንገድ መኪናቸውን አያሽከረክሩም፤
የመኪናቸው የተለያዩ ክፍሎች በአግባቡ መስራታቸውን
ከመንቀሳቀሳቸው በፊት ያረጋግጣሉ፤
በመታጠፊያ መንገዶች ላይ ብርቱ ጥንቃቄ ያደርጋሉ፤
የተሻለ የአየር ሁኔታ እስኪገኝ ድረስ አያሽከረከሩም፤
ሌሎችና ራሳቸውን ከአደገኛ ሁኔታወች ይከላከላሉ፤ጠንቃቃና አስተዋይ
ይሆናሉ፤ወዘተ
የአሽከርካሪዎች አላስፈጊ ባህሪያት
የሌላውን መንገድ የሚዘጉና ካለእነርሱ በስተቀር ሌላ የመንገዱ
ተስተናጋጅ እንደሌለ የሚቆጥሩ
ቅጣት ከሌለ በስተቀር ህግን በራሳቸው ተነሳሽነት የማያከብሩ
መግጨትና መጋጨትን በቀላሉ የሚመለከቱ
ማቆም የማይገባቸው ቦታ ላይ መኪናቸውን የሚያቆሙና ለአጠቃላይ
እንቅስቃሴ እንቅፋት የሚሆኑ
ካልጠጡ የማይነዱ
ልታይ ባይነት ከተቃራኒ ፆታ ጋር ተቀምጠው ከነዱ ጠቅላላ ህጎችን
በመሻር በማናለብኝነትና በእብጠት በመወጠር በከፍተኛ ፍጥነት
በማሽከርከር ልታይ ልታይ የሚያጠቃቸው
ጫት መቃምና ማጤስን በሚያሽከረክሩበት ወቅት የሚያዘወትሩ
ናቸው፡፡
በማሽከርከር ችሎታ ላይ የአልኮል መጠጥ ተጽዕኖ
 የአልኮል መጠጥ በማእከላዊው ስርአተ-ነርቭ ላይ የመደበት
ተጽእኖ ያደርሳል፡፡

 የአልኮል መጠጥ በደማችን ውስጥ በፍጥነት በመሰራጨት


የአእምሮአችንን ስራ(ተግባር) የሚቀንስ ሲሆን ውሳኔ የመስጠት
ብቃት፣ስሜትንና ባህሪይ ላይም ተጽእኖ ያደርሳል፡፡

 የአልኮል መጠጥ የአሽከርካሪውን

የማየት፣የማተኮር፣የማገናዘብ፣ውሳኔ የመስጠት ችሎታውንና


ቅልጥፍናውን በመቀነስ የትራፊክ አደጋ እንዲፈጠር ምክንያት
ይሆናል
የአልኮል መጠጥ ጠጥቶ የሚያሽከረክር አሽከርካሪ ባህሪያት
 በራሱ ረድፍ ውስጥ ያለመቆየት
 በከፍተኛ ፍጥነት ማሽከርከር
 በጣም ዝግ ባለ ፍጥነት ማሽከርከር
 ሰፋ ያለ ቦታ በመውሰድ መኪናን ማዞር
 ፍጥነት መቀነስና በማይታመን ሁኔታ ፍጥነት መጨመር
 ከጎንና ከፊት ለፊት ያለን መኪና በጣም ተጠግቶ ማሽከርከር
 በግዴለሽነትና ምልክት ሳያሳዩ መቅደም
 የመኪናውን የፊት መብራት በአግባቡ ሳያበሩ ማሽከርከር
 የመኪናውን መሪ የመቆጣጠር ብቃት በማጣት ረድፍን ይዞ ማሽከርከር
ያለመቻል ወ.ዘ.ተ
የአልኮል መጠጥና የትራፊክ አደጋ
 44% የሚሆነው አደጋ የሚደርሰው የአልኮል መጠጥ ጠጥተው በሚያሽከረክሩ
አሽከርካሪዎች ነው፡፡ስለዚህ <<ከጠጡ አይንዱ ከነዱ አይጠጡ>> የሚለውን
የትራንስፖርት ደንብ ማክበር በዘርፉ ለሚደርሰው አደጋ መቀነስ አስተዋፅኦ ይኖረዋል፡
የአልኮል መጠጥና ህግ
 ከትራንስፖርት ህጎችና ደንቦች መካከል ዋናውና አንዱ በአልኮል መጠጥ በመድሃኒት
ወይም በአደንዛዥ ዕፅ ተመርዞ ማሽከርከር ክልክል መሆኑ ነው፡፡
 ስለሆነም አልኮል መጠጥ ጠጥቶ ማሽከርከር በህግ የሚያስጠይቅና የሚያስቀጣ መሆኑን
ተረድቶ በጠጡ ወቅት ያለማሽከርከር ተገቢ መሆኑን መረዳት ይገባል፡፡
 የአልኮል መጠጥ በጠጡ ወቅት ያለማሽከርከር፡- መጠጥ ሊጠጡ ካሰቡ
1. በህዝብ ትራንስፖርት ወይም ታክሲ መጠቀም
2. ሌላ አሽከርካሪ ማለትም አልኮል መጠጥ ያልወሰደ መኪናዎትን እንዲያሽከረክር
ማድረግ
3. የጠጡበት ቦታ ማደር
4 . ሌላ አሽከርካሪ እንዲያደርስዎት ስልክ ደውሎ መጥራት
5 . የአልኮል መጠጥ መጠጣት አስፈላጊ መስሎ ከታየዎት ከቤቴሰቦና ከጋደኞችዎ ጋር
በመኖሪያ ቤት ለመጠጣት መሞከር

 በአልኮል መጠጥ የተመረዘ አሽከርካሪ ሲያጋጥምዎት ማድረግ ያለብዎት


ክንዋኔዎች

 በመጠጥ ተመርዞ የሚያሽከረክሩ ተሽከርካሪዎችን አለመጠጋት


 በተለይ ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት እስከ ምሽት 8፡00 ሰዓት ድረስ አልኮል መጠጥ
ጠጥተው
 የሚያሽከረክሩ አሽከርካሪዎች የሚበዙበት ሰዓት ስለሆነ የተለየ ጥንቃቄ ማድረግ
ተገቢ ነው፡፡
ሞገደኛና ክልፍልፍ አነዳድ
የሞገደኛና ችኩል ሾፌሮች የአነዳድ ባህሪ

 ሞገደኛ አነዳድ በተደጋጋሚ በመጥፎ ስሜት ውስጥ የማሽከርከር


ውጤት ነው ተብሎ ይገመታል፡፡
ከሞገደኛ የአሽከርካሪ ሂደት ጋር የተያያዘ የተለያዩ ችግሮች አሉ፡፡
 ከእነርሱም መካከል በዋናነት የሚከተሉት ናቸው፡፡
1. አልኮል አደንዛዥ ዕፅ ከባድ መድሃኒት ወስዶ በእንቅልፍ በድብርት
ወይም በከባድ ህመም እየተሰቃዩ ማሽከርከር
2. ተናድው ተቆጥተው ወይም እነኝህን መሰል ስሜት ውስጥ ሆነው
ማሽከርከር
3. በፍርሀት ውስጥ ሆነው ማሽከርከር
1. በጭንቀት ውስጥ ሆነው ማሽከርከር
2. በማሽከርከር ላይ እያሉ አትኩሮት በሌላ ነገር መውሰድ
3. በፍጥነት የማሽከርከር ሱስ ተይዞ ማሽከርከር
4. የትራፋክ ህግችን ያለማክበር የተሳሳተ ግምትና ማጠቃለያ መሰጠት
5. የግንዛቤ አለመኖርና የራሰን አነዳድ ስህተትቶች አለመቀበል

የሞገደኛ አነዳድ ፈርጆች


የሞገደኛ አነዳድ ሂደትን በሶስት ከፍሎች ማየት ይቻላል፡፡

1. ትእግስት ማጣትና ትኩረት አለመስጠት


2. ተፅእኖ የማድረግ ትግል
3. ግድሌሽነት እና የመንገድ ዳር ፀብ
1. ትእግስት ማጣትና ትኩረት አለመስጠት

የትራፊክ መብራትን አለማክበር ( ቀይ መብራት መጣስ)


የትራፊክ ቢጫ መብራት እየበራ ፍጥነት ያለመቀነስ
ያለ አግባቡ ረድፍን መቀየር ወይም መሽሎክሎክ
ከተፈቀደው ፍጥነት በላይ ማሽከርከር
ከፊለት ለፊት ያለን ተሽከርካሪ በጣም ተጠግቶ ማሽከርከር
አስፈላግዉን የትራፊክ ምልክት ለሌሎች አሸከርካሪዎች አለማሳየት
ፍጥነት በመጨመርና በመቀነስ ማሸከርከር
2. ተፅእኖ የማድረግ ትግል
ተሽከርካሪን ላለማሳለፍ መንገድ መዝጋት
በተሸከርካሪዎች መካከል ሊኖር የሚገባው ክፍተት ሌላ
ተሸከርካሪ እንዳይገባ መዝጋት
ለመበቀል ተሸከርካሪን በድንገት ማቌረጥ
በበቀል ስሜት በድንገት ፍሬን
. 3. ግድሌሽነት እና የመንገድ ዳር ፀብ

በአልኮል መጠጥ ተመርዞ ማሽከርከር


በጣም ከፍተኛ በሆነ ፍጥነት ማሽከርከር
በመንገድ ዳር መኪና በማቆም ማስፈራራት ወይም መደባደብ
 የሞገደኛ አሽከርካሪ ላለመሆን መደረግ የሚገባቸው ክንዋኔዎች
በጣም በደከሙ በተበሳጩ በተቆጡና እነኝህን መሰል ስሜት በሚሰማበት ወቅት
አለማሽከርከር
ወደሚፈልጉበት ቦታ በሰዓቱ ለመድረስ በቂ ጊዜ መመደብ
ከተቻለ የጉዞን ፕሮግራም በስራ መግቢያና መውጫ ሰዓቶች ላይ አለማድረግ
ሊያዘገይዎት የሚችል ጉዳይ መኖሩን በቅድሚያ በስልክ መግለፅ
አዝናኝና ለስላሳ ሙዚቃዎችን በተሸከርካሪ ውስጥ ድምጹን ዝቅ አድርገው በመክፈት
ማድመጥና ብስጭትዎን ማብረድ
ስሜትን መቆጣጠር ሞገደኛ አሽከርካሪ ሲጋጥምዎት ከመበቀል መቆጠብ
ለሌሎች ቅድሚያ መስጠት፣ጨዋ መሆን፣ለሰው ልጅ ክብር መስጠትና ይቅር ባይ
መሆን
ለሚያደርጉት እንቅስቃሴ ሁሉ ልብ ይበሉ

ሞገደኛ አሽከርካሪ ሲያጋጥሞዎት ማድረግ ያለብዎት ክንዋኔዎች

ረድፍን ላለመልቀቅ ሲሉ ፉክክር ውስጥ አለመግባት


ፀያፍ ስድቦችንና ምልክቶችን ችላ ማለት
የአይን ለአይን ግንኙነትን ማስወገድ
ሳይበሳጩ ዘና ብለው ሁኔታዎችን መከታተል
ችግሩን ሳያባብሱ በሰላም ለመጨረስ ጥረት ማድረግ
ሁኔታውን ለትራፊክ ፖሊስና ለህግ አስከባሪዎች ማሳወቅ
እይታዎን በሚያሽከረክሩበት መንገድ ላይ ማድረግ
ሶስቱ የማሽከርከር ባህሪያት ዘርፎች
1. የስሜት ባህሪ
2. የመገንዘብ (አእምሮአዊ) ባህሪ
3. የክህሎት ባህሪ

1.የስሜት ባህሪ፡- ፍላጎትን፤ አመለካከትን፤ እሴትን፤ መነሳሳትን እና


ማንኛውንም ግብ ያለመ የሰዎች ድርጊትን ያጠቃልላል፡፡
2.የመገንዘብ (አእምሮአዊ) ባህሪ፡- መረዳትን፤ ማሰብን፤ ምክንያትና
ማንኛውንም ውሳኔ መስጠትን እና የሰዎችን ድርጊት ማጤንን ያካትታል
3. የክህሎት ባህሪ፡- በአእምሮ አዛዥነትና በአካላችን እንቅስቃሴ የሚፈፀሙ
ማናቸውንም የክህሎት ባህሪያት ያካተተ ነው
 የማሽከርከር ባህሪ ስነ-ባህሪ ዘርፎች

1. ኃላፊት
2. ጥንቃቄ (ደህንነት)
3. ብቃት
1.ኃላፊት
ሀ/ ስሜታዊ ኃላፊነት ፡- ለሌሎች ማሰብና ስነ ምግባራዊነት
1. የስሜታዊ ኃላፊነት ጉድለት፡-ራስ ወዳድነትና ቅንነት የጎደለው አስተሳብ
ለ/ አእምሮአዊ ሃላፊነት፡- አዎንታዊ ህሊናዊ አስተሳሰብና አእምሮአዊ ጤንነት
1. የአእምሮ አዊ ሃላፊነት ጉድለት ፡- ራስ ወዳድነትና ቅንነት የጎደለው አስተሳብ
ሐ/ ክህሎታዊ ኃላፊት ፡-ደስተኝነትና እርካታ
1. የክህሎታዊ ኃላፊነት ጉድለት፡-ውጥረትና ድብርት
2. ጥንቃቄ (ደህንነት)
ሀ/ ስሜታዊ ደህንነት፡- እራስን ማዘጋጀትና ሚዛናዊነት (እኩልነት
1. የስሜታዊ ደህንነት ጉድለት፡-የሞገደኝነት ስሜትና በአጋጣሚዎች የመጠቀም ፍላጎት
ለ / አእምሮአዊ ደህንነት ፡- ሚዛናዊ መለያ ባህሪያት
1.የአእምሮአዊ ደህንነት ጉድለት፡- ሚዛናዊነት የጎደለው መለያ ባህሪያት
ሐ.ክህሎታዊ ደህንነት ፡-ትህትና የተሞላበት መግባባትና የመረጋጋት ስሜት
1. የክህሎታዊ ደህንነት ጉድለት ፡- ትህትና የጎደለው ምልልስ እና የተጋነነ አፀፋ
3 . ብቃት
ሀ/ ስሜታዊ ብቃት ፡-ደንብን ማክበርና ልበ ሙሉነት
1.የስሜታዊ ብቃት ማነስ ፡-ደንብና ስርአትን ያለማክብረና በራስ ያለመተማመን
ለ/አእምሮአዊ ብቃት፡- የማሽከርከር መርህዎችንና መረጃዎችን ማወቅና በአእምሮ መያዝ
1. አእምሮአዊ ብቃት ማነስ ፡-በመረጃ ያልተደገፈና የተዛባ አስተሳሰብ
ሐ/ ክህሎታዊ ብቃት :-ትክክለኛ ተግባርና ጠንቃቃነት (ንቁነት]
1.የክህሎታዊ ብቃት ማነስ :-ትክክለኛ ያልሆነ አካሄድና የትኩረት ማጣት
ሀ/ ስሜታዊ ኃላፊነት
ለሌሎች ማሰብና ስነምግባራዊነት

- ለማሽከርከር ተግባር ሃሳብና እንቅስቃሴ ስነምግባራዊና ሃይማኖታዊ


መመሪያዎችን መጠቀም
- በሌሎች ላይ አደጋንና ጉዳትን ላለመፍጠር መጠንቀቅ
- በአውራ ጎዳና ላይ ለሚጠቀሙ እግረኞች ግብ እቅድና እንቅስቃሴ
ስኬታማ እንዲሆን በቅንነት መተባበር
.
ለ. የስሜታዊ ኃላፊነት ጉድለት

ራስ ወዳድነትና ቅንነት የጎደለው አስተሳብ


በበቀለኝነት ስሜትና በሌሎች የአውራ ጎዳና ተጠቃሚዎች ላይ ጉዳት
የማድረስ ፍላጎት
በራስ ላይ የደረሰን ችግር በሌሎችም ላይ እንዲደስ መሻት
የሌሎች አውራ ጎዳና ተጠቃሚዎችን ስሜትንና መብትን መጣስና አቃሎ
ማየት
ጥፋትን አለማመንና ጥፋታችንን የሚነግሩን የሚያሳዩንን ሰዎች በጥላቻ
መመልከት
የመንገደኞችን ምቾትና ደህንነትን በቸልታ መመልከት
ለ/ አእምሮአዊ ሃላፊነት

 አዎንታዊ ህሊናዊ አስተሳሰብና አእምሮአዊ ጤንነት


 የራስንና የሌሎችን የማሽከርከር ተግባር ሊያስከትል የሚችለውን
ውጤት ቀድሞ መገመት ወይም በህሊና ማሰብ
መኪናን በማሽከርከር ሂደት ውስጥ ራስን ከአሉታዊ ስሜቶች ነፃ
ማድረግ

ሰዎችንና ንብረትን ከአደጋ የሚጠብቅና የሚከላለል የማሽከርከር


ምናባዊ እቅድን መከተል
ደህንነቱ ለተረጋገጠ የአሽከርካሪ ባህሪ እራስን ለማስገዛት መሰረታዊ
መረጃዎችን መጠቀም (ለምሳሌ፡- የአደጋዎችን መጠን የሚያሳይ መረጃ)
የአእምሮ አዊ ሃላፊነት ጉድለት
አሉታዊ ህሊናዊ አስተሳሰብና አደገኛ የሆነ ባህሪ
አደገኛ የሆነ የማሽከርከር ምናበዊ እቅድን መከተል
ትርጉም ለሌውና ለተሳሳተ የማሽከርከር ተግባር ዋጋ መስጠት (ለምሳሌ፡-
መቀደምን እንደሽንፈት መቁጠር)
ሌሎች አሽከርካሪዎች ይተቹኛል ያወግዙኛል የሚል አስተሳሰብን መያዝ
የሌሎች አሽከርካሪዎችን ባህሪ በአቌማቸውና በመኪናቸው ሁኔታ መገመትና
ዝቅ አድርጎ ማየት
በመኪናዬ ውስጥ ብቻዬን ስላለሁ ማንም አይከታተለኝም ብሎ ማሰብ
መኪና እያሽከረከሩ በቅዠትና በቀን ህልም ውስጥ መዘፈቅ
ሐ/ ክህሎታዊ ኃላፊት
ደስተኝነትና እርካታ
የአነዳድ ሁኔታ አካባቢውን ያገናዘበ ጥንቃቄየታከለበትን እንቅስቃሴ
መውደድ
በማሽከርከር ወቅት ከፍተኛ የሆነ ንቃትንና የተረጋጋ መልካም ስሜትን
ማዳበር
በማሽከርከር ወቅት ገቢና መልካም የሆኑ አዕምሮአዊ ተግባሮችን
መፈፀም(ለምሳሌ፡- ማቀድ እራስ መገምገምና መወሰን)
በመልካም ስሜት ውስጥ ሆኖ መኪናማሽከርከርወ.ዘ.ተ
 የክህሎታዊ ኃላፊነት ጉድለት
ውጥረትና ድብርት
የሀዘንና የድብርት ስሜት እንዲሁም ለማሽከርከር ኃይልና ፍላጎት በማጣት
በማሽከርከር ስራችን ላይ አሉታዊ ተፅእኖ እንዲያሳድር መፍቀድ
በማሽከርከር ሂደት ውስጥ በሰራናቸው ስህተቶች ምክንያት እራስ ዝቅ
አድርጎ ማየትና ለራስ ክብር መንፈግ
በማሽከርከር ሂደት መፍራት መጨነቅና አለመረጋጋት

2. ጥንቃቄ (ደህንነት)
ሀ/ ስሜታዊ ደህንነት
እራስን ማዘጋጀትና ሚዛናዊነት (እኩልነት)
ለሌሎች አውራ ጎዳና ተጠቃሚዎች ሚዛናዊ ለመሆን መሞከር
የሌሎች አሽከርካሪዎችን የማሽከርከር እንቅስቃሴ ላለማስተጓጎል ፍላጎት
ማሳየት
ሌሎች አውራ ጎዳና ተጠቃሚዎች ሊሰሩት የሚችሉትን ስህተት በማሰብ
ጥንቃቄና ሰፋ ያለ ግንዛቤ መውሰድ
 የስሜታዊ ደህንነት ጉድለት
 የሞገደኝነት ስሜትና በአጋጣሚዎች የመጠቀም ፍላጎት
 ሌሎች አሽከርካሪዎችን ለመቅደም እራስን በውድድር ስሜት ውስጥ ማስገባት
 በሌሎች የአውራ ጎዳና ተጠቃሚዮች ላይ የማውገዝና የቁጣን ስሜት
ማንፀባረቅ
 በሌሎች አሽከርካሪዎች ተግባር የመገለልና የመፍራት ስሜትን ማሳየት
 ሌሎች አሽከርካሪዎች አስገዳጅና ፈታኝ ሁኔታ ውስጥ እንዲገቡ መፈለግ
ለ / አእምሮአዊ ደህንነት
 ሚዛናዊ መለያ ባህሪያት
 ለሌሎች አውራ ጎዳና ተጠቃሚዎች ሃሳብና ባህሪ ሚዛናዊና ምክንያታዊ የሆነ
ገለፃ መስጠት
 ለራስ የማሽከርከር ተግባርና ስሜት ሚዛናዊ የሆነ ምክንያት መስጠት
 ነገሮችን (ሁኔታዎችን) ከሌሎች የአውራ ጎዳና ተጠቃሚዎች አንፃር
መመልከት
በምናሽከረክርበት አካባቢ እየተከናወኑ ያሉትን ክስተቶች ለመረዳት
ሁኔታዎችን መተንተን

የአእምሮአዊ ደህንነት ጉድለት


ሚዛናዊነት የጎደለው መለያ ባህሪያት
የሌሎች አሽከርካሪዎችን ባህሪይ በመረጃ ባልተደገፈ ሚዛናዊ ባልሆነና
መሰረት የለሽ በሆነ ሁኔታ መፈረጅ መመልከት
የራስን የማሽከርከር ባህሪና ጥፋት በተሳሳተ መንገድ መተርጎምና መከላከል
የራስን የማሽከርከር ጥፋት ወደ ሌሎች አሽከርካሪዎች ለማሳበብ መሞከር
ለሰራነው ጥፋት መከላከያ የሚሆንና አሳማኝ የሚመስል ምክንያቶችን
ለራስ ማቅረብ
በእግረኖችና በሌሎች የአውራጎዳናተጠቃሚዎችላይፀያፍየሆኑ ቃላቶችንና
ተግባሮችን ከመፈፀም እራስን መቆጠብ
 የክህሎታዊ ደህንነት ጉድለት
 ትህትና የጎደለው ምልልስና የተጋነነ አፀፋ
 ሌሎች የአውራ ጎዳና ተጠቃሚዎችን በቃል ወይም በምልክት መሳደብ
 ሌላ አሽከርካሪ ለሚያሳየው አግባብነት የሌለው ባህሪ ተመሳሳይ (የተጋነነ)
አፀፋ መስጠት
 ሌሎች የአውራ ጎዳና ተጠቃሚዎችን መተቸት መናቅና ማጣጣል
 መንገደኞችንና ሌሎች የአውራ ጎዳና ተጠቃሚዎችን አስገዳጅ ሁኔታ ወስጥ
ማስገባ
ሐ/ ክህሎታዊ ደህንነት
 ትህትና የተሞላበት መግባባትና የመረጋጋት ስሜት
 ፈታኝ ስሜትን ጎጂ በሆነ ሁኔታ ውስጥ ማረጋጋትና ግፊትን መቌቌም

3. ብቃት
ሀ/ ስሜታዊ ብቃት
ደንብን ማክበርና ልበ ሙሉነት
•በምናሽከረክርበት ወቅት ስህተትን ለማስወገድ መሞከርና ጠንቃቃ ለመሆን መጣር
•ለትራፊክ እንቅስቃሴ ደንብና ስርዓት ራስን ማስገዛት
•የትራፊክ ህጎችንና ደንቦችን ማክበር
•በትራፊክ መብራቶች እንድንቆም በሚያስገድዱ ምልክቶችና በትራፊክ
•መጨናነቅ ምክንያት እንቅስቃሴያችን ሲገታና ሲዘገይ በትዕግስት በጠበቅ
•በልበሙሉነትና በራስ መተማመን መንፈስ ማሽከርከር
የስሜታዊ ብቃት ማነስ
•ደንብና ስርአትን ያለማክብረና በራስ ያለመተማመን
•ለትራፊክ ደንብና ስርአቶች ለሚያስከብሩ አካሎች/ፖሊስናየትራፊክ አባላት/እንዲሁም
•ተቆጣጣሪ ሰራተኞች የጥላቻ ስሜትን ማዳበር
•በመደበኛ የማሽከርከር ሁኔታ ውስጥተስፋየመቁረጥናያለመረጋጋት ስሜትን ማሳየት
•በትራፊክ እንቅስቃሴ ሂደት ታጋሽ ያለመሆን
ለ/ አእምሮአዊ ብቃት

እውቀትና ግንዛቤ

የማሽከርከር መርህዎችንና መረጃዎችን ማወቅና በአእምሮ መያዝ

በማሽከርከር ሂደት ሌሎች አሽከርካሪዎችና ራሳችን የሰራናቸውን


ስህተቶች ልብ ማለትና ማስታወሻ መውሰድ

የማሽከርከር አንቅስቃሴዎችን ስሜታችንንና ሃሳባችንን በሚገባ ማወቅ


ወ.ዘ.ተ…
የአዕምሮአዊ ብቃት ማነስ
በመረጃ ያልተደገፈና የተዛባ አስተሳሰብ
መንገዱ በሚፈቅደው የፍጥነት ልክ /ወሰን / መሰረት ማሽከርከር
መንቀርፈፍ እንደሆነማሰብ ፡፡
መንገዱ በሚፈቅደው የፍጥነት ገደብ መሰረት ከማሽከርከር ይልቅ ትራፊክ
ፖሊሶች በሉበት ቦታ ፍጥነትን ለመቀነስ በማሰብ ማሽከርከር ፡፡
መንገዱ በሚፈቅደው የፍጥነት ልክ ማሽከርከር በፍጥነት ከማሽከርከር
ይልቅ ለአደጋያጋልጣል ብሎ ማሰብ ፡፡
ቢያንስ ከ15-25 ኪሎሜትር ከተፈቀደው ፍጥነት በላይ ማሽከርከር
የተለመደና መደበኛየሆነአካሄድ እንደሆነ ማሰብ ፡፡
ትክክለኛ የሆነ የማሽከርከር እንቅስቃሱን እያከናወንን አካሄድ ትክክል
አይደለም የሚልአስተሳሰብ መያዝ ፡፡
የማሽከርከር ጥበብ የረዥም ጊዜ ትምህርትና ተከታታይ የብቃት ማሻሻያ
ስልጠና የሚፈልግ አይደለም ብሎ ማሰብ ፡፡
ሐ/ ክህሎታዊ ብቃት
 ትክክለኛ ተግባርና ጠንቃቃነት (ንቁነት
በተለመደ የማሽከርከር ሁኔታ ውስጥ ትክክለኛ የማሽከርከር ተግባራትን
ማከናወን ፡፡
ለትራፊክ ምልክቶችና ለሌሎች የአውራ ጎዳናው ተጠቃሚዎች እንቅስቃሴ
ትኩረት መስጠት ፡፡
የአካባቢውን ትራፊክ እንቅስቃሴ ፍሰት በመከተል የፍጥነት ገደብን ሳያልፍ
ማሽከርከር :
ለጥንቃቄና ራስን ለመቆጣጠር የሚያግዙ አባባሎችንና ቃላቶችን በመጠቀም
የማሽከርከር እንቅስቃሴያችንን መፈተሸ፡፡
በማሽከርከር ሂደት ውስጥ ለምናገኛቸው መልካምና አስደሳች ነገሮች
አድናቆት መስጠት
የክህሎታዊ ብቃት ማነስ
ትክክለኛ ያልሆነ አካሄድና የትኩረት ማጣት
በመደበኛ የማሽከርከር ሁኔታ ውስጥ ትክክለኛ ያልሆነና ህገወጥ ተግባርን
መፈፀም ፡፡
ያለበቂ አትኩሮትና በሌላ ሐሳብ ተጠምዶ ማሽከርከር ፡፡
የትራፊክ ምልከቶችን ያለማየትና የአካባቢውን የትራፊክ እንቅስቃሴ
በትኩረት ያለመከተል ፡፡
1.መልካም ያልሆነ ስሜትን መቆጣጠር
በማሽከርከር ሂደት ውስጥ መጥፎ ስሜቶችንን መቆጣጠር በሌሎች
የመንገድ ተጠቃሚዎችና በራሳችን ህይወት ላይ እንቅፋት ከመሆን
መቆጠብ አለብን
ሰለዚህም ፡-
የማሽከርከር ልምዳችን ጥሩ ስሜቶችን እንዲያጎለብት እንጂ መጥፎ
ባህሪያትን እንዲያጠናክር ዕድል ያለመስጠት ፣

ስሜትን ለመቆጣጠር ለስራችን ጥሩ ፍቅር እንዲኖር ማድረግ ፤


መልካም ያልሆኑ ስሜቶችን የሚቀሰቅሱ ሁኔታዎችን ለይቶ ማወቅ ፤
ስሜታችንን ተቆጣጥረን ማሽከርከር በማንችልበት ሁኔታ ውስጥ
ስንገባስሜታችንን መቆጣጠር እስከምንችልበት ጊዜ ድረስ
ያለማሽከርከር ናቸው
2. ጥቃቅን የማሽከርከር ስህተቶችን ልምድ ያለማድረግ
በየዕለቱ የማሽከርከር ስህተት ላለመፈፀም መሞከር ፤ ከስህተቶቻችን
ለመማር በመሞከር ተመሳሳይ ስህተት ያለመፈፀም ፡፡
የማሽከርከር ስህተት እየፈፀምን አደጋ ባነማድረስ የማሽከርከር
ስልቶታችን ትክክል እንደሆነ አድርጎ የመውስድ ባህሪን ማረም ፡፡
አንድን የማሽከርከር ስህተት ፈፅመን አደጋ ባለማድረሳችን ብቻ ስህተትን
የመደጋገም ልምድእንዳናዳብር ጥንቃቄ ማድረግ ፡፡
የተደጋገሙ ጥቃቅን የማሽከርከር ስህተቶች ተጠራቅመው ወደ አላስፈላጊ
የማሽከርከር ባህሪ እንዳያመራን ጥንቃቄ ማድረግ ፡፡
3. እራስን የማረሚያ ዘዴ
እራስን በራስ የመለወጥ ሶስት ደረጃዎች እንደሚከተለው
ተዘርዝረዋል፡፡ መጠንቀቅ /መመስከር /መቀየር

ደረጃ አንድ፡- አሽከርካሪው እኔ ይህ አሉታዊ ልማድ አለኝ ብሎ መጠንቀቅ


(Acknowledging)፣
ደረጃ ሁለት፡- አሽከርካሪው አሉታዊውን ልማድ ሲፈፅም በራሱ መመስከር
(witnessing)፣
ደረጃ ሦስት፡- ይህን አሉታዊ ልማድ መቀየር (modifying) ናቸው
4. ወደ አላስፈላጊ የማሽከርከር ባህሪ የሚገፋፋ ሁኔታዎችን ማስወገድ
አሽከርካሪዎች በትራፊክ ፍሰት ውስጥ ለመንገድ ደህንነት ተገቢውን
ጥንቃቄ ባለማድረግ በገበያ ፣ በንግድ ሁኔተእና በመሳሰሉት ጉዳዬች
መገፋፋትን ማሰስወገድ ይገባቸዋል ፡፡
አሽከርካሪዎች የስራ ባልደረባንና የጓደኛን መልካም ያልሆነ የማሽከርከር
ባህሪ አለመቅሰም ይጠበቅባቸዋል
በትራፊክ ፍሰት ውስጥ የመንገድ ተጠቃሚዎች ፍላጎት እንደሚለያይ
መረዳንትና ይህ ፍላጎት ከአሽከርካሪው ፍላጎትና ከመንገድ ደህንነት ጋር
የሚፃረር ሊሆን ስለሚችል ጥንቃቄ ማድረግ
5. ለራስህ ህይወት ዋጋ በመስጠት አደጋን ለመቀነስ መጣር
የአሽከርካሪዎች ግጭትቢደርስ የሚከሰተውን ስነ-ባህሪያዊ ፣ማህበራዊና
ኢኮኖሚያዊ ቀውስ በመገመት ጥንቃቄ ማድረግ ፡፡
ሲያሽከረክሩ አደጋን ለመከላከል በሚያስችል መልክ መሆኑን ማጤን ፡፡
ግድየለሽ የሆነ የማሽከርከር ሂደት የሚያደርሰውን ጉዳት በሚገባ ሁኔታ
አስቀድም ማሰላሰል ፡፡
አሽከርካሪው ለራሱ ፣ ለቤተሰቡ ፣ ልሀብረተሰቡና ብሎም ለሐገሪቱ
ከሚሰጠው
ጠቀሜታ አኳያ ለራሱ ህይወት ዋጋ መስጠትና ለራሱና ለቤተሰቡ
መሳሳትይገባዋል ፡
ራስን ከአደጋ ለመከላከል ቃል መግባት፤ ለተግባራዊነቱም በፅኑ
መንቀሳቀስ ይገባል::
6. ውጤታማ የመግባባት ክህሎትን ማዳበር
በሀሳብ መግባባት ለሰው ልጅ እርስ በእርስ ግኑኝነት መሰረት
ነው ፡፡ በመሆኑም ከሌሎች ጋር ብቃት ያለው ግንኙነት መፍጠር
በጣም አስፈላጊ ከሆኑት የህይወት ክህሎቶች ውስጥ አንዱ ነው ፡፡
ይህም የማዳመጥ ክህሎትንና ሌሎች እንዴት እንደሚገቡ
መረዳትን ያካትታል ፡፡ ውጤታማ መግባባትን በማከናወን የእርስ
በእር ግኑኝነትን ለማሳከት የሚከተሉትን የመግባቢያ ክህሎቶች
ማዳበር ይበጃል
መቻቻል ፡- የማንኛውንም ወይም የማንስማማበትን አመለካከት ፣
የአኗኗር ዘይቤ ፣ እምነት ፣ወዘተ ለመፍቀድ ዥግጁ መሆን ፡፡
ማካፈል ፡- አንዳንድ ነገር በጋራ ለማከናወን ከሌሎች ጋር መሳተፍ ፡፡ በሌላ
አነጋገር ያለህን ነገር ሌለሌላ እንዲጠቀም ፈቃደኛ መሆን ፡፡
አዛኝ መሆን ፡- ሌሎች ሰዎች ችግር ሲያዳጥማቸው ችግሩን እንደራስ
በማየትና በመገንዘብ የሚቃለልበትን መንገድ መፈለግን ያካትታል ፡፡
አፈፃፀሙም እነሱን በመናቅ ወይም በማውገዝ ሳይሆን ይልቁንም
ችግራቸውን በመካፈል መሆን ይገባዋል ፡፡
መደራደር ፡- ስሜትን የሚጎዱና እራስን ከአደጋ ላይ የሚጥሉ ሁኔታዎችን
የመቋቋም ችሎታ ነው ፡፡ ለምሳሌ በእርስ በርስ ግንኙነትና በቢጤ ግፊት
ወቅት የራስን አቋም ግልፅ በማድረግ የጋራ ግንዛቤ ከሚመለከተው ስው
ጋር በመያዝ ወደ ስምምነት የመድረሻ መንገድ ነው ፡፡ በሌላ አነጋገር
ሁለት ወገኖች አንዳንድ ጉዳዬችን በመተው የነበራቸውን ያለመግባባት
ሁኔታ ማስወገጃ ስልት ነው ፡፡
በአጠቃላይ የአሽከርካሪዎች ግንኙነት መጠናከርና ቀና
አስተሳሰብ መኖር ለትራፊክ ፍሰቱ ጤናማ መሆንና ለአደጋ
መቀነስ በጎ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ፡፡ ሌሎች አሽከርካሪዎችን
በሚረዱት መልኩ ማሽከርከር መልምካ ስነ- ምግባርን ፤ ጥሩ
ስሜትን ፤ በራስ መተማመንና ጤናን ያጠነክራል

አመሰግናለሁ!

You might also like