You are on page 1of 2

ፋ/መ/ቁ/91869

ታህሳስ 3 ቀን 2015 ዓ/ም

በፌዴራል የመጀመሪ ደረጃ ፍ/ቤት

የካ ምድብ አፈጻጸም ችሎት

አዲስ አበባ

የፍርድ በለመብት፡-ወ/ሮ ብርቅነሽ አበበ

አድራሻ፡-አዲስ አበባ የካ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ቁጥር አዲስ

የፍርድ በለመብት፡-አቶ ባህሩ ተሰማ

አድራሻ፡-አዲስ አበባ የካ ክ/ከተማ ወረዳ 12 የቤት ቁጥር አዲስ

በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ/378 መሰረት የቀረበ አፈጻጸም አቤቱታ ነው፡፡

ሀ.ይህን ፍርድ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት የካ ምድብ 5 ኛ ፍ/ብ/ ችሎት በቀን 19/6/2010 ዓ/ም
የሰጠው ውሳኔ ነው፡፡

ለ.በተሰተው ውሳኔ መሰረት የተፈጸመ ነገር የለም፡፡

ሐ.አፈጻጸሙን የማቀርበው ባለመብት ነኝ፡፡

መ.ይህ ፍ/ቤት የሚሰጠኝን መጥሪያና ማመልከቻ ለበለዕዳ በአድራሻ አደርሳለሁ፡፡

የአፈጻጸም አቤቱታ ዝርዝር ባጭሩ፤

1. የፍርድ በለመብት እና የፍርድ ባለዕዳ በህግ በሰማንያ ተጋብትን ባልና ሚስትነት አብረን ስንኖር
በለመግባባት ከቤቴ አስወጥቶኝ ነሓሴ ወር 2006 ዓ/ም ለዚሁ ፍ/ቤት የፍቺ አቤቱታ አቅርቤ ፍ/ቤቱ
የፍች ውሳኔ ከሰጠ በኋላ በጋራ ንብረት ላይ አከራክሮ በ 19/6/2010 ዓ/ም ውሳኔ ሰጥቷል፡፡በውሳኔ
መሰረት አልተፈጸመም፡፡
2. የጋራ መኖሪያ ቤት ግምት ፍ/ቤቱ በወሰነልኝ መሰረት የፍርድ በለዕዳ አልፈጸመልኝም፡፡
3. በዝርዝር ተመዝግቦ ቀበሌ የተቀመጠው ንበረት እንደ ውሳኔ አልተፈጸመልኝም፡፡
4. በቤት ውስጥ በጋራ ያፈራን ንብረት ፍ/ቤት በማስረጃ አረጋግጦ የወሰነልኝን ልዩ ልዩ ንብረቶች በወቅቱ
ዋጋ ግምት አልፈጸመልኝም፡፡
ስለዚህ በለዕዳ በመጥሪያ ቀርቦ በመ/ቁ. 91869 ቀን 2010 የፍ/ቤቱ ውሳኔ ያረፈበት መሰረት
የቤቱን ግምት ጥሬ ገንዘብ ከተወሰነ ጊዜ ጀምሮ የባንክ ወለድ ጭምር እና የቤት ውስጥ ቁሳቁስ
ከተወሰነበት ጊዜ ጀምሮ የፍርድ በለዕዳ ሲገለገልበት የቆየ በመሆኑ ግምቱን በ 2015 ዓ/ም የገበያ ዋጋ
ግምት መሰረት ተሰልቶ ድርሻዬን እንዲከፍል እንዲታዘዝልኝ ስጠይቅ የቀረበው የአፈጻጸም
ማመልከቻ እውነት መሆኑን በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ/ 92 መሰረት አረጋግጣለሁ፡፡

አመልካች፤ ብርቅነሽ አበበ

You might also like