You are on page 1of 1

የመ/ቁጥር ......

ቀን፦ 14/06/2016.ዓ.ም

በሀዋሳ ከተማ የመ/ደ/ፍ/ቤት

ለመሐልና ሐይቅ ዳር አካባቢ ምድብ ችሎት

ሀዋሳ

ከሳሽ፦ የሐይቅ ዳር መረዳጃ ዕድር

ተከሳሽ፦ አቶ ካቻው ሙኤ

በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁጥር 105 መሠረት በቃለ መሀላ የቀረበ አቤቱታ ነው

በከሳሽና በተከሳሽ መካከል በአለው የአፈፃፀም ክስ ከፍ/ቤቱ ለአፈ/ተከሳሽ መጥሪያ የተላከና መጥሪያውን የአፈ/ከሳሽ
ለማድረስ በአደረኩት ጥረት በቀን. 10/06/2016.ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 የአፈ/ተከሳሽ መጥሪያውን በምስክሮች ፊት
ለመቀበል ፈቃደኛ አልነበረም 2 ኛ/ በቀን 11./06/2016.ዓ.ም ከጠዋቱ 1:00 የተከሳሽ ያለበት ቤት ድረስ በመሄድ
በፖሊስ አባል በሻምበል ተመስገን አማካይነት ለመስጠት በተደረገው ጥረት የአፈ/ተከሳሽ ሆን ብሎ የፍ/ቤቱን መጥሪያ
ላለመቀበል " ከቤት የለም" በማስባል እየሸሸና እየተደበቀ በማስቸገሩ በተጨማሪ የአፈ/ተከሳሽ ለአቅመ ሄዋን የደረሰች
ልጁም መጥሪያውን ላለመቀበል እምቢተኛ ሆናለች በመሆኑም የአፈ/ከሳሽ የፍ/ቤቱን መጥሪያ በዚህ ቃለ መሀላ
ተመላሽ ለማድረግ ችያለሁ።

ስለዚህ ክቡር ፍ/ቤቱ በአፈ/ተከሳሽ ሆን ብሎ መጥሪያ ላለመቀበልና ፍርዱንም ላለመፈፀም እየሸሸ በመሆኑ የተከበረው
ፍ/ቤት በህጉ መሠረት ትዕዛዝ እንዲሰጥልኝ አመለክታለሁደ

አቤቱታው እውነት ነው

-የአፈ/ተከሳሽ የፍ/ቤቱን መጥሪያ አልቀበልም ስለማለቱ

የሚያውቁ ም/ሮች፦ 1 ኛ/አቶ ሰለሞን አበጋዝ

2 ኛ/አቶ ግርማ ማሞ

3 ኛ/ ሻምበል ተመስገን

You might also like