You are on page 1of 5

በቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት

የሕግ ጉዳዮች ክርክር ዳይሬክቶሬት


BOLE SUB-CITY ADMINISTIRATION JUSTICE OFFICE
LITIGATION AFFAIRS DIRCTORATE

መ/ቁ--156302
ቀን -05/03/2016 ዓ.ም
በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት
ለቦሌ ምድብ 4 ኛ ፍ/ብሄር ችሎት
አዲስ አበባ

ከሳሾች፡- 1 ኛ/ አቶ አሰፋ ማሞ

2 ኛ/ ወ/ሮ ታፈሰች ማሞ

3 ኛ/ አቶ ጌታቸው ማሞ

4 ኛ/ ወ/ሮ እምወድሽ ማሞ

5 ኛ/ ወ/ሮ ብርቱካን ማሞ

6 ኛ/ አቶ መላኩ ማሞ

የሁሉም አድራሻ፡- ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 የቤ.ቁ አዲስ

ተከሳሾች፡- 1 ኛ/ አቶ ነጋሽ ተክሌ ገላና

2 ኛ/ ወ/ሮ ሀሚድ ተማም ጅማ

3 ኛ/ ወ/ሮ መዓዛ አምሳሉ ሞላ

4 ኛ/ ኢንዱራንስ ሪል ስቴት ኃ/የተ/የግ ማህበር

5 ኛ/ የቦሌ ክ/ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት

ከሳሾች ጥቅምት 07 ቀን 2016 ዓ.ም ላቀረቡት ክስ ከ 5 ኛ ተከሳሽ የቀረበ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ እና በአማራጭ
የቀረበ የመከላከያ መልስ ነው፡፡
1. የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ
1.1 ከሳሾች በይዞታው ላይ ክስ ለማቅረብ መብት የሌላቸው ስለመሆኑ፡- ከሳሾች ቦታው በእኛ ይዞታ ስር
ነበር ይበሉ እንጂ ይህ ስለመሆኑ ምንም አይነት አግባብነት ያለው ማስረጃ አላቀረቡም እነደማስረጃ
የቀረቡት የእርሻ መሬት የግብር ደረሰኞችም ቢሆኑ በግብር ደረሰኝ አካራካሪው ይዞታ ላይ ያለን
መብት ለማስረዳት የማይቻል እና ደረሰኞቹ ክርክር ለተነሳበት ይዞታ ስለመገበራቸው የማያመለክቱ
እና በህግ ፊትም የፀና ውጠየት የላቸውም፡፡ ሌላኛው ከሳሾች ወራሾች ነን ብለው ያያያዙት
ማስረጃም የየትኛውን የሟቾች ንብረት እንደወረሱ የማያመለክት እና ሟቾች ያልነበራቸውን መብት
ወራሾች ሊወርሱ ስለማይችሉ እንዲሁም ስልጣን ባለው አካል ክርክር ለተነሳበት ቦታ ባለመብት
ስለመሆናቸው ህጋዊ ማስረጃ ባላቀረቡበት ይህንን ክስ ለመመስረት ስለማይችሉ በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ 33/2
መሰረት አለን የሚሉትን መብት እና ጥቅም በተገቢው አላስረዱም ተብሎ በብይን ውድቅ
እንዲደረግልን፡፡
1.2 ከሳሾች 5 ኛ ተከሳሽ ለቀሪዎቹ ተከሳሾች አላግባብ ካርታ ሰርቶ ሰጥቶብኛል ይህ የሰጠው
ካርታ ህገወጥ ነው ተብሎ ውሳኔ እንዲሰጠኝ በሚል የቀረበ ክስ ነው፡፡ ይህ ከሆነ ደግሞ ይህ
ጉዳይ በመጀመሪያ ደረጃ መቅረብ ያለበት በአስተዳደር ስነስርአት አዋጅ ቁጥር 1183/2011
መሰረት መሰል አስተዳደራዊ ውሳኔዎችን እና እርምጃዎችን ተገቢ አይደሉም መብቴን
ይጎዳሉ ብሎ የሚያምን ማንኛውም አካል በቅድሚያ ለሚመለከታቸው አስተዳደራዊ
ተቋማት ቅሬታቸውን አቅርበው ማለትም አስተዳደራዊ መፍትሄን አሟጠው የመጨረሻ
ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ በዚህም ውሳኔ ቅር የሚሰኝ አካል ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት
አስተዳደራዊ ችሎት ጉዳዩን ከሚያቀርብ በቀር በቀጥታ መደበኛ ፍርድ ቤት ላይ ክርክር
ሊያቀርብ አይችልም፡፡ስለሆነም ከሳሾች ያቀረቡት ክስ በዚህ አዋጅ የተመላከተውን ስነስርዐት
ያልተከተለ እና ጉዳዩን ለማየት ስልጣን ለሌለው ፍ/ቤት የቀረበ በመሆኑ በፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ
244/2/ሀ መሰረት መዝገቡ በብይን ውድቅ እንዲደረግልን እና ለተጉላላንበት በቂ ኪሳራ
በቁርጥ ከሳሾች እንዲከፍሉን ተብሎ ውሳኔ እንዲሰጥልን እንጠይቃለን፡፡

2. ፍ/ቤቱ መቃወሚያችንን የሚያልፍበት የህግ አግባብ ካለ በአማራጭ የቀረበ መልስ

2.1 ከሳሾች ክርክር ባስነሳው ይዞታ ላይ አርሶአደር ስለመሆናቸው ባልተረጋገጠበት እንዲሁም


በይዞታው ላይ መብት እንዳላቸው ያረጋግጥልናል ብለው ያቀረቡት የእርሻ መሬት ግብር
ደረሰኞችም ቢሆኑ በግብር ደረሰኝ አካራካሪው ይዞታ ላይ ያለን መብት ለማስረዳት የማይቻል
እና ደረሰኞቹ ክርክር ለተነሳበት ይዞታ ስለመገበራቸው የማያመለክቱ እና በህግ ፊትም የፀና
ውጠየት የላቸውም፡፡ ሌላኛው ከሳሾች ወራሾች ነን ብለው ያያያዙት ማስረጃም የየትኛውን
የሟቾች ንብረት እንደወረሱ የማያመለክት እና ሟቾች ያልነበራቸውን መብት ወራሾች
ሊወርሱ ስለማይችሉ እንዲሁም ስልጣን ባለው አካል ክርክር ለተነሳበት ቦታ ባለመብት
ስለመሆናቸው ህጋዊ ማስረጃ ባላቀረቡበት ያከራከረው ይዞታ ተወስዶብናል በማለት ከሳሾች
ያቀረቡት አቤቱታ ተቀባይነት የሌለው እና ይዞታው የከሳሾች አይደለም እንጂ ነው እንኳን
ቢባል ከሳሾች ለተወሰደባቸው ይዞታ ምትክ ቦታ እና ቤት ካሳ ያገኙ መሆኑን ፍ/ቤቱ ካያዝነው
የሰነድ ማስረጃ የሚረዳው ሆኖ በከሳሾች የተጠየቀው የይዞታ ይመለስልኝም ሆነ የካርታ
ይምከንልኝ አቤቱታ ተቀባይነት የሌለው በመሆኑ የከሳሾች አቤቱታ ሙሉ በሙሉ ውድቅ
ተደርጎ አላግባብ ተከሰን ለተጉላላንበት በቂ ኪሳራ በቁርጥ እንዲተኩልን እንጠይቃለን፡፡

2.2 5 ኛ ተከሳሽ በካርታ ቁጥር ቦሌ 12/82/9/17/248996/00 በ 1 ኛ ተከሳሽ አቶ ነጋሽ ተክሌ ገላና


ስም እንዲሁም ለሌሎቹ ተከሳሾች በዝውውር እና በሽያጭ ስም በህገወጥ መንገድ ይዞታችን
ላይ ካርታ ሰርቶ ሰጥቶብናል ይበሉ እንጂ ከቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 አስተዳደር ጽ/ቤት
ተረጋግጦ በተላከ ቃለ ጉባኤ አቶ ነጋሽ ተክሌ ገላና አርሶ አደር በመሆናቸው ክርክር በተነሳበት
ቦታ ላይ ካርታ ተሰርቶ የተሰጣቸው እና በሽያጭ ይዞታው ወደ 2 ኛ ተከሳሽ ከዚያም ወደ 3 ኛ
እና 4 ኛ ተከሳሽ የተላለፈ በመሆኑ እና ፍ/ቤቱም ካያያዝነው ማስረጃ የሚረዳው በመሆኑ
ከወረዳው አስተዳደር በአግባቡ ተጣርቶ በመጣው መሰረት ህግና መመሪያን ተከትለን
ለተከሳሾች ካርታ መስጠታችን በአግባቡ መሆኑ እንዳለ ሆኖ ከሳሾች በይዞታው ላይ መብት
እና ጥቅም እንዳላቸው ባላረጋገጡበት እና በማስረጃ ባላስደገፉበት በአስተዳደር በኩል እልባት
ማግኘት ያለበትን ጉዳይ ወደ ፍርድ ቤት ማምጣታቸው ተገቢነት የሌለው እና የፍድ ቤቱ
ስልጣንም ባልሆነበት የቀረበ ክስ በመሆኑ ከሳሾች በይዞታው ላይ መብት እና ጥቅም
እንዳላቸው የሚያሳይ ማስረጃ ባላቀረቡበት የቀረበ ክስ በመሆኑ እና ተከሳሽ መ/ቤትም ህግና
መመሪን በመከተል በሰራቸው እና መብት እንዲፈጠር ማድረጉ የተሰጠው ተግባር እና
ሃላፊነት በመሆኑ እና በማስረጃ ላይ ያልተደገፈ ከእውነት የራቀ ክስ ስለሆነ የከሳሾች አቤቱታ
ውድቅ እንዲደረግልን እንጠይቃለን፡፡
የቀረበው መልስ በእውነት የቀረበ መሆኑን
በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 92/3 መሰረት እናረጋግጣለን፡፡

በቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት


የሕግ ጉዳዮች ክርክር ዳይሬክቶሬት
BOLE SUB-CITY ADMINISTIRATION JUSTICE OFFICE
LITIGATION AFFAIRS DIRCTORATE

መ/ቁ--156302
ቀን -05/03/2016 ዓ.ም
በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት
ለቦሌ ምድብ 4 ኛ ፍ/ብሄር ችሎት
አዲስ አበባ

ከሳሾች፡- 1 ኛ/ አቶ አሰፋ ማሞ ተከሳሾች፡- 1 ኛ/ አቶ ነጋሽ ተክሌ ገላና


2 ኛ/ ወ/ሮ ታፈሰች ማሞ 2 ኛ/ ወ/ሮ ሀሚድ ተማም ጅማ
3 ኛ/ አቶ ጌታቸው ማሞ 3 ኛ/ ወ/ሮ መዓዛ አምሳሉ ሞላ
4 ኛ/ ወ/ሮ እምወድሽ ማሞ 4 ኛ/ ኢንዱራንስ ሪል ስቴት ኃ/የተ/የግ ማህበር

5 ኛ/ ወ/ሮ ብርቱካን ማሞ 5 ኛ/ የቦሌ ክ/ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት

6 ኛ/ አቶ መላኩ ማሞ

በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ 234 መሰረት የቀረበ የማስረጃ ዝርዝር


የሰነድ ማስረጃ
1. ከ 1 ኛ እስከ 4 ኛ ያሉት ተከሳሾች ክርክር ያስነሳው ቦታ ላይ በምን አግባብ መብት እንደተፈጠረላቸው የሚያሳይ
11 ገፅ ኮፒ ዋናው በጽ/ቤቱ የሚገኝ
2. ከሳሾች ምትክ ቦታ እና ቤት ካሳ የወሳዱ መሆኑን የሚያስረዳልን 17 ገፅ ኮፒ ዋናው በጽ/ቤቱ
የሚገኝ
የሰው ማስረጃ
1. ትዕግስት ተስፋዬ
2. አብይ ጌታቸው

ይህ የቀረበው የማስረጃ ዝርዝር በእውነት የቀረበ መሆኑን


በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁጥር 92/3/ መሠረት አረጋግጣለሁ

You might also like