Professional Documents
Culture Documents
7 2010
7 2010
1
የመሬት ይዞታ እንዲለቅ ለተደረገ ባለይዞታ የሚከፈለውን ካሣ ለመተመን እንዲቻል
ግምት ውስጥ መግባት የሚገባቸውን መሠረታዊ መርሆዎችን ለይቶ ማሻሻል
በማስፈለጉ፤
2
ክፍል አንድ
ጠቅላላ ድንጋጌ
1. አጭር ርዕስ
2. ትርጓሜ
3
ማስዋብ የመሳሰሉትን ሥራዎች እና መሬቱን በማስተካከል ለተከናወኑ
ተግባራት የዋለ ወጪ ነው::
5. "የህዝብ ጥቅም" ማለት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ማህበራዊና
ኢኮኖሚያዊ ልማትን ለማጎልበት አግባብ ያለው የፌዴራል ወይም የክልል
አካል በመሬት አጠቃቀም ዕቅድ ወይም በልማት ዕቅድ ወይም በመሠረተ
ልማት መሪ ፕላን መሠረት ለሕዝብ የተሻለ የጋራ ጥቅምና ዕድገት ያመጣል
ተብሎ የተወሰነው ነው፡፡
6. "የንብረት ካሣ" ማለት የመሬት ይዞታውን እንዲለቅ ለሚወሰንበት ባለይዞታ
በመሬቱ ላይ ለሰፈረው ንብረት በዓይነት ወይም በገንዘብ ወይም በሁለቱም
የሚከፈል ክፍያ ነው፡፡
7. "የመፈናቀያ ካሣ" ማለት ባለይዞታው የመሬት ይዞታውን ሲለቅ በመሬቱ ላይ
የመጠቀም መብቱ በመቋረጡ ምክንያት የሚደርስን ጉዳት ለማካካስ የሚከፈል
ክፍያ ነው፡፡
8. "መልሶ ማቋቋም" ማለት ለልማት ተብሎ በተወሰደው መሬት ምክንያት
የሚያገኙት ጥቅም ለሚቋረጥባቸው የልማት ተነሺዎች ዘላቂ የገቢ ምንጭ
እንዲኖራቸው የሚሰጥ /የሚደረግ / ድጋፍ ነው፡፡
9. "ቀመር" ማለት ለህዝብ ጥቅም በሚለቀቅ መሬት ላይ ለሠፈረ ንብረትና ለለማ
ቋሚ ንብረትና ሃብት ወጥ የሆነ የካሣ ስሌት የሚሰራበት ዘዴ ነው፡፡
10. "የማቋቋሚያ ፓኬጅ" ማለት ለህዝብ ጥቅም ሲባል ከመሬት ይዞታቸው
የሚነሱ ባለይዞታዎች ከንብረት ካሣ እና መፈናቀያ ካሣ በተጨማሪ
በአካባቢያቸው ከሚካሄደው ልማት ተጠቃሚ የሚሆኑበት እና ዘላቂ የሆነ የገቢ
ምንጭ ሊኖራቸው የሚያስችል አስፈላጊ የሆነ የመስሪያ ቦታ አቅርቦት፣
የገንዘብ፣ የሥልጠና እና የማማከር አገልግሎት ተሰጥቷቸው ወደ ስራ
የሚገቡበት እና ተጠቃሚ የሚሆኑበት ሁኔታ በፓኬጅ ተቀርጾ ተግባራዊ
የሚደረግበት ነው፡፡
11. "የጉዳት ደረጃ" ማለት የይዞታ መሬት፣ የለማ ቋሚ ንብረት ወይም ኑሮው
የተመሠረተበት የገቢ ምንጭ በተለያየ ደረጃ ለልማት ሲባል ይዞታውን
በመለቀቁ የሚደርስ ጉዳት ነው፡፡
4
12. “ማጨሻ ቦታ” ማለት ማንኛውም የገጠር መሬት ባለይዞታ በይዞታው ላይ
የመኖሪያ ቤት ሰርቶ በእርግጥም እየኖረበት ያለ ቦታ ነው፡፡
13. “ቢሮ” ማለት የአ.ብ.ክ.መ ገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ቢሮ ነው::
3. የተፈጻሚነት ወሰን
4. መርሆዎች
5
ክፍል ሁለት
6
በከተማው ወይም በወረዳ አስተዳደር ለሚገኜው የገጠር መሬት
አስተዳዳርና አጠቃቀም ተቋም ማቅረብ አለበት፡፡
2. የመሬት ይዞታቸውን እንዲለቁ ለሚደረጉ ባለይዞታዎች፣ በዚህ
መመሪያ መሠረት የሚከፈለው የንብረት እና የመፈናቀያ ካሣ በሌላ
አካል ካልተሸፈነ በስተቀር መሬት እንዲለቀቅለት የጠየቀው አካል
የመክፈል ግዴታ አለበት፡፡
3. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (2 እና 3) ከተገለጸው በተጨማሪ መሬት
እንዲለቀቀለት የጠየቀው አካል በቀጥታም ይሁን በተጓዳኝ የልማት
ተነሽዎችን በዘላቂነት የማቋቋምና ድጋፍ የማድረግ ግዴታ አለበት፡፡
7
4. ሕዝባዊና መንግስታዊ ተቋማትን፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎችን፣
የህዝብ አብያተ- መፃሕፍትን፣ የጥናትና ምርምር ማዕከላትን፤ የህብረት
ስራ ማህበራት አገልግሎቶችን ለማስፋፋት አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ፤
5. የውሃ ማስተላለፊያ መስመሮችንና የማጠራቀሚያ ጋኖችን፣ የፍሳሽ
ቆሻሻ ማስተላለፊያና ማሰወገጃ ቦዮችን፣ የኤሌክትሪክ መስመሮችንና
የማከፋፈያ ጣቢያዎችን፣ የመገናኛና ቴሌኮሙኒኬሽን አውታሮችን፣
ክልላዊና ብሄራዊ ፓርኮችን፣ ልዩ ልዩ ክበባትን፣ የህዝብ መናፈሻና
መዝናኛ ስፍራዎችን ለማዘጋጀት ወይም ለመገንባት ሲያስፈልግ፤
6. በገጠር የሚከናወኑ የግብርና ልማት ስራዎችን ማለትም የመስኖ
ቦዬችን፣ የማንጣፈፊያ ቦዮች እና መሰል የአገልግሎት መስጫ
መስመሮችን ለመገንባትና ለማሳለፍ ሲባል መሬቱን ነፃ ማድረግ
አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ፤
7. የመከላከያና የፖሊሰ አገልግሎት ማሰልጠኛ ተቋማትን ለመመሥረትና
አገልግሎታቸውን ለማስፋፋት መሬት ማስፈለጉ ሲታመንበት፤
8. በአገር አቀፍና በክልል ደረጃ የሚካሄዱ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን
ለማስፋፋት፤ የሠርቶ ማሣያ ጣቢያዎችን ማቋቋም ሲያስፈልግ፤
9. በተፈጥሮ ወይም በሰው ሰራሽ አደጋዎች እና በድንበር አከላለል ወይም
ሽግሽግ ምክንያቶች የሚፈናቀሉ ወገኖችን መልሶ ለማቋቋም መሬት
ማስፈለጉ ሲታወቅ፤
10. ለአካባቢ ደህንነት እንክብካቤ ሲባል፣ ከፕሮጀክቱ ክልል ውጭ ወደ
ምርት ተግባር እንዳይገባ የተከለለን ቦታ መጠበቅ ሲያስፈልግ፤
11. በክልሉ ውስጥ የኗሪውን ህብረተሰብ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት
የሚያፋጥኑ የልማት ተቋማትን ለማስፋፋት በቂ መሬት ሲያስፈልግ፤
12. ከባለይዞታው ቸልተኝነት ወይም ግዴለሽነት የተነሳ በተፈጥሮ ሃብት
ላይ አስከፊ ጉዳት በመድረሱ ይህንኑ ለመከላከል ይቻል ዘንድ
አካባቢውን ከልሎ መጠበቅ ሲያስፈልግ፤
8
13. አግባብ ባለው የመንግስት አካል በሚሰጥ ፍቃድ መሠረት የእምነትና
የአምልኮ ሥፍራን ለማሰናዳት መሬት ያስፈለገ እንደሆነ፤
14. የልማቱን ሥራ ለመደገፍ በገጠሩ አካባቢ በጥቅም ላይ ሊውሉ
የሚችሉ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን መገንባት አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ መሬት
ይለቀቃል፡፡
9. በቀበሌ ማዕከላት የመሬት ማስለቀቅ ስርዓት በሚከተለው መልኩ
ተደንግጓል፡፡
1. በገጠር የይዞታና የመጠቀም መብት የተሰጠው ማንኛውም ባለይዞታ
በቀበሌው ፕላን መሰረት ለልማት መሬት እንዲለቀቅ ሲጠየቅ
የመልቀቅ ግዴት አለበት፤
2. ለቀበሌ ማዕከላት፣ ለመንገድ መሰረተ ልማት ዝርጋታና ሌሎች የጋራ
መጠቀሚያ መሬት ማሰለቀቅን አስመልክቶ የሚከፈል ካሳ የሚሸፈነው
በቦታ ተረካቢዎች ይሆናል፤
3. በቀበሌ ማዕከላት ምክንያት የይዞታ መሬታቸዉ ለሚወሰድባቸዉ
ባለይዞታዎች በዚህ መመሪያ አንቀጽ 32 ንዑስ አንቀጽ (32.1) በተራ
ቁጥር 1 ከፊደል ሀ እስከ ረ በተጠቀሰው አግባብ በደረሰባቸው የጉዳት
መጠን መሰረት የመስሪያና የመኖሪያ ቦታ ይመቻችላቸዋል፤
4. መሬቱን የሚያስለቅቀው አካል የሽንሸና ስራ ከመከናወኑ በፊት
ተገቢውን ካሳ ለባለይዞታው ቅድሚያ መከፍል ይኖርበታል፤ ሆኖም
ከዚህ ውጭ የሚከናውን ማንኛውም የመሬት የማስለቀቅ ሂደት በህግ
ተጠያቂ ያደርጋል፡፡
10. በአገልግሎት መስመር ባለቤቶች የተዘረጉ መስመሮች እንዲነሱና መሬቱ
እንዲለቀቅ ስለማድረግ
1. መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ወይም የልማት ድርጅቶች
ንብረት የሆነ የአገልግሎት መስመር ያረፈበት መሬት የሚለቀቅ ሆኖ
ሲገኝ፣ መሬቱን የሚፈልገው አካል መስመሩ የሚገኝበትን ትክክለኛ
9
ሥፍራ በማመልከት ባለቤት ለሆነው አካል መስመሩ እንዲነሳ
ጥያቄውን በጽሁፍ ያቀርባል፤
2. የአገልግሎት መስመር ባለቤቶች በ30 ቀናት ጊዜ ውስጥ መስመሩን
ለመቀየር መከፈል ያለበትን ካሳ በማስላት የአገልግሎት መስመሩ
እንዲነሳ ለጠየቀው አካል ወይም ለአስፈፃሚ መስሪያ ቤቶች እና
ለከተማ ወይም ወረዳ አስተዳደር ማሳወቅ አለባቸው፤
3. የአገልግሎት መስመር ባለቤቶች ያቀረቡት የካሳ ክፍያ ጥያቄ
የአገልግሎት መስመሩ እንዲነሳ ለጠየቀው አካል ወይም ለአስፈፃሚ
መስሪያ ቤቶች በደረሰ በ30 ቀናት ጊዜ ውስጥ ካሣው ለመስመር
ባለቤቶቹ መከፈል ይኖርበታል፤
4. የአገልግሎት መስመር ባለቤቶቹም የካሳ ክፍያው በተፈፀመ በ60 ቀናት
ውስጥ መስመሩን በማንሳት መሬቱን ነፃ ያደርጋሉ፤
5. ከዚህ በላይ በተገለጸው የጊዜ ገደብ ውስጥ የአገልግሎት መስመሩ
ካልተነሣ፣ መሬቱን ነጻ ባለመደረጉ በፕሮጀክት ባለቤቶች ወይም
በአስፈፃሚ መስሪያ ቤቶች ላይ ለሚደርስ ጉዳት መስመሩን ማንሣት
የነበረባቸው ወገኖች የዕዳ ተጠያቂዎች ናቸው።
11. በሕዝብ ጥቅም ወይም አገልግሎት ሥም ስለማይለቀቁ ይዞታዎች
10
2. በቱሪዝምና በተፈጥሮ መስህብነት የሚታወቁ ሥፍራዎችና እነዚህኑ
ለመጠበቅ የተከለለ መሬት፤
3. ለአካባቢ ጥበቃና ለብዝሃ ሕይወት እንክብካቤ ማለትም አእዋፋትን፣
የዱር እንሰሳትንና የተፈጥሮ ተክሎችን ዝርያ ለመጠበቅ ሲባል
በጥብቅነት የሚታወቁ መሬቶች፤
4. ብሔራዊ ወይም ህዝባዊ ፓርኮችና የስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራዎች፤
5. በፌደራልና በክልል ደረጃ ለተለያዩ የምርምር አገልግሎቶች የተከለሉ
መሬቶች፤
6. በዚሁ አንቀጽ ከንዑስ አንቀጽ (1) እስከ (5) የተደነገገው እንደተጠበቀ
ሆኖ እነዚሁን ይዞታዎች ለመጠቀም እና ለአካባቢው ህብረተሰብ
ለሚከናወኑ የመንገድ፣ የስልክ፣ የውኃና የመብራት መሰረተ ልማቶችን
ለመዘርጋት መሬት ሲያስፈለግ ጉዳት በማያደርስ መልኩ መሬት
ሊለቀቅ ይቻላል፡፡
12. ለህዝብ ጥቅም ሲባል የመሬት ይዞታቸውን ስለሚለቁ ባለይዞታዎች
ተሳትፎ አስፈላጊነት
1. የንብረት ገማች ባለሙያዎች ቡድን በቀበሌው ተገኝቶ አግባብ ባለው
የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ኮሚቴ በመታገዝ የባለይዞታውንና
በመሬቱ ላይ ያለማውን ንብረት መረጃ በሚያሰባስቡበት ወቅት
ባለይዞታው በግንባር ተገኝቶ በስራው የመሣተፍና መረጃውን
የመስጠት ግዴታ አለበት፡፡
2. መረጃዎችን በማሰባሰብ ሂደት በመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም
ኮሚቴውና በንብረት ገማች ቡድን አባላቱ ቸልተኝነት ምክንያት
ትክክለኛ ባለይዞታውን ወይም ባለይዞታዎችን የመለዬት ችግር
እንዳይከሰት ብርቱ ጥንቃቄ መደረግ ይኖርበታል፡፡
3. ይዞታውን የመለካቱና የንብረት ቆጠራውም ሆነ ምዝገባው ተግባር
እንደተጠናቀቀ ዝርዝሩ በሰፈረበት ቅጽ ላይ ባለይዞታዎቹና የንብረት
11
ገማች ባለሙያዎች የስምምነት ፊርማቸውን ወይም የጣት አሻራቸውን
በንብረት መተማማኛ ሰነዱ እንዲያሳርፉ ይደረጋል፡፡
4. ማንኛውም ባለይዞታ መሬት የመለካቱና የለማ ንብረት ቆጠራ ሥራው
ከተጠናቀቀና መተማማኛ ከፈረመ በኋላ የመረጃ ይስተካከልልኝ ጥያቄ
ሊያቀርብ አይችልም፡፡ ሆኖም ይህ ድንጋጌ በዚህ መመሪያ መሠረት
የተጠበቁትን ቅሬታ ወይም ይግባኝ የማቅረብ መብቶቹን የሚከለክል
አይሆንም።
5. የይዞታ መሬቱ ሲለካና በመሬት ላይ ያለማው ንብረት ተቆጥሮ ለዚሁ
የሚያስፈልገው መረጃ ሲያዝ እንዲገኝ ጥሪው በአግባቡ ደርሶት በአካል
ለመገኜት ፈቃደኛ ያልሆነ ባለይዞታ፣ የመሬት መለካቱና ንብረት
ቆጠራው ወይም የምዝገባ ስራው በሌለበት ይካሄድ ዘንድ ሙሉ በሙሉ
እንደተስማማ ይቆጠራል፡፡
6. በግል ይዞታ የጋራ የመጠቀም መብት ያላቸው በመሬቱ ላይ የለማ
ንብረት መረጃ፣ ሁሉም ባለይዞታዎች ወይም ተጠቃሚዎች እና የወል
መሬት መረጃ ደግሞ በወል መሬት አስተዳዳር ኮሚቴዎች ወይም
ይኼው የሚገኝበት የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ኮሚቴ አባላት
በተገኙበት ይረጋገጣል፡፡
12
ክፍል ሦስት
13
ሀ. በ3 ወር ጊዜ ውስጥ ተገቢው ካሣ ካልተከፈለው በመሬቱ ላይ ከቋሚ
ተክልና ግንባታ በስተቀር ሌሎች ሥራዎችን ከመስራት መከልከል
የለበትም፤
ለ. በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ተገቢው ካሣ ካልተከፈለው በመሬቱ ላይ የመሬት
አጠቃቀም ዕቅዱን መሰረት አድርጎ ማንኛውንም ሥራ ከመስራት
መከልከል የለበትም፡፡
4. የማስለቀቂያ ትዕዛዝ የደረሰው ባለይዞታ ትዕዛዙ በደረሰው በ10 የሥራ ቀናት
ውስጥ ካሣ እና ምትክ ቦታ ወይም መስሪያ ቦታ መውሰድ አለበት፤
5. የማስለቀቂያ ትዕዛዝ የደረሰው ባለይዞታ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (3)
መሠረት በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ የካሣ ክፍያውን ካልወሰደ በከተማው
ወይም በወረዳው አስተዳደር ስም በሚከፈት ዝግ የባንክ ሂሳብ ገንዘቡ
እንዲቀመጥለት ይደረጋል፤
6. ለባለይዞታ የሚሰጠው የመልቀቂያ የጊዜ ገደብ ካሣና ምትክ ከተቀበለ ወይም
ካሣው በዝግ ሂሳብ ከተቀመጠበት ቀን ጀምሮ ከ90 ቀን ያነሰ መሆን
የለበትም፤
7. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (5) የተደነገገው ቢኖርም በሚለቀቀው መሬት ላይ
ሰብል፣ ቋሚ ተክል ወይም ሌላ ንብረት ከሌለ ባለይዞታው የመፈናቀያ ካሣ
ከተከፈለው በኋላ በ30 ቀናት ውስጥ ይዞታውን ለወረዳው ወይም ለከተማው
አስተዳደር ማስረከብ አለበት፤
8. በሕገ-ወጥ መንገድ በተያዘ ቦታ ላይ ለሰፈረ /ለተፈራ/ ንብረት ካሣ መክፈል
ሳያስፈልግ ለሰባት የሥራ ቀናት የሚቆይ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ በመስጠት
ወይም በቦታው በሰፈረው ንብረት ላይ በመለጠፍ እንዲለቀቅ ይደረጋል፤
9. የማስለቀቂያ ትዕዛዝ የደረሰው ባለይዞታ ወይም ባለንብረት በዚህ አንቀጽ
ንዑስ አንቀጽ (5) እና (6) በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ያለ በቂ ምክንያት
ይዞታውን ካላስረከበ የከተማው ወይም የወረዳው አስተዳደር መሬቱን
ለመረከብ የፖሊስ ኃይል መጠቀም ይችላል፤
14
10. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (9) መሰረት በፖሊስ ኃይል እንዲለቅ የተደረገ
ባለይዞታ ግንባታ፣ በህግ አስገዳጅነት እንዲፈርስ የተደረገ እንደሆነ ግንባታውን
ለማፍረሰ የወጣውን ወጪ ባለይዞታው እንዲሸፍን ወይም ባለይዞታው
ከሚከፈለው የካሳ መጠን ላይ እንዲቀነስ ሊወሰን ይችላል፤
11. ማንኛውም ባለይዞታ በመሬቱ ላይ ያለውን የዛፍ ተክል ቆርጦ ለማንሳት
ፈቃደኛ ካልሆነ ለባለይዞታው የተወሰነው ካሳ ተከፍሎት ዛፉን መቁረጥ
አስፈላጊ ከሆነ በጨረታ እንዲሸጥ ተደርጎ ገንዝቡ በከተማ ወይም በወረዳ
ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ተቋም በኩል ገቢ እንዲሆን ይደረጋል፡፡
14. ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የሚለቀቁ መሬቶችን ስለ ማሳወቅና የለማ ንብረት
ቆጠራ ጥሪን ስለማስተላለፍ
1. በፌደራልም ሆነ በክልልም ደረጃ የሚቀርቡ የመሬት ማስለቀቅ ጥያቄዎችን
አስመልክቶ ጉዳዩ የሚመለከተው አካል ወይም የልማት ፕሮጀክቱ ባለቤት
ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የሚፈለገውን መሬት ለማስለቀቅ እንዲቻል የይዞታውን
ስፋት፣ መሬቱ የሚገኝበትን ትክክለኛ ስፍራ፣ መሬቱ የተመረጠበትን አግባብና
ሌላ አማራጭ አለመኖሩን ከሚያብራራ መግለጫ ጋር መረጃዎችን በካርታ
በማስደገፍ በመሬቱ ላይ የታቀደው ስራ ከመጀመሩ ቢያንስ ከአንድ ዓመት
በፊት ለቢሮው ወይም ለተዋረድ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም
ተቋም እንዲታወቅ ማድረግ ይኖርበታል፤
2. በተዋረድ የሚገኘው የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ተቋም የቀረበውን
ጥያቄ መነሻ በማድረግ ንብረቶቹ እንዲነሱና መሬቱ እንዲለቀቅ
ለባለይዞታዎቹ ያሳውቅ ዘንድ በመሬቱ ላይ የታቀደው የልማት ስራ
ከመጀመሩ ቢያንስ ከ3 ወራት በፊት የወረዳ ወይም የከተማ አስተዳደር
እንዲያውቀው ያደርጋሉ፤
3. ለህዝብ ጥቅም ሲባል የሚለቀቁ መሬቶች አካባቢ ለሚገኘው ህብረተሰብ
ስለታሰበዉ ልማት፣ ስለሚለቀቁት መሬቶች ስፋት፣ መሬቱ ስለተመረጠበት
አግባብና ስለ አጠቃላይ አፈጻጸሙ በቂ ግንዛቤ እንዲኖረው በቅድሚያ
መደረግ ይኖርበታል፤
15
4. የሚፈለገው መሬት ለህዝብ ጥቅም መሆኑን የተወሰነበትንና የማስለቀቂያ
ትእዛዝ የከተማ ወይም የወረዳው አስተዳደር አግባብ ላለው የገጠር መሬት
አስተዳደርና አጠቃቀም ተቋም መላክ አለበት፤
5. የገጠር መሬት አስተዳዳርና አጠቃቀም ተቋም ለህዝብ ጥቅም ሲባል የመሬት
ይዞታ የሚለቀቅበትንና የንብረት ካሳ የሚከፈልበትን ሁኔታ አስመልክቶ
ለልማት የተፈለገውን መሬት ስፋት፤
6. በካርታ በማስደገፍ፣ መሬቱ የሚለቀቅበትንና ንብረቶቹ የሚነሱበትን ጊዜ፣
ሊከፈለው የሚገባውን ካሳ፣ ምትክ መሬት ስለመኖሩ ወይም ስለ አለመኖሩና
ስለ ቅሬታና ይግባኝ አቀራረብ በማብራራት ለባለይዞታው ከ90 ቀናት በፊት
በቅድሚያ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የመስጠት ኃላፊነት አለበት፤
7. መሬቱ በወረዳ ወይም በከተማው አስተዳደር ወይም በህብረተሰቡ አነሳሽነትና
ጥያቄ እንዲለቀቅ የሚያስፈልግና ካሳ ከፋዩም ወይም ትክ መሬት የሚሰጠው
ህብረተሰቡ ራሱ ሆኖ በሚገኝበት ጊዜ፣ መሬቱ የሚገኝበት ቀበሌ ህዝብ በጉዳዩ
ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ማሳለፉ የግድ ሲሆን ይኸው ለወረዳ ወይም ለከተማ
አስተዳደር ምክር ቤት ቀርቦ ካልፀደቀ ተፈፃሚ አይሆንም፤
8. ማንኛውም ባለይዞታ ለህዝብ ጥቅም መሬቱን እንዲለቅ ውሳኔ የተሰጠበት
እንደሆነ መሬቱ በሚለካበትና የለማ ንብረቱ በሚቆጠርበት ወቅት ይህንኑ
በቦታው ተገኝቶ እንዲያስለካ፣ እንዲያስቆጥርና መተማመኛ እንዲፈርም
በአካል ሊነገረው ወይም በጽሁፍ ማስታወቂያ ወይም በግል ለባለይዞታውና
ለቤተሰቡ አባላት በሚደርስ ደብዳቤ መልእክቱ እንዲደርሰው ይደረጋል፤
9. በንብረት ቆጠራ ወቅት የምንጠቀመው የመሬት ልኬታ መረጃ ከእጅ
ጅ.ፒ.ኤስ ውጭ ባሉ የተሻሻሉ የቅየሳ መሳሪያዎች ተለክቶ የሚገኝ መረጃን
መሆን ይኖርበታል፡፡
15. ለካሳ ትመና አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን ስለማሰባሰብ፤
1. በዚህ መመሪያ መሰረት የንብረት ገማች ባለሙያዎች ለንብረት ግመታ
ስራው የሚሰበስቧቸው የመሬት ልኬታና የመሬት ሃብት መረጃዎች ከዚህ
በታች የተመለከቱትን ዝርዝሮች ሊይዙ ይገባል፡፡
16
ሀ. የመሬቱ ባለይዞታ/ዎች ሙሉ ስም /ከነ አያት/ እና የመኖሪያ
አድራሻ፤
ለ.የባለይዞታው የይዞታ/ተጠቃሚነት ማረጋገጫ ማስረጃዎች ማለትም
የይዞታ መሬቱ መለያ ቁጥር፣ የይዞታው ስፋት፣መሬቱ የሚገኝበት ልዩ
ስፍራ ወይም አዋሳኞቹ እና ከይዞታው የሚቀነሰው መሬት በሄ/ር
የማሳ ካርታ የሚያመለክት መረጃዎች መሟላት ይኖርባቸዋል።
2. በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀጽ (1) ሥር የተገለጹትን መረጃዎች ለማሟላት
ሲባል የመሬት ይዞታ ምዝገባና ቋሚ የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር የመስጠት
ስራ የመረጃ ማሰባሰቡ ስራ ከመጀመሩ በፊት መጠናቀቅ አለበት፡፡
3. የባለይዞታው የመሬት አጠቃቀም አይነት ማለትም ለግጦሽ፣ ለመስኖ፣
ለአመታዊ ሰብል፣ ለቋሚ ተክል፣ ለደን ልማት፣ ለአግሮ ፎረስትሪ ልማት፣
ለመኖሪያ ቤትና የጓሮ መሬት መሆን አለመሆኑ መረጃው ተለይቶና
ተዳረጅቶ መያዝ አለበት፤
4. በመኸር፣ በበልግ ወይም በቀሪ ዕርጥበት የሚለማ መሬት ስፋት፣ ለአለፉት
አምስት ዓመታት መሬቱ በሚወሰድበት አካባቢ የተዘሩ እስከ ሶስት
በሚደረሱ ዋና ዋና ሰፊ ሽፋን ያላቸው ሰብሎች በሰብል ፈረቃነት የሚዘሩ
በአይነት የቅርብ አምስት ዓመታት ምርታማነትና የወቅቱ የገቢያ ዋጋ
በኩንታል ተሰልቶ መታወቅ አለበት፤
5. የሚለማ መሬት በመኸር፣ በበልግና በቀሪ ዕርጥበት፣ በመስኖ የሚያመርት
ወይም የጓሮ መሬት ከመሆኑ የተነሣ የሰብል ፈረቃው የሚለያይ ከሆነ
ይኸው ተለይቶ በስሌቱ ውስጥ ታሣቢ መደረግ ይኖርበታል፤
6. ይዞታው በመስኖ የሚለማ የእርሻ መሬት ሲሆን የዚሁ ስፋት፣ ለአለፉት
አምስት ዓመታት የተዘሩ ዋና ዋና በፈረቃ የሚዘሩ ሰብሎች አይነት፣
የየዓመቱ የምርት ድግግሞሽ /በየሰብል አይነቱ/፣ የቅርብ አምስት ዓመታት
ምርታማነትና የወቅቱ የገቢያ ዋጋ በኩንታል መሰላት ይኖርበታል፤
7. የሰብል ወይም ቋሚ ተክሉ ምርታማነት ከአምስት ዓመት ላነሰ ጊዜ የተገኘ
ከሆነ በእነዚሁ ዓመታት በተገኘው ምርታማነት መሰረት ተደርጎ ይሰራል፤
17
8. የሰብል ወይም ቋሚ ተክል የሚመረትበት ወይም የተተከለበት መሬት ምርት
መስጠት ያልጀመረ ከሆነ ሰብልን በተመለከተ በአካባቢው ባለው ተመሳሳይ
የይዞታ መጠን ከተመሳሳይ ሰብል፤ የቋሚ ተክል ማፈናቃያ ካሳው
የሚሰላው በአባባና ፍሬ በመጥለፍ ደረጃ ላይ ሁኖ ሲገኝ ከሚመለከተው
የግብርና ተቋም ተጣርቶ በሚገኝ መረጃ መሰረት እያንዳንዱ በቋሚ ተክል
አግር ተቆጥሮ ሊያስገኝ በሚችለው የሚችለው ምርት በወቅቱ የገቢያ ዋጋ
ተስልቶ ካሳው የሚሰላ ይሆናል፤
9. አካባቢውን የሚወክል የአለፉት አምስት ዓመታት ምርታማነት መሬቱ
በሚወሰድበት አካባቢ በሚገኘው የቀበሌ ግብርና ልማት ጽ/ቤቶች
የሚሰሰሰብ ሁኖ መረጃው በወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ተረጋገጦ የሚቀረብ
ይሆናል፤ ነግር ግን የምርታማነት መረጃው በማይኖርበትና አጠራጣሪ ሁኖ
ሲገኝ የመሬቱን ለምነት፣ ተዳፋትነት፣ የአፈር አይነት፣ የመሬት ገጽታና፣
የዝናብ ሁኔታን ባገናዘበ መልኩ በተቋሙ በሚገኘው የመሬት አጠቃቀም
ቡድንና በወረዳው ግብርና ጽ/ቤት በጋራ ተረጋግጦ በሚቀርብ መረጃ
የግመታ ስራው ይከናወናል፤
10. የግጦሽ መሬት ያለ እንደሆነ የዚሁ ስፋት፤ በአካባቢው ለአለፉት ሶስት
ዓመታት በድርቆሽ መሬቶች የተገኘ ድርቆሽ መጠን በሸክም ወይም ሌሎች
ለመኖ ልማት ሊውሉ የሚችሉ ቋሚ እፅዋት ለምሳሌ እንደ ሳስፓኒያ፣
ሉኪኒያ፣ የዝሆኔ ሳር ወ.ዘ.ተ የመሳሰሉ ቅጠላቸው ቢቆረጥ ሊገኝ የሚችል
የመኖ ምርት በሸክም ብዛትና የወቅቱ የአንድ ሸክም የድርቆሽ ወይም
የሌሎች የመኖ ተክሎች የገበያ ዋጋ በስሌቱ ውስጥ ገብቶ ይታሰባል፤
11. በይዞታ መሬት ላይ ወጥ በሆነ መልኩ የተተከለና የለማ የዛፍ አይነት
በሚኖርበት ጊዜ የዛፉ ቁጥር የሚወሰነው አግባብ ባለው የግብርና ጽ/ቤት
በሚሰጥና በሳይንሳዊ መንገድ በአንድ ሄ/ር መሬት ላይ ተተክሎ ሊለማ
የሚችለውን የዛፍ ብዛት ከዕድገት ደረጃ፣ ቁመትና ውፍረት ጋር ባገናዘበ
መልኩ ይሆናል፤
18
12. በመሬቱ ላይ ያለ ተፈጥሯዊ የዛፍ አይነት፣ ብዛትና የእድገት ደረጃ የታወቀ
እንደሆነ ይህም በስሌቱ ውስጥ የሚገባ ይሆናል፤
13. በይዞታ መሬቱ ላይ የለማው ቋሚ ተክልና የአግሮ ፎረስትሪ ልማት ሲሆን
ፍሬ መስጠት ያልጀመረ ቋሚ ተክል ከሆነ አንድን ቋሚ ተክል ለማሳደግ
የወጣው ግብዓት፣ ጉልበትና ሌሎች አስፈላጊ ወጪዎች አግባብ ባለው
የግብርና ጽ/ቤት በሚሰጥና በሳይንሳዊ መንገድ በአንድ ሄ/ር መሬት ላይ
ተተክሎ ሊለማ የሚችለውን ተወስዶ የሚገመት ይሆናል፤ ነገር ግን
ካሳይንሳዊ አሰራር ውጭ የተሻለ ካሳ እንዳገኝ በሚል ለተተከለ ቋሚ
ተክልም ሆነ የባህር ዛፍ ዝርያ በአንድ እግር በተቆጠረ ቆጠራ ካሳ
አይገመትም፤ ቋሚ ማፈናቀያ ካሳም አይሰራለትም፤
14. መሬቱ በቋሚነት የሚለቀቅ ሆኖ ፍሬ መስጠት የጀመረ ቋሚ ተክል ሲሆን
በግንባር በአንድ ቋሚ ተክል የሚገኝ አማካይ ምርታማነትን መሰረት
በማድረግ ያስገኘው ገቢ በታሣቢነት ይወሰዳል።
15. በአገልግሎት ላይ ያሉ ባአጥጋቢ ሁኔታ የሚገኙ የአፈርና ውሃ ጥበቃ
ስራዎች ማለትም እርከኖች፣ ክትሮች፣ የውሃ ማፋሰሻ ቦዮች፣ ለውሃ ልማትና
ማሰባሰቢያ የተሰሩ የማጠራቀሚያ ኩሬዎች፣ ጉድጓዶችና መሰል ስራዎች እ
16. ርዝመት፣ ብዛት፣ ስፋትና ደረጃም በዋጋ ስሌቱ የሚካተት ይሆናል።
17. በጊዘያዊነትም ሆነ በቋሚነት የሚለቀቅው መሬት ላይ ለባለይዞታው ጥቅም
የሚሰጥ በተለያየ ወይም በተመሳሳይ ደረጃ ባህር ዛፍ የተተከለበትን
አስመልክቶ መሬቱ ለልማት ተፍለጎ ሲወስድ፣ በንብረት ቆጠራ ወቅት
በግንባር ባህር ዛፉ ተቆርጦ ሲገኝ፣ ቀሪ ጉቶው በማቆጥቆጥ ደረጃ ከሆነና
ባህር ዛፉ ተመልሶ ጥቅም እንደሚሰጥ ከቀበሌ ግብርና ጽ/ቤት ማረጋጋጫ
በጹሁፍ ሲቀርብ ቀደም ብሎ በተለያየ ደረጃ በአስገኜው የምርት ዓይነት
በወቅቱ ዋጋ ተባዝቶ የማፈናቃያ ካሳ ይሰራለታል፤ ነገር ግን ተመልሶ
ለማያቆጠቁጥ የባህር ዛፍ ጉቶ ካሳ አይከፈለም፡፡
18. የወቅቱ የገበያ ዋጋ በሚሰላበት ወቅት አካባቢውን በትክክል የሚወክል
መረጃ ያልተገኜ እንደሆነ የሚገመተው ምርት፣ ቋሚ የመሬት ማሻሻያ
19
ወይም ቋሚ ንብረት በሚሸጥበት ወይም ልውውጥ በሚካሄድበት አቅራቢያ
ያለውን የገቢያ ዋጋ ቀረቤታ፣ የአካባቢው የህዝብ ብዛትና የኢኮኖሚ
ሁኔታዎችን ወ.ዘ.ተ አገናዝቦና ተጠንቶ መሠራት ይኖርበታል፤
19. እያንዳንዱን ልማታዊ ተግባር ለማከናወን የወጣ የገንዘብና የጉልበት ወጪ
እንዲሁም የፈጀው ጊዜና ማቴርያል፣ አሁን ያለበት ደረጃ በአዲስ መልኩ
ለማደስ የሚያስፈልገው ተጨማሪ ቁሣቁስና ሰብአዊ ግብዓት በወቅቱ
የሚጠይቀው የገበያ ዋጋ በስሌቱ ውስጥ መካተት ይኖርበታል፤
20. መኖሪያ ቤቶች፣ የእህል መጋዘኖች፣ የእንሰሳት መጠለያዎችና ሌሎች
ግንባታዎች ከተሰሩበት ስፋት፣ የጥሬ እቃ አይነትና ብዛት ጋር የወቅቱን
የገቢያ ዋጋ መሰረት በማድረግ መገመት አለባቸዉ፤
21. መረጃዎቹ ተሰብስበው እንደተጠናቀቁ ዝርዝራቸውን የያዘው መግለጫ
በባለይዞታው ወይም የባለይዞታዎቹ ወይም ህጋዊ ወኪላቸውና የገማች
ባለሙያ አባላት ሙሉ ስም፣ ፊርማና በቀበሌው ገጠር መሬት አስተዳደርና
አጠቃቀም ማህተም መረጋገጥ ይኖርበታል፤
22. የግንባታዎች የጥሬ እቃ ፍጆታና የወቅቱ የገበያ ዋጋ ዝርዝር አግባብነት
ካላቸው የተቋሙ ባለሙያዎች ወይም ከሌሎች አስፈፃሚ ተቋማት
መሠብሰብ ይኖርበታል፤
23. ልዩ ግመታ የሚፈልጉትን ግንባታዎች የግብዓት ፍላጎትና የወቅቱን የገበያ
ዋጋ የሚያሳየውን ዝርዝር ከአገልግሎቱ ዘርፍ ባለቤቶችና ከሚመለከታቸው
ተቋማት ተጠይቆ የሚገኝ ይሆናል፤
24. ለተለያዩ ሰራዎች የሚያሰፈልገው እለታዊ የሰው ጉልበት ዋጋ አመልካች
መረጃ በወቅቱ መሠብሰብ ይኖርበታል።
16. የካሣ ግመታ ስለማካሄድ
1. ለህዝብ ጥቅም ሲባል ህጋዊ የመሬት ይዞታ በሚለቀቅበት ጊዜ የሚከፈለው
የካሳ ክፍያ፦
21
ሊረከቡት ፈቃደኛ ካልሆኑ ካሳው ከተለቀቀው ይዞታ ንብረት ግምት ጋር
ተዳምሮ እንዲከፈልና ይዞታው በጋራ ሃብትነት እንዲያገለግል ይደረጋል፤
6. ለህዝብ ጥቅም ሲባል ከሚለቀቀው መሬት ጋር ሲወዳደር በስፋቱ፣
በምርታማነቱ እና ከመኖሪያ ቤቱ ባለው ርቀት ተመጣጣኝ የሆነና በቀላሉ
ታርሶ ምርት ሊያሰገኝ የሚችል ትክ መሬት የሚሰጠው መሆኑ በከተማ
ወይም በወረዳው አስተዳደር እና አግባብ ባለው የገጠር/መ/አስ/አጠ/ተቋም
በኩል የተረጋገጠለት ማንኛውም ባለይዞታ፣ መሬቱ ለአንድ ዓመት
የሚያስገኘውን አማካይ ዓመታዊ ገቢ ወይም የቅርብ አምስት ዓመታት
አማካይ ምርታማነት በወቅቱ የገቢያ ዋጋ ተሠልቶ የመፈናቀያ ካሳ
እንዲያገኝ ይደረጋል፡፡ ትክ መሬት ካለ ወይም ከተገኘ በቀዳሚነት
የሚሰጠው መሬታቸውን በቋሚነት ለሚለቁ ባለይዞታዎች ይሆናል፤
7. በግል ይዞታ መሬት ላይ በጽሁፍ በተደረገና የኪራይ ውል ለመመዝገብ
ስልጣን ባለው አካል የተመዘገበ የኪራይ መሬት ሌላ አማራጭ መሬት
ባለመኖሩ የውለታ ዘመኑ ከማብቃቱ በፊት ለህዝብ አገልግሎት እንዲለቀቅ
የተደረገ እንደሆነ፣ ካሣው ለመሬቱ ባለይዞታ ይከፈለዋል፡፡ መሬቱን
ያከራየው ሰው ለተከራዩ በጽሁፍ በተገለጸው የኪራይ ውል መሰረት
በቅድሚያ ለተከፈለ የቀሪ የኪራይ ዘመን ብቻ በካሣ ከተገኘው ገንዘብ
ተሰልቶ ይከፈለዋል፡፡ በጽሁፍ በተደረገው ውል መሰረት ከተደረገው የኪራይ
ውል ዘመን በላይ የሚከፈለውን የመፈናቀያ ካሳ በስሌቱ መሰረት ቋሚ
ባለይዞታው እንዲያገኝ ይደረጋል፡፡ ሆኖም በጽሁፍ ላልተደረገና
ላልተመዘገበ የኪራይ ውል ካሳው የሚከፈለው ለባለይዞታው ብቻ ይሆናል፤
8. በሊዝ የተሰጠ መሬት የውሉ ዘመን ከማብቃቱ በፊት ሊለቀቅ የሚችለው፣
መንግሥት ላፀደቃቸው የልማት ፕሮግራሞች ማስፈፀሚያነት በወረዳ ወይም
በከተማ አስተዳደር ውሳኔ ሲታመንበት በመሬቱ ላይ ላፈራው ቋሚ ንብረት
ለሊዝ ባለመብቱ ከሚከፈለው ካሳ በተጨማሪ ያልተጠቀመበት የሊዝ ክፍያ
ካለው ተመላሽ ይደረግለታል፤ ነግር ግን የቋሚ የማፈናቀያ ካሳ
አይከፈለውም፤
22
9. ለህዝብ ጥቅም ሲባል በሚለቀቀው መሬት ላይ የሚገኝ የሙታን መካነ
መቃብር የፈረሰ እንደሆነ ለዚሁ የሚከፈለው ካሳ መካነ መቃብሩን
ለማንሳት፣ ተለዋጭ የማረፊያ ቦታ ለማዘጋጀት፣ አጽሙን ለማዛወርና
ለማሳረፍ እንዲሁም ከዚሁ ጋር ተያይዞ ለሚደረግ ሃይማኖታዊና ባህላዊ
ስርዓት ማስፈፀሚያ የሚያስፈልጉትን ወጪዎች ያጠቃልላል፡፡ ለተጠቀሱት
ወጪዎች በወቅቱ የገቢያ ዋጋ መሰረት የአካባቢውን የእቃ፣ የትራንስፖርት
አገልግሎትና የሰው ጉልበት ግምት ውስጥ እንዲገባ ይደረጋል፡፡
23
8. በግጦሽ መሬት ላይ የሚገኝ ሳር፣ የመኖ ዛፎችና ከንብረቶቹ ጋር
ተመሳሳይነት ያላቸው የማይንቀሳቀሱ ቋሚ ንብረቶች ወይም የተደረጉ
ማሻሻያዎች፡፡
24
መብታቸውን በህግ ሲያጡ፣ በመሬት ላይ ላፈሩትና አንስተው
ለማይወስዷቸው ቋሚ ንብረቶች ተገቢው የንብረት ካሳ በህጉ መሰረት
መሬቱን በሚረከበው አካል ክፍያ ይፈጽማል፡፡ መሬቱን የሚረከበው አካል
መክፈል የማይችል ከሆነ ወይም ፈቃደኛ ካልሆነ መክፈል ለሚችል አካል
መሬቱ ይተላለፋል/ይሰጣል/፡፡
20. መሬቱን በራሱ ፍላጎት /በፈቃደኝነት/ ለሚለቅ ባለይዞታ ስለሚከፈል ካሳ
1. ማንኛውም ባለይዞታ የመሬት ይዞታ መብቱን በራሱ ፈቃድ መተውን
በፈቃደኝነት የለቀቀው መሬት የሚገኝበትን ልዩ ሥፍራ፣ መጠኑን
ከነአዋሳኞቹ ለቀበሌው መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ኮሚቴ ከ6 ወራት
በፊት በማመልከትና ከመቼ ጀምሮ መሬቱን እንደሚለቅ በጽሁፍ አስታውቆ
መልቀቅ ይችላል፤
25
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ(1) መሰረት ሁሉም ባለይዞታዎች የመተላለፊያ
አገልግሎቱ እኩል ተጠቃሚዎች ከሆኑና የጋራ መገልገያ ከመሆኑ የተነሣ
የሁሉንም የይዞታ መሬት የሚነካ ከሆነ በዚህ መመሪያ መሠረት የሚከፈል
ካሳ አይኖርም፡፡ ይልቁንም የተዘረጋው መተላለፊያ መስመር
የሚያስከትለውን ወጭ እንደ አጠቃቀማቸው ይጋራሉ፤
3. የመተላለፊያ መሬት አጠቃቀምን በሚመለከት በቀጥታ በተጠቃሚዎችና
በመሬቱ ባለይዞታዎች መካከል የጋራ ስምምነት ሊደረግ ይችላል፡፡
ስምምነቱም ለቀበሌው መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ጽ/ቤት ቀርቦ
ይመዘገባል፤
4. ከዚህ በላይ የሠፈሩት ድንጋጌዎች ተፈፃሚነት የሚኖራቸው ይህ መመሪያ
በሥራ ላይ ከዋለ በኋላ አዲስ በሚገነቡ ወይም በሚዘረጉ የመተላለፊ
መስመሮች ላይ ይሆናል።
22. መሬትን ኩታ ገጠም በማድረግ ሂደት ስለሚከፈል ካሳ
1. ማሳን ለማቀራረብ ሲባል የመሬት ልውውጥ በሚደረግበት ወቅት አንዱ ማሳ
ከሌላው ማሳ በመብለጡ ምክንያት ወይም በመሬቱ ላይ የለማን ንብረት
ማካካስ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ከፍተኛውን የመሬት ይዞታ የሚረከበው ሰው
በመሬቱ ላይ የለማ ንብረት ወይም ተጨማሪ መሬት ለነበረው ባለይዞታ በዚህ
መመሪያ መሠረት ተመጣጣኝ ካሣ ይከፍለዋል፡፡
26
3. ቋሚ ንብረት ያለበት መሬት የደረሰው አርሶ አደር በመሬቱ ላይ ለለማው
ቋሚ ንብረት የሚከፍለውን ካሳ በአንድ ጊዜና በቅድሚያ ለመክፈል አቅም
የሌለው ሆኖ የተገኘ እንደሆነ ይህንኑ ገልጾ ለወረዳዉ የመሬት አስተዳደርና
አጠቃቀም ጽ/ቤት በጽሑፍ ማመልከት አለበት፡፡ በዚህም መሰረት፡-
ሰ. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (26.1.1) ከፊደል ተራ ቁጥር “ሀ” እስከ “ረ”
የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ የቤት፣ የመጋዘን፣ የመጠለያና ሌሎች
ግንባታዎች ካሳ ግመታ አሰራር ቀመር= የወቅቱ የግንባታ ወጪ
(የማቴርያል + የጉልበት + የገንዘብ ወጪ) + በመሬት ላይ የተደረገ ቋሚ
ማሻሻያ (ምንጣሮ + መሬት ማስተካከል + ድንጋይ ለቀማ + ሌሎች
የመሬት ልማት ሥራዎች) ወጪ + የቀሪ ዘመን የመሬት ሊዝ ተመላሽ
ክፍያ ቢኖር፣
29
26.1.2. የአጥር፣ የእንሰሳት በረት ወይም ጉረኖ ስራዎች ካሣ አተማመን
30
መ. የመኸር የሰብል አብቃይ ካሳ = [የመኸር መሬት ስፋት በሄ/ር x በአንድ
ሄ/ር መሬት የሚገኝ ምርት በኩንታል x የሰብሉ የወቅቱ የገቢያ ዋጋ ብር
በኩንታል] + የመሬት ቋሚ ማሻሻያ ወጪ
ሠ. የበልግ የሰብል አብቃይ ካሳ = [የበልግ መሬት ስፋት በሄ/ር x በአንድ ሄ/ር
መሬት የሚገኝ ምርት በኩንታል x የሰብሉ የወቅቱ የገቢያ ዋጋ ብር
በኩንታል] + የመሬት ቋሚ ማሻሻያ ወጪ
ረ. የቀሪ ዕርጥበት የሰብል አብቃይ ካሳ = [የቀሪ ዕርጥበት መሬት ስፋት በሄ/ር
x በአንድ ሄ/ር መሬት የሚገኝ ምርት በኩንታል (የቀሪ ዕርጥበት ለሚያለሙ
አካባቢዎች ብቻ)] x የሰብሉ የወቅቱ የገቢያ ዋጋ ብር በኩንታል] + የመሬት
ቋሚ ማሻሻያ ወጪ
ሰ. የመስኖ የሰብል አብቃይ ካሳ = [(በመስኖ የሚለማ መሬት ስፋት በሄ/ር x
ከአንድ ሄ/ር መሬት ላይ የሚገኝ ምርት በኩንታል x የሰብሉ የወቅቱ የገቢያ
ዋጋ በኩንታል) X ምርቱ በሚሰበሰብበት ጊዜ] + የመሬት ቋሚ ማሻሻያ
ወጪ (በዓመት ከ2 አስከ 3 ጊዜ ለሚያለሙ መሬቶች ብቻ)]
ሸ. የሰብል ተረፈ ምርት ካሣ = የቦታው ስፋት (በሄ/ር)የሰብሉ ተረፈ ምርት
ወቅታዊ የገበያ ዋጋበአንድ ሄ/ር ስፋት ላይ የሚገኝ ተረፈ ምርት በኩ/ል
ወይም በሸክም X ምርቱ በሚሰበሰብበት ጊዜ]
ቀ. የሰብል ተረፈ ምርት ካሣ የሚገመተው በመኸር፣ በበልግ፣ በቀሪ ዕርጥበት
ወይም በመስኖ የምርት ወቅት በሚገኜው የምርት ድግግሞሽ ታሳቢ ተደርጎ
የሚሰላ ይሆናል፡፡
26.1.4. የቋሚ ተክል ካሳ
1. የቋሚ ተክል ካሣ የሚሰላው ተክሉ ፍሬ መስጠት ያልጀመረ ከሆነ ተክሉ
በሚገኝበት ደረጃ ለማድረስ የሚያስፈልገውን ወጪ ግምት በማስላት እና
በመሬቱ ላይ ያደረገው ቋሚ ማሻሻያ ካለ ያሻሻለበት የገንዘብና የጉልበት
ወጭዎች የሚተካ ካሳ ይከፈለዋል፡፡ ፍሬ መስጠት ያልጀመረ የተባለው
ተዛውሮ ተተክሎ የጸደቀ ችግኝን ይጨምራል፡፡
31
ሀ. ፍሬ መስጠት ያልጀመረ የቋሚ ተክል ካሳ = [የተክል ብዛት
(በእግር) X በአንድ እግር ለጉልበትና ለማቴሪያል የወጣ ወጪ
ግምት] + የመሬት ቋሚ ማሻሻያ ወጪ
2. ፍሬ መስጠት የጀመረ የቋሚ ተክል ካሳ የሚሰላው ወቅታዊ የቋሚ ተክሉ
ምርት ወቅታዊ የገበያ ዋጋ እና በመሬቱ ላይ የቋሚ ማሻሻያ
ያደረገበትን የገንዘብና የጉልበት ዋጋ የሚተካ ካሳ ጨምሮ ይከፈለዋል፡፡
ሀ. ፍሬ መስጠት የጀመረ የቋሚ ተክል ካሳ = [የተክል ብዛት
(በእግር)/ ወይም በአንድ ሄ/ር ሊኖር የሚችል ተክል ብዛት X በሄ/ር
X ተክሉ በአንድ እግር በዓመት የሚያሰገኘው ምርት ብዛት (በኪሎ
ግራም) x የቋሚ ተክሉ ምርት የወቅቱ የገቢያ ዋጋ ብር በኪሎ
ግራም] + የመሬት ቋሚ ማሻሻያ ወጪ
ለ. የዛፍ ካሣ = [የዛፉ ዓይነት ምሳሌ ዋንዛ (ከፍተኛ ዛፍ ብዛት x
የአንዱ ዋጋ) + (መካከለኛ ዛፍ ብዛት x የአንዱ ዋጋ) + (ዝቅተኛ
ዛፍ ብዛት x የአንዱ ዋጋ)] + [የዛፉ ዓይነት ግራር (ከፍተኛ ዛፍ
ብዛት x የአንዱ ዋጋ) + (መካከለኛ ዛፍ ብዛት x የአንዱ ዋጋ) +
(ዝቅተኛ ዛፍ ብዛት x የአንዱ ዋጋ)] + …...
ሐ. ለማገዶና ለግንባታ የተተከለ ባህር ዛፍ ወይም ተመሳሳይ ዛፍ =
(የወራጅ ብዛት x የአንዱ ዋጋ) + (የማገር ብዛት x የአንዱ ዋጋ) +
(ምሰሶ ብዛት x የአንዱ ዋጋ) + (የጨፈቃ ብዛት x የአንዱ ዋጋ)
/በወቅቱ የገበያ ዋጋ መሠረት/
26.1.5. የንብረት ማንሻና መልሶ መትከያ ካሣ ተመን በተመለከተ
ሀ. የንብረት ማንሻና መልሶ መትከያ ካሣ ተመን = የንብረቱ ማንሻ
ወጪ + የማዛወሪያ ወጪ + መልሶ የመትከያ ወጪ /በወቅቱ የገበያ
ዋጋ መሠረት/
26.1.6. የጥብቅ ሳር ካሳ ተመን በተመለከተ
ሀ. የጥብቅ ሳር ካሳ = ሳሩ የሸፈነው ቦታ በሄ/ር x በሄ/ር የሚሰበሰበው ሳር
በሸክም x የሚመረተው የሳር ምርት ወቅታዊ የገቢያ ዋጋ በሸክም
32
26.1.7. የመካነ መቃብር ካሣ ተመን በተመለከተ
ሀ. የመካነ መቃብር ካሣ = ለመካነ መቃብር ማንሻ ወጪ+ የተለዋጭ
ማረፊያ ቦታ ማዘጋጃ ወጪ+ አጽሙን ለማዛወሪያና ማሳረፊያ የዋለ ወጪ+
ሀይማኖታዊና ባህላዊ ስርዓት ማስፈፀሚያ ወጪ
26.1.8. ለውሃ ጉድጓድ፣ የጎለበቱ ምንጮች፣ የተቆፈሩ ኩሬዎች፣ የመስኖ
ግንባታዎች፣ የውሃ ማፋሰሻ ቦዮች፣ የውሃና አፈር ጥበቃ ህዳጎች እና ሌሎች
ስትራክተሮች ተመን በተመለከተ
ሀ. ለውሃ ጉድጓድ፣ የጎለበቱ ምንጮች፣ የተቆፈሩ ኩሬዎች፣ የመስኖ
ግንባታዎች፣ የውሃ ማፋሰሻ ቦዮች፣ የውሃና አፈር ጥበቃ ህዳጎች እና
ሌሎች ስትራክተሮች = የወቅቱ የግንባታ ወጪ (የማቴርያል + የጉልበት
+ የገንዘብ ወጪ)
26.2. የመፈናቀያ ካሳ
1. የመሬት ይዞታውን ለተወሰነ ጊዜ እንዲለቅ ለሚደረግ የገጠር መሬት
ባለይዞታ ወይም ለወል መሬት ባለይዞታዎች መሬቱ እንዲለቀቅ ከመደረጉ
በፊት በነበሩት አምስት ዓመታት ያገኙት አማካኝ ምርታማነት በወቅቱ
የገቢያ ዋጋ ተባዝቶ መሬቱ እሰኪመለስ ድረስ ባለው ጊዜ ታስቦ ከሚከፈለው
የግንባር ካሳ በተጨማሪ የማፈናቀያ ካሳ ይከፈላቸዋል፡፡ ሆኖም የሚከፈለው
የካሳ መጠን በቋሚነት ከሚከፈለው የማፈናቀያ ካሳ መብለጥ የለበትም፡፡
2. በጊዚያዊነት ለሚለቀቁ ይዞታዎች = (የሰብል ካሳ + ፍሬ መስጠት የጀመረ
ቋሚ ተክል ካሳ + የጥብቅ ሳር ካሳ + የተረፈ ምርት ካሳ) x በሚወሰደው
ጊዜ ብዛት
3. በቋሚነት ለሚለቀቁ ይዞታዎች = (የሰብል ካሳ + ፍሬ መስጠት የጀመረ
ቋሚ ተክል ካሳ + የጥብቅ ሳር ካሳ+ የተረፈ ምርት ካሳ) x 10
4. በማናቸውም ሁኔታ የተደረገ የመሬት ቋሚ ማሻሻያ ወጪ የሚከፈለው
ለአንድ ጊዜ ብቻ ይሆናል፤ በቋሚ ማፈናቀያ ካሳ ስሌት አብሮ
አይታሰብም፡፡
33
5. በዚህ መመሪያ መሠረት ከለቀቁት መሬት ጋር ተመጣጣኝ የሆነ ትክ መሬት
ያገኙ ባለይዞታዎች የመፈናቀያ ካሣ አይከፈላቸውም፡፡ ይሁን እንጂ ትክ
መሬቱ ከቀድሞው ይዞታ ጋር ተመጣጣኝ መሬት ካልሆነ ላጋጠመው ልዩነት
ብቻ የመፈናቀያ ካሣው ሊከፈለው ይገባል፡፡
26.3. ስለሌሎች የተለያዩ የካሣ ክፍያዎች ስሌት ቀመር
34
ክፍል አራት
35
ባለይዞታ የተገመትለትን የካሳ መጠን በዝርዝር ተገልጾ በደብዳቤ
እንዲደረሰው ይደረጋል፡፡
28. የካሳ አከፋፈል ስርዓት
36
4. በተዋረድ የሚገኘው የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ተቋም ለካሳ
ተከፋዮች ገንዘቡ በእያንዳንዱ ተከፋይ በተከፈተው የቁጠባ ሂሳብ
በትክክል መግባቱንና ክፍያ መፈጸሙን ያረጋግጣል፤
29. በቀበሌ ማዕከላት በኩል የሚፈጸም ካሳ ክፍያን አስመለክቶ
ሀ. ከእያንዳንዱ ቦታ ፈላጊ ግለሰብ ወይም ተቋም በተገመተው ካሳ መሰረት
በተዋረድ የሚገኘው የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ተቋም በአማራ ብድርና
ቁጠባ ተቋም አማካኝነት በሚከፈተው የቁጠባ ሂሳብ ቁጥር የሚፈለገው
ገንዘብ ገቢ እንዲሆን ያደርጋል፤ ከፋዩ አካል ገቢ ያደረገበትን ህጋዊ የሂሳብ
ደረሰኝ ቦታውን ከመረከቡ በፊት ማቅረብ ይኖርበታል፤
ለ. በጥቅል ከእያንዳንዱ መሬት ተረካቢ ገቢ ከተደረገው የካሳ ገንዘብ፣ ለካሳ
ተከፋዮች ክፍያ እንዲፈጸም በእያንዳንዱ ተከፋይ ስም በአማራ ብድርና
ቁጠባ ተቋም በተከፈተው የቁጠባ ሂሳብ ገንዘቡ እንዲተላለፍላቸው የመሬት
ይዞታ ማረጋገጫ ደበተር፣ የተወሰደውን የመሬት ስፋት የሚያሳይ ካርታ፣
ለባለይዞታው የሚከፈለው ዝርዝር ካሳ ገንዘብ መጠን፤ የቀበሌ መታወቂያና
ሌሎች ደጋፊ መረጃዎችን በማያያዝ የወረዳው ገጠር መሬት አስተዳዳርና
አጠቃቀም ጽ/ቤት የክፍያ ትዕዛዝ ለወረዳው ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር
ጽ/ቤት ይሰጣል፤
ሐ. የወረዳው ገጠር መሬት አስተዳዳርና አጠቃቀም ጽ/ቤት ለካሳ ተከፋዮች
ገንዘቡ በአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም በእያንዳንዱ ተከፋይ ስም በተከፈተው
የቁጠባ ሂሳብ በትክክል መግባቱንና ክፍያ መፈጸሙን ያረጋግጣል፡፡
30. ስለካሳ አከፋፈልና ውሳኔ አሰጣጥ
30.1. የካሳ አከፋፈል ሂደት
1. በገጠር መሬት ይዞታዎች ላይ ይህንን መመሪያ መሠረት በማድረግ
የተሠራው ግምት ለከተማው ወይም ለወረዳው የመሬት ጠያቂ አካላት
ወይም ባለቤቶች እንደ ደረሰ በፕሮጀክቱ ወይም በወኪሎቻቸው
አማካኝነት በ30 ቀናት ውስጥ አግባብ ላላቸው ባለይዞታዎች ወይም
እነርሱ በህግ ለሚወክሏቸው ሰዎች እንዲከፈል ይደረጋል፤
37
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) መሠረት ማንኛውም ባለይዞታ የካሳ
ክፍያውን ለመቀበል ፈቃደኛ ካልሆነ፣ ለዚሁ ዓላማ በወረዳው ወይም
በከተማ አስተዳደር ዘንድ በስሙ በተከፈተ ዝግ የባንክ ሂሣብ
እንዲቀመጥና ይህንኑ ባለይዞታው እንዲያውቀው ይደረጋል፡፡
3. በክልሉ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ደንብ መሰረት፡-
38
5. የወል መሬት የካሳ ክፍያ ለወል መሬቱ ተጠቃሚዎች በጋራ
ለሚጠቀሙበት የማህበራዊ አገልግሎትና መሰረተ ልማት ግንባታ
ይውላል። የወል መሬት የካሳ ገንዘብ ለወል ተጠቃሚዎች በግለሰብ
ደረጃ አይከፋፈልም፡፡
40
2. መሬት የመለካትና የንብረት ሃብት ቆጠራ ሥራው በሚካሄድበት
ወቅት ሆነ ብሎ መረጃዎችን ማዛባትና የካሳ ክፍያ እንዲፈጸም
ማድረግ በህግ ተጠያቂ ያደርጋል፤
3. ማንኛውም ባለይዞታ ነኝ ባይ በማናቸውም ሁኔታ የሰጠው መረጃ
ትክክለኛ ሆኖ ካልተገኘና ይዞታውም የእርሱ አለመሆኑ ከተረጋገጠ
የጠየቀውን የካሣ ክፍያ አያገኝም፡፡ ክፍያውን ከወሰደ በኋላም ቢሆን
በተሳሳተ ማስረጃ የተከፈለ መሆኑ ከተረጋገጠ በህግ ተገዶ እንዲመልስ
ይደረጋል፤ በፈጸመው የማጭበርበር ስራ በህግ ተጠያቂ ይሆናል፤
4. በዚህ መመሪያ መሠረት ባለይዞታዎች ድንበር መግፋታቸው
ከተረጋገጠና ችግሩ በአዋሳኝ ባለይዞታዎች ስምምነት ካልተፈታ
ይኸው እስኪስተካከልና ስሌቱ በዚያው መሠረት እስኪታረም ድረስ
በተጨማሪ ለተያዘው መሬት ወይም ለተገፋው ድንበር የተጠየቀው
የካሳ ክፍያ ሊፈፀም አይችልም፤
5. በዚህ መመሪያ መሠረት የንብረት ገማች ቡድን በፈፀመው የመሬት
መለካትና የሃብት ቆጠራ ተግባር ስህተት ምክንያት በማንኛውም ሰው
ላይ ጉዳት የደረሰ እንደሆነ፣ የጉዳቱን ካሣ በመክፈል ረገድ ሀላፊነት
ያለበት አግባብ ያለው የወረዳ ወይም የከተማ አሰተዳደር ይሆናል፡፡
ሆኖም የወረዳው ወይም የከተማ አስተዳደር ለተጐጅው የከፈለውን
የጉዳት ካሣ እንዲተካለት ጥፋቱን የፈፀመውን ሰራተኛ ወይም የገማች
ባለሙያዎች ቡድን እንደአግባብነቱ በተናጠል ወይም በቡድን በህግ
ተጠያቂ ያደርጋል፤ የከፈለውን ገንዘብ ያስመልሳል፡፡
30.2.5. በክርክር ላይ ስላሉ የመሬት ይዞታዎች የካሳ አከፋፈል ሂደት
1. ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የይዞታ መሬት እንዲለቀቅ በሚደረግበት
ወቅት የሚነሳ ማናቸውም የይገባኛል ጥያቄ መጀመሪያ በክልሉ
የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም የህግ ማዕቀፍ መሰረት
በሽምግልና ታይቶ በዕርቅ እንዲፈታ ይደረጋል፡፡
41
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (2.5.1) ላይ የተጠቀሰው እንደተጠበቀ
ሆኖ በባለይዞታዎች መካከል በህግ ክርከር ላይ ያለ መሬት
ወይንም የይገበኛል ጥያቄ የቀረበበት ይዞታ የካሳ ግምት ክርክሩ
ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ ለጊዜው በወረዳው ወይም በከተማ፣ወይም
በወረዳ አስተዳደር ስም በሚከፈት ዝግ የባንክ ሂሣብ ተቀመጦ
ውሳኔ እንዳገኘም ካሣው ለባለመብቱ ይከፈላል።
42
ክፍል አምስት
43
ሀ. እንደ የፍላጎታቸው በተናጠልም ሆነ በጋራ በመደራጀት በተለያዩ
የስራ ዘርፎች ተፈላጊው ፕሮጀክት ተቀርጾላቸው ወደስራ እንዲገቡ
ይደረጋል፤
ለ. በመንግሥትም ሆነ በአልሚ ባለሃብቶች አማካኝነት የስራ እድል
በቅድሚያ እንዲፈጠርላቸውና ለስራ የደረሱ የቤተሰብ አባሎቻቸውም
በአካባቢው ከሚካሄደው ልማት ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ ተገቢው
ክትትልና ድጋፍ ይደረግላቸዋል፤
ሐ. እንደ አስፈላጊነቱ የብድር አገልግሎት ወይም ሌላ አይነት ልዩ
ድጋፍ ይመቻችላቸዋል፤
መ. የሚያቀርቧቸው ምርቶች በገበያ ረገድ ተወዳዳሪዎች እንዲሆኑ
በስልጠናና በግብይት እሴት ሰንሰለት ትስስር ፈጠራ ረገድ ተገቢው
ድጋፍ ይደረግላቸዋል፡፡
32. ለልማት ተነሽዎች በጉዳት መጠናቸው መሰረት የመሥሪያና የመኖሪያ
ቦታ አሰጣጥ ስርዓት
46
መመሪያ መሰረት ተገቢው የንብረትና የመፈናቀያ ካሳ እንዲከፈላቸው
ተደርጎ ቦታው ከሶስተኛ ወገን ነጻ ይደረጋል፤
4. በትክነት የተመረጠው ቦታ በሚመለከተው ከተማ አማካኝነት አስፈላጊው
የማስፋፊያና የሽንሻኖ ፕላን ተዘጋጅቶለት የከተማው የዕድገት ፕላን አካል
ሆኖ እንዲጸድቅና በዚሁ ፕላን መሰረት በሚመለከተው አካል መሰረተ-
ልማት እንዲሟላለት ይደረጋል፤
5. በከተሞች ለማስፋፊያም ይሁን ለሌላ ልማት ተብሎ ፣ መሬት ከገጠር
መሬት ባለይዞታ በሚወሰድበት ጊዜ፤ ባለይዞታው የማጨሻ ቤት ወይም
ቤትና ቦታ በራሱ ወይም በትዳር ጓደኛው ስም በከተማው ፕላን ውስጥ
ከሌለው 500 ካሬ ሜትር የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ በቅድሚያ
እንዲያገኝ ይደረጋል፤ ሆኖም ግን ከከተማው ፕላን ውጭ ቤት ቢኖረውም
ወደ ከተማ ከሚካለለው ወይም በልማት ምክንያት ከሚወሰድበት መሬት
ላይ ማጨሻ ቤት ባይኖርም 500 ካሬ ሜትር የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ
ለባለይዞታው በቅድሚያ እንዲያገኝ ሊደረግ ይችላል፤
6. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (5) የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ፣ በከተማው
የፕላን ወሰንም ሆነ ከከተማ ፕላን ወሰን ውጭ ለልማት ሲባል የአርሶ
አደሮች የመሬት ይዞታ በሚወሰደበት ወቅት፣ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት
በላይ ለሆናቸውና በቀበሌው የሚኖሩም ይሁን በማንኛውም ደረጃ
በትምህርት ላይ የሚገኙ ልጆቻቸው እንዲሁም በተሻሻለው የገጠር መሬት
አስተዳደተርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 252/2009 አንቀጽ 2 ንዑስ አንቀጽ
(9) የቤተሰብ አባል ተብሎ ትርጉም በተሰጠው መሰረት የቤተሰብ አባል
ለሆኑም ጭምር መረጃው እየተጣራ ለመኖሪያ ቤት የሚውል የመስሪያ
ቦታ በከተማው ፕላን እስታንዳርድ መሰረት ወደ ከተማ የተካለለው
የወላጆቻቸው/ የአሳዳጊዎቻቸው መሬት በቂ ሆኖ እስከ ተገኘ ድረስ የቤት
መስሪያ ቦታ እንዲያገኙ ይደረጋል፤
7. በውርስ የባለይዞታነት መብታቸውን በህግ አግባብ አረጋግጠው የሚቀርቡ
አመልካቾች፣ በከተማው ውስጥ የመኖሪያ ቤት የሌላቸው መሆኑ ሲረጋገጥ
47
ወደ ከተማ ከተካለለው መሬት በአባወራ/በእማወራ ባለ ይዞታዎች የቦታ
መጠን ልክ የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ እንዲያገኙ ይደረጋል፤
8. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (6) እና (7) የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ፣
በጊዜያዊነት በስደት ከአካባቢያቸው የሌሉ ወደ ሀገር ውጭም ይሁን በሃገር
ውስጥ የተሰደዱ/ የህብረተሰብ ክፍሎች ወደ አካባቢያቸው ከተመለሱ
የቆይታ ጊዜ ከግምት ውስጥ ሳይገባ እና የወላጆቻቸው መሬት ወደ ከተማ
ክልል ከተካተተ እንደመበኛ የቀበሌው ነዋሪ ተቆጥረው በከተማው የፕላን
ስታንዳርደድ መሰረት የቤት መሰሪያ ቦታ ሊሰጣቸው ይገባል፤
9. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (7) እና (8) የተደነገገው ቢኖርም በውርስ
የባለይዞታነት መብታቸውን አረጋግጠው የሚቀርቡ አመልካቾች፣ ምንም
እንኳ ገጠር ላይ የመኖሪያ ቦታበ /ቤት/ ቢኖራቸውም በከተማው ውስጥ
የመኖሪያ ቦታ ከሌላቸው በአባወራ/በእማወራ ባለ ይዞታዎች የቦታ መጠን
ልክ ወደ ከተማ ከተካለለው ወይም ለልማት ከተወሰደው መሬት ውስጥ
የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ እንዲያገኙ ይደረጋል፤
10. በተሻሻለው የክልሉ ገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም አዋጅ
ቁጥር 252/2009 ዓ.ም አንቀፅ 10 ንዑስ አንቀፅ /4/ ስር እድሜያቸው 18
ዓመት ያልሞላቸዉ ወላጆቻቸውን ያጡ ህፃናት የሚተዳደሩበት መሬት
በሞግዚቶቻቸው ወይም በወኪሎቻቸው አማካኝነት ሊያገኙ እንደሚችሉ
አስቀድሞ የተደነገገ መሆኑን ታሳቢ በማድረግ፣ ተሰጥቷቸው የነበረው
ይኸው የመሬት ይዞታ በልማት ምክንያት ተወስዶ ለልማት እንዲውል
የተደረገ እንደሆነ፣ ተገቢውን ካሳ የማግኘት መብታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ
በአባወራ/በእማወራ ባለ ይዞታዎች የቦታ መጠን ልክ አንድ የመኖሪያ ቤት
መስሪያ ቦታ ብቻ ይሰጣቸዋል፤ ሆኖም ግን እድሜያቸው 18 ዓመት
የሞላቸው ወራሾች የውርስ መሬቱን በጋራ የሚጠቀሙበት ከሆኖነና
የመሬቱ መጠን በቂ ሆኖ እስከተገኘ ድረስ በከተማው ፕላን ስታንዳርድ
መሰረት ለእያንዳንዳቸው የቤት መስሪያ ቦታ ይሰጣቸዋል፡፡ ነገር ግን
48
መሬቱ በቂ ሆኖ ካልተገኘ አንድ የአባዎራ ወይም የእማወራ የቦታ ድርሻ
ይሰጣቸዋል፤
11. በየትኛውም የከተማ ፕላን ወሰን የሚኖሩ የመሬት
ባለይዞታዎች፣የመኖሪያ ይዞታቸው በከተማው የፕላን ምደባ የንግድ
አገልግሎት ሆኖ ከተገኘና በዚሁ በግል ይዞታቸው ላይ የማልማት ፍላጎትና
አቅም ካላቸው፣ የከተማውን ስታንዳርድ የሚያሟሉ ከሆነ እና በከተማው
ፕላን መሰረት ደረጃውን የጠበቀ የፕሮጀክት ሃሳብ አቅርበው በዚሁ
መሰረት የውል ግዴታ ለመግባት እስከተስማሙ ድረስ፣ በከተማው የፕላን
ምድብ የቦታ ስታንዳርድ መጠን የመሬት ባለይዞታዎች በተናጠል
በስማቸው አንድ የንግድ ቦታ ብቻ ሊከበርላቸው እና ቅድሚያ ተሰጥቷቸው
ሊስተናገዱ ይገባል፤ ይዞታቸውም በካርታ ተደግፎና ተረጋግጦ
ይሰጣቸዋል፤
12. በማንኛውም ከተማ የፕላን ወሰን በተጠቃለለ የገጠር ቀበሌ ውስጥ
በሚገኝ የግል ይዞታው ላይ የመኖሪያ ቤት ወይም የንግድ ድርጅት
ለመገንባት የተፈቀደለት ማንኛውም ባለይዞታ፣ በከተማው በኩል የይዞታ
ማረጋገጫ ካርታና የምስክር ወረቀት የተሰጠው እንደሆነ በምስክር ወረቀቱ
ላይ የተመለከተው ይኸው የቦታ መጠን በገጠር የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ
ደብተሩ ላይ ከሰፈረው ጠቅላላ ይዞታው ላይ ተቀናሽ ተደርጎ፣ ደበተሩ
ላይና ባህር መዘገብ ላይ የሰፈረው የቀድሞው መረጃ መስተካከል
ይኖርበታል፡፡
33.2. የመሬት ይዞታቸው ለህዝብ ጥቅም ሲባል የሚወሰድባቸውን ባለይዞታዎች
በዘላቂነት ስለማቋቋምና ስለመደገፍ
1. በቦታ አቅርቦት ረገድ ቅድሚያ ስለማግኘት፡
49
እንዲችሉ ለዚሁ የሚያስፈልገው ቦታ በቅድሚያ በነጻ ምደባ
ይሰጣቸዋል፤
ለ. በተሻሻለው የክልሉ ገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም
አዋጅ ቁጥር 252/2009 ዓ.ም አንቀፅ 18 ንዑስ አንቀጽ (1)
መሰረት ማንኛውም የገጠር መሬት ባለይዞታ የመጠቀም መብቱን
እንደያዘ በከተማው የፕላን ምድብ በሚፈቅደው መሰረት በግል
ይዞታው ላይ ከግል ባለሃብቱ ጋር በጹህፍ ተዋውሎ ይዞታውን
በጋራ የማልማት መብት ይኖረዋል፤
ሐ. ከመሬቱ የተነሳ የገጠር መሬት ባለይዞታ በመሬት የመጠቀም
መብቱን በካፒታል መዋጮነት በመጠቀም ቅድሚያ የማልማት
መብት ይከበርለታል፤
መ. በልማት ምክንያት ከይዞታቸው የሚነሱ ባለይዞታዎች
ተደራጅተው G+1 እና ከዚያ በላይ የሆኑ የገበያ ማዕከላትን ወይም
ተመሳሳይ አገልግሎት የሚሰጡ ህንፃዎችን በጋራ ለመገንባትና
ለመጠቀም በሚፈልጉበት ጊዜ፣ በጥናት ላይ ተመስርተው
የሚያቀርቡትን የፕሮጀክት ሰነድ መነሻ በማድረግ የሚጠይቁት
የከተማ ቦታ በምደባ ይሰጣቸዋል፡፡
34. ከከተማ ውጭ ለህዝብ ጥቅም ሲባል ከመሬታቸው ለሚነሱ የገጠር
መሬት ባለይዞታዎች የሰፈራ ቦታ፣ ትክ የእርሻ እና የግጦሽ መሬት ስለ
መለየትና ስለ ማዘጋጀት
1. ከከተማ ውጭ ለህዝብ ጥቅም ሲባል በልዩ የልማት ፕሮጀክት
ምክንያት ከመሬታቸው ለሚነሱ ባለይዞታዎች ትክ ሆኖ
የሚያገለግል የመልሶ ማቋቋሚያ ሰፈራ ቦታ በጥናት ተለይቶ
ተመጣጣኝነት ያለው የእርሻ፣ የግጦሽ እና የመኖሪያ ስፍራ
እንዲዘጋጅ ይደረጋል፤
50
2. የተመረጠው ትክ ወይም የሰፈራ ቦታ የመሬት አጠቃቀም ዕቅድ
ተዘጋጅቶለት እንዲጸድቅና ፕላኑን ተከትሎ አስፈላጊው መሰረተ
ልማት እንዲሟላለት ይደረጋል፡፡
35. ስለ ሌሎች ተጨማሪ ድጋፎች
1. በልማት ምክንያት ከመሬታቸው የሚፈናቀሉ ህጋዊ ባለይዞታዎች ይኸው
መፈናቀል የሚያስከትልባቸው ጉዳት ከወዲሁ ታይቶ፡-
51
ሀ. በተሰጠው የግንባታ ፈቃድ መሰረት ቤቱን አጠናቀው እስኪገቡ ድረስ
በወቅታዊ የኪራይ ግምት ተሰልቶ የአንድ ዓመት የቤት ኪራይ ክፍያ
እንዲከፈላቸው ይደረጋል፤
ለ. በጊዜያዊነት ለሚነሱ ባለይዞታዎች ቤታቸውን ለቀው ወይም ከመኖሪያ
ቦታቸው ተነስተው ለሚቆዩበት ጊዜ በወቅታዊ የኪራይ ግምት ተሰልቶ
የቤት ኪራይ ክፍያ ይፈጸመላቸዋል፤ ነገር ግን የቤት ኪራይ ክፍያው
የሚከፈለው ወደ ቀድሞ የመኖሪያ ቤታቸው ተመልሰው እስከሚገቡበት
ጊዜ ድረስ ላለው ተሰልቶ ይከፈላቸዋል፡፡
52
ክፍል ስድስት
53
5. ቅሬታ አቅራቢው ቅሬታ የቀረበበትን ማሳ፣ የቅሬታው መነሻ ምንጭ፣
ይዞታው የሚገኝበት ቀበሌ፣ ን/ቀበሌና ጎጥ የሚገልጹ መረጃዎች ከቅሬታ
ማመልከቻው ጋር አያይዞ ማቅረብ ይኖርበታል፤
6. ባለይዞታው የካሣ ክፍያውን ከተቀበለ በኋላ በካሳው መጠንም ይሁን
በንብረት አገማመቱ ላይ ቅሬታ ማቅረብ አይችልም፡፡
7. በንብረት ገማች ቡድን/ባለሙያዎች በኩል በተወሰነው የካሳ መጠን ወይም
በካሳው አከፋፋል ላይ ቅር በመሰኘቱ አቤቱታና ይግባኝ በማቅረቡ ለህዝብ
አገልግሎት መለቀቅ የሚገባው መሬት ርክክብ እንዲታገድ ወይም እንዲዘገይ
አያደርገውም፡፡ በመሆኑም በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (5) መሠረት ይግባኝ
የሚያቀርብ የመሬት ይዞታ ማስለቀቂያ ትዕዛዝ የደረሰው ባለይዞታ ይግባኙ
ሊታይለት የሚችለው እንዲለቀቅ ትዕዛዝ የተሰጠበትን መሬት ለወረዳው
ወይም ለከተማ መሬቱን ማስረከቡን የሚያረጋግጥ ሰነድ ከይግባኝ አቤቱታው
ጋር አያይዞ ካቀረበ ብቻ ይሆናል፤
8. የካሳ ቅሬታ አጣሪ ኮሚቴው የቀረበውን የአቤቱታና ቅሬታ ማመልከቻ
መሰረት በማድረግ አግባብ ያላቸውን ሰነዶች በመመርመር፣ ጉዳዩ
የሚለከታቸውን አካላት በማነጋገር እና ስራ ላይ ከዋሉ የህግ ማዕቀፎች ጋር
በማገናዘብ አቤቱታው በደረሰው በ7 ቀናት ጊዜ ውስጥ ውሳኔውን ለአቤቱታ
አቅራቢዎች ወይም ለተወካዮቻቸው፣ ለወረዳው ወይም ለከተማ አስተዳደር
የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ተቋም በጽሁፍ ውሳኔ መስጠት
አለበት፤
9. ቅሬታ ያቀረበው ባለይዞታ ወይም ተከራካሪ ወገን በካሳ ቅሬታ አጣሪ ኮሚቴ
ውሳኔ ቅር ከተሰኘ ይግባኙን ውሳኔው በተሰጠው በ30 ቀናት ጊዜ ውስጥ ለዞን
ከፍተኛ ፍ/ቤት ማቅረብ ይችላል፡፡ በከፍተኛ ፍ/ቤት የተሰጠው ውሳኔ ያልረካ
አስከ ሰበር ሰሚ ማቅረብ ይችላል፤
10. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (9) የተመለከተው የይግባኝ ማቅረቢያ ጊዜ
አመልካቹ ይግባኝ ሲጠይቅ የውሳኔውን ግልባጭ አዘጋጅቶ ለመስጠት
የሚወስደውን ጊዜ አይጨምርም፤
54
37. መረጃ ስለመጠየቅና ስለመቀበል
1. በዚህ መመሪያ መሠረት የንብረት ገማች ወይም የካሳ ቅሬታ አጣሪ
ኮሚቴዎች ለሚያከናውኗቸው ተግባራት አስፈላጊ የሆኑትን መረጃዎች
አግባብ ካላቸው የፌዴራል፣ የክልል፣ የወረዳ፣ የከተማ፣ የቀበሌ ወይም ሌሎች
አካላት የመጠየቅና የማግኘት መብት አላቸው፤
2. በዚህ አንቀጽ መሰረት ጥያቄ የቀረበለት ማንኛውም አካል የተጠየቁትን
መረጃዎች የመስጠት ግዴታ አለበት፤
3. የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ተቋም ለካሳ ግመታ የሚጠይቃቸው
የምርታማነትና የወቅቱ የገቢያ ዋጋ መረጃዎች አለመኖራቸው ሲረጋገጥ
ቡድኑ የግል የአሰራር ስልትና ዕውቀት በመጠቀምና ቅኝታዊ ጥናት
በማካሄድ መረጃዎችን ይሰበስባል፣ ያደራጃል፤ ጥቅም ላይ እንዲውል
ያደርጋል፤
55
መልኩ ይሰበስባል፣ ያጣራል፣ ይመረምራል፣ በህብረተሰቡ
ያስገመግማል፣ ያደራጃል፤
1.3. የመሬት ምዝገባና የመለካት ስራ እንዲሁም የንብረት ቆጠራ
በሚካሄድበት ጊዜ የመሬት ባለይዞታዎች፣ አጎራባች ባለይዞታዎች፣
የቀበሌ የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ኮሚቴ ተወካዮች እንዲገኙ
ጥሪ መደረጉን ወይም አስፈላጊው ጥሪ ደርሷቸው አለመገኘታቸውን
በማረጋገጥ የመሬት መለካት፣ መመዝገብና የንብረትና በመሬቱ ላይ
የተደረጉ ማሻሻያዎችን የቆጠራ ተግባር ያከናውናል፤
1.4. የመሬት ልኬታና በመሬት ላይ ያፈሩት ንብረት ቆጠራ
ባለይዞታዎችን ያሳተፈ መሆኑን ለማረጋገጥ በመሬት ምዝገባውና
በንብረት ቆጠራው ላይ ባለይዞታዎቹና የንብረት ገማች ቡድን
አባላት በመተማማኛ ቅጹ ላይ እንዲፈርሙበት ያደርጋል፤
1.5. በመሬት ልኬታና በንብረት ቆጠራ የተሰባሰቡ መረጃዎችን
ለህብረተሰቡ በማቅረብ የማስተቸትና ባለቤትነታቸውን የማረጋገጥ
ስራ ያከናውናል፤
1.6. ለንብረት ግመታ ስራ አስፈላጊ የሆኑ የቅርብ አምስት ዓመታት
የምርታማነት መረጃና ወቅታዊ የገቢያ ዋጋ እና ሌሎች ለትመና
ስራው አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች ከሚመለከታቸው የወረዳው ወይም
የከተማ መስሪያ ቤቶች ህጋዊ ጥያቄ በማቅረብ ተረጋግጠው ለገጠር
መሬት አስተዳርና አጠቃቀም ተቋም መሰጠት አለበት፤
እንዳስፈላጊነቱም ተጨማሪ መረጃ ሲያሰፈለግ የገማች ባለሙያዎች
ቡድን ጥናት እያካሄደ ያልተሟሉ መረጃዎችን ይሰበስባል፤ ያደራጃል
ይተነትናል፤
1.7. በመሬት ልኬታ፣ በንብረት ሃብት ቆጠራና ወቅታዊ የገበያ ዋጋ፣
ከሚመለከታቸው አካላት የተሰባሰቡ መረጃዎችን ጥቅም ላይ በማዋል
የካሳ ትመና ያካሄዳል፤
56
1.8. ካሳ ገማች ቡድኑ የሚያከናውናቸውን ማናቸውም ተግባራት
በሚመለከት የተሟላ ቃለጉባኤ ይይዛል፤ ቃለጉባኤዎችና ሌሎች
መረጃዎች ከካሳ ሰነዱ ጋር አብረው ተሰነደው ወይም ተደራጅተው
እንዲያዙ የደርጋል፤
1.9. በካሳ ግመታ ላይ የሚነሱ ጥያቄዎች፣ አስተያየቶችና አቤቱታዎችን
ተቀብሎ እንደተገቢነቱ ወቅታዊ ምላሾችንና ማብራሪያዎችን
ይሠጣል፤
1.10. አግባብነት በሌላቸው የይዞታ ማረጋገጫ ሰነዶችና ሆነ ተብሎ
በተጭበረበረ ማስረጃ ባለይዞታዎችን ለመጥቀምም ሆነ ለመጉዳት
በሚካሄድ አሰራርና ትክክለኛ ባለይዞታውን በአግባቡ ባለመለየት
ምክንያት ካሳ እንዲከፈል አድርገው የተገኙ እንደሆነ ለተጎጅው
የሚገባውን ካሳ ከመሸፈን በተጨማሪ በተናጠልም ይሁን በቡድን
በህግ ተጠያቂ ይሆናሉ፤
57
አስተዳዳርና አጠቃቀም ተቋም በኩል ጥያቄው ሲቀረብ ንብረቱን
ለመገመት የሚችሉ ልዩ ሙያና ልምድ ያላቸው ባለሙያዎች
እንዲካተቱ ያደርጋል፤
2.2. የመሬት ማስለቀቅ እና ግመታ ስራው የሚካሄድበትን ጊዜና ሁኔታ
ይወስናል፤
2.3. የመሬት ምዝገባና የመለካት ስራ እንዲሁም የንብረት ቆጠራ
በሚካሄድበት ወቅት የመሬት ባለይዞታዎች፣ አጎራባች ባለይዞታዎች፣
የቀበሌ አስተዳደርና የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ተወካዮች
እንዲገኙ ትዕዛዝ ይሰጣል ተግባራዊነቱን ይከታተላል፤
2.4. ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የይዞታ መሬታቸውን ለለቀቁ ባለይዞታዎች
ፀድቆ የተላከው የካሳ ክፍያ ለትክክለኛ ባለይዞታዎች ወይም
የመሬቱ ተጠቃሚዎች መድረሱን ይከታተላል፤ ያረጋግጣል፤
2.5. ካሳ የተከፈለበትን መሬት ለልማት መለቀቁንና መተላለፉን
ያረጋግጣል፤ መሬቱ ለመሬት ጠያቂው ካልተላለፈ የማስተካከያ
ዕርምጃ ይወስዳል፤
2.6. የሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶች መሬት የሚለቁ
ባለይዞታዎቹን ለዘለቄታው ማቋቋም የሚያስችሉ አማራጮች
እንዲያቀርቡ ያደርጋል፤ መፈጸማቸውንም ይከታታላል፤
ይቆጣጠራል፤ አስፈላጊውን ምክርና ድጋፍ መሰጠቱን ያረጋግጣል፤
2.7. በልማት ምክንያት ከመሬታቸው የተነሱ ባለይዞታዎችን በዘላቂነት
መልሶ ለማቋቋም ኃላፊነታቸውን የማይወጡትን የመንግሰት የስራ
ኃላፊዎች ተጠያቂ እንዲሆኑ ያደርጋል፡፡
3. ከመሬት ማስለቀቅ፣ ካሳ ግመታና ክፍያ ጋር በተያያዘ ለሚቀረቡ
ቅሬታዎችና አቤቱታዎች በወረዳው ወይም በከተማ አስተዳደሩ 3 አባላት
ያሉት የካሳ ቅሬታ አጣሪ ኮሚቴ ይቋቋማል፡፡ የካሳ አጣሪ ኮሚቴው በመሬት
ማስለቀቅና ካሳ ክፍያ የሚቀረቡ ቅሬታዎችን በህጉ መሰረት በማጣራት
58
የውሳኔ አስተያየት ሲያቀርብ መርምሮ ይወሰናል፤ ለቅሬታ አቅራቢው
በፁሁፍ ምላሽ ይሰጣል፡፡
40. ስለ መሬት አቅርቦት ጠያቂ አካላት
59
7. የክፍያ አፈፃፀሙን በተመለከተ ለወረዳው ወይም ለከተማ አስተዳደርና
ለሚመለከተው የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ተቋም ወቅታዊ
መረጃዎችን ይሰጣል፤
60
ክፍል ስባት
ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
42. የመሸጋገሪያ ድንጋጌ
በዚህ መመሪያ የተሸፈኑና ይህ መመሪያ ከመጽናቱ በፊት ተጀምረው ያልተቋጩ
ጉዳዮች በወቅቱ በነበሩት ህግጋት፣ ደንቦችና መመሪያዎች መሠረት
መስተናገዳቸውን ቀጥለው እልባት ያገኛሉ።
61