You are on page 1of 7

በቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት

የሕግ ጉዳዮች ክርክር ዳይሬክቶሬት


BOLE SUB-CITY ADMINISTIRATION JUSTICE OFFICE
LITIGATION AFFAIRS DIRCTORATE

መ/ቁ -145803
ቀን -19/03/2015 ዓ.ም
በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት
ለቦሌ ምድብ 6 ኛ ፍ/ብሄር ችሎት
አዲስ አበባ

ከሳሾች-------1 ኛ/ ባልቻ ጉርሙ


2 ኛ/ ሰቦቃ ገመቹ
3 ኛ/ ማሞ አቦዬ
4 ኛ/ ገነት ክፈለው
5 ኛ/ ዳንኤል በቀለ ሪፖረርት አቀራረፅ
6 ኛ/ ዮሃንስ በቀለ
7 ኛ/ ተዋበች ፈንታ
8 ኛ/ እሜቱ አሰፋ
9 ኛ/ አዲስ አሰፋ
10 ኛ/ ቢኒያም አሰፋ
አድራሻ፡- ቦል ክ/ከተማ ወረዳ 07
ተከሳሾች፡ -------1 ኛ/ ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 07 አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ
2 ኛ/ ሾላ አክሲዮን ማህበር
አድራሻ፡- ቦል ክ/ከተማ ወረዳ 07
ከሳሾች ህዳር 02 ቀን 2015 ዓ.ም ላቀረቡት ክስ ከ 1 ኛ ተከሳሽ የቀረበየመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ እና በአማራጭ የቀረበ
የመከላከያ መልስ ነው፡፡
1. የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ
1.1 በነገሩ ልንከሰስ የማይገባ ስለመሆኑ፡- ከሳሾች አሁን ክርክር ያስነሳውን ይዞታ 1 ኛ ተከሳሽ በ 1997 ዓ.ም ምንም
ከሳና ምትክ ቦታ ሳይሰጠን በጉልበት ከይዞታችን አፈናቅሎናል ይበሉ እንጂ በቀድሞ ስሙ ቦሌ ኮተቤ ቀበሌ ገበሬ
ማህበር ስር ሲተዳደር ለነበረ ይዞታ በጉልበት ከይዞታቸው ያፈናቀላቸው የአሁን 1 ኛ ተከሳሽ ስለመሆኑ
ባልተረጋገጠበት እና ማስረጃ ባልቀረበበት እንዲሁም ቦታውን ማስለቀቅን በተመለከተ የ 1 ኛ ተከሳሽ ስልጣን
እና ሃላፊነት እንዳልሆነ እየታወቀ 1 ኛ ተከሳሽ ክርክር ያስነሳውን የቀድሞ ይዞታችን የነበረውን ምንም ህጋዊ
መብት ለሌለው 2 ኛ ተከሳሽ ከህግና ስርአት ውጪ ካርታ ሳይኖር የወረዳው ግንባታ ፍቃድ ቁጥጥር ጽ/ቤት
ለ 2 ኛ ተከሳሽ በቀን 02/02/2015 ዓ.ም የአጥር እድሳት በሚል ሰበብ የግንባታ ፍቃድ በመስጠቱ 2 ኛ ተከሳሽ
ምንም መብት ሳይኖረው አጥሮ እንዲይዝ አድርጓል በሚል የቀረበው የከሳሾች አቤቱታ በግልፅ የሚያሳየው እና
አምነው የገለፁት ነገር የአጥር ዕድሳት በሚል የግንባታ ፍቃዱን የሰጠው የአሁን 1 ኛ ተከሳሽ ሳይሆን የወረዳው
ግንባታ ፍቃድ እና ቁጥጥር ጽ/ቤት በመሆኑ እንዲሁም ቦታው ለግሪን ኤሪያነት እንዲውል ያደረገው የከተማ
አስተዳደሩ የአካባቢ ጥበቃ እና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን በመሆኑ 1 ኛ ተከሳሽ በጉዳዩ ገብተን ውሳኔ ያልሰጠን
በመሆኑ በጉዳዩ የምንከሰስበት ምክንያት ስለማይኖር በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 244/2/መ መሰረት ጉዳዩ
አይመለከታቸውም ሊከሰሱ አይገባም ተብሎ በብይን እንድንሰናበት እንጠይቃለን፡፡
1.2 ከሳሾች በይዞታው ላይ ክስ ለማቅረብ መብት የሌላቸው ስለመሆኑ፡- ከሳሾች ቦታው በእኛ ይዞታ ስር ነበር ይበሉ
እንጂ ይህ ስለመሆኑ ምንም አይነት አግባብነት ያለው ማስረጃ አላቀረቡም እነደማስረጃ የቀረቡት የእርሻ መሬት
የግብር ደረሰኞችም ቢሆኑ በግብር ደረሰኝ አካራካሪው ይዞታ ላይ ያለን መብት ለማስረዳት የማይቻል እና
ደረሰኞቹ ክርክር ለተነሳበት ይዞታ ስለመገበራቸው የማያመለክቱ እና በህግ ፊትም የፀና ውጠየት የላቸውም፡፡
ሌላኛው ከሳሾች ወራሾች ነን ብለው ያያያዙት ማስረጃም የየትኛውን የሟቾች ንብረት እንደወረሱ
የማያመለክት እና ሟቾች ያልነበራቸውን መብት ወራሾች ሊወርሱ ስለማይችሉ እንዲሁም ስልጣን ባለው አካል
ክርክር ለተነሳበት ቦታ ባለመብት ስለመሆናቸው ህጋዊ ማስረጃ ባላቀረቡበት ይህንን ክስ ለመመስረት
ስለማይችሉ በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 33/2 መሰረት አለን የሚሉትን መብት እና ጥቅም በተገቢው አላስረዱም ተብሎ
በብይን ውድቅ እንዲደረግልን፡፡
1.3 ክሱ በይርጋ የታገደ ስለመሆኑ፡- ንብረት አላግባብ ተወስዶብኛል ወይም ለተወሰደብኝ ንብረት ካሳ ይገባኛል
የሚል አካል መብቱን መጠየቅ ያለበት ንበረቱን ባጣ ወይም ከጁ ከወጣ በሁለት(2) አመት ውስጥ እንደሆነ
በፍ/ብ/ህ/ቁ 2143/1 ላይ ተደንግጓል፡፡ይህ እንኳን ቢታለፍ በማናቸውም የፍታብሄር ጉዳዮች ላይ በፍ/ብ/ህ/ቁ
1845 መሰረት በአስር(10)ዓመት ውስጥ ክስ ካልቀረበ ክስ የማቅረብ መብቱ በይርጋ እንደሚታገድ ተደንግጓል፡፡
ስለሆነም በቀረበው የከሳሽ አቤቱታ ላይ ያከራከረው ይዞታ ተወስዶብናል እንዲሁም በንብረት እና ቤታችን ላይ
ጉዳት ደርሶብናል የሚሉት በ 1997 ዓ.ም ሲሆን ይዞታው የከሳሾች አለመሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ይዞታው
የከሳሾች ነው እንኳን ቢባል የጉዳት ካሳ እና ምትክ ቦታ ይሰጠን ቅሬታ ማቅረብ የነበረባቸው ይዞታው አእጃችን
ወጣ ከሚሉበት ከ 1997 ዓ.ም አንስቶ በሁለት አመት ውስጥ በቂ ምክንያት ካለ ደግሞ ግፋ ቢል በአስር አመት
ውስጥ በመሆኑ እና በዚህ ጊዜ ገደብ ውስጥ ቅሬታ አቅርበው ምላሽ ስለማጣታቸው ምንም አይነት ማስረጃ
ሳያቀርቡ አስራ ስምንት(18) ዓመት በላይ ካለፈ በኋላ ቆይተው ክስ ማቅረባቸው ይርጋ ስለሚያግደው
በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 244/2/ሠ መሰረት መዝገቡ በብይን እንዲዘጋልን፡፡
1.4 ከሳሾች ተገቢውን ዳኝነት ከፍለው ያልቀረቡ ስመሆኑ፡- ከሳሾች ይገባኛል የሚሉት የይዞታ ስፋት 10.137 ካ.ሜ
በላይ እና አላግባብ ለወደመብን እና ለተወሰደብን ንብረት እና ቤት የጉዳት ካሳ 250.000 ብር ተከሳሾች
ሊከፍሉን ይገባል በማለት አቤቱታ ያቀረቡ ቢሆንም ለጠየቁት ዳኝነት ገምተው ያቀረቡት ዋጋ 250.000 ብር
ብቻ ነው ይህ ደግሞ ተቀባይነት የሌለው እና በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የዚህን ያክል ስፋት ያለው ይዞታ
በየትኛውም መስፈርት በከሳሾች የተገለፀውን ያክል አነስተኛ የዋጋ ግምት ሊኖረው የማይችል እና የጉዳት ካሳ
ሊከፈለን ይገባል በማለት ያቀረቡት የብር መጠን እራሱ 250.000 ብር ስለሆነ የአካባቢውን የመሬት ሊዝ ዋጋ
መሰረት ተደርጎ ተገቢው ግምት ከወጣለት በኋላ ተገቢውን ዳኝነት ከፍለው እንዲቀርቡ እንዲታዘዝልን
እንጠይቃለን፡፡
1.5 የ 1 ኛ ተከሳሽ ኃላፊዎች ስልጣናቸውን ያላግባብ በመጠቀም ከህግ ውጪ ያለምንም የካሳ ክፍያ እና ምትክ ቦታ
ከይዞታችን እና ከንብረታችን በማፈናቀል የእርሻ መሬታችን እና ንብረታችንን በመውሰድ አሁን ክስ
ያቀረብንበትን ይዞታ ከእጃችን እንዲወጣ አድርገዋል በሚል የቀረበ ክስ ነው፡፡ ይህ ከሆነ ደግሞ በአስተዳደር
ስነስርአት አዋጅ ቁጥር 1183/2011 መሰረት መሰል አስተዳደራዊ ውሳኔዎችን እና እርምጃዎችን ተገቢ
አይደሉም መብቴን ይጎዳሉ ብሎ ለሚያምን ማንኛውም አካል በቅድሚያ ለሚመለከታቸው አስተዳደራዊ
ተቋማት ቅሬታቸውን አቅርበው ማለትም አስተዳደራዊ መፍትሄን አሟጠው የመጨረሻ ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ
በዚህም ውሳኔ ቅር የሚሰኝ አካል ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አስተዳደራዊ ችሎት ጉዳዩን ከሚያቀርብ በቀር
በቀጥታ መደበኛ ፍርድ ቤት ላይ ክርክር ሊያቀርብ አይችልም፡፡ስለሆነም ከሳሾች ያቀረቡት ክስ በዚህ አዋጅ
የተመላከተውን ስነስርዐት ያልተከተለ እና ጉዳዩን ለማየት ስልጣን ለሌለው ፍ/ቤት የቀረበ በመሆኑ
በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 244/2/ሀ መሰረት መዝገቡ በብይን ውድቅ እንዲደረግልን እና ለተጉላላንበት በቂ ኪሳራ በቁርጥ
ከሳሾች እንዲከፍሉን ተብሎ ውሳኔ እንዲሰጥልን እንጠይቃለን፡፡

2. ፍ/ቤቱ መቃወሚያችንን የሚያልፍበት የህግ አግባብ ካለ በአማራጭ የቀረበ መልስ

2.1 የ 1 ኛ ተከሳሽ ሃላፊዎች ስልጣንን ያላግባብ በመጠቀም ከህግ ውጪ ያለምንም የካሳ ክፍያ እና ምትክ ቦታ
ሳይሰጠን በ 1997 ዓ.ም ከይዞታችን እና ከንብረታችን በማፈናቀል የእርሻ መሬታችን እና ንብረታችንን
በመውሰድ አሁን ክስ ያቀረብንበትን ይዞታ ከእጃችን እንዲወጣ እና ለአረንጓዴ መናፈሻነት አግልግሎት እንዲውል
አድርገዋል በሚል የቀረበው ክስ

ከሳሾች ይዞታውን ካሳ እና ምትክ ሳይሰጠን በጉልበት ከእጃችን እንዲወታ ተደረገብን ይበሉ እንጂ በይዞታው ላይ
መብት እና ጥቅም እንዳላቸው በማስረጃ ባላረጋገጡበት መብት እና ጥቅም አላቸው እንኳን በቀድሞ ስሙ ቦሌ
ኮተቤ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ስር ሲተዳደር ለነበረ ይዞታ በጉልበት ከይዞታቸው ያፈናቀላቸው የአሁን 1 ኛ ተከሳሽ
ስለመሆኑ ባልተረጋገጠበት እና ማስረጃ ባልቀረበበት እንዲሁም ቦታውን ማስለቀቅን በተመለከተ የ 1 ኛ ተከሳሽ
ስልጣን እና ሃላፊነት እንዳልሆነ እየታወቀ እንዲሁም ከሳሾች በክሳቸው ላይ በግልፅ አምነው የገለፁት ነገር
የአጥር ዕድሳት በሚል የግንባታ ፍቃዱን የሰጠው የአሁን 1 ኛ ተከሳሽ ሳይሆን የወረዳው ግንባታ ፍቃድ እና
ቁጥጥር ጽ/ቤት መሆኑን አረጋግጠው የገለፁት በመሆኑ እንዲሁም ቦታው ለግሪን ኤሪያነት እንዲውል ያደረገው
የከተማ አስተዳደሩ የአካባቢ ጥበቃ እና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን በመሆኑ 1 ኛ ተከሳሽ በጉዳዩ ገብተን ውሳኔ
ያልሰጠን በመሆኑ በጉዳዩ የምንከሰስበት ምክንያት ባይኖርም ክሱ ይመለከታችኋል እንኩዋን ቢባል ክርክር
ያስነሳው ይዞታ መሬት ባንክ የገባ የመንግስት ቦታ ሲሆን ለአሁን 2 ኛ ተከሳሽ በጊዜያዊነት ቦታውን እንዲያለማ
ለአረንጓዴ ልማት በሚል በጊዜያዊነት የተላለፈ በመሆኑ ከሳሾች በይዞታው ላይ መብት እና ጥቅም እንዳላቸው
የሚያሳይ ማስረጃ ባላቀረቡበት የቀረበ ክስ በመሆኑ እና ቦታው መሬት ባንክ የገባ የመንግስት ይዞታ በመሆኑ
የከሳሾች አቤቱታ ውድቅ እንዲደረግልን እንጠይቃለን፡፡
2.2 ከሳሾች ነባር አርሶ አደር እና የአርሶ አደር ልጆች መሆናችንን በአርሶ አደር ኮሚቴ አረጋግጠናል ያሉት ተቀባይነት
የሌለው እና በማስረጃም ያልተደገፈ መሆኑ እንዳለ ሆኖ በወረዳው ውስጥ ነባር አርሶ አደር እና የአርሶ አደር
ልጆች ናቸው ቢባል እንኳን ክርክር ባስነሳው ይዞታ ላይ አርሶአደር ስለመሆናቸው ባልተረጋገጠበት እንዲሁም
በይዞታው ላይ መብት እንዳላቸው ያረጋግጥልናል ብለው ያቀረቡት የእርሻ መሬት ግብር ደረሰኞችም ቢሆኑ
በግብር ደረሰኝ አካራካሪው ይዞታ ላይ ያለን መብት ለማስረዳት የማይቻል እና ደረሰኞቹ ክርክር ለተነሳበት ይዞታ
ስለመገበራቸው የማያመለክቱ እና በህግ ፊትም የፀና ውጠየት የላቸውም፡፡ ሌላኛው ከሳሾች ወራሾች ነን ብለው
ያያያዙት ማስረጃም የየትኛውን የሟቾች ንብረት እንደወረሱ የማያመለክት እና ሟቾች ያልነበራቸውን መብት
ወራሾች ሊወርሱ ስለማይችሉ እንዲሁም ስልጣን ባለው አካል ክርክር ለተነሳበት ቦታ ባለመብት ስለመሆናቸው
ህጋዊ ማስረጃ ባላቀረቡበት ያከራከረው ይዞታ ተወስዶብናል እንዲሁም በንብረት እና ቤታችን ላይ ጉዳት
ደርሶብናል የሚሉት በ 1997 ዓ.ም ሲሆን ይዞታው የከሳሾች አለመሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ይዞታው የከሳሾች ነው
እንኳን ቢባል በቦታው ላይ ምንም አይነት ቤትም ሆነ ንብረት ያልነበረ መሆኑ እና በይዞታው ላይ የነበረን ቤት እና
ንብረት ወድሞብናል የሚለው አቤቱታ ከእውነት የራቀ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በይዞታው ልይ ቤት እና ንበረት
ነበር ቢባል እንኳን ለደረሰው ጉዳት የጉዳት ካሳ እና ምትክ ቦታ ይሰጠን ቅሬታ ማቅረብ የነበረባቸው ይዞታው
አእጃችን ወጣ ከሚሉበት ከ 1997 ዓ.ም አንስቶ በሁለት አመት ውስጥ በቂ ምክንያት ካለ ደግሞ ግፋ ቢል በአስር
አመት ውስጥ በመሆኑ እና በዚህ ጊዜ ገደብ ውስጥ ቅሬታ አቅርበው ምላሽ ስለማጣታቸው ምንም አይነት
ማስረጃ ሳያቀርቡ አስራ ስምንት(18) ዓመት በላይ ካለፈ በኋላ ቆይተው ክስ ማቅረባቸው ይርጋ ስለሚያግደው
በከሳሾች የተጠየቀው የይዞታ ይመለስልኝም ሆነ የካሳ ሊሰጠኝ ይገባል አቤቱታ ተቀባይነት የሌለው በመሆኑ
የከሳሾች አቤቱታ ሙሉ በሙሉ ውድቅ ተደርጎ አላግባብ ተከሰን ለተጉላላንበት በቂ ኪሳራ በቁርጥ እንዲተኩልን
እንጠይቃለን፡፡

የቀረበው መልስ በእውነት የቀረበ መሆኑን


በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 92/3 መሰረት እና

በቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት


የሕግ ጉዳዮች ክርክር ዳይሬክቶሬት
BOLE SUB-CITY ADMINISTIRATION JUSTICE OFFICE
LITIGATION AFFAIRS DIRCTORATE

መ/ቁ -145803
ቀን -19/03/2015 ዓ.ም
በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት
ለቦሌ ምድብ 6 ኛ ፍ/ብሄር ችሎት
አዲስ አበባ

ከሳሾች-------1 ኛ/ ባልቻ ጉርሙ


2 ኛ/ ሰቦቃ ገመቹ
3 ኛ/ ማሞ አቦዬ
4 ኛ/ ገነት ክፈለው
5 ኛ/ ዳንኤል በቀለ
6 ኛ/ ዮሃንስ በቀለ
7 ኛ/ ተዋበች ፈንታ
8 ኛ/ እሜቱ አሰፋ
9 ኛ/ አዲስ አሰፋ
10 ኛ/ ቢኒያም አሰፋ
አድራሻ፡- ቦል ክ/ከተማ ወረዳ 07
ተከሳሾች፡ -------1 ኛ/ ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 07 አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ
2 ኛ/ ሾላ አክሲዮን ማህበር
አድራሻ፡- ቦል ክ/ከተማ ወረዳ 07
በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 234 መሰረት የቀረበ የማስረጃ ዝርዝር

የሰነድ ማስረጃ

1. የአካባቢ ጥበቃ እና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን ክርክር የተነሳበት ቦታ ከነይዞታ ካርታው ጭምር በግሪን ኤሪያነት እንዲለማ
ለ 2 ኛ ተከሳሽ በቀን 24/07/2013 ዓ.ም የሰጠበት ደብዳቤ 2 ገፅ ኮፒ ዋናው በጽ/ቤቱ የሚገኝ
2. የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 07 ግንባታ ፍቃድ ቁጥጥር ጽ/ቤት ለ 2 ኛ ተከሳሽ ለግነባታ በሚል ፍቃድ የሰጠበት
01 ገፅ ኮፒ ዋናው በጽ/ቤቱ የሚገኝ
3. ቦሌ ክ/ከተማ መሬት ልማት አስተዳደር ጽ/ቤት ቦታው መሬት ባንክ የገባ እና በጊዜያዊነት ለ 2 ኛ
ተከሳሽ እንዲያለማው በሚል የተሰጠ መሆኑን የገለፀበት 01 ገፅ ኮፒ ዋናው በጽ/ቤቱ የሚገኝ
4. ክርክር ባስነሳው ይዞታ ላይ ካሳ ስለመበላቱ እና ክርክር ያስነሳውን ይዞታ በአርሶአደርነት ይዘው
ሲጠቀሙበት የነበሩ ሰዎች እነማ እንደነበሩ የሚያስረዳልንን ማስረጃ በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 145 መሰረት ከአ.አ
መሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ፍ/ቤቱ በትዕዛዝ እንዲያስቀርብልን፡፡
5. የቦሌ ክ/ከተማ መሬት ልማት እና አስተዳደር ፅ/ቤት ክርክር ያስነሳው ይዞታ በ 1988 እና በ 1997 በተነሳ
አየር ካርታ ቦታው ላይ የተገነባ ቤት መኖር አለመኖሩን በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 145 መሰረት አታርቶ ምላሽ
እንዲሰጥ ፍ/ቤቱ ትዕዛዝ እንዲሰጥልን፡፡

ይህ የቀረበው የማስረጃ ዝርዝር በእውነት የቀረበ መሆኑን


በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁጥር 92/3/ መሠረት አረጋግጣለሁ

በቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት


የሕግ ጉዳዮች ክርክር ዳይሬክቶሬት
BOLE SUB-CITY ADMINISTIRATION JUSTICE OFFICE
LITIGATION AFFAIRS DIRCTORATE

መ/ቁ -53375
ቀን -04/04/2015 ዓ.ም
በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት
ለቦሌ ምድብ 5 ኛ ውርስ ሀ ችሎት
አዲስ አበባ

ከሳሾች-------1 ኛ/ ወ/ሮ ገነት ደምሴ


2 ኛ/ አቶ ሸዋንግዛው ደምሴ
3 ኛ/ አቶ ወንድወሰን ደምሴ
አድራሻ፡- ቦል ክ/ከተማ ወረዳ 07
ተከሳሾች፡ -----1 ኛ/ ወ/ሮ አለሚቱ ገርቢ
2 ኛ/ መንግስቱ ደምሴ
3 ኛ/ ወ/ሮ ብርሃኔ ደምሴ

ጣልቃ ገብ፡-1 ኛ ወ/ሮ ዝናሽ ደምሴ


2 ኛ/ ወ/ሪት ናታሊን ዳኜ

በህዳር 13 ቀን 2015 ዓ.ም በተሰጠው ዕግድ ላይ ከቦሌ ክ/ከተማ የከተማ ውበት እና አረንጓዴ ልማት ጽ/ቤት የተሰጠ
አስተያየት

በዚህ መዝገብ ላይ የተጠየቀው ቦታ በወራሾች መካከል ክርክር ሊካሄድበት የማይችል እና የሟች አቶ ደምሴ ጩቄ
የውርስ ሀብትም ያልሆነ እና በመንግስት እጅ ስር የሚተዳደር በከተማው መዋቅራዊ ፕላን መሰረት በወረዳ ደረጃ
ለመናፈሻነት በሚል በግሪን ኤሪያነት የተያዘ የመንግስት ቦታ በመሆኑ ወራሾች በዚህ ይዞታ ላይ መብት እና ጥቅም
ሳይኖራቸው ቦታው ላይ የሚደረገውን የልማት ስራ ለማደናቀፍ ዕግድ እንዲሰጥላቸው መጠየቃቸው ተገቢነት የሌለው
እና የተጀመረውን የልማት ሂደት እያደናቀፈብን በመሆኑ የተሰጠው ዕግድ እንዲነሳልን እየጠየቅን በይዞታው ላይ
ወራሾች መብት እና ጥቅም ሳይኖራቸው አላቸው እንኳን ቢባል በወራሽነት መዝገብ ላይ የእነሱ ያልሆነን ንብረት
በውርስ ሪፖርት ላይ ማካተት የማይችሉ እና በሌላ ክስ የመፋለም ክርክር የሚቀርብበት እንጂ በዚህ መዝገብ ተጣቶ
ውሳኔ የሚሰጥበት አለመሆኑ እንዳለ ሆኖ መታየት ይቻላል የሚባል ከሆነም በዚህ መዝገብ ላይ ጣልቃ ገብተን
መብታችንን እንድናስከብር ፍ/ቤቱ ትዕዛዝ እንዲሰጥበት እንጠይቃለን፡፡

ይህ የቀረበው አስተያየት በእውነት የቀረበ መሆኑን


በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁጥር 92/3/ መሠረት አረጋግጣለሁ

በቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት


የሕግ ጉዳዮች ክርክር ዳይሬክቶሬት
BOLE SUB-CITY ADMINISTIRATION JUSTICE OFFICE
LITIGATION AFFAIRS DIRCTORATE

መ/ቁ -145803
ቀን -19/03/2015 ዓ.ም
በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት
ለቦሌ ምድብ 6 ኛ ፍ/ብሄር ችሎት
አዲስ አበባ
ከሳሾች-------1 ኛ/ ባልቻ ጉርሙ
2 ኛ/ ሰቦቃ ገመቹ
3 ኛ/ ማሞ አቦዬ
4 ኛ/ ገነት ክፈለው
5 ኛ/ ዳንኤል በቀለ
6 ኛ/ ዮሃንስ በቀለ
7 ኛ/ ተዋበች ፈንታ
8 ኛ/ እሜቱ አሰፋ
9 ኛ/ አዲስ አሰፋ
10 ኛ/ ቢኒያም አሰፋ
አድራሻ፡- ቦል ክ/ከተማ ወረዳ 07
ተከሳሾች፡ -------1 ኛ/ ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 07 አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ
2 ኛ/ ሾላ አክሲዮን ማህበር
አድራሻ፡- ቦል ክ/ከተማ ወረዳ 07

በቀን 18/05/2015 ዓ.ም ለፍ/ቤቱ በቀረበው የትዕዛዝ ውጤት ላይ ከ 1 ኛ ተከሳሽ የተሰጠ አስተያየት

1. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ እና የቦሌ ክ/ከተማ መሬት ልማት
አስተዳደር ጽ/ቤት በጋራ ክርክር ያስነሳው ይዞታ በልዩ ስሙ ጃክሮስ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኘው
ስፋቱ 10፣137 ካ.ሜ የሆነው ቦታ በማን ስም ተመዝግቦ እና በማን ይዞታ ስር ተካቶ እንደቆየ ተጣርቶ
እንዲቀርብ ፍ/ቤቱ ባዘዘው መሰረት በ 2 ኛ ተከሳሽ በውስጡ ባሉ ነዋሪዎች በአረንጓዴ ልማት እየለማ ያለ
መሆኑን እና ለ 2 ኛ ተከሳሽ ከ 1992 ዓ.ም ጀምሮ በፈር ግሪን በሚል ተመላክቶ የተሰጠ ቢሆንም በይዞታ
ማረጋገጫ ካርታ ወሰን ውስጥ ያልተካተተ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ይህም የሚያሳየው ክርክር ያስነሳው ይዞታ
ከ 1992 ጀምሮ በ 2 ኛ ተከሳሽ ተይዞ የቆየ መሆኑን እና በ 1 ኛ ተከሳሽ በኩል መሬት ባንክ እንዲገባ የተደረገ
በጊዜያዊነት ለግሪን ኤሪያ ልማት በሚል ለማህበሩ የተሰጠ መሆኑን የሚያሳይ እና በቀረበብን ክስ ላይ
የሰጠነውን ምላሽ የሚያጠናክር ውጤት የቀረበ ሲሆን 1 ኛ

ተከሳሽ ክርክር ያስነሳው ይዞታ መሬት ባንክ የገባ መሆኑን ጠቅሰን በማስረጃነትም አያይዘን ያቀረብነው
ሰነድ የሚያስረዳልን በባለቤትነት ደረጃ ቦታው የመንግስት መሆኑን የሚያሳይ እና ቦታውን ከመያዝ እና
ከማልማት አንፃር ለ 2 ኛ ተከሳሽ የተሰጠ መሆኑን የቀረበው ውጤት የሚያጠናክርልን በመሆኑ እና ከሳሾች
ክርክር ባስነሳው ይዞታ ላይ መብት እና ጥቅም እንዳላቸው የሚያሳይ ምንም አይነት ማስረጃ ባለመኖሩ
የቀረበው ውጤት ላይም ከሳሾች በቦታው ላይ ሲገለገሉበት እንደነበር እና የነሱ እንደነበር የቀረበ ነገር
ባለመኖሩ የከሳሾች ክስ ውድቅ እንዲደረግልን እንጠይቃለን፡፡
2. በሁለተኛ ደረጃ እንዲጣራ በፍ/ቤቱ የታዘዘው ከዚህ በፊት ይዞታው የማን እንደነበር እና በዚህ ይዞታ ላይ
ካሳ እና ምትክ የተሰጠ መሆን አለመሆኑን እንዲገለፅ ባለው መሰረት በ 1990 ዎቹ ከይገባኛል ነፃ የተደረገ
መሬት (ቦታ) እንደነበር እና ከ 1990 በፊት ባለቤትነቱ የማን እንደነበር ማወቅ አልተቻለም በሚል ምላሽ
የቀረበ ሲሆን በዋናነት ከ 1990 በፊት ይዞታው በማን እጅ እንደነበር የሚረጋገጠው በሚመለከታቸው
ተቋማት በሚቀርብ የሰነድ ማስረጃም ጭምር እንደሆነ እና በከሳሾች በኩልም ከሚመለከተው አካል
ይዞታው የእነሱ እንደነበር የሚገልፅ ምንም አይነት ማስረጃ የሌላቸው እና የግብር ደረሰኝ በማለት
እንዲሁም የሰው ምስክሮች በሚል ካቀረቡት ውጪ እንደማስረጃ ያያያዙት ነገር የሌለ እና በፍ /ቤቱ በተሰጠ
ትዕዛዝ ላይ በቀረበው ውጤት ላይም ስለከሳሾች የይዞታው ባለቤት ስለመሆናቸው ማስረጃ ባልቀረበበት
የባለቤትነት መብትን በሰው ምስክር ብቻ ማረጋገጥ የማይቻል እና የግብር ደረሰኞቹም ክርክር በተነሳበት
ይዞታ ላይ ስለመገበራቸው የሚያሳይ ነገር ባለመኖሩ እንዲሁም ይዞታው ከ 1990 በፊት የከሳሾች ነበር
እንኳን ቢባል እስካሁን መብት እና ጥቅማቸውን ለማስከበር ምንም አይነት ጥረት ሳያደርጉ ከ 25 ዓመት
በኋላ ይህንን ዳኝነት መጠየቅ እንደማይችሉ እና ለተጎዱ አርሶ አደሮች ተጠቃሚነት በሚል የወጣውን
መመሪያ ቁጥር 20/2013 አላግባብ በመተርጎም ከቅን ልቦና ውጪ አላግባብ ለመበልፀግ በሚል የቀረበ ክስ
በመሆኑ የከሳሾች አቤቱታ ተቀባይነት የሌለው እና በፍ/ቤቱ በተሰጠ ትዕዛዝ ላይ በቀረበው ውጤት ላይም
መረዳት የሚቻለው ይህንን በመሆኑ የከሳሾች ክስ ውድቅ እንዲደረግልን እየጠየቅን ይህ የቀረበው አስተያየት
በእውነት የቀረበ መሆኑን በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁጥር 92/3/ መሠረት እናረጋግጣለን፡፡

You might also like