You are on page 1of 1

ቀን መስከረም 4 ቀን 1994 ዓ.

የመኖሪያ ቤት እና የእርሻ ቦታ ስጦታ ውል ስምምነት

ስጦታ አድራጊ፡- ……………..1 ኛ/ ወ/ሮ ደሜ ሀይሌ ዜግነት ኢትዮጵያዊ

አድራሻ፡- አዲስ አበባ ወረዳ 28 አንቆርጫ ቀ/ገ/ማ

ስጦታ ተቀባይ፡- ……………… አቶ ካብታሙ አርጋ /ዜግነት ኢትዮጵያዊ

አድራሻ፡- አዲስ አበባ ወረዳ 28 አንቆርጫ ቀ/ገ/ማ

እኛ ስጦታ አድራጊዎች ወ/ሮ ደሜ ሀይሌ ለልጃችን ለአቶ ካብታሙ አርጋ በዚህ በአዲስ አበባ ከተማ ወረዳ 28 አንቆርጫ
ቀበሌ ገበሬ ማህበር ክልል ውስጥ አዋሳኞቹም በምስራቅ ቶሎሳ ይዞታ በምእራብ ወንዝ በሰሜን አቶ ወንዱ መንግስቱ
በደቡብ ወ/ሮ ደሜ ሀይሌ የሚያዋስነውን ከይዞታችን ላይ ቀንሼ የሰጠሁት ቤት መሆኑን በስሙ አዛውሮ እንዲጠቀምበት
የሰጠነው ሲሆን ይህን ስጦታ በፍ/ብ/ሕ/ቁ/ 2427 መሰረት የሰጠሁት መሆኑን በፊርማችን እናረጋግጣለን፡፡

እኔም ስጦታ ተቀባይ አቶ ካብታሙ አርጋ ከላይ በተጠቀሰው መሰረት በዚህ በአዲስ አበባ ከተማ ወረዳ 28 አንቆርጫ
ቀበሌ ገበሬ ማህበር ውስጥ ከሚገኘው ይዞታቸው ላይ ቀንሰው የሰጡኝን የመኖሪያ ቤት በስሜ አዛውሬ እንድጠቀምበት
የሰጡኝ ሲሆን ይህን ስጦታ በፍ/ብ/ሕ/ቁ/ 2436 መሰረት የሰጠችን መሆናኔን በፊርማችን አረጋግጣለሁ፡፡

ይህንን የስጦታ ውል ስናደረግ በቦታው የነበሩ እማኞች

1. አቶ አሸናፊ ደምሴ አድራሻ፡- አ.አ ወረዳ 28 አንቆርጫ ቀ/ገ/ማህበር


2. አቶ ደረጄ ቶሎሳ አድራሻ፡- አ.አ ወረዳ 28 አንቆርጫ ቀ/ገ/ማህበር
3. አቶ ነጋሽ ጥላሁን አድራሻ፡- አ.አ ወረዳ 28 አንቆርጫ ቀ/ገ/ማህበር

እኛም እማኞች ስጦታ አድራጊዎች በትክክለኛ አእምሯቸው ማንም ሰው ሳያስገድዳቸው ይህን የስጦታ ውል ለአቶ
ካብታሙ አርጋ ስጦታ ተቀባይ ካላቸው ይዞታ ላይ ሲሰጡ ያየን በቦታው የነበርን መሆናችንን በውሉ ላይ ፈርመናል፡፡ ይህ
የስጦታ ውል በአራት ኮፒ ተፅፎ በግራና ቀኝ በስጦታ አድራጊዎች እና በስጦታ ተቀባይ እጅ ተቀማጭ ይሆናል፡፡

የስጦታ አድራጊዎች ስምና ፊርማ የስጦታ ተቀባይ ስምና ፊርማ

1. -------------------------------------------- 1. ----------------------------------------
የምስክሮች ስምና ፊርማ
1. --------------------------------------------
2. --------------------------------------------
3. --------------------------------------------

You might also like