You are on page 1of 74

የዉርስ ህግ በኢትዮጵያ

አዘጋጅና አቅራቢ ፦ አቶ አማረ ማንጆ

ለ11ኛ ዙር የቅድመ ሥራ ላይ ሰልጣኞች ስልጠና የተዘጋጀ

ሰኔ 2013 ዓ.ም
ማዉጫ
መግቢያ
ምዕራፍ 1. የዉርስ ህግ በጠቅላላዉና የአወራረስ ሥርዓት በኢትዮጵያ
1.1 ስለዉርስ ህግ በጠቅላላዉ
1.2 የዉርስ ህግ መሰረታዊ ዓላማ
ምዕራፍ 2. የኢትዮጵያ የዉርስ አስተላለፍ ሥርዓት በጠቅላላዉ
2.2.1 ዉርስ የሚከፈትበት ጊዜና ስፍራ
2.2.2 የች ዉርስ አከፋፈት በህግ መወሰኑ አስፈላጊነት
2.4 ለመዉረስ የሚያስፈልግ ችሎታ
የቀጠለ…

ምዕራፍ 3 የዉርስ ስርዓት የሚፈፀምባቸዉ መንገዶች

3.1 ጠቅላላ
3.2 ያለኑዛዜ ዉርስ /ፍ/ህ/ቁ. 842-856
3.3 የኑዛዜ ዉርስ
3.3.1 የኑዛዜ ዓይነቶች
3.3.1.1 በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ /የፍ/ህ/ቁ.881
3.3.1.2 በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜ /ፍ/ህ/ቁ. 884- 891/
3.3.1.3 በቃል የሚደረግ ኑዛዜ /ፍ/ህ/ቁ. 892-894/
3.4 የኑዛዜ መሻር
3.5 የኑዛዜ ዉድቅ መሆን
3.6 ኑዛዜ መኖሩን ስለማስረዳት
ምዕራፍ 4 ዉርስ ማጣራትና ዉርስን ማስተዳደር
4.1 የዉርስ አጣሪዎች ግዴታዎችና ኃላፊነቶች
4.2 ከዉርስ ማጣራት ጋር ተያይዞ የሚያጋጥሙ ችግሮች
ምዕራፍ 5 የዉርስ ይርጋ
5.1 ይርጋ ለምን አስፈለገ?
5.2 ክስ ማቅረቢያ የይርጋ ጊዜ መቆጠር አጀማመር
5.3 የይርጋ መረጥ
5.4 ከዉርስ ሀብት ጋር የተያያዙ የይርጋ ገደቦች
5.5 ስለዉርስ የተደነገጉ የይርጋ ገደቦች የዉይይት ሀሳቦች
የቀጠለ…
መግቢያ

የሰው ልጅ ወደዚች ምድር ከመጣበት /ከተወለደበት/ እለት አንስቶ እስከ


ሕይወቱ ፍፃሜ ድረስ የሚቆይበት ለተወሰነ ጊዜ ነው፡፡ የሰው ልጅ በዚች
ምድር ላይ ዘላለማዊ አይደለም፡፡ ይህ የምድር ላይ ቆይታው በሞት
ይጠናቀቃል፡፡

በዚች ምድር ላይ በቆይታው ጊዜ የሰው ልጅ የተለያዩ መብቶች እና


ግዴታወች አሉ፡፡ ለምሳሌ ያህል ንብረት የማፍራት መብት የሚጠቀስ
ነው፡፡ በእለት ተእለት ኑሮው የተለያዩ ሥራዎችን እየሠራ የራሱን ብሎም
የቤተሰቡን ጉርስ ለመሸፈን ጥረት ያደርጋል፡፡ በዚህም የራሱ የሆነ ሀብት
ማፍራቱ አይቀሬ ነው፡፡ በሀብቱ የሚጠቀመዉ በህይወት እስካለ ብቻ ነው፡፡
የቀጠለ…
በማናቸዉም ምክንያት ሰዉ ሲሞት በህይወት ሳለ ባፈራዉ ሀብት ላይ የማዘዝ መብቱ ጋር
ይለያያል፡፡ አንድ ሰዉ ከሞተ በኋላ ይህን ያፈራውን ንብረት የሚጠቀሙት በሕይወት ያሉ የሱ
የቅርብ ሰዎች ናቸው፡፡ በሕይወት ያሉ ዘመዶች የሟችን ንብረት የሚጠቀሙበት በመውረስ ነው፡፡

የሰው ልጅ ወደዚች ምድር ከተቀላቀለበት እለት አንስቶ እስከ እለተ ሞቱ ድረስ መብቶችና
ግዴታዎች አሉት፡፡ ለምሳሌ የመኖር መብት፣ከቦታ ቦታ የመዘዋወር መብት፣ ሀሳብን የመግለፅ
፣መልካም ስም የመቀጠል፣ ች ንብረቱን በተመለከተ የገለፃቸዉ ሀሳቦች፣ ከግዴታዎቹ መካከል
ደግሞ የፍትሀብሄር ዕዳ የመክፈል ግዴታ ወዘተ…

ስለ ዉርስ ሲናነሳ ዉርስ በባህሪይዉ ሁለት ዓበይት ጉዳዮችን ያቅፋል፡፡ ሞትና ሀብት ናቸዉ፡፡ ሁለቱ
በሌሉበት ዉርስ አይኖርም፡፡

ሞት የሰዉን ልጅ ተፈጥሮአዊ ሰዉነት (personality) የሚያስቀር ወሳኝ ኩነት ነዉ፡፡ ሰዉነት ከሌለ
መብቶች ማረፊያ ያጣሉ፡፡
የቀጠለ…
 የሟች ንብረት እንዲሁም መብትና ግዴታዎቹ በውርስ ሕግ መሠረት ለወራሾች
የሚተላለፉ ናቸው፡፡ ለምሳሌ መልካም ስም የመቀጠል፣ ች ንብረቱን በተመለከተ
የገለፃቸዉ ሀሳቦች፣የፍትሀብሄር ዕዳ የመክፈል ግዴታ ወዘተ ይጠቀሳሉ፡፡ ይህ
አጠቃላይ ደንብ ነው፡፡
 ነገር ግን ሁሉም መብትና ግዴታዎች ሊወረሱ ወይም ለወራሾች ሊተላለፉ አይችሉም፡፡
ለምሳሌ በሞት ምክንያት ቀሪ የሚሆኑ መብቶችና ግዴታዎች መካከል የመኖር
መብት፣ከቦታ ቦታ የመዘዋወር መብት ሀሳብን የመግለፅ መብት እና ሌሎችም
ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡ እነዚህ መብቶች በባህሪያቸዉ ግለሰባዊ በመሆናቸዉ ለሌሎች
የማይተላለፉ ናቸዉ፡፡
 በመሆኑም በች ሞት ምክንያት ቀሪ የማይሆኑና ማረፊያ ያጡት መብቶች በሙሉ
ከች ሰዉነት ተነስተዉ ች ትቶት ባለፈዉ ሀብት ላይ ያርፋሉ፡፡
የቀጠለ…
 በህብረተሱ ዉስጥ ለዘመናት የሰፈነዉ ፍላጎት የች ሀብት ከሥጋ ዝምድና
ሳይወጣ ተጠብቆ እንዲቆይ ማድረግ ነዉ፡፡
 የዉርስ ህግ የች ሀብት በህይወት ላሉ ሰዎች የሚተላለፍበት መመሪያ ሲሆን
ዝርዝር ሁኔታዉ ግን ከሀገር የሚለያይበት ሁኔታ ይኖራል፡፡
 በኢትዮጵያ የዉርስ አወራረስ ስርዓት ሲናነሳ የህገ መንግስቱ አንቀፅ 34 (5) አብሮ
ይነሳል፡፡ ይህም የግልና የቤተሰብ ህግን በተመለከተ በተከራካሪዎች ሙሉ ፈቃድ
በመረጡት የአወራረስ ደንብ መዳኘት እንደሚችሉ መብት ያጎናፅፋቸዋል፡፡ በህገ
መንግስቱ አንቀፅ 78 (5) ህገ መንግስቱ ከመፅደቁ በፊት ዕዉቅና አግኝተዉ
ሲሰራባቸዉ የነበሩ የሃይማኖትና የባህል ፍርድ ቤቶች ዕዉቅና በማግኘታቸዉ
በአዋጅ ቁጥር 188/1992 በፌዴራል የሸርያ ፍርድ ቤት የተመ ሲሆን በዚሁ
መሰረት በደቡብ ክልልም ተል፡፡
 በኢትዮጵያ 3 ዓይነት አወራረስ ዓይነቶች አሉ፡፡ እነዚህም 1ኛ ባህላዊና ልማዳዊ
2ኛ ሀይማኖታዊ 3ኛ በፍትሀብሄር ህጉ የተመለከቱ የተለያዩ ባህሪይና ዉጤት
ያላቸዉ የአወራረስ ስርዓቶች ተግባራዊ እየሆኑ ይገኛሉ፡፡
የቀጠለ…

ከላይ የተጠቀሱ የአወራረስ ደንቦች በዋናነት ሁለት ባህሪያት አላቸዉ


1ኛዉ ሶስቱም የአወራረስ ደንቦች በመላ ሀገሪቱ ተግባራዊ እየሆነ
መገኘታቸዉ ሲሆን 2ኛዉ ደግሞ በች የዉርስ አወራረስ ሂደት ስርዓት
ሲፈፀም የሚነሱ ክርክሮች ተፈፃሚነት ያላቸዉን የአወራረስ ደንብ
የመምረጥ መብት ሙሉ በሙሉ የተከራካሪዎች መሆኑ ነዉ፡፡
እዚህ ላይ ግልፅ ሊሆን የሚገባዉ የፍትሀብሄር ህጉን የአወራረስ ደንብ
ተፈፃሚነት ሊያስቀር የሚችለዉ ጉዳዩ በባህላዊ ወይም በሀይማኖታዊ
የአወራረስ ደንብ እንዲፈፀም ተከራካሪዎች ሙሉ በሙሉ ፈቃደኛ
ሲሆኑ ነዉ፡፡
የኢፌዴሪ ህገ መንግስት 35(5) እና የፌዴራል ሸሪያ ፍርድ ቤቶችን
አም ለማጠናከር የወጣ አዋጅ ቁጥር 188/92 አንቀፅ 4(2) ይመልከቱ፡፡
የቀጠለ…

በዚህ ላይ ለምሳሌ የፌዴሬሽን ም/ቤት ዉሳኔ የሰጠበት የወ/ሮ ከድጃ በሽር ጉዳይ ነዉ፡፡
በዚህ ጉዳይ ወ/ሮ ከድጃ በሽር በሸርያ ፍርድ ቤት የች የአቶ ሰማን አበጋዝ ህጋዊ ምስት
ስለመሆ የምስክር ወረቀት ከተቀበለች በላ ይህንን ማስረጃ በማያያዝ የች ወራሾች
የሚስትነት ንብረት ድርሻዋን እንዲያካፍሉ በመደበኛ ፍርድ ቤት ክርክር ትጀምራለች፡፡
በዚህን ጊዜ የች ወራሾች ከሳሽ የሚስትነት ማስረጃ ከሸሪያ ፍርድ ቤት ያወጣች
መሆኑን በመጥቀስ ጉዳዩ መታየት ያለበት በሸሪያ ፍርድ ቤት ነዉ ሲሉ ተከራከሩ፡፡
የወረዳዉ ፍርድ ቤት ከሳሽ በሸሪያ ፍርድ ቤት ክስ መቀጠል እንዳለባት በመጥቀስ የንብረት
ድርሻ ክስ ዉድቅ ያደርግባታል፡፡ በይግባኝ ሰሚዉና በሰበር በመፅናቱ ጉዳዩ ለፌዴሬሽን
ም/ቤት ቀርቦ የህገ መንግስቱ አንቀፅ 34(5) እና የፌዴራል ሸሪያ ፍርድ ቤቶችን አም
ለማጠናከር የወጣ አዋጅ ቁጥር 188/92 አንቀፅ 4(2) በመጥቀስ ሙሉ ፈቃድ
ባልሰጠችበት በሸሪያ ፍርድ ቤት እንዲትዳኝ መወሰኑ የህገ መንግስታዊ ድንጋጌ ጥሰት ነዉ
ሲል ህገ መንግስታዊ ትርጉም ሰጥቶበታል፡፡
በዚህ ስልጠና በፍትሀብሄር ህጉና ተያያዥነት ባላቸዉ በሌሎች ህጎች የተመለከቱ የዉርስ
ህግ ድንጋጌዎችን በሰባት ምዕራፎች ከፍለን እንመከታለን፡፡
ምዕራፍ 1 የዉርስ ህግ በጠቅላላዉና የአወራረስ ሥርዓት
በኢትዮጵያ

1.1 ስለዉርስ ህግ በጠቅላላዉ

ዉርስ ምንድነዉ?
 ለዉርስ አንድ ወጥ ትርጉም መሰጠት ያስቸግራል
 ዉርስ አንድ ሰዉ ትቶት የሞተዉ ሀብት እና ዕዳ ነዉ፡፡
ዉርስ በህይወት ያሉ ሰዎች ከች ሀብት ላይ ሊደርሰን ይገባል የሚሉት ንብረት

ነዉ፡፡
ውርስ ምንድን ነው የሚለውን ትርጉም በሃገራችን የውርስ ሕግ ውስጥ በቀጥታ
ተተርጉሞ ባናገኘም ከሕጉ ጠቅላላ መንፈስ ግን ትርጉሙን መረዳት እንችላለን፡፡
ይህም ውርስ ማለት የአንድ በሞት የተለየን ሰው ንብረት እና ኃብት እንዲሁም
ሊተላለፍ የሚችሉ መብት እና ግዴታዎች በሕይወት ላሉ አንድ እና ከዚያ በላይ
ለሆኑ ሰዎች የሚተላለፍበት መንገድ ነው፡፡
የቀጠለ…

 እዉቁ የህግ መዝገበ ቃላት Black's Law Dictionary “succession is the transmission
of the rights and obligations of the des eased to the heirs, also the estates,
right and charges which a person leaves after his death” በማለት ይገልፀዋል፡፡
የቃሉ ትርጉም በግርድፉ “ውርስ ማለት የሟች መብትና ግዴታዎች እንዲሁም

ሃብት ፣በሃብቱ ላይ ያለው መብትና ግዴታ በሕይወት ላሉት ወራሾቹ

የሚተላለፍበት መንገድ ነው” በማለት ይገልፀዋል፡፡

 ዉርስ ከች አንፃር እና ከወራሾች አንፃር የተለያየ እይታ ቢኖረዉም ዉርስ ማለት ሰዉ
ትቶት ሲሞት በህይወት ላሉ ሰዎች የሚተላለፍ ሃብት ነዉ፡፡
የቀጠለ…

የዉርስ ህግ ምንድነዉ?
የውርስ ሕግ ጠቅለል ባለ አገላለፅ የሟች (አውራሽ) መብቶች እና ግዴታዎች በሕይወት ላሉት
ወራሾቹ የሚተላለፍበት መንገድ የያዘ ሕግ ነው፡፡ የሟች ውርስ መች እና እንዴት ይከፈታል፣
ወራሾች እነማን ናቸው፣ ወራሽነትን የሚያሳጡ ነገሮች ምንድን ናቸው፣ የሟች ኑዛዜ ምን
ማሟላት አለበት፣ ውርሱ እንዴት እና በማን ይጣራል፣ የውርስ ክፍያ እንዴት እና በማን
ይፈፀማል እና የመሳሰሉትን የሚመራ ሕግ የውርስ ሕግ ነው፡፡

ከላይ እንደተገለጸው ውርስ ማለት የሟችን መብቶችን እና ግዴታዎች ወደ ወራሾች


ማስተላለፍ ሲሆን ሂደቱም የተሟላ እንዲሆን የሚከተሉት ቅደም ተከተሎች ማየት ተገቢ
ነው፤
ሀ/ ወራሾችን ማጣራት (መውረስ የሚችሉ እነማን እነደሆኑ ማወቅ )፣
ለ/ ውርስ ማጣራት እና
1.2 የዉርስ ህግ እና መሰረታዊ ዓላማ

 የች ሀብት በህይወት ላሉ ሰዎች የሚከፋፈለብትን መርህ መቀየስ ሲሆን በዝርዝር


ህጎች ደረጃ ከሀገር ሀገር ይለያያል፡፡
 ምሳሌ ለምሳሌ በእንግሊዝ ዉርስ ህግ ሚስት ባüን ባል ደግሞ ሚስት መዉረስ
ትችላለች /ይችላል/ ነገር ግን በፈረንሳይ ሀገር ባልና ሚሰት አንዳቸዉ አንዳቸዉን
መወረስ አይችሉም፡፡ በደቡብ አፍሪካ ደግሞ ሚስት ወይም ባል ከጋራ ሀብት
የሚደርሳቸዉ ድርሻ አነስተኛ ከሆነ አንዳቸዉ ከአንዳቸዉ የዉርስ ንብረት ተካፋይ
የሚሆኑበት የዉርስ ስርዓት አለ፡፡
ምዕራፍ 2. የኢትዮጵያ የዉርስ አስተላለፍ ሥርዓት በጠቅላላዉ

2.1 የዉርስ ህግ ድንጋጌዎች አደረጃጀት

 የዉርስ ህግ ድንጋጌዎች አቀራረፅ በፍትሀብሄር ህጉ አምሰተኛ አንቀፅ አንቀፅ 826-


1125 ድረስ ያለ ሲሆን ድንጋጌዎቹን ለሁለት ከፍለን እናያለን፡፡ የዉርስ ህግ
ጠቅላላ መሪ የሆኑ ጠቅላላ የህግ ድንጋጌዎች እና ልዩ የህግ ድንጋጌዎች ናቸዉ፡፡
 የዉርስ ህጉ ጠቅላላ መሪ የሆኑ ጠቅላላ የህግ ድንጋጌዎች የሚባሉት ከ826-841
ድረስ ያሉት ሲሆኑ ለኑዛዜም ሆነ ያለኑዛዜ የዉርስ ስርዓት መሪ ደንብ በመሆን
በእኩልነት ተፈፃሚነት ያላቸዉ አጠቃላይ መርህ የሚያንፀባርቁ ድንጋጌዎች
ሲሆኑ ተከታዮቹ ደግሞ ዉርስ ለወራሾች የሚተላለፍበትን ዝርዝር ደንቦች የያዙ
የዉርስ ህጉን አብዛኛዉን ክፍል የሚሸፍኑ ናቸዉ፡፡
 የሁለቱ ክፍል ድንጋጌዎች መካከል አለመጣጣም ቢያጋጥመን ሁለቱ የህግ
ድንጋጌዎች ተቻችለዉ በሥራ ላይ እንዲዉሉ የማድረግ የህግ አተረጎም መርህን
መከተል ያስፈልጋል ነገር ግን በሁለቱ መካከል መሰረታዊ ልዩነት ሲያጋጥመን ለልዩ
የህግ ድንጋጌዎች ብልጫ በመስጠት ተፈፃሚ ማድረግ አለብን፡፡
2.2 የዉርስ መከፈትና በዉርስ ስለሚተላለፉ መብቶችና ግዴታዎች

2.2.1 ዉርስ የሚከፈትበት ጊዜና ሥፍራ


 ሰዉ ከተወለደበት ቀን አንስቶ እስከሞተበት ቀን ድረስ የህግ መብት
አለዉ፡፡/የፍ/ህ/ቁ/1;
 የች ዉርስ ተከፈተ የምንለዉ ች በህይወት ዘመኑ የነበረዉን መብት ተጠቅሞ
ያፈራዉ ሀብቱ ወይም ንብረቱ ባለቤት በማጣቱና ለግዴታዉም ተጠያቂ የሚሆን
ባለመኖሩ ህግ የችን መብትና ግዴታ ለሌሎች ለማስተላለፍ ስለች ንብረት
አስተዳደር ትኩረት ሰጥቶ ጥበቃ ማድረግ መጀመሩን የሚናመለክትበት ነዉ፡፡
 ች ህይወት ማለፉ ከተረጋገጠበት ቅፅበት አንስቶ ዉርስ ይከፈታል፡፡
 የች ዉርስ የሚከፈተዉ ች በሞተበት ጊዜ ዋና የመኖሪያ በነበረዉ ስፍራ ነዉ፡፡
ሟች ከመሞቱ በፊት ከአንድ በላይ የመኖሪያ ስፍራ የነበረው ቢሆን እንኳን ውርሱ
የሚከፈተው ሟች በሞተበት ጊዜ ዋና መኖሪያው በነበረው ስፍራ ነው፡፡ /የፍ/ህግ
ቁ.174-191/
የቀጠለ…

2.2.2 የች ዉርስ አከፋፈት በህግ መወሰኑ አስፈላጊነት


- የች ወራሽ ች ከመሞቱ አስቀድሞ በህይወት የነበረ
መሆኑን ለማረጋገጥ ቁጥር /230/ ፣
- የሟች ሃብትና ንብረት እንዲሁም ወራሾች በተለያየ ቦታ ሊገኙ
ስለሚችሉ ሁሉንም በአንድ ቦታ አጠቃልሎ ለማግኘት እንዲያመች
- በውርስ ላይ ክርክር ቢነሳ ጉዳዩን የመዳኘት ሥልጣን ያለውን ፍርድ ቤት
ለይቶ ለመወሰን እንዲቻል ውርስ የሚከፈተው ቦታ ተለይቶ መታወቅና
በሕግም መገለፅ አለበት፡
የቀጠለ…

ከዉርስ መከፈት ጋር ተያያዥ ጉዳዮች


 የች ዉርስ መከፈትና የች ወራሾች ነን የሚሉ ሰዎች የወራሽነት የምስክር
ወረቀት እንዲሰጣቸዉ በፍ/ህግ ቁጥር 996-1002 ድረስ ባለዉ ከሚያቀርቡት
አቤቱታ የተለየ ነዉ፡፡
 ዉርስ መከፈት የች ሞት ተከትሎ ቅፅበታዊ ሲሆን የወራሽነት የምስክር ወረቀት
ይሰጠኝ አቤቱታ ደግሞ ች ከሞተበት ጊዜ አንስቶ የህጉ የይርጋ ገደቡ
እስከሚገድበዉ የሚቀርብ ነዉ፡፡ /የፍ/ህ/ቁ./1000/
 አንዳአንድ የህግ ግንዛቤ የሌላቸዉ ሰዎች የች ዉርስ ተከፈተ የሚሉት የች አርባ
ቀን ካለፈ በላ ነዉ የሚል አስተሳሰብ አላቸዉ፡፡
 የች አርባ ቀን የች ቤተሰቦች ዘመዶች ተሰባስበዉ የች ንብረት፣በትዉሰት
የሰጣቸዉ ዕቃዎች፣የገንዘብ ብድር ወዘተ… ለማጣራት ምክክር የሚደረግበት
ሲሆን ከዉርስ መከፈት ይለያል፡፡
2.2.3 የች ዉርስ የሚከፈትበት ስፍራ በህግ የመወሰን ጠቀሜታ

 የግዛት ክልል ስልጣን ያለዉን ፍርድ ቤት ለመለየት / የፍ/ሥ/ሥ/ህግ ቁጥር 23 ሂሳቡ


በመጣራት ባለ ዉርስ ምክንያት ክርክር በተነሳ ጊዜ ክሱ የሚቀርበዉ የዉርሱ ክፍያ
በተጀመረበት ቦታ ለሚገኘዉ ፍርድ ቤት ነዉ፡፡/
 የዉርስ ክርክር የት መጀመር ይኖርበታል ለሚለዉ የፍ/ህ/ሥ/ሥ/ ህጉን አንቀፅ 23
መመልከት ተገቢ ነዉ፡፡ ይህ አንቀፅ 23 “ ሂሳቡ በመጣራት ላይ ባለ ዉርስ ምክንያት
ክርክር በተነሳ ጊዜ ክሱ የሚቀርበዉ የዉርሱ ክፍያ በተጀመረበት ቦታ ለሚገኘዉ
ፍርድ ቤት ነዉ ይላል፡፡”
 የዉርስ ሀብቱ በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙ በሆነ ጊዜ የሚነሱ ክርክሮች የውርሱ ክፍያ
በተጀመረበት ቦታ ለሚገኝ ፍ/ቤት የሚቀርቡና የሚስተናገዱ ይሆናሉ፡፡ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ.
23 /የሰ/መ/ቁ. 34076 ወ/ሮ ዘነበወርቅ ወልዱ ፀጋ እና እነ እማሆይ ድብቅነሽ ግዛው ሰኔ
10/2000 ገፅ 21 7
2.3 ከች ለወራሾች ሊተላለፉ የሚችሉና ሊተላለፉ የማይችሉ መብትና ግዴታዎች
/የፍ/ህ/ቁ.828/

 ለች ዘመዶች፣ባል ወይም ሚስት የሚሰጡ ጡረታዎች


 የካሳ ክፊያዎች /ምሳሌ ች በሚደርስበት የሞት አደጋ ለቤተሰቡና ለዘመዶቹ
ለወላጆቹ በመተዳደሪያ ረገድ ለደረሰባቸዉ ጉዳት ካሳ የተከፈለ/
 በሞት ጊዜ የሚከፈል የህይወት ኢንሹራንስ ገንዘብ ች ተጠቃሚዉን ያልወሰነ
ከሆነ ወይም ኢንሹራንስ ዉል አፈፃፀም የሚከፈሉ ገንዘቦች የዉርስ ንብረት ክፍል
ይሆናሉ፡፡ ተቃራኒ ሁኔታ ሲኖር የዉርስ ሀብት ክፍል አይሆኑም፡፡ (የፍ/ህ/ቁ.827(1)
እንዲሁም በንግድ ህጉ 701(2) ስማቸዉ በዉል ባይጠቀስም ወይም ተጠቃሚዉ
ማን እንደሆነ ፍንጭ ያልሰጠ እንደሆነ በዉሉ መሰረት የሚከፈለዉ ገንዘብ በዉርስ
ንብረት ክፍል እንደሚሆን የፍ/ህ/ቁ/ 827(1) ይደነግጋል፡፡
የቀጠለ…
 በፍትሀብሄር ህጉ ቁ.827(1) እና በንግድ ህጉ 701(2) መካከል ያለዉን ልዩነት እንዴት
ማስማማት ይቻላል? ሁለቱም ህጎች በመስከረም 1 1953 የወጡ ሲሆን የንግድ
ህጉ ስለ ህይወት ኢንሹራንስ ዉል ክፊያና የኢንሹራንሱ ተጠቃሚ የሚደነግግ
በመሆኑ ከጠቅላላዉ የዉርስ ህግ ድንጋጌ የበለጠ ተፈፃሚነት ሊሰጠዉ የሚገባዉ
ነዉ የሚሉ አሉ
 ሌሎች ደግሞ ዉርስ ህግን የሚመለከተዉ የፍትሀብሄር ህጉ ነዉ የሚሉም አሉ፡፡
 ሁለቱን አቻችሎ መተርጎም አስፈላጊ ነዉ የሚሉም አሉ፡፡ /ሁሉንም ተጠቃሚ
ማድረግ ይቻላል/
2.4 ለመዉረስ የሚያስፈልግ ችሎታ
 የች ወራሽ በመሆን የሚቀርቡት የተፈጥሮ ሰዎችና የህግ ሰዎች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡
አንድ ዉርስ ይገባኛል የሚል ተከራካሪ በህግ የተመለከቱትን ቅድመ ሁኔታዎችን
ሳያላ በስመ ተወላጅነት ወይም በኑዛዜ ስሙ ቢጠቀስም ወራሽ ሊሆን
አይችልም፡፡
 የመዉረስ ችሎታ ሲንል ችን ለመዉረስ የሚቀርቡ የተፈጥሮና የህግ ሰዉነት
ያላቸዉ ሰዎች በቅድሚያ ማላት የሚገባቸዉ መሰረታዊ ቅድመ ሁኔታዎች
1. የተፈጥሮ ሰዎች በሆኑ ጊዜ ሁለት ነገሮችን ማላት ይኖርባቸዋል፡፡
ሀ/ዉርስ ሲከፈት በህይወት ያለ መሆን ለ/ ለዉርስ የማይገባ አለመሆን
ናቸዉ፡፡ /የፍ/ህግ ቁጥር 830/
 ከዜግነት ጋር በተያያዘ የፍ/ህግ 837 መሰረት በመርህ ደረጃ ዜግነት በወራሽነት
ልዩነት አያመጣም ነገር ግን በቁ.391፣1089 የዉጭ ዜጎች በመንግስት ፈቃድ ካልሆነ
በስተቀር የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለሀብት ሊሆኑ አይችሉም፡፡ ሆኖም ይህ ድንጋጌ
ኢትዮጵያ ካወጣቻቸዉ የኢንቬስትመንት አዋጆችና ደንቦች ጋር ተጣጥመዉ
መታየት አለባቸዉ፡፡
የቀጠለ

 በዉርስ ህጋችን ች ሲሞት በህይወት የነበረ ሰዉ ሁል ጊዜ ለመዉረስ ችሎታ


አለዉ ማለት አይቻለም፡፡ / የፍ/ህ/ቁ.830/
 ችን ለመዉረስ ተጨማሪ መላት ያለባቸዉ ቅድመ ሀኔታዎች አሉ፡፤
 ወራሾች ችን ለመዉረስ ያልተገባ ነዉ የሚያሠኙ ተግባራትን ያልፈፃሙ
መሆናቸዉ መረጋገጥ አለበት፡፡ /የፍ/ህ/ቁ 838 እና 840. /፡፡
 በህግ በግልፅ ከተቀመጡ ተግባራትን ከመፈፀም ዉጭ ዳኞች ሌሎች ነጥቦችን
በማንሳት ያልተገባህ ነህ በማለት መወሰን አይችሉም፡፡
 በዚህ ጉዳይ ላይ የፍትሀብሄር ህጉ ድንጋጌ አሳሪ ወይም አስገዳጅ እንጅ አመልካች
አይደለም፡፡
 ለወራሽነት ያልተገባ መሆን /Anworthy of succeding the deceased/ እና
ከዉርስ መነቀል /Disherison/ በህግ የተለያዩ ፅንሰ ሀሳቦች ናቸዉ፡፡
 ለወራሽነት ያልተገባ መሆን በህግ የተከለከሉ ተግባራትን በመፈጸም የወራሽነት
ማጣት ሲሆን ከዉርስ መነቀል ግን በች ኑዛዜ ቃል መሰረት ከዉርስ ዉጭ
የሚደረግበት ነዉ /የፍ/ህ/ቁ. 939/፡፡ የመጀመሪያዉ ምንጭ ህግ ሲሆን የሁለተኛዉ
ምንጩ የች ኑዛዜ ቃል ነዉ፡፡
የቀጠለ…


ለዉርስ ያልተገባ ነዉ የሚያሠኙ ምክንያቶች በሁለት የተከፈሉ ሲሆን
የመጀመሪያዉ የወንጀል ድርጊቶችን ፈፅሞ በፍርድ ጥፋተኛ መባልና መቀጣት
/የፍ/ህ/ቁ.838/ ሲሆን ሁለተኛዉ ደግሞ በህጉ በግልፅ የተመለከቱት ሌሎች
ተግባራትን መፈፀም /የፍ/ህ/ቁ.840/ ናቸዉ፡፡
 እነዚህ ችን ለመዉረስ ያልተገባ ነዉ የሚያሠኙ ተግባራት 1ኛ በፍ/ህ/ቁ.838
እንደተመለከተዉ ችን ወይም ወደ ታች የሚቆጠር ተወላጆችን ወይም ወደ ላይ
የሚቆጠሩ ወላጆች አንዱን ወይም የችን ባል ወይም ሚስት አስቦ በመግደል
ወይም በመግደል ሙከራ የተፈረደበት ወይም በሀሰት በመወንጀል በመመስከር
ከነዚህ ሰዎች መካከል አንዱን የሞት ፍርድ ወይም ከ10 ዓመት የበለጠ ፅኑ እስራት
ቅጣትን ለማስከተል የሚያሰጋ ሆኖ የተቀጣ ማንኛዉም ሰዉ እንዲሁም በፍ/ህ/ቁ.
840 የችን ሰዉነት ሁኔታ ምክንያት በማድረግ አዉራሹ ከመሞቱ በፊት ባሉት 3
ወራት ኑዛዜ እንድያደርግ ፣እንዳይለዉጥ ፣እንዳዳይሽር ያደረገ እንድሁም አስቦ
ያለች ፈቃድ የመጨረሻ ኑዛዜን ያበላሸ፣እንዳይገኝ ያደረገ፣ ያጠፋ ወይም ጉዳዩን
በማወቅ በሀሰት ኑዛዜ የተጠቀመ የወራሽነት መብት ያጣል፡፡
የቀጠለ…

 ይህ ግን ተፈፃሚ የማይሆንባቸዉ ሁለት ምክንያቶች አሉ፡፡


1. ወራሽ የሆነ ሰዉ ወንጀሉን ወይም የወንጀል ሙከራዉን ያደረገዉ
አዉራሽ ከሞተ በላ ከሆነ
2. ከላይ የተጠቀሱ ሁለቱንም ዓይነት ድርጊቶች ች ግልፅ በሆነ ፅሁፍ
ይቅርታ ያደረገለት እንደሆነ ወይም በኑዛዜ የሚደረግ ስጦታ ሲሆን
ች በኑዛዜ ስጦታዉን ያደረገዉ ወራሽ መሆን እንዳይገባዉ
የሚያደርገዉ ነገር ከተፈፀመ በላና ጉዳዩንም አዉቆት ከሆነ ወራሽ
የወራሽነት መብት አያጣም፡፡
ምዕራፍ 3 የዉርስ ስርዓት የሚፈፀመዉ ቢያንስ በሶስት ዓይነት መንገዶች

3.1 ጠቅላላ
 ች ከሞተ በላ የዉርስ ስርዓት የሚፈፀመዉ ቢያንስ በሶስት ዓይነት መንገድ
እንደሆነ የፍ/ህጉ ይደነግጋል፡፡
-1ኛዉ ች የተወዉ ኑዛዜ ካለ በኑዛዜ
- 2ኛዉ ኑዛዜ ከሌለ ያለ ኑዘዜ እንዲሁም ች በከፊል
ኑዛዜ የተወና በከፊል ንብረቱ ያለ ኑዛዜ መከፋፈል
እንዳለበት የተወዉ ኑዛዜ ካለ ዉርሱ በከፊል በኑዛዜ
- በከፊል ያለ ኑዛዜ ይፈፀማል፡፡/ፍ/ህ.ቁ.829/

3.2 ያለኑዛዜ ዉርስ /ፍ/ህ/ቁ. 842-856


 በመርህ ደረጃ በዉርስ ህግ ች ሲሞት የተወዉ ኑዛዜ ካለ ዉርስ በኑዛዜዉ
መሰረት ይፈፀማል፡፡ ች ሁሉን ንብረት በኑዛዜ ካደላደለ ዉርስ ያለኑዛዜ
ለመፈፀም አይቻልም፡፡
የቀጠለ

 ዉርስ ያለኑዛዜ በሚፈጸምበት ጊዜ ሶስት ዓይነት የአወራረስ ስርዓቶች ያጋጥማሉ፡፡


- 1ኛዉ የተለመደ ተፈጥሮአዊ አወራረስ /Natural Succession/
የሚባል ሲሆን የሚፈፀመዉ በሁለት የተፈጥሮ ሰዎች መካከል ነዉ፡፡
ወራሾቹ የች የስጋ ዘመዶች ናቸዉ፡፡ በህጋችን በአብዛኛዉ ያለ
ኑዛዜ የሚደረግ ዉርስ ይህን ይከተላል፡፡ /የፍ/ህ/ቁ. 842-856 /
- 2ኛዉ ያልተለመደ አወራረስ /Irregular Succession/ሲሆን ች
የተወዉ ኑዛዜ ከሌለና ወራሽ የሚሆኑ የስጋ ዘመዶች ከሌሉ የች
ወራሽ መንግስት ወይም በህግ በግልፅ የተጠቀሰ የበጎ አድራጎት
ድርጅት እንዲሆን የሀገሪቱ ህግ የሚፈቅድ ሲሆንና ዉርሱም በዚሁ
መንገድ የሚፈፀምበት ነዉ፡፡ /የፍ/ህ/ቁ. 851-852 /
የቀጠለ


3ኛዉ የዉርስ ስርዓት ክፍት የዉርስ ሁኔታ /Vacant Succession/ ሲሆን ይህም ች
ኑዛዜ ካልተወ፣ያለኑዛዜ ወራሽ ከሌለዉና የሀገሪቱ ህግም በዚህ ሁኔታ
ንብረቱ ለማን መተላለፍ እንደሚገባዉ ሳይደነግግ ክፍት አድርጎ ሲተዉ
ነዉ፡፡ በመሆኑም የኢትዮያ የዉርስ ህግ የአወራረስ ስርዓት 1ኛዉንና 2ኛዉን
የአወራረስ ስርዓት የተከተለ ይመስላል፡፡

 ያለኑዛዜ ወራሽነት ፅንሰ ሀሳቡ የተመሰረተዉ በስጋ ዝምድና ላይ ነዉ፡፡


ከች ጋር የስጋ ዝምድና የሌለዉ ከጉድፈቻ ልጅ በስተቀር
/የፍ/ህ/ቁ. 836./ ያለኑዛዜ ወራሽ መሆን አይችልም፡፡
 የች ልጆች በመጀመሪያ ደረጃ የች ወራሾች ናቸዉ፡፡ /ፍ/ህ/ቁ.842 /1/
 የች ልጆች ወይም ከልጆቹ አንዱ የሞተ እንደሆነና ወደታች የሚቆጠር
ተወላጆች ትተዉ እንደሆነ በነሱ ምትክ ሆነዉ ይወርሳሉ፡፡ /የፍ/ህ/ቁ/842/3/
 ች ወደ ታች የሚቆጠር ተወላጅ ያልተወ እንደሆነ አባትና እናት ወራሾች
ይሆናሉ፡፡ የፍ/ህ/ቁ.843/
3.3 የኑዛዜ ዉርስ

 የኑዛዜ ዉርስ በፍ/ህ/ቁ 857-941 ድረስ በሚሸፍነዉ ዉስጥ ከፍ/ህ/ቁ. 857-908


ድረስ ያሉት አንድ ኑዛዜ ኑዛዜ ነዉ ተብሎ በህግ ፊት ዉጤት ለመስጠት መላት
ያለባቸዉን የስረ ነገር ሁኔታዎችን የያዙ ናቸዉ፡፡
 በኑዛዜ ዉርስ አንድ ኑዛዜ ማላትያለባቸዉ እነዚህ የስረ ነገር ሁኔታዎች በሁለት
ሊመደቡ የሚችሉ ናቸዉ፡፡
 የመጀመሪያዉ ኑዛዜዉን ሁለንተናዊ ወይም ተፈጥሮአዊ የሚባሉ አስፈላጊ
ነገሮችን የሚደነግጉ ሲሆኑ ይዘታቸዉም ተናዛዡ ኑዛዜ በሚያደርግበት ሰዓት
የነበረን የአዕምሮ ሁኔታ ወይም ኑዛዜ የማድረግ ሀሳብ የነበረ መሆኑን የሚመለከቱ
ናቸዉ፡፡ ምሳሌ ኑዛዜ ጥብቅ የተናዛዡ የግል ሥራ መሆኑን /ፍ/ህ/ቁ. 857/ ፣ /የጋራ
ኑዛዜ ስለመከልከሉ የፍ/ህ/ቁ 858/፣ ችሎታ አካለ መጠን ያላደረሰ /ቁ.880/ ( በፍርድ
የተከለከለ ሰዉ /ቁ.861/፣በህግ የተከለከለ ሰዉ /ቁ.864)፣ /ህገ ወጥ የኑዛዜ ፍ/ህ.ቁ.
866/ የማይቻል ኑዛዜ /የፍ/ህ/ቁ.665/፣ኃይል /ቁ. 667/፣የመንፈስ መጫን ቁ.668
ወዘተ… ናቸዉ
 የተናዛዡን የአዕምሮ ሁኔታ ለማወቅ ኑዛዜ ጉዳይ የሚነሳዉ የተናዛዡን ሞት
ተከትሎ በመሆኑ እንዴት ማወቅ ይቻላል የሚለዉ አከራካሪ ነዉ፡፡
የቀጠለ
 ምሳሌ የማይቻል ኑዛዜ በሰበር መ/ቁ 18394 ቅፅ 8 ወ/ሮ ዝናሽ በቀለ እና ወ/ሮ ሀረገ
ወይን በቀለ መካከል ባለዉ የኑዛዜ ይፍረስ ክርክር ወ/ሮ ዝናሽ ች አባታቸዉ
የመንገስት ዉርስ ቤት በኑዛዜ ሰጥተዉ የማይፈፀም ኑዛዜ በመሆኑ ፈራሽ እንዲሆን
ክስ አቅርበዉ ተከሳሽ ደግሞ በቤቱ አበል እየተከፈለበት በመሆኑ ሊፈፀም የሚችል
ነዉ በማለት ተከራክረዋል፡፡ በመጨረሻም ሰበር ችሎቱ ሊፈፀም የማይችል ነዉ
በማለት የስር የወረዳዉ ፍ/ቤት ኑዛዘዉ ይፀናል አለ የከፍተኛዉና የጠቅላይ ፍ/ቤት
ኑዛዘዉ ሊፈርስ ይገባል ሲሉ ወሰኑ የደቡብ ክ/ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ችሎት የከፍተኛዉና
የጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ዉሳኔ በመሻር ኑዛዘዉን አፀና፡፡ የፌዴራል ሰበር ችሎት
የፍ/ህ/ቁ. 1047 (1‚2 ) እና የፍ/ህ/ቁ 913 የኑዛዜ ስጦታና የክፍያ ደንብ የሚለዉን
በማንሳት አመልካች ወራሽ በመሆ አባት እያወቁ መብት የሌለን ቤት
በመስጠታቸዉ ይህ ደግሞ ስጦታ ሳይሆን የክፊያ ደንብ በመሆኑ የክፊያ ደንብ
የሚገዛዉ ድንጋጌ 913 ሳይሆን 1117 እና 1123(1) በመሆኑ ወራሽ 1/4ኛ የበለጠ
ጉዳት ከደረሰ ይህ እንድሻሻል መጠየቅ የሚችል በመሆኑ በዚሁ መንገድ ተመርምሮ
እንድወሰን አሻሽሎ ለስር ፍርድ ቤት መለሰዉ፡፡
የቀጠለ…

 ኑዛዜ አድራጊዉ በሙሉ ሀሳብና ፍላጎት ኑዛዜዉን ያደረገዉ መሆኑን ለመረዳት


ከግምት ዉስጥ የሚገቡ ሁኔታዎች
- ተናዛዡ ራሱ በሙሉ ሀሳብ ኑዛዜ የፈፀመ መሆኑ
- የተናዛዡ ኑዛዜ የመፈፀም ችሎታ
- ኑዛዜዉ በመገደድ ወይም በስህተት ወይም በመንፈስ መጫን
ያልተድረገ መሆኑ
- ኑዛዜዉ ህጋዊ መሆኑ ናቸዉ፡፡
 ሁለተኛዉ ለኑዛዜ ዋጋ መኖር አስፈላጊ ሁኔታ ኑዛዜዉ በህጉ የተደነገገዉን ፎርም
አልቶ የመገኘቱ ሁኔታ ነዉ፡፡ የኑዛዜ ፍርም ለኑዛዜ ዋጋ ዋነኛዉ አስፈላጊ ነገር
ነዉ፡፡ የኑዛዜ ፎርም የሚደነግጉ ድንጋጌዎች እጅግ ጥብቅና አስገዳጅ ናቸዉ፡፡ ይህ
ማለት የኑዛዜ ፎርማቶችን ኑዛዜ አድራጊዉ ሲፈልግ የሚከተላቸዉ አሊያም
የሚተዋቸዉ አይደሉም፡፡ የኑዛዜ ፎርም አልቶ አለመገኘት ኑዛዜዉን በህግ ፊት
ዋጋ ያሳጣዋል፡፡
3.1.1 የኑዛዜ ዓይነቶች
በኢትዮጵያ የዉርስ ህግ ኑዛዜ በሶስት ዓይነት ፎርም ሊፈጸም እንደሚችል
ይደነግጋል፡፡
ይኼም 1. በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ
2. በተናዛዥ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜ
3. በቃል የሚደረግ ኑዛዜ
ከላይ ከተጠቀሱ የኑዛዜ ዓይነቶች በተጨማሪ “የቁም ኑዛዜ ስጦታ” የሚባለዉ ስጦታ ነዉ
ወይስ ኑዛዜ ነዉ? ተፈፃሚ የሚሆነዉስ መቼ ነዉ? አንድ ሰዉ የቁም ኑዛዜ ስጦታ በሚል
ሰነድ አስቀምጠዉ ቢሞቱ ይህ ሰነድ የስጦታ ሰነድ ነዉ ወይስ የኑዛዜ ሰነድ?
በዚህ ጉዳይ ላይ በፌዴራል ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ችሎት የተወሰነ አንድ ዉሳኔ እንመልከት፡፡
የሰ/መ/ቁ. 32337 ቅፅ 5 ወ/ሮ ፀሀይነሽ ይህደጎ እና ወ/ሮ ትህሽ በርሄ መካከል በተደረገ
የቁም ኑዛዜ ስጦታ ሰነድ ክርክር ሰበር ችሎት ያነሳቸዉ ነጥቦች ስጦታ ዓይነት
በኢትዮጵያ ህግ፣ በማይነቀሳቀስ ንብረት ላይ የሚደረግ ስጦታ በግልፅ ኑዛዜ አደራረግ
ስርዓት በፍ/ህ/ቁ. 2443 መሰረት የሚደረግ መሆኑ፣ የቁም ኑዛዜ ስጦታ ከተባለ
የሚፈፀመዉ ከኑዛዜ አድራጊ ሞት በላ የሚፈፀም መሆኑን ይጠቅሳል፡፡
የቀጠለ…
3.1.1.1 በግልፅ የሚደረግ ኑዛዜ /የፍ/ህ/ቁ.881
 ይህ ኑዛዜ ተናዛዡ ኑዛዜዉን ሲፈፅም ሌሎች ሰዎች ወይም እማኞች ባሉበት የሚደረግ ለህብረተሰቡ ግልፅ
የሆነኑዛዜ ነዉ፡፡ ስለግልፅ ኑዛዜ ሲናወራ የዉርስ ህጉ ሁለት ድንጋጌዎች አንድ ላይ በትክክል መታየት
አለባቸዉ፡፡ የመጀመሪያዉ በአንቀፅ 881(1) እና ሲሆን ሁለተኛዉ ንዑስ (2) ናቸዉ፡፡

በዚህ መሰረት ግልፅ ኑዛዜ ስለመኖሩ የሚከተሉትን አራት ነገሮች መላት አለባቸዉ፡፡
1. ተናዛዡ እየተናገረ የሚናገረዉ ሳይጨመር ሳይቀነስ ሳይለጥ ሌላ
ሰዉ የፃፈዉ ወይም ተናዛዡ ራሱ የፃፈዉ
2. አራት ምስክሮች ባሉበት በተናዛዡና በአራት ምስክሮች ፊት
መነበብ እና ወድያዉኑ መፈረም
3. የማንበብ ፎርማሊቲ ማላቱን ማመልከት
4. ኑዛዜዉ የተፃፈበትን ቀን ማመልከት

በሌላ በኩል ግን በግልፅ የተደረገዉ ኑዛዜ የተፈፀመዉ አንድ ዳኛ ወይም ዉል


ለማዋዋል ስልጣኝ በተሰጠዉ ሰዉ ፊት ከሆነ ሁለት ምስክሮች ከተገኙበትና
ተነብቦላቸዉ ከፈረሙበት በቂ ነዉ ፡፡
የቀጠለ
 በአንድ ግልፅ ኑዛዜ ላይ የተፃፈበት ቀን፣አራት ምስክሮች ስም ፊርማ እና ኑዛዜዉ መስማታቸዉና
ማየታቸዉ ከተገለፀ ግን የመነበቡን ስርዓት የሚገልፅ ነገር ባይኖር ኑዛዜዉ ፎርማሊቲዉን
አላላም ሊባል ይችላል? የሰበር መ/ቁ. 17429 ºð/¤ ‹” ሆርዶፋና ተስፋዬ ከበደ መካከል የተደረገ
የዉርስ,ክርክር እንደ ምሳሌ ሊጠቀስ ይችላል ፡፡ በዚህ ዉሳኔ አብላጫዉ ኑዛዜዉን ሲናዘዙ
ሰምተናል አይተናል ማለት ምስክሮች ኑዛዜዉን ያዩትና የሰሙት ኑዛዜዉ ሲደረግና የተፃፈዉ
ሲነበብ ነዉ በማለት ሲተረጉሙ በልዩነት የመዘገበዉ ዳኛ ግን አይተናል ሰምተናል የሚለዉ ቃል
ኑዛዜዉ ሲደረግ እንጅ ሲነበብ መሆኑን አያሳይም የሚል ወስል፡፡ የቱ ትክክል ነዉ ትላላችሁ

 አካለመጠን ያደረሱ በፍርድ ወይም በህግ ያለተከለከሉ ምስክሮች መሆን


ኑዛዜዉ የተፃፈበትን ን ማወቅ የተፃፈዉንም ለመስማትና
ለማንበብ ችሎታ መኖር /ይህ ግዴታ አይደለም የሚሉም አሉ፡፡/
 ከላይ የተጠቀሱ መስፍርቶች ጥብቅና አስገዳጅ ናቸዉ፡፡

ምሳሌ በስተርሚ ተተርጉሞ ቢፃፍስ በሶስት ምስክሮች ፊት


ቢደረግስ ለምስክሮች ተነብቦ ግን
በኑዛዜዉ ፅሁፍ ይህ ባይገለፅስ
የቀጠለ…

3.1.1.2 በተናዛዡ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜ /ፍ/ህ/ቁ. 884- 891/


 በተናዛዡ በራሱ ፅሁፍ የሚደረግ ኑዛዜ ህጋዊ ዉጤት የሚኖረዉ
- ራሱ በሚረዳዉ ን ማንበብና መፃፍ አለበት
- ኑዛዜዉን ሙሉ በሙሉ በራሱ የእጅ ፅሁፍ ፣ ቀኑን፣ ፅሁፉ ኑዛዜ
መሆኑን በግልፅ አመልክቶ፣ ሲሆን ከአንድ ገፅ በላይ ሲሆን
በእያንዳንዱ ገፅ ቀኑን መፃፍና መፈረም አለበት፡፡/ቁ.884./
- ተናዛዡ በኮምፒዩተር የፃፈዉ ከሆነ በኮምፒዩተር የፃፈዉ ራሱ
መሆኑን በእጅ ፅሁፍ ማመልከት ይኖርበታል፡፡ ይህ ካልተገለፀ
ኑዛዜዉ ዉጤት አይኖረዉም፡፡ ቁ›885/
- ህጉ ምስክሮች እንደሚኖሩ አላመለከተም፡፡
የቀጠለ

3.1.1.3 በቃል የሚደረግ ኑዛዜ /ፍ/ህ/ቁ. 892-894/


 ማንኛዉም ሰዉ ሞቱ ጊዜ እንደደረሰ ተሰምቶት ሁለት አካለ መጠን የደረሱ የፍርድና የህግ
ክልከላ ባልተደረገባቸዉ ምስክሮች ፊት ያለ ፅሁፍ በቃል ብቻ የሚያደርገዉ ኑዛዜ ነዉ፡፡
 የቃል ኑዛዜ ህጋዊ ዉጤት የሚኖረዉ
- የመሞቻ ጊዜ መድረሱ በርግጥም የተሰማዉ መሆን
- ሁለት ምስክሮች ፊት መሆን
- በቃል ኑዛዜ የሚደረግባቸዉ ነገሮች የቀብር ወጭ መመሪያ
መስጠት፣የእያናዳንዱ ዋጋ ከ500 ብር ያልበለጠ ልዩ የኑዛዜ ስጦታ
ማድረግ ፣አካለ መጠን ላለደረሱ ልጆች አስተዳደሪወይም ሞጊዚት
መሾም ይችላል፡፡
- በቃል ኑዛዜ ከ500 ብር በላይ ከተደረገ በ500 ብር ልክ ይቀነሳል፡፡
ፍ/ህ/ቁ/894/1/
- በፍ/ህ/ቁ. 893 ከተመለከቱት ዉጭ የሚደረግ ኑዛዜ ፈራሽ ነዉ፡፡
የቀጠለ…
3.2 የኑዛዜ መሻርና ዉድቅ መሆን
3.2.1 የኑዛዜ መሻር
 በኢትዮጵያ የዉርስ ህግ ኑዛዜ በተገቢዉ ሁኔታ ተዘጋጅቶ የተቀመጠ ኑዛዜ እስካልተሻረ ድረስ
ፀንቶ ይኖራል፡፡ ይሁን እንጅ ኑዛዜ አድራጊ ከመሞቱ በፊት በማናቸዉም ጊዜ መሻር
ይችላል፡፡ ኑዛዜ ላለመሻር የተገባ ግዴታ ቢኖር እንን እስከመቼዉም ጊዜ ድረስ በከፊልም
ሆነ በሙሉ ከመሻር አይከለከልም፡፡ ኑዛዜ በግልፅ ወይም በተዘዋዋሪ መንገድ ሊሻር
ይችላል፡፡
 በዉርስ ህጋችን ኑዛዜ በሚከተሉት መንገዶች ሊሻር እንደሚችል ተደንግል
1. በግልፅ መሻር -
ኑዛዜዉን በግልፅ በመሻር ይህም በሁለት መንገድ ሊሆን ይችላል፡፡ 1ኛዉ
ተናዛዡ ኑዛዜዎች ዋጋ ያላቸዉ እንደሆኑ በሚያስፈልገዉ ፎርም ዓይነት
ግልፅ አድርጎ በማሳወቅ ሲሆን ሌላዉ ደግሞ ከፊተኛዉ ኑዛዜ ጋር አንድ
ላይ ሊፈፀም የማይችል ሌላ ኑዛዜ ያደረገ እንደሆነ ነዉ፡፡
2. በተዘዋዋሪ መንገድ መሻር
- ኑዛዘዉን በማጥፋት ወይም በመሰረዝ
- በኑዛዜ የተሰጠን ነገር በሌላ በመቀየር
- ኑዛዜ ከተደረገ በላ ልጅ በመዉለድ
-ከኑዛዜ በላ ፍች መከሰት
የቀጠለ..

እዚህ ላይ የሚነሳዉ ክርክር ኑዛዜ መሻር የሚችለዉ ተናዛዡ ብቻ ነዉ፡፡ ነገር ግን ሲሽር በምን መንገድ
ይሽራል የሚለዉ ነዉ፡፡ በፍ/ህ/ቁ. 898 /1/ ተናዛዡ ኑዛዜዎቹ ዋጋ ያላቸዉ እንደሆኑ በሚያስልፈገዉ
ፎርም ዓይነት ግልፅ አድርጎ በማሳወቅ ኑዛዜዉን የሻረዉ እንደሆነ ነዉ ይላል፡፡ እዚህ ላይ ዋጋ ያላቸዉ
እንደሆኑ በሚያስፈልገዉ ፎርም የሚለዉ አባባል በቃል የተደረገን በቃል በግልፅ የተደረገን በግልፅ በራስ እጅ
ፅሁፍ የተደረገን በራስ እጅ ፅሁፍ በተደረገ ፎርም ዓይነት ብቻ ነዉ ወደሚለዉ ትርጉም ይወስደናል፡፡
በመሆኑም ከኑዛዜ መሰረታዊ ባህሪይ በመነሳት መተርጎም ያለብን የተናዛዡን ኑዛዜ የመሻር ስልጣን
በሚያጣብብ መልኩ ነዉ ወይስ ሰፋ ባለ ሁኔታ የሚለዉ መታየት አለበት፡፡
ብዙዎች የሚስማሙበት ግን ች ከሞተ በላ እንዳይፈፀም የሚፈልገዉን ኑዛዜ በግልፅ እስከሻረ ድረስ
የኑዛዜ ህጉን ድንጋጌ አጥብቦ በመተርጎም ዉጤት መስጠት ተገቢ አይደለም የሚል ነዉ፡፡ በዚህ ላይ
በሰ/መ/ቁ. 96364 በቅፅ 17 በወ/ሮ እልፍነሽ ወርቁና በወ/ሮ ኤልሳበጥ አስራት መካከል በተደረገ ክርክር
አንድ ተናዛዥ ኑዛዜዉን መሻር ሲፈልግ በማያሻማ ሁኔታ በመግለፅ ከሻረ ኑዛዜዉ ዋጋ ያላቸዉ እንደሆኑ
በሚያስፈልገዉ ፎርም ዓይነት ግልፅ አድርጎ አልሻረም ሊባል እንደማይቻል ተወስል፡፡

ኑዛዜዉን በተዘዋዋሪ መንገድ የመሻር መገለጫዎች ኑዛዘዉን ማጥፋት ፣ መሰረዝ ወይም በኑዛዜ
የተሰጠን ነገር ለሌላ ማስተላለፍ ሲሆኑ ተናዛዡ እነዚህን ግዙፍ ተግባራት ካከናወነ ኑዛዜዉን ለመሻር ግልፅ
ፍላጎት እንዳለዉ ይገመታል፡፡ የፍ/ህ/ቁ 899/2/ 899/3/
ነገር ግን እነዚህ የህግ ግምቶች ሊስተባበሉ የሚችሉ የህግ ግምቶች በመሆናቸዉ በሌላ ተቃራኒ ማስረጃ
ማስተባበል ይቻላል፡፡
3.2.2 ኑዛዜ ዉድቅ መሆን
 ኑዛዜ ዉድቅ መሆንና ኑዛዜ መሻርን አንድ አድርጎ መመልከት አለ፡፡ ሁለቱ የተለያዩ ፅንሰ ሀሳቦች ናቸዉ፡፡
 ኑዛዜ መሻር በተናዛዡ የሚፈፀም ተግባር ሲሆን ኑዛዜ ዉድቅ የሚሆነዉ በዉርስ ህግ ድንጋጌዎች ነዉ፡፡ ኑዛዜ ዉድቅ
የሚሆንባቸዉን ሁኔታዎችን የሚደነግገዉ ህገ አዉጭዉ ነዉ፡፡
 በዉርስ ህጉ ኑዛዜ ዉድቅ የሚሆንባቸዉ ሁኔታዎች
1. የቃል ኑዛዜ ሲሆን ኑዛዜ ያደረገዉ ሰዉ ኑዛዜ ካደረገበት ጊዜ ጀምሮ በህይወት መኖር

2 ተናዛዡ በህግ እንደፈፅም የታዘዘዉን አለማድረግ ምሳሌ


በተናዛዡ እጅ ፅሁፍ የተደረገ ኑዛዜ በተደረገ በ7 ዓመታት
ዉስጥ ለማዋዋል ስልጣን ባለዉ አካል ዘንድ ወይም በፍርድ
ቤት መዝገብ ቤት ያልተቀመጠ ሲሆን ኑዛዜዉ ዉድቅ
ይሆናል፡፡ የፍ/ህ/ቁ. 907
3- ኑዛዜዉ ከተደረገ በላ የተፈጠሩ ክስተቶች ምሳሌ ተናዛዥ
ኑዘዜ ካደረገ በላ ልጅ ከተወለደ ወይም አንድ ተወላጅ ተወልዶ
በተተኪነት ዉርሱን ለመቀበል ፈቃደኛ ከሆነ፣
4- ባል ለሚስቱ ወይም ሚስት ለባü ኑዛዜ ካደረጉ በላ ጋብቻዉ በሞት
ሳይሆን በሌላ ምክንያት የፈረሰ እንደሆነ
5- ኑዛዜ የተደረገለት ሰዉ ከተናዛዡ በፊት የሞተ ወይም ኑዛዜዉን
ለመቀበል ያልቻለ ወይም ያልፈቀደ እንደሆነ የሚሉ ናቸዉ፡፡
የቀጠለ…

ከላይ የተጠቀሱ ኑዛዜዉ ከተደረገ በላ የተፈጠሩ ክስተቶች ጋር ተያይዞ ጥንቃቄ መወሰድ
ያለባቸዉ ነጥቦች
 ች ኑዛዜ ካደረገ በላ ልጅ ቢወለድም ዳኞች ኑዛዜዉን አይተዉ በፍ/ህ/ቁ.905 መሰረት
ኑዛዜዉ በከፊል ዉጤት እንድኖረዉ የማድረግ ስልጣን አላቸዉ፡፡
 ከተናዛዡ በፊት የሞተዉ ሰዉ ጠቅላላ የኑዛዜ ስጦታ የተደረገለት ሲሆን የኑዛዜ ስጦታዉ
ተጠቃሚዉ ከተናዛዡ ቀድሞ ቢሞትም የእሱ ተተኪዎች በዉርሱ ሊከፈሉ እንደሚችሉ
እንዲሁም የልዩ ኑዛዜ ስጦታ ተደርጎለት ከሆነ ች የስጋ ዘመድ ወራሽ በማጣቱ ንብረት
ለመንግስት የሚገባ በሆነ ጊዜ የልዩ የኑዛዜ ስጦታ ተጠቃሚዉ ወራሾች እሱን ተክተዉ በች
ዉርስ ሊካፈሉ እንደሚችሉ የፍ/ህ/ቁ.908 ይደነግጋል፡፡
የቀጠለ…

3.4 ኑዛዜ መኖሩን ስለማስረዳት


 የኑዛዜ ቃልና ይዘት አስመልክቶ ማን ማስረዳት እንዳለበትና ምን አይነት
ማስረጃዎችን ማቅረብ እንደሚገባዉ በዉርስ ህግ ዉስጥ ልዩ ድንጋጌዎች
ተደንግገዋል፡፡
 በፍ/ህ/ቁ.896 መሰረት የኑዛዜ ተጠቃሚዉ ች በህይወት ዘመኑ ለእሱ ጥቅም ያደረገዉ
ኑዛዜ ስለመኖሩ የኑዛዜዉ ቃልና ይዘት ምን እንደሆነ የማስረዳት ሸክም አለበት፡፡ በመሆኑም
የኑዛዜ ተጠቃሚዉ
- ች በህግ ፊት ዉጤት ያለዉን ኑዛዜ የፈፀመ መሆኑን
- የኑዛዜዉን ቃልና ይዘት
- እሱ በኑዛዜዉ ተጠቃሚ መሆኑን ማስረዳት አለበት
የኑዛዜ ጉዳይ ላይ በሚቀርቡ ክርክሮች እያንዳንዱ መስፍርት መላቱ መመዘን ያለበት የኑዛዜዉን
አጠቃላይ ሁኔታ በመመልከትና ተናዛዥም ሆነ ምስክሮች በኑዛዜ ባሰፈሩት ቃላትና ሀረጎች ነዉ፡፡
የቀጠለ…

 የዉርስ ህጉ የማስረዳት ሸክም ብቻ ሳይሆን ለምን ዓይነት ኑዛዜ ምን ዓይነት ማስረጃ


ሊቀርብ እንደሚገባም ጥብቅ የሆነ መስፍርት አስቀምል፡፡
ለምሳሌ በግልፅ የተደረገ ኑዛዜና በተናዛዡ እጅ የተደረገ ኑዛዜ መኖሩን ለማረጋገጥ መቅረብ
የሚገባዉ የኑዛዜዉ ሰነድ ዋናዉ ወይም ዉል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠዉ ሰዉ ዘንድ ወይም በፍርድ
መዝገብ ሹም ትክክለኛኘቱ የተረጋገጠ ኮፒ መቅረብ እንዳለበት /የፍ/ህ/ቁ.897/1/ ይደነግጋል፡፡
ከሁለቱ ዉጭ ሌላ ሊቀርብ አይችልም፡፡ የፍ/ህ/ቁ.897/2/ ከላይ በተጠቀሰዉ ስልጣን በተሰጠዉ አካል
ያልተመሰከረለት ኮፒ ሊቀርብ እንደማይችል አስገዳጅ ድንጋጌ ተደንግል፡፡
በተለይ የኑዛዜ ሰነድ ቢጠፋ ቢበላሽ ህጉ ያስቀመጠዉ መፍትሔ ያጠፋዉን ሰዉ በኑዛዜዉ ከች
ሊገኝ ባለዉ ጥቅም ያህል ካሳ ክስ ማቅረብና ማስከፈል እንደሆነ በፍ/ህ/ቁ.897/3/ ላይ ይናገራል፡፡
የቀጠለ…

በዚህ በሰነድ ማስረጃ ላይ ክርክር ቢነሳ በተለይም በሰነዱ ላይ ያለዉ ፊርማ የች
አይደለም ቢባልና ሰነዱ ለፎረንስክ ቢላክ ፎረንስክ መረማሪዎች ፊርማዉ የማን እንደሆነ
ለመለየት አልተቻለም የሚል ምላሽ ሰጡ፡፡ ፍርድ ቤቱ በሰነዱ ላይ የፈረሙ ምስክሮችን
ጠርቶ በመስማት ኑዛዜዉ በትክክል በች መደረጉ ተረጋግል በማለት ቢወስን ኑዛዜን
ለማስረዳት በዉርስ ህጉ የተደነገገዉን ድንጋጌ አይቃረንም?
ምዕራፍ 4 ዉርስ ማጣራትና ዉርስን ማስተዳደር

 የች ዉርስ ማጣራት ስራ በች ዉርስ ስርዓት አፈፃፀም ዉስጥ ትልቁን ስፍራ ይይዛል፡፡ በመሆኑም የዉርስ
ማጣራቱን ተግባር ኃላፊነት ወስዶ የሚያስፈፅም አንድ ወይም ከዚያ በላይ የሖኑ ሰዎች መኖር አለባቸዉ፡፡
እነዚህ የሚመረጡ ሰዎች የዉርስ አጣሪዎች ይባላሉ፡፡
6.1 ዉርስ ማጣራት
ዉርስ ማጣራት ማለት /የፍ/ህ/ቁ.944/
- የች ወራሾች እነማን እንደሆኑ አጣርቶ መወሰን
- የዉርስ ሀብት መጠን ዓይነትና ግምት እንዲሁም የሚገኝበትንቦታ አጣርቶ መወሰን
- ሌሎች ሰዎች ከች የተበደሩትን ገንዘብ መሰብሰብና ከች ዉርስ ላይ የሚከፈሉ እዳዎችን አጣርቶ መክፈል

- ች ልዩ የኑዛዜ ስጦታ ያደረጉላቸዉን ሰዎች የተሰጣቸዉን ልዩ የኑዛዜ ስጦታ መክፈል ናቸዉ፡፡


የዉርስ አጣሪዎች መሾም
የዉርስ አጣሪ ከሶስት በአንዱ መንገድ ይሾማል፡፡ እነዚህ ሶስቱ መንገዶች
- በች ኑዛዜ /በኑዛዜ የተሾመ ሲኖር ወይም ጠቅላላ የኑዛዜ ስጦታ የተደረገለት
ሰዉ ከተገኘ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የጠቅላላ ኑዛዜ ስጦታ የተደረገለት ሰዉ
በቅድመ ተከተል ዉርስ አጣሪ ይሆናል፡፡
- በህግ ሊመረጥ ወይም ስልጣኑ በህግ ሊያገኝ / ከላይ የተጠቀሱ ሁለቱ በሌሉ ጊዜ
የች ያለ ኑዛዜ ወራሾች ያለአንዳች ቅድመ ሁኔታ ዉርስ አጣሪ ይሆናሉ፡፡
- በዳኞች መሾም /የዉርስ አጣሪ በፍርድ ቤት የሚሰየመዉ የች ወራሾች የማይታወቁ ሲሆን ያለኑዛዜ ወራሾች
ዉርሱን ለማጣራት ያልፈቀዱ መሆናቸዉን ከገለፁ እንዲሁም ች የኑዛዜም ሆነ ያለኑዛዜ ወራሽ ያልተወና
ሀብቱንም መንግስት የሚወርሰዉ እንደሆነ ነዉ፡፡
የቀጠለ…

 በፍ/ህ/ቁ. 949 መሰረት ዳኞች ዉርስ አጣሪ የሚሾሙ ሲሆን በ951 ደግሞ ከላይ በሶስት መንገድ
የተሰየሙ ዉርስ አጣሪዎችን የመተካት ስልጣን እንዳላቸዉ የሚደነግግ ነዉ፡፡ ሁለቱ ፅንፀ ሀሳቦች
የተለያዩ ናቸዉ፡፡
 ፍርድ ቤቱ በች በህግ፣ኑዛዜ ወይም በፍርድ ቤት የተሰየመን ዉርስ አጣሪ በማንሳት ሌሎችን
የሚሰይመዉ /የፍ/ህ/ቁ/951/
- ዉርስ አጣሪዉ የተሰየመበት ኑዛዜ ዋጋ ያለዉ ኑዛዜ መሆኑ አጠራጣሪ ሆኖ ሲገኝ
- በሌላ ምክንያት ዉርስ አጣሪዉን በመለየት ላይ አጣራጣሪ ሁኔታ ሲያጋጥም
- ብዙ ያለኑዛዜ ወራሾች ኖረዉ በፍ/ህ/ቁ.947 በሚመነጭ የአጣሪነት ስልጣን በጋራ
ተግባብተዉና ተስማምተዉ መስራት ሳይችሉ ሲቀሩ
- ከወራሾቹ አንዱ ለአቅመ መጠን ያላደረሰ፣በህግ ወይም በፍርድ የተከለከለ፣
የታወቀ እብድ መሆን ወዘተ… ምክንያት ጥቅሙን ማስከበር ሳይችል ሲቀር
- ዉርስ ማጣራቱ ስራ ልዩ ችግር ያስነሳና ልዩ ሙያ ያላቸዉን ችግሩን መቅረፍ
የሚችሉ ሰዎችን መሰየም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ
- በህግ፣በች ኑዛዜ ወይም በፍርድ ቤት የተሰየመ ዉርስ አጣሪ ቸልተኛ፣ ትጉህ
ያልሆነ፣ የማጭበርበር ባህሪይ የሚታይበት፣ሀቀኝነት የማይታይበት ችሎታ
የሌለዉ ሲሆን ነዉ፡፡
4.1 የዉርስ አጣሪዎች ግዴታዎችና ኃላፊነቶች

የዉርስ አጣሪዎች ተግባር በፍ/ህ/ቁ.956 ላይ በዝርዝር ተመልክል፡፡ ዋና ዋናዎቹ


- ች በህይወት ዘመኑ ያደረገዉ ኑዛዜ ካለ መፈለግና ያለኑዛዜና የኑዛዜ
ወራሾችን መለየት
- የዉርስ ንብረት ከብልሽትና ከብክነት ለመታደግ ተገቢዉን ጥንቃቄ መዉሰድ
- በግልፅ የታወቁ ክርክር የማያስነሱ ዕዳዎችን በቅድመ ተከተል መክፈል
- ች በልዩ ኑዛዜ ያደረጋቸዉን ስጦታዎችን መክፈልና የችን ኑዛዜ ቃል
ለመፈፀምና ዉጤት ለመስጠት ማንኛዉንም አስፈላጊ ጥንቃቁ መዉሰድ
- ዉርስ አጣርቶ ከጨረሰ በላ ሪፖርቱን ለወራሾች ማቅረብ
- ዉርስ አጣሪዎች የዉርስ ንብረቱን አጣርተዉ ሪፖርት ለፍርድ ቤት አቅርበዉ ምንም ተቃዉሞ
ሳይነሳ መዝገቡ ከተዘጋ በላ የፍርድ ባለመብት የሆነ ወገን በፍርድ ባለዕዳዉ ላይ የዉርስ ክፍፍል
እንዲፈፀም የአፈፃፀም ክስ ቢያቀርብ የዉርስ አጣሪ ሪፖርት የፍርድ ነቤት ዉሳኔ አይደለም
በመሆኑም የአፈፃፀም ክስ ሊቀርብበት አይችልም ቢል ተገቢ ነዉ? ºŠ‰ ÞÒጋገር የዉርስ አጣሪ
ሪፖርት ፍርድ ቤት ቀርቦ መዝገብ መዘጋቱን መነሻ በማድረግ የፍርድ አፈፃፀም ማመለከቻ ለፍርድ
ቤት ማቅረብ ይቻላል ወይ? ሰበር መ/ቁ. 18576 ወ/ሮ ድስታ መኮንን ወ/ሪት መሰሉ ጌታሁን ቅፅ 7
ገፅ 330
የቀጠለ…
ከዉርስ ማጣራት ጋር ተያይዞ በፍርድ ቤቶች
ከሚያጋጥሙ ችግሮች ጥቂቶቹ
- ዉርስ አጣሪዎች ወራሽ በሆኑ ወገኖች የሚቀርቡትን ተገቢነት ያላቸዉን ማስረጃዎችን
በሙሉ የመስማት ጉዳይ እንዲሁም ይህ ቢታለፍ ፍ/ቤት የዉርስ አጣሪ ሪፖርት ሲቀርብ
በሪፖርቱ የግራ ቀኙን ሀሳብ ተቀብሎ ማስረጃ መስማት (ፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ.241‚270‚345)
- የዉርስ አጣሪዎች የዉርስ ንብረት የዉርስ አካል ስለመሆኑ ክርክር ሲነሳ የግራ ቀኝ ማስረጃ
ሰምተዉ የሪፖርት አካል አድርገዉ ለሚመለከተዉ ፍርድ ቤት ማቅረብ እንጂ ማስረጃዎችን
መዝነዉ ንብረቱ የዉርስ አካል ነዉ አይደለም ብለዉ የህግ ክርክር (ይርጋ) ጭምር ላይ
የመወሰን ስልጣን ተሰጥቶአቸዋልን? የሰበር መ/ቁ. 28764 በወ/ሮ አመለ ወርቅ እየሱስ እና
በአቶ መስፍን አስፋዉ 6 ሰዎች የዉርስ ክርክር የዉርስ አጣሪ ፍ/ቤቱ ሹሞ ባቀረቡት
ሪፖርት አመልካች የፍ/ህ/ቁ 1000 በመጥቀስ የ3 ዓመት ይርጋ መነሻ በማድረግ በዉርስ
ንብረት ላይ የራሱን ዉሳኔ አሳርፎ ለፍ/ቤቱ አቀረበ፡፡ የሰበር ችሎት በዉሳኔዉ ላይ ይህ
ለዉርስ አጣሪ ያልተሰጠ ስልጣን ሲል ወሰል፡፡
- የዉርስ ሀብት አጣሪ ሪፖርት በፍርድ ቤት ከፀደቀ በላ በሂደቱ ተሳታፊ የሆነ ወራሽ
እንደገና በፍ/ህ/ቁ 358 መሰረት ጣልቃ ሊገባ በሚል በሚቀርብ አቤቱታ ላይ የሚሰጥ ዉሳኔ
 የገጠር መሬት ከሌሎች ንብረቶች ጋር የዉርስ ክርክሩ አካል ሆኖ ሲቀርብ እንዲሁም ይህ
ክርክር በሁለት ክልል ነዋሪዎች መካከል ሆኖ ሲቀርብ የማጣራቱ ጉዳይ መከናወን ያለበት
በገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ኮሚቴ ነዉ ወይስ በዉርስ አጣሪ ነዉ ወይስ የመሬቱ
ጉዳይ በገጠር መሬቱ አዋጅ ሆኖ ሌላዉ ንብረት በዉርስ አጣሪ የሚለዉ ጉዳይ የፍ/ህ/ቁ. 956
እና የደቡብ ክልል የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁ.110/99
 ኑዛዜ የተደረገለት ሰዉ በቀጥታ የንብረቱ ድርሻ ከፍፍል እንዲደረግ መጠየቅ ይኖርበታል ወይስ
ኑዛዜዉ በፍርድ ቤት መፅደቅ ይኖርበታል? ኑዛዜዉ በፍርድ ቤት መፅደቅ በኑዛዜዉ ህጋዊነት
ላይ የሚጨምረዉ ነገር አለን ?
 ኑዛዜዉ እንዲፀድቅ ፍርድ ቤት ክስ ጀምሮ የኑዛዜ ክፍያ ጥያቄ ሳያቀርብ ይርጋ ያለፈበት ሰዉ
ይርጋዉ በፍርድ ቤት ባለዉ ክርክር ምክንያት ይረጣል ቢል ያዋጣዋል፡፡ የሰበር መ/ቁ.49359
ቅፅ 11 ወ/ሮ ቀለ ወርቅነህ እና ሻምበል ጌታሁን ገብሬ
 ዉርስ አጣሪዎች በተለያዩ ምክንያቶች የማጣራቱን ሂደት የሚያዘገዩበት ሁኔታ ሲኖር ፍርድ
ቤት ምን ማድረግ አለበት? ገለልተኝነት ማጣት፣ በቀጠሮ አለመገኘት
 ዉርስ ከተጣራ እና ድርሻ ከተለየ የክፍፍል ጥያቄ የማቅረቢያ ጊዜ ይርጋ እንደለለዉ ፍርድ
ቤቶች ያለመገንዘብ
የቀጠለ
ለዉይይት
ምዕራፍ 5 የዉርስ ይርጋ

 ማንኛዉም ጉዳይ አንድ ሰዉ በህግ በዉል በፍርድ ቤት ዉሳኔ መብት ያገኘ እንደሆነ
መብቱን የሚጠይቅበትና በስራ ላይ የሚያዉልበት የተወሰነ የጊዜ ገደብ ይሰጠዋል፡፡
ባለመብቱ በህግ በተቀመጠዉ የጊዜ ገደብ ዉስጥ መብቱን ለመጠየቅ ተገቢዉን ትጋት
ማድረግ ይኖርበታል፡፡ በጊዜ ገደቡ ዉስጥ መብቱን ካልተጠቀመ መብቱ በይርጋ
ይታገዳል፡፡
 ይርጋ የሚለዉ ቃል መነሻዉ ረጋ ከሚለዉ የአማርኛ ቃል የመጣ እንደሆነና ትርጉሙም የሰዉ
ሀሳብ ከመዉጣት ከመዉረድ በሀሳብ ከመዞር ከመባከን ከመናወጥ ፀጥ አለ ማለት ነዉ ሲል
ደራሲ ተሰማ ኃብተ ሚካኤል “ ከሰተ ብርሃን ተሰማ ”በ2000 ዓ.ም ባሳተሙት የአማርኛ
መዝገበ ቃላት ገልፆታል፡፡
 በመሆኑምበአንድ ጉዳይ ላይ ክስ የማቅረብ ወይም መብት የመጠየቅ ጉዳይን አስመ
ልክቶ በጉዳዩ ላይ ክስ የሚያቀርብበት ሰው ስለጉዳዩ ያለውን ሀሳብ ከመውጣት ከመ
ውረድ በሀሳብ ከመዞርና ከመባከን ከመናወጥ ከረጋ (ፀጥ) ካለ በኋላ ሊከሰስ ወይም
ሊጠየቅ እንደማይገባ ያመለክታል በሚል ልንወስደው እንችላለን፡፡
 በሌሎች ፅሁፎች ላይም ይርጋ ማለት አንድ መብቱ ወይም ጥቅሙ የተነካበት ሰው በሌ
ላ ሰው ላይ ክስ፣ አቤቱታ ወይም የይገባኛል ጥያቄ እንዲያቀርብ በሕግ ተለይቶ የተቀመ
ጠ የክስ (አቤቱታ) ማቅረቢያ ጊዜ ነው፡፡
 ይርጋ በፍትሀብሄር ጉዳይ በተከራካሪ ወገን በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነት የሚቀርብ
የቀጠለ

5.1 ይርጋ ለምን አስፈለገ?

የተለያዩ የህግ ምሁራን በህግ ይርጋ እንዲኖር የተፈለገባቸዉን ሶስት ምክንያቶች እንዳሉ
ይገልፃሉ፡፡
 አንደኛዉ ከሳሽ በተገቢ ትጋትና በቂ ምክንያት መብቱን እንዲጠይቅ ለማስቻል
ነዉ፡፡
 ሁለተኛዉ ደግሞ ተከሳሽ በጊዜ ቆይታ ምክንያት ዘግይተዉ የሚመጡ ክሶችን
ለመከላከል ማስረጃዎችን እንዳያጣ ለማድረግ ነዉ፡፡
 ሶስተኛዉና የመጨረሻዉ ደግሞ ዘግይተዉ የሚቀርቡ ክሶች ፍትህ ከማስገኘት
ይልቅ ለበቀልና ለማጥቅያ መሳሪያነት እንዳያገግሉ ለመከላከል ነዉ፡፡
የቀጠለ

5.2 ክስ ማቅረቢያ የይርጋ ጊዜ መቆጠር አጀማመር

በህግ የተመለከቱ የተለያዩ ጉዳዮች የየራሳቸዉ ክስ ማቅረቢያ ወይም መብት መጠየቂያ


የተለያየ መጠን የጊዜ ይርጋ ወይም ገደብ በህግ ተደንግገጎ እናገኛለን፡፡ ይህ ማለት ግን
በፍትሀብሄር ጉዳዮች የዉርስ ህግ ጨምሮ በይርጋ የማይታገዱ ጉዳዮች እንዳሉም ማየት
ተገቢ ይሆናል፡፡
በመሆኑም በተለያዩ ህጎች ለተለያዩ ጉዳዮች የክስ ማቅረቢያ ጊዜ ከመቼ ወይም ከምን
ሁኔታ ጀምሮ መቆጠር እንደሚጀምር ተመልክል፡፡ በዚህ ላይ አንዳንዴ የክስ የይርጋ ጊዜ
መቆጠር የሚጀምረዉ የክርክሩ መነሻ የሆነዉ ጉዳይ ከተፈጠረበት ወይም ከተከሰተበት
ጊዜ ጀምሮ ሲሆን አንዳንዴ ደግሞ በጉዳዩ ጥቅም ያላቸዉ ወገኖች ክስተቱን ካወቁበት
ጊዜ ጀምሮ ይሆናል፡፡
የቀጠለ

5.3 የይርጋ መረጥ


በህግ የተመለከተዉ የክስ ማቅረቢያ ወይም የመብት መጠየቂያ የጊዜ ገደብ መረጥ
ሲባል ክስ ለማቅረብ መብት ወይም ጥቅም ያለዉ ወገን በህግ ላይ የተቀመጠዉ የይርጋ
ጊዜ ካለፈም በላም ቢሆን ክስ ለማቅረብ የሚያስችል መብት ለከሳሽ ወገን የሚሰጥ
ፅንሰ ሀሳብ ነዉ፡፡

እንግዲህ ስለ ይርጋ በጠቅላላዉ ይህን ያህል ካልን በመቀጠል ከዉርስ ጋር የተያያዙ የይርጋ
ገደቦችን በአጭሩ እንመለከታለን፡፡
5.4 ከዉርስ ሀብት ጋር የተያያዙ የይርጋ ገደቦች

5.4.1 ኑዛዜን ስለመቃወም የተቀመጠ ይርጋ


 የዉርስ አጣሪ የችን ኑዛዜ በማፈላለግ ባገኘ ጊዜ ያለኑዛዜ ወራሾች የሚናገርበት
ች በሞተ በ40 ቀን ነዉ፡፡
 ች ኑዛዜ ያልተወ እንደሆነ የዉርሱን አደራረግ እና አከፋፈል ዓይነት እንዴት
ሊፈፅም እንዳቀደ ዉርስ አጣሪ ያለ ኑዛዜ ወራሾች የሚያሳዉቅበት
ች በሞተ በ40 ቀን ነዉ፡፡ የፍ/ህ/972
5.4 ከዉርስ ሀብት ጋር የተያያዙ የይርጋ ገደቦች

አንድ ወራሽ የዉርስ ንብረት በሌላ ወራሽ የተያዘዉ እንድከፈለዉ የሚቀርብ ክስ ይርጋ
 ከዉርስ ሀብት ጋር በተያያዘ ወራሽ ነኝ የሚል ወገን መብቱና ንብረቱ በሌላ ወራሽ
መያዛቸዉን ካወቀ ከ3 ዓመት በላ የሚያቀርበዉ የወራሽነት ክሰ በይርጋ
ይታገዳል፡፡ የፍ/ህ/ቁ.1000(1) ሰ/መ/ቁ. 26422 ቅፅ 6 በዚሁ መዝገብ ወ/ሮ ስንልሽ
ማዝንጊያ በእነአቶ ተስፉ ማዝንጊያ ላይ ባቀረበችሁ ክስ የአዉራሻቸዉ የሆነ
የዉርስ ንብረት በእጃቸዉ ያለዉን ያካፍሉ የሚል ሲሆን ተከሳሾች በፍርድ ቤት
ዉርስ አስወስነዉ ከ10 ዓመት በላይ በእጃቸዉ ያደረጉትን መጠየቅ አይችሉም
በማለት 1000 (1) በመጥቀስ ተከራክረዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም የፍ/ህ/ቁ/1000(2)
በመጥቀስ ይርጋን ዉድቅ አድረገ፡፡ ጠቅላይ ፍ/ቤት አፀና፡፡ የፌዴራል ሰበር የስር
ፍርድ ቤት የጠቀሰዉ አንቀፅ 1000 (2) ማለትም ከዘር የወረደ ርስት በማለት
የወሰነዉ አግባብነት የለዉም በማለት የፍ/ህ/ቁ.1000 (1) በመጥቀስ በይርጋ ክሱን
ዉድቅ አድርጎታል፡፡ በተጨማሪም በሰ/መ/ቁ. 20295 ቅፅ 6 በሆነዉ በአቶ ደጀነ
ለገሰ እና በአቶ መላኩ ጌታቸዉ መዝገብ ላይ ወራሽነትን ካረጋገጡ በላ ንብረት
ተይዞብኛል ይመልስልኝ የሚል ወራሽ የሆነ ሰዉ በሌላ ወራሽ በሆነ ሰዉ ላይ
የሚያቀርበዉ ክስ በ3 ዓመት ይርጋ የሚታገድ ስለመሆኑ በፍ/ህ.ቁ.1000 ጠቅሶ
ወስኖበታል፡፡
 በተመሳሳይ መልኩ በሰ/መ/ቁ 25567 ቅፅ 6 ላይ በወ/ሪት አይናለም አበበ እና አቶ
ደገፉ ጉርሙ በተከራከሩበት ወ/ሪት አይናለም የች የአቶ አበበ ጉርሙ ልጅ
አልወለደም ነገር ግን ወ/ሪት አይናለም የአቶ አበበ ልጅ ነች ተብሎ ወራሽነቱ
የተረጋገጠዉ በአግባቡ ስላልሆነ ዉሳኔዉ ይሻር የሚል ቀርቦ ወ/ሪት አይናለምም
በበኩü የዛሬ 21 ዓመት ህፃን ሆኜ ያስወሰንኩትን መቃወም አትችልም በሚል
በቀረበ ክርክር የወረዳዉ ፍ/ቤት ፍ/ህ/ቁ.1000 ለንብረት ተይዞብኛል ክርክር እንጅ
ወራሽ ናት አይደለችም ክርክር አያገለግልም በሚል ይርጋዉን ዉድቅ በማድረግ ልጅ
ባለመሆ ያለኑዛዜ ወራሸ አይደለችም በማለት ወሰነ፡፡ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ
ቤት ይህን ዉሳኔ ሽሮ አመልካች ልጅ ስለሆነች የመጀመሪያ ደረጃ ወራሽ ናት አለ፡፡
በይግባኝ የተመለከተዉ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት የከፍተኛዉን ዉሳኔ ሽሮ
የወረዳዉን አፀና፡፡ አቤቱታ የቀረበለት የፌዴራል ሰበር ችሎት የስር ፍርድ ቤት
የፍ/ህ/ቁ.1000 በጠባቡ መተርጎሙ አግባብ አይደለም አመልካች ወራሽነትን
አረጋግጣ ከ20 ዓመት በላይ የቆየ የባለሀብትነት ድርሻ ግልፅ ስለሆነ የተጠሪ ክስ
በ1000 መሰረት ክርክሩ በይርጋ ይታገዳል ሲል ወሰነ፡፡
 በሌላ የይርጋ ክርክር የሰ/መ/ቁ. 25664 ቅፅ 6 በአቶ ተገኝ ይማምና በአቶ ካሳሁን ደሳለኝ
መዝገብ አቶ ካሳሁን ደሳለኝ በአቶ ተገኝ ላይ ች እህታቸዉ ልጅ ሳትወልድ ስለሞተች
በትዳር ያፈራችዉን ንብረት ግማሽ ድርሻ ያካፍል በማለት ክስ አቅርቦ ተከሳሽ የፍ/ህ/ቁ.
1000(2) እና 1845 ይርጋ አነሳ፡፡ ፍርድ ቤትም ዉርሱ በይርጋ ቀሪ አይሆንም በማለት ወሰነ፡፡
ይግባኝ ሰሚዉም አፀናዉ፡፡ የሰበር ችሎቱ አቤቱታ ቀርቦለት ያስቀርባል በማለቱ
ተጠሪዎች(እነ ካሳሁን ) ክስ ያቀረብነዉ 15 ዓመት ሳይሞላ ነዉ በማለት 1000(2) በመጥቀስ
እንዲሁም የፍ/ህ/ቁ/1845 በዉል ላይ ለተመሰረቱ ጉዳዮች ይርጋ እንጂ ዉርስ አይመለከትም
ሲሉ ተከራከሩ፡፡ የሰበር ችሎት የፍ/ህ/ቁ. 1000(2) የሚነሳዉ ክርከሩ በወራሾች መካከል ቢሆን
ነዉ፡፡ በዚህ ጉዳይ የቀረበዉ ክርክር በወራሾች መካከል ባለመሆኑ 1000(2) ተፈፃሚነት
የለዉም፡፡ ጉዳዩ ተጠሪዎች ክስ ሳይመሰርቱ ከአስር ኣመት በላይ የቆዩ መሆኑ የተረጋገጠ
ስለሆነ የሚመለከተዉ ድንጋጌ የፍ/ህ/ቁ. የፍ/ህ/ቁ.1677 (1) እና 1845 ነዉ፡፡1677 ግዴታዎቹ
ከዉል የተገኙ ባይሆኑም የዚህ አንቀፅ ደንቦች ይፈፀሙባቸዋል ይላል በመሆኑም የ1845 የ10
ዓመት ይርጋ ክሱን ያግዳል ሲል ወሰነ፡፡
 በልዩነት ያስመዘገበዉ ዳኛ ለዚህ ጉዳይ ተፈፃሚ የሚሆነዉ ድንጋጌ ይህ አይደለም 1000 (1
እና 2) ነዉ ይህን ከተከተልን ክሱ በይርጋ አይታገድም በሚል በልዩነት ሲያዝመዘግብ ግን
ዉሳኔዉ በአብላጫዉ ተወሰነ፡፡
 ወራሽ የሆነ ሰዉ ወራሽ ባልሆነ ሰዉ ላይ የዉርስ ንብረት ይለቀቅልኝ በሚል በሚያቀርበዉ ክስ ላይ ተፈፃሚ የሚሆነዉ
የ10 ዓመት ይርጋ የሚቆጠረዉ ወራሽ ወራሽነት ከተረጋገጠበት ጊዜ ጀምሮ ሳይሆን ንብረቱ ወራሽ ባልሆነዉ ሰዉ እጅ
ከተያዘበት ጊዜ ጀምሮ ነዉ፡፡ ሰ/መ/ቁ.47201 ቅፅ 11
የቀጠለ

 የዉርስ ሀብቱን በእጁ አድርጎ በመገልገል ላይ ያለ ተከራካሪ የሆነ ወራሽ የክርክሩ


ምክንያት የሆነዉን ንብረት በጋራ ይዞ በቆየ ሰዉ ላይ የሚያነሳዉ የዉርስ ጥያቄ
በይርጋ የሚታገድ አይሆንም፡፡ የሰ/መ/ቁ. 44025 ቅፅ 10 ክርክሩ በወ/ሪት ፀሀይ
ሃይሌ 4 ሰዎች እና በወ/ሮ ፈልቃ በኛ መካከል በሰበር የተደረገ ሲሆን በስር
ከአባታችን የዉርስ ሀብት ድርሻ እንዳናገኝ ተጠሪ ድርሻችንን ትስጠን ነዉ፡፡ ንብረቱ
ግራ ቀኙ በጋራ ሲያስተዳድሩት የቆየ ስሆን ከ1997 ጀምሮ ደግሞ በአመልካች እጅ
ያለ ሲሆን ከዚህ ንብረት ድርሻ ለመቀበል አመልካቾች ክስ መስርተዋል፡፡
የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ክሱን በይርጋ ሲያግድ በከፍተኛ ይግባኝ ፀና፡፡
የፌዴራል ሰበር ግን ንብረቱ በአመልካች እጅ ሆኖ በጋራ ሲጠቀሙ ስለነበር ክሱ
በይርጋ የሚገደብ አይደለም ሲል ወሰነ፡፡
 የወራሽነት መብትን በህግ በተመለከተዉ ጊዜ ዉስጥ ያረጋገጠ ወራሽ የዉርስ
ንብረት ክፍፍል ጥያቄን በማናቸዉም ጊዜ ማቅረብ ይችላል፡፡ የፍ/ህ/ቁ. 996
1000(1) 1000 (2) 1060 1062 የሰ/መ/ቁ. 38533 ቅፅ 10 በዚህ የሰበር መዝገብ
ወ/ሮ ፅጌ ወ/መስቀል 6 ሰዎች በአቶ ስዩም ክፍለ ላይ ባቀረቡት ክርክር የዉርስ
ንብረት መብት አሰቀድመዉ ያስወሰኑ መሆናቸዉንና ከዚያ ወድህ በዉርስ ቤቱ
ከሌሎች ወራሾች ጋር አብረዉ መኖራቸዉን ጠቅሰዉ የንብረት ክፍፍል ጠይቀዉ
ተከሳሾች የፍ/ህ/ቁ 1000(1) መሰረት አድርገዉ ተከራክረዋል፡፡ የተሰጠዉ ዉሳኔ
የፍ/ህ/ቁ/1000(1) የወራሽነት ጥያቄ ማቅረቢያ የጊዜ ገደብ ነዉ፡፡ የወራሽነት
መብታቸዉን አረጋግጠዉ የተቀመጡ ወራሾችን ጉዳይ የሚገዛዉ ድንጋጌ
በፍ/ህ/ቁ.1062 መሰረት በማናቸዉም ጊዜ ሊቀርብ የሚችል ነዉ ሲል ወሰነ፡፡
ፍ/ህ/ቁ.1062 “ዉርስ በተጣራ ጊዜ በማናቸዉም ጊዜ ቢሆን እያንዳንዳቸዉ የጋራ
ወራሾች ዉርሱን እንከፋፈል ብለዉ መጠየቅ ይችላሉ”
የቀጠለ

 የዉርስ ንብረት ይልቀቅልኝ ክርክሩ በወራሾች እና ወራሽ ባልሆኑ ሰዎች መካከል


በሆነ ጊዜ የይርጋ ገደቡ 10 ዓመት ይሆናል /የፍ/ህ/ቁ.1845/ ፡፡ ሰ/መ/ቁ. 25664 ቅፅ
6 ከሳሽ አቶ አቶ ካሳሁን ደሳለኝ የች እህታቸዉ የወ/ሮ ያልጋ ደሳለኝ ድርሻ
ከባለቤታቸዉ ከአቶ ተገኝ ይማም ግማሽ ንብረት ለመካፈል ከ13 ዓመታት በላ
ክስ አቅርበዉ ተከሳሽ የፍ/ህ/ቁ.1000 (1) በማንሳሰት ተከራክረዋል፡፡ በዚህ መዝገብ
ክርክሩ በወራሾች መካከል ሳይሆን ወራሽ ባልሆኑ ሰዎች መካከል ነዉ፡፡ ፍርድ ቤቱ
ክርክሩ ወራሽ ባልሆኑ ሰዎች መካከል የተደረገ በመሆኑ ይህ ድንጋጌ አያገለግልም
ተፈፃሚ የሚሆነዉ የፍ/ህ/ቁ. 1845 ነዉ በማለት በ10 ዓመት ይርጋ ይታገዳል ሲል
ወሰነ፡፡ በልዩነት የወሰነዉ ዳኛ መደምደሚያ የፍ/ህ/ቁ.1845 ሊጠቀስ አይገባም
የሚል ነዉ፡፡ የአብላጫዉን ዉሳኔና የአናሳዉን ድምፅ ከዉርስ ህግ ይርጋ ድንጋጌዎች
ጋር በማዛመድ ተከራከሩ:: በየትኛዉ ሃሳብ ትስማማላችሁ?
የቀጠለ

 በተጨማሪም የፍ/ህ/ቁ. 1001 (1) እና (2) አንድ ህጋዊ ወራሽ ወራሽ ባልሆኑ
ሰዎች የተያዘን ንብረት ለማስመለስ የሚያቀርበዉ ክርክር የጊዜ ገደብ
በሚመለከት ነዉ፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ክርክሩ ወራሽ ባልሆነ ሰዉ ላይ ህጋዊ ወራሽ
ያቀረበዉ ቢሆንም የክርክሩ ነጥብ የተያዘ ንብረት ይመለስ ሳይሆን የች
ንብረት ዉርስ ክፍያና ሊደርሰኝ የሚገባዉ ድርሻ ይሰጠኝ የሚል በመሆኑ
አግባብነት ያለዉ የይርጋ ድንጋጌ የፍ/ህ/ቁ. 1080 ነዉ በመሆኑም ክሱ በይርጋ
ሊታገድ አይገባም ሲል ወሰነ፡ የፍ/ህ/ቁ. 1080 “ የክፊያዉ ጠያቂ ክፊያዉን
ካወቀ ከአንድ ዓመት በላ ወይም በማናቸዉም ሁኔታ ች ከሞተበት ጊዜ
ጀምሮ በአስር ዓመት ጊዜ ዉስጥ ካልቀረበ ዉድቅ ይሆናል” ይላል፡፡ የፍ/ህ/ቁ.
1845 ደግሞ ተፈፃሚ አይሆንም የተባለዉ ህግ በሌላ አካኀን ካልወሰነ በቀር
ስለሚል እና ህግ ደግሞ ከላይ በተጠቀሱ ድንጋጌዎች ይርጋን ያስቀመጠ በመሆኑ
ነዉ የሚል ይገኝበታል፡፡
 የፍ/ህ/ቁ.1080(1) ተፈፃሚነቱ አስቀድሞ የዉርስ ማጣራት ተደርጎ እንደገና
ክፍፍሉም በወራሾች መካከል ተደርጎ አንዱ ወራሽ በክፍፍል ሳይሳተፍ ቀርቶ
ወይም ወኪልም ያልተመደበ እንደሆነ የተደረገዉን ክፍፍል በመቃወም ፈራሽ
እንዲሆን ጥያቄ የሚቀርብበትን ይርጋ የሚመለከት እንደሆነ በቅፅ 10 የሰ/መ/ቁ.
40418 በአቶ ተስፋዬ ሞላና በአቶ እሸቱ ምኔ መዝገብ ላይ ተወስlል፡፡
የቀጠለ…

 ወራሽነት ተረጋግጦና ንብረቱ ተጣርቶ የክፍፍሉ ጥያቄ በቀረበበት ቤት ዉስጥ


እየኖሩ ግን የዉርስ ክፍያ እንድፈፀም የሚቀርብ ክርክር ከወራሽነት ጥያቄ የተለየ
በመሆኑ ተገቢዉ ይርጋ የፍ/ህ/ቁ.1000 (1) ሳይሆን የፍ/ህ/ቁ.1062 ነዉ፡፡ ይህ
ድንጋጌ የሚለዉ ዉርስ በተጣራ ጊዜ በማናቸዉም ጊዜ ቢሆን እያንዳንዱ የጋራ
ወራሾች ዉርሱን እንከፋፈል ብሎ ለመጠየቅ ይችላሉ ይላል፡፡ በሌላ አነጋገር
ወራሽነትን አረጋግጦ ሰ/መ/ቁ.38533 ቅፅ 10
 በዉርስ አጣሪ ተጣርቶ የቀረበ ንብረት ክፍያ የሚፈፀመዉ በወራሾች ስምምነት
ነዉ፡፡ በክፍያ ላይ በሚቀርብ ክርክር የዉርስ ሀብት ድርሻ ክፍፍል በተመለከተ
ከወራሾች አንዱ ሳይኖር የቀረ ወይም በሚገባ ወኪል ያላደረገ እንደሆነ ክፍያዉን
ዳኞች ካላፀደቁት ፈራሽ ነዉ፡፡ በመሆኑም እርሱ ሳይኖር ክፍያ የተፈፀመበት ወራሽ
ክፍያዉን በመቃወም ክስ ማቅረብ የሚችለዉ የክፍያዉን ፈራሽነት ካወቀበት ጊዜ
ጀምሮ በአንድ ዓመት ጊዜ ዉስጥ ነዉ፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በማናቸዉም ሀሳብ
ቢሆን ች ከሞተበት ቀን አንስቶ በሚቆጠር 10 ዓመት ዉስጥ ካልቀረበ ጥያቄዉ
ዉድቅ ይሆናል፡፡ የፍ/ህ/ቁ.1080 /3/ የሰ/መ/ቁ.40418 ቅፅ 10
የቀጠለ..

 በኑዛዜ የተገኘ ንብረት በሆነ ጊዜ ኑዛዜዉ እንድፈጸም በ10 ዓመት ዉስጥ ጥያቄ ካልቀረበበት
በይርጋ ይታገዳል፡፡ ሰ/መ/ቁ.38152 ቅፅ 8
 በስጦታ ሰጭ ላይ በተደረገ የመንፈስ መጫን ምክንያት የስጦታ ዉሉ ይፍረስ ጥያቄ
የማቅረቢያ ጊዜ ስጦታዉ በተደረገ በ2 ዓመት ዉስጥ ሲሆን አጠቃላይ የስጦታ ዉል
በመቃወም የሚቀርብ ክስ በፍ/ህ/ቁ. 1845 መሰረት በ10 ዓመት ይርጋ ይታገዳል፡፡ ሰ/መ/ቁ.
105652 ቅፅ 18
 በፍ/ህ/ቁ. 973/1/ ስለኑዛዜ መነበብ እንድሁም ኑዛዜዉ ሲነበብ የነበሩ ሰዎች ወይም የተወከሉ
ሰዎች ኑዛዘዉ አይፀናም ወይም አንዱ በኑዘዜዉ የተነገረዉ ቃል አይፀናም በማለት ክስ
ለማቅረብ ያላቸዉን ሀሳብ መግለጫ ወይም ስለክፊያዉ በዉርስ አጣሪዉ የቀረበዉን
የድልድልን አመዳደብ ሀሳብ ለመቃወም ኑዛዜ ከተነበበት አንስቶ በ15 ቀናት ዉስጥ ለዉርስ
አጣሪ ወይም ለሽማጊሌ ወይም ለፍርድ ቤት መግለጫ ማቅረብ አለባቸዉ፡፡ መግለጫዉም
የሚቀርበዉ በፅሁፍ ነዉ፡፡ የሰ/መ/ቁ. 82585 ቅፅ 15 ወ/ሮ ሱዛን ምንታልባን 3 ሰዎች እና
አቶ ሙራድ አሊ /ፍ/ህ/ቁ.973 (1‚3) እና 974 (1) (2) ልዩነትና አንድነት/
 በንዑስ አንቀፅ 3 ደግሞ መግለጫ ከተሰጠበት ቀን አንስቶ አስከ 3 ወር ክስ ለፍርድ ቤት
ወይም ለሽማጊልና ዳኞች መቅረብ አለበት፡፡ በዚህ ጊዜ ክስ ካልቀረበ በድልድል አመዳደብ
ሀሳብ ላይ ክስ የማቅረብ መብት በይርጋ ቀሪ ይሆናል፡፡ የድልድላ አመዳደብ ሀሳብ የንብረት
ክፍፍል እንዳልሆነ መታወቅ ያለበት ነዉ፡፡ ይህ የድልደላ አመዳደብ ሀሳብ እቅድ ነዉ፡፡
የቀጠለ

 በኑዛዜዉ ንባብ ሥነ ሥርዓት ያልነበሩ ወይም በኑዛዜዉ ንባብ ሥነ ሥርዓት በወኪልነት


ላልሰሙ ሰዎችና እንዲሁም ኑዛዜዉ በሌለበት በዉርስ አጣሪዉ የቀረበን የድልድል አመዳደብ
ሃሳብ መቃወም የሚቻለዉ በፍ/ህ/ቁ. 973 /1/ መሰረት ይህ ሀሳብ ከተነገራቸዉ ቀን አንስቶ
ነዉ፡፡ ይሁን እንጅ ስለክፊያዉ አመዳደብ ሃሳብ መግለጫ ላይ ኑዛዜ ከፈሰሰበት ጊዜ ከ5 ዓመት
በላ ወይም ኑዛዜ የሌለ እንደሆነ ች ከሞተበት ከ5 ዓመት በላ በማናቸዉም ምክንያት
መቃወሚያ ሊቀርብበት አይችልም፡፡ የፍ/ህ/ቁ/974/2/
.
 ከዉርስ መነቀል ምክንያት የሚቀርብ ክስ ይርጋ በተመለከተ የስጦታ ክፍያ እንድቀር
የሚደረገዉ ክስ ወደ ላይ በሚቆጠረዉ ስጦታ አድራጊ ወላጅ አባት በሞተ በ2 ዓመት ዉስጥ
እና የስጦታዉ መከፋፈል ከተደረገበት ቀን አንስቶ በ10 ዓመት ዉስጥ ካልቀረበ ክስ የማቅረብ
መብት ቀሪ ይሆናል፡፡ እዚህ ላይ ሁለት የተለያዩ ነገሮችን እንመለከታለን፡፡ የመጀመሪያዉ 2
ዓመት የስጦታ ክፍያ እንድቀር የሚደረገዉ ክስ ማቅረቢያ ሲሆን 10 ዓመቱ ግን የስጦታ
መከፋፈል ከተደረገ ክፍያዉ ከተደረገበት ጊዜ ጀምሮ ያለዉን ነዉ፡፡ ይህ የሚሆነዉ
በፍ/ህ/ቁ.1123 /1/ መሰረት በስጦታዉ አከፋፈል ወደ ታች ከሚቆጠሩ ተወላጆች መካከል
አንዱ ከሚደርሰዉ ዉርስ ሀብት ከሩብ በበለጠ ጉዳት ደርሶት እንነደሆነ የስጦታ አከፋፈሉ
እንድቀር ሊጠይቅ ይችላል፡፡
የዉርስ ይርጋ ገደብ ማጠቃለያ

 ኑዛዜን ስለመቃወም የተቀመጠ ይርጋ የዉርስ አጣሪ የችን ኑዛዜ በማፈላለግ ባገኘ ጊዜ
ያለኑዛዜ ወራሾች የሚናገርበት ች በሞተ በ40 ቀን ነዉ፡፡ ች ኑዛዜ ያልተወ እንደሆነ
የዉርሱን አደራረግ እና አከፋፈል ዓይነት እንዴት ሊፈፅም እንዳቀደ ዉርስ አጣሪ ያለ ኑዛዜ
ወራሾች የሚያሳዉቅበት ች በሞተ በ40 ቀን ነዉ፡፡ የፍ/ህ/972
 ከዉርስ ሀብት ጋር በተያያዘ ወራሽ ነኝ የሚል ወገን መብቱና ንብረቱ በሌላ ወራሽ
መያዛቸዉን ካወቀ ከ3 ዓመት በላ የሚያቀርበዉ የወራሽነት ክሰ በይርጋ ይታገዳል፡፡
የፍ/ህ/ቁ.1000(1)
 ክርክሩ ትክክለኛ ወራሽ በሆነና ባልሆነ ሰዉ መካከል ሲሆን ክስ ሳይመሰርቱ ከአስር ኣመት
በላይ የቆዩ መሆኑ የተረጋገጠ ስለሆነ የሚመለከተዉ ድንጋጌ የፍ/ህ/ቁ. የፍ/ህ/ቁ.1677 (1)
እና 1845 ነዉ፡፡1677 ግዴታዎቹ ከዉል የተገኙ ባይሆኑም የዚህ አንቀፅ ደንቦች
ይፈፀሙባቸዋል ይላል በመሆኑም የ1845 የ10 ዓመት ይርጋ ክሱን ያግዳል፡፡
 ከላይ እንደተጠቀሰዉ ወራሽ የሆነ ሰዉ ወራሽ ባልሆነ ሰዉ ላይ የዉርስ ንብረት ይለቀቅልኝ
በሚል በሚያቀርበዉ ክስ ላይ ተፈፃሚ የሚሆነዉ የ10 ዓመት ይርጋ የሚቆጠረዉ ወራሽ
ወራሽነት ከተረጋገጠበት ጊዜ ጀምሮ ሳይሆን ንብረቱ ወራሽ ባልሆነዉ ሰዉ እጅ ከተያዘበት
ጊዜ ጀምሮ ነዉ፡፡ ሰ/መ/ቁ.47201 ቅፅ 11
የዉርስ ይርጋ ማጠቃለያ የቀጠለ..…

 የዉርስ ሀብቱን በእጁ አድርጎ በመገልገል ላይ ያለ ተከራካሪ የሆነ ወራሽ የክርክሩ


ምክንያት የሆነዉን ንብረት በጋራ ይዞ በቆየ ሰዉ ላይ የሚያነሳዉ የዉርስ ጥያቄ በይርጋ
የሚታገድ አይሆንም፡፡ የሰ/መ/ቁ. 44025 ቅፅ 10 ክርክሩ በወ/ሪት ፀሀይ ሃይሌ 4 ሰዎች
እና በወ/ሮ ፈልቃ በኛ መካከል በሰበር ችሎት የተደረገ ክርክር ዉሳኔ
 የወራሽነት መብትን በህግ በተመለከተዉ ጊዜ ዉስጥ ያረጋገጠ ወራሽ የዉርስ ንብረት
ክፍፍል ጥያቄን በማናቸዉም ጊዜ ማቅረብ ይችላል፡፡ የፍ/ህ/ቁ. 996 1000(1) 1000
(2) 1060 1062 የሰ/መ/ቁ. 38533 ቅፅ 10 በዚህ የሰበር መዝገብ ወ/ሮ ፅጌ ወ/መስቀል
6 ሰዎች በአቶ ስዩም የሰበር ክርክር ዉሳኔ የወራሽነት መብታቸዉን አረጋግጠዉ
የተቀመጡ ወራሾችን ጉዳይ የሚገዛዉ ድንጋጌ በፍ/ህ/ቁ.1062 መሰረት በማናቸዉም
ጊዜ ሊቀርብ የሚችል ነዉ ሲል ወሰነ፡፡ ፍ/ህ/ቁ.1062 “ዉርስ በተጣራ ጊዜ
በማናቸዉም ጊዜ ቢሆን እያንዳንዳቸዉ የጋራ ወራሾች ዉርሱን እንከፋፈል ብለዉ
መጠየቅ ይችላሉ”
 የፍ/ህ/ቁ.1080 (3) ተፈፃሚነቱ አስቀድሞ የዉርስ ማጣራት ተደርጎ ከወራሾቹ
መካከል አንዱ ሳይገኝበት ክፍፍል ከተደረገ ክፍፍሉን በመቃወም ጥያቄ
የሚቀርብበትን ይርጋ የሚመለከት እንደሆነ በቅፅ 10 የሰ/መ/ቁ. 40418 በአቶ
ተስፋዬ ሞላና በአቶ እሸቱ ምኔ መዝገብ ላይ ተወስል፡፡
የዉርስ ይርጋ ማጠቃለያ የቀጠለ..…

 በኑዛዜ የተገኘ ንብረት በሆነ ጊዜ ኑዛዜዉ እንድፈጸም በ10 ዓመት ዉስጥ ጥያቄ ካልቀረበበት በይርጋ ይታገዳል፡፡
ሰ/መ/ቁ.38152 ቅፅ 8
 በስጦታ ሰጭ ላይ በተደረገ የመንፈስ መጫን ምክንያት የስጦታ ዉሉ ይፍረስ ጥያቄ የማቅረቢያ ጊዜ ስጦታዉ በተደረገ
በ2 ዓመት ዉስጥ ሲሆን አጠቃላይ የስጦታ ዉል በመቃወም የሚቀርብ ክስ በፍ/ህ/ቁ. 1845 መሰረት በ10 ዓመት ይርጋ
ይታገዳል፡፡ ሰ/መ/ቁ. 105652 ቅፅ 18
 ኑዛዜዉ ሲነበብ የነበሩ ሰዎች ወይም የተወከሉ ሰዎች ኑዛዘዉ አይፀናም ወይም አንዱ በኑዘዜዉ የተነገረዉ ቃል
አይፀናም በማለት ክስ ለማቅረብ ያላቸዉን ሀሳብ መግለጫ ወይም ስለክፊያዉ በዉርስ አጣሪዉ የቀረበዉን የድልድልን
አመዳደብ ሀሳብ ለመቃወም ኑዛዜ ከተነበበት አንስቶ በ15 ቀናት ዉስጥ ለዉርስ አጣሪ ወይም ለሽማጊሌ ወይም
ለፍርድ ቤት መግለጫ ማቅረብ አለባቸዉ፡፡ መግለጫዉም የሚቀርበዉ በፅሁፍ ነዉ፡፡በንዑስ አንቀፅ 3 ደግሞ መግለጫ
ከተሰጠበት ቀን አንስቶ አስከ 3 ወር ክስ ለፍርድ ቤት ወይም ለሽማጊልና ዳኞች መቅረብ አለበት፡፡ በዚህ ጊዜ ክስ
ካልቀረበ በድልድል አመዳደብ ሀሳብ ላይ ክስ የማቅረብ መብት በይርጋ ቀሪ ይሆናል፡፡ የድልድላ አመዳደብ ሀሳብ
የንብረት ክፍፍል እንዳልሆነ መታወቅ ያለበት ነዉ፡፡ ይህ የድልደላ አመዳደብ ሀሳብ እቅድ ነዉ፡፡ በኑዛዜዉ ንባብ ሥነ
ሥርዓት ያልነበሩ ወይም በኑዛዜዉ ንባብ ሥነ ሥርዓት በወኪልነት ላልሰሙ ሰዎችና እንዲሁም ኑዛዜዉ በሌለበት
በዉርስ አጣሪዉ የቀረበን የድልድል አመዳደብ ሃሳብ መቃወም የሚቻለዉ በፍ/ህ/ቁ. 973 /1/ መሰረት ይህ ሀሳብ
ከተነገራቸዉ ቀን አንስቶ ነዉ፡፡ ይሁን እንጅ ስለክፊያዉ አመዳደብ ሃሳብ መግለጫ ላይ ኑዛዜ ከፈሰሰበት ጊዜ ከ5 ዓመት
በላ ወይም ኑዛዜ የሌለ እንደሆነ ች ከሞተበት ከ5 ዓመት በላ በማናቸዉም ምክንያት መቃወሚያ ሊቀርብበት
አይችልም፡፡ የፍ/ህ/ቁ/974/2 የሰ/መ/ቁ. 82585 ቅፅ 15 ወ/ሮ ሱዛን ምንታልባን 3 ሰዎች እና አቶ ሙራድ አሊ
/ፍ/ህ/ቁ.973 (1‚3) እና 974 (1) (2) ልዩነትና አንድነት/
 ከዉርስ መነቀል ምክንያት የሚቀርብ ክስ ይርጋ በተመለከተ የስጦታ ክፍያ እንድቀር የሚደረገዉ ክስ ወደ ላይ
በሚቆጠረዉ ስጦታ አድራጊ ወላጅ አባት በሞተ በ2 ዓመት ዉስጥ እና የስጦታዉ መከፋፈል ከተደረገበት ቀን
አንስቶ በ10 ዓመት ዉስጥ ካልቀረበ ክስ የማቅረብ መብት ቀሪ ይሆናል፡፡
አመሰግናለሁ
የቀጠለ…

You might also like