You are on page 1of 10

በቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት

የሕግ ጉዳዮች ክርክር ዳይሬክቶሬት


BOLE SUB-CITY ADMINISTIRATION JUSTICE OFFICE
LITIGATION AFFAIRS DIRCTORATE

መ//ቁ--መ/ቁ-147737
ቀን -01/10/2015 ዓ.ም
በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት
ለቦሌ ምድብ 6 ኛ ፍ/ብሄር ችሎት
አዲስ አበባ

ከሳሾች፡- 1 ኛ/ ወ/ሮ ቡርሴ በዩ ደሞ

2 ኛ/ አቶ በቀለ በዩ ደሞ

ተከሳሾች፡- 1 ኛ/ ወ/ሮ እናት ተሰማ ገመቹ

2 ኛ/ ወ/ሮ ደስታ ተሰማ ገመቹ

3 ኛ/ ወ/ሮ አስቴር ተሰማ ገመቹ

4 ኛ/ ወ/ሮ አስናቀች በቀለ

5 ኛ/ ወ/ሮ አሰለፈች ዲባባ

6 ኛ/ አቶ አዲሱ መኮንን

7 ኛ/ አቶ ሃብታሙ ፍቃዱ

8 ኛ/ የቦሌ ክ/ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት

ከሳሾች ሚያዚያ 24 ቀን 2015 ዓ.ም ላቀረቡት ክስ ከ 8 ኛ ተከሳሽ የቀረበ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ እና በአማራጭ
የቀረበ የመከላከያ መልስ ነው፡፡
1. የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ
1.1 ከሳሾች በይዞታው ላይ ክስ ለማቅረብ መብት የሌላቸው ስለመሆኑ፡- ከሳሾች ቦታው በእኛ ይዞታ ስር
ነበር ይበሉ እንጂ ይህ ስለመሆኑ ምንም አይነት አግባብነት ያለው ማስረጃ አላቀረቡም እነደማስረጃ
የቀረቡት የእርሻ መሬት የግብር ደረሰኞችም ቢሆኑ በግብር ደረሰኝ አካራካሪው ይዞታ ላይ ያለን
መብት ለማስረዳት የማይቻል እና ደረሰኞቹ ክርክር ለተነሳበት ይዞታ ስለመገበራቸው የማያመለክቱ
እና በህግ ፊትም የፀና ውጠየት የላቸውም፡፡ ሌላኛው ከሳሾች ወራሾች ነን ብለው ያያያዙት
ማስረጃም የየትኛውን የሟቾች ንብረት እንደወረሱ የማያመለክት እና ሟቾች ያልነበራቸውን መብት
ወራሾች ሊወርሱ ስለማይችሉ እንዲሁም ስልጣን ባለው አካል ክርክር ለተነሳበት ቦታ ባለመብት
ስለመሆናቸው ህጋዊ ማስረጃ ባላቀረቡበት ይህንን ክስ ለመመስረት ስለማይችሉ በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 33/2
መሰረት አለን የሚሉትን መብት እና ጥቅም በተገቢው አላስረዱም ተብሎ በብይን ውድቅ
እንዲደረግልን፡፡
1.2 ከሳሾች 8 ኛ ተከሳሽ ለቀሪዎቹ ተከሳሾች አላግባብ ካርታ ሰርቶ ሰጥቶብኛል ይህ የሰጠው ካርታ
ህገወጥ ነው ተብሎ ውሳኔ እንዲሰጠኝ በሚል የቀረበ ክስ ነው፡፡ ይህ ከሆነ ደግሞ ይህ ጉዳይ ሙሉ
ለሙሉ መቅረብ ያለበት ለፍርድ ቤቶች ሳይሆን ለራሱ ለአስተዳደሩ ቅሬታቸውን ከማቅረብ በቀር
ፍርድ ቤት የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም ሰበርም በተደጋጋሚ አስገዳጅ ፍርድ የሰጠበት ጉዳይ ነው ይህ
እንዳለ ሆኖ ፍርድ ቤቶች ስልጣን አላቸው ቢባል እንኩዋን በአስተዳደር ስነስርአት አዋጅ ቁጥር
1183/2011 መሰረት መሰል አስተዳደራዊ ውሳኔዎችን እና እርምጃዎችን ተገቢ አይደሉም መብቴን
ይጎዳሉ ብሎ ለሚያምን ማንኛውም አካል በቅድሚያ ለሚመለከታቸው አስተዳደራዊ ተቋማት
ቅሬታቸውን አቅርበው ማለትም አስተዳደራዊ መፍትሄን አሟጠው የመጨረሻ ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ
በዚህም ውሳኔ ቅር የሚሰኝ አካል ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አስተዳደራዊ ችሎት ጉዳዩን
ከሚያቀርብ በቀር በቀጥታ መደበኛ ፍርድ ቤት ላይ ክርክር ሊያቀርብ አይችልም፡፡ስለሆነም ከሳሾች
ያቀረቡት ክስ በዚህ አዋጅ የተመላከተውን ስነስርዐት ያልተከተለ እና ጉዳዩን ለማየት ስልጣን ለሌለው
ፍ/ቤት የቀረበ በመሆኑ በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 244/2/ሀ መሰረት መዝገቡ በብይን ውድቅ እንዲደረግልን እና
ለተጉላላንበት በቂ ኪሳራ በቁርጥ ከሳሾች እንዲከፍሉን ተብሎ ውሳኔ እንዲሰጥልን እንጠይቃለን፡፡

2. ፍ/ቤቱ መቃወሚያችንን የሚያልፍበት የህግ አግባብ ካለ በአማራጭ የቀረበ መልስ

2.1 ከሳሾች ክርክር ባስነሳው ይዞታ ላይ አርሶአደር ስለመሆናቸው ባልተረጋገጠበት እንዲሁም በይዞታው
ላይ መብት እንዳላቸው ያረጋግጥልናል ብለው ያቀረቡት የእርሻ መሬት ግብር ደረሰኞችም ቢሆኑ
በግብር ደረሰኝ አካራካሪው ይዞታ ላይ ያለን መብት ለማስረዳት የማይቻል እና ደረሰኞቹ ክርክር
ለተነሳበት ይዞታ ስለመገበራቸው የማያመለክቱ እና በህግ ፊትም የፀና ውጠየት የላቸውም፡፡ ሌላኛው
ከሳሾች ወራሾች ነን ብለው ያያያዙት ማስረጃም የየትኛውን የሟቾች ንብረት እንደወረሱ
የማያመለክት እና ሟቾች ያልነበራቸውን መብት ወራሾች ሊወርሱ ስለማይችሉ እንዲሁም ስልጣን
ባለው አካል ክርክር ለተነሳበት ቦታ ባለመብት ስለመሆናቸው ህጋዊ ማስረጃ ባላቀረቡበት ያከራከረው
ይዞታ ተወስዶብናል በከሳሾች የተጠየቀው የይዞታ ይመለስልኝም ሆነ የካርታ ይምከንልኝ አቤቱታ
ተቀባይነት የሌለው በመሆኑ የከሳሾች አቤቱታ ሙሉ በሙሉ ውድቅ ተደርጎ አላግባብ ተከሰን
ለተጉላላንበት በቂ ኪሳራ በቁርጥ እንዲተኩልን እንጠይቃለን፡፡
2.2 8 ኛ ተከሳሽ ከ 1 ኛ እስከ 5 ኛ ተከሳሾች ካርታ ያላግባብ ሰርቶ ሰጥቶብኛል በሚል የቀረበው ክስ
በተመለከተ ከወረዳው ተጣርቶ በመጣው መሰረት ህግና መመሪያን ተከትለን ለተከሳሾች ካርታ
መስጠታችን በአግባቡ መሆኑ እንዳለ ሆኖ ከሳሾች በይዞታው ላይ መብት እና ጥቅም እንዳላቸው
ባላረጋገጡበት እና በማስረጃ ባላስደገፉበት በአስተዳደር በኩል እልባት ማግኘት ያለበትን ጉዳይ ወደ
ፍርድ ቤት ማምጣታቸው ተገቢነት የሌለው እና የፍድ ቤቱ ስልጣንም ባልሆነበት የቀረበ ክስ በመሆኑ
ከሳሾች በይዞታው ላይ መብት እና ጥቅም እንዳላቸው የሚያሳይ ማስረጃ ባላቀረቡበት የቀረበ ክስ
በመሆኑ እና ተከሳሽ መ/ቤትም ህግና መመሪን በመከተል በሰራቸው እና መብት እንዲፈጠር ማድረጉ
የተሰጠው ተግባር እና ሃላፊነት በመሆኑ እና በማስረጃ ላይ ያልተደገፈ ከእውነት የራቀ ክስ ስለሆነ
የከሳሾች አቤቱታ ውድቅ እንዲደረግልን እንጠይቃለን፡፡
የቀረበው መልስ በእውነት የቀረበ መሆኑን
በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 92/3 መሰረት እናረጋግጣለን፡፡
1. ለተከሰስንበት መልስ ለመስጠት እንዲያመቸን ከ 8 ኛ ተከሳሽ በድጋሜ ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲሰጠን በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 205
በቃለመሃላ ተደግፎ የቀረበ አቤቱታ ነው፡፡

ለተከሰስንበት ክስ በቂ ምላሽ ለመስጠት ማስረጃዎችን ማሰባሰብ ላይ የነበርን ቢሆንም ማስረጃዎቹን ለማግኘት ወረዳ ድረስ በመውረድ
ማጣራት በማስፈለጉ እና በ 8 ኛ ተከሳሽ መ/ቤት የቢሮ ለውጥ በመደረጉ ሰነዶችን በአጭር ጊዜ ፈልጎ ማግኘት ላይ የተቸገርን ሲሆን
ሌላው ዋንኛ ምክንያት መረጃዎችን በኮምፒውተር በሲስተም ፋይል የተደረጉት አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ ቢሮ በመቀየሩ ምክንያት
ወደ ስራ ያልገቡ እና በኮምፒውተር መረጃ ማግኘት ያልቻልን በመሆኑ እና ዋንኛ የማስረጃ ምንጫችንም ዳታ ቤዝ ላይ የተቀመጠው
መረጃ በመሆኑ እንደ ጽ/ቤት ሴስተም ወደ ስራ በቅርቡ ስለሚገባ ይህንን ታሳቢ ተደርጎ ተገቢውን ማስረጃ ለማግኘት የተቸገርን
በመሆኑ በቂ ምላሽ ለመስጠት እና ማስረጃዎችን ለማሰባሰብ ይረዳን ዘንድ መልስ ይዞ ለመቅረብ ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲሰጠን
እንጠይቃለን፡፡

ከላይ ያቀረብነው አቤቱታ በእውነት የቀረበ


ስለመሆኑ በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 92/3 መሰረት እናረጋግጣለን፡፡

በቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት


የሕግ ጉዳዮች ክርክር ዳይሬክቶሬት
BOLE SUB-CITY ADMINISTIRATION JUSTICE OFFICE
LITIGATION AFFAIRS DIRCTORATE

ቁጥር-ቦ/ክ/ከ/ፍ/ጽ/ቤት----------

ቀን -04/09/2015 ዓ.ም

ለቦሌክ/ከተማ መሬት ልማት አስተዳደር ጽ/ቤት

አዲስ አበባ

ከሳሾች፡- 1 ኛ/ ወ/ሮ ቡርሴ በዩ ደሞ

2 ኛ/ አቶ በቀለ በዩ ደሞ

ተከሳሾች፡- 1 ኛ/ ወ/ሮ እናት ተሰማ ገመቹ

2 ኛ/ ወ/ሮ ደስታ ተሰማ ገመቹ


3 ኛ/ ወ/ሮ አስቴር ተሰማ ገመቹ

4 ኛ/ ወ/ሮ አስናቀች በቀለ

5 ኛ/ ወ/ሮ አሰለፈች ዲባባ

6 ኛ/ አቶ አዲሱ መኮንን

7 ኛ/ አቶ ሃብታሙ ፍቃዱ

8 ኛ/ የቦሌ ክ/ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት

ጉዳዩ፡- ማስረጃ እና ማብራሪያ እንድትልኩልን ስለመጠየቅ

በቀን 01/09/15 በደብዳቤ ቁጥር ቦ/ክ/ከ/መ/ል/አስ/ጽ/ቤት 11132/15 ለላካችሁልን ክስ መልስ አዘጋጀተን ለመስጠት ይረዳን ዘንድ
በእናተ በኩል የሚከተሉትን ማስረጃዎች ከማብራሪያ ጋር በ ሶስት ቀን ውስጥ እንድትልኩልን እንጠይቃለን፡፡

1. ክርክር ያስነሳው በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ክልል ውስጥ ልዩ ቦታው ሸማቾች ቀጠና ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኘው
በሰሜን አቶ ፍቃዱ ዱባለ በደቡብ አቶ ባህሩ እና አቶ አባያ ራያ በምስራቅ መንገድ እና በምዕራብ ፅጌ ወ/ሃና እና አቶ ባህሩ
የሚያዋስኑት በግምት 2800 ካ.ሜ ነው በማለት ክስ የቀረበበት ይዞታ
2. ቀድሞ በማን እጅ እንደነበር አሁን በማን እጅ ተይዞ እንደሚገኝ እና የይዞታው ህጋዊ ባለቤት ማን እንደሆነ ይገለፅ
3. ይህ ክርክር የተነሳበት ይዞታ ቀድሞ በከሳሾች እጅ ነበር ወይስ አልነበረም?በከሳሾች እጅ ነበር ከተባለ በምን አግባብ
ከእጃቸው ሊወጣ እንደቻለ ካሳ እና ምትክ ማግኘት አለማግኘታቸው ተብራርቶ ይገለፅ
4. ከሳሾች ክርክር ባስነሳው ይዞታ ላይ አርሶ አደር ስለመሆናቸው ከአርሶአደር ኮሚቴ የተሰጠ ማረጋገጫ አለ ወይስ የለም?
አለ ከተባለ ሰነዱ በማስረጃነት እንዲያያዝልን፡፡
5. ይዞታው ላይ በ 1997 አየር ካርታ ላይ የሚታይ ግንባታ ቤት ወይም አጥር አለ ወይስ የለም ተብራርቶ ይገለፅ
6. ከላይ ከ 1 ኛ እስከ 7 ኛ ለተጠቀሱት ተከሳሾች ለእያንዳንዳቸው በስማቸው ክርክር ባስነሳው ይዞታ ላይ ተሰርቶ
የተሰጣቸው ካርታ ካለ በማስረጃነት እንዲያያዝልን እና በምን አግባብ ካርታው እንደተሰጣቸው ተብራርቶ ይገለፅ
7. በአሁን ሰዓት ቦታው ላይ ግንባታም ሆነ አጥር መኖሩ ወይም ባዶ ቦታ መሆኑ ተጣርቶ ምላሽ ይሰጥበት
8. ባጠቃላይ ተከሳሽ መ/ቤታችሁ አለኝ የሚለውን የሰው እና የሰነድ ማስረጃ እንዲሁም ከነማብራሪያው በሶስት ቀን ውስጥ
አጣርታችሁ እንድትልኩልን እየገለፅን በተጠቀሰው ጊዜ ማስረጃዎቹ ሳይላኩ ቢቀሩ ለሚመጣው ሃላፊነት የስራ ሂደታችን
የማይጠየቅ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

ከሠላምታ ጋር

ግልባጭ
በቦሌ ክ/ከተማ አስተዳደር
 ለፍትህ ጽ/ቤት
 ለሕግ ጉዳዮች ክርክር ዳይሬክቶሬት
በቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት
የሕግ ጉዳዮች ክርክር ዳይሬክቶሬት
BOLE SUB-CITY ADMINISTIRATION JUSTICE OFFICE
LITIGATION AFFAIRS DIRCTORATE

መ/ቁ -145803
ቀን -19/03/2015 ዓ.ም
በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት
ለቦሌ ምድብ 6 ኛ ፍ/ብሄር ችሎት
አዲስ አበባ

ከሳሾች-------1 ኛ/ ባልቻ ጉርሙ


2 ኛ/ ሰቦቃ ገመቹ
3 ኛ/ ማሞ አቦዬ
4 ኛ/ ገነት ክፈለው
5 ኛ/ ዳንኤል በቀለ ሪፖረርት አቀራረፅ
6 ኛ/ ዮሃንስ በቀለ
7 ኛ/ ተዋበች ፈንታ
8 ኛ/ እሜቱ አሰፋ
9 ኛ/ አዲስ አሰፋ
10 ኛ/ ቢኒያም አሰፋ
አድራሻ፡- ቦል ክ/ከተማ ወረዳ 07
ተከሳሾች፡ -------1 ኛ/ ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 07 አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ
2 ኛ/ ሾላ አክሲዮን ማህበር
አድራሻ፡- ቦል ክ/ከተማ ወረዳ 07
ከሳሾች ህዳር 02 ቀን 2015 ዓ.ም ላቀረቡት ክስ ከ 1 ኛ ተከሳሽ የቀረበየመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ እና በአማራጭ የቀረበ
የመከላከያ መልስ ነው፡፡
3. የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ
3.1 በነገሩ ልንከሰስ የማይገባ ስለመሆኑ፡- ከሳሾች አሁን ክርክር ያስነሳውን ይዞታ 1 ኛ ተከሳሽ በ 1997 ዓ.ም ምንም
ከሳና ምትክ ቦታ ሳይሰጠን በጉልበት ከይዞታችን አፈናቅሎናል ይበሉ እንጂ በቀድሞ ስሙ ቦሌ ኮተቤ ቀበሌ ገበሬ
ማህበር ስር ሲተዳደር ለነበረ ይዞታ በጉልበት ከይዞታቸው ያፈናቀላቸው የአሁን 1 ኛ ተከሳሽ ስለመሆኑ
ባልተረጋገጠበት እና ማስረጃ ባልቀረበበት እንዲሁም ቦታውን ማስለቀቅን በተመለከተ የ 1 ኛ ተከሳሽ ስልጣን
እና ሃላፊነት እንዳልሆነ እየታወቀ 1 ኛ ተከሳሽ ክርክር ያስነሳውን የቀድሞ ይዞታችን የነበረውን ምንም ህጋዊ
መብት ለሌለው 2 ኛ ተከሳሽ ከህግና ስርአት ውጪ ካርታ ሳይኖር የወረዳው ግንባታ ፍቃድ ቁጥጥር ጽ/ቤት
ለ 2 ኛ ተከሳሽ በቀን 02/02/2015 ዓ.ም የአጥር እድሳት በሚል ሰበብ የግንባታ ፍቃድ በመስጠቱ 2 ኛ ተከሳሽ
ምንም መብት ሳይኖረው አጥሮ እንዲይዝ አድርጓል በሚል የቀረበው የከሳሾች አቤቱታ በግልፅ የሚያሳየው እና
አምነው የገለፁት ነገር የአጥር ዕድሳት በሚል የግንባታ ፍቃዱን የሰጠው የአሁን 1 ኛ ተከሳሽ ሳይሆን የወረዳው
ግንባታ ፍቃድ እና ቁጥጥር ጽ/ቤት በመሆኑ እንዲሁም ቦታው ለግሪን ኤሪያነት እንዲውል ያደረገው የከተማ
አስተዳደሩ የአካባቢ ጥበቃ እና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን በመሆኑ 1 ኛ ተከሳሽ በጉዳዩ ገብተን ውሳኔ ያልሰጠን
በመሆኑ በጉዳዩ የምንከሰስበት ምክንያት ስለማይኖር በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 244/2/መ መሰረት ጉዳዩ
አይመለከታቸውም ሊከሰሱ አይገባም ተብሎ በብይን እንድንሰናበት እንጠይቃለን፡፡
3.2 ከሳሾች በይዞታው ላይ ክስ ለማቅረብ መብት የሌላቸው ስለመሆኑ፡- ከሳሾች ቦታው በእኛ ይዞታ ስር ነበር ይበሉ
እንጂ ይህ ስለመሆኑ ምንም አይነት አግባብነት ያለው ማስረጃ አላቀረቡም እነደማስረጃ የቀረቡት የእርሻ መሬት
የግብር ደረሰኞችም ቢሆኑ በግብር ደረሰኝ አካራካሪው ይዞታ ላይ ያለን መብት ለማስረዳት የማይቻል እና
ደረሰኞቹ ክርክር ለተነሳበት ይዞታ ስለመገበራቸው የማያመለክቱ እና በህግ ፊትም የፀና ውጠየት የላቸውም፡፡
ሌላኛው ከሳሾች ወራሾች ነን ብለው ያያያዙት ማስረጃም የየትኛውን የሟቾች ንብረት እንደወረሱ
የማያመለክት እና ሟቾች ያልነበራቸውን መብት ወራሾች ሊወርሱ ስለማይችሉ እንዲሁም ስልጣን ባለው አካል

ክርክር ለተነሳበት ቦታ ባለመብት ስለመሆናቸው ህጋዊ ማስረጃ ባላቀረቡበት ይህንን ክስ ለመመስረት


ስለማይችሉ በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 33/2 መሰረት አለን የሚሉትን መብት እና ጥቅም በተገቢው አላስረዱም ተብሎ
በብይን ውድቅ እንዲደረግልን፡፡
3.3 ክሱ በይርጋ የታገደ ስለመሆኑ፡- ንብረት አላግባብ ተወስዶብኛል ወይም ለተወሰደብኝ ንብረት ካሳ ይገባኛል
የሚል አካል መብቱን መጠየቅ ያለበት ንበረቱን ባጣ ወይም ከጁ ከወጣ በሁለት(2) አመት ውስጥ እንደሆነ
በፍ/ብ/ህ/ቁ 2143/1 ላይ ተደንግጓል፡፡ይህ እንኳን ቢታለፍ በማናቸውም የፍታብሄር ጉዳዮች ላይ በፍ/ብ/ህ/ቁ
1845 መሰረት በአስር(10)ዓመት ውስጥ ክስ ካልቀረበ ክስ የማቅረብ መብቱ በይርጋ እንደሚታገድ ተደንግጓል፡፡
ስለሆነም በቀረበው የከሳሽ አቤቱታ ላይ ያከራከረው ይዞታ ተወስዶብናል እንዲሁም በንብረት እና ቤታችን ላይ
ጉዳት ደርሶብናል የሚሉት በ 1997 ዓ.ም ሲሆን ይዞታው የከሳሾች አለመሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ይዞታው
የከሳሾች ነው እንኳን ቢባል የጉዳት ካሳ እና ምትክ ቦታ ይሰጠን ቅሬታ ማቅረብ የነበረባቸው ይዞታው አእጃችን
ወጣ ከሚሉበት ከ 1997 ዓ.ም አንስቶ በሁለት አመት ውስጥ በቂ ምክንያት ካለ ደግሞ ግፋ ቢል በአስር አመት
ውስጥ በመሆኑ እና በዚህ ጊዜ ገደብ ውስጥ ቅሬታ አቅርበው ምላሽ ስለማጣታቸው ምንም አይነት ማስረጃ
ሳያቀርቡ አስራ ስምንት(18) ዓመት በላይ ካለፈ በኋላ ቆይተው ክስ ማቅረባቸው ይርጋ ስለሚያግደው
በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 244/2/ሠ መሰረት መዝገቡ በብይን እንዲዘጋልን፡፡
3.4 ከሳሾች ተገቢውን ዳኝነት ከፍለው ያልቀረቡ ስመሆኑ፡- ከሳሾች ይገባኛል የሚሉት የይዞታ ስፋት 10.137 ካ.ሜ
በላይ እና አላግባብ ለወደመብን እና ለተወሰደብን ንብረት እና ቤት የጉዳት ካሳ 250.000 ብር ተከሳሾች
ሊከፍሉን ይገባል በማለት አቤቱታ ያቀረቡ ቢሆንም ለጠየቁት ዳኝነት ገምተው ያቀረቡት ዋጋ 250.000 ብር
ብቻ ነው ይህ ደግሞ ተቀባይነት የሌለው እና በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የዚህን ያክል ስፋት ያለው ይዞታ
በየትኛውም መስፈርት በከሳሾች የተገለፀውን ያክል አነስተኛ የዋጋ ግምት ሊኖረው የማይችል እና የጉዳት ካሳ
ሊከፈለን ይገባል በማለት ያቀረቡት የብር መጠን እራሱ 250.000 ብር ስለሆነ የአካባቢውን የመሬት ሊዝ ዋጋ
መሰረት ተደርጎ ተገቢው ግምት ከወጣለት በኋላ ተገቢውን ዳኝነት ከፍለው እንዲቀርቡ እንዲታዘዝልን
እንጠይቃለን፡፡
3.5 የ 1 ኛ ተከሳሽ ኃላፊዎች ስልጣናቸውን ያላግባብ በመጠቀም ከህግ ውጪ ያለምንም የካሳ ክፍያ እና ምትክ ቦታ
ከይዞታችን እና ከንብረታችን በማፈናቀል የእርሻ መሬታችን እና ንብረታችንን በመውሰድ አሁን ክስ
ያቀረብንበትን ይዞታ ከእጃችን እንዲወጣ አድርገዋል በሚል የቀረበ ክስ ነው፡፡ ይህ ከሆነ ደግሞ በአስተዳደር
ስነስርአት አዋጅ ቁጥር 1183/2011 መሰረት መሰል አስተዳደራዊ ውሳኔዎችን እና እርምጃዎችን ተገቢ
አይደሉም መብቴን ይጎዳሉ ብሎ ለሚያምን ማንኛውም አካል በቅድሚያ ለሚመለከታቸው አስተዳደራዊ
ተቋማት ቅሬታቸውን አቅርበው ማለትም አስተዳደራዊ መፍትሄን አሟጠው የመጨረሻ ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ
በዚህም ውሳኔ ቅር የሚሰኝ አካል ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አስተዳደራዊ ችሎት ጉዳዩን ከሚያቀርብ በቀር
በቀጥታ መደበኛ ፍርድ ቤት ላይ ክርክር ሊያቀርብ አይችልም፡፡ስለሆነም ከሳሾች ያቀረቡት ክስ በዚህ አዋጅ
የተመላከተውን ስነስርዐት ያልተከተለ እና ጉዳዩን ለማየት ስልጣን ለሌለው ፍ/ቤት የቀረበ በመሆኑ
በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 244/2/ሀ መሰረት መዝገቡ በብይን ውድቅ እንዲደረግልን እና ለተጉላላንበት በቂ ኪሳራ በቁርጥ
ከሳሾች እንዲከፍሉን ተብሎ ውሳኔ እንዲሰጥልን እንጠይቃለን፡፡

4. ፍ/ቤቱ መቃወሚያችንን የሚያልፍበት የህግ አግባብ ካለ በአማራጭ የቀረበ መልስ

4.1 የ 1 ኛ ተከሳሽ ሃላፊዎች ስልጣንን ያላግባብ በመጠቀም ከህግ ውጪ ያለምንም የካሳ ክፍያ እና ምትክ ቦታ
ሳይሰጠን በ 1997 ዓ.ም ከይዞታችን እና ከንብረታችን በማፈናቀል የእርሻ መሬታችን እና ንብረታችንን
በመውሰድ አሁን ክስ ያቀረብንበትን ይዞታ ከእጃችን እንዲወጣ እና ለአረንጓዴ መናፈሻነት አግልግሎት እንዲውል
አድርገዋል በሚል የቀረበው ክስ

ከሳሾች ይዞታውን ካሳ እና ምትክ ሳይሰጠን በጉልበት ከእጃችን እንዲወታ ተደረገብን ይበሉ እንጂ በይዞታው ላይ
መብት እና ጥቅም እንዳላቸው በማስረጃ ባላረጋገጡበት መብት እና ጥቅም አላቸው እንኳን በቀድሞ ስሙ ቦሌ
ኮተቤ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ስር ሲተዳደር ለነበረ ይዞታ በጉልበት ከይዞታቸው ያፈናቀላቸው የአሁን 1 ኛ ተከሳሽ
ስለመሆኑ ባልተረጋገጠበት እና ማስረጃ ባልቀረበበት እንዲሁም ቦታውን ማስለቀቅን በተመለከተ የ 1 ኛ ተከሳሽ
ስልጣን እና ሃላፊነት እንዳልሆነ እየታወቀ እንዲሁም ከሳሾች በክሳቸው ላይ በግልፅ አምነው የገለፁት ነገር
የአጥር ዕድሳት በሚል የግንባታ ፍቃዱን የሰጠው የአሁን 1 ኛ ተከሳሽ ሳይሆን የወረዳው ግንባታ ፍቃድ እና
ቁጥጥር ጽ/ቤት መሆኑን አረጋግጠው የገለፁት በመሆኑ እንዲሁም ቦታው ለግሪን ኤሪያነት እንዲውል ያደረገው
የከተማ አስተዳደሩ የአካባቢ ጥበቃ እና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን በመሆኑ 1 ኛ ተከሳሽ በጉዳዩ ገብተን ውሳኔ
ያልሰጠን በመሆኑ በጉዳዩ የምንከሰስበት ምክንያት ባይኖርም ክሱ ይመለከታችኋል እንኩዋን ቢባል ክርክር
ያስነሳው ይዞታ መሬት ባንክ የገባ የመንግስት ቦታ ሲሆን ለአሁን 2 ኛ ተከሳሽ በጊዜያዊነት ቦታውን እንዲያለማ
ለአረንጓዴ ልማት በሚል በጊዜያዊነት የተላለፈ በመሆኑ ከሳሾች በይዞታው ላይ መብት እና ጥቅም እንዳላቸው
የሚያሳይ ማስረጃ ባላቀረቡበት የቀረበ ክስ በመሆኑ እና ቦታው መሬት ባንክ የገባ የመንግስት ይዞታ በመሆኑ
የከሳሾች አቤቱታ ውድቅ እንዲደረግልን እንጠይቃለን፡፡
4.2 ከሳሾች ነባር አርሶ አደር እና የአርሶ አደር ልጆች መሆናችንን በአርሶ አደር ኮሚቴ አረጋግጠናል ያሉት ተቀባይነት
የሌለው እና በማስረጃም ያልተደገፈ መሆኑ እንዳለ ሆኖ በወረዳው ውስጥ ነባር አርሶ አደር እና የአርሶ አደር
ልጆች ናቸው ቢባል እንኳን ክርክር ባስነሳው ይዞታ ላይ አርሶአደር ስለመሆናቸው ባልተረጋገጠበት እንዲሁም
በይዞታው ላይ መብት እንዳላቸው ያረጋግጥልናል ብለው ያቀረቡት የእርሻ መሬት ግብር ደረሰኞችም ቢሆኑ
በግብር ደረሰኝ አካራካሪው ይዞታ ላይ ያለን መብት ለማስረዳት የማይቻል እና ደረሰኞቹ ክርክር ለተነሳበት ይዞታ
ስለመገበራቸው የማያመለክቱ እና በህግ ፊትም የፀና ውጠየት የላቸውም፡፡ ሌላኛው ከሳሾች ወራሾች ነን ብለው
ያያያዙት ማስረጃም የየትኛውን የሟቾች ንብረት እንደወረሱ የማያመለክት እና ሟቾች ያልነበራቸውን መብት
ወራሾች ሊወርሱ ስለማይችሉ እንዲሁም ስልጣን ባለው አካል ክርክር ለተነሳበት ቦታ ባለመብት ስለመሆናቸው
ህጋዊ ማስረጃ ባላቀረቡበት ያከራከረው ይዞታ ተወስዶብናል እንዲሁም በንብረት እና ቤታችን ላይ ጉዳት
ደርሶብናል የሚሉት በ 1997 ዓ.ም ሲሆን ይዞታው የከሳሾች አለመሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ይዞታው የከሳሾች ነው
እንኳን ቢባል በቦታው ላይ ምንም አይነት ቤትም ሆነ ንብረት ያልነበረ መሆኑ እና በይዞታው ላይ የነበረን ቤት እና
ንብረት ወድሞብናል የሚለው አቤቱታ ከእውነት የራቀ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በይዞታው ልይ ቤት እና ንበረት
ነበር ቢባል እንኳን ለደረሰው ጉዳት የጉዳት ካሳ እና ምትክ ቦታ ይሰጠን ቅሬታ ማቅረብ የነበረባቸው ይዞታው
አእጃችን ወጣ ከሚሉበት ከ 1997 ዓ.ም አንስቶ በሁለት አመት ውስጥ በቂ ምክንያት ካለ ደግሞ ግፋ ቢል በአስር
አመት ውስጥ በመሆኑ እና በዚህ ጊዜ ገደብ ውስጥ ቅሬታ አቅርበው ምላሽ ስለማጣታቸው ምንም አይነት
ማስረጃ ሳያቀርቡ አስራ ስምንት(18) ዓመት በላይ ካለፈ በኋላ ቆይተው ክስ ማቅረባቸው ይርጋ ስለሚያግደው
በከሳሾች የተጠየቀው የይዞታ ይመለስልኝም ሆነ የካሳ ሊሰጠኝ ይገባል አቤቱታ ተቀባይነት የሌለው በመሆኑ
የከሳሾች አቤቱታ ሙሉ በሙሉ ውድቅ ተደርጎ አላግባብ ተከሰን ለተጉላላንበት በቂ ኪሳራ በቁርጥ እንዲተኩልን
እንጠይቃለን፡፡

የቀረበው መልስ በእውነት የቀረበ መሆኑን


በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 92/3 መሰረት እና
በቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት
የሕግ ጉዳዮች ክርክር ዳይሬክቶሬት
BOLE SUB-CITY ADMINISTIRATION JUSTICE OFFICE
LITIGATION AFFAIRS DIRCTORATE

መ/ቁ -145803
ቀን -19/03/2015 ዓ.ም
በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት
ለቦሌ ምድብ 6 ኛ ፍ/ብሄር ችሎት
አዲስ አበባ

ከሳሾች-------1 ኛ/ ባልቻ ጉርሙ


2 ኛ/ ሰቦቃ ገመቹ
3 ኛ/ ማሞ አቦዬ
4 ኛ/ ገነት ክፈለው
5 ኛ/ ዳንኤል በቀለ
6 ኛ/ ዮሃንስ በቀለ
7 ኛ/ ተዋበች ፈንታ
8 ኛ/ እሜቱ አሰፋ
9 ኛ/ አዲስ አሰፋ
10 ኛ/ ቢኒያም አሰፋ
አድራሻ፡- ቦል ክ/ከተማ ወረዳ 07
ተከሳሾች፡ -------1 ኛ/ ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 07 አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ
2 ኛ/ ሾላ አክሲዮን ማህበር
አድራሻ፡- ቦል ክ/ከተማ ወረዳ 07
በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 234 መሰረት የቀረበ የማስረጃ ዝርዝር

የሰነድ ማስረጃ

1. የአካባቢ ጥበቃ እና አረንጓዴ ልማት ኮሚሽን ክርክር የተነሳበት ቦታ ከነይዞታ ካርታው ጭምር በግሪን ኤሪያነት እንዲለማ
ለ 2 ኛ ተከሳሽ በቀን 24/07/2013 ዓ.ም የሰጠበት ደብዳቤ 2 ገፅ ኮፒ ዋናው በጽ/ቤቱ የሚገኝ
2. የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 07 ግንባታ ፍቃድ ቁጥጥር ጽ/ቤት ለ 2 ኛ ተከሳሽ ለግነባታ በሚል ፍቃድ የሰጠበት
01 ገፅ ኮፒ ዋናው በጽ/ቤቱ የሚገኝ
3. ቦሌ ክ/ከተማ መሬት ልማት አስተዳደር ጽ/ቤት ቦታው መሬት ባንክ የገባ እና በጊዜያዊነት ለ 2 ኛ
ተከሳሽ እንዲያለማው በሚል የተሰጠ መሆኑን የገለፀበት 01 ገፅ ኮፒ ዋናው በጽ/ቤቱ የሚገኝ
4. ክርክር ባስነሳው ይዞታ ላይ ካሳ ስለመበላቱ እና ክርክር ያስነሳውን ይዞታ በአርሶአደርነት ይዘው
ሲጠቀሙበት የነበሩ ሰዎች እነማ እንደነበሩ የሚያስረዳልንን ማስረጃ በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 145 መሰረት ከአ.አ
መሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ፍ/ቤቱ በትዕዛዝ እንዲያስቀርብልን፡፡
5. የቦሌ ክ/ከተማ መሬት ልማት እና አስተዳደር ፅ/ቤት ክርክር ያስነሳው ይዞታ በ 1988 እና በ 1997 በተነሳ
አየር ካርታ ቦታው ላይ የተገነባ ቤት መኖር አለመኖሩን በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 145 መሰረት አታርቶ ምላሽ
እንዲሰጥ ፍ/ቤቱ ትዕዛዝ እንዲሰጥልን፡፡

ይህ የቀረበው የማስረጃ ዝርዝር በእውነት የቀረበ መሆኑን


በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁጥር 92/3/ መሠረት አረጋግጣለሁ

በቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት


የሕግ ጉዳዮች ክርክር ዳይሬክቶሬት
BOLE SUB-CITY ADMINISTIRATION JUSTICE OFFICE
LITIGATION AFFAIRS DIRCTORATE

ቁጥር-ቦ/ክ/ከ/ፍ/ጽ/ቤት----------

ቀን -04/09/2015 ዓ.ም

ለቦሌክ/ከተማ መሬት ልማት አስተዳደር ጽ/ቤት

አዲስ አበባ

ከሳሾች፡- 1 ኛ/ ወ/ሮ ቡርሴ በዩ ደሞ

2 ኛ/ አቶ በቀለ በዩ ደሞ

ተከሳሾች፡- 1 ኛ/ ወ/ሮ እናት ተሰማ ገመቹ

2 ኛ/ ወ/ሮ ደስታ ተሰማ ገመቹ

3 ኛ/ ወ/ሮ አስቴር ተሰማ ገመቹ

4 ኛ/ ወ/ሮ አስናቀች በቀለ

5 ኛ/ ወ/ሮ አሰለፈች ዲባባ

6 ኛ/ አቶ አዲሱ መኮንን

7 ኛ/ አቶ ሃብታሙ ፍቃዱ

8 ኛ/ የቦሌ ክ/ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት

ጉዳዩ፡- ማስረጃ እና ማብራሪያ እንድትልኩልን ስለመጠየቅ

በቀን 01/09/15 በደብዳቤ ቁጥር ቦ/ክ/ከ/መ/ል/አስ/ጽ/ቤት 11132/15 ለላካችሁልን ክስ መልስ አዘጋጀተን ለመስጠት ይረዳን ዘንድ
በእናተ በኩል የሚከተሉትን ማስረጃዎች ከማብራሪያ ጋር በ ሶስት ቀን ውስጥ እንድትልኩልን እንጠይቃለን፡፡

9. ክርክር ያስነሳው በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ክልል ውስጥ ልዩ ቦታው ሸማቾች ቀጠና ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኘው
በሰሜን አቶ ፍቃዱ ዱባለ በደቡብ አቶ ባህሩ እና አቶ አባያ ራያ በምስራቅ መንገድ እና በምዕራብ ፅጌ ወ/ሃና እና አቶ ባህሩ
የሚያዋስኑት በግምት 2800 ካ.ሜ ነው በማለት ክስ የቀረበበት ይዞታ
10. ቀድሞ በማን እጅ እንደነበር አሁን በማን እጅ ተይዞ እንደሚገኝ እና የይዞታው ህጋዊ ባለቤት ማን እንደሆነ ይገለፅ
11. ይህ ክርክር የተነሳበት ይዞታ ቀድሞ በከሳሾች እጅ ነበር ወይስ አልነበረም?በከሳሾች እጅ ነበር ከተባለ በምን አግባብ
ከእጃቸው ሊወጣ እንደቻለ ካሳ እና ምትክ ማግኘት አለማግኘታቸው ተብራርቶ ይገለፅ
12. ከሳሾች ክርክር ባስነሳው ይዞታ ላይ አርሶ አደር ስለመሆናቸው ከአርሶአደር ኮሚቴ የተሰጠ ማረጋገጫ አለ ወይስ የለም?
አለ ከተባለ ሰነዱ በማስረጃነት እንዲያያዝልን፡፡
13. ይዞታው ላይ በ 1997 አየር ካርታ ላይ የሚታይ ግንባታ ቤት ወይም አጥር አለ ወይስ የለም ተብራርቶ ይገለፅ
14. ከላይ ከ 1 ኛ እስከ 7 ኛ ለተጠቀሱት ተከሳሾች ለእያንዳንዳቸው በስማቸው ክርክር ባስነሳው ይዞታ ላይ ተሰርቶ
የተሰጣቸው ካርታ ካለ በማስረጃነት እንዲያያዝልን እና በምን አግባብ ካርታው እንደተሰጣቸው ተብራርቶ ይገለፅ
15. በአሁን ሰዓት ቦታው ላይ ግንባታም ሆነ አጥር መኖሩ ወይም ባዶ ቦታ መሆኑ ተጣርቶ ምላሽ ይሰጥበት

16. ባጠቃላይ ተከሳሽ መ/ቤታችሁ አለኝ የሚለውን የሰው እና የሰነድ ማስረጃ እንዲሁም ከነማብራሪያው በሶስት ቀን ውስጥ
አጣርታችሁ እንድትልኩልን እየገለፅን በተጠቀሰው ጊዜ ማስረጃዎቹ ሳይላኩ ቢቀሩ ለሚመጣው ሃላፊነት የስራ ሂደታችን
የማይጠየቅ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

ከሠላምታ ጋር

ግልባጭ
በቦሌ ክ/ከተማ አስተዳደር
 ለፍትህ ጽ/ቤት
 ለሕግ ጉዳዮች ክርክር ዳይሬክቶሬት

You might also like