You are on page 1of 3

ፓርክላንድ ኮሌጅ የመምህራን የሥራ ቅጥር ውል ተዋዋይ ወገኖች

ይህ የቅጥር ውል ስምምነት የተፈረመው በፓርክላንድ ኮሌጅ /ከዚህ በኋላ ቀጣሪ እየተባለ በሚጠራው/ እና በአቶ/ወሮ
________________________ /ከዚህ በኋላ ተቀጣሪ/ እየተባለ/ች በሚጠራው መካከል ሲሆን ከዚህ በታች የተቀጣሪው
ሙሉ አድራሻ ተቀምጧል፡፡

የተቀጣሪው ስም : _______________________________

የትውልድ ዘመን : _______________________________

የትውልድ ቦታ : ክልል ____ ዞን ______ወረዳ _____ቀበሌ ____የቤ/ቁጥር_____

ስልክ ቁጥር : ሞባይል _____________የቤት ____________

ፖ.ሣ.ቁጥር : _________________________

በአዋጅ ቁጥር 377/96 በአንቀጽ 4, 5,6,7,8 የአሰሪና ሰራተኞች አዋጅን መሠረት በማድረግ በውል ሰጭና በውል ተቀባይ
መካከል ለተወሰነ ጊዜ የሚመሰረት የስራ ውል ሲሆን የሚከተለውን የውል ስምምነት በመፈፀም ለዚህ ስምምነት አንቀጾች
ለመገዛት ተስማምተዋል፡፡

1. ቅጥር

ኮሌጁ ተቀጣሪውን በ--------------------------------------- የት/ክፍል በመምህርነት ቀጥሮታል ፡፡ ተቀጣሪው ባለው


የአካዳሚያዊ ዕውቀት ስፋትና ልክ ከዚህ በታች የተጠቀሱትን ተግባራት ለማከናወን ተስማምቷል፡፡

 የተመደበለትን ኮርስ በገለፃና በሌላ የማስተማሪያ ዘዴዎች በተግባር በማሳየት ማስተማርና እንዲሁም
የቁጥጥር ስራና ሌሎች ስራዎችን ከኮሌጁ ዲንና ከት/ክፍሉ ኃላፊ በሚደርሰው መመሪያ መሠረት
ያከናውናል፡፡
 የኮሌጁን ስራ ለማከናወን በተለያዩ ኮሚቴዎች ፣ክበባት፣ ማህበራት ወይም/እና በት/ክፍል ሲመረጥ ወይም
ሲሾም ይሰራል፡፡
 የሚሰጡትን ስራዎችና ተግባራት ሙያዊ ባህሪን በተላበሰ መልኩ በአካዳሚያዊ ደረጃዎች፣ ዓላማዎችና
አግባብ ባለው የኮሌጁ አካል በተቀመጠው የኮሌጁ አጠቃላይ መመሪያና ፍልስፍና መሠረት ይከውናል፡፡
 በተለያዩ ጊዜያት ለሚያስተምራቸው ኮርሶች TTLM በማዘጋጀት ለዲን ቢሮ ማስገባት፡፡
 ተቀጣሪው የሚኖረው ዝቅተኛውና ከፍተኛው የማስተማሪያ ሰዓቶች ገደብ በኮሌጁ ሕግ መሠረት
የሚወሰን ይሆናል፡፡

2. ደመወዝ
 ተቀጣሪው ወርሃዊ ደመወዝ ብር______/_____________________________የሙያ አበል ብር
________/______________________________________ እና የወንበር አበል ብር
_________/_________________________ በአጠቃላይ ብር _____/__________________
በኢትዮጵያውያን ዘመን አቆጣጠር በወሩ መጨረሻ ይከፈለዋል፡፡
 ከሚከፈለው ደመወዝ ላይ ሥራ ግብር ይቆርጣል፡፡
 በዚህ ውል ቁጥር ሦስት ላይ የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ ተቀጣሪው በራሱ ፍቃድ ከስራው ሲቀርና
የሚያቀርበው የሕክምና ማስረጃ ከሌለ ለቀረበት ቀን ክፊያ አይፈፀምም ፡፡
 ለሠራተኛው ክፍያ የሚፈፀመው ኮሌጁ ከትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ወይም ከትምህርት ሚኒስቴር ዕውቅና
አግኝቶ ሥራ ሲጀምር ነው፡፡
 ተቀጣሪው ያልሰራበት የስራ ቀን /ሰዓት/ አይከፈለውም፡፡
 በበዓላት ቀን ለተሰሩ ሥራዎች በአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጽ 67 መሠረት ይከፈለዋል፡፡
3. የሕክምና ፍቃድ

ቀጣሪው ከዚህ እንደሚከተለው በተገለፀ ሁኔታ የሕመም ፍቃድ ክፍያን በትምህርት ዘመን ወቅት ይሰጠዋል፡፡

1. የመጀመሪያውን አንድ ወር ከሙሉ ደመወዝ ክፊያ ጋር


2. ለሚቀጥሉት ሁለት ወራት ከደመወዙ ሃምሳ በመቶ
3. ለሚቀጥሉት ሦስት ወራት ያለክፍያ
4. እያንዳንዱ የታመመበት ቀን በሕክምና የምስክር ወረቀት የተረጋገጠ ካልሆነ በ”1” ላይ የተጠቀሰው ተፈፃሚ
አይሆንም፡፡በዚህ የሕመም ወቅት ተማሪዎች ያልተከታተሏቸውን ክፍለ ጊዜዎች በተመለከተ ተቀጣሪ ከዲን
እና/ወይም ከትምህርት ክፍል ኃላፊ ጋር በመሆን በመመካከር እነዚህን ከሕመሙ የተነሳ ያላስተማራቸውን
ክ/ጊዜዎች ለተማሪዎች ጊዜ አመቻችቶ መስጠት አለበት፡፡ ለማካካሻ ክፍለ ጊዜዎችም የሚከፈል ክፍያ
አይኖርም፡፡
4. የአሰሪው ግዴታዎች
በአዋጅ ቁጥር 377/96 በአንቀጽ 12 ከቁጥር 1-9 የተመለከቱትን ተግባራዊ ያደርጋል፡፡ ለተፈፃሚነታቸውም አስፈላጊውን
ሁሉ ያደርጋል፡፡
5. የሰራተኛው ግዴታዎች
በአዋጅ ቁጥር 377/96 በአንቀጽ 13 ከቁጥር 1-7 የተመለከቱትን ተግባራዊ የማድረግና ስራውን በታማኝነት መወጣት
አለበት፡፡

6. ውል ማደስና ማቋረጥን በተመለከተ


 ኮሌጁ ይህን ውል በቂ ምክንያት በሚያገኝበት ወቅት ለተቀጣሪው የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ በመስጠት ማቋረጥ
ይችላል፡ እንዲሁም መምህሩ በተማሪዎች በኩል የብቃት ችግር ጥያቄ ከተነሳበትና ይኸም በኮሌጁ ዲን
ከተረጋገጠና ተቀጣሪው በገባው ውል መሠረት ስራውን የኮሌጁን ሕግ በመጠበቅ ሳይሰራ ሲቀር ከስራ
ለማሰናበት በቂ ምክንያቶች ናቸው፡፡

 ኮሌጁ በሚያከናውነው የመዋቅር ለውጥ ተቀጣሪዎቹን የማሰናበት መብት አለው፡፡


 ኮሌጁ የተቀጣሪውን የቅጥር ውል ማቋረጥ ከፈለገ የአንድ ወር በፅሁፍ የተደረገ ቅድመ
ማሳወቂያን ለተቀጣሪ መስጠት አለበት፡፡
 በአንቀጽ 3 መሠረት ተቀጣሪው ስራውን መልቀቅ ከፈለገ ስራውን ከመልቀቁ 2 ወር ቀደም ብሎ በፅሁፍ
ማሳወቅ አለበት፡፡
 በቁጥር 5 ሐ እና መ ከተገለፀው ውጭ ይህን ውል ቀጣሪ ወይም ተቀጣሪ ቢያቋርጥ ውሉን ያቋረጠው ወገን
ለሌላኛው ተዋዋይ ወገን ብር 3000.00/ሦስት ሽህ ብር/ መክፈል ያለበት ሲሆን ነገር ግን በቁጥር 5 ሰ እና መ
መሠረት ከተቋረጠ አንደኛው ተዋዋይ ወገን ለሌላኛው ተዋዋይ ምንም አይነት የካሳ ወይም የጉዳት
ክፍያዎችን አይከፍልም፡፡
 በአጠቃላይ ያለማስጠንቀቂያ የሥራ ውል ለማቋረጥ በአዋጁ ቁጥር 377/96 አንቀጽ 27 ከፊደል ተራ ሀ-ተ እና
በዚሁ አንቀጽ ከንዑስ ቁጥር 2 እስከ 4 ያለው ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
7. ውሉ ተፈፃሚ የሚሆንበት ጊዜ
 ሁለቱ ተዋዋዮች ከተዋዋሉበት ቀን ጀምሮ ከ ---------- እስከ ------------- ለ/1/ አንድ አመት ፀንቶ ይቆያል፡፡
 አሰሪው ውሉን መቀጠል ወይም አለመቀጠሉን በአዋጅ ቁጥር 377/96 በአንቀጽ 24
መሠረት ተፈፃሚ እንዲሆን ይደረጋል፡፡
ውል ሰጭ ውል ተቀባይ
ስም _______________________ ስም ______________________
ፊርማ ______________________ ፊርማ _____________________
ቀን ______________________ ቀን ____________________
እማኞች
1. ስም _______________________
ፊርማ ______________________
ቀን ______________________
2. ስም _______________________
ፊርማ ______________________
ቀን ______________________

You might also like