Professional Documents
Culture Documents
የከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባ የዋስትና ፈንድ ማቋቋሚያ
የከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባ የዋስትና ፈንድ ማቋቋሚያ
በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ተረጋግጦ የተመዘገበ የመሬት ይዞታ ባለመብት የሆነ
ሰው የመሬት ይዞታ መብቱ ዋስትና እንዲኖረው ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ስለተገኘ፤
በተከናወኑ ምዝገባዎች መሠረት በሚሰጡ የምዝገባ ማረጋገጫ ሰርተፊኬቶች ላይ ዋስትና
በመስጠት ሕብረተሰቡ በመሬት ይዞታ ምዝገባ ስረዓት ላይ እምነት እንዲኖረው ማደረግ
በማስፈለጉ፤በተሰጡ የምዝገባ ማረጋገጫ ማስረጃዎች መሠረት በማድረግ ሦስተኛ ወገኖች
በቅን ልቦና በሚፈጽሙት ተግባር ምክንያት ለሚደርስባቸው ጉዳት ካሣ ለመክፈል
የሚያስችል የዋስትና ፈንድ ማቋቋም ስለአስፈለገ፤
በከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 818/2ዐዐ6 አንቀጽ 41 ንዑስ አንቀጽ
/1/ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈፃሚ አካላት እንደገና ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር
64/2ዐ11 አንቀጽ 97 መሠረት የአዲስ አበባ ከተማ ካቢኔ ይህንን ደንብ አውጥቷል፡፡
1. አጭር ርዕስ
ይህ ደንብ “የከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባ የዋስትና ፈንድ ማቋቋሚያ የአዲስ አበባ ከተማ
ካቢኔ ደንብ ቁጥር 108/2ዐ11” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡
2. ትርጓሜ
1
3. “ቢሮ” ማለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፋይናንስ ቢሮ ነው፤
4. “ኤጀንሲ” ማለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር የመሬት ይዞታ ምዝገባና
መረጃ ኤጀንሲ ነው፤
5. “አዋጅ” ማለት የከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 818/2ዐዐ6 ነው፤
6. “ደንብ” ማለት የከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ
ቁጥር 324/2ዐዐ6 ነው፤
7. “መመሪያ” ማለት የከተማ መሬት ይዞታ ማረጋገጥ እና ምዝገባ በከተማ
ልማትና ቤቶች ሚኒስቴር ተሻሽሎ የወጣ መመሪያ ቁጥር 61/2ዐ1ዐ ነው፤
8. “የመሬት ይዞታ” ማለት የሊዝ ሥሪት በሚመራበት ህግ መሠረት በሊዝ
የተያዘ ወይም በሊዝ ሕግ መሠረት ዕውቅና የተሰጠው የከተማ ነባር የመሬት
ይዞታ ላይ የተገኘ የተጠቃሚነት መብት ነው፤
9. “መዝጋቢ ሹም” ማለት በአዋጁ መሠረት የመሬት ይዞታ መብትን፣ ክልከላንና
ኃላፊነትን እንዲመዘግብ እና ማረጋገጫዎችን እንዲሰጥ ሥልጣን የተሰጠው
ሰው ነው፤
10. “የማይንቀሳቀስ ንብረት” ማለት የከተማ መሬትንና በመሬቱ ላይ የሚገኘውን
መሬት ነክ ንብረት፣ በመሬት ላይ በቋሚነት የተገነቡ ግንባታዎችን ወይም
የተተከሉ ቋሚ ተክሎችን የሚያካትት ሲሆን ሌሎች ተነሺ ንብረቶች አንደ
ሰብል፣ ሣር እና ቋሚ ያልሆኑ ተክሎችን አይጨምርም፤
11. “የዋስትና ፈንድ” ማለት ኤጀንሲው ላረጋገጣቸውና ለመዘገባቸው የከተማ
መሬት ይዞታዎች በተቋሙ ስህተት በተፈጠሩ የመሬት ይዞታ መብት
መዛባቶች ምክንያት ለሚደርስ ጉዳት ካሣ ክፍያ እንዲውል በየጊዜው
ከሚደረግ የከተማ መሬት ይዞታ የመጠቀም መብት ዝውውር ከግብይቱ ዋጋ
አንድ መቶኛ ሣይበልጥ የሚሰበሰብ ክፍያ ነው፤
12. “ሰው” ማለት የተፈጥሮ ሰው ወይም በሕግ የሰውነት መብት የተሰጠው አካል
ነው፤
13. በዚህ ደንብ ውስጥ በወንድ ፆታ የተደነገገው የሴትንም ፆታ ያካትታል፡፡
3. የተፈፃሚነት ወሰን፣
2
ይህ ደንብ በኤጀንሲው በሚፈፀም የመሬት ይዞታ መብት የስም ዝውውር ላይ
ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
ክፍል ሁለት
ስለ ከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባ የዋስትና ፈንድ መቋቋም
የከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባ የዋስትና ፈንድ /ከዚህ በኋላ “ፈንዱ” እየተባለ
የሚጠራ/ ቢሮው በሚከፍተው ልዩ የባንክ ሂሣብ ውስጥ ተቀማጭ እንዲሆን በዚህ
ደንብ ተቋቁሟል፡፡
5. የፈንዱ ምንጮች
የሚከተሉት ምዝገባዎች ለፈንዱ የሚውል ተጨማሪ ክፍያ ይከፈልባቸዋል፤
1. የመሬት ይዞታ መብት በሙሉ ወይም በከፊል በሽያጭ፣ በስጦታ፣ በዓይነት
መዋጮ ወይም በሌላ ህጋዊ መንገድ በመተላለፉ፣
2. የመሬት ይዞታ መብት በውርስ በመተላለፉ ፣
6. የፈንዱ ዓላማ
የፈንዱ ዓላማ፣
1. በኤጀንሲው ተረጋግጦ የተመዘገበ የመሬት ይዞታ ባለመብት የሆነ ሰው
የመሬት ይዞታ መብቱ እና በይዞታው ላይ ያረፈ የማይንቀሳቀስ ንብረቱ
ባለቤትንት መብቱ ዋስትና እንዲኖረው ለማድረግ፣
2. በኤጀንሲው ተረጋግጠው ለተመዘገቡ ምዝገባዎች በተሰጡ የምዝገባ ማረጋገጫ
ሰርተፊኬቶች ላይ ዋስትና በመስጠት ሕብረተሰቡ እምነት እንዲኖረው
ለማድረግ፡
3. ኤጀንሲው በሰጠው የምዝገባ ማረጋገጫ ማስረጃ ላይ በመደገፍ ሦስተኛ
ወገኖች በቅን ልቦና በሚፈጽሙት ተግባር ምክንያት ለሚደርስባቸው ጉዳት
ካሳ ለመክፍል ፡
3
ይሆናል፡፡
7. ስለክፍያዎች
4
በዚህ ደንብ አንቀጽ 9 ንዑስ አንቀጽ /1/ በተወሠነው የክፍያ ተመን
መሠረት ለፈንዱ የሚውል ተጨማሪ ክፍያ መፈፀም አለበት፡፡
5
ፈንዱን ካቢኔው ተገቢ ናቸው በሚላቸው በዋስትና ሰነዶች ላይ ኢንቨስት
ሊያደርግ ይችላል፡፡
ክፍል ሦስት
ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
15. ኦዲት
6
19. ደንቡ የሚፀናበት ጊዜ
ታከለ ኡማ በንቲ