Professional Documents
Culture Documents
በ
ሀብታሙ ዱጉማ
ውበቱ በዛብህ
ገነነ ተስፋዬ
1. መግቢያ
1.1. የጥናቱ አነሳሽ ምክንያት (STATEMENT OF THE
PROBLEM)
ትምህርት ቤቱ አዲስ በመሆኑ በትምህርት ቤቱ አጠቃላይ
ማህበረሰብ ችግር መከሰቱ አይቀሬ ነው፡፡
ከሁሉም ችግሮች ተማሪዎች ላይ የሚደርሱ ችግሮች ስሱ
(sensitive) በመሆናቸው ቅድሚያ ሊሰጣቸው ይገባል፡፡
በተማሪዎች ላይ ካጋጠሙ ችግሮች ውስጥ የት/ቤቱን ማለፊያ
ነጥብ ማምጣት ያልቻሉ ተማሪዎች መኖራቸው አንዱ ነው፡፡
በ2014 ዓ.ም በመጀመሪያው መንፈቀ ዓመት 38 (9.41%)
ተማሪዎች የማለፊያ ነጥብ ማምጣት አልቻሉም፡፡
የቀጠለ…
በክፍል ደረጃ ደግሞ ከ9ኛ ክፍል 21 ተማሪዎች
(17.4%)፣ ከ10ኛ ክፍል 1 ተማሪ (2.3%)፣ ከ11ኛ ክፍል
8 ተማሪዎች (4.42%)፣ ከ12ኛ ክፍል 8 ተማሪዎች
(13.8%) የማለፊያ ነጥቡን ማስመዝገብ አልቻሉም፡፡
እነዚህ ተማሪዎች የማለፊያ ነጥብ እንዳያመጡ
እንቅፋት የሆኑባቸውን ጉዳዮች በመለየት መፍትሔ
ለመስጠት በማሰብ ይህ ጥናት ተከናውኗል፡፡
1.2. የጥናቱ ዓላማዎች (OBJECTIVES OF THE STUDY)
ይህ ጥናት የሚከተሉትን ሁለት ዓላማዎች አሳክቷል፡፡
ተማሪዎቹ የማለፊያ ነጥብ እንዳያመጡ ያደረጓቸውን
ጉዳዮች መለየት፤
በተማሪዎቹ ውጤት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ላሳደሩ ጉዳዮች
መፍትሔ መስጠት፡፡
1.3. የጥናቱ አስፈላጊነት (IMPORTANCE OF THE
STUDY)
ይህ ጥናት በመከናወኑ በዋናነት ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ርእሳነ
መምህራን እና አጥኝዎች ተጠቃሚዎች ናቸው፡፡
ተማሪዎች ችግሮቻቸው እንዲፈቱላቸውና የማለፊያ ነጥቡን
አንዲያስመዘግቡ እድል ይፈጥርላቸዋል፡፡
መምህራን ያሉባቸውን ችግሮች በመለየት ችግሮቹ እንዲቀረፉና
ተማሪዎቻቸውን ውጤታማ እንዲያደርጉ እድል
ይፈጥርላቸዋል፡፡
ርዕሳነ መምህራን ተማሪዎቹ ያጠማቸውን ችግር በመገንዘብ
መፍትሄ እንዲሰጡ አጋጣሚ ይፈጠርላቸዋል፡፡
አጥኝዎች ለሚሰሯቸው ጥናቶች በመነሻ ሀሳብነትና በመረጃ
ምንጭነት ያገለግላቸዋል፡፡
1.4. የጥናቱ ወሰን (SCOPE OF THE STUDY)
ይህ ጥናት ከማጥኛ ስፍራ፣ ከተጠኝዎችና ከጥናቱ ርእሰ ጉዳይ
አንጻር የራሱ ወሰን አለው፡፡
ከማጥኛ ስፍራ አንጻር በእቴጌ መነን የልጃገረዶች አዳሪ 2ኛ ደረጃ
ት/ቤት ላይ የተወሰነ ሲሆን ውጤቱ የሌላ ት/ቤቶችን ውጤት
ላይወክል ይችላል፡፡
ከተጠኚዎች አንጻር በት/ቤቱ በሚገኙ በ2014 የመጀመሪያው
መንፈቀ ዓመት የማለፊያ ነጥብ ያላመጡ ተማሪዎች ላይ ብቻ
የተገደበ ሲሆን ከዚህ ውጭ ያሉት ተማሪዎች በጥናቱ
አልተዳሰሱም፡፡
ከጥናቱ ርዕሰ ጉዳይ አንጻር በተማሪዎቹ ውጤት ላይ እንቅፋት
የሆኑ ጉዳዮች ላይ ብቻ ያተኮረ ጥናት ነው፡፡
1.5. የጥናቱ ውስንነት (LIMITATION OF THE STUDY)
ይህ ጥናት ከጽሑፍ መጠይቅ አሞላልና ከጊዜ እጥረት አንጻር
ውስንነት ነበረበት፡፡
የተወሰኑ ተማሪዎች የጽሑፍ መጠይቁን በሚገባ
ባለመሙላታቸው ከመረጃ ትንተና ውጭ ተደርገዋል፡፡
የጊዜ እጥረት በማጋጠሙ ምክንያት ቃለ መጠይቅን
መጠቀም አልተቻለም፡፡
ሆኖም ግን የቃለ መጠይቅ ጥያቄዎች በጽሑፍ
መጠይቁ ተካትተው ክፍተቱ ተሞልቷል፡፡
2. የአጠናን ዘዴ (RESEARCH METHOD)
2.1. የጥናቱ ንድፍ እና ዘዴ (DESIGN OF THE STUDY)
ይህ ጥናት ከጥናቱ ንድፍ አንጻር መሰረታዊ የጥናት ንድፍን
(basic research design) በመከተል ተከናውኗል፡፡
ይህም የሆነበት ምክንያት ያጋጠሙ ችግሮችን በመቃኘት
የመፍትሄ ሀሳብ ማቅረብ ላይ ያተኮረ ጥናት በመሆኑ ነው፡፡
ከጥናት ዘዴ አንጻር ቅይጥ የጥናት ዘዴን (mixed research
method) ተከትሎ የተከናወነ ሲሆን ይህም የሆነበት
አይነታዊና መጠናዊ መረጃዎች (quantitative and
qualitative data) ስለተሰበሰቡ ነው፡፡
2.2. የናሙናዎች አመራረጥ (Sampling method)