Professional Documents
Culture Documents
" - (Apologi / - " - (Apologia) "
" - (Apologi / - " - (Apologia) "
1. እግዚአብሔር ስለሚያዝ፡-
• ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “የተስፋን ቃል የሰጠው የታመነ ነውና እንዳይነቃነቅ የተስፋችንን ምስክርነት
እንጠብቅ” (ዕብ. ፲፡፳፫) እንዳለን፤
• እምነትን ከቀሳጥያን መጠበቅ የእያንዳንዱ ክርስቲያን መንፈሳዊ ግዴታ እንጂ ለተወሰነ የቤተ ክርስቲያን
አካል ብቻ የሚሰጥ ሓላፊነት አይደለም፡፡
• ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስም “በእናንተ ስላለ ተስፋ
ምክንያትን ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር
የተዘጋጃችሁ ሁኑ፤ ነገር ግን በየዋሕነትና በፍርሃት ይሁን” (፩ኛ
ጴጥ. ፫፡፲፭) በማለት እያንዳንዳችን ስለ እምነታችን
የምንጠየቀውን ለመመለስ ብቁና ዝግጁ ሆነን መኖር
እንደሚገባን ነግሮናል።
• በሌሎች ትምህርት እንዳንወሰድና የራሳችንን አጥብቀን
እንድንይዝ ታዘናል፡፡
• እግዚአብሔር መከራከሪያ ማስረጃችንን እንድናቀርብ
አዞናል፡፡ ከእርሱ ጋር ኑ እንዋቀስ ብሎ፣ ከሌሎች ጋር ደግሞ
“ክርክራችሁን አቅርቡ ይላል እግዚአብሔር፤ ማስረጃችሁን
አምጡ ይላል የያዕቆብ ንጉሥ። ያምጡ፤ የሚሆነውንም
ይንገሩን፤ ልብም እናደርግ ዘንድ ፍጻሜአቸውንም እናውቅ
ዘንድ፤ የቀደሙት ነገሮች ምን እንደ ሆኑ ተናገሩ፤
የሚመጡትንም አሳዩን።” (ኢሳ. ፵፭፡፳፩-፳፪)
• ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን በሥጋዌው ወራት ከተለያዩ አካላት
ለተነሡ ጥያቄዎች መልስ ሰጥቷል፤
• ሐዋርያት፣ ሐዋርያውያን አበው፣ የእምነት ጠበቆች የሚባሉት እነ
ቅዱስ ሄሬኔዎስ፣ ሰማዕቱ ቅዱስ ዮስጢኖስ፣ ቅዱስ ቴዎፍሎስ
ዘአንጾኪያና ሌሎችም፣ ከእነርሱ ቀጥለው በዘመነ ሊቃውንት የተነሡ
ቅዱሳን አባቶች ሁሉ የዕቅበተ እምነት ሥራ ሠርተዋል፡፡
• እኛ ደግሞ “የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሯችሁን ዋኖቻችሁን
አስቡ፣ የኑሯቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነት
ምሰሏቸው” (ዕብ. ፲፫፡፯) ስለተባልን በስም ያይድለ በግብር
እነርሱን መከተል ያስፈልገናል፡፡
• ቤተ ክርስቲያን ይህን ሥራ የሚሠራ መዋቅር እንዲኖራት
ከማድረግ ጎን ለጎን ልጆቿ በእምነታቸው ላይ የሚነሡ ጥያቄዎችን
ለመመለስ የሚችሉ ማድረግ ስለሚያስፈልግ ዕቅበተ እምነት
መሠረታዊ ትምህርት ነው፡፡
2.