Professional Documents
Culture Documents
1
1
በደብረ ፍስሃ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 2
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
መግቢያ..................................................................................................................................................................................................................................5
ምዕራፍ 1፡- የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ትምህርት ........................................................................................................................................7-13
1.1 የቃሉ ትርጉም......................................................................................................................................................................................................7
1.2 የመጽሐፍ ቅዱስ ቅድስና.....................................................................................................................................................................................8
1.3 መጽሐፍ ቅዱስን ከሌሎች ቅዱሳት መጻሕፍት ልዩ የሚያደርጉት ነጥቦች.....................................................................................................9
1.4 የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅም......................................................................................................................................................................................10
1.5 መጽሐፍ ቅዱስ በነማን፣ መቼ፣ በምን ቋንቋ፣ በየት ቦታ ተጻፈ? ....................................................................................................................11
1.6 የመጽሐፍ ቅዱስ ከቋንቋ ወደ ቋንቋ መተርጎም.................................................................................................................................................11
1.7 የመጽሐፍ ቅዱስ ቁጥር /ቀኖና/cannonization..............................................................................................................................................12
1.8 የምዕራፍ አንድ የክለሳ ጥያቄዎች........................................................................................................................................................................13
በደብረ ፍስሃ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 3
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
በደብረ ፍስሃ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 4
መግቢያ
ከእግዚአብሔር ከአምላካችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሠላም ለእናንተ ይሁን!!! የተወደዳችሁ እና
የተከበራችሁ ተማሪዎች በዚህ ክፍለ ትምህርት እግዚአብሔር ለእኛ ፍቃዱን የገለጠበትንና እኛ ልጆቹ እንመራበት
ዘንድ የሠጠውን ቅዱስ መጽሐፍ (መጽሐፍ ቅዱስ) ምንነት እና አጠቃላይ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ የቅድስት
ቤተክርስቲያንን አስተምህሮ በስፋት ለመመልከት እንሞክራለን፡፡ ከዚያ አስቀድሞ ለመነሻነት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ
ሺኖዳ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ የጻፉትን ጽሑፍ ለመግቢያነት እንመልከት፡-
“መጽሐፍ ቅዱስ የመጽሐፎች መጽሐፍ ነው፡፡ እውነትም ታላቅ መጽሐፍ ነው፡፡ መጽሐፍም ሲባል
የእግዚአብሔር መጽሐፍ ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ቃሉ ነው፡፡ በእርሱ አንተን ይናገርበታል፡፡ መጽሐፍ
ቅዱስ በእግዚአብሔር የተገለጠና በቅዱሳን ነቢያትና ሐዋርያት አንደበት የተነገረ እውነት ነው፡፡1 ጥቅሙም
እንድትማርበት፣ ለእግዚአብሔር የቀና ልብ እንዲኖርህ በአጠቃላይ የፈጣሪህን ፍቃድ ተከታይ እንድትሆን ለማድረግ
ነው፡፡2 መጽሐፍ ቅዱስ ለአንተ ከእግዚአብሔር የተላለፈልህ መልእክት ነው፡፡ በዚህ ከአምላኩ ከእግዚአብሔር
በመጣለት መልእክት ደስ የማይለው ማን ነው? በአንድ ወቅት ታላቁ ቅዱስ አባት አባ እንጦስ ከንጉስ ቆስጠንጢኖስ
የተላከ ደብዳቤ ደረሰው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም አባታቸው የንጉስ ደብዳቤ ስለደረሰው እጅግ በጣም ተደሰቱ እርሱ ግን
ምንም የተለየ ግምት ሳይሠጠው ወደ ጎን አለው፡፡ አሁንም ተማሪዎቹ በመደነቅ ብዛት ለማንበብ በጣም ጓጉ አባ
እንጦስ ግን ‹‹ልጆቼ ከሠው ለመጣ ደብዳቤ እንዴት እንደዚህ ደስ ይላችኋል? እነሆ የነገስታት ንጉስ እግዚአብሔር
የብዙ ብዙ ደብዳቤዎችን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ልኮልናል ለምን በዚህ መልዕክት አትደሠቱም? ለማንበብስ
እንዴት አልጓጓችሁም?›› ብሎ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ካስተማራቸው በኋላ ደብዳቤውን አነበበ፡፡ ለንጉሱም
የሚያስፈልገውን የበረከት መልስ ሠጠው፡፡ አንተስ ከምትወደውና ከምትናፍቀው ሰው ደብዳቤ ቢደርስህ እጅግ
ተደስተህ በየሰዓቱ ታነበው የለምን? ከሆነ ደግሞ ከእግዚአብሔር ለመጣልህስ ይህን ያህልና የበለጠ መደሰትና
መጓጓት በየሠዓቱ ማንበብ አይገባህም ነበር? ይህ ከእግዚአብሔር ወደ አንተ የተላከው መልእክት በመንፈስ ቅዱስ
የተቃኘ ይመራቸው የነበሩ ነብያት የተነገረ እና ቃሉ ራሱ በመንፈስ ቅዱስ የሆነ መልእክት ነው፡፡ ይህን ደግሞ
በውስጡ ባለው መንፈስና ሕይወት መረዳት ትችላለህ፡፡ ጌታችንም ‹‹እኔ የነገርኳችሁ ቃል መንፈስ ነው ሕይወትም
ነው››3 ሲል ተናግሯል፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ ተመግበኸው ሕይወት እንድታገኝበት ከእግዚአብሔር የተሠጠህ መንፈሳዊ ምግብ ነው፡፡
ጌታችን ዲያቢሎስ ሊፈትነው በቀረበው ጊዜ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጠቅሶ እንደተናገረው ‹‹ሰው ከእግዚአብሔር አፍ
በሚወጣው ቃል እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም››4 እናም ለስጋዊ ሕይወትህ የሚሆን ስጋዊ ምግብ ትመገባለህ
እንዲሁም በውስጥህ የማይሞት የማይበሰብስ መንፈስ ስላለ መንፈሳዊውንም ምግብ መጽሐፍ ቅዱስን መመገብ
እና ሕይወትን ማግኘት አለብህ ‹‹እውነት እውነት እላችኋለው ቃሌን የሚሠማ የላከኝንም የሚያምን የዘላለም
ሕይወት አለው›› ዮሐ 5፡24 እናም ወንድሜ ሆይ መኖር የምንችለው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ባለው የሕይወት
ቃል ጭምር እንጂ በእንጀራ ብቻ እንዳልሆነ እርግጠኛ ሁን ‹‹የዕለት ምግባችንን ስጠን ዛሬ››5 እያልን ስንጸልይም
የሕይወት ምግባችንንም የሚያጠቃልል እንደሆነና ስለ ስጋችን ብቻ እንደማትጠይቅ ልብ ልንል ይገባል.... እናም
ዘወትር ቃሉን አጥናው!!! ሁሌም አትርሳው!!! ይህ የበጎ ነገር መጀመሪያ ነውና!!!
1
2ጴጥ 1፡21
2
2ጢሞ 3፡16
3
ዮሐ 6፡63
4
ዘዳ 8፡3፣ማቴ 4፡4
5
ማቴ 5፡11-12
6
ጉዞ ወደ እግዚአብሔር ከገጽ 24-27
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
በማለት አባታችን አቡነ ሺኖዳ መጽሐፍ ቅዱስ ምን እንደሆነና በሕይወታችን ያለውን የጎላ ድርሻ በማስረዳት
ዘወትር ልናነበው እንደሚገባ ይስረዱናል፡፡ ከዚህ በመቀጠልም የነፍስ ምግብ ስለሆነው መጽሐፍ ቅዱስ በዝርዝር
በዚህ ክፍለ ትምህርት የምንመለከት ይሆናል፡፡ ሰው ሁሉ ለመንገዱ ብርሃን ይሆንለት ዘንድ ነፍስም ሕይወትን
አግኝታ እንድትኖርበት ነብያቱንና ሐዋርያቱን ያናገረ የተናገሩትንም በመጽሐፍ እንዲጽፉት ያደረገ አምላካችን
ምስጢርና ጥበቡን ይገልጥልን ዘንድ የእርሱ በጎ ፈቃድ ይሁንልን!!!
መልካም ትምህርት
ተከታታይ ትምህርት ክፍል
ማሳሰቢያ
ውድ ተማሪዎች በማስተማሪያ ኖቱ ላይ ማብራሪያ ሀሳቦችንና መጣቀሻ መጻሕፍትን በግርጌ ማስታወሻ
ላይ ያሠፈርን በመሆኑ በትምህርቱ ላይ ከግርጌ ስር ካለው ማጣቀሻ ጋር በማጣቀስ እንድታነቡ
በምዕራፉ መጨረሻ ያሉትን የክለሳ ጥያቄዎች እንድትሰሩ በጥያቄዎቹም ላይ ማብራሪያና ምላሽ
እንደዲሰጡ የምትፈልጓቸውን ጥያቄዎች ለመምሕራቹ በማቅረብ ማብራሪያ እንዲሰጡባቸው
እንድታደርጉ
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 6
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ምዕራፍ 1
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ትምህርት
በአንድ ጥራዝ ስር የተሰበሰበ ጽሑፍን ሲገልጽ ቅዱስ8 የሚለው ቃል ደግሞ የግዕዝ ቃል ሲሆን የተለየ፣የተከበረ፣…
የሚል የአማረኛ ትርጉምን ይሠጠናል፡፡ ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስ ማለት በአንድ ጥራዝ ስር የተሰበሰበ የተለየ፣
የተከበረ ጽሁፍ ማለት ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ማለት የተለየ፣ የተቀደሰ እና የተከበረ ዘመን የማለውጠው
ዓለማዊውም ሆነ መንፈሳዊው ዓለም በስፋት የተዳሰሰበት ቀዋሚ የሆነ ገጽታ ያለው ጾታ ዕድሜ እና ነገድ
የማይለየው ለሰው ልጆች ሁሉ የተሠጠ መጽሐፍ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም መጽሐፍ ቅዱስ ብቻዉን መቆም
የሚችል እዉነት ነው፡፡ ይህ ማለት የትኛዉም እዉነት በመጽሐፍ ቅዱስ ይረጋገጣል እንጂ መጽሐፍ ቅዱስን
ማረጋገጥ የሚችል ሌላ እዉነት የለም፡፡
ከዚህ ዉጪ መጽሐፍ ቅዱስ ምንድን ነው ለሚለው ጥያቄ መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ለህዝቡ
ያስተላለፈው ቅዱስ ቃል ነዉ የሚለዉ ምላሽ ነው፡፡ የእግዚአብሔር ቃል ደግሞ፡-
ሀ. የመንፈስ ምግብ ነዉ
“ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም”
ማቴ 4÷4፣ ዘዳ 8፡3
“ቃልህ ተገኝቷል እኔም በልቼዋለሁ አቤቱ የሠራዊት አምላክ ሆይ በስምህ ተጠርቻለሁና ቃልህ
ሐሤትና የልብ ደስታ ሆነኝ” ኤር 15፡16
“የሰው ልጅ ሆይ ያገኘኸውንም ብላ ይህንንም መጽሐፍ ብላ ሄደህም ለእስራኤል ቤት ተናገር አለኝ
አፌንም ከፈትኩ መጽሐፉንም አጎረሰኝ እርሱም፡- የሰው ልጅ ሆይ አፍህ ይብላ በምሰጥህም በዚህ
መጽሐፍ ሆድህን ሙላ አለኝ እኔም በላሁት በአፌም ውስጥ እንደማር ጣፈጠ” ሕዝ 3÷1-3
“ቃልህ ለጉሮሮዬ ጣፋጭ ነው ከማርና ከወለላ ይልቅ ለአፌ ጣፈጠኝ” መዝ 118÷103
ለ. ብርሃን ነዉ
“ሕግህ ለእግሬ መብራት ለመንገዴም ብርሃን ነው” መዝ 118÷105
ሐ. ህያዉና የሚሰራ ነዉ
“የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና የሚሠራ ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው
ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምን እስኪለይ ድረስ ይወጋል የልብንም ስሜትና ሀሳብ
ይመረምራል” ዕብ 4÷12
መ. ዘላለማዊ ነዉ
7
መጽሐፍ ቅዱስ በግሪክ ቋንቋ “ቢብሎስ/ Byblos/ ወይም “ግራፌ ከሚል ቋንቋ የተገኘ ሲሆን ቢብሎስ ማለት ከኒቂያ ወደቦች መካከል ከቤይሩት 25
ማይል ርቆ የሚገኝ ከተማ ሲሆን በዛች ከተማ ለመጻፍ የሚያገለግል “ፓፒረስ/ደንገል የተባለው ተክል እንደ ወረቀት አድርገው የሚሠሩበት ቦታ ነው፡፡
ቦታውንም መጀመሪያ ግሪኮች “ቢብሎስ ብለው ይጠሩት ነበር፡፡ ከረጅም ጊዜ ቆይታ በኋላ ግን ስያሜው ለመጽሐፍ ቅዱስ ብቻ መጠቀም ጀመረ፡፡
በላቲን ደግሞ “ስክሪፕቸር/ የሚል ስም ሲኖረው ይህም ለሁሉም ጽሑፍና መጽሐፍ ማመላከቻ ሆኖ ከቆየ በኋላ ለመጽሐፍ ቅዱስ ማመላከቻ ብቻ
ሆኖ ከጊዜያት በኋላ ተቀይሯል፡፡ በኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ቅዱሳት መጻሕፍት ደግሞ በተለይ በፍትሐ ነገስት ላይ “መጻሕፍት አምላካውያት”ተብሎ ይጠራል፡፡
8
ቅዱስ የሚለው ቃል በዕብራይስጥ “ክዳሽ ፣ በሱርስት “ካዲሽ የሚሉትን ቃላት ይተካልናል፡፡
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 7
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
9
2ጢሞ 3፡15
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 8
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
እናም የተወደዳችሁ ተማሪዎች ከላይ በዝርዝር የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎችን በመጥቀስ ለመግለጽ
እንደሞከርነው መጽሐፍ ቅዱስን ለመጻፍ የእግዚአብሔር አነሳሽነት እና ገላጭነት እንደሚያስፈልግና መጽሐፍ
ቅዱስ እግዚአብሔር በጠራቸው እና በመረጣቸው ቅዱሳን ሠዎች በእግዚአብሔር ገላጭነት የተፃፈ መጽሐፍ
በመሆኑ ቅዱስ ሊባል ችሏል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ መጽሐፍ ቅዱስን ቅዱስ ያስባለው፡-
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 9
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ከዚህ በተጨማሪ መጽሐፍ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት በቅዱሳን ሰዎች የተጻፈ ቅዱስ መጽሐፍ
በመሆኑ የሚያነቡትን፣ የሚያጠኑትን እና ለጸሎት የሚጠቀሙበትን ሁሉ የሚቀድስ መጽሐፍ ነው፡፡
“በእውነት ቀድሳቸው ቃልህ እውነት ነው” ዮሐ 17፡17
“ከቃሉ ጋር አጽንቶ እንዲቀድሳት ራሱን አሳልፎ ሰጠ” ኤፌ 5፡26
10
ኢዮብ 11፡7-10
11
መዝ 65(66)፡3
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 10
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
መጽሐፍ ቅዱስ በዕብራይስጥና በጽርዕ ቋንቋ የተጻፈ ሲሆን ከእነዚህ ቋንቋዎች ወደ ተለያዩ ቋንቋዎች
በተለያዩ ጊዜያት ተተርጉሟል፡፡ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት በ284 ዓ.ዓ የንጉስ በጥሊሞስ ዘመን በሰባው ሊቃውንት
አማካይነት ከዕብራይስጥ ወደ ጽርፅ ቋንቋ ተተርጉሟል፡፡ በዘመነ አዲስም መጽሐፍ ቅዱስ ወደ ተለያዩ ቋንቋዎች
ተተርጉሟል፡፡ ከእነዚህም መካከል፡-
ወደ ላቲን በአባ ጄሮም በ420 ዓ.ም
ወደ እንግሊዘኛ በዊክሌፍ /1329-1384/ እና ቴንዴል /1494-1536/
ወደ ጀርመንኛ ደግሞ በ1545 ዓ.ም ተተርጉሟል፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ በአሁን ሰዓትም ከ200 በላይ በሚሆኑ ቋንቋዎች ተተርጉሟል፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያም ህገ
ኦሪትን ከእስራኤል ቀጥላ ከዓለም ሁሉ አስቀድማ በፈቃዷ የተቀበለች ሃገር ናት፡፡ በዚህ እግዚአብሔር በሰጣት
12
የሶሪያ ቋንቋ ነው
13
ዕብራይስጥ የዕብራውያን ቋንቋ ሲሆን በ2ነገ 18፡26 ላይ “የአይሁድ ቋንቋ ተብሎ ተገልጧል
14
የግሪክ ቋንቋ ነው
15
የሮማውያን ቋንቋ ነው
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 11
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ረጅም የሃይማኖት ዘመን ብዙ ቅዱሳት መጻሕፍትን ወደ ቋንቋዋ ተርጉማለች ይኸውም በ980 ዓ.ዓ ገደማ
ከመጀመሪያው የብሉይ ኪዳን መጽሐፍ እስከ ንጉስ ሰለሞን ዘመን ድረስ የተጻፉት መጻሕፍት በቀዳማዊ ምኒሊክ
አማካኝነት መጥተው ከዕብራይስጥ ወደ ግዕዝ ቋንቋ ተተርጉመዋል ከዚህ በኋላ የተጻፉት ደግሞ በምርኮ ዘመን
በስደት ከኢየሩሳሌም ወደ ኢትዮጵያ በመጡ አይሁዳውያን ነገስታቱ እየተጻጻፉ በመላላክና እንደ ኢትዮጵያዊው
ጃንደረባ16 ኢየሩሳሌም ተሳልመው የሚመለሱ አበው ይዘው እየመጡ ተተርጉመዋል፡፡ በአዲስ ኪዳንም፡-
በ330 ዓ.ም በአባ ሰላማ17 ከሱርስት፣ ከዕብራይስጥና ከጽርዕ ቋንቋዎች ወደ ግዕዝ ቋንቋ ተተርጉሟል፡፡
ከ480 ዓ.ም ዘጠኙ ቅዱሳን18 ወደ ኢትዮጵያ ተሰደው ከገቡ በኋላ ግዕዝን ተምረው በአቡነ ሰላማ
የተወጠነውን በተለይም አዲስ ኪዳንን ከጽርዕና ከሱርስት ወደ ግዕዝ ተርጉመዋል
ከዚያም አባ ሰላማ ዘአዜብ /መተርጎም/ ከ1343-83 ዓ.ም/ ከሰባው የአይሁድ ሊቃውንት ትርጉም ጋር
በማነፃፀር ክለሳ አድርገው ከአብረኛ ወደ ግዕዝ ሙሉ ትርጉም ተረጉሙ፡፡
ወደ አማረኛም በአባ አብርሃም19 በተባሉ መነኩሴ አማካይነት ከ1808ዓ.ም እስከ 1818ዓ.ም ባለዉ
አስር አመታት ዉስጥ ተተርጉሟል፡፡
በአለቃ ተወልደ መድኀን አማካይነት ወደ ትግረኛ ሲተረጎም በአናሲሞስ አማካይነት ደግሞ ወደ
ኦሮምኛ ተተርጉሟል፡፡
በዚህ መሰረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በቀኖናዋ መሰረት 81 መጻሕፍትን ትቀበላለች፡፡
/ፍት.ነገ.አን 2/ እነዚህም 46 የብሉያትና 35 የሀዲሳት መጻሕፍት ናቸዉ፡፡ ከቤተክርስቲያን ውጪ ያሉ እምነቶችን
ብንመለከት አይሁድ 39 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን ሳምራውያን 5ቱን የሙሴ መጻሕፍት ሲቀበሉ የካቶሊክ
እምነት 73 የግሪክ ኦርቶዶክስ 76 ፕሮቴስታንት 66 እንዲሁም የራስል ተከታዮች /ጆሆሻውያን/ የ1000 ቃላት
እርማት አድርገው 66 መጻሕፍትን ይቀበላሉ፡፡
16
ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ባኮስ ሲባል ታሪኩን በሐዋርያት ሥራ 8፡27 እናገኘዋለን፡፡
17
አባ ሰላማ ከሶሪያ ወደ ኢትዮጵያ የመጡ አባት ናቸው፡፡ ወደ ኢትዮጵያ ከመግባታቸው በፊት ፍሪምናጦስ ይባሉ ነበር፡፡ በኢትዮጵያም መጽሐፍ ቅዱስን ወደ
ግዕዝ ከመተርጎማቸውም በተጨማሪ ነገስታቱን ኢዛናንና ሳይዛናን በማጥመቅ ክርስትና የመጀመሪያው ሃይማኖት እንዲሆን አድርገዋል፡፡ ወንጌል በኢትዮጵያ
እንዲስፋፋ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ኤጲስ ቆጶስ ሆነው በቅዱስ አትናቴዎስ እጅ ተሹመው በመምጣት ታላላቅ ገዳማትን በመገደም የመጀመሪያው ትምህርት
ቤት /ቤተ ቀጢም/ በማቋቋም በኢትዮጵያ ወንጌል እንዲስፋፋ በማድረጋቸው “ከሳቴ ብርሃን ወይም “ብርሃን ገላጭ ተብለው ተጠርተዋል፡፡
18
ወይም ተሰዓቱ ቅዱሳን
19
ሌላኛው ስማቸው አባ ሮሜ ሲባሉ ከጎንደር ወደ ግብፅ ካይሮ በመሄድ በ10 ዓመት ውስጥ መጽሐፍ ቅዱስን ወደ አማርኛ ቋንቋ ተርጉመዋል፡፡
20
የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገጽ 270 ይመልከቱ
21
“ክርታስ ማለት ለመጻፊያ የሚያገለግል ወፍራም ወረቀት ከእንሰሳ ቆዳ የሚሰራውም የብራና ጥቅልል ክርታስ ይባላል፡፡ (ኤር34፡4-6) የመጽሐፍ ቅዱስ
መዝገበ ቃላት ገጽ 203
22
እነዚህ መጻሕፍት አስራው መጻሕፍት በመባል ይታወቃሉ፡፡ እነዚህ መጸሕፍት ለሌሎች መጻሕፍት መሰረቶች በመሆናቸው አስራው (መሰረቶች) ተብለዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ እነዚህ መጻሕፍት በሌላ መጽሐፈ አምላካውያት ተብለዋል፡፡
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 12
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ምዕራፍ ፪
የመጽሐፍ ቅዱስ አጠናን ዘዴ
መጽሐፍ ቅዱስ የሰው ልጅ የሃይማኖት መሰረት ነው፡፡ አምላኩን በአግባቡ እንዲያውቅ፣ እውነቱንም
ከሀሰት እንዲለይ እና ፍጹም ድኅነት የሚገኝበትን መንገድ እንዲያገኝ የሚረዳው ታላቅ መጽሐፍ ነው፡፡ እናም
ይህንን መጽሐፍ ሰናነብ (ስናጠና) እንደሌሎች ተራ መጻሕፍት መሆን የለበትም ይልቁኑ ከመጽሐፍ ቅዱስ
የሚገኘውን ጥቅም ተጠቃሚ ለመሆን ልንተገብራቸው የሚገቡ ተግባራት አሉ፡፡ እናም የተወደዳችሁ ተማሪዎች
በዚህ ምዕራፍ መጽሐፍ ቅዱስን ስናጠና ልንከተለው የሚገባውን ዘዴ በስፋት ለመመልከት እንሞክራለን፡፡
23
ከማስተማሪያ ኖቱ በተጨማሪ ለጥያቄዎቹ ምላሽና ማብራሪያ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት በአባይነህ ካሴ የተጻፈና በማህበረ ቅዱሳን የታተመ መጽሐፍ እና
በሠንበት ትምሕርት ቤታችን የርቀት ክፍል የተዘጋጀውን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ መጽሐፍን ይመልከቱ፡፡
24
መዝ 86(87)፡6
25
ዘዳ 8፡3
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 13
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
26
ሐዋ 8፡26-38
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 14
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
የሚያነብ ኢትዮጵያዊ ሰው እንደ ሀገሩ ባሕል ለመተርጎም ቢሞክር ወደ ስህተት ማምራቱ የማይቀር ነው፡፡
ምክንያቱም እረኛ በእስራኤላውያን ባህል በጎቹን ፊት ለፊት እየመራ የሚሄድ ሲሆን27 በኢትዮጵያውያን ባሕል ግን
እረኛ ከበጎቹ ኋላ ሆኖ እየነዳቸው የሚሄድ ነው፡፡ ስለዚህ ማንም መጽሐፍ ቅዱስን በሚያነብበት ወቅት ከላይ
የተጠቀሱትን ነጥቦች ከግምት ወስጥ በመክተት የመጽሐፍ ቅዱስን ባሕል በመረዳት ሊያነበው ይገባል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ ሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስን ባሕሎችን ከዚህ ቀጥለን በዝርዝር ለመመልከት እንሞክራለን፡፡
ይህም የእስራኤላውያንን ባሕል መመልከት የመጽሐፍ ቅዱስን ባሕል ለማወቅ ይረዳል፡፡ ይህም የእስራኤላውያንን
የስም አወጣጥ፣ የአነጋገር ዘይቤ፣ ማሕበራዊ ሕይወትን መመልከት እና መረዳት ይገባል፡፡ ምክንያቱም መጽሐፍ
ቅዱስ የተጻፈው አብዛኛው የእስራኤላውያንን ባሕል መሰረት በማድረግ ስለሆነ ነው፡፡ ይህም በውስጡ
የእስራኤላውያንን የአነጋገር ዘይቤ ተክትሎ የተጻፈ በመሆኑና የተለያዩ የእስራኤላውያንን ማህበራዊ ኑሮ በተመለከተ
በውስጡ ስለሚገልጥ ነው፡፡
በሌላ መልኩ መጽሐፍ ቅዱስ ሌላ ዓይነት ባሕል ይንጸባረቅበታል፡፡ ይህም የአጻጻፍ ስልቱን የሚመለከት
ይሆናል፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ፈርጀ ብዙ ቃላት እንደየአገባባቸው የተለያየ ትርጉምን የሚይዙ አንዳንድ ቃላት
ይገኛሉ፡፡ ከዚህም ባሻገር መጽሐፍ ቅዱስ አንድን ነገር ለመግለጽ ተራ ቋንቋ አይጠቀምም፡፡ ለምሳሌ የአንድን ሴት
ተገድዶ መደፈር ለመግለጥ ቢፈልግ የአድራጊውን ስም በማንሳት እገሊትን አስነወራት ይላል፡፡28 ከዚህ በተጨማሪ
ሌሎችን የመጽሐፍ ቅዱስ ባህል ከዚህ በመቀጠል በዝርዝር የምንመለከት ይሆናል፡፡
ሀ. ለሰዎች የተሠጠ ስም
አዳም ፡- በአረማይክ ቋንቋ “መሬት” ማለት ሲሆን ይህም አዳም ከምን እንደተፈጠረ ለማመላከት ነው፡፡30
29
ሴት፡- ትርጉሙም ምትክ ማለት ሲሆን በአቤል ምትክ የተወለደ በመሆኑ ይህ ስም ተሰጥቶታል፡፡31
ይስሐቅ32፡- ትርጉሙም “መሳቅ” ማለት ሲሆን አብርሃምና ሳራ እድሜያቸው ገፍቶ እግዚአብሔር ልጅ
ትወልዳላችሁ ባለ ጊዜ ሳራ በልቧ ስለሳቀች ይህን ለማስታወስ ልጃቸውን ይስሐቅ ብለው ጠርተውታል፡፡33
ያዕቆብ፡- ትርጉሙ “ተረከዝን ይይዛል” ማለት ሲሆን ይህም በተወለደ ጊዜ የወንድሙን የኤሳውን ተረከዝ
ይዞ በመወለዱ ይህ ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡34
ሙሴ፡- ትርጉሙም “ከባሕር የወጣ” ማለት ሲሆን ይህም በዘመኑ እስራኤላውያን በግብጽ ፈርዖን35 ትዕዛዝ
ወንድ ልጅ ከተወለደ ይገደል ስለነበር እናቱ ከወለደችው በኋላ መሸሸግ ስላልቻለች በወንዝ ላይ ጣለችው፡፡
የፈርዖኑ ልጅም ልትታጠብ በወንዙ ላይ በወረደች ጊዜ ይህን መልከመልካም ልጅ አገኘችው በዚህ የተነሳ
ሙሴ ተብሎ ተጠርቷል፡፡36
27
ዮሐ 10፡2-5
28
ዘፍ 34፡3-5
29
አዳም ማለት በግዕዝ ያማረ መልካም ማለት ነው፡፡ ይህም አዳም ከፍጥረታት ሁሉ እጅግ ያማረ እና መልካም የሆነ ፍጥረት መሆኑን የሚያመላክት ነው፡፡
(ዘፍ 1፡26-31)
30
ዘፍ 2፡7
31
ዘፍ 4፡25
32
ይስሐቅ የሚለው ቃል በዕብራይስጡ “ሻሐቅ በእንግሊዘኛ አይዛክ የሚል ቃል ይይዛል፡፡
33
ዘፍ 18፡12 እና ዘፍ 21፡3
34
ዘፍ 25፡26
35
በኢትዮጵያ ነገስታት “አጼ የሚል የማዕረግ ስም እንደሚሠጣቸው የግብጽ ነገስታትም ፈርዖን ይባሉ ነበር፡፡
36
ዘጸ 1፡15-2፡10
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 15
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ምናሴ፡- ማለት “ማስረሻ” ማለት ሲሆን ዮሴፍ መከራውንና የአባቱን ቤት በመርሳቱ ይህ ስያሜ
ተሰጥቶታል፡፡37
ኤፍሬም፡- ማለት ትርጉሙ “ማፍራት” ማለት ሲሆን የዮሴፍ ሁለተኛ ልጁ ነው፡፡ በግብጽ መከራውን ሁሉ
ረስቶ ፍሬ ማፍራቱን (ልጆች መውለዱን) ለመግለጽ ልጁን ኤፍሬም ብሎ ሠይሞታል፡፡38
ኢካቦድ፡- ማለት “ክብር ከእስራኤል ለቀቀ” ማለት ሲሆን የፊንሐስ ሚስት ልጇን በወለደችበት ሠዓት ታቦተ
ጽዮን የተማረከችበት እና ሁለቱ ወንድማማቾች አፍኒንና ፊንሐስ የተገደሉበት ጊዜ በመሆኑ የልጇን ስም
ኢካቦድ ብላ ጠርታዋለች39
ዘሩባቤል፡- ማለት “የባቢሎን ዘር” ማለት ሲሆን በተወለደ ጊዜ ሕዝበ እስራኤል በባቢሎን ምርኮ ስለነበርና
የተወለደውም በባቢሎን በመሆኑ ያንን ታሪክ ለመግለጥ ዘሩባቤል ተብሏል፡፡40
የተወደዳችሁ ተማሪዎች ለአብነት እነዚህን አነሳን እንጂ ሌሎች ስሞችም በጊዜው ከነበረው ሁኔታ ጋር
የወጡ ናቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ እስራኤላውያን የቦታ ስያሜዎችንም ሲገልጡ በወቅቱ ከተፈጸመው ድርጊት ጋር
በማዛመድ ያወጡ ነበር፡፡ ከዚህ በመቀጠልም የተወሠኑትን ለመመልከት እንሞክራለን፡፡
ለ. ለቦታዎች የተሠጠ ስም
ቤቴል፡- ትርጉሙ “የእግዚአብሔር ቤት” ማለት ሲሆን ያዕቆብ በሕልሙ በዛች ስፍራ ላይ እግዚአብሔርን
በማየቱ ቦታዋን ቤቴል ብሎ ሠይሟታል፡፡41
ብኤል ለሃይሮኢ፡- ትርጉሙም “ሕያው የሆነውን የሚያየኝንም ያየሁበት የውሃ ጉግጓድ” ማለት ሲሆን
በዚህ ስፍራ አጋር42 የእግዚአብሔርን መልአክ በማየቷ ይህን ስያሜ ልትሰጥ ችላለች፡፡43
መሪባ፡- ማለት “ክርክር” ማለት ነው፡፡ እስራኤላውያን ከምድረ ግብጽ ከወጡ በኋላ በራፊዲም ሰፍረው ሳለ
በዛች ቦታ ውሃ ባለመኖሩ “ለምን ከግብጽ ምድር አወጣኸን” በማለት ሙሴን ተናገሩት ሙሴም ወደ
እግዚአብሔር ጸለየ፡፡ እግዚአብሔር ባመላከተው መሰረትም በበትሩ የኮሬብን ዓለቶች መታ በዚያም ሕዝቡ
ከኮሬብ ዓለቶች የፈለቀውን ውሃ ጠጡ በዚህም የተነሳ ስለ እግዚአብሔር ሕዝቡ ከሙሴ ጋር ተከራክረዋልና
ሥፍራውን “መሪባ” ብለው ጠሩት፡፡44
አቤንዔዘር፡- ማለት ትርጉሙ “እግዚአብሔር እስካሁን ድረስ ረድቶናል” ማለት ሲሆን ነብዩ ሳሙኤል
እግዚአብሔር እስራኤላውያንን ከፍልስጤማውያን እጅ ባዳናቸው ወቅት አንድን ድንጋይ አንስቶ በምጽጳና
በሻይን መካከል አቁሞ ቦታውን የጠራበት ስያሜ ነው፡፡45
ጌልገላ፡- ማለት “ማንከባለያ” ማለት ሲሆን አስራኤል ከግብጽ ከወጡ በኋላ በምድረ በዳ የተወለዱት ወንዶች
አልተገረዙም ነበር፡፡ እናም እግዚአብሔርም ኢያሱን እነዚህ ልጆች እንዲገረዙ አዘዘው፡፡ ኢያሱም
እንደታዘዘው አደረገ በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር ኢያሱን የግብጽን ነውር ከእርሱ ላይ እንዳንከባለለ ገልጾለታል፡፡
በዚህ የተነሳ ስፍራው ጌልገላ ተብሏል፡፡46
ጎልጎታ፡- ማለት የዕብራይስጥ ቃል ሲሆን47 ትርጓሜውም “የራስ ቅል” ማለት ነው፡፡48 የራስ ቅል
የተባለበትም ምክንያት አስቀድሞ የአባታችን የአዳም አጽም የተቀበረበት ሥፍራ በመሆኑ ነው፡፡49
37
ዘፍ 41፡51
38
ዘፍ 41፡52
39
1ሳሙ 4፡21
40
1ዜና 3፡19
41
ቤቴል አስቀድሞ ስሟ ሎዛ ይባል ነበር፡፡ ከኢየሩሳሌምም ርቃ የምትገኝ ስፍራ ናት፡፡ (ዘፍ 28፡10-19)
42
አጋር ይናገራት የነበረውንም የእግዚአብሔር ድምጽ “ኤልሮኢ ብላ የጠራችው ሲሆን ትርጉሙም “የሚያየኝን በውኑ አየሁት ማለት ነው፡፡ (ዘፍ 16፡13)
43
ዘፍ 16፡13-14
44
ዘጸ 17፡1-8
45
1ሳሙ 7፡12
46
ጌልገላ በኢያሪኮና በዮርዳኖስ መካከል የምትገኝ ስፍራ ናት፡፡ (ኢያ 5፡2-9)
47
በግሪክ ቃል “ቀራንዮ ይባላል፡፡
48
ዮሐ19፡17-18
49
አባታችን አዳም በደብረ ቅዱስ ሳለ መካነ ጸሎት ለይቶ ይኖር ነበር፡፡ እርሱ ከሞተ በኋላም የእርሱ ልጆች ዐጽሙን እንደታቦት አድርገው መሥዋዕተ ጸሎት
ያደርጉ ነበር፡፡ በዚህ ሁኔታ እስከ ኖኅ ድረስ ዘለቀ ኖኅም ወደ መርከቡ ሲገባ ዐጽሙን ይዞት ገባ በዚያም እንደቀደመው አደረገ፡፡ ኖኅም ከመርከብ ሲወጣ
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 16
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ላዳነኝ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይገባል በማለት ዐጽመ አዳምን እንደታቦት አድርጎ መሥዋዕትን ለእግዚአብሔር አቀረበ ከዚህም በኋላ ኖኅ ልጁን ሴምን ጠርቶ
ዐጽመ አዳምን እግዚአብሔር ካዘዘህ ቦታ ወስደህ አስቀምጥ አለው፡፡ ሴምም መልከ ጸዴቅን አሰናብቶ አጽሙን አሸክሞት ይዞት ሄደ መላዕክትም እየመሩት
ማዕከለ ምድር ቀርንዮ ደረሰ (ይህች ምድር አስቀድሞ አዳም የተፈጠረባት ሥፍራ ስትሆን “ኤልዳ” ተብላ ትጠራለች፡፡) የጌታ መስቀልም ከሚያርፍበት ሥፍራ
ሲደርስ ምድር ተከፈተችለት በዚያም አጽመ አዳምን አኖረ፡፡ መልከ ጸዴቅንም ጠብቅ ብሎት ትቶት ሄደ፡፡ መልከ ጸዴቅም የአዳምን አጽም እንደ ታቦት አድርጎ
መሥዋዕትን ይሰዋ ነበር፡፡
50
ማቴ 3፡1፣ 14፡8፣ ማቴ 16፡14፣ ማር 8፡28
51
ዮሐ 19፡26፣ 21፡20
52
የሐ.ሥራ 9፡43
53
ሉቃ 2፡25፣ 8፡2፣ ኤር 38፡7፣ 1ነገ 17፡1፣ ሩት 2፡21፣ ወዘተ.... ይመልከቱ፡፡
54
First person
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 17
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ወይም “እናንተ” እያለ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ራስን በማራቅ በሦስተኛ መደብ55 የሚናገሩበት ዘይቤ ነው፡፡ ይህም
“አንተ” በማለት ፋንታ “እርሱ” ብለው ይናገራሉ፡፡ ለምሳሌ የተወሰኑትን እንመልከት፡-
ኢያሱ ቅዱስ ሚካኤልን “ጌታዬ ለባርያው የሚናገረው ምንድን ነው?”56 በማለት ራሱን “ለባሪያው”
በማለት (በሦስተኛ ወገን በመጥራት) ይናገራል፡፡ እንደ እኛ ሀገር የአነጋገር ዘይቤ ቢሆን ግን
“ጌታዬ ለባርያህ የምትነግረኝ ምንድን ነው?” ብሎ በተናገረ ነበር፡፡
ከዚህ በተጨማሪ ቅዱስ ዳዊት ስለራሱ ሲናገር፡- “ቸርነቱን ለቀባው ለዳዊትና ለዘሩ ይሰጣል”57
በማለት ራሱን በሦስተኛ ወገን ይገልጣል እንደኛ ሀገር የአነጋገር ዘይቤ ቢሆን ግን “ቸርነቱን
ለቀባኝ ለእኔና ለዘሬ ይሰጣል” ብሎ በተናገረ ነበር፡፡
በአዲስ ኪዳን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በፊሊጶስ ቂሳርያ ሐዋርያትን “ሰዎች
የሰውን ልጅ ማን እንደሆነ ይሉታል?”58 በማለት በዚህ የአነጋገር ዘይቤ ሲናገር እናያለን እንደ
እኛ ሀገር የአነጋገር ዘይቤ ቢሆን ኖሮ “ሰዎች እኔን ማን ይሉኛል?” ብሎ በተናገረ ነበር፡፡
የተወደዳችሁና የተከበራችሁ ተማሪዎች ለአብነት እነዚህን አነሳን እንጂ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይህ
አይነት የአነጋገር ዘይቤ በተለያየ ቦታ ተጠቅሶ የምናገኝ ይሆናል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ራስን በሦስተኛ ወገን
አርቆ የመናገር ባሕል እንዳለና መጽሐፍ ቅዱስን በምናነብበት ጊዜ ይህን ባሕል ጠንቅቆ መረዳት ያስፈልጋል፡፡
ስለዚህ እኛም በምናነብበት ጊዜ ይሄንን የአነጋገር ዘይቤ በመረዳት ልናነብ ይገባል፡፡
55
Third person
56
ኢያ 5፡14
57
መዝ 17(18)፡50
58
ማቴ 16፡13
59
Second person
60
ዘፍ 18፡32
61
1ሳሙ 24፡14
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 18
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
62
1ነገ 17፡18
63
ዮሐ 2፡3
64
በዕብራውያን “አንቺ ሴት የሚለው አነጋገር የክብር አነጋገር መሆኑን ልብ ልንል ይገባል፡፡ በእኛ ሀገር የአነጋገር ዘይቤ ግን ይህ ቃል ንቀትን ሊያመላክት
ይችላል፡፡
65
ዘኁ 18፡15-16
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 19
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
66
ከላይ የጠቀስነውን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል መሠረት በማድረግ “እመቤታችን ቅደስት ድንግል ማርያም ከጌታ በኋላ የወለደቻቸው ልጆች አሉ ብለው”
የሚያነሱ አሉ ነገር ግን ይህን የሚሉበት ምክንያት የመጽሐፍ ቅዱስን ባሕል ካለመረዳት መሆኑን ልብ ልንል ይገባል፡፡
67
ዕብ 2፡16
68
ዮሐ 1፡12፣ ማቴ 6፡9
69
ዮሐ 19፡26
70
ማር 6፡3
71
ከላይ ዝምድና ያላቸው ሰዎች “ወንድም እንደሚባሉ አይተናል እናም “የጌታ ወንድሞች የተባሉበትም ምክንያት ይህ ነው እንጂ እውነት የጌታ እናት ሌሎች
ልጆች ኖረዋት አይደለም፡፡ (ማቴ 10፡3)
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 20
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ሀ. ፈሪሃ እግዚአብሔር ሊኖረው ይገባል፡- መጽሐፍ ቅዱስ ከአንድ ቋንቋ ወደ ሌላ ቋንቋ በሚተረጎምበት
ወቅት ተርጓሚው በፈሪሃ እግዚአብሔር የታነጸ መሆን ይገባዋል፡፡ ይህ ካልሆነ ግን ተረጓሚው በፈሪሃ እግዚአብሔር
የታነጸና ታማኝ ካልሆነ የግሉን አስተሳሰብ ሊጨማር አልያም ከመጽሐፉ እርሱ የማያምንበትን ሊቀንስ ይችላል፡፡
ይህም በተለያየ ጊዜ የተለያዩ መናፍቃን ሲያደርጉት ቆይተዋል፡፡ ለማሳያም አንድ ምሳሌ መዘን ለመመልከት
እንሞክር፡-
በዘመናችን መናፍቃን በ2ቆሮ 5፡20 ላይ አንዲት ፊደል በመለወጥ የሀሰት ትምህርታቸውን ለማስረጽ
ሞክረዋል፡፡ የተወደዳችሁ ተማሪዎች ይህ ግልጥ ይሆን ዘንድ እዛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ላይ ያሉትን
የፊደል ቅርፆች ማየት ተገቢ ነው፡፡ የተስተካከለው ቃል የሚለው “እንግዲህ እግዚአብሔር በእኛ
እንደሚማልድ ስለ ክርስቶስ መልዕክተኞች ነን” ነው ነገር ግን እዛው ክፍል ላይ ከፍ ብለን ቁጥር 18 ላይ
“አገልግሎት” የሚለውን ቃል የፊደል ቅርጽ ልብ እንበል ቀጥሎም ቁጥር 20 ላይ “እንለምናለን” የሚለውን
የፊደል ቅርጽ ልብ እንበል ቀጥሎም ቁጥር 20 ላይ “እንደሚማልድ” የሚለውን ቃል ልብ እንበልና እዚሁ
ቃል ላይ ያለችውን “ል” የተሰኘችውን ፊደል እንመልከት ይህች ፊደል መስተካከል አለመስተካከሏን (“ለ”
የነበረችውን “ል” ተደርጋ መስተካከልዋን አለምስተካከልዋን) ከላይ ለማመሳከሪያነት በጠቅስናቸው የመጽሐፍ
72
አዋልድ መጻሕፍትን
73
የትርጉም ዘዴዎች፡- ቃል በቃል ፣ ዓውደ ምንባባዊ (contextual)፣ ውርስ ትርጉም (adaptation)፣ አሳጥሮ መግለጽ እና
የጽሑፉ ሃሳብ ላይ ማተኮር የሚሉት የትርጉም ዘዴዎች ተጠቃሽ ናቸው፡፡
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 21
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ቅዱስ ቃላት ላይ ማለትም “አገልግሎት” የሚለውን ቃልና “እንለምናለን” የሚለውን ቃል ያሉትን የ “ለ”
እና የ “ል” ፊደላት አቀራረጽ ተመልክተን “እንደሚማልድ” የሚለውን ቃል ስንመለከት “ል” ተስተካክላ
እንደሆነ ግልጽ ይሆንልናል፡፡ ይህም ማለት ቃሉ አስቀድሞ “እንደሚማለድ” እንደነበረና ከጊዜያት በኋላ
የቅዱሳንን አማላጅነትና የጌታችንን ተማላጅነት በሚቃወሙ መናፍቃን እንደተስተካከለ (“እንደሚማለድ”
የነበረው “እንደሚማልድ” ወደሚል)74 ያስታውቃል፡፡ በዚህ መነሻነት “እንደሚማልድ” የሚለው ቃል
ትርጉም አልባ ሁኗል፡፡ ምክንያቱም ከታች “እንለምናለን” ማለታቸው የቅዱሳንን አማላጅነት የሚያመላክት
ሲሆን ከላይ ያለው ቃል አስቀድሞ ስለተማላጁ የተነገረ ነበር፡፡ ነገርግን ቃላቱ በመስተካከሉ ትርጉም አልባ
እንዲሆን አድርጎታል፡፡ ይልቁኑ ይህንን ቃል “እንደሚማለድ (እንደሚለመን)” በሚለው ቃል ተክተን
ብናነበው የአረፍተ ነገሩ አጠቃላይ ሃሳብ ግልጽ ይሆንልናል፡፡75
እናም የተወደዳችሁ ተማሪዎች መጽሐፍ ቅዱስ ከቋንቋ ወደ ቋንቋ በሚተረጎምበት ወቅት ተርጓሚው
ታማኝ እና ፈሪሃ እግዚአብሔር ያደረበት ሊኖረው ይገባዋል፡፡ ይህም ተርጓሚው በመጽሐፉ ላይ በመጨመሩም
ሆነ በመቀነሱ ሊመጣበት ካለው መቅሰፍት76 ለመዳን በማሰብ ሊተረጉም ይገባዋል፡፡ ሆኖም ከላይ ለአብነት አንድ
ምሳሌ አየን እንጂ ሌሎችም መጽሐፍ ቅዱስን ያለ ፈሪሃ እግዚአብሔር የራሳቸው ሃሳብ ያካተቱ ብዙ መናፍቃን
በየዘመኑ ተነስተዋል፡፡
ለ. የቋንቋ እውቀት ሊኖር ያስፈልጋል፡- መጽሐፍ ቅዱስን ከአንድ ቋንቋ ወደ ሌላ ቋንቋ ለመተርጎም
በቂ የቋንቋ እውቀት ተርጓሚው ሊኖረው ይገባዋል፡፡ ይህ ሲባል ተርጓሚው የሚተረጉምበትንም ሆነ
የሚተረጉምለትን ቋንቋ በበቂ ሁኔታ ሊያውቅ ይገባዋል፡፡ ይህ መሆን ከቻለ መጽሐፍ ቅዱስ ሳይበረዝና ሳይፈለስ
ዓላማውን እንደጠበቀ ከቋንቋ ወደ ቋንቋ መተርጎም ይቻላል፡፡ ነገር ግን በዚህም ላይ መጽሐፍ ቅዱስ ከቋንቋ ወደ
ቋንቋ በሚተረጎምበት ወቅት ተርጓምያኑ በቂ እውቀት ሳይኖራቸው በመተርጎም ችግር ሲፈጥሩ ታይተዋል፡፡
ለአብነትም አንዳንድ ድርጅቶች በቂ የቋንቋ ዕውቀት ሳይኖራቸው መጽሐፍ ቅዱስን ለመተርጎም ባደረጉት ጥረት
እነዚህ የትርጉም ስህተቶች በጉልህ ታይተዋል፡፡ ለምሳሌ በ2ቆሮ 5፡20 ላይ ያለውን “ስለ ክርስቶስ መልዕክተኞች
ነን” የሚለውን ቃል “ስለ ክርስቶስ አንባሳደሮች ነን” በማለት ለመተርጎም ሞክረዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም
“መሰረቶቿ” የሚለውን መሰረቶቹ (መሰረቱ) በማለት ተርጉመዋል77፡፡ እንዲህ ያለው ታማኝነት የጎደለው ሥራ
የመተርጉማኑን ሥውር ዓላማና ያለበቂ ዕውቀት እንዲሁም ያለ ፈሪሃ እግዚአብሔር በድፍረት ለመተርጎም
መሞከራቸውን የሚያሳይ ነው፡፡
ከዚህ ውጪ መጽሐፍትን በምናነብበት ወቅት በውስጡ ያሉትን ኃይለ ቃላት ለመረዳት የግድ የመጽሐፉን
ኃይለ ቃል ትርጉም መረዳት ያስፈልጋል፡፡ እናም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉ ኃይለ ቃላትን የምንተረጉምባቸው
የአተረጓጎም አይነቶች አሉ እነዚህም፡-
፪.3.3 ነጠላ ትርጉም
በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ በቀጥታ ትርጉም78 የሚወሰዱ እና የተለየ ምሳሌያዊም ሆነ ምስጢራዊ ትርጉም
የሌላቸው በርካታ ኃይለ ቃሎች አሉ፡፡ ለምሳሌ የተወሰኑትን ለመጥቀስ ሲሞከር፡-
“እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን ፈጠረ” ዘፍ 1፡1
“ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ” ማቴ 26፡41
“እስከመጨረሻ የሚጸና እርሱ ግን ይድናል” ማቴ 24፡13 ወዘተ.....
ለእነዚህና ለመሳሰሉት የመጽሐፍ ቅዱስ ኃይለ ቃላት የሚሠጠው ማብራሪያ ነጠላ ትርጉም በመባል
ይታወቃል፡፡
፪.3.4 ምሳሌያዊ ትርጉም
በመጽሐፍ ቅዱስ አንድን ነገር በተሻለና በበለጠ ግልጽ ለማድረግ በምሳሌያዊ ትርጉም ይነገራል፡፡ ይህም
“ነገር በምሳሌ...” እንዲሉ አበው ሃሳቡን ይበልጥ ግልጽ ለማድረግ ይረዳል፡፡ ነገር ግን ምሳሌ ሁልጊዜ ከአማናዊው
74
“ለ ን እዛው ወደ “ል ተቀይሯል መቀየሩም የፊደሉ ቅርጽ ሌሎች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከተጻፉ “ል ዎች በጣም የተለየና አስቀድሞ “ለ የነበረ መሆኑ
የሚያስታውቅ ነው፡፡
75
በተጨማሪ ክርስቶስ ተማላጅ እንጂ አማላጅ መሆኑን የሚከተሉትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ይመልከቱ፡- “ዮሐ 10፡30፣ 16፡15፣ 17፡10፣ 16፡26
76
ራዕ 22፡18-19፣ 2ጴጥ 1፡20
77
መዝ 86 (87)፡1
78
Literal meaning
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 22
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ወይም ከሚመሰልለት ነገር ያንሳል፡፡79 በመጽሐፍ ቅዱስም በምሳሌ የተነገሩ ብዛት ያላቸው ክፍሎች ይገኛሉ፡፡
ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በመዋዕለ ስጋዌው ለደቀ መዛሙርቱ ካስተማረባቸው ዘዴዎች አንዱ
በምሳሌ ማስተማር80 ነው፡፡ በዚህም የተነሳ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንዲህ ተብሎ ተገልጧል፡-
“መስማትም በሚችሉበት መጠን እነዚህን በሚመስል በብዙ ምሳሌ ቃሉን ይነግራቸው ነበር፡፡ ያለ
ምሳሌ ግን አልነገራቸውም” ማር 4፡33-34
የተወደዳችሁ ተማሪዎች ከዚህ በተጨማሪ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በርካታ ነገሮች በምሳሌ ተመስለዋል፡፡
ለአብነትም የተወሰኑትን ከዚህ በመቀጠል በዝርዝር ለመመልከት እንሞክራለን፡-
79
በዚህም መነሻነት አበው “ምሳሌ ዘየሐጽጽ ይላሉ፡፡
80
ለምሳሌ በጠፋው ልጅ፣ በበግ እና በድሪም..... ሉቃ 15፡3-32፣ በፈሪሳዊና በቀራጭ ....... ሉቃ 18፡9-14፣ በሰናፍጭ ቅንጣት ....... ማር 4፡30-32፣ ወዘተ...
81
በተጨማሪ፡- ኢሳ 5፡1 (አንድምታ)፣ ኢሳ 5፡7 ዋናው እና አንድምታውን ይመልከቱ፡፡
82
ማቴ 27፡14
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 23
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ስለዚህ ተማሪዎች መጽሐፍ ቅዱስ ምስጢራዊ ትርጉምን ያዘለ በመሆኑ እግዚአብሔር ለመረጣቸውም
የሚገለጥ መሆኑን መረዳት አለብን፡፡ እናም የመጽሐፍ ቅዱስን ምስጢራዊ ትርጉምን ለመረዳት የተለያዩ መንገዶች
አሉ፡፡ ጌታም ለሐዋርያቱ “ከእኔ የተማራችሁትንና የተቀበላችሁትን የሰማችሁትንም ያያችሁትንም እነዚህን አድርጉ”
በማለት እንደተናገረው ከመምህራን መማርና “የተቀበላችሁትን” እንዳለ በትውፊትም ትርጓሜ መጻሕፍትን ማግኘት
ይቻላል፡፡ በዚህ መሰረት ቅዱሳን አባቶች ገጽ በገጽ ከሐዋርያት የተማሩትን፣ ያዩትንና የሠሙትን በቀጥታ ለእኛ
አድርሰውልናል፡፡ ከዚያም ሐዋርያው የተቀበላችሁትን እንዳለ በትውፊት (በቅብብሎሽ) መጻሕፍቱንና
83
ዘፍ 22፡13፣ ራዕ 5፡6 እና ቁ.13ነነ፤/፣ 6፡1፣ 7፡10፣ 17፡14፣ 12፡11፣ 14፡1 እና ቁ4፣ ወዘተ.....
84
ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊውም በማክሰኞ ውዳሴ ማርያም ድርሰቱ ላይ ይህንን ሲያጎላ፡- “ነብዩ ዳንኤል ያየው ያለእጅ ከረጅም ተራራ የተፈነቀለ ያ ደንጊያ ከአብ
ዘንድ የወጣው ቃል (ኢየሱስ ክርስቶስ) ነውና መጥቶ ያለ ወንድ ዘር ከድንግል ተወልዶ አዳነን”
85
ምስጢር የሚለው ቃል በግዕዙ “አመሠጠረ ወይም “ሠጠረ ከሚለው ቃል የተገኘ ነው፡፡ ቃሉ በዕብራይስጥ “ሳታር”፣ በአረብኛ “ሰተር”፣ በሱርስት “ስታር”፣
በእንግሊዘኛ “ሚስትሪ ይሉታል፡፡
86
ኤፌ 3፡9
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 24
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ለእኛ አብነት ይሆን ዘንድ፡- ጌታችንም በተለያየ ጊዜና በተለያየ ቦታ እርሱን አብነት እንድናደርግና እርሱ
የሰራውን እኛም እንድንሰራ አዞናል፡፡90 ከዚህ በተጨማሪም እርሱን አብነት አድርገው በሕይወታቸው
ያሳዩን ቅዱሳን ሐዋርያት እነርሱን አብነት እንድናደርግ አዘውናል፡፡91 ጌታችንም ሰው በመሆኑ
ጾሟል፣ጸልዮዓል፣ አልቅሷል፣አዝኗል92 ፣ ከዚህ በተጨማሪም ስለ ሰዎች ምህረትን ለምኗል93 ወዘተ...
እናም ይህንን ሁሉ ያደረገበት ለእኛ አብነት ለመሆን ነው፡፡ እንጂ እርሱ ንጹሀ ባሕርይ ጉድለት የሌለበት
ሁሉም በእርሱ ፈቃድ የሚሆን እንጂ አንዳች ያለእርሱ ፈቃድ የማይደረግ አምላክ ነው፡፡94 ስለዚህ እርሱ
ቢጾም ቢጸልይ ለእኛ አብነት ለመሆን እንጂ የጎደለበት ነገር ኖሮ ይሞላለት ዘንድ አይደለም፡፡ ስለዚህም
ጌታችን ስለምን “አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ አለ ቢባል ለእኛ አብነት ለመሆን ነው፡፡ ይህም እኛ
በሃይማኖት የተነሳ መከራ ቢጸናብን ጌታችን ሁልጊዜ ከጎናችን ሆኖ መከራውንና ስቃዩን ያሳልፍልን ዘንድ
“አትተወን” ማለት እንደሚገባን ለማስተማር (ለእኛ አብነት ለመሆን) በመስቀል ላይ ይህንን ቃል
ተናግሮታል፡፡
87
ማቴ 6፡1-4
88
ሉቃ 14፡13-14
89
ሉቃ 14፡13-14
90
ማቴ 11፡29፣ ዮሐ 13፡12-15
91
1ቆሮ 11፡1
92
ማቴ 4፡1፣ ዮሐ 11፡33፣ ሉቃ 22፡41፣.....
93
እርሱ ለማኝ አብ ተለማኝ ሆኖ ሳይሆን ለእኛ አብነት ይሆንልን ዘንድ ነው፡፡ ይህም ሰዎች መከራን ቢያጸኑብንም ስለእነርሱ ምህረትን መለመን እንደሚገባን
ለማስተማር ነው፡፡ ከእርሱም በኋላ እርሱን አብነት በማድረግ ይህንን የጌታችንን ተግባር ቅዱሳኑ ፈጽመውታል፡፡ ለምሳሌ ቅዱስ እስጢፋኖስን ማንሳት
ይቻላል፡፡ (የሐዋ. ሥራ 7፡60)
94
ቆላ 1፡15-18
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 25
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ትንቢቱን ለመፈጸም፡- ይህም አስቀድሞ በነብዩ ዳዊት ተነገረውና95 አዳምና የአዳም ልጆች ሁሉ በሲዖል
ውስጥ ሆነው የመሲሁን ወይም የክርስቶስን መምጣት በመናፈቅ የጮሁት ጩኸት ነው፡፡
የተወደዳችሁ ተማሪዎች ለአብነት ይህንን አነሳን እንጂ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በነጠላ ትርጉም
የማይተረጎሙ ይልቁኑ በምስጢራዊ ትርጉማቸው የሚተረጎሙ ወይም በአንድምታ የሚተረጎሙ እጅግ ብዙ ኃይለ
ቃላት አሉ፡፡ እነዚህ ኃይለ ቃላት በተለይ በዘመናችን የተነሱ መናፍቃን ለሚያነሷቸው የምንፍቅና ጥያቄዎች ምንጭ
ናቸው፡፡ አብዛኞቹም መሰል ጥያቄዎች የሚነሱት የመጽሐፍ ቅዱስን ምስጢራዊ ትርጉም ካለመረዳት የተነሳ ነው፡፡
እናም እናንተም ይበልጥ ግንዘቤያችሁ ይሰፋ ዘንድ በምዕራፉ የክለሳ ጥያቄዎች ላይ የተጠቀሱትን የመጽሐፍ ቅዱስ
ኃይለ ቃላት መምሕራነ ቤተክርስቲያንን በመጠየቅ የኃይለ ቃሉን ትርጉም ለመረዳት እንሞክር፡፡ በበለጠ ደግሞ
ቀጣይ በምትማሯቸው ትምህርቶች ላይ እነዚህ ቃላት በተብራራ መልኩ እንደሚመሱላችሁ ተስፋ እናደርጋለን፡፡
ላሁን ግን ወደ ቀጣዩ ርዕስ እንሸጋገር፡-
95
መዝ 21(22) ፡1
96
እሩቅ ብዕሲ ነው
97
ለጥያቄዎቹ በቂ ምላሽ ለማግኘት “የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት በኦርቶዶክስ ተዋህዶ በአባይነህ ካሴ የተፃፈና በማህበረ ቅዱሳን 2002 ላይ የታተመውን መጽሐፍ
ይመልከቱ
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 26
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ምዕራፍ ሦስት
የመጽሐፍ ቅዱስ አከፋፈል
የተወደዳችሁ ተማሪዎች በምዕራፍ አንድ አንድና በምዕረፍ ሁለት ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ምንነትና እንዴት
ማጥናት እንደሚገባን በዝርዝር ተመልክተናል፡፡ በዚህኛው ምዕራፍ ደግሞ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ አከፈፈል እና ይዘት
እንዲሁም ስለ ጸሐፊያኑ ማንነት በዝርዝር ለመመልከት እንሞክራለን፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ በዋናነት ብሉይ ኪዳንና የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ተብሎ በሁለት ዐበይት ክፍሎች
ይከፈላል፡፡ ብሉይ ኪዳን በውስጡ አርባ ስድስት መጻሕፍትን የያዘ ሲሆን አዲስ ኪዳን ደግሞ ሰላሳ አምስት
መጻሕፍትን የያዘ ነው፡፡ በውስጣቸውም ያሉት መጻሕፍት እንደይዘታቸው በተለያየ አከፋፈል እንከፋፍላቸዋለን፡፡
እናም የተወደዳችሁ ተማሪዎች ለመግቢያ በሁለቱም አከፋፈሎች ውስጥ ያለውን እንዲህ ከተመለከትን በቀጣይ
በውስጣቸው ያሉትን መጻሕፍት አከፋፈልና ይዘት እንዲሁም ስለ ጸሐፊዎቹ ማንነት በዝርዝር የምንመለከት
ይሆናል፡፡
3...1 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት
3.1.1 የቃሉ ትርጉም
ብሉይ ማለት ያረጀ፣ ጥንታዊ፣ ቀዳማዊ፣ የድሮ፣ የቀድሞ፣ የፊት፣ወዘተ.... ማለት ሲሆን፤ ኪዳን98 ማለት
ደግሞ ውል፣ ስምምነት፣ ወዘተ... ማለት ነው፡፡ ባጠቃላይ ብሉይ ኪዳን ማለት የጥንት የቆየ የመጀመሪያ ውል
ስምምነት ማለት ነው፡፡ ይህም ያረጀ መባሉ ከሱ የተሻለው ኪዳን አዲስ ኪዳን በመኖሩ ነው እንጂ ኪዳኑ ዛሬም
የጸና ኪዳን ነው፡፡ ምክንያቱም እግዚአብሔር ከቅዱሳኑ ጋር የሚገባው ቃል ኪዳን በዘመናት የማይሻር በመሆኑ
ነው፡፡ ከዚሀ በተጨማሪም ብሉይ ኪዳን ያረጀ መባሉ ኪዳኑ የተገባበት ዘመን በማርጀቱ ይህም ማለት ኪዳኑ
የተገባበት ዘመን በኋላ ረጅም ጊዜያት ማለፉን ለማጠየቅ ነው፡፡ ብሉይ ኪዳን በአጠቃላይ ከጌታ ልደት በፊት የአንድ
አምላክ አማኞች የሆኑትን የእስራኤላውያንን ታሪክ የሚተርክ መጽሐፍ ነው፡፡ በውስጡም በዋናነት ከአምስት ሺ
አምስት መቶ ዘመን በኋላ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በፍጹም ድንግልና የሚወለደውን ጌታ ሕዝቡ
ተዘጋጅቶ እንዲጠብቅ በተለያዩ የነብያት ትንቢትን ይዟል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም እግዚአብሔር ከወዳጆቹ ጋር
የገባውን ቃል ኪዳን በአጠቃላይ ያካትታል፡፡99
98
አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመጽሐፈ ሰዋሰው ወግስ ላይ ኪዳን የሚለውን ቃል ሲተረጉሙት፡- በቁሙ ውል ፣ቁም ነገር፣ የፍቅርና የአንድነት መሐላ፣
ሰላማዊ ህግ፣ ሁለቱን ወገን አንድ የሚያደርግ ስለ ረብና ስለ ጥቅም በተስፋ የቆመ የተጻፈ ሥርዓት ቢያፈርሱት ጉዳትና ጠብ የሚያመጣ ጥቅም የሚያሳጣ
በማለት ተርጉመውታል፡፡ (ገጽ 529) ኪዳን በሁለት አካላት (ውል ሰጪና ውል ተቀባይ) የሚደረግ ውል ሲሆን ብሉይ ኪዳንም እግዚአብሔር ከተለያዩ
ቅዱሳን ጋር የሚያደርገው ወል አሊያም ስምምነት ነው፡፡
99
መዝ 88(89)፡3
100
በ395ዓ.ም፣ 397ዓ.ም፣ 399ዓ.ም እና በ419 ዓ.ም
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 27
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ክፍል አንድ
የህግ መጻሕፍት/ብሔረ ኦሪት/
ኦሪት የሚለው ቃል የሱርስት ቃል ሲሆን ሕግ ማለት ነው፡፡ ሕግ ማለት ደግሞ ብርሃን ማለት ነው፡፡ ከዚህ
ቃል ጋር ተያይዘው የሚጠሩ መጻሕፍት አምስት ሲሆኑ የተጻፉትም በሊቀ ነቢያት ሙሴ አማካኝነት በሲና ተራራ
በ1500 ዓ.ዓ ነው፡፡ መጻሕፍቱ በዕብራይስጥ ቋንቋ ለእስራኤል ዘስጋ የተጻፉ ናቸው፡፡ እነዚህ መጻሕፍት በውስጣቸው
ሦስት ታላላቅ ህግጋትን ይዘዋል፡፡ እነሱም:-
1. የሞራል ህግ
2. የክህነት ህግ
3. የአስተዳደር ህግ ነው፡፡
ከዚህ በተጨማሪም እነዚህ መጻሕፍት ከህግ በተጨማሪ ታሪክን፣ ትንቢትንና፣ትምህርትን የያዙ መጻሕፍት
ናቸው፡፡ እነዚህም፡-
1 ኦሪት ዘፍጥረት 4 ኦሪት ዘኅልቁ
፪ ኦሪት ዘጸአት 5 ኦሪት ዘዳግም
3 ኦሪት ዘሌዋውያን
101
Genesis
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 28
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ከምዕራፍ 6-11 የሰው ልጆች በኃጢአት መክፋትና የደረሰባቸው ቅጣት የባቢሎን ግንብ ታሪክ
ከምዕራፍ 12-26 የአብርሃም የሃይማኖት ጉዞ የሰዶምና የገሞራ ጥፋት እንዲሁም የይስሃቅ
ታሪክ
ከምዕራፍ 27-50 የያዕቆብና የዮሴፍ ታሪክ የእስራኤል ወደ ግብጽ መውረድ፡፡
፪. ኦሪት ዘጸአት102
“ጸአት” ማለት የግዕዝ ቃል ሲሆን መውጣት ማለት ነው፡፡ ይህም መጽሐፉ የእስራኤል ሕዝብ በሙሴ
መሪነት ከግብጽ ባርነት መውጣታቸውን በሰፊው የሚያወሳ ስለሆነ በዚሁ ተሰይሟል፡፡ ይህ መጽሐፍ ሕዝበ
እስራኤል ከ430 ዓመት የባርነትና የስቃይ ቆይታ በኋላ በሙሴ መሪነት ከግብጽ ከባርነት ወጥተው እስከ ሲና
ተራራ ድረስ ያለውን ታሪክ ይተርካል፡፡ መጽሐፉ 40 ምዕራፎች አሉት፡፡
አከፋፈሉም፡-
ከምዕራፍ 1-4 ከሙሴ ልደት ነጻ ለማውጣት እስከተጠራበት
ከምዕራፍ 5-11 በግብጽ ስለወረዱ 10 መቅሰፍቶች
ከምዕራፍ 12-15 የኤርትራን ባህር በእግዚአብሔር ኃይል መሻገራቸው
ከምዕራፍ 16-40 እስራኤል መና እንደወረደላቸው የሙሴ በሲና ሕግን መቀበል እንዲሁም
የእስራኤልን ጣዖት ማምለክና መቀጣት የሚገልጽ ታሪክ ይገኛል፡፡
3. ኦሪት ዘሌዋውያን103
ዘሌዋውያን የሚለው ቃል ሌዊ ከተሰኘ የያዕቆብ ልጅ ስም የተገኘ ነው፡፡ የሌዊ ልጆች104 (ትውልድ) ለእስራኤል
ሕዝብ ካህናት እንዲሆኑ የተመረጡ ሲሆኑ በተለይም የሙሴ ወንድም አሮን ሊቀ ካህናት ተብሎ ከተሾመ ጀምሮ
የነበረውን የእነዚህን ካህናት ሥርዓት በዝርዝር ስለሚያስረዳ በዚህ ስም ተሰይሟል፡፡ ይህ መጽሐፍ የእግዚአብሔር
ሕዝብ በሁለንተናው ንጹህ (ቅዱስ) መሆን ስለሚናገር የቅድስና መጽሐፍ ይባላል፡፡105 ይህ መጽሐፍ 27 ምዕራፎች
አሉት፡፡ አከፋፈሉም፡-
ከምዕራፍ 1-10 ስለ መስዋዕትና ስለ ሥርዓተ ክህነት
ከምዕራፍ 11-16 ስለ መባልዕትና የማንጻት ሥርዓት
ከምዕራፍ 17-22 ስለ ጋብቻና የክህነት ምርጫ
ከምዕራፍ 23-27 ህግና በዓላትን ስለማክበር በዚያም የሚገኘውን በረከትን መርገም የሚገልጽ
ሲሆን በውስጥ በርካታ ሕግጋተ እግዚአብሔር ተገልጠዋል፡፡
4. ኦሪት ዘኁልቁ106
በግዕዝ “ኆለቀ” ማለት ቆጠረ ማለት ሲሆን ዘኁለቁ ማለት ደግሞ የቁጥር መጽሐፍ ማለት ነው፡፡ እስራኤል
ከግብጽ ባርነት ከወጡ በኋላ በታሪካቸው ሁለት ጊዜ የተቆጠሩበት መጽሐፍ ነው፡፡ ይህም በመጀመሪያ በሲና ምድረ
በዳ107 ቀጥሎም በሞዓብ ሃገር108 መቆጠራቸውን ስለሚገልጽ በዚህ ስም ተሰይሟል፡፡ ይዘቱም የማርያምንና የአሮንን
ሞት በመጨረሻም ምድረ ርስትን እንዴት እንደሚከፋፈሉ ከእግዚአብሔር የተሰጠውን ትዕዛዝ ገልጧል፡፡ መጽሐፉ
36 ምዕራፎች አሉት፡፡ አከፋፈሉም፡-
ከምዕራፍ 1-5 ህዝበ እስራኤል በሲና መቆጠራቸዉ
ከምዕራፍ 6-25 ከሲና ተራራ እስከ ዮርዳኖስ ወንዝ መጓዛቸዉ፣ 12ቱ ሰላዮች፣ የሙሴ
ኢትዮጵያዊታን ማግባት
102
Exodus
103
Leviticus
104
እነዚህ ለክህነት አገልግሎት የተመረጡና ስለ ህዝቡ ኃጢአትና በደል መስዋዕትን ዘወትር የሚያቀርቡ ከእግዚአብሔር ጋር ሕዝቡን ያስታርቁና
ኃጢአታቸውንም ያስተሰርዩላቸው የነበሩ ናቸው፡፡
105
ዘሌ 19፡2
106
Numbers
107
ዘኁ 1፡1-3
108
ዘኁ 26፡1-3
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 29
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
5. ኦሪት ዘዳግም109
ዘዳግም ማለት ትርጉሙ የተደገመ ማለት ነው፡፡ ከላይ ከተጠቀሱት ከኦሪት ዘጸአት እስከ ኦሪት ዘኁልቁ
ድረስ ያሉትንና የቀሩትን ዋና ዋና ኃይለ ቃሎች በስብከት መልክ ስለሚደግማቸው ዘዳግም(የሚደግም) ተብሏል፡፡
መጽሐፉ 34 ምዕራፎች ሲኖሩት በዮርዳኖስ ምድር ባለችው በሞአብ ሀገር ለእስራኤል ሕዝብ የተናገረው ነው፡፡
ይህም እግዚአብሔር ስለሰጣቸው ደንቦች እንደ አዲስ የሚተረጉምና የወደፊቱን በትንቢት የሚናገር መጽሐፍ ነዉ፡፡
አከፋፈሉም፡-
ከምዕራፍ 1-4 እግዚአብሔር ለህዝቡ ያረጋቸዉን ድርጊቶች መገለጹ፣ በሙሴ መሪነት
የተከናወነ የእስራኤላዉያን ታሪክ
ከምዕራፍ 5-26 ከእግዚአብሔር የተሰጡ ህግጋት ተደጋግመዉ እንዲነገሩና ህዝቡም
ህግጋቱን እንዲከተሉ ምክር መሰጠቱ
ከምዕራፍ 27-30 ለሰዎች የተሰጡ ምርጫዎች፣ በመታዘዝ በረከት ባለመታዘዝ መርገም
እንዳለ መገለጹ
ምዕራፍ 31 ማስጠንቀቂያ
ከምዕራፍ 32-33 የመጨሻዎቹ የሙሴ መዝሙራትና በረከት
ምዕራፍ 34 የሙሴ ሞት
ክፍል ሁለት
የታሪክ መጻሕፍት
በዚህ ክፍል 17 መጻሕፍትን እናገኛለን፡፡ በዉስጡም ከመስፍኑ ከኢያሱ ወልደ ነዌ አነሳስ ጀምሮ እስከ ዮሴፍ
ወልደ ኮርዮን ድረስ ያሉትን መጻሕፍት ይይዛል፡፡ እነዚህ መጻሕፍት በአጠቃላይ የሚያወሱትም በእስራኤላዉያንና
በእግዚአብሔር መካከል ስለነበረዉ ግንኙነት110 ነው፡፡ የተወደዳችሁ ተማሪዎች ከዚህ በመቀጠል የመጽሐፍቱን
ይዘት እና ስለጸሐፊያኑ እንዲሁም አከፋፈላቸውን በዝርዝር ለመመልከት እንሞክራለን ተከተሉን፡-
109
Deuteronomy
110
ይህም ሲባል ህዝበ እስራኤል የእግዚአብሔርን የአምላካቸውን ህግ ሲያከብሩ ሰላምና ብልጽግና ያገኙ እንደነበር ከአምላካቸው ፈቃድ ሲወጡ ደግሞ
ጦርነትና መዓት እንዲሁም ምርኮ ይገጥማቸው እንደነበር ያወሳሉ፡፡
111
joshua
112
ከኢያሱ ጋር ተመሳሳይ ትርጓሜ ያላቸው ስሞች አሉ፡፡ ለምሳሌ ኢየሱስ እና ኢሳይያስ ይጠቀሳሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ኢያሱ ህዝበ እስራኤልን በምድረበዳ
መርቶ ቃል ወደተገባላቸው ርስተ ከንዓን በማግባቱ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌም ነው፡፡ ምክንያቱም እስራኤል ዘነፍስ (ክርስቲያኖች)
ርስት መንግስተ ሠማያትን የምንወርሰው በክርስቶስ መሪነት በመሆኑ ነው፡፡
113
ኢያ 24፡29
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 30
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
አከፋፈሉም፡-
ከምዕራፍ 2-12 ስ እስራኤል ከነዓን መግባት
ከምዕራፍ 13-22 ምድረ ርስትን ስለመከፋፈላቸው
ከምዕራፍ 23-24 የኢያሱን የመጨረሻ ምክርና ዕረፍት ይገልጻል፡፡
፪. መጽሐፈ መሳፍንት114
መሳፍንት ማለት ፈራጆች፣ አስተዳዳሪዎች ማለት ነው፡፡ እነዚህም ኢያሱ ከሞተ በኋላ እስከ ንጉስ ሳኦል
ድረስ ለ400 ዓመታት እስራኤልን ያስተዳድሩ ነበር፡፡115 መጽሐፉም ትረካቸውን በመግለጡ በስማቸው ተጠርቷል፡፡
ይህን መጽሐፍ ኢያሱ እንደጻፈው ይታመናል፡፡116 የተጻፈውም ከ1380-1050 ዓ.ዓ እንደሆነ ይታመናል፡፡117
መጽሐፉም 21 ምዕራፎች ያሉት ሲሆን የእስራኤልን ታሪክ የያዘ እንደመሆኑ በዕብራይስጥ ቋንቋ በምድረ እስራኤል
ተጽፏል፡፡ በዚህ የመሳፍንት ዘመን ለእስራኤል ንጉስ ያልተሾሙበትና በሕገ እግዚአብሔር ጸንተው በሰላምና በፍቅር
የኖሩበት በመሆኑ ዘመኑ መንግስት እግዚአብሔር ይባላል፡፡ በዚህ መጽሐፍ የተጠቀሱት መሳፍንት 13 ሲሆኑ
እነሱም፡-
1. ጎቶንያል /መሳ 3፡7-11/ 8. ኢያዕር /መሳ 10፡3/
2. ናዖድ /መሳ 3፡12-30/ 9. ዮፍታሔ /መሳ 11፡1/
3. ሰሜጋር /መሳ 3፡31/ 10. ኢብጻን /መሳ 12፡11/
4. ዲቦራና ባርቅ /መሳ 4፡8/ 11. ኤሎም /መሳ 12፡8/
5. ጌዴዎን /መሳ 6፡11/ 12. አብዶን /መሳ 12፡33/
6. አቤሜሌክ /መሳ 9፡22/ 13. ሶምሶን /መሳ 13፡1-16/ ናቸው፡፡
7. ቶላ /መሳ 10፡1-2/
አከፋፈሉም፡-
ከምዕራፍ 1-2 እስራኤል የእግዚአብሔርን ውለታ ስለመዘንጋታቸው
ከምዕራፍ 3-16 ስለመሳፍንቱ አነሳስና በእነሱ አማካኝነት ስለተፈጸሙ ታሪኮች
ከምዕራፍ 17-21 መሳፍንቱ ባልነበሩበት ዘመን ስለተፈጸሙ ታሪኮች
3. መጽሐፈ ሩት118
መጽሐፉ በነቢዩ ሳሙኤል የተጻፈ መጽሐፍ ሲሆን የስያሜው ምክንያት የእርሷን ታሪክ ስለሚተርክ ነው፡፡
ይህቺ ሴት ከአህዛብ ወገን ስትሆን119 ታሪኳ የተጻፈው በደግነቷ እንዲሁም የዳዊት ቅድመ አያት ሆና ከጌታ
ትውልድ ሐረግ በመግባቷ ነው፡፡120 መጽሐፉ 4 ምዕራፎች አሉት፡፡
አከፋፈሉም፡-
ምዕራፍ 1 ኑሃሚን ከባሏና ከሁለት ልጆቿ ጋር ከሀገሯ ስለመሰደዷና ከሩት ጋር ወደሃገሯ
ስለመመለሷ
ከምዕራፍ 2-3 ሩት የቦዔዝን እርሻ እየቃረመች ኑሃሚንን ስለመርዳቷ
ምዕራፍ 4 ቦዔዝን አግብታ በዳዊት የዘር ሐረግ መጠቀሷን እናገኛለን፡፡
114
judges
115
አንዳንድ መንጮች እንደሚገልጡት እነዚህ መሳፍትን እስራኤልን ያስተዳደሩበትን ዘመን 430 ነው፡፡
116
መምህር ቸርነት አበበ “መሰረታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ አጠናን ዘዴ በሚለው መጽሐፋቸው ላይ ገጽ 99 ላይ መጽሐፈ አቡሻኽርን በመጥቀስ እንደገለጹት
የዚህ መጽሐፍ ጸሐፊ መስፍኑ ኢያሱ ነው፡፡
117
የደ/ፍ/መ/ሰ/ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ውሉደ ብርሃን ሰ/ት/ቤት የርቀት ማስተማርያ መጽሐፍ ገጽ 24
118
ruth
119
ሞዓባዊት ናት
120
ማቴ 1፡5
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 31
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
4. መጽሐፈ ሳሙኤል
ሳሙኤል ማለት “እግዚብሔር ሰማኝ” ማለት ነው፡፡ አባቱ ሕልቃና እናቱ ሐና ይባላሉ፡፡ በእስራኤል ከተነሱ
መሳፍንት የመጨረሻ መስፍን ነው፡፡ ሳሙኤል121 እስራኤልን ለ20 ዓመታት መርቶ የመጀመሪያው የእስራኤል
ንጉስ ሳዖል ሲነግስ ዘመነ መሳፍንት አብቅቷል፡፡ ይህ ነቢይ ሁለተኛውን የእስራኤል ንጉስ ዳዊትን ቀብቶ አርፏል፡፡
መጽሐፉን ሰባው ሊቃውንት ለሁለት ከመክፈላቸው በፊት አንድ ነበሩ በኋላም በሰባው ሊቃውንት አማካይነት
መጻሕፍቱ ለሁለት በመከፈል መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ እና ካልዕ ተብለዋል፡፡ ይህ መጽሐፍ በነብዩ በሳሙኤል
ስም የተጠራበት ምክንያት፡
መጽሐፉ የሚጀምረው የሳሙኤልን የህይወት ታሪክ በመተረክ በመሆኑ
ጸሐፊው ራሱ ነብዩ ሳሙኤል በመሆኑ ነው፡፡
5. መጽሐፈ ነገስት
የጻፈው ማን እንደሆነ በትክክል ባይታወቅም ነቢዩ ኤርምያስ እንደጻፈው ይነገራል፡፡125 መበሌላ በኩል
ደግሞ ካህኑ ዕዝራ ነው የሚሉም አሉ፡፡ በአጠቃላይ ይህን መጽሐፍ ስንመለከተው ከንጉሥ ሰሎሞን አንስቶ እስከ
ባቢሎን ምርኮ126 የተነሱ የይሁዳና የእስራኤልን ነገስታት ታሪክ እንዲሁም በዘመናቸው ስለተፈጸሙ ታሪኮች
ይገልጣል፡፡ በመሆኑም መጽሐፉ በዚህ ስም ተሰይሟል፡፡
121
ሳሙኤል እናትና አባቱ በስዕለት ያገኙት ልጃቸው በመሆኑ ጡት ሲጥል እናቱ ለቤተመቅደስ ሰጥታዋለች፡፡ በዚያን ወቅት እስራኤልን በመስፍንነትም ሆነ
በካህንነትም ያገለግል የነበረው ነብዩ ኤሊ ነበር፡፡ (1ሳሙ 1፡25፣ 2፡11) ኤሊም ሲያርፍ የመጨረሻው የእስራኤል መስፍን ሆኖ እስራኤልን አስተዳድሯል፡፡
122
1 samuel
123
1ሳሙ 10፡25
124
2 samuel
125
1000-590 ዓ.ዓ ባለው ጌዜ ውስጥ
126
በዘመን ስናስቀምጠው የ400 ዓመት ታሪክ ነው፡፡ (የደ/ፍ/መ/ሰ/ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ው/ብ/ሰ/ት/ቤት የርቀት የማስተማሪያ ኖት)
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 32
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
6. ዜና መዋዕል ቀዳማዊ129
ዜና መዋዕል ማለት የዕለት ዜና ማለት ነው፡፡ የተጻፈው ከባቢሎን ምርኮ በኋላ በካህኑ በዕዝራ ነው፡፡
ሁለቱ የዜና መዋዕል መጻህፍት አንድ የነበሩ ሲሆን ከሰባው ሊቃውንት ትርጉም በኋላ ለሁለት ተከፍለዋል፡፡
መጻህፍቱ በይዘታቸው ከመጻሕፍት ነገስት ጋር ተመሳሳይነት አላቸው፡፡ መጻሕፍቱ የተጻፉት በ400 ዓ.ዓ ገደማ
ነው፡፡ 1ኛ ዜና መዋዕል 29 ምዕራፎች ያሉት ሲሆን አከፋፈሉም፡-
ከምዕራፍ 1-9 የቤተ እስራኤል የትውልድ ሐረግ ቆጠራ
ከምዕራፍ 10-29 ስለ ሳዖል መንግስት አወዳደቅ ስለዳዊት መንግስት አነሳስ እንዲሁም በዘመኑ
ስለተፈጸሙ ታሪኮች በመጨረሻም ንጉስ ዳዊት መንግስቱን ለልጁ ለሰሎሞን አስረክቦ ማረፉን
ይገልጻል፡፡
127
1 kings
128
2 kings
129
1chronicles
130
1chronicles
131
2ነገ 20፡1-7
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 33
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
33፡18 ላይ ምናሴ እንደጸለየ ስለሚናገር እና ሁለቱ መጻሕፍት በታሪክ ተያያዥነት ስላላቸው እንደ አንድ
ሊቆጠሩ ችለዋል፡፡
8. መጽሐፈ ኩፋሌ
ኩፋሌ ማለት ክፋይ /የተከፈለ/ ማለት ሲሆን የተከፈለውም ከኦሪት ዘፍጥረትና ከኦሪት ዘጸአት የተከፈለ
መጽሐፍ ነው፡፡ ከመጀመሪያው የሥነ ፍጥረት ታሪክ ጀምሮ እስከ እስራኤላዉያን ከግብጽ እስከወጡበት ዘመን
ድረስ ያለውን ታሪክ ከህግጋት ጋር እያዛመደ ጊዜውን በሱባኤ እየቀመረ የሚገልጽ መጽሐፍ ነው፡፡ መጽሐፉ 34
ምዕራፎች ያሉት ሲሆን በነቢዩ ሙሴ በዕብራይስጥ ቋንቋ የተጻፈ መጽሐፍ ነው፡፡ አጻጻፉም፡-
ከአዳም እስከ ሙሴ ያለውን የ3830 ዓመታት ታሪክ ይገልጻል
ታሪኮቹ የተፈጸሙበትን ዘመን በሱባኤ አቆጣጠር ይገልጻል
ታሪኩን ከህግጋት ጋር እያዛመደ ያስረዳል፡፡ ለምሳሌ፡- አዳምና ሔዋን ከተፈጠሩበት ወደ ገነት
የገቡት በ40 እና በ80 ቀናቸው እንደሆነ በምዕራፍ 4÷8-13 ሲገለጽ ይህንም በዘፍ 2፡7-5
ካለው ታሪክ ጋር አዛምዶ የተፈጸመበትን ጊዜያት በሱባዔ ቆጥሮ ይገልጻል፡፡ /ኩፋ 4÷6/
9 መጽሐፈ ሄኖክ
ሄኖክ ማለት ተሐድሶ ማለት ነው፡፡ ይህ አባት ከአዳም ሰባተኛ ትውልድ ነው፡፡ በሕይወተ ስጋ ሳለም
እግዚብሔርን በማስደሰቱ ሞትን ሳይቀምስ ብሔረ ሕያዋን የገባ አባት ነው፡፡ በዚያም /በብሔረ ሕያዋንም/ እያለ
የሆነውን እና የሚሆነውን እንዲሁም የተለያዩ ምስጢራት ተገልጾለት ጽፏል፡፡ መጽሐፉ የተጻፈበት ዘመን 1486
ዓ.ዓ ነዉ፡፡ ይህም ከቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ አስቀድሞ የተጻፈ መጽሐፍ ያደርገዋል፡፡ የተጻፈዉም በዕብራይስጥ
ቋንቋ ነዉ፡፡132 መጽሐፉ ከተጻፈ በኋላም 70 ሊቃናት ከዕብራይስጥ ወደ ጽርዕ ተርጉመውታል፡፡ ይዘቱም፡-
ስለጌታችን በዚህ ዓለም መወለድና ማስተማር ሞቶም ሰዎችን ስለማዳኑ ይገልጻል
ስለቅዱሳን መላእክት አገልግሎት
ስለጸሐይና ጨረቃ ዑደትና ስለ እጽዋት ምስጢር
ስለጻድቃን የዘላለም ዋጋና ስለኃጥአን ፍዳ
በኖህ ዘመን ስለሚፈጸመው ኃጢአትና ቅጣት በሰፊው የሚገልጥ ባለ 42 ምዕራፍ መጽሐፍ
ነው፡፡
፲. መጻሕፍተ ዕዝራ እና መጽሐፈ ነህምያ
ሁለቱ መጽሐፍት በሰማንያ አሐዱ መጽሐፍት ዝርዝር ዉስጥ እንደ አንድ የሚቆጠሩ ናቸዉ፡፡
132
ከዚህ መጽሐፍ ሐዋርያት ለትምህርታቸው ማስረጃነት ጠቅሰዋል፡፡ /ለምሳሌ ይሁዳ 1፡14 ሄኖ 1፡9/
133
Ezra
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 34
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
134
nehemiah
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 35
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
መጻሕፍተ መቃብያን
መቃብያን ማለት “ጀግኖች” ማለት ሲሆን በዓለም ላይ በመቃብያን ስም የሚጠሩ ስምንት መጻሕፍት
ይገኛሉ፡፡ መጻሕፍቱ ማን እንደጻፋቸው አይታወቅም ከስምንቱ መጻሕፍትም አራቱ በግሪክ የቀሩት አራቱ ደግሞ
በግዕዝ የተጻፉ ናቸው፡፡ በግዕዙ ተጽፈው ከሚገኙት ውስጥ ቤተክርስቲያናችን መጽሐፈ መቃብያን ቀዳማዊና ካልዕን
ከቅዱሳት መጻሕፍት ቆጥራ የምትቀበል ሲሆን መቃብያን ሳልስን ከይዘቱ አንጻር (የብሉይ ኪዳንን ታሪክ እየገለጸ
ፅድቅና ኩነኔን እያነጻጻረ ስለሚሰብክ) ከአዋልድ መጻሕፍት መድባ ትቀበለዋለች፡፡ አራተኛው መጽሐፈ መቃብያን
በሌላ ስሙ መጽሐፈ ዮሴፍ ወልድ ኮርዮን በመባል ይታወቃል፡፡
135
Esther
136
በፋርሳውያን ቋንቋ
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 36
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ምዕራፍ ሶስት
የመዝሙር ክፍል መጽሐፍት
መዝሙር ማለት ምሥጋና ማለት ሲሆን ዘመረ ከሚለው የግእዝ ግስ የተወሰደ ነው፡፡ እነዚህ መጻሕፍት
የትምህርት እና የእውቀት መጻሕፍት ተብለው ይታወቃሉ፡፡137 መጻሕፍቱ በግጥም በዝማሬ እንዲሁም በትረካ
መልክ የተዘጋጁ ናቸው፡፡ ዓላማቸውም ሰውን በለሰለሰ መንገድ ማስተማር መሳብና ወደ መልካም ጠባይ መለወጥ
ነው፡፡ ውድ ተማሪዎች በዚህ ክፍል የምንመለከታቸው የመጽሐፍት ብዛት ስምንት ሲሆኑ ጸሐፊዎቹ ደግም አራት
ናቸው፡፡ ከዚህ በመቀጠልም ስለ እያንዳንዱ መጻሕፍት በዝርዝር ለመመልከት እንሞክራለን፡-
1 መጽሐፈ ኢዮብ138
ኢዮብ ማለት አበባ ማለት ሲሆን ዖፅ በምትባል ሀገር ይኖር የነበረ ጻድቅ ሰው ነው፡፡ ከአኗኗሩና ከሥርዓተ
አምልኮው ተነስተው ከሙሴ ዘመን በፊት አብርሃም አምስተኛ ትውልድ እንደሆነ ሊቃውንት ይናገራሉ፡፡ መጽሐፉ
በአጻጻፉ ከሁለት ምዕራፎች በስተቀር በግጥም መልክ የተጻፈ መጽሐፍ ነው፡፡ መጽሐፉ 42 ምዕራፎች አሉት፡፡
ጸሐፊው ማን እንደሆነ አልታወቀም ነገር ግን በአንዳንድ መጻሕፍት ላይ የመጽሐፉ ጸሐፊ ኢዮብ እንደሆነ
ይገልጣሉ፡፡139 አከፋፈሉም፡-
137
በዘመን ሲቀመጥ ከአዳም ጀምሮ እስከ 70 ዓም ድረስ ያለውን ታሪክ ይተርካል፡፡
138
job
139
መሠረታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ አጠናን ዘዴ ገጽ 108
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 37
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
፪. መዝሙረ ዳዊት140
ዳዊት ከበግ እረኝነት ለንግስናና ለነብይነት የተመረጠ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ዳዊት በነብዩ ሳሙኤል ተቀብቶ
በነገሰ141 ጊዜ ሰባት የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎችን አግኝቷል፡፡ ከእነዚህም አንዱ ሀብተ ትንቢት ነው፡፡ በዚህ ስጦታው
በትንቢት መነጽርነት ያለፈውንና የሚመጣውን ምስጢር ዓለም ተገልጦለት ጽፏል፡፡የተጻፈበት ዘመን 1000 ዓ.ዓ
አካባቢ ነው፡፡ በእስራኤልም ሆነ በክርስቲያኖች ዘንድ ለቤተክርስቲያንም ሆነ ለግል ጸሎት እጅግ የተወደደ ሲሆን
በይዘቱም መዝሙር፣ ጸሎት፣ ትምህርትና ቅኔ በአንድነት ይገኙበታል፡፡ መጽሐፉን አሁን ባለበት ሁኔታ አሰባስቦ
ያዘጋጀው ካህኑ ዕዝራ ነው፡፡ መዝሙረ ዳዊት ደረቅ ሐዲስ በመባልም ይታወቃል ምክንያቱም ስለ ክርስቶስ ስለ
እመቤታችን ስለ ምዕመናን /ቤተክርስቲያን/ በግልጥና በብዛት ስለሚናገር ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በይዘቱ
ከመዝሙረ ዳዊት ሰባት ዋና ዋና መንፈሳዊ ነገሮችን እንማራለን፡-
1. ጠላትን መውደድ /መዝ 16፡4/ 5. ኃጢአትን ማመን /መዝ 37፡4/
2. ትህትና /መዝ 21፡6/ 6. ሰርየተ ኃጢያት /ይቅርታ/ መዝ 50፡2
3. ሃይማኖት /መዝ 21፡10/ 7. ምጽዋት /መዝ 111፡9/
4. ተስፋ መንግስተ ሰማያት /መዝ 26፡13/
መዝሙረ ዳዊት “ከዘላለም እስከ ዘለዓለም እግዚአብሔር ይባረክ አሜን አሜን” በሚለው ቃል ለአምስት
ከፍለን ማየት ይቻላል፡፡ ይህም፡-
ከምዕራፍ 1-40 ድረስ
ከምዕራፍ 41-71 ድረስ
ከምዕራፍ 72-88 ድረስ
ከምዕራፍ 89-105 ድረስ
ከምዕራፍ 106-150 ድረስ
በቅድስት ቤተክርስቲያንም ምዕመናን ለጸሎት ከሚጠቀሙባቸው መጻሕፍት መካከል አንዱ ነው፡፡ ይህም
ሰዎች በዚህ ዓለም ከሚያጋጥሟቸው ሁኔታዎች ሁሉ ምን መጸለይ እንደሚገባቸው የሚያስረዳ መጽሐፍም ስለሆነ
ነው፡፡ የተወደዳችሁ ተማሪዎች ከዚህ በመቀጠልም የመጽሐፉን ይዘት በሰንጠረዥ መልክ የምንመለከት ይሆናል፡፡
ተከተሉን፡-
140
pslams
መምህር ቸርነት አበበ “መሰረታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ አጠናን ዘዴ በሚለው መጽሐፋቸው ላይ እንደገለጹት ከሆነ የዳዊት የንግስና ዘመን ከ1011-971 ዓ.ዓ
141
4 መጽሐፈ ተግሳጽ
ከመጽሐፈ ምሳሌ ጋር ተመሳሳይ አቀራረብ ያለው ሲሆን 7 ምዕራፎች አሉት፡፡ በንጉስ ሰሎሞን በአጉርና
እና በልሙኤል የተነገሩ ሲሆን በ780 ዓ.ዓ በንጉስ ሕዝቅያስ ዘመን ከነቢያት የተሰበሰቡ ናቸው፡፡ በአማርኛው
በመጽሐፈ ምሳሌ 25፡31 ጀምሮ በቅንፍ “ተግሳጽ” ተብሎ ተገልጧል፡፡
አከፋፈሉም፡-
ከምዕራፍ 1-5 የንጉስ ሰሎሞን ምሳሌዎች
ምዕራፍ 6 የማሳ አገር ሰው አጉር ለኢትኤልና ለኡካል የተናገረው
ምዕራፍ 7 የማሳ ንጉስ የልሙኤል ቃል
142
proverbs
143
ጠቢቡ ሠሎሞን 3ዐዐዐ ምሳሌዎችና 1ዐዐ5 መዝሙራት የጻፈ ታላቅ የጥበብ አባት ነው፡፡ /1ኛ ነገ 4፣32/
144
1ነገ 3፡6-9
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 39
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
5. መጽሐፈ ጥበብ
የዚህ መጽሐፍ ጸሐፊ ሰሎሞን ሲሆን በ19 ምዕራፎች የተከፋፈለ ነው፡፡ ከመጽሐፈ ምሳሌ ጋር ተመሳሳይ
ሀሳብ አለው ስለጥበብ በመናገር ሰው ጥበብን እንዲፈልግ ይመክራል፡፡ የተጻፈበት ዘመን ከመጽሐፈ ምሳሌ
አይለይም፡፡ አጠቃላይ ይህ መጽሐፍ ስለ ሦስት ዋና ዋና ነገሮች ይናገራል፡-
1. ስለ መነናውያም
2. ስለ አይሁድ
3. ስለ ሰዶማውያን
6 መጽሐፈ መክብብ145
መክብብ ማለት አለቃ፣ ሹም፣ ሰባኪ ወይም አስተማሪ ማለት ነው፡፡ ይህን መጽሐፍ የጻፈው ንጉስ ሰሎሞን
ሲሆን በሌላ አጠራር መጽሐፉ ጥበብ ባጉር ይባላል፡፡ ባጉር የሰሎሞን የፍልስፍና ስሙ ሲሆን የዓለምን ከንቱነት
እንዲሁም ከፀሀይ በታች ምንም አዲስ ነገር እንደሌለ ይናገራል፡፡ የጭንቅና የህይወት ፍፃሜ ሳይደርስ ሁሉ ከንቱ
ስለሆነ በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ በማለት ከራሱ ህይወት በመነሳት ያስተምራል፡፡ በአጠቃላይ መጽሐፉ
12 ምዕራፎች ያሉት ሲሆን አከፋፈሉም፡-
ምዕራፍ 1 ከፀሐይ በታች ሁሉም ዞሮ ዞሮ እንደሚመጣና ፍጻሜም እንደሌለዉ
ምዕራፍ 2 የዚህ አለም ደስታ የሆነዉ ሁሉ ከንቱና ሁሉም ነፋስን እንደመከተል የማያጠግብ እንደሆነ
ከምዕራፍ 3-11 ዓለም ምንም ውብ ብትሆን ሰው ግን ተስፋውን ሊመሰርትባት እንደማይገባ
ምዕራፍ 12 አጥጋቢ ደስታ የተትረፈረፈ ሕይወት በዓለም ነገር በማናቸዉም በኩል እንደማይገኝ
8. መጽሐፈ ሲራክ
ሲራክ ማለት ጸሐፊ ማለት ነው፣፡ መጽሐፉ በዚህ ቅጽል ስም ይጠራ እንጂ የጸሐፊው ዋና ስም ኢያሱ
ይባላል፡፡ በ80 ዓ.ዓ በግዞት እያለ ጽፎታል ስለ መንፈሳዊና ስለስጋዊ ሕይወት ጥበብና ምክር ይሰጣል፡፡ ሲራክ
ስጋዊና መንፈሳዊ ጥበብን ከእግዚአብሔር ለምኖ ተገልጾለት የጻፈው ነው፡፡ መጽሐፉ 51 ምዕራፎች አሉት፡፡
በአቀራረቡም ከመጽሐፈ ምሳሌ ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡
ምዕራፍ አራት
የትንቢት ክፍል
ነቢይ149 ማለት አፈ እግዚአብሔር ፣መምህር ፣ወደፊት የሚሆነውንና ከሱ በፊት የሆነዉን የሚናገረው
የሚተነብይ ማለት ሲሆን የሚናገረው ቃል ደግሞ ትንቢት150 ይባላል፡፡ ነቢያት በተለያዩ ክፍሎች ይከፈላሉ፡፡
በመጀመሪያ ከትንቢት አገላለጻቸው አንጻር በሁለት ይከፈላሉ
ሀ. የቃል ነቢያት፡- የተናገሩትን ትንቢት በመጽሐፍ ያልጻፉ ታሪካቸው በቅዱሳን መጻሕፍት ተጽፎ
የሚገኙ ናቸው፡፡ ለምሳሌ ኤልያስ፣ ኤልሳዕ፣ ናታን፣ ጋድ ወዘተ… ናቸው፡፡
145
Ecclesiastes
146
Song of solomon
147
መኃ 1፡1
148
ኤፌ 5፡21፡33
149
አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመጽሐፈ ሰዋሰው ወግስ ላይ ነብይ የሚለውን ቃል ሲተረጉሙት በተመሳሳይ “መንፈሰ ትንቢት ያደረበት፣ ራዕይ
የሚያይ፣ትንቢት የሚናገር፣ ሰባኪ መምሕር ማለት ነው፡፡ በማለት ይተረጉሙታል፡፡ (ገጽ 620)
150
ትንቢት ማለት በቁሙ ራዕይ ንግግር ገና ወደፊት የሚመጣ ነገር፣ አስቀድሞ የሚታይና የሚገለበጥ፣ ከመንፈስ ቅዱስ የሚሠጥ ማለት ነው፡፡ (መጽሐፈ
ሰዋሰው ወግስ ገጽ 620)
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 40
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ለ. የጽሑፍ ነቢያት፡- 16ቱን መጽሐፍት የፃፉ ነብያት ናቸው፡፡ እነዚህ ነብያት ደግሞ የተናገሩትን
ትንቢት በመጽሐፍ ያሰፈሩ ናቸው፡፡
ከዚህ በተጨማሪ ነብያት በጻፏቸው መጻሕፍት ብዛትና በማዕረጋቸው እንዲሁም በፃፉት መጽሐፍ ይዘት
መሰረት ለሁለት ይከፈላሉ፡፡
ሀ. ዐበይት ነብያት፡- በዚህ ክፍል ዉስጥ የሚመደቡት ነብያት አራት ናቸው፡፡ እነርሱም፡- ነብዩ
ኢሳይያስ፣ ነብዩ ኤርምያስ፣ ነብዩ ህዝቅኤል እና ነብዩ ዳንዔል ናቸዉ፡፡
ለ. ደቂቅ ነብያት፡- በዚህ ክፍል ዉስጥ ቀሪዎቹ 12 ነብያት ይመደባሉ፡፡
1. ትንቢተ ኢሳይያስ151
ኢሳይያስ ማለት መድኃኒት152 ማለት ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ “እግዚአብሔር ደህንነት ነው” የሚልም
ትርጓሜ ይሰጣል፡፡ ኢሳይያስ አባቱ አሞጽ ይባላል፡፡ ከዓበይት ነቢያት የሚመደብ ነብይ ነው፡፡ ኢሳይያስ ከዘመነ
አካዝ ጀምሮ ይታወቅ የነበረ በዘመነ ምናሴ በመጋዝ ተተርትሮ ያረፈ የይሁዳ ነቢይ መሆኑ በሊቃውንተ
ቤተክርስቲያን ይነገራል፡፡ የነበረበት ዘመን በ700 ዓ.ዓ አካባቢ ሲሆን 66 ምዕራፎች ያሉት መጽሐፍ ጽፏል፡፡
በትንቢቱም ስለባቢሎን ምርኮና ከምርኮ ስለመመለሳቸው እንዲሁም ጽዮን153 በሚል ስያሜ ስለተጠሩ ስለ
ኢየሩሳሌም፣ ስለ እስራኤል፣ ስለ ቤተክርስቲያን፣ ስለ እመቤታችንና መንግስተ ሰማያት የተነበየ ነብይ ነው፡፡154
ከዚህም በተጨማሪ ስለጌታ ሰው መሆን የተለያዩ ግልጽ ትንቢቶችን ተናግሯል፡፡155 በዚህም ምክንያት በሊቃውንተ
ቤተክርስቲያን “ወንጌላዊው ነቢይ” ሲባል መጽሐፉ ደግሞ “ደረቅ ሐዲስ” ተብሎ ይጠራል፡፡ አከፋፈሉም፡-
ከምዕራፍ 1-12 ይሁዳንና ኢየሩሳሌምን የሚመለከቱ ትንቢቶች
ከምዕራፍ 13-23 ከይሁዳና ከእስራኤል ውጪ የሆኑ አሕዛብን የሚመለከቱ ትንቢቶች
ከምዕራፍ 24-35 በዓለም ላይ ስለሚሆነው የመጨረሻ ፍርድ እና እግዚአብሔር መንግስት
ከምዕራፍ 36-39 ስለ እስራኤላውያን መሸነፍና የኢየሩሳሌም ህዝብ በባቢሎን ስለመማረካቸው
ከምዕራፍ 40-55 በባቢሎን ምርኮ ምክንያት በባቢሎን የሚኖሩ አይሁድን የሚያጽናና እና ወደ
ሀገራቸው አየሩሳሌም ለመመለስ የሚያደርጉትን ዝግጅት የሚያሳይ የትንቢት ክፍል
ከምዕራፍ 56-66 ስለጽዮን (ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም) ዘላለማዊ ክብር የተነገሩ
ትንቢት የክፉዎች መወገድና ስለ እግዚአብሔር ሕዝብ
151
Isaiah
152
አባቶቻችን እንደሚተረጉሙት ከሆነ ኢሳይያስና ኢያሱ በትርጓሜ ተመሳሳይ ናቸው፡፡ የሁለቱም ትርጉም “መድኃኒተ ስጋ ማለት ሲሆን ኢየሱስ ማለት ግን
“መድኃኒተ ስጋ ወነፍስ ማለት ነው፡፡ ይህም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የነፍስም የስጋም መድኃኒት መሆኑን የሚያመላክት ነው
153
ጽዮን ማለት አምባ ማለት ነው፡፡ (የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገጽ 280)
154
ለምሳሌ የሚከተሉትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ይመልከቱ፡- ኢሳ 8፡18፣ 18፡7፣ 24፡23፣ 49፡14፣ 60፡14፣ ወዘተ....
155
ለምሳሌ የሚከተሉትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ይመልከቱ፡- ኢሳ 7፡14፣ 9፡6፣ 53፡1
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 41
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
2. ትንቢተ ኤርምያስ156
ኤርምያስ ማለት “እግዚአብሔር ከፍ ከፍ ያደርጋል” ማለት ነው፡፡157 አባቱ በኢዮስያስ ዘመን የሕጉን
መጽሐፍ ያገኘው ኬልቅያስ መሆኑን ብዙ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ያምናሉ፡፡ ከእናቱ ማህጸን የተመረጠና158 በ20
ዓመቱ የነቢይነትን አገልግሎትን የጀመረ ነቢይ ሲሆን የኖረውም ከ600 ዓ.ዓ ጀምሮ እንደሆነ ይነገራል፡፡ ኤርምያስ
በባቢሎን ምርኮ አብሮ የተማረከ ከምርኮም የእስራኤል ልጆች እየመራ የመጣ በመጨረሻም በድንጋይ ተወግሮ
በሰማዕነት ያረፈ የይሁዳ ነቢይ ነው፡፡159 ትንቢት በሚናገርበት ዘመን ሁሉ መከራ ስለነበረና እያለቀሰ ይናገር
ስለነበር “የሐዘን የሰቆቃ ነቢይ” ሲባል እስራኤል ደግሞ “አልቃሻው ነቢይ” ብለው ይጠሩታል፡፡ መጽሐፉ 52
ምዕራፎች አሉት በይዘቱም ስለ ኢየሩሳሌምና ስለ ጐረቤት አገሮች፣ ስለ ባቢሎን ምርኮና ህዝቡ ከበደላቸው
እንዲመለሱ ማስጠንቀቅ ነው፡፡ አከፋፈሉም፡-
ከምዕራፍ 1-2 የነብዩ መጠራት
ከምዕራፍ 3-20 የሕዝቡ በደልና ወደ እግዚአብሔር ተመለሱ የሚል ተግሳጽ ያስተላለፈበት
ከምዕራፍ 21-29 ለህዝቡ ለምርኮኞችና ለሐሰተኛ ነብያት ያስተላለፈው መልዕክትና የተሰጡ
ምልክቶች
ከምዕራፍ 30-33 እግዚአብሔር ስለህዝቡ ስለ ኢየሩሳሌምና ስለ አዲስ ኪዳን የሰጠው ተስፋ
ከምዕራፍ 34-39 ስለኢየሩሳሌም መውደቅ
ከምዕራፍ 40-42 በይሁዳ ከቀሩ ሰዎች ጋር ስለመኖር
ከምዕራፍ 43-44 በግብጽ ስለመኖሩ
ከምዕራፍ 45-52 በህዝቡ ላይ ስለተነገሩ ትንቢቶችና ስለኢየሩሳሌም መውደቅ
ከዚህ መጽሐፉ በተጨማሪ አብረው የሚቆጠሩ በእርሱና በደቀመዝሙሩ በባሮክ የተጻፉ መጻሕፍት አሉ፡፡
እነሱም፡-
ሰቆቃው ኤርምያስ160 ፡- ኤርምያስ ከተማረከ በኃላ በቤሩት አፋፍ ላይ ቆሞ የተናገረዉ የሀዘን ቃል
ነዉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ እስራኤላዉያን በባቢሎን ሳይማረኩ በናቡከደነፆር ተከበዉ ሳሉ የጻፈው
እንደሆነ ይነገራል፡፡ መጽሐፉ 5 ምዕራፎች ያሉት ሲሆን በይዘቱም እስራኤል በእግዚአብሔር ፊት
በመበደላቸዉ በባቢሎዉያን የደረሰባቸዉን ጥፋት እና በንስሐ በመመለሳቸዉ ስለተሰጣቸው ተስፋ
እንዲሁም ከምርኮ መልስ ያለውን የኢየሩሳሌም ገጽታ ሃያ ሁለቱን161 አሌፋት መነሻ በማድረግ
የሚተነትን መጽሐፍ ነዉ፡፡
ተረፈ ኤርምያስ ፡- ይህ መጽሐፍ የኤርምያስ አርአያ መጽሐፍ በመባል ይታወቃል፡፡
መጽሐፈ ባሮክ ፡- ባሮክ ማለት ብሩክ ማለት ነው፡፡ ባሮክ የነብዩ ኤርምያስ ታማኝ ወዳጅና ጸሐፊ
ነው፡፡ መጽሐፉ የተጻፈው በባሮክ አማካይነት ሲሆን የተጻፈዉም በባቢሎን ምርኮ ለነበሩት
እስራኤላዉያን ነው፡፡ በውስጡም፡- በምርኮ ስላሉት አይሁድ ኑሮ፣ ስለ ንስሃና ስለጸሎት ለአይሁድ
የቀረቡ ምክሮች ይገኙበታል፡፡
3. ትንቢተ ሕዝቅኤል162
ሕዝቅኤል ማለት “እግዚአብሔር ብርታትን ይሰጣል” ማለት ሲሆን ከጌታ ልደት በፊት በ6ዐዐ ዓ.ዓ አካባቢ
የነበረ ነብይ ነው፡፡ በልጅነቱ ወደ ባቢሎን የተማረከ ነብይ ነው፡፡163 ካህንም እንደነበረ በመጽሐፉ ጽፏል፡፡ በዚያም
እያለ ለ2ዐ ዓመታት ሲያገለግል ቆይቶ በሰማዕትነት ያረፈ ነቢይ ነው፡፡ መጽሐፉ 48 ምዕራፎች ሲኖሩት
አከፋፈሉም፡-
156
jeremiah
157
የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገጽ 183
158
ኤር 1፡5
159
በባቢሎን ምርኮ የተማረከውም ለነብይነት በተጠራ ከ40 ዓመት በኋላ ነው፡፡ (የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገጽ 183)
160
lamentations
161
ሀያ ሁለቱ አዕሌፋት የሚባሉት የእግዚአብሔር ሕቡዕ ስሞች ናቸው፡፡ እነዚህን ስሞች ከሰቆቃው ኤርምያስ በተጨማሪ በመዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ 118 ላይ
እናገኛቸዋለን፡፡
162
Ezekiel
163
የባቢሎን ምርኮ የሆነው በ597 ዓ.ዓ ነው፡፡ (የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገጽ 25)
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 42
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
4. ትንቢተ ዳንኤል164
ዳንኤል ማለት “እግዚአብሔር ፈራጅ /ዳኛ/ ነው”165 ማለት ሲሆን ከነቢዩ ሕዝቅኤል ጋር በምርኮ ጊዜ አብሮ
የነበረ ጓደኛው ነው፡፡ የዳንኤል ሌላ ስሙ ብልጣሶር ሲሆን166 የባቢሎን ነቢይም ይባላል፡፡ መጽሐፉ 12 ምዕራፎች
ሲኖሩት በውስጡም፡- ስለ ሰለስቱ ደቂቅ ታሪክ ነቢዩ ስለራሱ የጻፈው ታሪክ እንዲሁም በተለያዩ ጊዜዎች የሚፈፀሙ
በምሣሌ ያያቸው ራዕዮች ተካተዋል፡፡
አከፋፈሉም፡-
ምዕራፍ 1 የዳንኤል ወደ ባቢሎን መማረክና መሾም
ምዕራፍ 2 ዳንኤል አንደኛውን የናቡከደነፆር ሕልም መተርጎሙ
ምዕራፍ 3 ሰልስቱ ደቂቅ በእቶን እሳት መጣላቸውና መዳናቸው
ምዕራፍ 4 ዳንኤል 2ኛውን የናቡከደነፆርን ህልም መተርጎሙና ፍፃሜው
ምዕራፍ 5 ዳንኤል በግድግዳ ላይ ስለብልጣሶር የተጻፈውን ቃል መተርጎሙ
ምዕራፍ 6 ዳንኤል ዳርዮስን እያገለገለ በአንበሳ ጉድጓድ መጣሉና መዳኑ
ከምዕራፍ 7-12 ስለ መሲህ መምጣት፣ ስለ ቅዱሳን መላዕክት ተራዳኢነት
5 ትንቢተ ሆሴዕ168
ሆሴዕ ማለት “እግዚአብሔር ያድናል” ማለት ሲሆን ከጌታ ልደት በፊት ከ765-725 ዓ.ዓ የነበረ ነቢይ ነው፡፡
በት.ሆሴ 6፡1 11፡1-7 ላይ እንደተጠቀሰው ትንቢቱን በራሱ በሚስቱ169 እና በልጆቹ እየመሰለ በእስራኤልና
በእግዚአብሔር መካከል ያለውን ግንኙነት ይናገር ነበር፡፡ መጽሐፉ 14 ምዕራፎች ያሉት ሲሆን በውስጡም፡-
እስራኤል ጣዖት በማምለካቸው የእግዚአብሔርን ሕግ ስለመጣሳቸው እንዲሁም ስለ ጌታችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ
ትንቢቶችን ተናግሯል፡፡ አከፋፈሉም፡-
ከምዕራፍ 1-3 የሆሴዕ ሚስት የጎሜር ማመንዘር ለእስራኤል መንፈሳዊ አመንዝራነት
164
Daniel
165
“ዳን ማለት ዳኛ ማለት ሲሆን ኤል ማለት ደግሞ የእግዚአብሔር ስሙ ነው፡፡ (የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገጽ 244 እና 245 ላይ ያሉትን ትርጉሞች
ይመልከቱ)
166
ት.ዳን 1፡7
167
ት.ዳን 3፡24-25
168
Hosea
169
ጎሜር ትባላለች፡፡ ይህች ሴት የዴብላይም ልጅ እና የኢይዝራኤልና የሎሩሃማ የሎዓሚ እናት ስትሆን ውሽሞቿን ተከትላ በባርነት የተሸጠች ነገርግን በሏ
ሆሴዕ ከባርነት የመለሳት ሴት ናት፡፡ (የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገጽ 262
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 43
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
6 ትንቢተ አሞጽ170
አሞጽ ማለት “ኃይል” ማለት ሲሆን ከእረኝነት የተጠራ የእስራኤል/የሰማርያ/ ነቢይ ነው፡፡ መጽሐፉ ዘጠኝ
ምዕራፎች ያሉት መጽሐፍ ሲሆን በይዘቱም፡- የፍልስጥኤምና የእስራኤል ኃጢአት በመብዛቱ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ፣
በሳምራውያን ላይ የሚመጣ ቁጣና ለእስራኤል የተነገረ ተስፋ ይገልጻል፡፡ መጽሐፉ ዘጠኝ ምዕራፎች ያሉት ሲሆን
አከፋፈሉም፡-
ከምዕራፍ 1-2 ፍርድ በእስራኤልና በእስራኤል ጎረቤት ሀገሮች
ከምዕራፍ 3-6 ፍርድ በእስራኤልና አለመመለስና ኃጢአት ምክንያት
ከምዕራፍ 7-9 እግዚአብሔር በእስራኤላውያን ላይ ስለሚመጣው ፍርድና በፍጻሜ ዘመን ስላለው
ተስፋ
ሚክያስ172 ማለት “እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው?”173 ማለት ሲሆን ከ722 ዓ.ዓ በፊት የነበረ የይሁዳ
ነቢይ ነው፡፡ ነብዩ ሚክያስ የብንያም ነገድ ሲሆን የነቢዩ ኢሳይያስ ጓደኛ የነበረ ነቢይ ነው፡፡ ነብዩ የጻፈው መጽሐፍ
ሰባት ምዕራፎች ያሉትን የትንቢት መጽሐፍን ሲሆን በይዘቱም፡- ስለ ሠማርያ እና እየሩሳሌም መፍረስ በኋላም
እግዚአብሔር ህዝቡን እንደመንጋ እንደሚሰበስብ እና እየሩሳሌምን ዳግም እንደሚሰራ፣ አህዛብም እግዚአብሔርን
እንደሚፈልጉ ይህም በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚፈጸም ተንብዮዓል፡፡174
አከፋፈሉም፡-
ከምዕራፍ 1—3 የሰማርያና የኢየሩሳሌም መፍረስ
ምዕራፍ 4 የእግዚአብሔር መንግስት መመስረት
ምዕራፍ 5 ከቤተልሔም የሚወጣ ገዢና እረኛ
ምዕራፍ 6 እግዚአብሔር ከህዝቡ ጋር ያለው ክርክር
ምዕራፍ 7 ተግሳጽና ተስፋ
8 ትንቢተ ኢዮኤል175
ኢዩኤል ማለት “እግዚአብሔር አምላክ ነው” ማለት ሲሆን ከጌታ ልደት በፊት በ6ዐዐ ዓ.ዓ የነበረ የይሁዳ
ነቢይ ነው፡፡ አባቱ ባቱዔል የሚባል የእስራኤል ነብይ ነው፡፡176 መጽሐፉ 3 ምዕራፎች ሲኖሩት በይዘቱም፡- በህዝቡ
ላይ ሊወርድ ስላለው የአንበጣ መንጋ ህዝቡ በጾምና በጸሎት ወደ አምላኩ እነዲቀርብ ማስጠንቀቅ፣ ስለ ርደተ
መንፈስ ቅዱስ /ስለ መንፈስ ቅዱስ መውረድ/ እንዲሁም ስለ እግዚአብሔር ቀን ይገልጣል፡፡177
አከፋፈሉም፡-
ምዕራፍ 1፡1-12 የአንበጣ መቅሰፍት
ምዕራፍ 1፡13-2፡27 ንስሐ ለሚገቡ የእግዚአብሔር በረከት
ምዕራፍ 2፡28-32 የእግዚአበሔር መንፈስ መፍሰስ
ምዕራፍ 3፡1-15 የዓለም ህዝቦች ፍርድ
170
Amos
171
Micah
172
የሚክያስ ቅጽል ስም “ሞሬታዊው ሚክያስ ሲባል ይህንን ስያሜ ያገኘው “ሞሬሼት ጌት በተባለች ከተማ ነው፡፡ ( ትንቢተ ሚክያስ 1፡1 እና የመጽሐፍ
ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገጽ 51
173
የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገጽ 51
174
ለምሳሌ የሚከተሉትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ይመልከቱ፡- ሚክ 1፡6፣ 2፡12፣4፡1-2 ፣7፡14፣ 7፡16
175
Joel
176
የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገጽ 176
177
ት.ኢዩ 1፡4፣ 3፡14፣ 2፡28
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 44
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
9 ትንቢተ አብድዮ178
አብድዮ ማለት “የእግዚአብሔር አገልጋይ” ማለት ሲሆን ለነብይነት ከመጠራቱ በፊት የእስራኤል ንጉስ
ለነበረው ለአክዓብ የቤቱ አዛዥ ነበር፡፡ ንግስቷ ኤልዛቤልም የእግዚአብሔር ነብያትን ባስገደለች ጊዜ መቶ ነብያትን
የሸሸገ ሰው ነው፡፡ ከጌታ ልደት በፊትም በ6ዐዐ ዓ.ዓ የነበረ የሰማርያ ነቢይ ነው፡፡ የጻፈው መጽሐፍም 1 ምዕራፍ
ሲኖረው ከነቢያት መጽሐፍት በጣም ትንሹ (ትንሽ ምዕራፍ ያለው) መጽሐፍ ነው፡፡ የሚናገረውም ስለ ኤዶምያስ
ነው፡፡ አከፋፈሉም፡-
ከቁጥር 1-9 በኤዶም ላይ ስለሚፈጸመው ፍርድ
ከቁጥር 10-14 ኤዶም በእስራኤላውያን ላይ ስለፈጸመችው በደል
ከቁጥር 15-21 ፍርድ በኤዶምያስና በአህዛብ ላይ የጽዮን መዳን
፲ ትንቢተ ዮናስ179
ዮናስ ማለት የዋህ ርግብ ማለት ነው፡፡ ዮናስ ከጌታ ልደት በፊት 9ዐዐ ዓ.ዓ የነበረ ነብይ ሲሆን ይኖር
የነበረውም በገሊላ በጋትሔፌር ከተማ ነበር፡፡180 መጽሐፉ በአራት ምዕራፎች የተከፈለ ነው፡፡ ዮናስ በቤተክርስቲያን
ሊቃውንት ትምሕርት በነብዩ በኤልያስ ዘመን የነበረና ኤልያስ ከሙታን ያስነሳው የመበልቲቱ ልጅ ነው፡፡ ካስነሳው
በኋላም የኤልያስ ደቀመዝሙር ሆኖ አድጓል፡፡ መጽሐፉ በይዘቱ፡- ዮናስ እግዚአብሔር ወደላከው ሃገር አልሄድም
ብሎ መኮብለሉ፣ በድጋሚ የዮናስ መላክና የነነዌ ንስሀና በንስሀቸዉም ሊደርስ የነበረው ጥፋት መመለሱ በዚህም
ምክንያት የነቢዩ አለመደስት ይገልጻል፡፡ አከፋፈሉም፡-
ምዕራፍ 1 ዮናስ ወደ ተርሴስ መኮብለል
ምዕራፍ 2 የዮናስ ጸሎትና መመለስ
ምዕራፍ 3 በዮናስ ስብከት ከንጉሱ እስከ ህዝቡ በንስሀ መመለስ
ምዕራፍ 4 የዮናስ ቁጣና የእግዚአብሔር መልስ
፲1 ትንቢተ ናሆም181
ናሆም ማለት “መጽናናት” ማለት ነው፡፡ ከጌታ ልደት በፊት በ7ዐዐ ዓ.ዓ የነበረ ነብይ ሲሆን ይኖርባት
የነበረችው ከተማ ኤልቆሽ ትባላለች፡፡ ይህች ከተማ ከይሁዳ ከተሞች የምትመደብ ናት፡፡182 ናሆም እንደ ነብዩ ዮናስ
በነነዌ ያስተማረ ነብይ ሲሆን ያስተማረበት ምክንያትም ከነብዩ ዮናስ አገልግሎት በኋላ በድጋሚ በመበደላቸው
የተነሳ ነው በዚህም የተነሳ እንደ ነብዩ ዮናስ የአህዛብ ነብይ ተብሎ ተጠርቶአል፡፡ መጽሐፉ 3 ምዕራፎች ያሉት
ሲሆን ይዘቱም፡- ስለ ይሁዳ ሕዝብና ስለ እስራኤል ነፃ መውጣት ስለ ነነዌ ዳግም ጥፋት ይገልጻል፡፡ አከፋፈሉም፡-
ምዕራፍ 1 እግዚአብሔር የፍርድና የበቀል አምላክ መሆኑ
ምዕራፍ 2 የነነዌ ጥፋት
ምዕራፍ 3 የነነዌ ጥፋት ምክንያት
፲2 ትንቢተ ዕንባቆም183
ዕንባቆም ማለት “ማቀፍ/እቅፍ/” ማለት ሲሆን ከጌታ ልደት በፊት በ6ዐዐ ዓ.ዓ የነበረ ነቢይ ነው፡፡ መፅሐፉ
በ3 ምዕራፎች የተከፈለ ሲሆን በይዘቱም፡- አይሁድ በኃጢያታቸው የሚደርስባቸውን መከራ ባቢሎናውያን
በሚገዟቸው ላይ ባደረጉት ግፍ የሚደርስባቸውን ቅጣትና ነቢዩ የጸለየውን ጸሎት ያካትታል፡፡ እከፋፈሉም፡-
ምዕራፍ 1 የነብዩ ዕንባቆም ጥያቄ
178
Obadiah
179
Jonah
180
የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገጽ 238
181
Nahum
182
የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገጽ 145
183
Habakkuk
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 45
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
፲3 ትንቢተ ሶፎንያስ184
ሶፎንያስ ማለት “እግዚአብሔር ሰውሯል” ማለት ሲሆን በ7ዐዐ ዓ.ዓ የነበረ የይሁዳ ነቢይ ነው፡፡ አባቱ ኩሲ
ይባላል፡፡ ሶፎንያስ በይሁዳ ንጉስ በአሞጽ ዘመነ መንግስት የተነሳ ነብይ ነው፡፡ መጽሐፉ 3 ምዕራፎች ሲኖሩት
በይዘቱም፡- አይሁድ እንዲመለሱ ምክርና ማስጠንቀቂያ፣ በኢየሩሳሌም አካባቢ ለሚገኙ ሕዝቦች ማስጠንቀቂያ፣
አህዛብ ወደ እግዚአብሔር እንዲመለሱ እንዲሁም እግዚአብሔር እስራኤልንና ይሁዳን ከምርኮ እንደሚመልሳቸው
ይገልጻል፡፡ አከፋፈሉም፡-
ምዕራፍ 1 ሁሉም ላይ ስለሚመጣው ፍርድ
ምዕራፍ 2 በልዩ ልዩ ሕዝቦች ላይ ስለሚመጣው ፍርድ
ምዕራፍ 3 በይሁዳ ስለሚመጣው ፍርድ እንዲሁም የእስራኤል ከተበተኑበት መሰብሰብና
ከእግዚአብሔር ስለሚያገኙት በረከት
184
Zephaniah
185
Haggai
186
Zechariah
187
ዘካ 1፡12፣ 4፡2፣ 9፡9፣ 14፡10፣ 12፡10
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 46
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ክፍል ሁለት
የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት190
3.፪.1 የቃሉ ትርጉም
አዲስ ኪዳን ማለት አዲስ ውል ስምምነት ማለት ሲሆን እግዚአብሔር ወዶ ፈቅዶ ባስነገረው ትንቢት መሰረት191
የፍቅር አምላክ በማይመረመር ጥበቡ ከድንግል ማርያም ተወልዶ ያደረገው የሰው ልጆችን የማዳን ጉዞና ከእስራኤል
ዘነፍስ /ከክርስትያኖች/ ጋር በክቡር ደሙ ያደረገውን የውል ስምምነት (ኪዳን) ያመለክታል፡፡192 በዚህ ዘመን
የተጻፉት መጻሕፍት የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት በመባል ይታወቃሉ፡፡ ብሉይ ኪዳንና አዲስ ኪዳን የማይነጣጠሉና
አንዱ በአንዱ ላይ ህልው ሆኖ የሚኖር ነዉ፡፡
ብሉይ ኪዳን የአዲስ ኪዳን ንባብ ሲሆን አዲስ ኪዳን የብሉይ ኪዳን ትርጉም ነዉ፡፡
ብሉይ ኪዳን የአዲስ ኪዳን ትንቢት ሲሆን አዲስ ኪዳን የብሉይ ኪዳን ፍፃሜ ነዉ፡፡
ብሉይ ኪዳን የአዲስ ኪዳን ጥላ ሲሆን አዲስ ኪዳን የብሉይ ኪዳን አካል ነዉ፡፡
አዲስ ኪዳን በብሉይ ኪዳን የተሰወረ ሲሆን ብሉይ ኪዳን ደግሞ በአዲስ ኪዳን የተገለጠ ነዉ፡፡
አዲስ ኪዳን የሚለው ቃል ከዚህ ኪዳን በፊት ኪዳን እንደነበረ የሚያስረዳና የቀደመውን ኪዳን መንደርደሪያ
አድርጎ የተነሳ አዲስ የውል ስምምነት መሆኑን የሚገልጥ ቃል ነው፡፡ የአዲስ ኪዳን ዘመን የሚባለው ጌታችን
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ ለድኅነተ ዓለም ቅዱስ ስጋውንና
ክቡር ደሙን ለምዕመናን ለመስጠት አዲስ ውል የተዋዋለበት ዘመን ነው፡፡ ይህም ክፍል ከመጽሐፍ ቅዱስ ሁለት
አበይት ክፍሎች አንዱ ነው፡፡ የዚህ ክፍል መጻሕፍት የተጻፉበት ጊዜ ከ45 ዓ.ም እስከ 100 ዓ.ም ባለው ጊዜ
ውስጥ ነው፡፡ የእነዚህ መጻሕፍት አቀራረብ በታሪክ በትምህርት ወይንም በትንቢት መልክ ቢሆንም ስለ ጌታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ የሚገልጡ ስለሆነና ማዕከላቸው እርሱ ስለሆነ በጥቅሉ ወንጌል ተብለው ሊጠሩ ይችላሉ፡፡ ከዚህም
ሌላ የአዲስ ኪዳን ዘመን ለብሉይ ኪዳን ዘመን ፍፃሜ ስለሆነ በዘመነ ብሉይ የተነገሩ ምሳሌዎችና ትንቢቶች በአዲስ
ኪዳን መጻሕፍት ተጠቅሰው ፍፃሜያቸውና ትርጉማቸው ተገልጧል፡፡193
188
Milachi
189
ት.ሚል 1፡2፣ 3፡1
190
New testment
191
ኤር 31፡31
192
ማቴ 26፡26 ዮሐ 6፡53-59 1ቆሮ 11፡23-26
193
ይህንን ለመረዳት መጻሕፍቱን ሲያነቡ ከህዳጉ ጋር በማስተያየት ያንብቡ፡፡
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 47
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ምዕራፍ አንድ
የወንጌል ክፍል
ወንጌል ማለት ቃሉ የግሪክ ሲሆን “ኢቫንጊሌዩን”194 ከሚለው ቃል የተገኘ ነው፡፡ ትርጉሙ ብስራት፣ የምስራች፣
ስብከት ማለት ነው፡፡ ወንጌል ደስታ/የምስራች/ የሚገለጥበት ቋንቋ ነው፡፡ የእግዚአብሔር ልጅ እንደነገሰ ዲያብሎስ
እንደተዋረደ ሞተ ሥጋ ወነፍስ እንደጠፋ ያወሳልና ነው፡፡ ይህም ቃል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
የተናገረውን ቅዱሳን ሐዋርያትና አርድዕት ያስተማሩትን ሁሉ የሚያጠቃልል ነው፡፡ ይህን ትምህርት ወንጌል
ብሎ የጠራው ራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡195 በዚህ ክፍል ውስጥ አራት የወንጌል
መጽሐፍት አሉ፡፡ እነርሱም፡-
1. የማቴዎስ ወንጌል 3. የሉቃስ ወንጌል
2. የማርቆስ ወንጌል 4. የዮሐንስ ወንጌል ናቸው፡፡
በጸሐፊዎቹ ስም መጠራታቸው ጸሐፊዎቹን ለማስታወቅ እንጂ ወንጌሉ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ
ክርስቶስ ነው፡፡ መጻሕፍቱን በጸሐፊዎቹ ስም የሰየሙት 318ቱ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ናቸው፡፡ አራቱም
ወንጌላት የሚተርኩት ስለ ጌታችን ስለ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቢሆንም በአገላለጥ እንዲሁም በይዘት
አንዱ ከአንዱ ይለያያል፡፡ የማቴዎስ የማርቆስና የሉቃስ በአጻጻፍ ይዘታቸው የሚመሳሰሉ ሲሆኑ ዮሐንስ ደግሞ
ለየት ባለ መልኩ ተጽፈዋል፡፡ በዮሐንስ ወንጌል በአብዛኛው ከጌታ ምድራዊ ልደት አንስቶ ረቀቅ መጠቅ ያሉ
ምስጢራተ መለኮት ተገልጸዋል፡፡ ከአራቱ ወንጌላውያን ማቴዎስና ዮሐንስ ከ12ቱ ሐዋርያት ውስጥ ሲሆኑ
ማርቆስና ሉቃስ ደግሞ ከሰባ ሁለቱ አርድዕት ውስጥ ናቸው፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት አለው፡፡ ከአርድዕት ወገን
የሆኑት ማርቆስና ሉቃስ እንዲጽፉ የተደረገበት ምክንያት ከአርድዕት ለማስተማር ሲወጡ እናንተ የውጭ ሰዎች
ናችሁ የውስጥማ ሰዎች ብትሆኑ ኖሮ ወንጌልን በጻፋችሁ ነበር ብለው አይሁድ ትምህርታቸውን ከመቀበል
ወደኋላ እንዳይሉ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የአርድዕት ክብር በአይሁድም ሆነ በክርስቲያኖች ዘንድ እንዲታውቅ
194
Evangellion
195
ማቴ24፡14፣ ማቴ26፡13፣ ማር16፡15
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 48
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ነው፡፡ አርድዕት በጌታ ዘንድ የከበሩ መሆናቸውን ወንጌሉን በመጻፋቸው ይታወቃል፡፡ ከሐዋርያት ወገንም ሁለቱ
ወንጌል እንዲጽፉ የተደረገው ስለ ወንጌል ክብር ነው፡፡ በአጠቃላይ ወንጌል በአርድዕት ብቻ ተጽፎ ቢሆን ኖሮ
ይህች ተርታ ህግ ናት ደገኛይቱ ህግ በሐዋርያት ልብ ቀርታለች በማለት አይሁድ ወንጌልን ከመቀበል ወደኋላ
ይሉ ነበር፡፡ ይህ እንዳይሆን ወንጌል በሐዋርያትም በአርድዕትም ተጻፈ፡፡
1 የማቴዎስ ወንጌል199
ማቴዎስ ማለት “የእግዚአብሔር ስጦታ” ማለት ነው፡፡ የመጀመሪያ ስሙ ሌዊ ይባላል፡፡200 የአባቱ ስም
ዲቁ /እልፍዮስ/ እናቱ ካሩትሰያ ትባላለች፡፡ ትውልዱ ከ12ቱ ነገደ እስራኤል ከነገደ ይሳኮር ነው፡፡ ለሐዋርያነት
ከመጠራቱ በፊት ቀራጭ ነበር፡፡ አህጉረ ስብከቱ ምድረ እስራኤል፣ ሕንድ፤ ኢትዮጵያ ወዘተ… እንደሆኑ የተለያዩ
የቤተክርስቲያን ታሪክ ጸሐፊዎች ያስረዳሉ፡፡ የቅዱስ ማቴዎስ እረፍቱ ጥቅምት 12 ቀን እንደሆነና ያረፈውም
በሰማዕትነት እንደሆነ በመጽሐፈ ስንክሳር እና በገድለ ሐዋርያት እንዲሁም በመቅድመ ወንጌል ላይ ተጽፎ
እናገኛለን፡፡201 ይህ ወንጌላዊ/ማቴዎስ/ ከአራቱ የሥላሴ መንበር ከሚሸከሙ ኪሩቤል በገፀ ሰብዕ/በሰው መልክ/
ይመሰላል፡፡ ምክንያቱም የጌታን ደኃራዊ ልደት /በሥጋ መወለድ/ ከሰው ወገን አንደሆነ “የዳዊት ልጅ የአብርሃም
ልጅ” በማለት ያስረዳልና ነው፡፡202 ወንጌሉ የተጻፈበት ዘመን ከኢየሩሳሌም ጥፋት ቀደም ብሎ ሲሆን ዘመኑም
በመቅድመ ወንጌል ላይ በገላውዴዎስ ቄሣር ዘመነ መንግስት ጌታ ባረገ በዘጠነኛው ዓመት እንደሆነ ይገልፀዋል፡፡
በዘመናዊ ታሪክ ጸሐፊዎች ዘንድ መጽሐፉ በ58 ዓ.ም እንደተጻፈ ይታመናል፡፡ ስለተጻፈበት ቦታ ደግሞ ሲገልፅ
በፍልስጤም ተጀምሮ በህንድ ሀገር እንደተፈፀመ በመቅድመ ወንጌል ላይ የተገለፀ ሲሆን የተጻፈበት ቋንቋ
እብራይስጥ እንደሆነ ይታመናል፡፡ ምክንያቱም የተጻፈላቸው ሰዎች አይሁድ /ዕብራውያን/ ስለሆኑ ነው፡፡ ይህንን
ወንጌል ወንጌላዊ ዮሐንስ ለተማሪዎቹ ከእብራይስጥ ቋንቋ ወደ ግሪክ ቋንቋ ተርጉሞላቸዋል፡፡ ማቴዎስ በሀገረ
196
synoptic
197
ማቴ 1፡1-17፣ ማር 8፡32፣ ሉቃ 3፡23-38
198
ዮሐ 1፡1-3፣ 3፡13፣ 6፡4-5፣ 8፡23
199
Matthiew
200
ማቴ 9፡9
201
አንዳንድ የታሪክ ጸሐፊዎች ቅዱስ ማቴዎስ ወደ ኢትዮጵያ ገብቶ እንዳስተማረና በኢትዮጵያም ሠማዕትነትን እንደተቀበለ ይገልጣሉ፡፡ ነገርግን ይህ
በኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ዘንድ ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ነው ምክንያቱም ኢትዮጵያ ከቅዱስ ማቴዎስም ስብከት በፊት አምልኮተ እግዚአብሔርን
የተቀበለች ሃገር ነች፡፡ በንጉስ ሰሎሞንም ዘመን የመጣችው ኢትዮጵያዊት ንግስት ማክዳ (ሳባ) የተናገረችው ንግግር ለዚህ ማስረጃ ነው፡፡ (2ነገ 10፡9) እናም
በዚህም መነሻነት ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ቅዱስ ማቴዎስ በኢትዮጵያ ሠማዕነትን እንደተቀበለ አያምኑም፡፡
202
ማቴ 1፡1
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 49
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
2 የማርቆስ ወንጌል203
ማርቆስ እናቱ ማርያም አባቱ አርስጦቡሎስ ይባላሉ፡፡ እናቱ ቤቷን ለትምህርተ ወንጌል ከመልቀቋም በላይ
የመጀመሪያ ቤተክርስቲያን የተመሠረተችውም ለቅዱስ ሐዋርያትም መንፈስ ቅዱስ የወረደላቸው በዚህችው
ከማርቆስ እናት ቤት ነው፡፡204 ማርቆስ በሌላ ስሙ ዮሐንሰ ተብሎ ይታወቃል፡፡205 ትርጉሙም “ፀጋ እግዚአብሔር”
ማለት ነው፡፡ ማርቆስ ማለት ደግሞ “ንብ” ማለት ነው፡፡ ንብ ማርዋን ለማዘጋጀት አስቀድማ ከተለያዩ አበቦች
እንደምትቀስም ሁሉ ቅዱስ ማርቆስም በመጀመሪያ ከጌታ ቀጥሎም ከሐዋርያት ስለተማረ ነው፡፡ ቅዱስ ማርቆስ
ከጌታ ዕርገት በኋላ የቅዱስ ጴጥሮስ ተከታይ በመሆን አገልግሏል፡፡ የቅዱስ ጴጥሮስ አህጉረ ስብከቶች በሆኑት
በሮምና በእስክንድርያ አስተምሯል፡፡ በተለይ ለእስክንድርያና ለሊቢያ ቤተክርስቲያን መስራች አባት እንደሆነ
ይነገርለታል፡፡ በነዚህ አገሮች ክርስትናን አስፋፍቶ ሚያዚያ 3ዐ ቀን 67 ዓ.ም በእስክንድርያ ከተማ በ70 ዓመቱ
በሰማዕትነት አርፏል፡፡ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ በገፀ አንበሳ ይመሰላል፡፡ ምሳሌውም አንበሳ ለላህም ጌታዋ ነው
ይሰብራታል ቅዱስ ማርቆስም በግብጽ የነገሰ አምልኮ ላህምን አጥፍቷልና በዚህ ይመሰላል፡፡ ቅዱስ ማርቆስ
ወንጌሉን የጻፈላቸው ለሮም ሰዎች በሮማይስጥ ቋንቋ ነው፡፡ ለዚህም ማስረጃ በሮማይስጥ ቋንቋ የሚታወቁት
ቃላት በወንጌሉ ይገኛሉ፡፡206 የተጻፈበት ዘመን እንደ ቤተክርስቲያን ትውፊት ጌታ ካረገ በኋላ በ11ኛው ዓመት
አልቆ በ12ኛው ዓመት ላይ ነው፡፡ መጽሐፉ 16 ምዕራፎች ያሉት ሲሆን በይዘቱም የክርስቶስን የኃይል ሥራ
በማጉላት ከጥምቀቱ እስከ እርገቱ ያለውን ታሪክ አውስቷል፡፡ አከፋፈሉም፡-
ከምዕራፍ 1-3 ጥምቀቱ፣ ድውይ መፈወሱ፣ አጋንንት ማውጣቱ
ከምዕራፍ 4-5 የዘሪው ምሳሌ፣ ነፋሳትን መገሰጹ፣ ሌጌዎን የነበረበት ሰው፣ ደም የሚፈሳትን ሴት
መፈወሱ፣ የምኩራብ አለቃውን ልጅ ከሞት ማንሳቱ
ከምዕራፍ 6-8 የዮሐንስ ሞት፣ የሐዋርያት በሥልጣን መላክ፣ በረከተ ኅብስት፣ ድውይ መፈወሱና
በቂሳርያ ሐዋርያትን መጠየቁ
ከምዕራፍ 9-10 ደብረ ታቦር፣ ጋኔን ማውጣቱ፣ የአይሁድ ጥያቄ፣ አይነ ስውሩ በርጠሜዎስ
ምዕራፍ 11 ሆሳዕና፣ ፍሬ የጠፋባት በለስ፣ ከቤተ መቅደስ ነጋዴዎችን ማስወጣቱ
ከምዕራፍ 12-13 የመንግስተ ሰማያት ምሳሌ፣ ትንሳኤ ሙታን፣ ፈሪሳውያንን መገሰጹ
ከምዕራፍ 14-16 ነገረ ምጽአት፣ ፋሲካ፣ ስቅለቱ፣ ትንሳኤውና እርገቱ
203
Mark
204
ሐዋ 2፡1
205
ሐዋ 12፡12
206
ማር 5፡9፣ 15፡16
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 50
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
3 የሉቃስ ወንጌል207
ሉቃስ ማለት “ሉካኖስ” ማለት ሲሆን ትርጉሙም “መብራት” ማለት ነው፡፡ አንድም ሉቃስ ማለት “ዐቃቤ
ስራይ (ሃኪም)” ማለት ነው፡፡ ለስብከተ ወንጌል ይፋጠናልና አንድም “መበስር (ነጋሪ)” ማለት ነው፡፡ የሉቃስ
ትውልድ ከአህዛብ ወገን ነው፡፡ አገሩ በገድለ ሐዋርያት ድልማጥያ ነው፡፡ ሲል በሌላ ታሪክ ደግሞ አንጾኪያ ነው
ይላል፡፡ ቅዱስ ሉቃስ ከመጠራቱ በፊት የሚያውቃቸው ሙያዎች ነበሩት፡፡ እነዚህም አንደኛው ባለመድኃኒት
/ሐኪም/ ነበር፡፡ ይህንንም ቅዱስ ጳውሎስ “የተወደደው ባለመድኃኒት” ብሎ መስክሮለታል፡፡208 ሁለተኛው ደግሞ
ሰዓሊ ነበር፡፡ በትውፊት ታሪክ ቅዱስ ሉቃስ ሰዓሊ እንደነበረ እንዲሁም የእመቤታችንን ምስለ ፍቁር ወልዳ
ስዕልንም የሳለው እሱ እንደሆነ ይነገራል “ከወንጌላውያን አንዱ የሆነው ጥበበኛው ሉቃስ ለሳላት ስእልሽ ሰላምታ
ይገባል፡፡” እንዲል መልክአ ስዕል ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ በመቄዶንያ ቅዱስ ጳውሎስ ባስተማራቸው ቦታዎች
በተለይም በሮም አስተምሯል፡፡ ቅዱስ ሉቃስ በኔሮን ዘመን ጥቅምት 22 በ84 ዓመቱ በሰማዕትነት አርፏል፡፡
ከዚያም ሥጋውን ወደ ባህር ቢጥሉት እግዚአብሔር ማዕበል አስነስቶ ወደ አንዲት ደሴት አወጣው በዚያም የመነነ
ክርስቲያን አግኝቶ ገንዞ ቀብሮታል፡፡ ወንጌላዊው ከአራቱ ገፀ ኪሩብ በገጸ ላህም ይመሰላል፡፡ ምክንያቱም የጌታን
በከብቶች በረት መወለድ ይጽፋልና፡፡209 ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን የጻፈበት ቦታ መቄዶንያ በዮናኒ ቋንቋ እንደሆነና
የተጻፈበት ዘመን ጌታ ባረገ 21ኛው ዓመት ተፈጽሞ በ22ኛው ዓመት እንደሆነ መቅድመ ወንጌሉ ያወሳል፡፡
ዘመናዊው ታሪክ ደግሞ ወንጌሉ ቅዱስ ጳውሎስ በቂሳርያ በታሰረበት ጊዜ በዚያው ቦታ በግሪክ/ጽርዕ/ ቋንቋ
እንደተጻፈ ያስረዳል፡፡ ወንጌላዊው ወንጌሉን የጻፈው ለመቂዶንያ ባለሥልጣን ለነበረው ለቴዎፍሎስ እንደሆነ
ገልጧል፡፡210ይህም ሰው በስብከቱ ያመነ ሰው ነው፡፡ ቴዎፍሎስ ማለት የእግዚአብሔር ወዳጅ ማለት ነው፡፡
አንዳንዶች ከዚህ ትርጉም መነሻነት ወንጌሉ የተጻፈው ለአንድ ግለሰብ ሳይሆን የእግዚአብሔር ወዳጅ የተባሉ
ወንጌሉን እንዲያነቡ ለተጻፈላቸው ሰዎች ሁሉ ነው የሚሉም አሉ፡፡ ይህ ግን ስህተት ነው፡፡ ለጊዜው ለዚህ አንድ
ሰው እንደተጻፈ “የከበርክ ቴዎፎሎስ ሆይ” የሚለው ቃል ላይ ያለው መልእክት በቂ ነው፡፡ የሉቃስ ወንጌል
“ወንጌለ አንዕስት” በመባል ይጠራል ምክንያቱም በሌሎች ወንጌላት የማናገኛቸውን የሴቶች ታሪክ በዚህ ወንጌል
እናገኛለን ለአብነትም፡- የእመቤታችንን፣ የቅድስት ኤልሳቤጥን፣ የማርያም እንተ እፍረትን፣ወዘተ… የመሳሰሉትን
ሴቶች ታሪክ የያዘ በመሆኑ ነው፡፡ ስለ መንፈስ ቅዱስ ጸጋ ደጋግሞ ይገልፃልና “ሰባኪ መንፈስ ቅዱስ” ተብሎም
ይጠራል፡፡ እንዲሁም “የአህዛብ ወንጌል” ተብሎም ይጠራል፡፡ ምክንያቱም ለአህዛብ ስለተጻፈ ነው፡፡ እንደ አህዛብ
ልማድም መጽሐፉ ትረካን ከማብዛቱ በተጨማሪ አህዛብ ሱባኤ የመቁጠር ትንቢት የመጠበቅ ልማድ ስለሌላቸው
ከነብያት ትንቢት በብዛት አልጠቀሰም፡፡ ከዚህም ውጪ ወንጌሉ ከጌታ ጽንሰት ጀምሮ እስከ እርገቱ ድረስ ያደረጋቸው
ተአምራትና ትምህርት በስፋት ይገኙበታል፡፡211 መጽሐፉ 24 ምዕራፎች ሲኖሩት አከፋፈሉም፡-
ከምዕራፍ 1-2 ልደተ ዮሐንስ፣ ብስራተ መልአክ፣ የጌታ ልደትና አስተዳደግ
ከምዕራፍ 3-5 ማስተማር መጀመሩ፣ የትውልድ ሐረጉ፣ በዲያቢሎስ መፈተኑ፣ በምኩራብ
ማስተማሩ፣ የሌዊ ግብዣ
ከምዕራፍ 6-7 ድውይ መፈወሱ፣ አጋንንትን ማውጣቱ፣ ትምህርተ ብጹአን፣ የመቶ አለቃውን
ልጅ ማዳኑ፣ የመበለቷን ልጅ ማስነሳቱ፣ የዮሐንስ መልእክተኞች፣ ማርያም እንተ እፍረት
ምዕራፍ 8 ማርያም መግደላዊት፣ የዘሪው ምሳሌ፣ ነፋሳትን መገሰጹ፣ ጋኔን ማውጣቱ፣ ደም
ይፈሳት የነበረችውን ሴት ማዳኑ፣ የምኩራብ አለቃውን ልጅ ማዳኑ
ከምዕራፍ 9-14 ተልዕኮተ ሐዋርያት፣ በረከተ ኅብስት፣ ደብረ ታቦር፣ ደጉ ሳምራዊ፣ ማርያምና
ማርታ፣ ጸሎት፣ ፈሪሳውያን፣ ታማኝ መጋቢ የገሊላውያን ጥፋት፣ ሰንበትና መንግስተ ሰማያት
ከምዕራፍ 15-17 የጠፋው ልጅ፣ ዓመጸኛው መጋቢ፣ አልአዛር ነዳይ፣ 10 ለምጻሞች፣ ነገረ
ምጽአት
ከምዕራፍ 18-20 ፈሪሳዊና ቀራጭ፣ ዕውር ማብራቱ፣ ዘኪዎስ፣ 10ሩ ባሮች፣ ሆሳዕና፣ የወይን
አትክልት ምሳሌ፣ ትንሳኤ ሙታን፣ የአይሁድ መገሰጽ
ከምዕራፍ 21-24 ጸሪቀ መበለት፣ ነገረ ምጽአት፣ ፋሲካ፣ ስቅለት፣ ትንሳኤና እርገት
207
Luke
208
ቆላ 4፡14
209
ሉቃ 2፡1
210
ሉቃ 1፡1-4
211
ከወንጌላት ሁሉ ከጌታ ጽንሰት እስከ እርገት የሚገልጥ መጽሐፍ የሉቃስ ወንጌል ብቻ ነው፡፡
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 51
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
4 የዮሐንስ ወንጌል212
ዮሐንስ ማለት “ፍስሃ ወሐሴት/ተድላ ደስታ/” ማለት ነው፡፡ አንድም “የእግዚአብሔር ጸጋ (ስጦታ) ነው”
ማለት ነው፡፡ አንድም “ርህራሄ ወሳህል (ሩህሩህ መሐሪ)” ማለት ነው፡፡ አባቱ ዘብዴዎስ እናቱ ማርያም
ይባላሉ፡፡213 ይህ ወንጌላዊ ቁጥሩ ከ12ቱ ሐዋርያት ሲሆን ብዙ መጠሪያዎች አሉት፡፡ “የዘብድዎስ ልጅ”፣
“የነጉድጓድ ልጅ”፣ “የጌታ ወዳጅ”(ፍቁረ እግዚእ)፣ “ታዖሎጎስ” (የመለኮት ምስጢር ተናጋሪ ወይም “ነባቤ መለኮት”)
“አቡቀለምሲስ” /ባለራዕይ/ ይባላል፡፡ ለሐዋርያትነት የተጠራውም ከወንድሙ ከያዕቆብ ጋር ዓሣ በማጥመድ ላይ
ሳለ ነበር፡፡214 ቅዱስ ዮሐንስ ያስተማረበት አገር የተለያየ እንደሆነ ይነገራል በመጀመሪያ ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር
በኢየሩሳሌምና በአካባቢዋ በአንጾኪያ ነበር፡፡ ከዚያም ሎዶቅያ አስተምሯል፡፡ ኤፌሶን የነበረውን የአርጤምስ ጣኦተ
አምልኮ በመቃወም ሲያስተምር ተይዞ በድምጥያኖስ ፍርድ በፍጥሞ ደሴት ታስሯል፡፡ በቤተክርስቲያን ሊቃውንት
ዘንድ ቅዱስ ዮሐንስ አርፏልም ተሰውሯዋልም ይባላል፡፡ እረፍቱን ሲገልፁ እድሜ ጠግቦ አርጅቶ ነው ይሉታል፡፡
ተሰውሯል የሚሉት ደግሞ በዮሐ 21፡22 ላይ “እስክመጣ ይኖር ዘንድ ብወድስ አንተ ምን አግደህ” ያለውን ቃል
ይዘው ዮሐንስ ሞትን አልቀመሰም የሚሉም አሉ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በገጸ ንስር ይመሰላል፡፡ ምክንያቱም
ንስር እንደሌሎች እንስሳት በእግሩ ይሽከረከራል ከእነርሱ ተለይቶ በክንፍ መጥቆ ይበራል ዮሐንስም እንደወንድሞቹ
ሐዋርያት የሰው ልጅ ከሰማይ ወረደ እያለ ምድራዊ ልደቱን ይናገራል፡፡ ከእነርሱ ለየት ብሎ የሥላሴ አካል
ከሕልውና ተገልጦለት “በመጀመሪያ ቃል ነበር” ብሎ ይናገራል፡፡215 የንስር ዓይኑ ጽሩይ ነው ወደላይ ወጥቶ ረቦ
ቁልቁል በተመለተ ጊዜ የሰናፍጭ ቅንጣት ታህል ሥጋ እንኳን አትሰወረውም ያቺን አንስቶም ይመገባታል
ዮሐንስም ንጽሐ ሥጋ፣ ንጽሐ ነፍስና ንጽሐ ልቦና ተሰጥቶት ረቂቅ ምስጢር ተገልጦለት “በመጀመሪያ ቃል ነበር”
ብሎ ተናግሯልና በገጸ ንስር ይመሰላል፡፡ ዮሐንስ ወንጌሉን ራዕይ ባየበትና በጻፈበት በኤዥያን ባህር ውስጥ
በምትገኘው በፍጥሞ ደሴት እንደጻፈው ስንክሳር ላይ ተጽፎ ይገኛል፡፡ በወንጌል ትርጓሜ መቅድም ላይ ደግሞ
በኤፈሶን እንደሆነ ይገልጣል፡፡ መጽሐፉ በግሪክ/ጽርዕ/ ቋንቋ ወይም በዮናኒ ቋንቋ ጌታ ባረገ በ3ዐኛው ዓመት
ለኤፌሶን ሰዎች እንደተጻፈ ይነገራል፡፡ ወንጌሉ የተጻፈበት ዓላማ የኤፌሶን ሰዎች ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር
ልጅ እንደሆነ ያምኑ ዘንድ እንዲሁም በመናፍቃን ይታወኩ ስለነበር የእነርሱን ትምህርት ለመቃወም ነው፡፡
የዮሐንስ ወንጌል የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ታሪክ ከቅድምናው አንስቶ አስከ ሥጋዊው /ሰው መሆኑ/ ከዚያ
እስከ እርገቱ ድረስ ያለውን ታሪክ እንዲሁም በዘመነ ሥጋዌው የሰራውን ተዓምራት /ሥራ/ እና ያስተማረውን
ትምህርትን ይዟል፡፡ መጽሐፉ 21 ምዕራፎች ሲኖሩት አከፋፈሉም፡-
ምዕራፍ 1 ስለ ቃል ቀዳማዊነት፣ የዮሐንስ ምስክርነት፣ የሐዋርያት መጠራት
ከምዕራፍ 2-3 የመጀመሪያው ተኣምር፣ ፋሲካ፣ ንቆዲሞስ፣ የዮሐንስ ምስክርነት
ከምዕራፍ 4-5 ሳምራዊቷ ሴት፣ መጻጉዕ፣ ትንሳኤ ሙታንና ዘላለማዊ ሕይወት
ከምዕራፍ 6-9 በረከተ ኅብስት፣ የሕይወት እንጀራ፣ የዳስ በዓል፣ ዘማዊቷ ሴት፣ የዓለም
ብርሃን፣ እውር ሆኖ የተወለደው
ከምዕራፍ 10-13 አንቀጸ አባግዕ፣ የአላዛር መነሳት፣ ማርያም እንተ እፍረት፣ ሆሳዕና፣ ፋሲካ
ከምዕራፍ 14-16 ስለ ሞቱና ትንሳኤው፣ ስለ እርገቱና ዳግም መምጣቱ፣ ደቀ መዛሙርቱን
ለአባቱ አደራ መስጠቱ
ምዕራፍ 17 ስለ እግዚአብሔር አብ
ከምዕራፍ 18-21 ስቅለቱ፣ ሞቱና ትንሳኤው
ምዕራፍ ሁለት
የታሪክ ክፍል
የተወደዳችሁ ተማሪዎች በዚህ ክፍለ ትምህርት ከአዲስ ኪዳን ዘመን መጻሕፍት ሁለተኛ ክፍል የሆነውንና
በውስጡ አንድ መጽሐፍ የያዘውን የታሪክ ክፍል እንመለከታለን፡፡ በውስጡ የሚካተተው መጽሐፍም የሐዋርያት
ስራ ነው፡፡ ሐዋርያት ማለት “ሖረ” ሄደ፣ ተጓዘ፣ ተላከ፣ መሰከረ፣ አስተማረ፣ ወዘተ.... ከሚለው የግዕዝ ግስ
212
John
213
ማቴ 20፡20
214
ማቴ 4፡21፣ ማር 1፡19
215
ዮሐ 1፡1
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 52
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
የተገኘ ሲሆን ታዛዥ፣ ምስክር፣ መምሕር፣ መልእክተኛ ማለት ነው፡፡ይህ ስያሜ የተሰጣቸው ጌታችን
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመረጣቸው 12ቱ ሐዋርያት ናቸው፡፡ እነዚህ ሐዋርያት ወንጌልን በዓለም ዞረው
ያስተምሩ ዘንድ በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የተላኩ ናቸው፡፡216
ምዕራፍ ሦስት
የትምህርት/የመልእክታት/ መጻሕፍት ክፍል
በዚህ ክፍል ቅዱሳን ሐዋርያት ቀደም ብለው ላስተማሯቸውና በተለያዩ ምክንያቶች ላመኑ ምዕመናን
የጻፉት መልእክታት ከጌታ ትንሣኤ በኋላ ከማረጉ በፊት የተሰጡ የቤተክርስቲያን መመሪያ ትምህርቶች እንዲሁም
በሐዋርያት ጉባኤ /ሲኖዶስ/ የተሠሩ ሥርዓቶች ይካተታሉ፡፡ ይህ ክፍል በውስጡ 21 መጻሕፍትን ያጠቃልላል፡፡
216
ማቴ 10፡2-7
217
Acts
218
ሉቃ 1፡1 ሐዋ 1፡1
219
ማቴ 28፡20
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 53
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
220
Romans
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 54
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ልጅነታቸው በኦሪታቸው እየተመኩ አህዛብን ሲነቅፉ አህዛብ ደግሞ አየሁድ እግዚአብሔርን እያወቁ መበደላቸውን
እርሱ/አህዛብ/ ቢያጠፉም ባለማወቃቸው መሆኑን እያነሱ የአንዲት ቤተክርስቲያን ልጆች በማይረባ ነገር
ተለያይተው ሲኖሩ ይህን ያስተዋሉ አቂላና ጵርስቅላ የተባሉ ባልና ሚስት ፌቨን የተባለች እናት ይህንን ችግር
ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ቆሮንቶስ በወጣ ጊዜ ነገሩት ሁለቱንም አህዛብንም አይሁድንም ለማስታረቅ ሁለቱም የዳኑት
በእግዚአብሔር ቸርነት መሆኑን ለማስረዳት በሃይማኖት በምግባር ለማጽናት አይሁድ በኦሪታቸው መመካታቸውን
አህዛብም ባለማወቅ ማመካኘታቸውን ትተው በወንጌሉ ተመስርተው በሃይማኖት እንዲጸድቁ ለማስተማር በ52
ዓ.ም ጽፎ የክንክራኦስ ቤተክርስቲያንን በምታገለግል በፌቨን እጅ ልኮላቸዋል፡፡ መልእክቱን እርሱ ቢልከውም
የጻፈው ጠርጥዮስ የተባለ ሰው ነው፡፡ መልእክቲቱ በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት መረጃነት የተጻፈች ጥቅል ትምህርት
የምትሰጥ ናት፡፡ በአጻጻፋም ከእብራውያን መልእክት ጋር ይመሳሰላል፡፡ የመልእክቱ ይዘትና አከፋፈልም፡-
ከምዕራፍ 1፡1-17 የመግቢያ ሰላምታ
ከምዕራፍ 1፡18-3 ስለ አረማውያን፣ ስለአይሁዳውያንና ስለ እግዚአብሔር ጽድቅ
አስፈላጊነት
ከምዕራፍ 4-5 የእግዚአብሔር ጽድቅ ለሰው በእምነት የሚገኝ ስለ መሆኑ
ከምዕራፍ 6-8 ሰው በጽድቅ ሕይወት የሚኖር ከሆነ ኃጢአት ከህግና ከሞት ነፃ ስለመሆኑ
ከምዕራፍ 9-11 ስለ እስራኤል መመረጥና ተስፋ
ከምዕራፍ 12፡15-16 ስለ ክርስቲያኖች በዓለም፣ በግልና፣ በቤተክርስቲያን መኖር
ምዕራፍ 16 ስለ ቅዱስ ጳውሎስ ሰላምታ፣ የአደራ ምስጋና ጸሎት
221
1 Corinthians
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 55
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
222
2 Corinthians
223
Galatians
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 56
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
224
Ephesians
225
Philippians
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 57
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
226
Colossians
227
1 Thessalonians
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 58
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
228
2 Thessalonians
229
1ተሰ 4፡17
230
1 Timothy
231
2 Timothy
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 59
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
፲2 ወደ ቲቶ የተላከ መልእክት232
ቲቶ የተወለደው በቆሮንቶስ ሲሆን አባቱና እናቱ ግሪካውያን ናቸው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስን የተከተለው
በአንፆኪያ ነው፡፡ ከጢሞቴዎስ ጋር ቅዱስ ጳውሎስን በትምህርት፣ በመልእክተኛነት፣ በመከራው ጊዜ ሁሉ
ረድቶታል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ “በሃይማኖት ኀብረት እውነትኛ ልጄ” ብሎ ይጠራዋል፡፡233ብቃቱንም አይቶ የቀርጤስ
ሊቀ ጳጳስ አድርጐ ሾሞታል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ካረፈ በኋላ ወደ ሀገረ ስብከቱ ተመልሶ ሲያገለግል ቆይቶ በ94
ዓመቱ አርፏል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ መልእክቱን የላከበት ምክንያት የቀርጤስ ሊቀ ጳጳስ አድርጎ ስለሾመው ካህናትን
የሚሾምበት፣ ሕዝቡን የሚመራበት፣ ቤተክርስቲያንን የሚያስተዳድርበት ሥርዓትን /ሥርዓተ ኖሎትን/
ለማስተማር ነው፡፡ የሀገሩን /የቀርጤስን/ ሰዎች ክፋት ሳይፈራ እንዲያስተምር እንዲገስፅ ለማበረታታት ኒቆጽልን
ከተባለች ቦታ በ63 ዓ.ም ጽፎ በደቀመዝሙሩ በአርጣማ እጅ ላከለት፡፡ ይህ መልእክት 3 ምዕራፎች ሲኖሩት
አከፋፈሉም፡-
ምዕራፍ 1 የመግቢያ ሰላምታና በቀርጤስ ስላለችው የቤተክርስቲያን አስተዳደር
ምዕራፍ 2 ቲቶን መሪ አድርጎት አርአያነቱን እንዲጠብቅ
ምዕራፍ 3 ግብረ ገብነትን ማስተማር እንደሚገባው
232
Titus
233
ቲቶ 1፡4
234
ፊሊ 1፡22
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 60
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
የቤተክርስቲያን ሊቃውንት ግን ጸሐፊው ቅዱስ ጳውሎስ እንደሆነ ይገልፃሉ፡፡ ይህን ሲያስረዱ በዕብ 13፡23
ላይ የተጠቀሰውን የጢሞቴዎስን ስም መነሻ በማድረግ ነው፡፡ ከእነዚህም አባቶች መካከል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ይገኝበታል፡፡ ሐዋርያው በዚህች መልእክቱ ስሙን ያልጠቀሰበት ምክንያት፡-
አህዛብ ከአይሁድ ይልቅ ወንጌልን ለመቀበል ስለተዘጋጁ ቅዱስ ጳውሎስ አህዛበ ክርስቲያኖችን
ይወዳቸው ነበር፡፡ በዚህ ምክንያት አይሁድ ይጠሉት ነበርና ገና ስሙን በመልእክቱ ሲያዩ
መልእክቲቱን አንቀበልም ብለው ሳያነቡ እንዳይቀሩ፡፡
አጻጻፉ የግሪክ አጻጻፍን የመሰለው በመጀመሪያ ቅዱስ ጳውሎስ በዕብራይስጥ ቋንቋ ከጻፈው በኋላ
ወንጌላዊው ሉቃስ ወደ ግሪክ ቋንቋ በሚተረጉምበት ወቅት የአጻጻፉን ዘይቤ ለውጦታልና ነው፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ የኦሪት ሊቅ በመሆኑ ይህን መልእክት ለየት ባለ አገላለጽ የቤተመቅደስን
አገልግሎትና ሥርዓተ ኦሪትን በመጥቀስ ፍጻሜውን ለአይሁድ ፅፎላቸዋል፡፡
በዕብ 2፡3 ላይ ወንጌልን የተቀበለው ከሌላ ሰው እንደሆነ የገለፀው ራሱን ከእብራውያን ጋር ቆጥሮት
ለትህትና እንጂ ወንጌሉን ከሌላ ሰው እንደተቀበለ ለማስረዳት ፈልጎ አይደለም
ፊርማውንም ያላሰፈረው ጸሐፊው እርሱ መሆኑን ላለማሳወቅ ነው፡፡
ይህ መልእክት የተጻፈበት ምክንያት አይሁድ “ወንጌል ያለ ኦሪት ጥምቀት ያለ ግዝረት ክርስቶስ ያለ ሙሴ
አይጠቅሙም ኦሪትን ገንዘብ አድርጋችሁ ያዙ” እያሉ የክርስቲያኑን ልብ ከፍለው አንዳንዶቹ ወደ ኦሪት
እምነታቸው እየተመለሱ በመግባታቸው ወንጌል ከኦሪት፣ ጥምቀት ከግዝረት፣ ክርስቶስም ከሙሴ እንደሚበልጡ
ለማስረዳትና ከዚህ ጥፋት እንዲመለሱ ለማስተማር ከዚህም ሌላ አይሁድ ከሮማውያን አገዛዝ ነፃ ለመውጣት
ይታገሉ ነበር፡፡ በዚህ ትግላቸው ክርስቲያን አይሁድ ስላልተባበሩአቸው ይነቅፏቸውና ተጽእኖ ያደርጉባቸው ነበር፡፡
በዚህ ምክንያት ክርስቲያን አይሁድ ሊተባበሩአቸው ሲነሱ ክርስትናውን ትተው ወደ ኦሪት ገብተው ካልሆነ
አይሆንም ስላሏቸው ክርስትናውን እየተው ወደ አይሁድ ይቀላቀሉ ጀመር፡፡ ከዚህም ጥፋታቸው እንዲመለሱ
ለምመከርና የዳኑት መከራው የበዛባቸውን ለማጽናናት የቀድሞ አባቶችን እየጠቀሰ ለማበረታታት ጽፎላቸዋል፡፡
በመጨረሻም በብሉይ ኪዳን የነበሩ ሰዎችን ሥርዓቶችን ንዋየ ቅድሳትን እና ዘመነ ብሉይን እያነሳ ለዘመነ አዲስ
እንዴት ምሣሌ እንደሚሆን አስረድቷል፡፡ ይህ መልእክት 13 ምዕራፎች ሲኖሩት በሮም የመጀመሪያው እሥራቱ
ማብቂያ ላይ እያለ በ6ዐ ዓ.ም ጽፎ በጢሞቴዎስ እጅ ልኮላቸዋል፡፡አከፋፈሉም፡-
ከምዕራፍ 1፡1-3 የመግቢያ ሰላምታ
ከምዕራፍ 1፡4-4 ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነና ከቅዱሳን መላእክትና ከቅዱሣን ነቢያት
እንደሚበልጥ
ከምዕራፍ 5-1ዐ ሰለ ኢየሱስ ክርስቶስ የዘለዓለም ክህነት
ከምዕራፍ 11፡1-39 ስለ ሃይማኖት ታላቅነት
ከምዕራፍ 13፡18-25 ማጠቃለያ
235
Hebrews
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 61
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ለ. ሰባቱ መልእክታት
በዚህ ክፍል ውስጥ የምናገኛቸው መጻሐፍት ብዛት 7 ሲሆኑ ጸሐፊያኑ ብዛታቸው 4 ናቸው፡፡ እነዚህም፡-
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ……………… 2 መልእታትን
ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ……………….. 3 መልእክታትን
ሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ………………….. 1 መልእክትን
ሐዋርያው ቅዱስ ይሁዳ…………………… 1 መልእክትን ጽፈዋል፡፡
236
ዮሐ 1፡43
237
ማቴ 4፡18
238
ማቴ 16፡18፣ ዮሐ 21፡15-17፣ ሐዋ 2፡14-37
239
ኮሊሲየም በሚባል አደባባይ (የትያትር ቦታ)
240
1 Peter
241
2 Peter
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 62
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ነው፡፡ መጽሐፉ የተጻፈው በዛን ወቅት የነበሩ ክርስቲያኖች የትኛው ትምህርት እውነት እንደሆነ አውቀው
በክርስትና ሕይወታቸው ከበፊቱ ይበልጥ እንዲተጉ፣ ከሀሰት መምሕራን ተጠብቀው በእውነተኛ የሐዋርያት
እንዲመሩ ለማሳሰብ፣ የሚሞትበት ጊዜ ስለቀረበ ለሁልጊዜ የሚጠቀሙበትን ምክሩን ሊለግሳቸው የጻፈው ነው፡፡ይህ
መልእክት በ66 ዓ.ም አካባቢ የተጻፈ ሲሆን 3 ምዕራፎች አሉት፡፡ አከፋፈሉም፡-
ምዕራፍ 1 ስለ ተላለፈላቸው የወንጌል እውነተኛነት
ምዕራፍ 2 ስለ ሐሰተኛ መምህራን መነሳትና ጠቃሚ ትምህርት
ምዕራፍ 3 ቃሉን በማሰብ ስለሚደረግ ጥንቃቄ
242
1 John
243
2 John
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 63
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ሳይወናበዱ በፍቅር በአንድነት እንዲኖሩ ሮምናም በተሰጣት ጸጋ ጸንታ እንድትኖር ለመምከርና ለማበረታታት
እንዲሁም ስለመልካም ሥራዋ ለማመስገን ይህቺን መልእክት ጽፎ ልኮላታል፡፡ መጽሐፉ 1 ምዕራፍ ያለው ሲሆን
አከፋፈሉም፡-
ከቁጥር 1-3 ሰላምታ
ከቁጥር 4-6 አንድነታቸውን አጽንተው እንዲኖሩ
ከቁጥር 7-11 የሐሰት ትምሕርትን መቃወም
ከቁጥር 12-13 ለሌሎች የቀረበ ሰላምታ
244
3 John
245
james
246
በኖቱ ገጽ 20 ላይ ያለውን በእስራኤላውያን የወንድም ትርጉምን ይመልከቱ፡፡
247
በኖቱ ገጽ 17 ላይ ያለውን ለሰዎች የሚሰጡ ቅጽል ስሞችን ይመልከቱ፡፡
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 64
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ክፍል አራት
የትንቢት መጻሕፍት
በዚህ ክፍል እንደ ብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ብዙ የትንቢት መጻሕፍት አልተጻፈም አብዛኛው ትንቢተ
ነቢያት ፍፃሜ ያገኘው በዘመነ አዲስ ነውና፡፡249ይህ ሲባል ግን ምንም የትንቢት መፃሕፍት አልተጻፈም ማለት
አይደለም በወንጌላቱ በመልእክታቱ ከተነገሩት ትንቢቶች ሌላ በመደበኛነት የተጻፈ አንድ የትንቢት መጽሐፍ አለ፡፡
ይህም የዮሐንሰ ራዕይ ነው፡፡
የዮሐንስ ራዕይ250
እግዚአብሔር ለመረጣቸው ሰዎች ምሥጢር ከሚገልጽበት መንግድ አንዱ ራዕይ ይባላል፡፡ በዚህ መንገድ
ቀደም ሲል ለክቡራን ነቢያት ብዙ ምስጢር ተገልጦላቸው በቃል አስተምረዋል በመጽሐፍቶቻቸውም ጽፈዋል፡፡
ቅዱሣን ሐዋርያትም ምሥጢር ተገልጦላቸው አስተምረዋል በየመጻሕፍቶቻቸውም ጽፈዋል፡፡ ከእነዚህም አንዱና
ዋነኛው ቅዱስ ዮሐንሰ ወንጌላዊ ነው፡፡ ይህ ሐዋርያ የሥላሴ ምስጢር ተገልጦለት ንጽሐ ሥጋ፣ ንጽሐ ነፍስ፣
ንጽሐ ልቦና ተሰጥቶት ከጻፈው ድንቅ ወንጌል ሌላ እጅግ የሚያስደንቅ ብዙ ምስጢራትን ያዘለ ለጊዜው ለሰባቱ
የታናሽ እስያ አብያተ ቤተክርስቲያን ፍፃሜው ለምዕመናን ሁሉ ጠቃሚ የሆነ መጽሐፈ በራዕይ ተገልጦለት
ጽፏል፡፡ እነዚህ ሰባቱ የእስያ አብያተ ክርስቲያን የተመሠረቱት በሰባቱ ዮናናውያን ሕዝቦች ውስጥ መካከል ነው፡፡
እነዚህ ህዝቦች የተገኙትም እስያ ከተባለ ሰው ነው፡፡ እስያም ከነገደ ያፌት የተወለደ ሲሆን ያፌት ደግመ የኖህ
ልጅ ነው፡፡ ሰባቱ ዮናናውያን የተባሉት ህዝቦች
1. ኤፌሶን 5. ፊልድልፍያ
2. ሰምርኔስ 6. ሰርዴስ
3. ጴርጋሞን 7. ሎዶቅያ ናቸው፡፡
4. ትርያጥሮን
ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ከእመቤታችን እረፍት ከ49 ዓ.ም በኋላ ወደ ሐገረ ስብከቱ ወደ ኤፌሶንና አካባቢው
ወዳሉ ሀገሮች በመግባት እየተዘዋወረ ወንጌል በመስበኩ ሕዝቡ ያመልኩት ከነበረው አምልኮ ጣዖት ከአርጤምስና
ከዜውስ ጣዖታተ አምልኮና ከሰባቱ ከዋክብት አምልኮ ተላቀው ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር ከገቢረ ኃጢአት ወደ
ገቢረ ጽድቅ ተመልሰው አምነው ተጠመቁ በሚቆጥሩባቸው በሚያመልኩባቸው ሰባት ከዋክብት አንፃር በብርሃነ
ትምህርታቸው የምዕመናን ልቦና ብሩህ የሚያደርጉ ሰባት መንፈሳውያን ከዋክብት /ኤጲስ ቆጶሳትን/ ሾመላቸው፡፡
የጣዖት ካህናትም ከንጉሡ ከድምጥያኖስ ዘንድ ከሰውት በፍልውሃ እንዲሰቃይ ካደረጉት በኋላ ወደ ፍጥሞ ደሴት
እንዲጋዝ አደረጉት በብዙ ስቃይ በኋላ ከደቀመዝሙሩ ከአብሮኮሮስ ጋር እዚች ደሴት ደረሰ፡፡ ከዚህ በኋላ ወንድሞቹ
248
Jude
249
ማቴ 5፡17
250
Revelation
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 65
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
በዚህ መጽሐፍ ከተለያዩ ምሣሌያዊ ምሥጢራት ሌላ ለሃይማኖትና ለሥነ ምግባር ጠቃሚ የሆኑ
ትምህርቶችና ምስክሮች ተካተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም መጽሐፉ ስለፃድቃንና ሰማዕታት፣ ስለሐዋርያትና ስለ
ነቢያት፣ ስለመምህራንና ካህናት እንዲሁም ስለምዕመናን ክብር፣ ስለቅዱሣን መላእክት ማዕረግ ክብርና ተግባር
በስፋት ይገልፃል፡፡ ይህ መጽሐፍ በዘመነ ሰማዕታት /በዲዮቅልጢያኖስ የስደት ዘመን/ ምዕመናን በተሰደዱና በተደሉ
ጊዜ ጠፍቶ /ተቃጥሎ/ በርዕሱ ብቻ ሲታወስ የቆየ ሲሆን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በዚህ መጽሐፍ መጥፋት ታላቅ
የሆን መንፈሳዊ ቅንዓት ይዞት በደሴተ አጥራክያ በስደት እያለ ሱባዔ ይዞ እግዚአብሔርን ቢለምን የናቡከደነጾርን
ህልም ከነ ትርጓሜው ለነቢዩ ዳንኤል እንደተገለጠለት ሁሉ ለቅዱስ ዮሐንሰ አፈወርቅም ወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስ
ያየውን ራዕይ ከነትርጓሜው ተገልጦለት ጽፎታል፡፡ ከዚህ በኋላ የሚነሱ ሰዎች የራሳቸውን ሐሳብ
እንዳይጨምሩበትና ከተጻፈውም እንዳይቀንሱ ማስጠንቀቂያውን የጻፈው ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ነው፡፡252
መጽሐፉ 22 ምዕራፎች ሲኖሩት አከፋፈሉም፡-
ከምዕራፍ 1-3 ወደ ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት የተላከ
ከምዕራፍ 4-5 በሰማያት ስላለው ኑሮ
ከምዕራፍ 6-11 ስለ ሰባቱ ማህተሞችና መለከቶች
ከምዕራፍ 12-13 ስለ ዘንዶው /ስለ ሐሳዊው መሲህ/
ምዕራፍ 14 በሰማያት ስለሚሆኑ ነገሮች
ከምዕራፍ 15-16 ስለ ሰባቱ ጽዋዎች
ከምዕራፍ 17-19 ስለ ባቢሎን መፍረስ
ከምዕራፍ 20-22 ስለ እግዚአብሔር መንግስት
ክፍል አምስት
የሥርዓት መጻሕፍት
ከ35ቱ የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት መካከል ስምንቱ የአዲስ ኪዳን የቀኖና /የሥርዓት/ መጻሕፍት በመባል
ይታወቃሉ፡፡ እነዚህ መጻሕፍት የተጻፉበት ቋንቋ የሶሪያ ቋንቋ በሆነው በሱርስት ቋንቋ ሲሆን አንዳንድ ሊቃውንት
ደግሞ በፅርዕ ቋንቋ እንደተጻፉ ይገልጻሉ፡፡ በኋላ የተነሱ ሊቃውንትም የሱርስትና የግሪኩን ቋንቋ መሰረት በማድረግ
ወደ ተለያዩ ቋንቋዎች ተርጉመዋቸዋል፡፡253 የተጻፉበት ጊዜ ከትንሳዔ በኋላ ሲሆን በቅዱሳን ሐዋርያት ተጽፈዋል፡፡
እነዚህ መጻሕፍት በ3 ዋና ዋና ክፍሎች ይከፈላሉ፡፡ እነሱም፡-
ሀ. በቤተክርስቲያን አመሰራረት፡- የቤተክርስቲያን አወቃቀር፣ አጠቃላይ የአገልግሎት ሥርዓትና ትምህርት
ክፍል የሚያተኩሩ ናቸው፡፡ እነዚህም፡- ዲዲስቅልያና መጽሐፍተ ሲኖዶሳት /ትዕዛዝ፣ ግጽው፣አብጥሊስ፣ ሥርዓተ
ፅዮን/ ናቸው፡፡ እነዚህም ሐዋርያት በየጊዜው በመንፈስ ቅዱስ መሪነት እየተሰበሰቡ ያዘጋጁዋቸው መጻሕፍት
ናቸው፡፡
251
ራዕ 2፡1፣ 14
252
ራዕ 22፡18
253
ፍትሀ ነገስት መቅድም
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 66
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ለ. የኪዳን ክፍል፡- ይህ ክፍል ደግሞ 2 የኪዳን መጻሕፍትን የያዘ ነው፡፡ እነዚህም መጽሐፈ ኪዳን
ቀዳማዊና መጽሐፈ ኪዳን ካልዕ ናቸው፡፡ ጌታ በመዋዕለ ሥጋዌው /ከትንሳዔው በፊት/ ያደረገቸው “ወንጌል” ሲባል
ከትንሳዔው በኃላ ያደረጋቸው ሁሉ ደግሞ “ኪዳን” ይባላል፡፡ በሁለት የኪዳን መጻሕፍት ተዘጋጅቶ ቤተክርስቲያን
በጠዋት፣ በሰርክ፣ በሌሊት፣ በሁሉም ሠዓታት ለአገልግሎት እግዚአብሔርን በማመስገን እየተጠቀመችበት
ትገኛለች፡፡
ሐ. በአጠቃላይ አገልጋዮች፡- አበው ነብያትን፣ ሐዋርያትንና አርድዕትን ወዘተ… የሚመለከት ክፍል ነው፡፡
በተለይም ከቅዱስ ጴጥሮስ ሥርዓትን የተማረው ቅዱስ ቀለሜንጦስ ስለ ራሱ፣ ስለ ምዕመናን በሥርዓት መሄድ
እንዲገባ በስፋት ይተነትናል፡፡ መጽሐፉ በቅዱስ ጴጥሮስ ደቀ መዝሙር ስም በመሰየሙ መጻሕፍትን ሰፍረው
ቆጥረው ሲሰጡት ስምንት የሥርዓት መጻሕፍትንም ጨምረው እንደሰጡት ይነገራል፡፡ ውድ ተማሪዎች ከዚህ
ቀጥለን መጻሕፍቱን አንድ በአንድ እንመለከታለን፡፡ ተከተሉን፡-
መጻሕፈተ ኪዳን
ይህ መጽሐፍ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ ለቅዱሳን ሐዋርያት
ያስተማራቸውን ትምህርቶች የያዘ ባለ ሁለት ክፍል መጽሐፍ ነው፡፡ ኪዳን መባሉም ጌታ በዚህ ትምህርቱ
ከክርስቲያኖች ሁሉ ጋር ቃል /ኪዳን/ የተገባባ ስለሆነ ነው፡፡ “ዘዐቀበ ቃል ዝንቱ ኪዳን ይሄሉ ወየሐዩ ከመ
መላእክት /የዚህን ኪዳን ቃል የተጠበቀ እንደ መላዕክት ህያው ሆኖ ይኖራል/” እንዲል መጽሐፈ ኪዳን ፡፡ ይህ
መጽሐፍ መጽሐፈ ኪዳን ቀዳማዊ እና መጽሐፈ ኪዳን ካልዕ በመባል ይታወቃል፡፡ “ክልዔቱ ገበዋቲሃ ለመጽሐፍ”
እንዲል፡፡
መጻሕፈተ ሲኖዶስ
ሲኖዶስ ማለት ጉባኤ/ስብሰባ/ ማለት ሲሆን ቅዱሣን ሐዋርያት እነዚህን መጻሕፍት የጻፉት ለተለያዩ
የቤተክርስቲያን ጉዳዮች በተሰበሰቡ ጊዜ የወሰኗቸውን ውሳኔዎችን ለማሣወቅ ነው፡፡ በተለይ በ5ዐ ዓ.ም በኢየሩሳሌም
ከተማ በቅዱስ ያዕቆብ ሊቀመንበርነት ቅዱሣን ሐዋርያት /ቅዱስ ጳውሎስን ጨምሮ/ ባደረጉት ጉባዔ የተወሰኑ
ውሣኔዎችና የተሰሩ ሥርዓቶች ይገኙባቸዋል፡፡
3 ሥርዓተ ጽዮን
ፅዮን ማለት አንባ መጠጊያ ማለት ስለሆነ ለቤተክርስቲያን ሥርዓት በማርቆስ እናት በማርያም ጽርሐ
ፅዮን በተባለው ቤት በመጻፉ ምክንያት የተሰጠው ስያሜ ነው፡፡ መጽሐፉ ስለ ሥርዓተ ክህነት አገልግሎትና
ምግባር፣ ስለ በዓላትና አፅዋማት፣ ስለ ቅዱሳን ክብር በስፋት ይተነትናል፡፡
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 67
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
4 መጽሐፈ ትዕዛዝ
ትዕዛዝ ማለት በቁሙ ከስራ አስቀድሞ የሚሰጥና የሚነገር ህግ ወይም ሥርዓት እንዲሁም አድርግ
አታድርግ የሚል ፍቃድ ማለት ነው፡፡ መጽሐፉን ቅዱሳን ሐዋርያት በ1ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በኢየሩሳሌም
ጽፈውታል፡፡ ይኸውም ቅዱሳን ሐዋርያት በቀሌምንጦስ እጅ ለአህዛብ ህገ ቤተክርስቲያንን ለማሳወቅ እንደጻፉት
ይነገራል፡፡ በአጠቃላይ መጽሐፉ ስለ ሢመተ መላእክት፣ ስለ አስራት፣ መባዕ፣ ሥርዓተ ቁርባን በስፋት ያትታል፡፡
5 መጽሐፈ ግጽው
ግጽው ማለት የታየ፣የተገለፀ፣ ጉልህ ማለት ነው፡፡ ይኸውም ስለ ሢመተ ክህነትና ስለ ህዝባውያን ተልዕኮ፣
ስለ ትህትና፣ ስለ 10ቱ ቃላት፣ ስለ አሥራት፣ ስለ ሰንበት፣ ስለ ሙታን ተዝካር፣ ስለ ቁርባንና ስለ ጋብቻ በስፋት
ይገልፃል፡፡
6 መጽሐፈ አብጥሊስ
አብጥሊስ ማለት ሐዋርያውያን ቀኖናት ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ቀለሜንጦስ በአንደኛው መቶ ክፍለ ዘመን
ስለ ቅዱሳን ሐዋርያት የቅዱስ ሲኖዶስን ድንጋጌዎች እንደጻፈ ይነገራል፡፡ መጽሐፉ ከ 81ዱ ቅዱሳት መጻሕፍት
በዝርዝር ይገልፃል፡፡
7 መጽሐፈ ቀሌምንጦስ
ቀሌምንጦስ ትውልዱ ሮማዊ የሆነ የቅዱስ ጴጥሮስ ደቀ መዝሙርና የሮሜ የመጀመሪያው ሊቀጳጳስ
ነበር፡፡ ቅዱስ ቀሌምንጦስ ስሙ በሕይወት መጽሐፍ እንደተጻፈ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ተገልጧል፡፡254 ቅዱሣት
መጻሕፍት ቁጥራቸው 81 እንደሆነ ከቅዱሣን ሐዋርያት ተረድቶ የቅዱሣን መጻሕፍትን ዝርዝር ጽፎ ያዘጋጀ
አባት እንደሆነ የቤተክርስቲያን ሊቃውንት በመጽሐፍቶቻቸው ያትታሉ፡፡ ይህ መጽሐፍ ከ81 ቅዱሣን መጻሕፍት
የሚቆጠር ሲሆን የመጽሐፉን ምስጢር ከጌታ እየተነገረ የተረዳው ቅዱስ ጴጥሮስ ነው፡፡ ቀሌምንጦስም ቅዱስ
ጴጥሮስ እየነገረው ይህንን መጽሐፍ በመጻፍ በጸሐፊው ስም መጽሐፈ ቀሌምንጦስ ተብሏል፡፡ መጽሐፉ በውስጡ፡-
ከሥነ ፍጥረት ታሪክ አንስቶ እስከ ይሁዳ ንጉሥ እስከ ኢዮአታም ዘመን ያለውን ታሪክ
ቅዱስ ጴጥሮስ ለቀሌምንጦስ የነገረውን ብዙ መንፈሳውያን ምሥጢራት
ሰለ ሰው ልጅ የተደረገው ምህረት ሰዎች በምድር ላይ ሲኖሩ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ጌታ
ለቅዱስ ጴጥሮስ የሰጠውን ትምህርት
ጌታ ለቅዱስ ጴጥሮስ ያስተማረውን ሥርዓተ ቤተክርስቲያን
ስለ ሙሴ በትር ታሪክና ስለ ስምዖን ካርዮ ራዕይ ወዘተ… የገለጡ ብዙ ታሪኮች ያሉበት ሰፊ
መጽሐፍ ሲሆን በሰባት ክፍሎች የተከፈለ ነው፡፡
6 መጽሐፈ ዲድስቅልያ
ዲድስቅልያ ማለት ትምህርት ማለት ሲሆን ሐዋርያት ያስተማሩትና የሰሩት የቤተክርስቲያን ሥርዓት
የተጻፈበት መጽሐፍ ነው የተጻፈውም ከ12ዐ ዓ.ም በፊት ነው፡፡ በ43 ምዕራፎች የተከፋፈለ መጽሐፍ ሲሆን
በይዘቱም
ከምዕራፍ 1-7 ስለ ህይወትና ስለ ሞት
ከምዕራፍ 7-15 ሰለ ጾም ጸሎት ስለ ቅዱስ ቁርባን ሥርዓት ስለ ነቢያትና ሐዋርያት ትምህርት
ተዛምዶ
ሰለ ጥምቀት ሥርዓትና ጥምቀትን ሲያጠምቁ በስመ ስላሴ መሆን እንዳለበት
ስለ ጸሎት ሥርዓት /ቢያንስ በቀን 3 ጊዜ አቡነ ዘበሰማያት መጸለይ እንደሚገባ/
ጾመ ድህነት /የረቡዕና የዓርብ ጾም/ እንዲሆን የተወሰነ ውሣኔ
ጥምቀት የፈጸሙ ሴቶች ቅዱስ ቁርባን መቀበል እንዳለባቸው ወዘተ... የመሳሰሉት የቤተክርስቲያን
ሥርዓቶችና ትምህርቶች የያዘ መጽሐፍ ነው፡፡
በአጠቃላይ ከላይ የተመለከትናቸው ስምንት የአዲስ ኪዳን የቀኖና መጻሕፍት በይዘታቸው መመሪያ ሰጪና
ሥርዓትና መሪ /አስተማሪ/ ስለሆኑ ከትምህርት ክፍል መጻሕፍት ጋር ይቆጠራሉ፡፡
254
ፊሊ 4፡3
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 68
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ምዕራፍ አራት
አዋልድ መጻሕፍት
41 የቃሉ ትርጉም ፡- አዋልድ መጻሕፍት ማለት የመጻሕፍት ልጆች ማለት ሲሆን ልጅነታቸውም
ለአስራው መጻሕፍት ነው፡፡ እነዚህ መጻሕፍት በቅርፃቸውም ሆነ በይዘታቸው ከአስራው መጻሕፍት ጋር
የሚመሳሰሉ በቤተክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖትን፣ ሥርዓትን፣ እምነትና ክርስቲያናዊ ትውፊትን መሰረታውያን
የሆኑትን ንባብ እንጂ ትርጓሜ ጥሬ ቃል እንጂ ትንታኔ የሌላቸው ቀጥራቸው ሰማንያ አንድ የሆኑትን መጻሕፍትን
(አስራው መጻሕፍትን) የሚተነትኑ፣ የሚተረጉሙ፣ ምስጢሩን የሚያራቅቁ255 ትርጓሜውንም የአቃንተው
የሚያቀርቡ መጻሕፍት ናቸው፡፡ ይህም ማለት በቤተክርስቲያናችን ሊቃውንት አተናተን መሰረት አስራው መጻሕፍት
ብሉያት ቅዱሳት መጻሕፍት256 ንባብ አዲሳት ቅዱሳት መጻሕፍት257 አዋልድ መጻሕፍት258 ደግሞ ትርጓሜ ናቸው፡፡
255
ይህም ማለት መጽሐፍ ቅዱስ በምስጢራዊ ትርጉም ስለሚተረጎም ያንን ትርጉም የሚተረጉሙ መጻሕፍት ናቸው፡፡
256
የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት
257
የአዲስ ኪዳን መጻህፍት
258
በሌላ ስያሜያቸው መጻሕፍተ ሊቃውንት ይባላሉ፡፡
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 69
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 70
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ነጂነት ከጻፉ በኋላ ለቤተክርስቲያን አውርሰዋል፡፡ በመሆኑም እነዚህ መጻሕፈት የቤተክርስቲያን በመሆናቸው
ለትርጉማቸውና ለምስጢራቸው ጭምር መጠየቅ ያለባት ቅድስት ቤተክርስቲያን ናት፡፡
259
ይህ ቅዱስ አባት ኢትዮጵያን በንግስና አስተዳድሯል፡፡
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 71
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 72
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
38. መልክአ ኢየሱስ ቅ/ ዓምደ ሐዋርያት መነኮስ/ ኢትዮጵያ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ
ክርስቶስን የማዳን ስራና ምስጋና
የሚናገር የመልክዕ ድርሰት
39. መልክአ ሥላሴ ቅዱስ ስብሐት ለአብ መነኮስ/ ኢትዮጵያ የቅድስት ሥላሴን ምስጋና የሚናገር
የመልክዕ ድርሰት
40. ባሕረ ሀሳብ ቅዱስ ድሜጥሮስ ፓትርያርክ/ ግብጽ የበዓላትና የአጽዋማት ዘመን መቁጠሪያ
መጽሐፍ
41. ራዕየ ፊቅጦር ቅዱስ ፊቅጦር መነኮስ/ ግብጽ ትንቢታዊ መጽሐፍ
42. ረድዕ እንጦስ ቅዱስ ጊዮርጊስ መነኮስ/ ግብጽ ስለ ነገረ ሃይማኖትና ስለ መነኮሳት
ተልሙድ ህይወት የሚያትት
43. ፈውስ መንፈሳዊ ቅዱስ ሚካኤል ኤጲስ ቆጶስ/ ስለ ንስሐ፣ ኃጢአት፣ ነገረ ሃይማኖትና
ኢትዮጵያ ሥርዓተ ቤተክርስቲያን የሚያትት
44. ውዳሴ አምላክ ቅ/ ባስልዮስ ዘቂሳርያ ፓትርያርክ/ ቂሳርያ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ
ክርስቶስ ምስጋና
45. መጽሐፈ አክሲማሮስ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ ኤጲስ ቆጶስ/ የሥነ ፍጥረትን ጥንተ ታሪክ የሚያትት
ቆጵሮስ
46. ምስጢረ ሰማይ ቅ/ አባ ኃይለ ሚካኤል መነኮስ/ ኢትዮጵያ ስለ ፈጣሪ ሥነ ፍጥረትና ራዕይ የሚናገር
ወምድር መጽሐፍ
47. ሥርዓተ ቤክርስቲያን ቅ/ ዮሐንስ አፈወርቅ ፓትርያሪክ/ ሶሪያ ስለቤተክርስቲያን ሥርዓት የሚያትት
መጽሐፍ
48. አዕማደ ምስጢር ቅ/ ዮሐንስ አፈወርቅ ፓትርያርክ/ ሶርያ ስለ አምስቱ አዕማደ ምስጢራት
የሚያትት መጽሐፍ
49. የቅዱስ ዮሐንስ ቅ/ ዮሐንስ አፈወርቅ ፓትርያርክ/ ሶርያ የነገረ ሃይማኖትና የሥነ ምግባር
ድርሳንና ተግሳጽ መጽሐፍ
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 73
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
እንችላለን፡፡ እርሱም ቅዱስ ፊሊጶስ ወደ እርሱ ቀርቦ የሚያነበውን ነገር ምን ያህል እንደሚያስተውል በጠየቀው
ጊዜ የመለሰው መልስ ይህንኑ የሚያስዳ ነው፡፡
“የሚመራኝ ሳይኖር ይህ እንዴት ይቻለኛል” ሐዋ 8፡31
እናም እኛም መጽሐፍ ቅዱስን በምናነብበት ወቅት የመጽሐፍ ቅዱሱን ሃሳብ በአግባቡ እንድንረዳ
የሚያደርጉንን የቤተክርስቲያን አዋልድ መጻሕፍትን ልናነብ በእነርሱ ልንመራና ልንታገዝ ይገባል፡፡ ያለዚያ
መጻሕፍትን ያለእነርሱ አጋዥነት የማናነብ ከሆነ መጻሕፍትን በራሳችን መንገድ ባሻን አተረጓጎም እንተረጉማለን
ማለት ነው፡፡ ይህ ደግሞ የተከለከለ ነው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ማንም መጻሕፍትን በራሱ መንገድ ሊተረጉም እንደማገባ
አስተምሮናል፡፡260 እናም መጽሐፍ ቅዱስን በእነዚህ መጻሕፍት አጋዥነት ልናነብ ያስፈልጋል፡፡ በቤተክርስቲያናችን
የተለያዩ የአንድምታ መጻሕፍት ይገኛሉ ለአብነትም፡- ትርጓሜ ወንጌል፣ የቅዱስ ጳውሎስ መልዕክታት ንባቡና
ትርጓሜው፣ የትንቢተ ኢሳይያስ አንድምታ፣ ሰለስቱ ሐዲሳት ንባቡና ትርጓሜው፣ የመዝሙረ ዳዊት ንባቡና
ትርጓሜው፣ወዘተ.... መጥቀስ ይቻላል፡፡
ለ. ስንክሳር
ስንክሳር ማለት ስብስብ ማለት ሲሆን ከቃሉ እንደምንረዳው በይዘቱ የሥላሴን አንድነትና ሶስትነት፣
የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሰው መሆን ከመግለጡም በተጨማሪ የቅዱሳን መላዕክትን፣ የቅዱሳን
ነብያትን፣ የቅዱሳን ሐዋርያትን፣ የቅዱሳን ጻድቃንና የቅዱሳን ሠማዕታትን፣ወዘተ.... ተጋድሎ፣ ተኣምራት፣
ትሩፋትና መታሰቢያ በየዕለታቱ የሚዘክር የታሪክ ይዘት ያለው መጽሐፍ ነው፡፡ ይህ መጽሐፍ የተለያዩ ምንጮችን
መሰረት በማድረግ የተጻፈ ሲሆን በተለይም የብሉያትንና የሐዲሳት መጻሕፍትን መሰረት በማድረግ የተጻፈ
መጽሐፍ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ይህ መጽሐፍ የተለያዩ ቅዱሳን አባቶች በመንፈስ ቅዱስ በመመራት የጻፏቸው
መጻሕፍት ስብስብ ሲሆን አጻጻፉም በየዕለቱ እንዲነበብ ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡ ይህንን መጽሐፍ በመንፈስ ቅዱስ
ነጂነት ያዘጋጁት የአትሪብ ኤጲስ ቆጶስ አባ ሚካኤል፣ የብሩልስ ኤጲስ ቆጶስ አባ ዮሐንስና ሌሎች ቅዱሳን አባቶች
ናቸው፡፡ ይህ መጽሐፍ በዋናነት የቅዱሳንን ተጋድሎና ተኣምራት እንደመያዙ ምዕመናን ቅዱሳንን በመዘከር
የሚገኘውን ጸጋ261 ተካፋይ እንዲሆኑ የሚረዳ መጽሐፍ ከመሆኑም በተጨማሪ የእምነት ዋኖቻችንን በማሰብ
እነርሱ በሄዱበት ፍኖት እንድንጓዝ የሚረዳ መጽሐፍ ነው፡፡262
ሐ. የጸሎት መጻሕፍት
ለጸሎት የምንጠቀምባቸው መጻሕፍት ቅዱሳን አባቶች መጽሐፈ ቅዱስን መሠረት በማድረግ በመንፈስ ቅዱስ
መሪነት የጻፏቸው መጻሕፍት ናቸው፡፡ እነዚህ መጻሕፍት ቅዱሳኑ በተለያየ ጊዜ የጸለዮአቸው ጸሎቶች ሲሆኑ
እኛም በእነርሱ አንደበት የተመሰገነ እግዚአብሔርን ለማመስገን ለጸሎት የምንጠቀምባቸው ናቸው፡፡ በዋናነት
መጻሕፍቱ ለማኀበር የሚያገለግሉ፣ ለዘወትርና በተሠወኑ ዕለታት የምንጠቀምባቸው፣ ለካህናትና ለምዕመናን
ተብለው የተለዩ በንባብና በዜማ የሚደርሱ የምስጢር መፈጸሚያ እየልን ከፋፍለን ማየት እንችላለን፡፡
ለግል ጸሎት የሚያገለግሉ የምንላቸው መጻሕፍት በየጊዜውና በየሰዓቱ ለግል ጸሎት የምንጠቀምባቸው
መጻሕፍት ሲሆኑ ለአብነትም ውዳሴ ማርያም፣ ውዳሴ አምላክ፣ መዝሙረ ዳዊት፣ ወዘተ... ይጠቀሳሉ፡፡
ለማህበር ጸሎት የሚያገለግሉ እነዚህ ምዕመናን በቤተክርስቲያን እንዲሁም በተለያዩ ቦታዎች
የሚጠቀሙባቸው ናቸው፡፡ ለምሣሌም መጽሐፈ ቅዳሴ (የ14ቱ ቅዳሴያት መጽሐፍ) ተጠቃሽ ነው፡፡
ለዘወትር ጸሎት የሚየገለግሉ የምንላቸው ምዕመናን በዘወትር የጸሎት ሕይወታቸን ውስጥ በየዕለቱ
የሚጠቀሙባቸው ሲሆኑ ለአብነትም የዘወትር ጸሎት፣ ውዳሴ ማርያም፣ ውዳሴ አምላክ ወዘተ…
ይጠቀሳሉ
260
2ኛ ጴጥ 1፡20
261
ማቴ 10፡41-42
262
ዕብ 13፡7
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 74
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
በተወሰኑ ዕለታትና በበዓላት የሚያገለግሉ መጻሕፍት የሚባሉት በንዑሳንና በአበይት በዓላት እንዲሁም
በተለያዩ ወቅቶች የሚያገለግሉ ሲሆኑ ለምሣሌም ግብረ ሕማማት፣ ማህሌተ ጽጌ፣ ፆመ ድጓ፣ ድጓ፣
ወዘተ … ተጠቃሽ ናቸው፡፡
ለካህናትና ለምህመናን የሚያገለግሉ የምባሉት ደግሞ ለካህናት ኪዳን፣ ሊጦን፣ መስተብቁ፣ ዘይነግስ
እንዲሁም ለምዕመናን፡- ውዳሴ እግዚዕ፣ ውዳሴ ማርያም፣ ጸሎተ ሃይማኖት፣ መዝሙረ ዳዊት፣
ድርሳናት፣ ወዘተ... ናቸው፡፡
ለምሥጢር መፈጸሚያ የሚያገለግሉ የሚባሉት ምስጢራተ ቤተክርስቲያን ለመፈጸም የሚያገለግሉ ሲሆኑ
እነዚህም መጽሐፈ ተክሊል፣ መጽሐፈ ቅዳሴ፣ መጽሐፈ ክርስትና፣ መጽሐፈ ቀንዲል፣ መጽሐፈ ግንዘት
ናቸው፡፡
በዜማ የሚደርሱ የምንላቸው መጽሐፈ ቅዳሴ፣ ኪዳን፣ ውዳሴ ማርያም፣ ማህሌተ ጽጌ፣ ጾመድጓ፣ ጽጓ፣
መጽሐፈ ግንዘት፣ ወዘተ….ናቸው
መ. ገድላትና ድርሳናት
ገድል ማለት ትግል፣ ፈተና፣ ውጊያ፣ ሰልፍ፣ ድልና አክሊል እስኪገኝ ድረስ የሚደክሙት ድካም፣
የሚሰሩት ሥራ፣ የሚቀበሉት መከራና ጸጋ እንዲሁም ተጋድሏቸውን የሚናገር መጽሐፍ ነው፡፡ ይህ መጽሐፍ
ቅዱሳን ስለ ክርስቶስ ሲሉ የሚቀበሉትን መከራ፣ ስቃይ፣ ህማም እና የሚያሳዩትን ጽናት፣ ትዕግስት፣ወዘተ....
የሚያትት መጽሐፍ ነው፡፡ ይህም ቅዱሳን ሰማዕታት ስለክርስቶስ እጅ እግራቸውን ለስዕለት፣ አይናቸውን ለፍላት
ሰጥተው የፈጸሙትን መንፈሳዊ ተጋድሎ እና ቅዱሳን ጻድቃን የመዓልት ሐሩሩን የሌሊት ብርዱን ታግሰው፣ ዳዋ
ጥሰው፣ ድንጋይ ተንተርሰው፣ ጤዛ ልሰው፣ ሌጦ ለብሰው፣ የአራዊቱን ግርማ ታግሰው በየዱሩና በየጢሻው እየኖሩ
ስለክርስቶስ ሲሉ መከራውን ሁሉ በመታገስ በጾም በጸሎት በመጽናት የፈጸሙትን ተጋድሎ የሚዘክር መጽሐፍ
ነው፡፡ በአጠቃላይ ገድል ማለት ቅዱሳን ጻድቃንና ቅዱሳን ሠማዕታት በሕይወት ዘመናቸው የሰሩትን ታላቅ ስራ
የሚገልጥ መጽሐፍ ነው፡፡263 በውስጡም የቅዱሳኑን ተጋድሎ ከማተቱም በተጨማሪ እግዚአብሔር ለቅዱሳኑ
የገባውን ቃል ኪዳንና ክብራቸውን የሚያትት መጽሐፍ ነው፡፡264 በተዘዋዋሪ ገድላት የቅዱሳንን ተጋድሎ ብቻ
ሳይሆን እግዚአብሔር እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ሕይወት ውስጥ የሰራውን ታላቅ ሥራ የሚዘክርና የሚያትት
መጽሐፍ ነው፡፡
“ስለ ቅዱሳን መናገር ማለት በእነርሱ ላይ ጸጋውን ስላሳደረው ስለ እግዚአብሔር መናገር
ማለት ነው፡፡” ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናንዙ
ሠ. ተኣምራት
እነዚህ መጻሕፍት በዋናነት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጽሐፍ ቅዱስ ተጽፈው
የማናገኛቸውን ድንቅ ድንቅ ገቢረ ተኣምራት265፣ ጌታችንም ለቅዱሳኑ ይህች ተኣምር ትከተላቸዋለች ሲል በሰጠው
263
አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፈ ሰዋሰው ወግስ ገጽ 301
264
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥም የተለያዩ ቅዱሳን ተጋድሎዎች ተመዝግበው ይገኛሉ ለአብነትም በብሉይ ኪዳን የአብርሃም፣ የይስሐቅ፣ የያዕቆብ፣ የዳዊት፣ የነብዩ
ኤልያስ በአዲስ ኪዳን ደግሞ የቅዱሳን ሐዋርያት ተጋድሎዎች ተመዝግበው ይገኛል፡፡
265
በዮሐ 20፡30 ላይ “ኢየሱስም በዚህ መጽሐፍ ያልተጻፈ ሌላ ብዙ ምልክት በደቀ መዛሙርቱ ፊት አደረገ ተብሎ እንደተገለጸ ጌታችን በመዋዕለ ስጋዌው
ያደረጋቸው ድንቅ ተኣምራት ሁሉ በመጽሐፍ ቅዱስ ተጽፎ አይገኙም፡፡
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 75
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ተስፋ መሰረት ጻድቃን ሰማዕታት በሕይወተ ስጋ ሳሉ ከሞቱም በኋላ ስማቸው ከተጠራበት፣ ደመ ትረሩፋታቸው
በፈሰሰበት፣ ሥጋቸው በተቀበረበት፣ አጽማቸው በተከሰከሰበት፣ መታሰቢያቸው በሚደረግበት ሁሉ ሀይማኖታቸውን
ለመግለጥና ድንቅ ድንቅ ተኣምራት መስራታቸውን የሚያትት መጽሐፍ ነው፡፡
በብሉይ ኪዳንና በአዲስ ኪዳን የተገለጡ መሰረታዊ የሃይማኖት እና የሥነ ምግባር ትምህርቶችን ጠንቅቆ
ማወቅ
የእግዚአብሔርን ከሃሊነትና ቸርነት ያለምንም ጥርጥር ማመን
ለቅዱሳን የተሰጠውን ክብርና ሥልጣን መረዳት
ከሥጋዊ ፍልስፍና ጋር ቀላቅሎ ለመረዳት አለመሞከር
መጽሐፉ የተጻፈበትን ዘመን የነበሩትን ሁኔታዎች በማገናዘብ ማንበብ
ከእምነት፣ ከዕውቀት፣ ከሕሊና በላይ የሆኑ ሥራዎች በእግዚአብሔር ረዳትነትና አከናዋኝነት እንደሚሰሩ
ማመን ወዘተ... ይጠቀሳሉ፡፡
ማጠቃለያ
መጽሐፍ ቅዱስ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ገላጭነት ወይም መሪነት የተጻፈ መጽሐፍ ነው፡፡ ይህ
መጽሐፍ በአስገኚው ቅድስና፣ በጸሐፊዎቹ ቅድስና እንዲሁም አንባቢያኑም እርሱን በማንበባቸው፣ በመስማታቸው
እንዲሁም በመከተላቸው ወደ ቅደስና ስለሚመራቸው ቅዱስ መጽሐፍ ይባላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ መጽሐፍ ቅዱስ
ከመጽሐፍት ሁሉ ቀደምት፣ የሚያነቡትንና የሚሰሙትን የሚያንጽ እንዲሁም ስላለፈውና ወደፊት ስለሚመጣው
ነገር በእርግጠኝነት የሚናገር መጽሐፍ ነው፡፡ እናም ሰዎች አምላካቸው እግዚአብሔር ያስተላለፈላቸውን መልዕክት
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያገኙታል፡፡ ስለዚህ ይህንን መጽሐፍ ማንበብ ተገቢ ነው፡፡ በምናነብበትም ወቅት
እንደሌሎች ተራ መጻሕፍት ሳይሆን የራሱ የሆኑትን የአነባበብ ዘዴዎች በመጠቀም ማንበብ ከዚያም አልፎ
መመርመር ይገባል፡፡ ምክንያቱም ይህንን ድንቅና ጥልቅ መጽሐፍ ያለበቂ እውቀትና ያለ ፈሪሃ እግዚአብሔር
ብዙዎች በድፍረት በተሳሳተ አተረጓጎም እና አገላለጽ ስለተረጎሙት ነው፡፡ ስለዚህ እኛ ራሳችንን ከነዚህ የስህተት
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 76
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ትርጉሞች ለመጠበቅ የመጽሐፍ ቅዱስን የአተረጓጎም ዘዴዎች ማወቅ ይህም ማለት የመጽሐፍ ቅዱስን የአጻጻፍ
ባሕል ጠንቅቆ መረዳት ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በመንፈስ ቅዱስ ገላጭነት ቅዱሳን ሐዋርያትና ከእነርሱ
በኋላ የተነሱ ቅዱሳን አባቶች የጻፉልንን የአንድምታ መጻሕፍት ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር በማጣመር ልናጠና
ያስፈልጋል፡፡ ይህን የምናደርግ ከሆነ መናፍቃን ከሚያነሷቸው ትኛውም አይነት የምንፍቅና መርዞች ራሳችንን
ከዚያም አልፎ ተርፎ ሌሎች እህትና ወንድሞቻችንን መጠበቅ እንችላለን፡፡ በአጠቃላይ መጽሐፍ ቅዱስን ዘወትር
በምናነብበት ወቅት ወደ ስህተት እንዳናመራ ተገቢውን ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል፡፡ የመጽሐፍ ቅዱስን ምስጢር
ለመረዳትና ለማወቅ ከዚያም አልፎ ለጸሎት፣ የቅዱሳንን ትሩፋት ለመዘከርና ከእነርሱ ጸጋ ተካፋይ ለመሆን፣
ለትምህርትና ለተግሳጽ፣ ወዘተ.... ወዘተ የሚረዱ የአስራው ቅዱሳት መጻሕፍት ልጆች የሆኑ አዋልድ መጻሕፍት
አሉ እነዚህ መጻሕፍፍ ቅዱሳን ሊቃውንት በመንፈስ ቅዱስ ነጂነት የጻፏቸው ሲሆኑ በይዘታቸውና በቅድስናቸው
ከአስራው መጻሕፍት ጋር ፍጹም ተመሳሳይ በመሆናቸው ከአስራው መጻሕፍት ልጆች መሆናቸው ይረጋገጣል፡፡
ከአዋልድ መጻሕፍት ለአብነትም አንድምታዎች፣ የጸሎት መጻሕፍት እና ሌሎችም ተጠቃሽ ናቸው፡፡
የግዕዝ ቁጥሮች
1.. ......... አንድ ፳........... ሀያ
2 ........ ሁለት #........... ሰላሳ
3 .......... ሶስት $.......... አርባ
4 .......... አራት %.......... ሃምሳ
5.......... አምስት 8......... ስልሳ
6..............ስድስት &.../ ........ ሰባ
7............ ሰባት . ...... ሰማንያ
*
8........... ስምንት (........... ዘጠና
9........... ዘጠኝ ).......... መቶ
፲........... አስር
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 77
ለበጋ ኮርሠኞች የተዘጋጀ
[ኦርቶዶክሳዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የማስተማሪያ ኖት
ዋቢ መጻሕፍት
መጽሐፍ ቅዱስ/ በኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማህበር
የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት/ በኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማህበር
የትንቢተ ኢሳይያስ አንድምታ ትርጓሜ
የትንቢተ ሚክያስ አንድምታ ትርጓሜ
መጽሐፈ ሰዋሰው ወግ/ በአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ
መሠረታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ አጠናን ዘዴ/ በመምህር ቸርነት አበበ
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት/ በአባይነህ ካሴ
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት /የደብረ /ፍ/መ/ሰ/ቅቂ/ቤ/ያን/ዉ/ብ/ሠ/ት/ቤት የርቀት መማሪያ መጽሐፍ/
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት/ የማህበረ ቅዱሳን ጊቢ ጉባኤያት ማስተማሪያ መጽሐ
ጉዞ ወደ እግዚአብሔር/ በብጹዕ ወቅዱስ አቡነሺኖዳ
የክፍሉ የበፊት የማስተማሪያ ኖቶች እና የተለያዩ ማስታወሻዎች
በደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ዉሉደ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ተከታታይ ትምህርት ክፍል| 78