You are on page 1of 5

በቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት

የሕግ ጉዳዮች ክርክር ዳይሬክቶሬት


BOLE SUB-CITY ADMINISTIRATION JUSTICE OFFICE
LITIGATION AFFAIRS DIRCTORATE

መ/ቁ -145657
ቀን -23/03/2015 ዓ.ም
በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት
ለቦሌ ምድብ 10 ኛ ፍ/ብሄር ችሎት
አዲስ አበባ

ከሳሾች-------1 ኛ/ ወ/ሮ ብርቱካን በቀለ ወልደ


2 ኛ/ ወ/ሮ ፅጉ በቀለ ወልደ
3 ኛ/ ሲሳይ ኩምሳ ነዲ
አድራሻ፡- ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12
ተከሳሾች፡ -------1 ኛ/ ቦሌ ክ/ከተማ መሬት ልማት አስተዳደር ጽ/ቤት
2 ኛ/ አቶ ሸረፋ ሻፋ
አድራሻ፡- ቦል ክ/ከተማ ወረዳ 12
ከሳሾች ጥቅምት 29 ቀን 2015 ዓ.ም ላቀረቡት ክስ ከ 1 ኛ ተከሳሽ የቀረበ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ እና በአማራጭ የቀረበ
የመከላከያ መልስ ነው፡፡

1. የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ


1.1 ከሳሾች በይዞታው ላይ ክስ ለማቅረብ መብት የሌላቸው ስለመሆኑ፡ - ከሳሾች ቦታው በእኛ ይዞታ ስር ነበር ይበሉ እንጂ ይህ
ስለመሆኑ ምንም አይነት አግባብነት ያለው ማስረጃ አላቀረቡም እነደማስረጃ የቀረቡት የእርሻ መሬት የግብር ደረሰኞችም
ቢሆኑ በግብር ደረሰኝ አካራካሪው ይዞታ ላይ ያለን መብት ለማስረዳት የማይቻል እና ደረሰኞቹ ክርክር ለተነሳበት ይዞታ
ስለመገበራቸው የማያመለክቱ እና በህግ ፊትም የፀና ውጠየት የላቸውም፡፡ ሌላኛው ከሳሾች ወራሾች ነን ብለው ያያያዙት
ማስረጃም የየትኛውን የሟቾች ንብረት እንደወረሱ የማያመለክት እና ሟቾች ያልነበራቸውን መብት ወራሾች ሊወርሱ
ስለማይችሉ እንዲሁም ስልጣን ባለው አካል ክርክር ለተነሳበት ቦታ ባለመብት ስለመሆናቸው ህጋዊ ማስረጃ ባላቀረቡበት
ይህንን ክስ ለመመስረት ስለማይችሉ በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 33/2 መሰረት አለን የሚሉትን መብት እና ጥቅም በተገቢው
አላስረዱም ተብሎ በብይን ውድቅ እንዲደረግልን፡፡
1.2 ከሳሾች በአቤቶታቸው ላይ እርግጠኛ ባንሆንም 1 ኛ ተከሳሽ ለ 2 ኛ ተከሳሽ ክርክር ባስነሳው ይዞታ ላይ ካርታ ሰርቶ
የሰጠው መሆኑን የሰማን ሲሆን በዚህ መሰረትም የተሰጠው ካርታ እንዲመክንልን በሚል ያቀረቡት አቤቱታ ተቀባይነት
የሌለው እና ካርታ ተሰርቶ መሰጠት አለመሰጠቱን ዕንኳን በቅጡ ሳያውቁ በሰሚ ሰሚ ጉዳዩን ቀጥታ ወደ ፍ /ቤት ይዞ
መምጣት ስነስራተዊ ያልሆነ እና በእኛ በኩልም ምንም አይነት ካርታ ሰርተን ለ 2 ኛ ተከሳሽ ያልሰጠን በመሆኑ ከሳሾችም
በማስረጃ ያያያዙት ምንም ነገር ሳይኖር የቀረበ ክስ በመሆኑ ከሳሽ ከተከሳሽ ላይ የሚጠይቀውን ጥቅም ወይም መብት
በማረጋገጥ አቤቱታ ካላቀረበ በቀር በማንኛውም ሰው ላይ ክስ ሊያቀርብ እንደማይችል በፍ /ስ/ስ/ህ/ቁ 33(3) እንዲሁም
ካርታ ሰርተን ያልሰጠን በመሆኑ 1 ኛ ተከሳሽ በጉዳዩ የምንከሰስበት ምክንያት ስለማይኖር በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 244/2/መ
መሰረት ጉዳዩ አይመለከታቸውም ሊከሰሱ አይገባም ተብሎ በብይን እንድንሰናበት እየጠየቅን ለተጉላላንበት በቂ ኪሳራ
በቁርጥ ከሳሾች እንዲከፍሉን ተብሎ ውሳኔ እንዲሰጥልን እንጠይቃለን፡፡

2. ፍ/ቤቱ መቃወሚያችንን የሚያልፍበት የህግ አግባብ ካለ በአማራጭ የቀረበ መልስ

2.1 1 ኛ ተከሳሽ ከህግ ውጪ ከእናታችን ወ/ሮ ፀዳለ ወርቁ በውርስ ያገኘነውን ይዞታ ያለምንም የካሳ ክፍያ እና ምትክ ቦታ
ሳይሰጠን በ 2012 ዓ.ም ለ 2 ኛ ተከሳሽ ክርክር የተነሳበት ይዞታ ላይ እርግጠኛ ባንሆንም ካርታ ሰርቶ የሰጠው መሆኑን
የሰማን በመሆኑ እና 2 ኛ ተከሳሽ በይዞታው ላይ ከህግ ውጪ በቆርቆሮ አጥሮ ይዞታውን የያዘብን ስለሆነ ሁለቱም
ተከሳሾች ይዞታውን ለቀው እንዲያስረክቡን በሚል የቀረበ ክስ ነው ከሳሾች ይዞታውን ካሳ እና ምትክ ሳይሰጠን ከእጃችን
እንዲወጣ ተደረገብን ይበሉ እንጂ በይዞታው ላይ መብት እና ጥቅም እንዳላቸው በማስረጃ ባላረጋገጡበት ይህንን
ያረዳልናል ብለው ያቀረቡት የእርሻ መሬት የግብር ደረሰኞችም ቢሆኑ በግብር ደረሰኝ አካራካሪው ይዞታ ላይ ያለን መብት
ለማስረዳት የማይቻል እና ደረሰኞቹ ክርክር ለተነሳበት ይዞታ ስለመገበራቸው የማያመለክቱ እና በህግ ፊትም የፀና
ውጠየት የላቸውም፡፡ ሌላኛው ከሳሾች ወራሾች ነን ብለው ያያያዙት ማስረጃም የየትኛውን የሟቾች ንብረት እንደወረሱ
የማያመለክት እና ሟቾች ያልነበራቸውን መብት ወራሾች ሊወርሱ ስለማይችሉ እንዲሁም ስልጣን ባለው አካል ክርክር
ለተነሳበት ቦታ ባለመብት ስለመሆናቸው ህጋዊ ማስረጃ ባላቀረቡበት ይህንን ክስ ለመመስረት ስለማይችሉ እንዲሁም
ክርክር ያስነሳው ይዞታ መሬት ባንክ የገባ የመንግስት ቦታ በመሆኑ ከሳሾች በይዞታው ላይ መብት እና ጥቅም እንዳላቸው
የሚያሳይ ማስረጃ ባላቀረቡበት የቀረበ ክስ በመሆኑ እና ቦታው መሬት ባንክ የገባ የመንግስት ይዞታ በመሆኑ የከሳሾች
አቤቱታ ውድቅ እንዲደረግልን እንጠይቃለን፡፡
2.2 ከሳሾች በአቤቶታቸው ላይ እርግጠኛ ባንሆንም 1 ኛ ተከሳሽ ለ 2 ኛ ተከሳሽ ክርክር ባስነሳው ይዞታ ላይ ካርታ ሰርቶ
የሰጠው መሆኑን የሰማን ሲሆን በዚህ መሰረትም የተሰጠው ካርታ እንዲመክንልን በሚል ያቀረቡት አቤቱታ በዋናነት
በቦታው ላይ መብት እና ጥቅም የሌላቸው እና ይዞታው መሬት ባንክ የገባ የመንግስት ቦታ መሆኑ እንዳለ ሆኖ በይዞታው
ላይ መብት እና ጥቅም አላቸው እንኳን ቢባል ካርታ ተሰርቶ መሰጠት አለመሰጠቱን ዕንኳን በቅጡ ሳያውቁ በሰሚ ሰሚ
ያለ በቂ ማስረጃ ጉዳዩን ቀጥታ ወደ ፍ/ቤት ይዞ መምጣት አግባብነት የሌለው እና የፍርድ ቤቶችን ጊዜ በማይመለከታቸው
እና ባልሆነ ነገር ጊዜ ከመውሰዱ ውጪ በእኛ በኩልም ምንም አይነት ካርታ ሰርተን ለ 2 ኛ ተከሳሽ ያልሰጠን በመሆኑ
ከሳሾችም ካርታ ተሰርቶ ስለመሰጠቱ በማስረጃ ያያያዙት ምንም ነገር ሳይኖር የቀረበ ክስ በመሆኑ ከሳሽ ከተከሳሽ ላይ
የሚጠይቀውን ጥቅም ወይም መብት በማረጋገጥ አቤቱታ ማቅረብ ሲገባቸው እና በእኛ በኩል ካርታ ሰርተን ያልሰጠን
በመሆኑ 1 ኛ ተከሳሽ በጉዳዩ የምንከሰስበት ምክንያት ስለማይኖር የከሳሾች አቤቱታ ሙሉ በሙሉ ውድቅ ተደርጎ አላግባብ
ተከሰን ለተጉላላንበት በቂ ኪሳራ በቁርጥ እንዲተኩልን እንጠይቃለን፡፡

የቀረበው መልስ በእውነት የቀረበ መሆኑን


በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 92/3 መሰረት እናረጋግጣለን፡፡

በቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት


የሕግ ጉዳዮች ክርክር ዳይሬክቶሬት
BOLE SUB-CITY ADMINISTIRATION JUSTICE OFFICE
LITIGATION AFFAIRS DIRCTORATE

መ/ቁ -145657
ቀን -23/03/2015 ዓ.ም
በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት
ለቦሌ ምድብ 10 ኛ ፍ/ብሄር ችሎት
አዲስ አበባ

ከሳሾች-------1 ኛ/ ወ/ሮ ብርቱካን በቀለ ወልደ


2 ኛ/ ወ/ሮ ፅጉ በቀለ ወልደ
3 ኛ/ ሲሳይ ኩምሳ ነዲ
አድራሻ፡- ቦል ክ/ከተማ ወረዳ 12
ተከሳሾች፡ -------1 ኛ/ ቦሌ ክ/ከተማ መሬት ልማት አስተዳደር ጽ/ቤት
2 ኛ/ አቶ ሸረፋ ሻፋ
አድራሻ፡- ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12
በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 234 መሰረት የቀረበ የማስረጃ ዝርዝር

የሰነድ ማስረጃ

1. ቦሌ ክ/ከተማ መሬት ልማት እና አስተዳደር ጽ/ቤት ቦታው መሬት ባንክ የገባ መሆኑን የገለፀበት 01 ገፅ
ኮፒ ዋናው በጽ/ቤቱ የሚገኝ

ይህ የቀረበው የማስረጃ ዝርዝር በእውነት የቀረበ መሆኑን


በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁጥር 92/3/ መሠረት አረጋግጣለሁ

በቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት


የሕግ ጉዳዮች ክርክር ዳይሬክቶሬት
BOLE SUB-CITY ADMINISTIRATION JUSTICE OFFICE
LITIGATION AFFAIRS DIRCTORATE

ቁጥር-ቦ/ክ/ከ/ፍ/ጽ/ቤት/----------
ቀን 23/03/2015 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ከተማ ፍትህ ቢሮ ለህግ ጉዳዮች ክርክር
ዳይሬክቶሬት ለምክትል ቢሮ ሃላፊ

ጉዳዩ፡- በምንልክላችሁ ክርክር ሂደቱ ሰበር ላይ ያለ መዝገብ በፍ/ቤት የመጨረሻ ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊት ጉዳዩ
በድርድር እና በውይይት እንዲያልቅ በእናተ በኩል ጥረት እንዲደረግ ማሳወቅን ይመለከታል፡፡
በከሳሽ ኢትዮ ቴሌኮም እና በተከሳሽ ቦሌ ክ/ከተማ መሬት ልማት እና አስተዳደር ጽ/ቤት መካከል ሲካሄድ የነበረው ከውል ውጪ
ሀላፊነት ክርክር የከሳሽ ክስ የተከሳሽ መ/ቤት መልስ እና የፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት ቦሌ ምድብ 8 ኛ ፍ/ብሔር ችሎት በመ/ቁ 139652 ሰኔ
30 ቀን 2014 ዓ.ም በዋለው ችሎት የሰጠው የፍ/ቤቱ ውሳኔ እንዲሁም ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት አያስቀርብም ያለበት ውሳኔ
ተያይዞ የቀረበ እና ጉዳዩ አሁን በፌደራል ሰበር ሰሚ ችሎት ቅሬታ ያቀረብን ሲሆን የመጨረሻ ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊት በእናተ በኩል
ጉዳዩ በድርድር እና በውይይት እንዲያልቅ በእናተ በኩል ጥረት እንዲደረግ እንጠይቃለን፡፡

ከሠላምታ ጋር

ግልባጭ
በቦሌ ክ/ከተማ አስተዳደር
 ለፍትህ ጽ/ቤት
 ለሕግ ጉዳዮች ክርክር ዳይሬክቶሬት
አዲስ አበባ

በቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት


የሕግ ጉዳዮች ክርክር ዳይሬክቶሬት
BOLE SUB-CITY ADMINISTIRATION JUSTICE OFFICE
LITIGATION AFFAIRS DIRCTORATE

መ/ቁ -235372
ቀን 23/03/2015 ዓ.ም
ለፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት
ሰበር ሰሚ ችሎት
አዲስ አበባ

አመልካች----ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 14 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት


አድራሻ፡-ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 14
ተጠሪ-----አቶ ዮሴፍ አበራ ታሉ
አድራሻ፡-ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 14
በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 205 መሠረት በቃለ መሃላ ተደግፎ የቀረበ አቤቱታ

አመልካች በዚህ መዝገብ ላይ በስር ፍ/ቤት ውሳኔ መሰረት አፈፃፀም ስለመጣብን በሰበር ሰሚው ችሎት ውሳኔ
እስኪያገኝ ድረስ የአፈፃፀም መዝገቡ ታግዶ እንዲቆይልን በሚል የዕግድ አቤቱታ አስገብተን በዚህም መሰረት
በዚህ ችሎት የተቀጠረው የወደፊት ቀጠሮ እግድ ስለጣ በተሰብሮ እንዲታይ በሚል ቅሬታ ለማቅረብ ለ
21/03/2015 ጠዋት የተቀጠረ ቢሆንም መዝገቡን ስናስከፍት መዝገቡ 1 ኛ ሰበር አጣሪ እንደሚታይ የተነገረን
እና ይህ መዝገብ ወደ ሶስተኛ ሰበር አጣሪ ስለመዘዋወሩ የተነገረን መረጃ ባለመኖሩ ምክንያት እኛ በሰዓቱ
በዚያን እለት 1 ኛ ሰበር አጣሪ እየተጠባበቅን እያለ መዝገቡ በሶስተኛ ሰበር አጣሪ ታይቶ አመልካች በቀጠሮ ቀን
ስላልቀረቡ በመደበኛው ቀጠሮ እንዲቀርቡ ተብሎ ትዛዝ የተሰጠ በመሆኑ ይህ ደግሞ ቀጠሮ እሩቅ እና ተገደን
እንድንፈፅምም አፈፃፀም ችሎቱ ትዕዛዝ ስለሚሰጥበት ከተፈፀመም የምንተይቀው ዳኝነት ትርጉም
ስለማይኖረው 1 ኛ ሰበር አጣሪ የነበሩት መዝገቦች ወደ 3 ኛ ሰበር አጣሪ መዞራቸው ስላልተነገረን እና
ስላላወቅን 1 ኛ ሰበር አጣሪ በዕለቱ ቦታው ላይ ተገኝተን ስንጠባበቅ የነበረ መሆኑን ከግንዛቤ ገብቶልን
የተከበረው ፍ/ቤት ቅሬታ እንድናቀርብ እና የስር ፍ/ቤት መዝገብ እንዲታገድልን እንጠይቃለን፡፡

ያቀረብነው ቃለመሃላ እውነት መሆኑን በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 92/3 እና 205 መሠረት አረጋግጣለሁ፡፡

ስለ አመልካች

You might also like