Professional Documents
Culture Documents
Meserete Haymanot Grade 4
Meserete Haymanot Grade 4
መሠረተ ሃይማኖት
ነገረ ማርያም
አራተኛ ክፍል
ያግኙን
Email
office@eotc-gssu.org
YouTube
https://www.youtube.com/channel/UCZl-
WxxCvV2UzcSz1Qxh6UAg
Facebook
http://facebook.com/EOTC.GSSU
Telegram
https://t.me/EOTCNSSU
Website
https://eotc-gssu.org/a/
Twitter
https://twitter.com/tibeb_felege
Copyright ©
2015 E.C
ምዕራፍ አንድ
ነገረ ማርያም
ዓላማ
ተማሪዎች ይህንን ምዕራፍ ሲያጠናቅቁ
የማስጀመሪያ ጥያቄዎች
፩
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
፪
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
ማስታወሻ
አልዓዛር ከቅሥራ ሌላ ማታንን ወለደ፤ ማታንም ያዕቆብን
ወለደ፤ያዕቆብም ክርስቶስ ኢየሱስን የወለደች የማርያምን ጠባቂ
ዘመዷን ዮሴፍን ወልዷል።
፭
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
፰
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
፱
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
የመልመጃ ጥያቄዎች
ትክክል የሆነውን እውነት ትክክል ያልሆነውን ደግሞ ሐሰት
በማለት መልሱ።
፲፩
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
፲፫
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
የእመቤታችን ትንሣኤ
ነቢዩ “አቤቱ፥ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፥ አንተና የመቅደስህ ታቦት”መዝ
፻፪፩፥፰ በማለት በተነበየውም መሠረት እውነተኛዋ ታቦት የአምላክ
ማደሪያ ማህደረ መለኮት እመቤታችን ተነሥታለች።
የእመቤታችን ዕርገት
እመቤታችን ነሐሴ አሥራ ስድስት በተቀበረች በሦስተኛው ቀን ማለት
ነው ተነሥታ ዐርጋለች። (እዚህ ጋር እመቤታችን በእሁድ ዕለት በ14ት
ነው የተነሣችው ያረገችው የሚሉ መምህራንም አሉ። ምክንያታቸውም
ትንሣኤ ሙታን እሑድ ቀን ስለሚሆን፣ በእሑድ መነሳቷ ነው የልጇ
ትንሣኤ ጋር የሚያመሳስለው እና የ፲፮ቱ የማክሰኞው ሐዋርያት ሁለተኛ
ሱባዔ ከገቡ በኋላ ትንሣኤዋ የተገለጠበት ቀን ነው ይላሉ) ያም ሆነ ይህ
ግን ዕርገቷን በመጀመሪያ ያየው ቅዱስ ቶማስ ሲሆን እርሱም በደመና
ተጭኖ ከሕንድ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለስ መልአክ ሲያሳርጓት አይቷል
እርሷም ባርካው የመግነዟን ሰበን ሰጥታዋለች። ሌሎቹ ሐዋርያት ግን
ትንሣኤዋን አላዩም ነበርና የእመቤታችንን ነገር እንዴት ሆነች በማለት
ቅዱስ ቶማስ አውቆ ሲጠይቅ እርሷማ በጥር ሞታ በነሐሴ ቀበርናት
በማለት ስለመለሱለት። ይህማ አይሆንም ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር
ስላላቸው። ቅዱስ ጴጥሮስ አንተ ድሮም ተጠራጥረህ ሰው ታጠራጥራለህ
ብሎ ቆፍሮ ሊያሳየው ቢሄዱ አካሏን አጡት። ቅዱስ ቶማስም የያዘውን
ይዞ ነበርና የጠየቃቸው፤ ማረጓንበሰበኗ አሳያቸው። እነሱም ተካፈሉት
ተአምራትም አደረጉበት (ዛሬ ካህናት መስቀል ሲይዙ ዲያቆናትም የመጾር
፲፬
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
መስቀሉን ይዘው አብሮ የሚታየው ጨርቅ የዚህ ምሳሌ ነው)። ኋላም
ቶማስ ያየውን ማየት አለብን ብለው ሱባዔ በቀጣዩ ዓመት ገቡ ጌታም
እመቤታችንም ተገለጡላቸው። እርሷም ባረከቻቸው። ይህን ትንሣኤዋን
ዳግምም መገለጧን ቤተክርስቲያናችን እንደ ልጇ ትንሣኤ አክብሩት
በማለት ታውጃለች። ከነሐሴ ፲፮-፳፩ም ይከብራል። በመሆኑም ነሐሴ
አሥራ ስድስት ቀን በየዓመቱ የትንሣኤዋ መታሰቢያ ሆኖ ይዘከራል።
ሐዋርያት የጾሙትን ጾምም ጾመ ፍልሰታ ለማርያም በማለት እነሱን
አብነት አድርገን እንጾመዋለን።
ነቢዩ “በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች”
መዝ ፫፬፥፱ ብሎ በተነበየው መሠረት አሁን እመቤታችን በሰማይ ስለኛ
ለልጇ በተቀበለችው ቃል ኪዳን እያሳሰበችል አለች።
-“በሰማይም ያለው የእግዚአብሔር መቅደስ ተከፈተ፥ የኪዳኑም ታቦት
በመቅደሱ ታየ” ራእይ ፲፩፥፲፱
- “ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ
በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት
አንዲት ሴት ነበረች” ራእይ ፲፪-፩
፲፭
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
የመልመጃ ጥያቄዎች
ትክክል የሆነውን እውነት ትክክል ያልሆነውን ደግሞ ሐሰት
በማለት መልሱ።
፲፮
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
ምዕራፍ ሁለት
የእመቤታችን ክብር እና ቅድስና
ዓላማ
ተማሪዎች ይህንን ምዕራፍ ሲያጠናቅቁ
ሀ) የእመቤታችን ጽንዕትነት
እመቤታችን ጽንዕት በድንግልና የጸናች ናት። ሌሎች ሴቶች ቢጸኑ እስከ
ጊዜው ነው፤ ኋላ ተፈትሖ (ድንግልናን ማጣት) አለባቸው። እመቤታችን
ግን ከመፅነሷ በፊት፣ በፀነሰች ጊዜ፣ ከፀነሰች በኋላ፤ ከመውለዷ በፊት፣
በወለደች ጊዜ፣ ከወለደች በኋላ ጽንዕት ነችና በድንግልና የጸናች ናትና
ቅድስት እንላታለን። የጸናች ናትና ቅድስናዋን እንመሰክራለን።
ለ) የእመቤታችን ንጽሕትነት
እመቤታችን ምንም ምን ኃጢአት ያልነካት፣ ነውር የሌለባት ንጽሕት
ናት። ሴቶች ቢነጹ፣ ሰዎች ቢነጹ፣ መላእክት እንኳን ቢነጹ ከነቢብ
፳፪
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
(ኃጢአትን ከመናገር)፣ ከገቢር (ኃጢአትን ከማድረግ) ነው እንጂ ከኀልዮ
(ኃጢአትን ከማሰብ) አይነጹም (ከመላእክት ዲያብሎስ እንኳን ሐሰትን
አስቦ፤ አስቦም ሳይቀር ፈጽሟልና)። እመቤታችን ግን ከነቢብ ከቃል
ከአንደበት፣ ከገቢር ከድርጊት፣ ከኀልዮ ከሐሳብ ኃጢአትና ነውር ሁሉ
ንጽሕት ናት። ስለዚህም ቅድስት እንላታለን።
ሐ) የእመቤታችን ልዩነት
እመቤታችን ልዩ ናት ከማንም ከማን አትመሳሰልም። ሴቶች እናት ቢሆኑ
ድንግል መሆን አይችሉም፤ ድንግል ቢሆኑ እናት መሆን አይችሉም።
እመቤታችን ግን እናትነትን ከድንግልና፣ ድንግልናን ከእናትነት ጋር
አስተባብራ (በአንድነት) ይዛ የተገኘች እርሷ ብቻ ስለሆነች፤ ከእርሷ
በቀር ስላልነበረ፣ ስለሌለ እና ስለማይኖር ልዩ እንላታለን። በዚህም ነቢዩ
እንዳለው ምልክታችን ሆናለች።
መ) የእመቤታችን ተመሥጋኝነት
እመቤታችን ከለይ በጠቀስናቸው ማንነቶቿ ሁሉ ትመሠገናለች።
ስለዚህም እራሷ እንዲህ በማለት መስክራለች።
“እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፤ ብርቱ የሆነ እርሱ
በእኔ ታላቅ ሥራ አድርጎአልና፤ ስሙም ቅዱስ ነው።”ሉቃ.፩፥፵፰-፵፱
ካመሰገኗት መካከልም
፩. የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ሌሎቹን ሊቃነ መላእክት፣ መላእክት
እና ሠራዊተ መላእክትን እንደ አለቃነቱ ወክሎ፡
- “በስድስተኛውም ወር መልአኩ ገብርኤል ናዝሬት ወደምትባል ወደ
ገሊላ ከተማ፥ከዳዊት ወገን ለሆነው ዮሴፍ ለሚባል ሰው ወደ ታጨች
ወደ አንዲት ድንግል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ፥ የድንግሊቱም ስም
ማርያም ነበረ።መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ፦ ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ
ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ
አላት” ሉቃ ፩፥፳፮-፳፰ ይህ ጸሎት እመቤታችን ሆይ ብለን የምንጸልየው
፳፫
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
መሆኑን ልብ እንበል።
፪.ቅድስት ኤልሳቤጥ ጻድቃንን፣የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሆኑ ሰዎችን
ወክላ
“ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች ጊዜ ፅንሱ በማኅፀንዋ ውስጥ
ዘለለ፤ በኤልሳቤጥም መንፈስ ቅዱስ ሞላባት፥ በታላቅ ድምፅም ጮኻ
እንዲህ አለች፦ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ፥ የማኅፀንሽም ፍሬ
የተባረከ ነው።የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል?
እነሆ፥ የሰላምታሽ ድምጽ በጆሮዬ በመጣ ጊዜ ፅንሱ በማኅፀኔ በደስታ
ዘሎአልና።ከጌታ፤ የተነገረላት ቃል ይፈጸማልና ያመነች ብፅዕት ናት”
ሉቃ ፩፥፵፩-፵፭
ጌታችንም እመቤታችን መመስገን እንዳለባት በወርቃማ ቃሉ ነግሮናል።
- “ይህንም ሲናገር፥ ከሕዝቡ አንዲት ሴት ድምፅዋን ከፍ አድርጋ፦
የተሸከመችህ ማኅፀንና የጠባሃቸው ጡቶች ብፁዓን ናቸው አለችው።
እርሱ ግን፦ አዎን፥ ብፁዓንስ የእግዚአብሔርን ቃል ሰምተው የሚጠብቁት
ናቸው አለ” ሉቃ ፲፩-፳፯-፳፰ ይህም በመልክአ ማርያም ማመስገን
እንዳለብን አስረጅ ነው።
ከዚህ ዓለም ቅዱሳንና ቅዱሳት መካከል እንደ እመቤታችን ያለ በእርሱዋ
መጠን ፀጋን የተመላ በንጽሕናና ቅድስና የተዋበ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ
የሆነና በልዑል ኃይልም የተጠበቀ ሰውነት ያለው የለም። (ሉቃ ፩፥፳፰)
ስለዚህም ቅድስት ብቻ ሳይሆን ቅድስተ ቅዱሳን (ከተለዩ የተለየች፣
ከተመሠገኑ የተመሠገነች፣ ከከበሩ የከበረች፣ ከጸኑ የጸናች)፣ ንጽሕት
ብቻ ሳይሆን ንጽሕተ ንጹሐን በማለት መለየቷ ከሌሎች ፍጡራን ሁሉ
መሆኑን እንመሰክራለን።ስለዚህም ትውልድ የአዳም ዘር፣ የሴም የካም
የያፌት ልጆች ቅዱስ ዳዊት ለልጁ ለሰለሞን እንደመከረው እንዳለው
ሰው የሆኑ (፩ኛ ነገ ፪፥፪-፫) ሁሉ “ቅድስት ብፅዕት” እያሉ ሲያመሰግኗት
ይኖራሉ።
፳፬
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
፪.፫ የእመቤታችን ዘላለማዊ ድንግልና
ዘለዓለም ማለት መቼም መች ማለት ሲሆን ድንግል ማለት ግንኙነት
የማያውቅ የማታውቅ ማለት ነው። የእመቤታችን ዘለዓለማዊ ድንግልና
ስንልም መቼም መች ወንድ እንደማታውቅ የሚያሳይ ነው። ድንግል
የሚለው ቃል በርግጥ ቅድስናዋን ንፅሕናዋን ብቻ ሳይሆን ልዩ መሆንዋንም
ያመለክታል። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ከተለዩ የተለየች
ከከበሩ የከበረች የሚያደርጋት ማኅተመ ድንግልናዋ ሳይለወጥ አምላክን
በድንግልና ጸንሳ በድንግልና መውለዷ ነው። ምክንያቱም ሌሎች ሴቶች
እናትም ድንግልም መሆን አይችሉምና ነው። በዓለም ከነበሩና ከሚኖሩ
ሴቶች እንደ እመቤታችን ድንግልናን ከእናትነት እናትነትን ከድንግልና
አስተባብረው የተገኙሴቶችየሉም አይኖሩምም።
፳፯
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
፰. በሥራ
- “የኢዮሴዴቅም ልጅ ኢያሱ፥ ወንድሞቹም ካህናቱ፥ የሰላትያልም ልጅ
ዘሩባቤል ወንድሞቹም ተነሥተው በእግዚአብሔር ሰው በሙሴ ሕግ
እንደ ተጻፈ የሚቃጠለውን መሥዋዕት ያቀርቡበት ዘንድ የእስራኤልን
አምላክ መሠዊያ ሠሩ” ዕዝ ፫፥፪
፱. በሃይማኖት
- “ወንድሞች ሆይ፥ በሌሎቹ አሕዛብ ደግሞ እንደ ሆነ በእናንተም ፍሬ
አገኝ ዘንድ ብዙ ጊዜ ወደ እናንተ ልመጣ እንዳሰብሁ እስከ አሁን ግን
እንደ ተከለከልሁ ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ።” ሮሜ ፩፥፲፫
፲. ከነዚህ የተለየ የክርስቶስ ወንድምነት ይህም ሰው መሆኑን ያሳያል።
- “ስለዚህ የሕዝብን ኃጢአት ለማስተስረይ፥ ለእግዚአብሔር በሆነው ነገር
ሁሉ የሚምርና የታመነ ሊቀ ካህናት እንዲሆን፥ በነገር ሁሉ ወንድሞቹን
ሊመስል ተገባው።” ዕብ ፪፥፲፯
ስለዚህ ወንድሞቹ እህቶቹ ተብለው የተጠቀሱት ከድንግል የተወለዱ
ሳይሆን ከዮሴፍ የተወለዱ ዘመዶቹ ናቸው።
፳፱
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
፴
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
- መኃ ፬፥፰ “ሙሽራዬ ሆይ፥ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ፤ ከሊባኖስ ከእኔ
ጋር ነዪ”
ስለ እድገቷ
- መዝ ፵፬፥፲ “ልጄ ሆይ፥ ስሚ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤ ወገንሽን
ያባትሽንም ቤት እርሺ”
ጌታን ስለ መጽነሷና ስለመውለዷ
- ኢሳ. ፯፥፲፬ “ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋልእነሆ ድንግል
ትፀንሳለች ወንድ ልጅንም ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ትለዋለች”
ብሎ ነቢዩ ኢሳያስ በመንፈስ ቅዱስ ይህን ምሥጢር ተረድቶ ስለ
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተናግሯል።
ስለ ስደቷ
- ሆሴዕ ፲፩፥፩ “ልጄንም ከግብፅ ጠራሁት።”
ስለ ሐዘኗ
- ሉቃ ፪፥፴፬-፴፭ “በአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል”
ስለሞቷ ትንሣኤዋና ዕርገቷ
- መዝ ፻፴፩፥፰ “አቤቱ፥ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፥ አንተና የመቅደስህ ታቦት።”
በሰማይ ስለመኖሯ
- መዝ ፵፬፥፱ “በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ
ትቆማለች።”
፴፩
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
የመልመጃ ጥያቄዎች
ትክክለኛውን መልስ መልሱ።
፩- እመቤታችንን ለምን እናከብራታለን?
፪- ከ፴፫ቱ የእመቤታችን ዐበይት በዓላት መካከል ቢያንስ አምስቱን
ጥቀሱ።
፫- ስለ እመቤታችን የተተነበዩ ትንቢቶችን ዘርዝሩ።
፬- በመጽሐፍ ቅዱስ የእስከ አገባብን አስረዱ።
፭- ወንድሞች የሚለው ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ ያለውን ትርጉሞች ጻፉ።
፴፪
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
ምዕራፍ ሦስት
የእመቤታችን አማላጅነት
ዓላማ
ተማሪዎች ይህንን ምዕራፍ ሲያጠናቅቁ
፴፮
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
፫.፪ ስለ አማላጅነቷ
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በክብር ከፍጡራን ሁሉ በላይ ናትና
አማለጅነቷ እውነተኛ እና እውን ነው። እመቤታችንን አምነው ለጠሯት
ሩህሩህ፤አዛኝ ናትና ከልጇ ከአምላካችን ታማልደናለች እንደ እናትነቷም
ለአምላካችን ቅርብ ናት። ስለዚህም ልመናችንን ታስፈፅምልናለች።
ምክንያቱም ልጅ እናቱን ሲጠይቅ የማይፈፀምለት የለምና። እርሷም
በዮሐንስ በኩል ለእኛ እናት ሆና ተሰጥታናለች።
- “እናትህ እነኋት አለው” ዮሐ ፲፱፥፳፯
- እኛም የአደራ የመስቀል ሥር ልጆቿ ነን “እነሆ ልጅሽ” ዮሐ ፲፱፥፳፮
በዚህም ላይ ዘርዋ ልጆቿ እንደሆን ቅዱስ ዮሐንስ ራሱ “ዘንዶውም
በሴቲቱ ላይ ተቈጥቶ የእግዚአብሔርን ትእዛዛት የሚጠብቁትን የኢየሱስም
ምስክር ያላቸውን ከዘርዋ የቀሩትን ሊዋጋ ሄደ” ራእይ ፲፪፥፲፯ በማለት
ነግሮናል።
ስለ ምልጃዋም “የወርቅ ልብስ ተጐናፅፋ እና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ
ትቆማለች” በማለት መዝ ፵፬፥፩-፱ ላይ ነብዩ ዳዊት እመቤታችን ቅድስት
ድንግል ማርያም ንጽሕና ንገንዘብ አድርጋ ለአማላጅነት ከጎኑ በቀኙ በቅርብ
እንደምትቀመጥ አስረድቶናል። ይህም ንግሥቲቱ አስቴር እንዳደረገችው
ያለ ነው። እርሷ ወገኖቿን በምልጃዋ አትርፋለችና። መጽሐፈ አስቴር
፰፥፬-፮ “ንጉሡም የወርቁን ዘንግ ለአስቴር ዘረጋላት፤ አስቴርም ተነሥታ
በንጉሡ ፊት ቆመችና፦ ንጉሡን ደስ ቢያሰኘው፥ በፊቱም ሞገስ አግኝቼ
እንደሆነ፥ ይህም ነገር በፊቱ ቅን ቢሆን፥ እኔም በእርሱ ዘንድ ተወድጄ
እንደ ሆነ፥ አጋጋዊው የሐመዳቱ ልጅ ሐማ በንጉሡ አገር ሁሉ ያሉትን
አይሁድ ለማጥፋት የጻፈው ተንኰል ይገለበጥ ዘንድ ይጻፍ።እኔ በሕዝቤ
ላይ የሚወርደውን ክፉ ነገር አይ ዘንድ እንዴት እችላለሁ? ወይስ
የዘመዶቼን ጥፋት አይ ዘንድ እንዴት እችላለሁ? አለች።”
መቆምም ምልጃን እንደሚያሳይ ራሱ ቅዱስ ዳዊት አስቀምጧል።
“እንዳያጠፋቸው ቍጣውን ይመልስ ዘንድ የተመረጠው ሙሴ በመቅሠፍት
ጊዜ በፊቱ ባይቆም ኖሮ፥ ያጠፋቸው ዘንድ ተናገረ” መዝ ፻፭፥፳፫እንዲል።
፴፯
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
፵፩
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
፵፫
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
የመልመጃ ጥያቄዎች
ትክክለኛውን መልስ መልሱ።
፩- ቅዱሳን በምድር እያሉ እንደሚያማልዱ የሚያስረዳ አንድ የመጽሐፍ
ቅዱስ ታሪክ ጥቀሱ።
፪- እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በቃና ዘገሊላ ያደረገችውን
ምልጃ ተናገሩ።
፫- ጌታችን በቃና ዘገሊላ ሰርግ ላይ ጊዜዬ ገና አልደረሰም ያለበትን
ምክንያት ዘርዝሩ።
፵፬
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
ምዕራፍ አራት
የእመቤታችን ምሳሌዎች
ዓላማ
ተማሪዎች ይህንን ምዕራፍ ሲያጠናቅቁ
፵፭
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
፵፮
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
ከጐኑ አደረገልን።
• ደመና የእመቤታችን፣ ፬ቱ ኅብር/ ቀለም ያለው ቀስተ ደመና
የ፬ቱ ባሕርያቷ ምሳሌ ሲሆን ከእርሷ በነሣው ሰውነት ሰውን ለማዳኑ
ማሳሌ ነው።
ሥዕል ፰ ዕፀ ጳጦስ
፶፩
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
፶፫
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
፶፭
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
የመልመጃ ጥያቄዎች
ትክክለኛውን መልስ መልሱ።
፩- እመቤታችንን ለምን በኖኅ መርከብ ተመሰለች?
፪- ሙሴ ያያት ዕፀ ጳጦስ እንዴት የእመቤታችን ምሳሌ እንደምትሆን
አስረዱ።
፫- እግዚአብሔር በቀስተ ደመና ምልክት ቃል ኪዳን የገባለት ጻድቅ ማን
ይባላል?
፬- እመቤታችንን ለምን በአሮን በትር ተመሰለች?
፶፮
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
ዋቢ መጻሕፍት
• ሰማንያ አሐዱ መጽሐፍ ቅዱስ
• ወላዲተ አምላክ በመጽሐፍ ቅዱስ
• ውዳሴና ቅዳሴ ማርያም
• ተአምረ ማርያም
፶፯
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
መሠረተ ሃይማኖት አራተኛ ክፍል
፶፰
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት
የሰንበት ት/ቤት አመራር እና መምህራን
እንዲሁም ተማሪዎችና ወላጆች በመጽሐፉ ላይ
ያላችሁን ማንኛውም አስተያየት እና ግብዓት
በሚከተለው አድራሻ ላኩልን
office@eotc-gssu.org
https://t.me/GSSUCurricu-
lum_bot