Professional Documents
Culture Documents
በ ሸዋነሰሽ እምየው ዶዮ
ፍቼ ሰላሌ
i
የስዕል ማውጫ
ስዕል 1 :ፆታ ስርጭት ................................................................................................ 14
ስዕል 2፡የአብዲሳ ኣጋ የ 2011 ዓ.ም 8ኛ ክፍል ተማሪዎች የአማርኛ ክፍለ ጊዜ ተሳትፎ
................................................................................................................................. 24
ii
ዋና ማውጫ
ገፅ
የሠንጠረዥ ማውጫ ...................................................................................................... i
የስዕል ማውጫ ............................................................................................................. ii
ዋና ማውጫ ................................................................................................................. iii
አጠቃሎ ....................................................................................................................... v
ምስጋና........................................................................................................................ vi
ምዕራፍ አንድ ............................................................................................................... 1
1. መግቢያ ................................................................................................................... 1
1.1 የጥናቱ ዳራ ........................................................................................................ 1
1.2. ሰበበ ጥናት........................................................................................................ 3
1.3 የጥናቱ ዓላማ ..................................................................................................... 3
1.4 የጥናቱ ጠቀሜታ ................................................................................................ 3
1.5 የጥናቱ ወሰን...................................................................................................... 4
1.6 ያጋጥሙ ችግሮች እና የተወሰዱ መፍትሔዎች .................................................... 4
ምዕራፍ ሁለት.............................................................................................................. 5
2. ክለሳ ድርሳናት ......................................................................................................... 5
2.1 ጊዜ ንድፈ ሀሳባዊ ቅኝት ..................................................................................... 5
2.1.1. ለመማሪያ ክፍል ውስጥ የስርዓት መጓደል ምክንያቶች ................................... 6
2.1.2 በመማሪያ ክፍል ውስጥ ለሚከሰቱ ችግሮች መንስኤያቸውን መፈለግ ............... 8
2.1.3. በመማሪያ ክፍል ውስጥ የሚከሰቱ ችግሮቸን መቆጣጠር ................................ 9
2.1.4. በመማሪያ ክፍል ውስጥ ለሚከሰቱ ችግሮች የሚወሰዱ እርምጃዎች ................ 9
2.2. የተዛማጅ ፅሁፎች ቅኝት .................................................................................. 10
ምዕራፍ ሦስት ............................................................................................................ 12
3 የጥናቱ ዘዴ እና አካሄድ .......................................................................................... 12
3.1 ትምህርት ቤቱ ናሙና አወሳሰድ ........................................................................ 12
3.1.1 የክፍል ደረጃ ናሙና አወሳሰድ..................................................................... 12
3.1.2. የተማሪዎ እና መምህራን ናሙና አወሳሰድ ................................................. 12
3.2 የመረጃ መሰብሰቢያ መረጣ ................................................................................ 13
3.2.1 ምልከታ ..................................................................................................... 13
3.2.2 የፅሁፍ መጠይቅ ........................................................................................ 13
3.2.3 ቃለ መጠይቅ ............................................................................................. 13
iii
3.3የመረጃ አተናተን ................................................................................................ 13
ምዕራፍ አራት ............................................................................................................ 14
4 መረጃ ትንተና ...................................................................................................... 14
4.1 ከተማሪዎች በፅሁፍ መጠይቅ የተገኘ መረጃ ትንተና ........................................... 14
4.2 ከመምህራን በቃለ መጠይቅ የተገኙ መረጃዎች ትንተና .................................... 22
ምዕራፍ አምስት ......................................................................................................... 25
5. ማጠቃለያ እና የመፍትሄ ሃሳቦች ............................................................................ 25
5.1. ማጠቃለያ ........................................................................................................ 25
5.2 የመፍትሔ ሀሳቦች ............................................................................................ 27
6.ዋቢ መጽሐፍት ....................................................................................................... 28
አባሪ አንድ ................................................................................................................. 29
አባሪ ሁለት ................................................................................................................ 31
ደብዳቤዎች ................................................................................................................. 34
iv
አጠቃሎ
ይህ ጥናት በአብዲሳ ኣጋ አንደኛ እና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ስምንተኛ
ክፍሎች የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት የክፍል ውስጥ አመራር ሁኔታ ትንተና በሚል ርአስ
የተሰራ ነው።በመሆኑም አብይ አላማ አድርጎ የያዝው በትምህርት ቤቱ ስምንተኛ ክፍሎቸ
ያለውን የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት አቀራረብ ሁኔታን መተንተን እና ለቸግሮቹም ማቃለያ
ይሆኑ ዘንድ የመፍትሄ ሃሳቦችን ይዟል።
v
ምስጋና
ይህ ሁሉ ሊሆን የቻለው በእግዚአብሔር ፍቃድ ነውና አመሰግነዋለሁ።
በመጀመሪያ ተስፋ ቆርጠን ሳለ ይህንን የትምህርት እድል ላመቻቸልን ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
የአማርኛ ቋንቋ፣ ስነፅሁፍና ፎክሎር ትምህርት ክፍል ምስጋናይዬ ከፍ ያለ ነው። ሲቀጥል
የዚህ ስራ ውጤት ከጅማሬው እስከ ፍጻሜው እንዲሳካ ከፍተኛ እገዛ ላደረጉልኝ ለዶ/ር ታደሰ
ሰንቤቦ ምስጋናዬ ላቅ ያለ ነው። እንደዚሁም ጽሁፉን በማረም ለረዳችኝ ልጄ ለዶ/ር ነፃነት
አያሌው፣ፅሁፉን በመጻፍ ለተባበረችኝ ለወ/ሮ ስናፍቅሽ ደቀቦ ፣ ለውድ ባለቤቴ አያሌው አበበ፣
ለልጆቼ ቶማስ አያሌው፣አሸናፊ አያሌው፣ሄኖክ አያሌው እና ናኦል አያሌው ለሰጣችሁኝ
ሞራል ና ድጋፍ ፈጣሪ በጤና እና በፍቀር ያኑርልኝ። እንደዚሁም ትብብራችሁ ላልተለየኝ
የአብዲሳ ኣጋ አንደኛ እና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን እና የ 2011
ዓ.ም ስምንተኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ እግዚአብሔር ይስጥልኝ።
vi
ምዕራፍ አንድ
1. መግቢያ
1.1 የጥናቱ ዳራ
የክፍል ወስጥ አመራር ማለት መምህሩ በመማር ማስተማር ተግባር ጊዜ በመማሪያ ክፍል
ያሉትን ሁኔታዎች በአጠቃላይ የሚዳስሱ የመምህሩ ሚናዎች ናቸው:: በጥሩ የክፍል አመራር
ችሎት ያልታጀበ የማስተማር ተግባር የትምህርቱን ዓላማ ከግብ ለማድረስ አያስችልም፡፡
በመሆኑም ለትምህርቱ ስኬታማነት ከትምህርቱ በቂ እውቀት በተጨማሪ መምህሩ ጥሩ
የክፍል አመራር ችሎት ሊኖረው ይገባል፡፡ በክፍል አመራር ዙሪያ የተለያዩ ሙሁራን የተለያዩ
ብያኔዎች ሰጥተዋል፡፡ ከተሰጡት ብያኔዎች ውስጥ የሚከተሉት ይገኙበታል፡፡
እማርጀት (2003 151) አርቪን ኤስ ኪንግን በመጥቀስ እንደ ገለፀው “የክፍል ውስጥ አመራር
ዋንኛ አላማው ህግና ስርዓትን አቀናጅቶ በመያዝ እና በመተግበር እንከኖችን ለመከላከል እና
ለመቅረፍ የመማር ማስተማር ሂደቱን ማጠናከር ነው። እንደ እማርጀት ገለፃ የክፍል አመራር
እንደ ዋና አላማ አድርጎ ሊይዝ የሚገባው ጉዳይ የትምህርቱን አላማ ከግብ ማድረስ ነው።
“የክፍል አመራር ለመማር ሂደቱ አመቺ ሁኔታዎችን የመፍጠር ተግባር እንጂ ማስተማር
ልንለው አንችልም።” ክለርክ ድየል (2003: 111) እንደ ክለርክ ገለፃ ማስተማር ያለ ጥሩ
የክፍል አመራር ችሎታ ተግባራዊ ሊሆነ አለመቻሉን ያሳያል።
በአጠቃላይ በክፍል አመራር ዙሪያ ብዙ የተባለ ቢሆንም ያሲን አህመድን በመጥቀስ ሰይድ
እንዲሪሰ (1998፤ 1) ያለውን ሁሉንም ለማካተት ይሞክራል፡፡ የክፍል አመራር ለመማር
ማስተማር ሂደቱ ጥሩ ሁኔታን የመፍጠርና የመጠበቅ ጉዳይ ነው፡፡ ከብያኔው ለመረዳት
እንደሚቻለው የክፍል ውስጥ አመራር ማለት ለመማር ማስተማር ሂደቱ አመቺ ሁኔታዎችን
መፍጠር እና በመሀል የሚከሰቱ ችግሮች ካሉም እንዳይከሰቱ መቆጣጠርን እና ከተከሰተም
የመከላከል ሁኔታዎች ሁሉ የሚያካትት ተግባር ነው።
1
ለመማሪያ ክፍል ውስጥ ስርዓት መጓደል መንስኤ ሊሆኑ የሚችሉ በርካታ ምክንያቶች
ይጠቀሳሉ፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው፡፡
ሰይድ (1998፣7) ያሲን አህመድን በመጥቀስ እንደገለፀው በአንድ የመማሪያ ክፍል ውስጥ
የተማሪዎች ቁጥር መብዛት በመማሪያ ክፍሉ ስርዓት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ከሚያሳድሩ
ምክንያቶች ውስጥ አንዱ ነው፡፡
በአጠቃላይ የክፍል ውስጥ ስርዓት መጓደል በተለያዩ መንስኤዎች ሊከሰት መቻሉን ከላይ
ለአብነት በተጠቀሱት መንስኤዎች መረዳት ይቻላል። በመሆኑም አንድ መምህር መማሪያ
ክፍል ከመግባቱ በፊትም ሆነ ከገባ በኋላ የሚፈጽማቸው ማንኛውም ተግባራት እጅግ ጥንቃቄ
ብተሞላበት እና አላማውን መሰረት ያደረጉ መሆን ይኖርባቸዋል።
ስለ ክፍል ውስጥ አመራር ሁኔታ እና ለክፍል ውስጥ ስርዓት መጓደል መንስኤዎች ከላይ
ለመጥቀስ እንደተሞከረው ሆኖ ስለ አጥኝው በተግባር ልምምድ በአብዲሳ ኣጋ አንደኛ እና
መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በሄደበት ወቅት ያስተዋላቸው ትግባራት ከአማርኛ
ቋንቋ ትምህርት አንጻር ሲታይ አንዳንድ ችግሮችን በትምህርቱ ላይ የሚያሳድሩ መሆናችውን
ማስተዋል ተችሏል። በመሆኑም ይህ ጥናታዊ ጽሁፍ በአብዲሳ ኣጋ አንደኛ እና መለስተኛ
ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ስምንተኛ ክፍሎች የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት የክፍል ውስጥ
አመራር ሁኔታ ለመተንተን የተዘጋጀ ነው::
2
1.2. ሰበበ ጥናት
አንድ የቋንቋ መምህር ካለው በቂ የቋንቋ እውቀት በተጓዳኝ ጥሩ የክፍል ውስጥ አመራር
ችሎታ ከሌለው የመማር ማስተማሩ ስራ የተሟላ ሊሆን አይችልም፡፡ በመሆኑም አጥኚው
በተግባር ልምምድ በሄደበት ትምህርት ቤት ያስተዋላቸው አንዳንድ ችግሮች መንስኤዎቻቸው
ምን እንደሆነ ለማወቅ እና ከምን እንደሆነ ለመረዳት ሲል የጥናትና ምረምር ፅሁፉን በነዚህ
ርእስ ጉዳይ ላይ እንዲሰራ ካነሳሱት ምክንያቶች ውስጥ ተጠቃሽ ናችው፡፡
ናቸው፡፡
3
1.5 የጥናቱ ወሰን
አጥኚው ጥናቱን ለማድረግ የመረጠው ቦታ በአብዲሳ ኣጋ አንደኛ እና መለስተኛ ሁለተኛ
ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ ነው። በዚህም ትምህርት ቤት ወስጥ ካጋጠሙት ችግሮች ውስጥ
ከወጪ፣ ከጊዜ፣ ከሰው ኃይል እና ከጉዳዩ አንገብጋቢነት አንፃር በማየት በትምህርት ቤቱ
በስምንተኛ ክፍሎች የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት የክፍል ወስጥ አመራር ሁኔታ ትንተናን
መርጧል፡፡
የተወሰዱ መፍትሔዎች
4
ምዕራፍ ሁለት
2. ክለሳ ድርሳናት
2.1 ጊዜ ንድፈ ሀሳባዊ ቅኝት
የአመራርነት እውቀት የማያስፈልግበት የስራ መስክ እንደሌላ ብዙ ጊዜ በባለሙያዎች
ይነገራል፤ ይፃፋልም፡፡ አመራርነት በህዝባዊና መንግስታዊ አምራች ወይም አገልግሎት ሰጪ
ድርጅቶች ሁሉ አስፈላጊነቱ የታመነበት ነው። እንዲሁም በአንዳንድ የስራ መስኮች የስራ
መዳከምና አክሳሪነት ካስከተሉ ምክንያቶች አንዱ የአመራርነት ድክመት እንደሆነ በየጊዜው
ይሰማል፡፡ በዚህ ዋናው መፍትሄ ደግሞ ሙያው በየደረጃው እንዲሰርጽ ማድረግ ነው፡
የክፍል ውስጥ አመራር ከአመራር አይነቶች አንዱ ነው፡፡ መምህራን የመማር ማስተማር
ተግባርን ከግብ ለማድረስ ወይም ወጤታማ ለማድረግ አላማን ወስነው ለትምሀርቱ
የሚያስፈልጉትን ማቴሪያል በመማር ማስተማር ተግባር በቅልጥፍና እና በጥራት ወደ
ሚፈለገው ግብ የማድረስ ሂደት ነው፡፡
“የክፍል ውስጥ አመራር ዋንኛ አላማው ህግና ስርዓትን አቀናጅቶ በመያዝ እና በመተግበር
አና እንዲሁም እንከኖችን በመከላከል እና በመቅረፍ የመማር ማስተማር ሂደቱን ማጠናከር
ነው።” አማርጀት (2003፡ 151)፡፡ ከዚህ ብያኔ ለመረዳታ እንደሚቻለው የክፍል ውስጥ
አመራርነት የመማር ማስተማር ሂደቱን ወጤታማ ለማድረግ ሲባል የመማሪያ ክፍል ህግና
ደንቦችን በአግባቡ መጠቀም ወይም እንዲተገበሩ ማድረግ የሚለውን ሀሳብ ያስጨብጣል፡፡
5
ክፍል ውስጥ አመራር ትምህርቱን የሚያነቃቃ ድባብ ልመፍጠር የመምህሩ ጊዜን ቦታን
ቁሳቁሶችን የተማሪውን ሚና እና ባህሪ በህብር የመምራት ቸሎታ ነው።(ቱባ አንሲ ድህረገጽ)
እነደ ቱባ ገለፃ የክፍል አመራርነት በመማሪያ ክፍል ውስጥ የሚገኙትን ተግባራት በአጠቃላይ
ለትምህርቱ ምቹ ሁኔታ እንዲፈጥሩ አድርጎ የመምራት ሂደት ነው፡፡
በአጠቃላይ በክፍል አመራር ዙሪያ ብዙ የተባለ ቢሆንም የሲንግ (1995፣ 181) ራይነት እና
ሀርመርን በመጥቀስ የገለፀወ ሁሉንም ለማካተት ይሞክራል፡፡
ሀ. መምህር
ሊ ተማሪዎች
ሒ ተቋመ /ትምህርት ቤቱ
ሀ. መምህር
ሀርመር እንደሚለው አንድ መምህር ያለው አመለካከት እና ስብዕና በመማሪያ ክፍሉ ወስጥ
አንዳች ፋይዳን ያስገኛል ወይም በከፍሉ ወስጥ የሚፈጠር የስርዓት ጥሰት መሰረት ሊሆን
ይችላል፡፡ በመሆኑም ይላል ሀርመር የሚከተሉትን ተግባራት በፅናት በመከተል
የሚፈጠረውን ችግሮች መቅረፍ ይቻላል፡፡
6
ለ. እቅድ አዘጋጅቶ በእቅድ መመራት፡፡
ለ ተማሪዎች
ሀ. የሰዓቱ፡ ሁኔታ
ተማሪዎች በጠዋት ወይም ከሰአት በኋላ በሚኖረው ሞቃታማ ስዓት ወይም ከአድካሚ የስራ
ቆይታ በኋላ በመማሪያ ክፍል ውስጥ ከተገኙ ለመማሪያ ክፍሉ ስርዓት መጓደል መንስኤ
ይሆናል፡፡
በጉርመስና ወቅት የሰው ልጅ በተለያዩ ነገሮች መታወቅን ይሻል ወይም ሊታወቅበት የሚችሉ
ነገሮችን ይፈልጋል፡፡ ይህ ሁኔታ ተማሪዎችን ከቁጥጥር ውጪ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል::
ሐ. ተቋሙ/ትምህርት ቤቱ
አንድ ተቋም/ትምህርት ቤቱ/ ስነ ስርዓትን በተመለከተ የራሱ የሆነ ፖሊሲ ሊኖረው ይገባል።
ይህ ካልሆነ ግን መምህራኑ ፖሊሲው እንዲዘጋጅ ግፊት ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡
7
አስቸጋሪ /ከባድ/ የሆነ የስነ ስርዓት ጉድለቶች በትምህርት ቤቱ ባለስልጣናት አማካኝነት
ሊገደቡ/ሊታገዱ/ ይችላሉ፡፡
አንዳንድ አስቸጋሪ የሆኑ ባህሪያትን ያማከለ ነው የወጣው ህግ ወይም አንድ እና ከአንድ በላይ
የሆኑ ህጎችን መተግበር አለባቸው፡፡
በራስ የሆነ የመቆጣጠር ስልትን ተጠቅሞ ችግሮች ከተከሰቱ በፍጥነት ለማስወገድ መጣር
ተገቢ ነው፡፡ ይህ ካልሆነ ግን ችግሩ እያደገ ሄዶ ከፍተኛ የሆነ አስቸጋሪ ሁኔታዎችን
ይፈጥራል፡፡
8
ሬ የማስተማር ሂደቱ ለተማሪዎቹ ተስማምቷቸዋል?
በአጠቃላይ ከዚህ በላይ የተጠቀሱትን የኢሎትን ስድስቱን በክፍል ወስጥ ለምከሰቱ ችግሮች
መንስኤ መፈለጊያ መጠይቆች በመጠቀም መምህራን የችግሮችን መንስኤ በቀላሉ ሊያገኙ
ይችላሉ፡፡ ችግሮች ከተገኙ ደግሞ ለችግሮቹ መፍትሄ መፈለጉ እምብዛም ከባድ ሊሆን
አይችልም፡፡
መምህራን በመማር ማስተማር ሂደት ትግበራ ወቅት ችግሮች ከተከሰቱ ለችግሮቹ እልባት
ለማግኘት የማስተማር ሂደቱን በማስቆም ለጥቂት ደቂቃዎች ዝምታ በማስፈን የችግሩን
መፍትሔ አማርጠው ችግሩን ማስቆም/መከላከል / ይችላሉ፡፡
9
መ, የተለያዩ የአሰራር ዘዴዎችን መጠቀም
እንዲህ አይነቱ ችግር ያለባቸወን ተማሪዎች በቅርበት ለማወያየት የችግራቸው መንስኤ ከምን
የመነጨ እንደሆነ በማየትና መፍትሔን በመስጠት ችግሩን መከላከል ይቻላል፡፡
ከዚህ ጥናታዊ ፅኁፍ ጋር ተዛማጅነት ያላቸውን ስራዎች በ1998 በካሊስ ሀሰን እና በሰይድ
እንድሪስ ተሰርተዋል፡፡ ሁለቱንም ስራዎች ከዚህ ጥናታዊ ፅሁፍ ጋር ያላቸው አንድነት እና
ልዩነት ለማሳየት ተሞክሯል፡፡
ካሊስ 1998 ከጅማ ዩኒቨርስቲ ከባዮሎጅ ትምህርት ክፍል በመጀመሪያ ድግሪ የተመረቀ|
ሲሆን። ለመመረቂያ ይሆን ዘንድ ያዘጋጀው ጥናታዊ ፅሁፍም በጅማ ዞን በሰቃ ወረዳ በስቃ
ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤ «በስቃ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በክፍል ወስጥ አመራር
የሚያጋጥሙ ችግሮች» በሚል ርዕስ የቀረበ ነበር፡፡ ጥናቱ በዋናነት በትምህርት ቤቱ ያሉትን
የክፍል አመራር ችግሮች መመርመር እና የችግሮቹን መንስኤ በማወቅ የመፍትሄ ሀሳቦችን
ለመስጠት በአላማነት ሰንቆ የተነሳ ነበር። በመሆኑም ለጥናቱ ከተመረጡት አካላት መረጃዎቸን
በፅሁፍ መጠይቅ አማካኝነት በማስባሰብና የገላጭ የመተንተኛ ዘዴን ተጠቅሞ የችግሮችን
10
መንስኤዎች ተማሪዎች መሆናቸውን እና መምህራንም ተማሪዎች የባህሪ ለውጦችን
እንዲያመጡ ማድረግ እንዳለባቸው አስገንዝቦ ጥናታዊ ፅሁፉን አጠናቋል።
ሰይድ እንድሪስ በ1998 ዓ.ም ለአማርኛ ቋንቋ ስነ ፅሁፍ ትምህርት ክፍል «በቦንጋ በጊንቦና
በሰጦ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በዘጠነኛ እና አስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት
ክፍል አመራር ሁኔታ ትንተና በሚል ርዕስ ጥናታዊ ፅሁፍ አዘጋጅቶ ነበር። የሰይድ ጥናታዊ
ፅሁፍም ከክፍል ውስጥ ስርዓትና ከተማሪዎች የትምህርት ተነሳሽነት ጋር ተዛማጅንት
ያላቸውን ጉዳዮች በማጥናት የመለየት እና የመፍትሄ ሀሳቦችንም የመጠቀም አላማ ያለው
ነው፡፡ ይህንንም ከግብ ለማድረስ ሲል መረጃዎችን በፅሁፍ መጠይቅ እና በምልከታ አማካኝነት
አሰባስቦ በመተንተን ችግሮቸን ለይቶ የመፍትሔ ሀሳቦችን ለመስጠት ሞክሯል፡፡
11
ምዕራፍ ሦስት
3 የጥናቱ ዘዴ እና አካሄድ
አጥኝው ለጥናቱ የመረጠው የምርምር ዘዴ ገላጭ የምርምር ዘዴን ነው። ይህ ዘዴ ክስተቶችን
ባለብት ተፈጥሮአዊ አካባቢ ለመመርመር እና ለችግሮች መፍትሔ ለማፈላለግ የሚያስችል
በመሆኑ ነው አጥኝው ይህንን ዘዴ የመረጠው።
12
3.2 የመረጃ መሰብሰቢያ መረጣ
አጥኚው ለመረጃ መሰብሰቢያነት የተጠቀመው ሶስት ዓይነት የመረጃ ማሰባሰቢያ ዘዴዎችን
ነው፡፡ እነርሱም ምልከታ ፣የዕሁፍ መጠይቅ እና ቃለ መጠይቅ ናቸው፡፡
3.2.1 ምልከታ
አጥኚው ጥናቱን ለማድረግ በመርጣቸው የ8ኛ ክፍሎች ካሉት አጠቃላይ ክፍሎች 30%
በሚሆኑት ወይም 3 ክፍሎች ለሶስት ያህል ጊዜያት በመግባት መደበኛ እና ኢ-መደበኛ በሆኑ
መንገዶች መረጃዎችን በምልከታ አስባሰቧል፡፡ መደበኛውን ምልከታ በሚያደርግበት ጊዜ
የአመራሩ ሁኔታ መሰረት በማድረግ የተዘጋጁ 30 ያህል ጥያቄዎችን በቅድመ ምልከት ቼክ
ሊስት አዘጋጅቶ ሁኔታዎችን እና ተግባራትን እየተከታተለ በሰንጠረኝt የሞላ ሲሆን ኢመደበኛ
ውን ግን ከመምህራኑ ጋር በመግባት ሁኔታዎችን እና ተግባራትን እየተከታተለ ማስታወሻ
የያዘበት ነው፡፡ በአጠቃላይ ይህንን የመረጃ ማሰባሰቢያ ዘዴ ተጠቅሞ መረጃዎችን መሰባሰብ
የተፈለገበት ዋንኛ ምክንያቱ ከፅሁፍ መጠይቅ የሚገኘውን መረጃ ታአማኒነት ለማረጋገጥ
ሲባል ነው።
3.2.3 ቃለ መጠይቅ
ይህ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴ አጥኝው ከተጠቀመባቸው መረጃ ማሰባሰቢያዎች አንዱ ነው፡፡
በዚህም አማካኝነት ውሱን የሆነ ቃለ መጠይቆችን በመጠቀም ከመምህራን መረጃዎች
ተሰብስበዋል። እነዚህ የቃለ መጠይቅ መረጃዎች በመማር ማስተማር ሂደቱ ወቅት ያለውን
ምን እንደሚመስል እና በመማር ማስተማር ሂደቱ የመማር ክፍሎች የተማሪዎች ተሳትፎ
የሚያሳድሩት ተፅዕኖ ካለ እንዲገልፁ የተደረገበት ነው፡፡ በዚህም አማካኝነት መረጃዎችን
በሚፈለገው መልኩ ማግኘት ተችሏል፡፡
3.3የመረጃ አተናተን
በ 3 ዓይነት መንገድ የተሰበሰበትን መረጃዎች አይነታዊ የመረጃ መተንተኛ ዘዴን በመጠቀም
የተገኙ መረጃዎችን እንደ ተመሳሳይነታቸው የመላሾችን ብዛት በሰንጠረኝ በማሳየት
የመላሾችን መጠን እና መልሶቸውን በመተንተን ካለው ውጤት በመነሳት በመረጃዎቹ ላይ
ማጠቃለያ እና የመፍትሔ ሀሳብ ተሰጥተዋል፡፡
13
ምዕራፍ አራት
4 መረጃ ትንተና
በዚህ ምዕራፍ የጥናቱን ዓላማ መሰረት በማድረግ በተለያዩ መንገዶች ወይም ዘዴዎች ከመረጃ
ሰጪዎች የተገኙ መረጃዎች ተተንትነው ይቀርባሉ
48% ወንድ
52% ሴት
14
በላይ የሆናቸው ናቸው፡፡ በአጠቃላይ ለመረጃ ሰጪነት የተሳተፉት ተማሪዎች በአብዛኛው
እድሜያቸው ከ15-18 ባለው እርከን የሚገኙ መሆናቸውን እና በአማካኝ ሁለቱም ጾታዎች |
በእኩል መሳተፋቸውን ነው፡፡
እስማማለሁ 33 46.7
የአማርኛ ቋንቋ መምህርህ/ሽ ጊዜን አልስማማም 37 53.3
በአግባቡ ይጠቀማሉ? የተለየ 0 0
15
ይህ መረጃ እንደሚያሳየው የአማርኛ ቋንቋ መምህሩ ጊዜን በአግባቡ እንደማይጠቀሙ
37(53.3) የሚሆኑት ተማሪዎች ሲገልፁ 33(46.7%) የሚሆኑት ተማሪዎች መምህራኑ ጊዜን
በአግባቡ ይጠቀማሉ በሚለው ሀሳብ ተስማምተዋል፡፡
ሠንጥረዥ 4 መምህራኑ ወደ መማሪያ ክፍል ሲገቡ ያለው ሁኔታ በተመለከተ የቀረበ ጥያቄ
ተ.ቁ ጥያቄ አማራጮች ብዛት በመቶኛ
መምህርህ/ሽ ወደ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶችን ይይዛሉ 8 11.8
ክፍል ሲገቡ ለተማሪዎች ተገቢውን ሰላምታ |ያቀርባሉ 61 87.6
ለትምህርት አሰጣጥ ምቹ ሁኔታዎችን 17 23.6
ለመፍጠር ይጥራሉ
የተለየ 123
16
ሠንጠረዥ 5 በመማሪያ ክፍል ውስጥ የሚቀርበውን ይዘት በተመለከተ የቀረበ መጠይቅ
17
መምህራኑተማሪዎቸን በቡድን ወይም በጥንድ ያሰራሉ/ በሚለው ትያቄ 36(51.8%)
ተማሪዎች በጭራሽ አያሰሩም ሲሉ 26(36.5%) ተማሪዎች ብበከፊል ያሰራሉ ማለታቸውን
እና 8(11.8%) ተማሪዎች መምህራኑ በቡድን እና በጥንድ እንደማያሰሩ ገልፀዋል።
በሌላ በኩል በምልከታ የተገኘው ውጤት እንደሚያሳየው መምህራኑ ፊትለፊት ወንበር አከባቢ
የተቀመጡትን ተማሪዎች የሚመሰርቱትን ቡድን እንጂ ወደ መሀል በመግባት እንደማይቃኙ
የተገኘው መረጃ ይጠቁማሉ፡፡ በአጠቃላይ መምህራኑ በመማር ማስተማር ሂደቱ ጊዜ
በአንፃሩም ቢሆን የተመሰረቱትን በድኖች እየተዘዋወሩ አለመቃኘታቸውን ለመገንዘብ ተችሏል።
ለተማሪዎ ያልገባቸውን ጥያቄ በተገቢ መንገድ ያስረዳሉ? በሚል በቀረበው ጥያቄ የሰንጠረዡ
ውጤት እንደሚያሳየው 30 (42.9%) ተማሪዎች አያስረዱም ሲሉ 26(36.5%) ተማሪዎች
በከፊል ያስረዳሉ የሚል ምልስ የሰጡ ሲሆን የቀሩት 14(20.6%) አዎ ያስረዳሉ የሚል
ምላሽ መስጠታቸውን ነው። በአጠቃላይ ይሀ ውጤት እንደሚያሳየው መምህራኑ ተማሪዎችን
በተገቢ መንገድ የማያስረዱ መሆናቸውን ነው።
ከዚህ በተጨማሪ በምልከታ የተገኘው ውጤት ጥቂት መምህራን በመማር ማስተማር ሂደቱ
ከአንዳንድ ተማሪዎች የሚነሱትን ጥያቄዎች የጎደለው እርምት እንደሚስጡ ማየት ተችሏል።
18
ሠንጠረዥ 8 በመማሪያ ክፍል ውስጥ ለሚከስቱ የስርዓት ችግሮችን ለመከላከል የመምህሩን
ሚና በተመለከተ የቀረቡ ጥያቄዎች
19
የተጠቀሱት ጉዳዮች ለመማር ማስተማር ሂደቱ የተሳካ ይሆን ዘንድ በተገቢ ሁኔታ መፈፀም
ያለባቸው ሆኖ ሳለ መምህራኑ ግን በአግባቡ እየተገበሩዎቸው አይደለም።
እንዲሁም ይህንን መሰረት በማድረግ ለተማሪዎች በአንተ አስተያየት በክፍል ውስጥ የስርዓት
ችግር ለሚፈጥሩ ተማሪዎች እንዴት ከዚያ ተግባራቸው መከላከል ይቻላል ትላለህ/ትያለሽ?
በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ አብዛኞቹ ተማሪዎች ተማሪዎችን ምክር በመምከር ከጥፋታቸው
እንዲታረመ ማድረግ ይቻላል የሚል ሀሳብ የሰጡ ሲሆን እንዲሁም በአንፃሩ
20
ሠንጠረዥ 9 የተማሪዎች ተሳትፎ በተመለከተ የቀረበ ጥያቄ
21
አንደምንረዳው ለተማሪዎች ተሳትፎ ማነስ የተለያዩ ምክንያቶች ቢኖሩም እንኳ በይበልጥ
የመምህራኑ ተማሪዎችን አለማነሳሳት እና በትደጋጋሚ ክትትል እና ቁጥጥር አለማድረጋቸው
ዋንኛ ምክንያት እንሆነ ያሳያል።
አሉታዊ 0 0
22
ሰንጠረዡ እንደሚያመለክተው ለመረጃ ሰጪነት የተመረጡት መምህራን በሙሉ ለስራቸው
አዎንታዊ ፍቅር ያላቸው ናቸው፡፡
በጥያቄ ቁጥር 1 የቀረበው ሀሳብ መሰረት በማድረግ መማሪያ ክፍሎቹ ያለባቸውን ችግሮቹ
ሲገልጽ የመቀመጫ ወንበሮቹ ሁኔታ፤ የከፍሉ ጥበት፣ በመማሪያ ክፍሎች በቂ የሆነ ብርሃን
አለመኖሩ፣ በተለይ ከሰዓት በኋላ በከፍተኛ ሁኔታ ሙቀት ያለው መሆኑ እና ወለሎቹ ምቹ
በሆነ ሁኔታ የተገነቡ አለመሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡
በዚህ ሰንጠረዝ ወስጥ ሌላው መልስ የተሰጠበት ጥያቄ የተማሪዎች ቁጥር በመማር ማስተማር
ሂደቱ ላይ የአመራር ተፅዕኖ አሳድሯል በሚል የተጠየቀው ነው:: ለዚህም ጥያቄ መልስ አዎ
አሳድሯል በሚለው መልስ የሚስማሙ መሆኑን ምርጃው ይጠቁማል።
23
ሠንጠረዥ 13 የተማሪዎች ተሳትፎን በተመለከተ ለቀረበ ጥያቄ የተሰጠ ምላሾች
በአጠቃላይ በዚህ ምዕራፍ ከመረጃ ምንጮች የተገኙትን መረጃዎች ከላይ በተመለከተው መልኩ
ተተንትነው ቀርበዋል፡፡ ስለሆነም በሚቀጥለው ምዕራፍ የጥናቱን አጠቃላይ ውጤት ምን
እንደሚመስል የሚገለፅበትና ለታዩት ችግሮቹም የመፍትሔ ሀሳብ የሚሰጥበት ይሆናል፡፡
አያደርጉም 66.7
በከፊል 33.3
አዎ 0
0 10 20 30 40 50 60 70 80
24
ምዕራፍ አምስት
ለዚህ ጥናት እንደ መረጃ ምንጭነት የተወሰዱት የትምህርት ቤቱ ስምንተኛ ክፍል የአማርኛ
ቋንቋ መምህራኖች እና ስምንተኛ ክፍል ተማሪዎች ናቸው:: መምህራኑ በቁጥራቸው ትንሽ
በመሆናቸው እንዳለ የተወሰዱ ሲሆን ተማሪዎችን ግን ሙሉ በሙሉ ማካለል ስለማይቻል
ለናሙናነት ጥቂት ተማሪዎች ተወስደዋል።
ተችሏል።
25
ምመህራኑ ለስራቸው ፍቅር እንዳላቸው የገለፁ ቢሆንም በመማር ማስተማር ሂደቱ ግን ይህን
ሊያሳይ የሚችል ሁኔታዎችን ሲፈፅሙ ማስተዋል አልተቻለም፡፡ ይህም ማለት በጊዜ ወደ
መማሪያ ክፍል አለመገኘት ለቋንቋ ትምህርት ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር የማይጥሩ
በአጠቃላይ በዚህ ትምህርት ቤት ውስጥ ያለውን የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት የክፍል ውስጥ
አመራር ሁኔታ ሲፈተሽ ችግሮች እንዳሉበት ለማየት ተችሏል፡፡
26
5.2 የመፍትሔ ሀሳቦች
ምዕራፍ አራት የተተነተኑትን መረጃዎች መሠረት በማድረግ በዚህ ምዕራፍ መጀመሪያ ላይ
የማጠቃለያ ሀሳብ ለመስጠት ተሞክሯል። በመሆኑም በተሰጠው የማጠቃለያ ሀሳብ ውስጥ
ያሉትን ችግሮች መሰረት በማድረግ አጥኚው የሚከተሉትን የመፍትሔ ሀሳቦች ይሰነዝራል።
27
6.ዋቢ መጽሐፍት
Atklins J. (1995). Skills Development Methdology part 2 Addis Ababa: Adiss
School. (Unpublished)
ሰይድ እንድሪስ፡፡ (1998)። በጊንቦ ቦስጦና በቦንጋ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በዘጠነኛ እና
ንጉሴ ሀብተየስና ብርሀኑ ብርቄ፡፡ (1991)፡፡ የስራ አመራር እና አስተዳደረር መርሆች ተግባሮች
እና ዘዴዎች፡፡ አዲስ አበባ፡ ሜጋ አሳታሚ ድርጅት፡፡
28
አባሪ አንድ
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሂዩማኒቲስ፣ የቋንቋዎች ጥናት፣ የጋዜጠኝነትና ኮሚዩኒኬሽን ኮሌጅ
የአማርኛ ቋንቋ፣ ስነፅሁፍና ፎክሎር ክፍለ ትምህርት
የዚህ መጠይቅ አላማ በአበዲሳ ኣጋ አነደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ8ኛ ክፍሎች የአማርኛ
ቋንቋ ትምህርት አተገባበር ሁኔታን ለመተንተን የተዘጋጀ ጥናታዊ ፅሁፍ መረጃን ለመሰብሰብ
ነው።
1. ፆታ ወ ____ ሴ _____
ሀ. 0-5 ዓመት
ሊ 6-10 ዓመት
ሀ. አዎንታዊ___ ሊ አሉታዊ___
ሀ. አዎ ናቸው_______ ለ. አይደሉም________
_________________________________________________________________
_________________________________________________________________
_________________________________________________________________
_________________________________________________________________
_________________________________________________________________
__________________________________________።
29
_________________________________________________________________
_________________________________________________________________
_______________________________________________________።
_________________________________________________________________
____________________________________________።
_________________________________________________________________
____________________________________________።
11. የተማሪዎቹ ቁጥር በትምህርቱ ክፍለ ጊዜው አመራር ላይ ተፅዕኖ ያሳድሯል ይላሉ?
_________________________________________________________________
_________________________________________________________________
____________________________________።
30
አባሪ ሁለት
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሂዩማኒቲስ፣ የቋንቋዎች ጥናት፣ የጋዜጠኝነትና ኮሚዩኒኬሽን ኮሌጅ
የአማርኛ ቋንቋ፣ ስነፅሁፍና ፎክሎር ክፍለ ትምህርት
1. ፆታ ወ________ ሴ___________
መ. የተለየ__________________________
31
5. መምህርሽ/ህ ተማሪዎችን በጥንድ እና በቡድን ያስራሉ?
ሀ. አዎ ነው _____ለ.በከፊል ነው______ሐ.አይደለም________
8. መምህርሽ/ህ
መ. የተለየ________________________________
ሀ. አዎ ይጠቀማሉ__________ ሊ. አይጠቀሙም_____________
ማድረግ________________
መ. የተለየ_______________________
32
13.በአንተ /ቺ አስተያየት በክፍል ውስጥ የስርዓት ችግር ለሚፈጥሩ ተማሪዎች እንዴት ከዚህ
_________________________________________________________________
_________________________________________________________________
_________________________________________________________________
_________________________________________________________________
_________________________________________________________________
_________________________________________________________________
_________________________________።
ሰ የተለየ______________________________________
33
ደብዳቤዎች
34