Professional Documents
Culture Documents
Property Without Holder
Property Without Holder
com
ጥያቄዉ?
በዚህ ጽሁፍ መመለስ የምፈልገዉ ጥያቄ ቀላል ይመስላል፤ እንዴት ያለባለቤቱ ሙሉና ነጻ ፈቃድ
የተላለፈን ንብረት ማስመለስ፤ የተቋቋመን የመብት ገደብ ማስነሳት ይቻላል የሚለዉን ነዉ፡፡ ቀጥታ
ጥያቄዉን ወደ መመለሱ ከመሄዴ በፊት፤ ጥያቄዉ የሚመለከታቸዉ ሁኔታዎች ምን አይነቶቹን እንደሆነ
ግልጽ ላድርግ፡፡
1. ለምሳሌ በመጀመሪያ ግብይቱን ለማከናወን ሙሉ ስልጣን ኖሮት ነገር ግን ስልጣኑ በጊዜ ማለፍ
ምክንያት ወይም ባለቤቱ ስላነሳዉ ወይም ስለገደበዉ፤ ግብይቱን ሲያከናዉን ስልጣን የለለዉ ሆኖ
ነገር ግን ስልጣን እንደሌለዉ ወይም ስልጣኑ እንደተገደበ ወይም እንደተነሳ የማያዉቅና ማወቅ
የማይጠበቅበት ሰዉ በቅል ልቦና ነዉ ዉሉን የፈጸመዉ ሊባል ይችላል፡፡ ይህ ሰዉ ዉሉን
የፈጸመዉ እያወቀ ወይም ማወቅ እየተጠበቀበት ሊሆን ይችላል፡፡
2. ሰዉየዉ የባለቤቱ እንደራሴ ሆኖ ነገር ግን እንዲህ አይነት ዉሎችን የመዋዋል ስልጣን ላይኖረዉ
ይችላል፡፡ ይህ ሰዉዬ ግን ስልጣኑ እንዲህ አይነት ዉሎችን ይጨምር አይጨምር የሚያዉቅ
ወይም ማወቅ የሚጠበቅበት ወይም የማያዉቅ እና ማወቅ የማይጠበቅበት ሊሆን ይችላል፡፡
3. ዉልን እንዲመዘግቡ ወይም ንብረትን እንዲመዘግቡ፤ የባለቤትነት ማስረጃን እንዲሰጡ ወይም
ማስረጃን እንዲያረጋግጡ የተቋቋሙ መንግስታዊ ተቋማት በቅን ልቦና ወይም ያለቅን ልቦና
የቀረቡትን ማስረጃዎች ሊያረጋግጡ ወይም ዉልን ሊመዘግቡ ይችላሉ፡፡
4. እንዲሁም ንብረቱ የተላለፈለት ወይም መብቱ የተገደበለት ሰዉ፤ ንብረቱን ያስተላለፈለት ሰዉ
ባለቤት ስላመሆኑ ወይም ስልጣን የሌለዉ ስለመሆኑ የማያዉቅና ማወቅ የማይጠበቅበት ወይም
የሚያዉቅ ወይም ማወቅ የሚጠበቅበት ሊሆን ይችላል፡፡
11 የከሳሾች ክስና ማስረጃ ለተከሳሾች ደርሶ መልስ እንዲሰጡ ታዞ አንደኛ ተከሳሽ ተጠርቶ
12 ባለመቅረቡ ጉዳዪ በሌሉበት እንዲታይ ትዕዛዝ ተሰጥቷል፡፡
13 ሁለተኛ ተከሳሽ (የአሁን ተጠሪ) ቀርቦ ለክሱ ምክንያት የሆነዉን ቤት በመያዣነት መያዙን
14 አምኖ ይህንን ለማድረግ የቻለዉ አንደኛ ተከሳሽ በቤተዘመድ ጉባዬ ዓማካይነት በ24/1/87
15 ዓ.ም የሞግዚትነት ሥልጣን ተሰጥቶት ፍ/ቤትም ቀርቦ በመጽደቁ ምክንያት እንደሆነና
16 የተሰጠዉም የሞግዚትነት ሥልጣን ሞግዚት በሆነላቸዉ ሰዎች ስም የሚንቀሳቀስም ሆነ
17 የማይንቀሳቀስ ንብረት በዋስትና ለመስጠት እንደሚችል በሰነዱ ላይ ስለተመለከተ
18 በመሆኑ ለአንደኛ ተከሳሽ በተሰጠዉ የሞግዚትነት ሥልጣን ላይ ተመስርቶ የመያዣ ዉል
19 መፈራረሙ በአግባቡ ስለሆነ የመያዣ ዉሉ የሚፈርስበት ምክኒያት የለም በማለት
20 ተከላክሏል፡፡
31 በመሆኑም በወረዳ 6 ክልል የቤ.ቁ 563 ተመዝግቦ የሚገኘዉ የከሳሾችና የአንደኛ ተከሳሽ
32 የጋራ የዉርስ ሀብት ሆኖ እያለ አንደኛ እና ሁለተኛ ከሳሾች ስምምነታቸዉን ሳይሰጡ
33 በአንደኛ ተከሳሽ በኩል ከሁለተኛ ተከሳሽ ጋር የመያዣ ዉል የተፈጸመዉ የሕጉን ድንጋጌ
34 ባልተከተለ ሁኔታ ስለሆነ ጥቅምት 1987 ዓ.ም እና ሐምሌ 1987 ዓ.ም የተደረገ የመያዣ
35 ዉል ፈራሽ ነዉ በማለት ዉሳኔ ሰጥቷል፡፡
36 የሥር ሁለተኛ ተከሳሽ የአሁን አመልካች በዉሳኔዉ ቅሬታ አድሮበት የይግባኝ ቅሬታዉን
37 ለፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት አቅርቦ ፍ/ቤቱም በበኩሉ ግራ ቀኙን አከራክሮ አንድ ዉል
38 እንዲፈርስ ተዋዋይ ወገን ያልሆኑ ሦስተኛ ወገኖች ማቅረብ የሚችሉት በፍ/ብ/ሕ/ቁ/
39 1808(2) እና ተከታዮቹ ድንጋጌዎች መሠረት ነዉ፡፡ ዉል የማይረጋበት ምክንያት
40 ከቀረበት ጊዜ አንስቶ ከ2 ዓመት በኋላ የዉል ይሰረዝልኝ ክስ ሊቀርብ እንደማይችል
41 ጉዳቱ የደረሰበት ሰዉ አካለመጠን የደረሰ ሰዉ ከሆነ ክሱን ማቅረብ የሚገባዉ ሙሉ
42 በተደረገ በ2 ዓመት ጊዜ ዉስጥ እንደሆነ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1810(1) ላይ ተደንግጓል፡፡ በተያዘዉ
43 ጉዳይ ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱት መ/ሰጭዎች ዉሉ ሲደረግ ለአቅመ አዳም የደረሱ
44 መሆናቸዉ ከ4ኛ-7ኛ የተጠቀሱትም መ/ሰጭዎች ከ1995 ዓ.ም ጀምሮ ለአካለመጠን
45 የደረሱ መሆናቸዉ በመ/ሰጭዎች ያልተካደ በመሆኑ የዉል ይሰረዝልኝ ክሱ 2 ዓመት
46 ያለፈዉ መሆኑን ፍ/ቤቱ ተገንዝቧል፡፡ ስለሆነም በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1810(1) መሠረት የዉሉ
47 ይሰረዝልኝ ክሱ በይርጋ ቀሪ ሆኗል በማለት ዉሳኔ ሠጥቷል፡፡
48 የሥር ከሳሾች /የአሁን አመልካቾች/ በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ዉሳኔ ቅሬታ አድሮባቸዉ
49 የይግባኝ ቅሬታቸዉን ለፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ያቀረቡ ቢሆንም በፍ/ብ/ሕ/ሥ/ሥ/ቁ
50 337 መሠረት ፍ/ቤቱ ይግባኙን ሳይቀበለዉ ቀርቷል፡፡
በእርግጥ የሰበር ሰሚ ችሎት የሚሰጣቸዉ የሕግ ትርጎሞች በማንኛዉም የሃገሪቱ ፍርድ ቤት ላይ አስገዳጅ
እንደሆነ የሚደነግግ አዋጅ አለ፡፡ ነገር ግን ይህ ድንጋጌ ብቻዉን የሰበር ሰሚዉ የሚሰጣቸዉ የሕግ
ትርጉሞች አስገዳጅ እንዲሆኑ አያስችልም፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ይህ የአዋጅ ድንጋጌ የሚያስነሳዉ ጥያቄ፤
እንዴት ማስፈጸም ይቻላል የሚል ነዉ? አንድ ዳኛ ወይም ፍርድ ቤት የሰበር ሰሚ ችሎቱ የሰጠዉን የሕግ
ትርጉም ወደ ጎን በማለት ሌላ ትርጉም ቢሰጥ ይህ ቅጣትም ሆነ ሽልማትን ያልያዘን የአዋጅ ድንጋጌ
እንዴት ነዉ ማስፈጸም የሚቻለዉ? በእርግጥ ዳኞችን ወደ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለመሾም በሚደረገዉ
ግምገማ፤ አንድ ዳኛ ምን ያህን የሰበር ዉሳኔን ያከብራል የሚለዉ አንድ የግምገማ ነጥብ ሊሆን ይችላል፡፡
ግን ይህን የአዋጁ ማስፈጸሚያ መንገድ አድርጎ መዉሰድ ያስቸግራል፡፡ ሁለተኛዉ የማስፈጸሚያ መንገድ
ፍርድ ቤቱ ወይም ዳኛዉ ከዚህ በፊት በሰበር የተሰጠዉን የሕግ ትርጉም ባለመከሉ የተነሳ ጥቅሙ
የተነሳበት ወገን በሚያቀርበዉ ይግባኝ ወይም የሰበር አቤቱታ ነዉ፡፡ በእርግጥ ይህ ከሆነ ከዚህ በፊት
ተቃራኒ ትርጉም የሰጠዉ ሰበር ችሎች ወይም ይግባኝ ሰሚ ችሎት፤ የበታች ፍርድ ቤት የሰጠዉን የሕግ
ትርጉም ዉድቅ በማድረግ የቀደመዉን የሕግ ትርጉም ሊከተለዉ ይችላል፡፡ ጥያቄዉ ታዲያ፤ ይህ የአዋጅ
ድንጋጌ ባይኖም እንኳ በይግባኝ ወይም በሰበር አቤቱታ ይህ ሊስተካከል ከቻለ አዋጁ በግልጽ የሰበር
የሕግ ትርጉሞች አስገዳጅ ናቸዉ ማለቱ የሚጨምረዉ አዲስ ነገር ምንድን ነዉ?
እንደ እኔ እምነት ሰበር ችሎቹ የሚሰጣቸዉ የሕግ ትርጉሞች ከሰበር በታች በሃገሪቱ ባሉ ችሎቶች
ተቀባይነት እንዲኖረዉ ለማድረግ የአዋጅ ድንጋጌ ብቻዉን በቂ አይደለም፡፡ እንደዉም የአዋጅ ድንጋጌም
www.abyssinialaw.com
ላይስፈልግ ይችላል፡፡ የቀደምን የፍርድ ዉሳኔን እንደ ሕግ ቆጥረዉ በሚከተሉ አገሮች ይህን እንዲያደደርጉ
የሚያስገድድ የተጻፈ ድንጋጌ የለም፡፡ ሰበር ችሎቱ የሚሰጣቸዉ የሕግ ትርጎሞች አስገዳጅነታቸዉ
የሚመነጨዉ መመንጨትም ያለበት ከዉጭ (ከአዋጅ ድንጋጌ) ሳይሆን ከዉስጥ ነዉ፡፡ ማለትም
ከራሳቸዉ የሕግ ትርጉሞች ወይም የሰበር ዉሳኔዎች ናቸዉ፡፡ ዉጫዊ ፋክተሮች አጋዥ ናቸዉ፡፡
6. የሰበር ዉሳኔዉ ችሎቱ የተለያዩ የታች ፍርድ ቤቶች ከሰጧቸዉ የሕግ ትርጎሞች የተለየ ከተጠቀመ
ለምን የታች ፍርድ ቤቶች የሰጧቸዉ የሕግ ትርጉሞች ትክክል እንዳልሆኑ ማሳየት አለበት፡፡
እንዲሁም ሰበር ችሎቱ በተሟጋች ወገኖች የቀረቡትን መከራከሪያዎች እያንዳንዳቸዉን ለምን
እንደተቀበላቸዉና እንዳልተቀበላቸዉ በሚገባ ማስረዳት አለበት፡፡
7. የሰበር ችሎቱ የስር ፍርድ ቤቶችን ዉሳኔ የሚቀይር ከሆነ፤ የተለየ ትርጉም የሚሰጥ ከሆነ ለምን
የተለየ ትርጉም መስጠት እንዳስፈለገ ማስረዳት አለበት፡፡ እንደሚታወቀዉ የሰበር አቤቱታ
ተጨማሪ የይግባኝ መብት ወይም አማራጭ አይደለም፡፡ የሰበር አቤቱታ መሰረታዊ የሕግ ስህተት
ማስተካከያ አማራጭ ነዉ፡፡ የሕግ ስህተት ሳይሆን መሰረታዊ የሕግ ስህተት ማሰተካከያ ነዉ፡፡
በመሆኑም የስር ፍርድ ቤቶች የሰጧቸዉ የሕግ ትርጉሞች ስህተት መሆናቸዉን ማሳየት ብቻ በቂ
አይደለም፡፡ መሰረታዊ መሆናቸዉንም ማስረገጥ አለበት፡፡
8. በአዋጁ መሰረት አስገዳጅ የሆነዉ የሰበር ትእዛዙ ሳይሆን የሰበር ችሎቱ የሰጠዉ የሕግ ትርጉም
ነዉ፡፡ በመሆኑም ፍርድ ቤቱ የተረጎመዉን እና አስገዳጅ እንዲሆን ያሰበዉን አንድ ወይም ከዛ
በላይ የሕግ ትርጉም ግልጽ አድርጎ ማስቀመጥ አለበት፡፡
9. ከጉዳዩ ጋር የሚገኛኙ ከዚህ በፊት ዉሳኔ የተሰጣቸዉ የሰበር ዉሳኔዎች ካሉ እነሱን በዉሳኔዉ
ጠቅሶ ከጉዳዩ ጋር እንዴት እንደሚመሳሰሉና እንደሚለያዩ፤ ያሁኑ የሕግ ትርጉም ከዚህ በፊት
ከተሰጡት እንዴት እንደሚሄዱ ማስረዳት አለበት፡፡
10. የዉሳኔዉ የተለያዩ ክፍሎች እርስ በርሳቸዉ የማይጋጩ፤ በግልጽ ቋንቋ የተጻፉ መሆን አለባቸዉ፡፡
11. ሰበር ሰሚዉ በዉሳኔዉ የሚጠቀምባቸዉን ሕጎችና ይዘታቸዉን እንዲሁም ትርጉማቸዉን
በሚገባና በትክክል ማስቀመጥ አለበት፡፡ መሰረታዊ የሕግ ስህተት አርማለዉ በሚል እጅግ ቀላልና
ግልጽ ስህተት ሕግን በመለየትና በመተርጎም የሚሰራ ከሆነ ታማኝነቱን ይሸረሽረዋል፡፡
12. ሰበር ሰሚዉ በዉሳኔዉ ላይ መሰረታዊ የሕግ ስህተት መሰራቱን ለማስረዳት ወይም አንድ ሕግ
እንዴት መተርጎም እንዳበት ለማሳየት የተለያዩ አማራጭ ትርጉሞች የሚኖራቸዉን የወደፊት
አንድምታና መዘዝ፤ እንዲሁም የተከተለዉ ትርጉም ከሕጉ አላማ ጋር አብሮ የሚሄድ ስለመሆኑ
ማስረዳት አለበት፡፡ ሕግን ለመተርጎም የቋንቋን እና የሎጂክ መመሪያዎችን ብቻ የሚከተል ከሆነ
ሰበር ሰሚ ችሎቱ እንዴት ከመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተለየ የሚል ጥያቄ ያስነሳል፡፡
13. ሰበር ችሎቱ ከዚህ በላይ የተዘረዘሩትን በሚገባ ሲወጣ የሚያስተላልፈዉ መልእክት ዉሳኔዬን
በሚገባ አይቼ፤ በጣሙን አምኜበት፤ ብዙ ነገሮችን መዝኜ፤ ነዉ የሚል ነዉ፡፡ ማለትም ጉዳዩን
በሚገባ ከመርመሬ የተነሳ፤ ተመሳሳይ ጉዳይ ወደፊት ቢመጣልኝም እንኳ ተመሳሳይ ዉሳኔ እና
ትርጉም እከተላለዉ የሚል መልእክት ነዉ እያስተላለፈ ያለዉ፡፡ እነዚህን ነገሮች በሚገባ
www.abyssinialaw.com
ከላይ በግልጽ ለማስቀመጥ እነዚህ ጉዳዮች የአንድ ሰበር ሰሚ ዉሳኔ እኔ በዉሳኔዉ የተካተተዉ የሕግ
ትርጉም የሚኖረዉን የአስገዳጅነት ደረጃ የሚወስኑ ናቸዉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ያሉ ዉጫዊና አጠቃላይ
የሕግ አመለካከቶች የሕግ ትርጉሙን አስገዳጅነት ሊያጠናክሩት ወይም ሊሽሩት ይችላል፡፡
ከላይ ከተዘረዘሩት ነጥቦች አንጸር ሰበር ሰሚ ችሎቱ በእነ ሙና እንድሪስ እና የኢትዮጲያ ልማት ባንክ
መዝገብ የሰጠዉ ዉሳኔ የሚከተሉት ቅርጻዊ ጉድለቶች ታይተዉበታል፡፡
ከዚህ በላይ በተጠቀሱት አስር ቅርጻዊ ዉስንነቶችና እና ጉድለቶች ብቻ የሰበር ችሎቱ በእነ ሙና እንድሪስ
እና የኢትዮጲያ ልማት ባንክ የሰጠዉ የሕግ ትርጉም አስገዳጅነቱ አጠያያቂ ነዉ፡፡ ከላይ በግልጽ
ለማስቀመጥ እንደሞከርኩት የሰበር የሕግ ትርጉም አስገዳጅነት የሚመነጨዉ በአብዛኛዉ ከራሱ
ከዉሳኔዉ ነዉ፡፡
ይህ የሰበር ዉሳኔ ግልጽ አለመሆኑ እና ምክንያት አለማስቀመጡ ብቻ ሳይሆን ጉድለቱ እንደ እኔ እምነት
ብዙ የሕግ ስህተቶችን ፈጽሟል፡፡ እንደ እኔ እምነት ሰበር ችሎቱ የፈጸማቸዉ ስህተቶች መሰረታዊ
ናቸዉ፡፡ ከዚህ ቀጥሉ ባሉት ክፍሎች እነዚህን ስህተቶች ለመለየትና ለማብራራት ይሞከራል፡፡ እንዲሁም
ይህን ዉሳኔ እንደ መነሻ በጽሁፉ ርእስ የተነሳዉን ጥያቄ ለመመለስ ይሞከራል፡፡
(ይቀጥላል)