Professional Documents
Culture Documents
165245
ቀን፡ 27/02/2013
አዲስ አበባ
1. አመልካች ባቀረበችው ክስ ከ 2000 ዓ.ም ጀምሮ እንደባልና ሚስት አብረን እየኖርን ልጆችና ንብረት አፍርተን ሳለ
ባለመግባባታችን ከቤት ወጥቻለሁ በማለት ዳኝነት ጠይቃለች፡፡
2. የተጠሪ መልስ፡-
2.1. አብረን መኖር የጀመርነው ከየካቲት ወር 2001 ዓ.ም ጀምሮ እንጂ በ 2000 ዓ.ም አይደለም፡፡ ይኸውም ቤተሰቦቿ ቤት
እያለች የመጀመሪያ ልጃችንን አርግዛ የመውለጃ ጊዜዋ በመቃረቡ ቤት ተከራይቼ አብረን መኖር ጀመርን፡፡ የመጀመሪያ
ልጃችን ቢታንያ ታረቀኝ የተወለደችው መጋቢት 23 ቀን 2001 ዓ.ም ለመሆኑ የየካ ክ/ከተማ ጤና ጣቢያ ከልደት ካርዷ
ላይ በፍ/ቤቱ ትዕዛዝ ማረጋገጥ ይችላል፡፡
2.2. አመልካች ባለመግባባታችን ግንኙነታችንን አቋርጫለሁ ባለችው በእኔ በኩል ግንኙነታችንን ከጋብቻ ለይቼ ሳላይ በሙሉ
እምነት ንብረት በስሟ ገዝቻለሁ፡፡ ለምሳሌ፡ የመኖሪያ ቤታችንን በስሟ ገዝቻለሁ፤ በእርሷ የባንክ ሒሳብ ተቀማጭ
ገንዘብ ሳጠራቅም ኖሬያለሁ፡፡ እርሷ ግን በግል ንብረት በማፍራት ዓላማ ላይ ብቻ ስላተኮረች በግራ ቀኛችን ዘመዶች እና
ጎረቤቶቻችን ከአንድ ዓመት በላይ ሳስመክር፣ ሳስወቅስ ኖሬያለሁ፣ ቢሆንም አሁን የልጆቻችንን ሕይወት በሚጎዳ አኳኋን
ኑሮአችንን በመበተኗ ባዝንም በጥያቄዋ ከመስማማት በቀር ሌላ አማራጭ የለኝም፡፡
2.3. አመልካች አራቱም ልጆቻችን ከእርሷ ጋር እንዲያድጉና የሞግዚትነት እና የአሳዳጊነት ሥልጣን በፍ /ቤት
እንዲሠጣት የጠየቀችሁ የህግ አግባብነት የለውም፡፡ እኔም ልጆቼን የማሳደግ እና የመንከባከብ መብት አለኝ፡፡
ሁለቱ ነፍስ ያወቁ ልጆች ከእኔ ጋር፤ ሁለቱ ትንንሾች ከእርሷ ጋር ሆነው በየጊዜው እንዳገኛቸው፤ የትምህርት እና
የአካላቸውን እንዲሁም የሞራላቸውን ሁኔታ እንድከታተል እንዲወሰንልኝ አመልክታለሁ፡፡
2.4. አመልካች በክፋ ልቦና ተነሳስታ የግል ንብረቴን እና የባንክ ሒሳቤን ስታስከብር፤ በስሟ ያፈራነውን የጋራ
ንብረቶች ግን በንብረት ዝርዝር ሳታካትት ደብቃለች፡፡ ይኸውም 1 ኛ. በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 11 የቤት ቁ. አዲስ
ስፋቱ በግምት 200 ካ/ሜ ወሰኑ በምሥራቅ - ሐና ወ/ኪዳን፤ በምዕራብ - መንገድ፤ በደቡብ - ታዴዎስ ወ/ኪዳን፤
በሰሜን - አቶ ገላልቻ የሆነና ሦስት ክፍል መኖሪያ ቤታችንን ከነማዕድ ቤቱ 2 ኛ. ተቀማጭ ገንዘባችንን
የምናጠራቅምባቸውን የሒሳብ ቁ. 013200403553 አዋሽ ባንክ እና የሒሳብ ቁ. 310501065043 የኢትዮጵያ
ንግድ ባንክ በስሟ የሚንቀሳቀሰውን ሆነ ብላ ደብቃለች፡፡
2.5. በስሟ የተገዛውን መኖሪያ ቤታችንን በተመለከተ ያየር ካርታ መሸጥ ስለማይፈቀድ የሽያጭ ውሉ ሕጋዊነት
እንዳያጣብን በማለት መሬቱን ፈርሶ ከነበረው ማዕድ ቤት ጋር በ 1992 ዓ.ም እንደተገዛ ተደርጎ ይፃፍ እንጂ
በትክክል ግዢ ፈፅመን ገንዘብ የተከፈለው እና ርክክብ የተደረገው በ 2007 ዓ.ም ህዳር ወር ነው፡፡
2.6. አመልካች ከእርሷ ጋር መኖር ከመጀመራችን በፊት ዕጣ ወጥቶልኝ የቅድሚያ ክፍያዎችንም አጠናቅቄ
ያገኘሁትን የግል የኮንዶሚኒየም ቤቴን በጋራ ንብረት ዝርዝር ውስጥ ማካተቷም የማይገባትን ጥቅም ለማግኘት
በማሰብ ነው፡፡
3. ተጠሪ ለተከበረው ፍ/ቤት የማቀርበው የፍትህ ጥያቄ፡-
3.1. አመልካች የጋራ ነው ብላ ያቀረበችው የኮንዶሚኒየም ቤት አብረን መኖር ከመጀመራችን በፊት በ 2000 ዓ.ም
መጨረሻ በዕጣ ደርሶኝ በ 2001 ዓ.ም ኅዳር ወር የቅድሚያ ክፍያ ፈፅሜ የተረከብኩ ሲሆን፤ በየጊዜው የሚከፈለውንም
ክፍያ ከኪራዩ በተገኘ አላባ ያጠናቀቅሁ ነው ፡፡ ስለዚህ የግል ቤቴ መሆኑ በሰነድ እና በሰው ማስረጃ ተጣርቶ ከጋራ ንብረት
ዝርዝር ውስጥ እንዲወጣ እና የግል ቤቱ ነው ተብሎ እንዲወሰንልኝ፤
3.2. የመኖሪያ ቤታችንም አብረን መኖር ከጀመርን በኋላ በ 2007 ዓ.ም አመልካች ሦስተኛዋን ልጃችንን ዕድላዊት ታረቀኝን
ለመውለድ ወደ ጤና ተቋም ከመግባቷ በፊት የቤቱን ጠቅላላ ዋጋ ብር 130,000.00 (አንድ መቶ ሰላሳ ሺህ) ከተጠቀሱት
የአዋሽ እና የኢትዮ. ንግድ ባንክ ከአመልካች የባንክ ሂሳብ ወጪ አድርጋ ለሻጭ አቶ ታዴዎስ ወ/ኪዳን ከፍላ ወደ ጤና
ጣቢያ የሄደች ለመሆኑ ተጣርቶ የጋራ ንብረት ውስጥ እንዲካተትልኝ፤
3.3. አመልካች በስሟ ካሉት የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች የሚንቀሳቀስ ገንዘብ የጋራ መሆኑ እንዲወሰንልኝና ግንኙነታችን
ከተቋረጠ እና በመሐላችን ቅሬታ ከተካረረ ከአንድ ዓመት ወዲህ ገንዘብ በማሸሽ መልክ ያወጣችው ካለ የባንክ
ስቴትመንት በፍ.ብ.ሥ.ሥ ሕግ ቁ. 145 መሠረት በትዕዛዝ ቀርቦ ከተጣራ በኋላ ድርሻዬን እንድትከፍለኝ
እንዲወሰንልኝ፤
3.4. ሁለቱ የመጀመሪያ ልጆቻችን ከእኔ ጋር እንዲኖሩ ይህ የማይሆንበት ምክንያት ካለ ደግሞ በማናቸውም
ጊዜ ሁሉንም ልጆቼን ለማየት እና ለማግኘት እኔም ሆንኩ እነርሱ ሲፈልጉ ለማንሸራሸር እና የሚፈልጉትን ነገር
እንዳደርግላቸው ለመውሰድ እንድችል እንዲወሰንልኝ በታላቅ ትህትና አመለክታለሁ፡፡
ተጠሪ
ታረቀኝ መኩሪያ
መዝ.ቁ. 165245
ቀን፡ 27/02/2013
አዲስ አበባ
ተጠሪ
ታረቀኝ መኩሪያ
መዝ.ቁ. 165245
ቀን፡ 03/03/2013
አዲስ አበባ
በ 20/02/2013 ዓ.ም ተጠሪ ባቀረብኩት የእግድ አቤቱታ መሠረት የተከበረው ፍ/ቤት በአዋሽ ባንክ እና በኢት/ንግድ ባንክ
ጠቅሼ ባቀረብኳቸው የሒሳብ ቁጥሮች ያለው ሒሳብ ተከብሮ እንዲቆይ አዝዞልኝ ነበር፡፡
ይሁን እንጂ የኢት/ንግድ ባንክ የሂሳብ ቁ.310501065043 የሆነ የለም ብሎ ባንኩ ስለመሰለኝ እርግጠኛ የሆነ የሒሳብ
ቁጥር ባላገኝም እንኳ በአመልካች ስም በንግድ ባንኩ ተቀማጭ ገንዘብ እንዳለን እርግጠኛ ስለሆንኩ በባንኩ ውስጥ በስሟ ደብተር
ተከፍቶ የተቀመጠ ሒሳብ እንዲታገድ ተብሎ እንዲታዘዝልኝ በትህትና አመለክታለሁ፡፡
አመልካች
ታረቀኝ መኩሪያ