You are on page 1of 5

1

የሰ/መ/ቁ. 236987
ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ.ም
ዲኞች፡-
ተፈሪ ገብሩ (ድ/ር)

እንዲሻዉ አዲነ

ተሾመ ሽፈራዉ

መሊኩ ካሳዬ

ነፃነት ተገኝ
አመሌካች፡ ወ/ሮ አይናሇም ሃና ፊቃደ
ተጠሪ፡ ወ/ሮ ረምሊ ሳቢር
መዝገቡ ተመርመሮ ተከታዩ ፍርዴ ተሰጥቷሌ፡፡

ፍ ር ዴ
ይህ ጉዲይ የዉርስ ክርክርን የሚመሇከት ሲሆን፣ ክርክሩ በተጀመረበት በፌዳራሌ የመጀመሪያ ዯረጃ
ፍርዴ ቤት የአሁኗ አመሌካች ባቀረቡት ክስ የሟች ወሊጅ አባቴ የዉርስ ንብረት እንዱጣራ ዲኝነት ጠይቄ
በመ/ቁጥር 43370 ሊይ የዉርስ ሀብት ተጣርቶ የተወሰነ ቢሆንም፣ በጉራጌ ዞን በቡታጅራ ከተማ እሪንዛፍ
ክ/ከተማ ቀበላ 05 ክሌሌ ዉስጥ ሌዩ ስሙ ሀቱ ተብል በሚጠራዉ መንዯር ዉስጥ አዋሳኙ የተጠቀሰዉን
ሟች አባቴ ሇሰርግ መናፈሻ አገሌግልት እንዱዉሌ ይዞት ቤትና የተሇያዩ አትክሌቶች ያለበት ስፋቱ በግምት
8000 ካ/ሜትር ይዞታ ተጠሪ በመዯበቋ ሳይጣራ የታሇፈ መሆኑን ጠቅሰዉ በዉርስ አጣሪ ይጣራሌኝ በሚሌ
የጠየቁትን ዲኝነት መነሻ ያዯረገ ነዉ፡፡ ተጠሪ በበኩሊቸዉ የመጀመሪያ መቃወሚያ እና የፍሬ ነገር ክርክር
ያቀረቡ ሲሆን፣ በመጀመሪያ መቃወሚያነት ያቀረቡት መሌስ ይዘትም ጉዲዩ በመ/ቁጥር 43370 ሊይ ዉሳኔ
ያገኘ በመሆኑ ክሱ በዴጋሚ የቀረበ ነዉ የሚሌ ነዉ፡፡

ፍርዴ ቤቱም በቀረበዉ የመጀመሪያ መቃወሚያ ሊይ የግራ ቀኝ ክርክር ከሰማ በኋሊ ሇክርክሩ መነሻ
የሆነዉ መሬት እንዱጣራ በአመሌካች እና በላልችም ወራሾች በቀረበ አቤቱታ መነሻነት የዉርስ ንብረት
ተጣርቶ ጥቅምት 19 ቀን 2007 ዓ.ም የዉርስ አጣሪ ሪፖርት የቀረበ መሆኑን፣ በወቅቱም ሇዚህ ክርክር
መነሻ የሆነዉ ይዞታ የሟች መሆኑ በማስረጃ አሌተረጋገጠም በሚሌ በዉርስ አጣሪ ሪፖርቱ የተገሇጸ ሲሆን
ሪፖርቱም ጉዴሇት የሇበትም ተብል በፍርዴ ቤት የጸዯቀ ሲሆን በይግባኝ አሇመሻሩን ጠቅሶ አመሌካች
ያቀረቡት ክስ በዴጋሚ የቀረበ ነዉ በማሇት በብይን ዉዴቅ በማዴረግ ወስኗሌ፡፡ አመሌካች በዚህ ዉሳኔ
ባሇመስማማት ሇፌዳራሌ ከፍተኛ ፍርዴ ቤት ይግባኝ ያቀረቡ ቢሆንም፣ ከፍተኛ ፍርዴ ቤቱ የይግባኝ
መዝገቡን አስቀርቦ የግራ ቀኝ ክርክር ከሰማ በኋሊ የስር ፍርዴ ቤቱን ዉሳኔ በማጽናት ወስኗሌ፡፡

አመሌካች ህዲር 03 ቀን 2015 ዓ.ም ጽፈው ባቀረቡት የሰበር አቤቱታ ከዚህ በፊት በመ/ቁጥር
43370 ሊይ የጸዯቀዉ የዉርስ አጣሪ ሪፖርት ሊይ ዉርስ አጣሪዉ ሇክርክሩ መነሻ የሆነዉን ይዞታ
በተመሇከተ የዉርስ አጣሪዉ ማስረጃ ማግኘት አሇመቻለን ገሌፆ ባቀረበዉ ሪፖርት ሊይ ፍርዴ ቤቱ ምንም
አስተያየት ሳይሰጥበት ያሇፈ ሲሆን፣ በላሊ በኩሌ አንዴ ጉዲይ በዴጋሚ የቀረበ ነዉ ሇማሇት የሚቻሇዉ
በማስረጃ ተጣርቶ ዉሳኔ የተሰጠበት መሆን እንዲሇበት እና በተያዘዉ ጉዲይ በዉርስ ማጣራት ወቅት ፍርዴ

ማስታወሻ፡ - ይህ የ ሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነ ድ ለጥና ትና ምር ምር ሥራ ወይም ለግንዛ ቤ እ ንጂ


Abrham Yohanes
ለፍር ድ አ ፈጻ ጸ ም ዓላማ አ ያገ ለግልም
2

ቤቱ አጣርቶ ዉዴቅ ባሊዯረገበት ሁኔታ ዉሳኔ አርፎበታሌ ሇማሇት የሚቻሌበት ሁኔታ በላሇበት ክሱ
በዴጋሚ የቀረበ ነዉ በሚሌ በስር ፍርዴ ቤቶች የተሰጠ ዉሳኔ መሠረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት
በመሆኑ ታርሞ ይወሰንሌኝ በማሇት ዲኝነት ጠይቀዋሌ፡፡

የሰበር አቤቱታዉም በአጣሪ ችልት ተመርምሮ የዉርስ አጣሪ ሇክርክሩ መነሻ የሆነዉን ይዞታ
በተመሇከተ የቀረበ ማስረጃ የሇም በማሇት ያሇፈዉን የመጨረሻ ዉሳኔ እንዯተሰጠበት ተዯርጎ ክሱ በዴጋሚ
የቀረበ ነዉ በሚሌ ዉዴቅ የመዯረጉን አግባብነት ግራ ቀኝ በተገኙበት አጣርቶ ሇመወሰን ሲባሌ ያስቀርባሌ
በመባለ፣ ተጠሪ መሌስ እንዱያቀርቡ በተዯረገሊቸዉ ጥሪ መሠረት የካቲት 20 ቀን 2015 ዓ.ም በተፃፈ
መሌስ የአመሌካች አቤቱታ ዉዴቅ ሉዯረግ ይገባሌ የሚለባቸዉን ምክንያቶች በዝርዝር በመጥቀስ
ተከራክረዋሌ፡፡

ከስር ጀምሮ የጉዲዩ አመጣጥ እና የግራ ቀኙ ክርክር ይዘት አጠር አጠር ባሇ መሌኩ ሲታይ ከፍ
ሲሌ የተመሇከተዉን ሲመስሌ ይህ ችልትም የሟች የዉርስ ሀብት ተጣርቶ ባሇበት ሁኔታ አመሌካች
ያቀረቡት የዲግም የዉርስ ይጣራሌኝ ዲኝነት ተቀባይነት ያሇዉ መሆን አሇመሆኑን በጭብጥነት በመያዝ
ከግራ ቀኝ ክርክር እና ሇጉዲዩ አግባብነት ካሊቸዉ ዴንጋጌዎች ጋር በማገናዘብ መዝገገቡን እንዯሚከተሇዉ
መርምሮታሌ፡፡ እንዯመረመረዉም የሟች አቶ ፍቃደ ሰሴሮ የዉርስ ሀብት በዉርስ አጣሪ ተጣርቶ
ሪፖርቱም ሇፍርዴ ቤቱ ቀርቦ የጸዯቀ ስሇመሆኑ አሊከራከረም፡፡ ከሊይ እንዯተገሇጸዉ አመሌካች ሊቀረቡት
የዉርስ ይጣራሌኝ አቤቱታ መሠረት ያዯረጉት ሇክርክሩ መነሻ የሆነዉ ይዞታ የሚገኝበት ቦታ ወራሾች
ባሇማወቃቸዉ እና ተጠሪም የሇም ብሇዉ በመዯበቃቸዉ ዉርስ ሲጣራ በነበረበት ወቅት ሳይጣራ ታሌፏሌ
የሚሌ ይዘት ያሇዉ ስሇመሆኑ የስር ፍርዴ ቤት ዉሳኔ ግሌባጭ ያሳያሌ፡፡

በመሠረቱ ስሇ ዉርስ የሚዯዯነግገዉ የኢትዮጵያ የፍትሐብሔር ህግ ሟች እንዯሞተ የውርስ


ሀብት የማጣራት ስራ ተከናዉኖ ሇወራሾች የሚተሊሇፈው የጠራ ሀብት ከተሇየ በኋሊ የውርስ ክፍፍሌ
እንዯሚፈፀም ያዛሌ፡፡ የፍትሐብሔር ህጉ አንቀጽ 942 ዉርስ እስከተጣራ ዴረስ እንዯ ተሇየ ንብረት
ሆኖ ይቆጠራሌ (so long as a succession has not been liquidated, it shall constitute a
distinct estates) በሚሌ የሚዯነግግ ሲሆን፣ ይሄም የዉርስ ማጣራት ሥርዓትን የሚገዛ መሪ ዯንብ
ነዉ፡፡ በዚህ መሪ ዯንብ መሠረት የዉርስ ንብረት ከመጣራቱ በፊት የዉርስ ንብረት እንዯ አንዴ የተሇየ
የማይከፋፈሌ ንብረት ሆኖ ስሇሚቆጠር የሟች ወራሾች እና የዉርስ ንብረቶች መሇየትና መወሰን
እንዱሁም ዉርስ ዕዲዎችን የመሇየትና የመክፈሌ ተግባር እስኪከናወን ዴረስ የዉርስ ሀብቱ ከወራሾች
ንብረት ጋር ሳይቀሊቀሌ ይቆያሌ፡፡ ከዉርስ ሐብት ሊይ ገንዘብ ሇመጠየቅ መብት ያሊቸዉ ሰዎች
ማሇትም የሟች አበዲሪዎች እና የፍርዴ ባሇመብቶች ሇገንዘባቸዉ ዋስትናና መያዥያ የሚሆናቸዉ
ይሄዉ በመጣራት ሊይ ያሇዉ የዉርስ ንብረት ነዉ፡፡ በመሆኑም የሟች ዉርስ በመጣራት ሊይ እያሇ
ከሟች ወራሾች ገንዘብ ጠያቂ የሆኑ ሰዎች በወራሾች የግሌ ንብረት ሊይ አንዲችም ጥያቄ ማቅረብ
አይችለም፡፡ ከሟች ዉርስ ገንዘብ የሚጠይቁ ሰዎች ያሊቸዉ መብት የሟችን የዉርስ ንብረት መከታተሌ
ብቻ ነዉ፡፡ የሟች የዉርስ ሀብት ዴርሻም የሚታወቀዉ የሟች ዉርስ ከተጣራ ብቻ ነዉ፡፡ ዉርስ
እንዱጣራ የሚዯረገዉም በዚህ ምክንያት ነዉ፡፡

በዚህም መሠረት የፍትሐብሔር ህጉ ስሇ ዉርስ ማጣራት በሚዯነግገዉ ክፍሌ ዉርስ ማጣራት


ሇሚሇዉ ጽንሰ ሃሳብ ትርጉም በመስጠት የሚጀምር ሲሆን፣ የዉርስ አጣሪ ተግባራት ምን ምን
እንዯሆኑ እንዱሁም በሂዯቱ የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን በተሇያዩ አንቀፆቹ ይዯነግጋሌ፡፡

ማስታወሻ፡ - ይህ የ ሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነ ድ ለጥና ትና ምር ምር ሥራ ወይም ለግንዛ ቤ እ ንጂ


Abrham Yohanes
ለፍር ድ አ ፈጻ ጸ ም ዓላማ አ ያገ ለግልም
3

በፍትሐብሔር ህጉ እንዯተመሇከተዉ ዉርስ ማጣራት የሟች ወራሾች እነ ማን እንዯሆኑ አጣርቶ


መወሰን፣ የዉርስ ሀብት ምን መሆኑን መወሰን፣ ላልች ሰዎች ከሟች የተበዯሩትን ገንዘብ መሰብሰብና
በሟች ዉርስ ሊይ ሉከፍሊቸዉ የሚገቡ አስገዲጅ የሆኑ እዲዎችን አጣርቶ መክፈሌ እና ሟች በኑዛዜ
ስጦታ ያዯረገሊቸዉ ሰዎች የተሰጣቸዉን መክፈሌ ስሇመሆኑ የህጉ አንቀጽ 944 ዴንጋጌ ያሳያሌ፡፡
በዉርስ አጣሪዉ የሚከናወኑ ተግባራትንም ስንመሇከት ሟች ኑዛዜ ትቶ እንዯሆነ መፈሇግና በመጨረሻ
ዉርሱ የሚዯርሳቸዉ ሰዎች እነማን እንዯሆኑ ማረጋገጥ፣ የዉርስ ሀብት ማስተዲዯር፣ መክፈያቸዉ
የዯረሰዉን የዉርስ ዕዲዎች መክፈሌ፣ ሟች በኑዛዜ ያዯረጋቸዉን ስጦታዎች መክፈሌና የኑዛዜዉን ቃሌ
ሇመፈጸም ማናቸዉም ላልች አስፈሊጊ ጥንቃቄዎችን በማዴረግ ተገቢዉን ሁለ ካዯረገ በኋሊ
በመጨረሻም የዉርስ ማጣራት ስራዉ የሚዘጋ (closure of the liquidation) ስሇመሆኑ በህጉ አንቀጽ
956 እና 1052 ሊይ ከተመሇከቱት ዴንጋጌዎች መገንዘብ ይቻሊሌ፡፡

በዚህ ሁለ ሂዯት አሌፎ ዉርስ ተጣርቶ የተዘጋ እንዯሆነ የዉርስ ማጣራት የታሇመሇትን ዓሊማ
እንዲሳካ ይቆጠራሌ፡፡ ሆኖም በዉርስ ማጣራት ሂዯት ግዴፈት አይኖርም ወይም መጣራት የሚገባቸዉ
ሁለ ተጣርተዋሌ ወይም በሂዯቱ የወራሾች ወይም የሟች ገንዘብ ጠያቂዎች መብት አይነካም ማሇት
አይዯሇም፡፡ የዉርስ ማጣራት ሂዯቱ በአግባቡ ባሇመከናወኑ ወይም በላሊ ምክንያት መካተት የሚገባቸዉ
ንብረቶች ሳይካተቱ በመቅረታቸዉ ወይም መካተት ሳይገባቸዉ በመካተታቸዉ ወይም ወራሽ የሆነ ሰዉ
ስሙ ባሇመካተቱ ምክንያት ወይም ከዉርስ ሀብት ገንዘብ ሉከፈሇዉ የሚገባዉ የሟች ባሇገንዘብ
ሳይከፈሇዉ ሉቀር የሚችሌበት ሁኔታ ይኖራሌ፡፡ በዚህም ምክንያት በአንዴ ወይም በላሊ ምክንያት
ጉዲት ዯርሶብኛሌ ወይም መብቴ ተነክቷሌ ወይም ወራሽነቴ ይረጋገጥሌኝ የሚሌ ሰዉ መብቱን
ሉያስከብር የሚችሌበት ሥርዓት ሉኖር ግዴ ይሊሌ፡፡ ይህን ሁለ ከግምት ዉስጥ በማስገባትም
የፍትሐብሔር ህጉ ስሇ ዉርስ በሚዯነግገዉ ክፍለ ከዉርስ ጋር በተያያዘ መብት ያሇዉ ወገን ሇፍርዴ
ቤት አቤቱታ/ክስ አቅርቦ መብቱን ሉያስከብር የሚችሌባቸዉን ሥርዓቶች ይዯነግጋሌ፡፡ የተወሰኑትን
ሇመጥቀስ ያህሌም፣ ወራሽ መሆኑንና ከዉርስ ሀብቱ የሚዯርሰዉን የዴርሻ መጠን የሚያመሇክት
የወራሽነት የምስክር ወረቀት ፍርዴ ቤት እንዱሰጠዉ መጠየቅ እንዯሚቻሌ እና ፍርዴ ቤቱም ከሳሹ
ያቀረበዉን ማስረጃ ጨምሮ ተገቢዉን ማጣሪያ በማዴረግ አስፈሊጊ ከሆነም ዋስትና እንዱቀርብ
በማዴረግ የወራሽነት የምስክር ወረቀት እንዯሚሰጥ፣ የወራሽነት የምስክር ወረቀት የተሰጠዉ ሰዉም
በማስረጃዉ ሊይ በተገሇጸዉ መሠረት ወራሽ ነዉ ተብል እንዯሚገመት፤ በፍርዴ ቤት የተሰጠዉ
የወራሽነት የምስክር ወረቀት እንዱሰረዝ ወራሽ በሆነ ሰዉ ክስ ማቅረብ እንዯሚቻሌ እና ፍርዴ ቤቱም
የወራሽነት የምስክር ወረቀት የተሰጠዉ ሰዉ ወራሽ አሇመሆኑን ካረጋገጠ እንዯ ነገሩ ሁኔታ የተሰጠዉን
የወራሽነት የምሰክር ወረቀት በመሰረዝ ወይም እንዱመሇስ ወይም ተከሳሹ እንዲይገሇገሌበት ዉሳኔ
መስጠት እንዯሚችሌ፤ የወራሽነት መብት በላሇዉ ሰዉ የተያዘ ንብረት እንዱመሇስ እዉነተኛ ወራሽ
ክስ ማቅረብ እንዯሚችሌ፤ የዉርስ ማጣራት ሂዯቱ ተከናዉኖ የዉርስ ክፍያ ከተዯረገ በኋሊ በዉርስ
ንብረት ዉስጥ ገብተዉ የሚቆጠሩ አዱስ ሀብቶች የተገኙ እንዯሆነ በተገኙት አዱስ ንብረቶች መጠን
ክፍያ በዴጋሚ እንዱዯረግ መጠየቅ እንዯሚቻሌ፣ የአንዲንዴ ንብረቶች ዋጋ በተሳሳተ ሁኔታ የተገመተ
መሆኑ ከታወቀም የዉርስ ክፍያ ሥርዓቱ እንዱቃና መጠየቅ እንዯሚቻሌ እንዱሁም የዉርስ ሀብት
ከተከፋፈሇ በኋሊ የሚመጣ ገንዘብ ጠያቂ ካሇ ወራሾች በዯረሳቸዉ ዴርሻ ሌክ ዕዲዉን እንዱከፍለ
መጠየቅ እንዯሚቻሌ በፍትሐብሔር ህጉ አንቀጽ 996-999፣ 1003፣ 1005 እና 1010 ሊይ
የተመሇከቱትን ማየት ይቻሊሌ፡፡

ማስታወሻ፡ - ይህ የ ሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነ ድ ለጥና ትና ምር ምር ሥራ ወይም ለግንዛ ቤ እ ንጂ


Abrham Yohanes
ለፍር ድ አ ፈጻ ጸ ም ዓላማ አ ያገ ለግልም
4

ከሊይ በዝርዝር ያየናቸዉ ሃሳቦች በአጠቃሊይ የሚያሳዩን የዉርስ ማጣራት ስራ የሟች


ንብረቶችን፣ የሟች ወራሾችን፣ የሟች ኑዛዜ ተጠቃሚዎችን እና የሟች ባሇገንዘቦችን ሇይቶ ከዉርስ
ሀብት ሉከፈለ የሚገባቸዉ ዕዲዎች ከፍል በመጨረሻም ሇወራሾች የሚተሊሇፈዉን ሀብት መሇየት
ሲሆን፤ በወራሾች በእራሳቸዉ ወይም በፍርዴ ቤት በሚሾም የዉርስ አጣሪ የማጣራት ስራዉ ተከናዉኖ
የተዘጋ እንዯሆነ በማጣራቱ ሂዯት በተፈጸመ ግዴፈት ወይም በላሊ ምክንያት መብቱ የተነካበት ሰዉ
ካሇ በላሊ አግባብ መብቱን ማስከበር የሚችሌ መሆኑን ነዉ፡፡ በላሊ አነጋገር ዉርስ ማጣራት የወራሽነት
መብትን ማረጋገጥ ከሚቻሌባቸዉ መንገድች አንደ እንጂ ብቸኛዉ መንገዴ አሇመሆኑን ነዉ፡፡
ይሌቁንም፣ ከሊይ እንዯተገሇጸዉ፣ የውርስ ማጣራት ዋና ዓሊማ ባሇቤቱ በመሞቱ ምክንያት በቤተሰቦቹ
(ወራሾቹ) ዙሪያ በሚፈጠር ያሇመረጋጋትና የአስተዲዯር ችግር ወይም በላሊ ምክንያት የውርስ ሀብት
በየአቅጣጫው እንዲይባክንና የሟች ሀብት በአግባቡ ተጠብቆ በሕጉ ሇሚገባቸው ወራሾች
እንዱተሊሇፍሊቸው ሇማዴረግ፤ እንዱሁም የሟች ገንዘብ ጠያቂዎችን ጥቅም ሇማስጠበቅ እንጂ፣ ወራሾች
ከሟች ንብረት ጋር በተያያዘ ያሊቸዉን መብት ብቻ ሇመጠበቅ አይዯሇም፡፡ የዉርስ ማጣራት ስራ
ተጠናቆ የማጣራት ሂዯቱ መዘጋቱ ከታወቀ የሟች ንብረቶች፣ የሟች ወራሾች፣ የሟች የኑዛዜ
ተጠቃሚዎች እንዱሁም የሟች ባሇገንዘቦች ተሇይተዉ ታዉቀዉ ከዉርስ ሀብቱ የሟች ባሇ ገንዘቦች እና
የኑዛዜ/ስጦታ ተጠቃሚዎች ካለ ከዉርስ ንብረቱ ተከፍል እንዯተጠናቀቀ የሚገመት ከመሆኑ አንፃር
በዴጋሚ የዉርስ ይጣራሌኝ/ን አቤቱታ ሇፍርዴ ቤት ሉቀርብ የሚገባበት ህጋዊ ምክንያት የሇም፤ ፍርዴ
ቤትም ዲኝነቱን ሉቀበሇዉ አይገባም፡፡ በዉርስ ማጣራት ወቅት ያሌቀረበ ወራሽ መቅረቡ፣ በወቅቱ
ያሌተገኘ ንብረት መገኘቱ በወቅቱ ያሌቀረበ የሟች ባሇ ገንዘብ መቅረቡ ብቻዉን ዉርስ እንዱጣራ ጥያቄ
ሇማቅረብ ምክንያት ሉሆን አይችሌም፡፡

በዉርስ አጣሪ ተጣርቶ የቀረበ የዉርስ ማጣራት ሪፖርት በፍርዴ ቤት መጽዯቁ የማስረጃ ዋጋ
ያሇዉ ቢሆንም፣ እንዯ ፍርዴ ሉቆጠር እንዯማይችሌ የፌዳራሌ ጠቅሊይ ፍርዴ ቤት ሰበር ሰሚ ችልት
በሰ/መ/ቁጥር 18576 (ቅጽ 7 ሊይ የታተመዉን ጨምሮ) በላልችም መዛግብት ሊይ ገዥ የህግ ትርጉም
ሰጥቷሌ፡፡ ፍርዴ ቤቱ የዉርስ አጣሪ ሪፖርትን ሲያጸዴቅ አንዴን አከራካሪ ጭብጥ ይዞ፣ አከራክሮ እና
ማስረጃን ሰምቶ የፍርዴ ዉጤት በሚኖረዉ መሌኩ የወሰነዉ ካሌሆነ በቀር፣ የዉርስ አጣሪ ያቀረበዉን
ሪፓርት በማጽዯቅ የሰጠዉ ዉሳኔ በላሊ ክርክር እና ማስረጃ ሉስተባበሌ የሚችሌ መሆኑን ነዉ፡፡
በመሆኑም የዉርስ አጣሪ ሪፖርት በፍርዴ ቤት መጽዯቁም ከዉርስ ማጣራት ሂዯት ጋር በተያያዘ
ወይም በላሊ ምክንያት መብቴ ተነክቷሌ የሚሌ ሰዉ በላሊ አግባብ መብቱን እንዲያስከብር ምክንያት
አይሆንም፡፡

በአጠቃሊይ የዉርስ ማጣራት ስራ የተከናወነ መሆኑ ከታወቀ በዉርስ ማጣራቱ ሂዯት መብቴ
ተነክቷሌ ወይም በላሊ በማንኛቸዉም ምክንያት ከወራሽነት መብት ጋር በተያያዘ መብቴ ተነክቷሌ
የሚሌ ሰዉ ዲኝነት ከፍል በሚመሇከተዉ አካሌ ሊይ በህግ አግባብ ክስ አቅርቦ መብቱን ማስከበር
ከሚችሌ በስተቀር በዴጋሚ የዉርስ ይጣራሌኝ አቤቱታ ሉያቀርብ የሚችሌበት ህጋዊ ምክንያት የሇም፡፡
ከዚህ አንፃር የተያዘዉን ጉዲይ ስንመሇከት አመሌካች የሟች አባታቸዉ ዉርስ ከዚህ በፊት በዉርስ
አጣሪ ተጣርቶ ሪፖርቱ ሇፍርዴ ቤት ቀርቦ መጽዯቁን ሳይክደ፣ የዉርስ ይጣራሌኝ አቤቱታ በዴጋሚ
ሇፍርዴ ቤቱ ያቀረቡት ሇክርክሩ መነሻ የሆነዉን ይዞታ ዉርስ በሚጣራበት ወቅት የት እንዯሚገኝ
ባሇመታወቁ እና ተጠሪም በወቅቱ መዯበቃቸዉን በመግሇጽ ነዉ፡፡ ይሁንና በወቅቱ ሳይታወቅ ቀርቷሌ
አሌተካተተም የሚለ ከሆነ ምክንያቱን ጠቅሰዉ መብታቸዉን በላሊ አግባብ ማስከበር ከሚችለ በቀር

ማስታወሻ፡ - ይህ የ ሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነ ድ ለጥና ትና ምር ምር ሥራ ወይም ለግንዛ ቤ እ ንጂ


Abrham Yohanes
ለፍር ድ አ ፈጻ ጸ ም ዓላማ አ ያገ ለግልም
5

በዴጋሚ የሟች የዉርስ ሀብት እንዱጣራ ፍርዴ ቤቱ የዉርስ አጣሪ እንዱሾምሊቸዉ የጠየቁት ዲኝነት
የዉርስ ሀብት ማጣራት አስፈሊጊነት እና ዓሊማን መሠረት ያዯረገ ባሇመሆኑ ከመነሻዉም ዉዴቅ
ሉዯረግ የሚገባዉ ነዉ፡፡ ስሇሆነም፣ ጉዲዩን ከዚህ አንፃር ማየት ሲገባዉ፣ የፌዳራሌ የመጀመሪያ ዯረጃ
ፍርዴ ቤት የአመሌካችን ክስ ተቀብል ነገር ግን ክሱ በዴጋሚ የቀረበ ነዉ በማሇት የሰጠዉን ብይን
በማጽናት በፌዳራሌ ከፍተኛ ፍርዴ ቤት የተሰጠ ዉሳኔ መሠረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ሆኖ
ተገኝቷሌ፡፡ ስሇሆነም ተከታዩ ተወስኗሌ፡፡

ዉ ሳ ኔ

1. የፌዳራሌ የመጀመሪያ ዯረጃ ፍርዴ ቤት በመ/ቁጥር 97057 ሊይ ሚያዝያ 08 ቀን 2014 ዓ.ም


በዋሇዉ ችልት የሰጠዉ ብይን እንዱሁም የፌዳራሌ ከፍተኛ ፍርዴ ቤት በመ/ቁጥር በመ/ቁጥር
282683 ሊይ ነሐሴ 30 ቀን 2014 290314 ዓ.ም በዋሇዉ ችልት የሰጠዉ ዉሳኔ
በፍ/ብ/ሥ/ሥርዓት ህጉ አንቀጽ 348(1) መሠረት ተሽረዋሌ፡፡

2. አመሌካች መብታቸዉን ሇማስከበር በህግ አግባብ የሚያቀርቡትን ክስ ይህ ዉሳኔ አይከሇክሌም፡፡

3. በዚህ ችልት የተዯረገዉ ክርክር ያስከተሇዉን ወጪና ኪሳራ ግራ ቀኝ የየራሳቸዉን ይቻለ፡፡

መዝገቡ ተዘግቷሌ፤ ወዯ መዝገብ ቤት ይመሇስ

የማይነበብ የአምስት ዲኞች ፊርማ አሇበት

ፍ/ገ

ማስታወሻ፡ - ይህ የ ሰበር ችሎት ውሳኔ ሰነ ድ ለጥና ትና ምር ምር ሥራ ወይም ለግንዛ ቤ እ ንጂ


Abrham Yohanes
ለፍር ድ አ ፈጻ ጸ ም ዓላማ አ ያገ ለግልም

You might also like