Professional Documents
Culture Documents
ሐይማኖት ጌታቸው
ጥር 2009 ዓ.ም
i
ማውጫ
አርዕስት ገፅ
መግቢያ............................................................................................................................ 1
የስልጠናው ዓላማ ............................................................................................................. 4
ክፍል አንድ ...................................................................................................................... 5
1.የልማታዊ ጋዜጠኝነት ንድፈ ሃሳብና የማህበረሰብ ሚዲያ ................................................... 5
1.1 የማህበረሰብ ሚዲያ ምንድን ነው? ...................................................................................... 6
1.2 ልማታዊ ጋዜጠኝነት ማለት ምን ማለት ነው? .................................................................. 7
ክፍል ሁለት ..................................................................................................................... 9
2.የሬዲዮ ዜናና ፕሮግራም አዘገጃጀት .................................................................................. 9
2.1 ዜና ........................................................................................................................... 9
2.1.1 ዜና ምንድን ነው?............................................................................................................. 9
2.1.2 የዜና ዓይነቶች ................................................................................................................. 11
2.1.3 የዜና ጠቀሜታዎች ......................................................................................................... 13
2.1.4 የዜና ጥንካሬዎችና ድክመቶች........................................................................................ 14
2.1.5 የዜና መመዘኛ እሴቶች .............................................................................................. 15
2.1.6 የዜና አላባውያን .............................................................................................................. 22
2.2 የዜና ምንጮች .................................................................................................................... 27
2.2.1 ዜና ከየት ይገኛል? ...................................................................................................... 27
2.2.2 የዜና ምንጮች............................................................................................................. 28
2.2.3 የዜና ምንጮች አያያዝ ................................................................................................ 30
2.2.4 መረጃ እንዴት ይገኛል? .............................................................................................. 32
ሀ. ምልከታ ............................................................................................................................ 32
ለ. ቃለ መጠይቅ .................................................................................................................... 39
ሐ. ምርምርና ጥናት.............................................................................................................. 48
2.3 የዜና አፃፃፍ ስልት.............................................................................................................. 48
2.3.1 የዜና ቋንቋ................................................................................................................... 49
2.3.2 መሪ አንቀፅ (Lead) .................................................................................................... 52
2.3.3 የአርስተ ዜና አፃፃፍ .................................................................................................... 53
2.3.4 የዜና መዋቅር .............................................................................................................. 54
i
2.3.5 የሬዲዮ የዜና አፃጻፍ ፎርማቶች ................................................................................. 57
2.3.5 የሬዲዮ ዜና አፃጻፍ ደንቦች ......................................................................................... 63
3. የሬዲዮ ፕሮግራም ...................................................................................................... 65
3.1 የሬዲዮ ፕሮግራም ማለት ምን ማለት ነው? .................................................................... 65
3.2 የሬዲዮ ፕሮግራም ዓይነቶች .............................................................................................. 65
3.2.1 የማስተማርያ ፕሮግራም ............................................................................................. 65
3.2.2 የማሳወቂያ ፕሮግራም................................................................................................. 66
3.2.3 የመዝናኛ ፕሮግራም ................................................................................................... 66
3.3 የሬዲዮ ፕሮግራም ባህርያት .............................................................................................. 67
3.4 የሬዲዮ ፕሮግራም ዝግጅት ................................................................................................ 68
3.4.1 የቅድመ-ዝግጅት ምዕራፍ............................................................................................ 69
3.4.2 የዝግጅት ምዕራፍ ....................................................................................................... 73
3.4.1 የድህረ ዝግጅት ምዕራፍ ............................................................................................. 74
ዋቢ መፅሐፍት ............................................................................................................... 75
አባሪ፡- የሬዲዮ ፕሮግራም ፕሮፖዛል አዘገጃጀት ................................................................. 76
ii
መግቢያ
1
ጋዜጠኝነት ሰውን ልጅ ሰብዓዊ መብት የሚያስከብር፣ የታመነ
የዲሞክራሲ ስርዓት አራማጅ እንዲሁም የፍትህ ርትዕ ጠበቃና የህዝብ
ድምፅ ነው፡፡ ጋዜጠኝነት በነፃ ሃሳብን የመግለጫ መሳሪያ፣ እንዲሁም
የህሊናን ነፃነት ማዳበሪያ ፍቱን ማስተላለፊያ መሳሪያ በመሆኑ
በህብረተሰብ የሙያ ዝርዝሮች ውስጥ ከፍተኛውን ቦታ መያዝ የሚገባው
ተግባር ነው፡፡
የጋዜጠኝነት ዋነኛ የስራ ማሳያ የሆኑት የብዙሃን መገናኛዎች ናቸው፡፡ እነዚህን ብዙሃን
መገናኛዎች ህዝባዊ የሆኑ ጉዳዮችን በመረጃና በአስተያየት ተቀሽረው የሚቀርቡበት
ነው፡፡ ጋዜጠኝነት መረጃን ጥሩውን ከድፍርሱ፣ ምርቱን ከእንክርዳዱ በመለየት
መረጃዎችን፣ አስተያየቶችን እና ሁነቶችን ከህብረተሰቡ ለህብረተሰቡ የማሰራጨት ስራ
ነው፡፡
2
አድርገን የምንወስደው፡፡ ነገር ግን ጋዜጠኝነት ሁልጊዜም ከብዙሃን መገናኛ ጋር ብቻ
ማሰብ የተሳሳተ ግንዛቤ ነው፡፡ ምክንያቱም ብዙሃን መገናኛ የመረጃ ማስተላለፊ መንገድ
እንጂ በራሱ የጋዜጠኝነት ሙያ አይደለም፡፡ ስለዚህ በበራሪ ወረቀቶች፣ በማስታወቂያ
ሰሌዳዎች፣ በመስሪያ ቤት ህትመቶች ወዘተ የሚሰራጩ መረጃዎች በጋዜጠኝነት ዘውግ
ውስጥ ይከናወናሉ፡፡
3
የስልጠናው ዓላማ
4
ክፍል አንድ
በአሁኑ ሰዓት በዓለማችን የብዙሃን መገናኛ ተቋማት ዋነኛ የልማት ደጋፊ እንደሆነ
ይታመናል፡፡ ልማት ማለት ምን ማለት ነው የሚለው ጉዳይ የተለያዩ ዓይነት
ትርጓሜዎች ቢሰጠውም አሜሪካዊ ምሁር ሮጀርስ (1976) ልማት ምን እንደሆነ
የሚከተለውን ትርጉም ሰጥቷል፡፡
ከሮጀርስ ትርጉም መረዳት የሚቻለው ልማት ማለት ሂደት ነው፤ ልማት ማለት
ማህበራዊ ለውጥን ያመጣል፣ ልማት ማለት አብዛኛውን የማህበረሰብ ክፍል
ይጠቅማል፣ ልማት ማለት መሻሻል ነው፡፡
5
ያለውን ግንኙነት በማቋረጥ ለራስ መስራት ነው ይላሉ፡፡ በዚህ መሃል የሁለቱ ፅንፍ
የወጣ አስተምህሮ ዓለማችን በግሎባላይዜሽን ዘመን አንዱ ለአንዱ አስፈላጊ ስለሆነ
የሚያስሄድ ስላልሆነ ሶስተኛ አማራጭ “ሌላው አስተምሮ” የሚል የሶስተኛ ዓለም
ሃገራት ፈጠሩ፡፡ ይህ አስተምሮ ልማትን ማየት የሚፈልግበት ዕይታ ልማት መጀመር
ያለበት ታች ካለው ተራ ህዝብ ሲሆን የሃገሩን ባህልና ቋንቋ እንዲሁም ሥነ-ምህዳሩን
በጠበቀ መልኩ መሆን አለበት ይላሉ፡፡ ስለዚህ ይህንን አማራጭ በመያዝ ማህበረሰብን
ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ሥራዎች ሲሰሩ በዋናነት የሚከተሉት ማህበረሰቡን
ያሳተፈና ተጠቃሚ የሚያደርግ አካሄድን መሆን ይኖርበታል፡፡ ተራውን የማህበረሰብ
ክፍል ለማሳተፍ ደግሞ የመረጃ ተደራሽነት በዘልማዳዊው ሚዲያ አስቸጋሪ ስለሚሆን
የማህበረሰብ ሚዲያ ወይም የማህበረብ አገልግሎት የሚሰጡ የሬዲዮ ጣቢያዎች
በየአካባቢው መኖር ይጠበቅባቸዋል፡፡
6
የማህበረሰብ ሬዲዮ አራቱ መርሆች ብሎ ጃን ሰርቪያስ (2007) ያስቀመጣቸው
የሚከተሉት ናቸው፡፡
የመወያያ ጥያቄዎች
7
አጀንዳዎችን በትልቁም ሆነ በትንሹ በጥልቀት እየፈተሸ ይሰራል፡፡ የልማት ፕሮጀክቶችን
ተገቢነት እና አካሄድ ላይ የመደገፍ ሥህተቶች ካሉም የማጋለጥ ሥራ ይሰራል፡፡ በአጠቃላይ
ልማታዊ ጋዜጠኝነት የሚያተኩረው ልማት ተኮር የሆኑ ዜናዎችን መረጃ በመሰብሰብ
ለማህበረሰቡ ማድረስ ላይ ነው፡፡ የልማታዊ ጋዜጠኝነት ቁልፍ ተግባራት (አጋራዋል፣ 1980)
የቡድን ውይይት
ማጠቃለያ
8
ክፍል ሁለት
2.1 ዜና
የመወያያ ጥያቄዎች
ዜና ምንድን ነው?
በየቀኑ ምን ያህል ዜና ትሰማላችሁ?
ዜና ያስፈልጋል ወይስ አያስፈልግም?
9
አያሌ የጋዜጠኝነት ምሁራን “ዜና” ለሚለው ቃል የተለያዩ ትርጎሞች ይሰጡታል፡፡
የትርጉማቸው መሰረተ ሃሳብ አንድ ቢሆንም የአተረጓጉም ዘይቤያቸው ግን በመጠኑ
ልዩነት አለው፡፡ በእንግሊዘኛ ቋንቋ የዜና አቻ ትርጉም ነው የሚባለው “News”
የሚለውን ቃል ከቁም ትርጉሙ ሌላ ሁለት ዓበይት ቁምነገሮች ያንፀባርቃል፡፡ አንደኛው
የቃሉ ዝርዝር ፊደላት N (North) ሰሜን, E (East) ምስራቅ, W (West) ምዕራብ እና
S (South) ደቡብ ማለት ነው ይላሉ፡፡ ስለዚህ “News” በሚለው ቃል ውስጥ ያሉት
አራት ፊደላት አራቱን መልክዓ ምድራዊ የዓለም ማዕዘናት ይጠቁማሉ ማለት ነው፡፡
ሁለተኛው “News” (ዜና) ከሚለው ቃል የሚገኘው ቁም ነገር ጋዜጣ “Newspaper”
ለሚለው የእንግሊዘኛ ቃል መነሻ ወይም መሠረት መሆኑ ነው፡፡ ብዙዎቹ የሙያው
ምሁራን ዜናን ዜና የሚያደርገው በዜና መልክ መዘጋጀቱ ብቻ ሳይሆን ለህብረተሰቡ
መሰራጨቱ ነው ይላሉ፡፡
10
መለስ ዜናዊ ህልፈተ-ህይወት አሁን ላይ ታሪክ ቢሆኑም በወቅቱ ግን የተመረጡ
ዜናዎች ነበሩ፡፡
11
1. የቀጥታ ዜና (Hard News)
12
ለምሳሌ ያህል ግለታሪኮች፣ የመዝናኛ ወሬዎች፣ ባህላዊ ወጎችና የመሳሰሉት የሚጠቀሱ
የተዋዛ ዜና ሁነታዎች ናቸው፡፡
13
ሠራተኞች ከሃምሌ ጀምሮ የደመወዝ ጭማሬ ሊያደርግ ነው የሚሉ ዜናዎች
የዜናን የመንገር ጠቀሜታ ያሳያሉ፡፡
ዜና በጣም ከፍተኛ የሆነ ተፈላጊነት ያለው የጋዜጠኝነት ዘውግ ነውው፡ ይኸውም ሰዎች
ለተለያዩ ምክንያቶች ትኩረት ሰጥተው የሚከታተሉት ዘውግ፡፡ ዜና የራሱ የሆነ የአፃፃፍ
ስልት ያለው ሲሆን በቀጥታና በተዋዛ መል ይቀርባል፡፡ ዜና የራሱ የሆነ ጠንካራና
ደካማ ጎኖች አሉት፡፡
14
የዜና ጥንካሬዎች
15
ነገር ግን እነዚህ እሴቶች በመጠቀም ዜናው በሚገመገምበት ሰዓት ከግምት ውስጥ
የሚገቡ ሁኔታዎች አሉ፡፡ እነዚህመም ሁኔታዎች
16
ከነዚህ ሁለት ዜናዎች የትኛው ዜና የበለጠ ለኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት
አድማጭ ተመልካች ትኩረት ይሰጠዋል? ለምን?
አንዳንድ ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ደግሞ የበለጠ ቅርብ የሚሆኑበት አጋጣሚ አላቸው፡፡
ለምሳሌ የነዳጅ ዋጋ መጨመር፣ የታላላቅ ዓለም አቀፍ ተቋማት ኪሳራ፣ የአስከፊ
ወረርሽኝ መከሰት፣ ወዘተ ናቸው፡፡ እንደነዚህ ዓይነት የዓለማችን አንገብጋቢ ዜናዎችን
መስራት የምንችለው ደግሞ ከአገራችን አውድ ጋር በማዛመድ ነው፡፡ ስለዚህ ዜናችን
ተፅዕኖ መፍጠር እንዲችል ተገቢነት ያስፈልገዋል፤ ተገቢነት እንዲኖረው ደግሞ ቅርበት
ሊኖረው ይገባል፡፡
በአጠቃላይ አንድ ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ለሚገኝ ግለሰብ መጀመሪያ ስለደብረ
ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ፤ ከዚያም ስለጎጃምና አካባቢው፤ ቀጥሎ ስለአማራ፣ ስለኢትዮጵያና
ስለአፍሪካ እያለ ስለተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች ቢነገረው ትኩረት የመስጠት
ሁኔታውም በየደረጃው ከፍ እያለ የሚሄድበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡
ለምሳሌ፡
17
ሰዎችን የስኬት፣ የውድቀት፣ አስተዳደግ፣ ውሎና አዳር፣ ሽንፈትና ድል እንዲሁም
ውስጠ-ምስጢራቸውን ማወቅ ለሚፈልግ አድማጭ ተመልካች ያንን ይዞ መገኘት ትልቅ
የዜና እሴት ነው፡፡ በዜና ውስጥ የታዋቂ ሰዎች ስም ካለበት ዜናው የዕለቱ ዜና ተደርጎ
ይቀርባል፡፡
3. ወቅታዊነት (Timeliness)
ዜናን ዜና የሚያሰኘው አዲስ ነገር ይዞ መገኘቱ ነው፡፡ በአገራችን የዜና ቋንጣ የለውም
ይባላል፡፡ ይህም ማለት አንድ ድርጊት እንደተከሰተ ወዲያውኑ መደበኛ የሆኑ የጋዜጠኛ
ጥያቄዎችን መመለስ ይጠበቅበታል፡፡ እነዚህም ጥያቄዎች በእንግሊዘኛ 5 W and H
questions በመባል ይታወቃሉ፡፡
ምን ተከሰተ?
ማን ፈፀመው?
መቼ ተከፈተ?
የት ተከሰተ?
ለምን ተከሰተ? እና
እንዴት ተከሰተ? የሚሉት ናቸው፡፡
ስለዚህ ድርጊቱ በተከሰተበት ፍጥነት፤ ቴክኖሎጂው እስከፈቀደ ድረስ ዜና በፍጥነት
ወቅቱን ጠብቆ መሠራት አለበት፡፡ የብሮድካስት ሚዲያ በተለይ ሬዲዮ በቀጥታ በቀላሉ
ነገሮችን ለማስተላለፍ ይረዳል፡፡ ወቅታዊነት በብሮድካስትና በህትመት የብዙሃን
18
መገናኛዎች እኩል አይደለም፡፡ ምክንያቱም እንደብሮድካስት ሚዲያ በፍጥነት በህትመት
ውጤቶች ላይ ማስተላለፍ አይቻልም፡፡ ይኸውም የህትመት መውጫ ቀን መጠበቅንና
ሁሉንም ሂደቶች ማለፍ ስለሚያስፈልግ ነው፡፡
ወቅታዊነት ማለት ዛሬ የሆነን ክስተት ብቻ መዘገብ ማለት አይደለም፡፡ ነገር ግ እስከዛሬ
ድረስ ተደብቀው የተቀመጡ መረጃዎችን እንደተገኙ ማቅረብን ይጨምራል፡፡ ለምሳሌ
የቀዳማዊ ኃይለስላሴ አሟሟት እስካሁን ድረስ ግልፅ የሆነ ነገር የለውም፡፡ ነገር ግን
ከገዳዮቹ አንዱ አሁን ሊሞት ሲል የነበረውን ሂደት ቢናዘዝና መረጃ ቢወጣ
ወቅታዊነትን አያዛባም፡፡ ከወቅታዊነት ጋር በተያያዘ ግን ቶሎ ብሎ ዜናን ለማቅረብ
ያልተጣሩ መረጃዎችን ይዞ መውጣትም ይሁን ያልጠራ ፅሁፍ መስራ ተገቢ አይደለም፡፡
5. አወዛጋቢነት (Controvesy)
19
ለምሳሌ፡- ሞሮኮ የ2015 የአፍሪካን ዋንጫ አላዘጋጅም አለች፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የኢቦላ
ወረርሽኝ መስፋፋት ነው፡፡ በሌላ በኩል የአፍሪካ ዋንጫ ኮንፌዴሬሽን ውድድሩን
የማታዘጋጅ ከሆነ ከፍተኛ የሆነ ቅጣት እንደሚጣልባት አስታውቋል፡፡
6. ተገቢነት (Relevance)
ተገቢነት ለቅርበት የተሻለ ትኩረት ይሰጠዋል፡፡ ቅርበቱ ሲጠብ ዜናው በአንድ ሃገር
ውስጥ የተለያዩ ቡድኖች ፍላጎት ማሟላት ይሳነዋል፡፡ ለምሳሌ የምርት ማዳበሪያ ዋጋ
መውረድ ለአርሶ አደሮች ጥሩ ዜና ነው፤ ተገቢነትም አለው፡፡ ለብረታ ብረት ኢንዱስትሪ
ባለሃብቶች ግን ተገቢነት የለውም፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የብረታ ብረት ዋጋ ጭማሬ
ለኢንዱስትሪው ባሃብቶች ተገቢ ሲሆን ለአርሶ አደሮች ግን ምንም አይደለም፡፡ ይህም
የሚያሳየው የዜናዎች ጠቃሚነት በቅርበትና በተገቢነት የተወሰነ መሆኑ ነው፡፡
7. ትንግርት (Uniqueness)
20
ያልተለመደ ሲሆን የዜናውን እሴት በመጨመር የአድማጭ ተመልካችን ቀልብ መግዛት
ይችላል፡፡
ለምሳሌ፡-
ከላይ ከተጠቀሱት ሁለት ዜናዎች የበለጠ የዜና እሴት ያለው ሁለተኛው ነው፡፡
ምክንያም የሰው ልጅ አይቀሬ የሆኑ ጉዳዮች ልደትና ሞት የተለመዱ ሲሆኑ በነዚህ
መካከል ግን ያልተለመዱ ሁኔታዎችን እንደ አራት ልጆች በሰላም መውለድ ዓይነት
ሁኔታዎች ሲፈጠሩ ግን ዜና ይሆናል፡፡
ለምሳሌ
21
9. ልብ ሰቀላ (Suspense)
1. እውነትነት (Accuracy)
2. ሚዛናዊነት (Objectivity)
3. ምልዑነት (Completeness)
4. ግልፅነት (Clarity)
5. ምንጭን መለየትና መግለፅ (Source Identification and Attribution )
22
እውነትነት
ምንጭን
መለየትና ሚዛናዊነት
መግለፅ
ግልፅነት ምልዑነት
1. እውነትነት
ታማኝነትን ያሳጣል
አድማጭ ተመልካችን ያሳጥል ወይም ምርጫቸውን እንዲቀይሩ ያደርጋል
አላስፈላጊ የሆኑ ብዥታዎችን ይፈጥራል
ስለዚህ ከነዘህ እና መሰል ችግሮች መፈጠር በፊት ዜናውን የሚያዘጋጀው ጋዜጠኛ ጊዜ
ወስዶ ያሉትን መጃዎች ደግሞ ደጋግሞ ማረጋገጥ ይገባዋል፡፡ ምክንያቱም የጋዜጣ
ወይም የሬዲዮ ወይም ማንኛውም ዜና በተቻላቸው መጠን እውነት የሆነውን ነገር ነው
መዘገብ ያለባቸው፡፡ እውነትነት መጓደል ከሁለት በኩል ሊከሰት ይችላል፤ ከፀሐፊውና
ከመረጃ ምንጩ፡፡ በእውነት ላይ የተመሰረተ ዜና የማይሰሩ ጋዜጠኞች እንደመንስኤ
የሚቆጠረው ደግሞ ትኩረት ባለመስጠር (በእንዝህላልነት)፣ በስንፍና፣ ባልተሟላ
መረጃ፣ በተዛባ መረጃ እና በተባራሪ ወሬዎችና አሉባልታዎች ላይ ተመርኩዘው
መስራታቸው ነው፡፡ ነገር ግን መታየት ያለበት በነዚህና መሰል መንስኤዎ ምክንያት
እውነት ያልሆነ ነገር መዘገብ በጣም ከፍተኛ የሆነ ችግር መፍጠሩ ነው፡፡
23
2. ሚዛናዊነት
24
3. ምልዑነት
4. ግልፅነት
ዜና መዘገብ ያለበት አጭርና ግልፅ በሆነ መልኩ ነው፡፡ በተለይም ለብሮድካስት ሚዲያ
መዘገብ ያለበት አንድ ጊዜ ተሰምቶ በቀላሉ ለአድማጭ ተመልካች በሚገባበት መልኩ
መሆን አለበት፡፡ ምክንያቱም የብሮድካስት አድማጭ ተመልካቾች እንደገና ደግመው
የመስማት ዕድል የላቸውም ወይም ያልገባቸውን ነገር ከተለያዩ ነገሮች ላይ ለማጣቀስም
ሆነ ለማሰብ ጊዜ ስለሚያስፈልጋቸው ያንን ሲያደርጉ ሌሎች ዜናዎች ስለሚያልፉ ነው፡፡
ስለዚህ ዜናው ግልፅና በቀላሉ ለአድማጭ ተመልካች የሚገባ መሆን ይጠበቅበታል፡፡
ለዚህ ደግሞ የዜናው ፀሐፊዎች የሚመርጧቸው ቃላትና የዓረፍተ ነገር አወቃቀራቸው
ቀላልና ያልተንዛዛ መሆን አለበት፡፡ ይህም የአድማጭ ተመልካችን ሥራ ከማቅለሉ በላይ
ዜናውን ተደማጭ ያደርገዋል፡፡
25
5. ምንጭን መለየትና መግለፅ
26
2.2 የዜና ምንጮች
የመወያያ ጥያቄ
የመረጃ ምንጭ ማለት ማንኛውም ግለሰብ፣ ድርጅት፣ ተቋም ወይም ቡድን በትክክል
የተዋቀረ መረጃ ማቅረብ ወይም መስጠት የሚችል ነው፡፡ እነዚህ የመረጃ ምንጮች
ከጋዜጠኛው ጋር በሚኖራቸው ጊዜ ስለድርጅታቸው ወይም ስለራሳቸው ትክክለኛ መረጃ
የመስጠት አቅም ሊኖራቸው ይገባል፡፡ በተመሳሳይ ሪፖርተሩም የመረጃ ምንጮችን
አያያዝ በተመለከተ አግባብነት ያለው አካሄድ ሊኖረው ይገባል፡፡ ይህም ማለት በመረጃ
ምንጩና በጋዜጠኛው መካከል መልካም ግንኙነት ሊመሰረት ይገባል፡፡ ምክንያቱም
ያለመረጃ ምንጮች የጋዜጠኛነትን የዕለት ከዕለት የሥራ እንቅስቃሴ የተሟላ ማድረግ
ስለማይቻል ነው፡፡
27
ተጠንክሮ መቀጠልም ይኖርበታል፡፡ ስለዚህ በጋዜጠኛውና በመረጃ ምንጩ መካከል
ያለውን ግንኙነት ለማሳደግ የሚከተሉት ተግባራት መከናወን ይገባቸዋል፡፡
28
ማዕከላትም የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ)በ እና ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል
(ዋልታ) ናቸው፡፡ የውች ሃገር ዜናዎችን ደግሞ የቻይናው ሽንዋ፣ አጃንስ ፋራንስ
ፕሬስ፣ ዩናይትድ ፕሬስ ኢንተርንሽናል፣ ፓን አፍሪካን ኒውስ ኤጀንሲ (ፓና)፣
ሮይተርስ፣ ወዘተ የሚጠቀሱ ዋና ዋና የዜና ምንጮች ናቸው፡፡
29
2.2.3 የዜና ምንጮች አያያዝ
መረጃ ምንጮችን በተገቢው መንገድ መያዝ በጣም ጠቃሚ ነው፡፡ የመረጃ መ፣ንጮች
ስማቸው እንዳታወቅ የሚፈልጉ፣ ማንነታቸው እንዳይታወቅ የሚፈልጉ ወይም ደግሞ
ስማቸውንና ማንነታቸው በሚስጢር እንዲያዝላቸው የሚፈልጉ፣ ድምፃቸውና ምስላቸው
እንዳይቀረፅ የሚከለክሉ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ እነዚህን የመረጃ ምንጮች እንዴት መጠቀም
እንዳለበት የሚያውቅ ጋዜጠኛ ደግሞ በሥራው ከፍተኛ ትርፍ ያገኛል፡፡
30
ከአሁን በፊት ስላስቀየማቸው ጋዜጠኛ ይቅርታ በመጠየቅ የራስን ስብዕና
ማስረዳት
ምንጮች የነሱ መረጃ ጠቃሚ መስሎ ካልታያቸው በጣም ጠቃሚ የሆነ መረጃ
እንሱ ጋ እንደሚገኝ ሌለ፤ ሰው ላይ ያንን መረጃ ማግኘት እንደማይቻል
በማሳመነን መረጃ እንዲሰጡ ማድረግ
31
ላለመግለፅ ከተስማማ ደግሞ ስምምነቱን ማክበር ይጠበቅበታል፡፡ ምክንያቱም ቃላችንን
ካላከበርነ ሌላ ጊዜ በፍፁም መረጃ ማግኘት ላይቻል ይችላል፡፡ ይህ ደግሞ ጋዜጠኝነት
የአንድ ቀን ሥራ ስላልሆነ የጋዜጠኝነት ሥራ በከፍተኛ ሁኔታ ይጎዳዋል፡፡
ሀ. ምልከታ
በአንድ ጉዳይ ላይ የተሻለ ሽፋን ለመስጠት ተመራጩ መንገድ ቦታው ድረስ በመሄድ
ተግባር መሆን ያለበት የመረጃ መሰብሰቢያ መንገድ ነው፡፡ ጋዜጠኛው በቦታው ተገኝቶ
ሁኔታዎችን መመልከት ካልቻለ የአንድ ዜና ጥንቅር ምልዑነት አስተማማኝ አይሆንም፡፡
ምክንያቱም ቦታው ድረስ ሄዶ መመልከት በሌሎች መንገዶች የሚሰበሰቡትን ጉዳዮች
በዓይን ተመልክቶ የማረጋገጥ ወይም ደግሞ ውድቅ የማድረግ ሥራዎችን ለማድረግ
ተጨማሪ ኃይል ስለሚሰጥ ነው፡፡
“ማየት ማመን ነው” እንደሚባለው በዜና አሰባስባችን ውስጥ ቦታው ድረስ በመሄድ
መመልከት የራሱ የሆነ ጥቅምና ጉዳት አለው፡፡ አንድን ጉዳይ ቦታው ድረስ ሄዶ
መመልከት የሚያስገኛቸው ጥቅሞች፡-
32
ከሚታየው ነገር ባሻገር ስላለው እውነት ለማወቅ
ሠው በንግግር ሊገልፃቸው የማይችሉ ጉዳዮችን ለማግኘት ዕድል ይሰጣል
ከባለጉዳዮች ጋር ቅርርብ መፍጠር ስለሚችል… ወዘተ
በሌላ በኩል አንድን ጉዳይ ቦታው ድረስ ሄዶ መመልከት ያሉት ጉዳቶች፡
ከፍተኛ የሆነ ወጪ ይጠይቃል (የማቴሪያል፣ የገንዘብና የጉልበት ወጪ)
ጊዜ ይፈጃል
ወደ ቦታው ለመግባት አስቸጋሪ ሁኔታዎችን መጋፈጥ ይጠይቃል
ከጉዳዩ ባለቤቶች የሚደርሱ ክልከላዎችና ማስፈራሪያዎች ወዘተ ይገኙበታል፡፡
ምንም እንኳ አንድን ጉዳይ ቦታው ድረስ ሄዶ መመልከት የራሱ የሆነ ጥቅሞችና
ጉዳቶች ቢኖሩትም ስለጉዳዩ ምልዑ የሆነ መረጃ ለመሰብሰብ መድረክ ስለሚከፍት
ተመራጭ መንገድ ያደርገዋል፡፡
ለምሳሌ፡- በቦረና አካባቢ 4.5 ሚሊዮን ህዝቦች ተርበዋል የሚል ወሬ ሰምታችሁ የመረጃ
ምንጫችሁ ምናልባትም የመንግስት ባለስልጣናት የሚሰጡትን መግልጫ ጉባኤ ከአዲስ
አበባ ብትከታተሉ ወይም ከቦረና የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የሚልከውን
ጋዜጣዊ መግለጫ ፅሁፍ እንደምንጭ ብትጠቀሙ ምናልባት የጉዳዩን ሁለትከመቶ
እንኳን በሚገባ መረዳት አይቻልም፡፡ ምክንያቱም የጉዳዩን አስከፊነት ሠዎች
ከሚነግሯችሁ በላይ ቦታው ድረስ ሂዳችሁ ብትመለከቱ የበለጠ መረዳት ስለምትችሉ
ነው፡፡ እስካሁን ባለው ሁኔታ አስር ሰዎች ሞተዋል ሲባል መስማትና አስር ሰዎች
በረሃብ አለንጋ ተገርፈው ቆዳቸው ከአጥንታቸው ተጣብቆ ሲሞቱ ማየት ለጋዜጠኛ
የበለጠ ትርጉም የሚሰጠው የትኛው እንደሆነ የታወቅ ነው፡፡
የምልከታ ዓይነቶች
33
መደበኛ በሆነ መልኩና በተደራጀ አካሄድ የሚደረግ ነው፡፡ እነዚህን የምልከታ ዓይነቶች
በውስጣቸው የተለያዩ የምልከታ ዓይነቶች ይዘዋል፡፡
የአንድ ጊዜ ምልከታ
እነዚህ ሶስቱ የምልከታ ዓይነቶች አንድ ድርጊት ሲፈጸም ወይም ክስተት ሲከሰት ቦታው
ላይ በመገኘት የሚከናወኑ የምልከታ ዓይነቶች ናቸው፡፡
ሀ. ልማዳዊ ምልከታ
34
የመረጃ ምንጩ ጋዜጠኛው እንዲያይለት የሚፈልገውን ነገር በሙሉ ለማሳየት
ይጥራል፣ ይኸውም የመረጃ አድማሱን ያሰፋዋል፡፡
ጋዜጠኛው ራሱን የጉዳዩ አካል ስለማያደርግ በተቻለ መጠን ነፃና ሚዛናዊ ሆኖ
እንዲሰራ ይጠቅማል፡፡
ጋዜጠኛው የጋዜጠኛ የሥራ መሳሪያዎችን (ካሜራ፣ መቅርፀ- ድምፅ፣ ማስታወሻና
ሌሎችንም) እንዲጠቀም ይረዳዋል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ ልማዳዊ ምልከታ የራሱ የሆነ ድክመቶች አሉት፡፡ ልማዳዊ ምልከታ
በአንድ የተወሰነ ጊዜ ውስጥ ውስን የሆነን እንቅስቃሴ ለማየት የሚደረግ ስለሚሆን
በዋናነት በዛች ሰዓትም የመረጃ ምንጩ የጋዜጠኛውን መኖር እያወቀ በመካሄዱ
ምክንያት የተለያዩ ድክመቶች አሉት፡፡ የጋዜጠኛውን መኖር ስለሚያውቁ ትክክለኛ
ሥራቸውንና ሰብዕናቸውን እንዲደብቁ ያደርጋል፡፡ በተጨማሪም ጋዜጠኛው የመረጃ
ምንጩ በወቅቱ በሚያሳየው ነገር ላይ እንዲወሰን ያደርገዋል፡፡
ለምሳሌ፡- የአባይ ግድብን ለመመልከትና ስለግድቡ መረጃ እንዲኖረን የሥራ ኃላፊዎችን
ማግኘት ስላለብን የምናገኘው በልማዳዊ ምልከታ ነው፡፡
ለ. ድብቅ ምልከታ
35
እርዳታ ተደብቆ በመግባት መመልከት ይገባል፡፡ ስለዚህ የሰዎችን ድብቅ ማንነት
በድብቅ በማየት የህፃናቱን መደፈር መረጃ መሰብሰብ ይቻላል፡፡
ሐ. አሳታፊ ምልከታ
36
ምንም እንኳ ጋዜጠኛው ራሱን መግለፅ ከክህደትና አጭበርባሪነት ተግባር ነፃ
ቢያደርገውም ነገሮች ተፈጥሮአዊ በሆነ መንገድ ራሳቸውን ጠብቀው እንዲሄዱ
ጋዜጠኛው ራሱን በሚስጢር ደብቆ መመልከት የተሸለ ታሪክ ይዞ እንዲመጣ
ያደርገዋል፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ ጉዳዩ ቀላልና ለማየት የማይከለከል ከሆነ ራሳቸውን
ጋዜጠኞች እንደሆኑ በመናገር መሳተፍ ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ፡- በመስቀል በዓል የጉራጌን
የክትፎ አዘገጃጀት በተመለከተ ጋዜጠኛው አብሮ እየሠራ መመልከት በምስጢር
ከመመልከቱ የተሻለ ነው፡፡
ሥርዓታዊ ምልከታ
37
ይጠበቅበታል፡፡ ከዚያም በየቀኑ የሚሰበሰቡ መረጃዎችን በማደራጀት መጠቀም ተገቢ
ነው፡፡ የህዝብ አስተያየቶችም ከቀን ቀን ስለሚለያዩ ሠፋ ያለ ጊዜ ወስዶ መመልከት
ይጠይቃል፡፡
የይዘት ትንተና፡- በአንድ ወቅት የተሰበሰቡትን ሰነዶችና መዛግብት በአንድ ጊዜ መርምሮ
ማስቀመጥ አይቻልም፡፡ ለምሳሌ በኢትዮጵያ ውስጥ በምርጫ 97 ወቅት የነበሩ የግል
ጋዜጦች ምን ዓይነት አቋም ነበራቸው በሚል ርዕስ የይዘት ትንተና ለማድረግ ብንፈልግ
የአንድን ጋዜጣ አንድ ህትመት ብቻ አይተን ፀረ-ኢህአዴግ ናቸው ልንል አንችልም፡፡
ሰፋ ላለ ጊዜ ሰፊ ናሙና ተወስዶ ሊሰራ ይገባል፡፡
38
የተግባር ልምምድ
ለ. ቃለ መጠይቅ
የውይይት ጥያቄ
1. ቃለ መጠይቅ ምንድን ነው?
2. ቃለ መጠይቅ በማን ይካሄዳል?
3. ቃለ መጠይቅ እንዴት ይካሄዳል?
4. ጋዜጠኛ የሚያደርገው ቃለ መጠይቅ ምን የተለየ ነገር አለው?
39
ሁለት መሰረታዊ ህጎች አሉት፡፡ አንደኛው በጥንቃቄ መስማት ነው፡፡ ይህም ቃለ
መጠይቅ የሚሰጠው ሰው የሚናገረውን ነገር በትክክል መስማት፣ ላልተብራሩ ነገሮች
ተጨማሪ ማብራሪያ መጠየቅ ወዘተ መሰረታዊ አሰራሮች ናቸው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ
እንግዳችንን/ መላሽን የማክበር ተግባር ነው፡፡ ይህም ሲባል መላሹ የሚሰጠው መልስ
ምንም ያህል ተገቢና አሳማኝ ባይሆንም እንኳን ሁልጊዜ የቃለ መጠይቅ ተሳታፊውን
ማክበር ይገባል፡፡
40
ተሳታፊ ይሆናል፡፡ ነገር ግን ጋዜጣዊ ቃለ መጠይቅ ሁሉም ሰው ተሳታፊ
አይደለም ምክንያቱም በማህበረሰቡ ውስጥ የሚያሳየው አንድምታ ከግምት
ውስጥ ይገባል፡፡
41
ምክንያቱም አንድ ሰው ስለአንድ ጉዳይ በቴሌቪዥን፣ በጋዜጣ ወይም በሬዲዮ
ቃለ መጠይቅ አደረገ ማለት የሚያመጣው ማህበራዊ ተፅዕኖ ከፍተኛ ነው፡፡
11. ጋዜጣዊ ቃለ መጠይቅ ቁጥብ ነው፡፡ ይኸውም የሚሰራው በጊዜና በቦታ ተወስኖ
ስለሆነ የሚደረገው ቃለ መጠይቅ በአንድ ጉዳይ ላይ ለሚኖረን የአየር ሰዓት
ወይም በሚኖረው የጋዜጣ ገፅ ስፋት ብቻ የሚወሰን ነው፡፡
42
ዓይነት የምናደርገው በአንድ አካባቢ፣ ድርጅት፣ ቢሮ፣ ወዘተ የተፈጠሩ አዲስ ነገር
መኖሩን ቆፍረን በማውጣት ለአድማጭ ተመልካች የማቅረብ ሥራ ነው፡፡ ስለዚህ
ምንድን ነው እየተካሄደ ያለው? ምንድን ነው የተፈጠረው? የሚሉትን ጥያቄዎች ምላሽ
የማግኘት ዓላማ አለው፡፡
ስለአንድ ጉዳይ መረጃው ከደረሰን በኋላ የሚከናወን ነገር ቢኖር ስለመረጃው መጠየቅ
ሳይሆን ማብራሪያ፣ አመክንዮ ወይም አስተያየት መጠየቅ ነው፡፡ ስለዚህ ለዚህ ደግሞ
ለማብራሪያ የሚደረግ ቃለ መጠይቅ ከጉዳዩ ባለቤት ጋር ይደረጋል፡፡ እንደዚህ ዓይነት
መረጃ አለ እርስዎ ይህ ነገር እንዴት ሊፈጠር እደቻለ ሊያስረዱኝ ይችላሉ? የእርስዎ
አስተያየትስ ምንድን ነው? ለምን ተፈጠረ? እንዴት ተከሰተ? ለዚህ ሁሉ ነገር
ምክንያቱስ ምንድን ነው? ዓይነት ጥያቄዎችን በመጠየቅ ምላሽ ይገኝባቸዋል፡፡
ይህ የቃለ መጠይቅ ዓይነት የሚከናወነው መንገድ ላይ፣ ገበያ ውስጥ፣ በዓል ቦታ፣
ወዘተ የሚገኙ ሰዎችን አስተያየትና ሃሳብ ለማወቅ ነው፡፡ ለቃለ መጠይቅ የሚጠየቀው
ጥያቄ ደግሞ ተመሳሳይና ቀላል መሆን አለበት፡፡ ለምሳሌ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣
ብሄረሰቦችና ህዝቦች በዓል በአሶሳ ከተማ ሲከበር ጋዜጠኛው በዓሉን እንዴት አገኙት?
እያለ በርካታ ሠዎችን ሃሳብ ቢጠይቅ ይህ የህዝብ ድምፅ ነው፡፡ በህዝብ ድምፅ ሚቀርቡ
43
ጥያቄዎች የባለሙያ ትንታኔ የማይፈልጉና ሁሉን ተሳታፊዎች እኩል ሊያሳትፍ
የሚችሉ ሊሆኑ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ስለዚህ የብኼሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀንና
የኢትዮጵያን ህገ-መንግስት እንዴት ያዩታልቨ ብሎ የባለሙያ ትንታኔ የሚፈልግ ጥያቄ
መጠየቅ ስህተት ነው፡፡
የተግባር መልመጃ
44
ይህ የቃለ መጠይቅ ዓይነት ጋዜጠኛው ተዘጋጅቶበት የሚሄድ ሲሆን በቀጥታ በሬዲዮና
በቴሌቪዥን የሚጠይቃቸውን ሠዎች ይዞ በመቅረብ ያለምንም የአርትኦት ሥራ
የሚያስተላልፈው የቃለ መጠይቅ ዓይነት ነው፡፡
ቃለ መጠይቅ በሁለት ሠዎች መካከል የሚካሄድ ቢሆንም አንድ ጋዜጠኛ ከአንድ ቡድን
ጋር የሚያደርገውን የሁለትዮሽ ንግግር ይጨምራል፡፡ ለምሳሌ አንድ ጋዜጠኛ ከአንድ
የፖለቲካ ፓርቲ የተለያየ ደረጃ አመራሮች ጋር በአንድ ጊዜ ቃለ መጠይቅ ቢያደርግ
ወይም ደግሞ ከአዲስ አበባ የመልሶ ማልማት ተነሺዎች ጋር ቃለ መጠይቅ ቢያደርግ
በቡድንና በፓናል የቃለ መጠይቅ ዓይነት አካሄደ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ይህ ዓይነት ቃለ
መጠይቅ በቡድንና በፓናል ሠፋፊ አውዶች ላይ የሚካሄድ የቃለ መጠይቅ ዓይነት
ነው፡፡
45
የስኬታማ ጋዜጣዊ ቃለ መጠይቅ ሂደቶች
46
አሉታዊ መሆን አለበት፡፡ ቃለ መጠይቁ በዚህ መልኩ ጥያቄዎችን ማቅረብ ከቻለ
አርኪና ስኬታማ ይሆናል ማለት ነው፡፡
47
እዚህ ከላይ የተጠቀሱት የቃለ መጠይቅ ቴክኒኮች ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡ በሌላ በኩል
ደግሞ ቃለ መጠይቅ በሚደረግበት ጊዜ መጥፎ የሆኑ ላማዶች አሉ፡፡ እነዚህም መጥፎ
ልማዶች የሚከተሉት ናቸው፡፡
የተዘጉ ጥያቄዎች ወይም አዎ ወይም አይደለም የሚል መልስ ያላቸውን ጥያቄዎችን
መጠየቅ
ጥያቄ ያልሆኑ ዝም ብሎ መናገር ብቻ የሚያደርጉ ሰዎች
ሁለትና ከዚያ በላይ ጥያቄዎችን በአንድ ጊዜ መጠየቅ
ዝም ብሎ ራስን ብቻ መነቅነቅ
የማያልቁ ተያያዥነት ያላቸውን ጥያቄዎች ተከትሎ መሄድ
ሐ. ምርምርና ጥናት
ሁልጊዜ አጭር የዜና አፃፃፍ ይቅርና ማንኛው ዓይነት አጭር የፅሁፍ አቀራረብ በጣም
ተመራጭ፣ መሳጭ፣ ለመረዳት ቀላል፣ ለአድማጭ የማይሰለች ነው፡፡ ስለ የአጭር
ፅሁፍ ተመራጭነት አስመልክቶ አንዱ የ17ኛው ክ/ዘመን ፈረንሳዊው ብለይዝ ፓስካል
የሂሳብ ፈላስፋ እንዲህ ብሎ ነበር፡፡ ‘I have made this letter longer than usual,
only because I have not had the time to make it shorter.’ በአማርኛው
ሲተረጎም “ይህ የምፅፈው ደብዳቤ ከድሮው የተለየ ረዘም ያለ አድርጌዋለህ፡፡ እንዲህ
ያደረኩበት ምክንያት ለማሳጠር ጊዜ ስለሌለኝ ነው፡፡” ይህ ምሳሌ የሚያሳየን ነገር ቢኖር
49
አጭር ፅሁፍ ወይም አጭር ዜና ለመፃፍ የተካነ ቋንቋ ችሎታና ጊዜ እንደሚያስፈልገን
ነው፡፡ ስለ አጭር ዜና አፃፃፍ መታወቅ ያለበት ጉዳይ ዜና በአጭሩ ተፃፈ ማለት
ማስተላለፍ ያለበት ፍሬ ጉዳይ (መልዕክት) ሳያስተላልፍ በቁንፅሉ መተው ማለት
አይደለም፡፡ ዜና በአጭር ቋንቋ ተፃፈ ማለት ሙሉ መልእክት ማስተላለፍ በሚችል
መልኩ በተመረጡ ሐረጎችና ቃላት ሳይንዛዛ ሲቀርብ ነው፡፡ ስለዚህ ዜና በአጭር የቋንቋ
አፃፃፍ ለማቅረብ ከባድ ከመሆኑ የተነሳ ጥበብና ትዕግስት ይጠይቃል፡፡
የዜና አፃፃፍ በአጭር ቋንቋ በጥቂት ቃላት ማለትም ድርጊቶች፣ ድራማዎች፣ ቀለም
እንዲሁም የአንባቢው ፍላጎት ሳይሸራረፍ ለማቅረብ ተደጋጋሚ ልምምድ ያስፈልጋል፡፡
ጥሩ የዜና አፃፃፍ በጥሩ ቋንቋ ሲሆን በተቻለ መጠን በአጭርና ባልተንዛዛ አቀራረብ
ይፃፋል፡፡ እንዲህ በመሆኑም ጥሩ ቋንቋ የተጠቀመ የዜና አፃፃፍ ለመረዳት በጣም ቀላል
ነው፡፡ እንዲህ ሲባል ዜና ለአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የአረዳድ ደረጃ ልኬት መፃፍ አለበት
ለማለት አይደለም፡፡ ለማለት የተፈለገው ቀጥተኛና ማራኪ መሆን (direct and
snappy) አለበት ለማለት ነው፡፡ ጥሩ የዜና ንግርት በጥሩ ቋንቋ ሲፃፍ (news story)
አንባቢዎች ወይም አድማጮች የዜናው ጭብጥ ለመረዳት ሁለት ጊዜ ወይም ከዛ በላይ
የሚያነቡት የሚጨቃጨቁት ወይም የሚነታረኩበት ዓረፍተ-ነገሮችን መያዝ የለበትም፡፡
በአጭር ቋንቋ ዜና ለመፃፍ ምንም ዓይነት ቴክኒክ ወይም ቀመር (formula) የለም፡፡
ቢሆንም ግን ይህ ለመቻል ብዙ የልምምድ ጊዜ እንደሚያስፈልግ ማናችን አንስተዉም፡፡
ስለዚህ የተመረጠና የተሳካለት ጥሩ የዜና ቋንቋ ለመጠቀም ተሞክሮ ያላቸው የጋዜጣ
ዜናዎች በተከታታይ ማንበብ ያስፈልጋል፡፡ የቃላት ምጣኔ (word economy) ማወቅም
አንዱ መፍትሄ ሊሆን ይችላል፡፡
የዜና አፃፃፍ ቋንቋ የተለየ ሕግና ቀመር ባይኖረውም ዜና ሲፃፍ ከሌላ ዓይነት የቋንቋ
ፅሁፎች መለየት እንዳለበት በማወቅ አንድ ዜና በጥሩ ቋንቋ ስንፅፍ ግምት ውስጥ
መግባት ያለባቸው እና መካተት ያለባቸው ቋንቋ አጠቃቀም ክህሎት ይኖራሉ፡፡ በዚህ
ጉዳይ ቀጥሎ በሚቀርብ የዜና አፃፃፍ ቋንቋ በአጭር መቃኛት ያቻላል፡፡ የአፃፃፍና
የመገናኛ የአሰራር ስምምነት (House Style) እንዳለ ሁኖ፡፡
50
አጭር ቃል ወይም የድርጊት ግስ መጠቀም፡፡ (የምንጠቀመው የድርጊት
ግስ ምን እንደተፈፀመ፡ እንደተከናወነ፡ እንደተሰራ የሚገልፅ መሆን
አለበት፡፡ አንድ ድርጊት ለመግለፅ ግስ (action verb) ብቻ አስፈላጊ ነው፡፡
አላስፈላጊ የድርጊት ግሶች ማስወገድ አለብን፡፡ ቃላት ለአብነት የስም ገላጭ
ወይም የድርጊት ግሶች ባልተፈለገ ቦታና ላልተፈለገ ማብራርያ መግባት
የለባቸውም፡፡ ለምሳሌ ነጭ ቀለም (white color) ነጭ በራሱ ቀለም መሆኑ
ስለ ሚታወቅ ነጭ ራሱ እንደ የስም ገላጭ ሁኖ መግባት የለበትም፡፡
ምንም ለመግለፅ ወይም ለማመልከት የገቡ ቃላት መወገድ አለባቸው፡፡
ለምሳሌ የቃላት ድግግሞሽ መኖር የለበትም፡፡ ለምሳሌ
ሀ) የኢትዮጵያ ህዝቦች ባለፉት 20 ዓመታት ድህነት
ለማሸነፍ እልህ አስጨራሽ፣ አድካሚና መራራ ትግል
አሳልፏል
ለ) የኢትዮጵያ ህዝቦች በተለያዩ ቦታዎች በንፁህ ውሃ
እጥረት ምክንያት መንከራተት፣ እንግልት፣ ላልተፈለገ
ወጪ እየተዳረገ መሆኑ አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ገለፁ
ከላይ በዜና መልክ ከቀረቡ ሁለት ፅሁፎች ተመሳሳይ ትርጉምና ግብር ያላቸው ቃላት
የመደጋገም ዕድል ታይተዋል፡፡ የቃላትና ሐረጎች አላስፈላጊ ድግግሞሽ መኖር
የለበትም፡፡ በ ‘ሀ’ ላይ ያለ የዜና ቋንቋ እልህ አስጨራሽና አድካሚ የሚሉ ሐረጎች
የትርጉምና የግብር ልዩነት የላቸዉም፡፡ በ ‘ለ’ ላይም መንከራተት፡ እንግልት አንድ
አይነት ትርጉም ያላቸው ቃላት ናቸው፡፡ ስለዚ የቃላት ድግግሞሹ ፋይዳ የለውም፡፡
1.ማን (who)
2. ምን (what)
3. መቼ (when)
4.የት (where)
5. ለምን (why)
6.እንዴት (how)
52
የነዚህ አምስት መጠይቆች አላማ በዜና መሪ አንቀፅ (lead) የእያንዳንዱ መጠይቅ
መልስ ተካትቶ እንዲቀርብና የመጠይቆች መልስ ተመልሶ እንዲፃፉ ነው፡፡ እንዲህ ሲባል
የግድ በማንም ዜና መሪ አንቀፅ የሚቀርብበት አጋጣሚ ብዙ ነው፡፡ እንደ ግዴታ
ሳይሆን እንደየ ሁኔታው ነው፡፡ አንድ መታወቅ ያለበት ጉዳይ ግን በዜና ትርጓሜ
መሰረት ከአምስቱ መጠይቆች መቅረት የሌለበትና በርዕስ ዜና በመጀመርያ መመለስ
ያለባቸው መጠይቆች ማን (who) እና ምን (what) ናቸው፡፡ የዜና አንድምታዊ ትርጉም
ምን ተሰራ፣ ተከናወነ፣ ተደረገ እና ማን ሰራው ወይም እነ ማን ሰሩት ስለሆነ ማን
(who) እና ምን (what) የግድ መመለስ ያለባቸው ሁለት ዋና መጠይቆች ናቸው፡፡
አንድ በጥሩ የዜና ቋንቋ አፃፃፍ የቀረበ አርእስተ ዜና / Headline/ በዜናው ንግርት/
Story/ ከሚሰጣቸው ጥቅሞችና አገልግሎቶች የሚከተሉት ናቸው፡፡
1. በቀኑ ምን ምን እንደተሰራ ያበስራል ስለጥቅሙም ያወሳል፡፡
2. ለአንባቢው ወይም ለአድማጩን በጣም ጠቃሚ ከሆኑ እውነታዎች እንዲመሰጥ
ያደርጋል፡፡
53
3. ለዜና ንግርት የአንድ ነገር ድርጊት አብሳሪነት በመሆን ዜና ተፈላጊ እንዲሆን
ያደርገዋል፡፡
የአርስተ ዜና ለመፃፍ ክህሎትና ተመስጦ ያስፈልጋል፡፡ የምንፅፈው የአርስተ ዜና ስለ
ዜናው ጭብጥ ወይ ንግርት ፍሬ ነገር የሚሰጥ መሆን አለበት፡፡ The headline that
we write must give the essence of the story. ስለዚህ የዜና አርእስት ሲፃፍ
የዜና ንግርት /news story/ ዋና አንኳር ሀሳብ የሚያንፀባርቅ መሆን አለበት፡፡
የተገለበጠ ፒራሚድ
አብዛኛዎቹ ዜናዎች የዜናው ዋና ጉዳይ በሆነው ነገርና ከዛሬ መቶ ዓመት በፊት ጀምሮ
በሚሰራበት አወቃቀር ይጀምራሉ፡፡ የተገለበጠው ፒራሚድ የሚባለው ይህ አወቃቀር
በጣም አስፈላጊውን መረጃ ከላይ ያስቀምጣል፡፡ እንዲሁም እንደ አወቃቀር በጣም
አስፈላጊውን መረጃ ከላይ ያስቀምጣል፡፡ እንዲሁም እንደ አስፈላጊነታቸው ቅደም
ተከተል ከላይ ወደታች ይወርዳል፡፡ የዚህ ዓይነቱ የዜና ቅርፅ ወቅታዊነት አስፈላጊ
በሚሆንበት ጊዜ ወይም ሰበር ዜናን ሲዘግቡ ጠቃሚ ነው፡፡ የአንድ ክስተት ሂደት
ለመዘገብ የመጀመሪያው ሰው ከሆንክ ለታዳሚዎቹ ምን እንደተከናወነ በዜናው
የመጀመሪያ የበላይ ጫፍ ላይ ታስታውቃቸዋለህ፡፡ ለምሳሌ ስለ ከባድ አውሎ ነፋስ
የሚሰራ ዘገባ በሞቱት ሰዎች ቁጥርና ክፉኛ ጉዳት የደረሰበትን ስፍራ በመግለፅ
ይጀምራል፡፡ የዚህን ዓይነት የዜና መዋቅር የማይቀበሉ ፀሐፊዎች “መግቢያውን ቀበሩ”
54
ተብለው ይወቀሳሉ፡፡ አቀራረባቸው ለታዳሚዎቻቸው የዜናውን ጠቀሜታ ለማግኘት
አስቸጋሪ ስለሚያደርጉት፡፡
የአውሎ ነፋስ ዘገባን በሚመለከት ፀሐፊው መጥፎ ጥፋት የደረሰበትን ስፍራ ሊገልፅ
ይችላል፡፡ ከዛ ከተረፉት ሰዎች ወይንም ከአደጋው መከላከል ሰራተኞች መካከል የአንዱን
ጥቅስን ማስፈር ይችላል፡፡ ደጋፊ አንቀፆች ርዕሱን ሊያብራሩ ይችላሉ፤ ዝርዝር ነገሮችን
በመሙላትና ስለማዕበሉ ተጨማሪ መረጃ በመስጠት፡፡ የማዕበሉ ዜና ስለ ዓለም አቀፍ
ዕርዳታ ጥረትና ለተረፉት ሰዎች ስለሚያስፈልግ የቅርብና የረጅም ጊዜ የዕርዳታ ፍላጎት
ሀሳብ ሊጨምር ይችላል፡፡ የተገለበጠ ፒራሚድ መዋቅር ዋናው ጥቅም የዜናው አዘጋጅ
ጠቃሚ ዜና ሳያጓድል ከፒራሚዱ በታች በኩል ያሉትን መረጃዎች በመቀስ መቁረጥ
መቻሉ ነው፡፡
55
የአፍሪካ ህብረት Copy slug/ የዜና
መግለጫ ወይም መለያ
ጥር 22፣ 2009
(ኤፍ.ቢ.ሲ)
የተመረጡት።
ታሪካቸው ያሳያል።
ሆነውም አገልግለዋል።
__________________________0__________________________
56
2.3.5 የሬዲዮ የዜና አፃጻፍ ፎርማቶች
ተመድ በኢትዮጵያ ለተከሰተው ድርቅ አለም አቀፍ ድርጅቶች ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠየቀ፡፡
የመንግሥታቱ ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የአየር ንብረት ለውጥን ተከትሎ በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንንን ጨምሮ የመንግሥታት ድርጅት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ
የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ኢትዮጵያ በተለይም ባለፈው ዓመት ከዓመታት በኋላ ያጋጠማትን ድርቅ በራሷ አቅም
በመመከት በሰውና በእንሰሳት ላይ ይደርስ የነበረውን ጉዳት መከላከል መቻሏ የሚወደስ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን የጎረቤት አገራት ስደተኞችን ተቀብላ ማስተናገዷ የመንግሥታቱ ድርጅቱ በአዎንታ
እንደሚያየው ነው የተናገሩት።
በተያዘው ዓመት በኦሮሚያ፣ በደቡብና በሶማሌ ክልሎች የተከሰተውን ድርቅ ለመቋቋም መንግሥት እያደረገ ካለው ጥረት
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ልማትን ማምጣት
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በበኩላቸው መንግሥት ድርቅ በተከሰተባቸው አካባቢዎች በሰውና በእንሥሳት
አገሪቷ ባለፈው ዓመት የተከሰተውን ደርቅ ለመቋቋም ከፍተኛ በጀት መድባ ከ10 ሚሊየን በላይ ዜጎችን ከድርቅ አደጋ
57
በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የተከሰተው ድርቅ በዓለም አቀፍ ደረጃ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን የተናገሩት ምክትል ጠቅላይ
ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ይህን ለመቋቋም የአረንጓዴ ልማት ኢኮኖሚን ለመገንባት እየሰራች መሆኑን ነው ያብራሩት።
በአሁን ወቅት በሀገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች የተከሰተውን ድርቅ ለመቋቋም መንግሥት 47 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር መድቦ
የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ ሲሆን ድርቁን ለመከላከል ግን 948 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር እንደሚያስፈልግም አብራርተዋል።
ሀገሪቱ ድርቅን ጨምሮ ሌሎች የተፈጥሮ አደጋዎችን ለመከላከል ለምታደርገው ጥረት የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ድጋፍ
እንደሚያስፈልጋትም አስታውቀዋል።
በተመድ የሰብዓዊ ጉዳዮች አስተባባሪ ስቴቨን ኦሪን የተመራ ቡድን በሶማሌ ክልል የሦስት ቀናት ጉብኝት በማድረግ ድርቁ
በአካባቢው መንግሥትና ሰብዓዊ ድርጅቶች ለድርቅ ተጎጂዎች ውኃ፣ ምግብና መድኃኒት እንዲሁም ለእንሥሳት መኖ
የኢትዮጵያ ህዘብና መንግሥት ድርቁን ለመቋቋም በቁርጠኝነት እየሰሩ ቢሆንም ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ከ 5 ነጥብ 6
ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ከአደጋው ለመታደግ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ድጋፍ ሊያደርህ እንደሚገባ ስቴቨን ኦሪን ተናግረዋል።
መንግሥት በድርቅ በተጠቁ አካባቢዎች ለሚኖሩ ዜጎች የከፋ ጉዳት እንዳይደርስባቸው የምግብና የቁሳቁስ ድጋፍ ከወዲሁ
እያደረገ መሆኑን ብሄራዊ የአደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽን ማስታወቁ የሚታወስ ነው።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በኢትዮጵያ ለተከሰተው ድርቅ አለም አቀፍ ድርጅቶች ድጋፍ
እንዲያደርጉ ጠየቀ፡፡ የተመድ ከፍተኛ ባለስልጣናትም ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮነን
ጋር ውይይት አካሂደዋል፡፡
58
ተመድ ጥር 22፣ 2009 (አበበ ከበደ)
የመንግሥታቱ ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የአየር ንብረት ለውጥን ተከትሎ በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንንን ጨምሮ የመንግሥታት ድርጅት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ
የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ኢትዮጵያ በተለይም ባለፈው ዓመት ከዓመታት በኋላ ያጋጠማትን ድርቅ በራሷ
አቅም በመመከት በሰውና በእንሰሳት ላይ ይደርስ የነበረውን ጉዳት መከላከል መቻሏ የሚወደስ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን የጎረቤት አገራት ስደተኞችን ተቀብላ ማስተናገዷ የመንግሥታቱ ድርጅቱ በአዎንታ
እንደሚያየው ነው የተናገሩት።
በተያዘው ዓመት በኦሮሚያ፣ በደቡብና በሶማሌ ክልሎች የተከሰተውን ድርቅ ለመቋቋም መንግሥት እያደረገ ካለው
ጥረት ባሻገር የዓለም አቀፉ ማህብረሰብ ድጋፍ እንዲያደርግ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ጠይቀዋል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ልማትን ማምጣት
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በበኩላቸው መንግሥት ድርቅ በተከሰተባቸው አካባቢዎች በሰውና
በእንሥሳት ላይ ጉዳት እንዳይደርስ የአጭርና የረጅም ጊዜ ዕቅድ አውጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
አገሪቷ ባለፈው ዓመት የተከሰተውን ደርቅ ለመቋቋም ከፍተኛ በጀት መድባ ከ10 ሚሊየን በላይ ዜጎችን ከድርቅ አደጋ
በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የተከሰተው ድርቅ በዓለም አቀፍ ደረጃ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን የተናገሩት ምክትል
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ይህን ለመቋቋም የአረንጓዴ ልማት ኢኮኖሚን ለመገንባት እየሰራች መሆኑን ነው
ያብራሩት።
በአሁን ወቅት በሀገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች የተከሰተውን ድርቅ ለመቋቋም መንግሥት 47 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር
መድቦ የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ ሲሆን ድርቁን ለመከላከል ግን 948 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር እንደሚያስፈልግም
አብራርተዋል።
59
ሀገሪቱ ድርቅን ጨምሮ ሌሎች የተፈጥሮ አደጋዎችን ለመከላከል ለምታደርገው ጥረት የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ድጋፍ
እንደሚያስፈልጋትም አስታውቀዋል።
በተመድ የሰብዓዊ ጉዳዮች አስተባባሪ ስቴቨን ኦሪን የተመራ ቡድን በሶማሌ ክልል የሦስት ቀናት ጉብኝት በማድረግ
በአካባቢው መንግሥትና ሰብዓዊ ድርጅቶች ለድርቅ ተጎጂዎች ውኃ፣ ምግብና መድኃኒት እንዲሁም ለእንሥሳት መኖ
የኢትዮጵያ ህዘብና መንግሥት ድርቁን ለመቋቋም በቁርጠኝነት እየሰሩ ቢሆንም ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ከ 5 ነጥብ 6
ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ከአደጋው ለመታደግ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ድጋፍ ሊያደርህ እንደሚገባ ስቴቨን ኦሪን
ተናግረዋል።
መንግሥት በድርቅ በተጠቁ አካባቢዎች ለሚኖሩ ዜጎች የከፋ ጉዳት እንዳይደርስባቸው የምግብና የቁሳቁስ ድጋፍ
ከወዲሁ እያደረገ መሆኑን ብሄራዊ የአደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽን ማስታወቁ የሚታወስ ነው።
ኬንያ ፣
ጥር 22/ 2009
ቢቢሲ
ኬንያውያኑ ጥንዶች ጋብቻቸውን ለመፈፀም ለሚካሄደው የሰርግ ስነስርዓት አንድ የአሜሪካ ዶላርን ብቻ
ዊልሰን እና አን ሙቱራ በፈረንጆች 2016 ሊጋቡ ቀን ቆርጠው ሁለት ጊዜ አራዝመውታል፤ ምክንያቱም እስከ
በመሆኑም ዊልሰን እና አን ሙቱራ የሰርጋቸውን እለት በዚህኛው ዓመት ቀለል ባለ መልኩ ለማድረግ
ወስነዋል።
ሙሽሪት አን በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ አስመልክታ ገንዘብና ጋብቻ መተሳሰር የለባቸውም ብላለች፡፡
60
የአና ድምፅ (10 ሴኮ.)
"ጋብቻን በገንዘብ ሳይሆን በእርስ በእርስ መዋደድ እና መተሳሰብ መመስረት ልዩ ፀጋ ነው" ፡፡
ይህን ያደረጉት ጥንዶቹ በአንድ ዶላር የተከናወነው የሰርግ ስነስርዓት በሚል በማህበራዊ ድረገጾች የሰርክ
ውሉን ለሚመለከተው የመንግስት ተቋም ለማሳወቅ ክፍያን ስለሚጠይቅ፥ እነሱም ወጪውን መሸፈን
ስለማይችሉ ነው፡፡
እንዲህ ያለው የ27 ዓመቱ የዊልሰን እና የ24 ዓመቷ የአን የፍቅር ታሪክ የበርካታ ማህበራዊ የትስስር ገጽ
ከሶስት ዓመት የፍቅር ግንኙነት በኋላ በገንዘብ ምክንያት ሰርጋቸውን በወጉ ያላደረጉት ሁለቱ ጥንዶች፥
ሰርጋቸውም ድግስ ሳይደገስ፣ ኬክ ሳይቆረስ፣ ያለምንም የሰርግ ጌጣጌጥ እና አበባ፣ በናይሮቢ ተደርጓል፡፡
አለባበሳቸውም የተለመደ ጂንስ ሱሪ፣ ቲሸርት እና መደበኛ ጫማ ሲሆን፥ ሰርግ የሚያስመስለው ነገር ቢኖር
በቤተክርስቲያን ውስጥ ሰርጉ ሊፈጸም በነበረበት ወቅትም ዊልሰን ሁለቱን በአነስተኛ ዋጋ የሚሸጡ የብረት
በማህበራዊ ድረገጽ የተለቀቀውን የሁለቱን ጥንዶች ነገረ ጋብቻ የተመለከቱ እና ፀጋው ያላቸው ሁሉ
ስጦታቸውን እየላኩላቸው ሲሆን፥ አንድ የጉዞ ድርጅትም የአምስት ቀን የጫጉላ ሽርሽር እንዲያደርጉ ሙሉ
61
ኬንያ ፣
ጥር 22/ 2009
ቢቢሲ
ኬንያውያኑ ጥንዶች ጋብቻቸውን ለመፈፀም ለሚካሄደው የሰርግ ስነስርዓት አንድ የአሜሪካ ዶላርን ብቻ
ኬንያ ፣
ጥር 22/ 2009
አስቴር ተሾመ (ቢቢሲ)
ዊልሰን እና አን ሙቱራ በፈረንጆች 2016 ሊጋቡ ቀን ቆርጠው ሁለት ጊዜ አራዝመውታል፤ ምክንያቱም እስከ
በመሆኑም ዊልሰን እና አን ሙቱራ የሰርጋቸውን እለት በዚህኛው ዓመት ቀለል ባለ መልኩ ለማድረግ
ወስነዋል።
ሙሽሪት አን በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ አስመልክታ ገንዘብና ጋብቻ መተሳሰር የለባቸውም ብላለች፡፡
ውሉን ለሚመለከተው የመንግስት ተቋም ለማሳወቅ ክፍያን ስለሚጠይቅ፥ እነሱም ወጪውን መሸፈን
ስለማይችሉ ነው፡፡
እንዲህ ያለው የ27 ዓመቱ የዊልሰን እና የ24 ዓመቷ የአን የፍቅር ታሪክ የበርካታ ማህበራዊ የትስስር ገጽ
62
ከሶስት ዓመት የፍቅር ግንኙነት በኋላ በገንዘብ ምክንያት ሰርጋቸውን በወጉ ያላደረጉት ሁለቱ ጥንዶች፥
ሰርጋቸውም ድግስ ሳይደገስ፣ ኬክ ሳይቆረስ፣ ያለምንም የሰርግ ጌጣጌጥ እና አበባ፣ በናይሮቢ ተደርጓል፡፡
አለባበሳቸውም የተለመደ ጂንስ ሱሪ፣ ቲሸርት እና መደበኛ ጫማ ሲሆን፥ ሰርግ የሚያስመስለው ነገር ቢኖር
በቤተክርስቲያን ውስጥ ሰርጉ ሊፈጸም በነበረበት ወቅትም ዊልሰን ሁለቱን በአነስተኛ ዋጋ የሚሸጡ የብረት
በማህበራዊ ድረገጽ የተለቀቀውን የሁለቱን ጥንዶች ነገረ ጋብቻ የተመለከቱ እና ፀጋው ያላቸው ሁሉ
ስጦታቸውን እየላኩላቸው ሲሆን፥ አንድ የጉዞ ድርጅትም የአምስት ቀን የጫጉላ ሽርሽር እንዲያደርጉ ሙሉ
--------------------0----------
63
የተወሳሰቡ ቁጥሮችን በአሃዝና በማጠጋጋት ግልጽ ማድረግ
በአንድ ገፅ የማያልቁ ዜናዎችን ምልክት ማስቀመጥ
ዜናው ማለቁን የሚገልጽ ምልክት ማስቀመጥ
በመስመሮች መካከል ያለውን ቦታ ለዓይን ምቹ እንዲሆን 2 ማድረግ
ዜናዎችን በተገቢው ቅደም ተከተል ማስቀመጥ
ማጠቃለያ
64
3. የሬዲዮ ፕሮግራም
1. የማሳወቂያ ፕሮግራም
2. የማስተማሪያ ፕሮግራም እና
3. የመዝናኛ ፕሮግራም ናቸው፡፡
66
የሚፈጥሩ የሬዲዮ ፕሮግራሞች ሲሆኑ በዋናነት አድማጮች ጊዜያቸውን ለፕሮግራሙ
ለመስጠት መዝናናትን በመፍጠር ዘና እያሉ የማህበረሰባዊ ጉደዮችን የሚያከናውኑበትን
ምቹ ሁኔታ መፍጠር የሚችል የሬዲዮ ተወዳጅ ፕሮግራም ነው፡፡ ይህ ፕሮግራም
ለአድማጮች የሚከተሉት ገጸ በረከቶች ያበረክታል፡፡
ደስታን ይሰጣል፣
ከጭንቀትና ከድካም ይገላግላል፣
ተሳትፎን ያበረታታል፣
ልምድን ያሰፋል፣
የባህል ተግዳሮቶችን ያጠፋል/ከተግዳሮቶች ባሻገር ያለውን እንዲታሰብ
ያደርጋል፣
የውይይት አጀንዳዎችን እንዲቀረፁ ያስችላል፣
የማህበረሰብ አገልግሎትን የሚያሳድጉ የጋራ ተሞክሮን ያቀርባል፣
የተግባቦትና የጠያቂነት ክህሎትን ያዳብራል፣
ሌላ ወጭ የሚበዛባቸውን የመዝናኛ መንገዶች በማስቀየር አማራጭ ይሆናል፣
የሌሎችን ባህል ያስተምራል፡፡
የውይይት ጥያቄዎች
አንድ የሬዲዮ ፕሮግራም ፕሮግራም ሊያሰኙት የሚችሉ የራሱ የሆኑ ባህርያት አሉት፡፡
እነዚህም ባህርያት፡-
67
የተለየ የፕሮግራም መክፈቻ ወይም መለያ ሙዚቃ (signature tune/ Jingle)
የታወቀና ሙሉ ሃላፊነት የሚወስድ አዘጋጅ እና
ለየት ያለ የራሱ የይዘት አቀራረብ ያለው
የውይይት ጥያቄዎች
68
3.4.1 የቅድመ-ዝግጅት ምዕራፍ
1. ዓላማውን መለየት
69
በአጠቃላይ የአድማጮችን ባህርይና ፍላጎት የበለጠ በታወቀ ቁጥር የሬዲዮ ፕሮግራሙ
ለአድማጮች የሚሰጠው ጥቅም ከፍተኛ ነው፡፡
3. ማቀድና መበጀት
70
በሬዲዮ ፕሮግራም ዝግጅት ላይ የዕቅድ ሥራ ውስጥ ሊካተቱ የሚገባቸው ግብዓቶች
የሚሆኑት መረጃ፣ ሰዎች፣ መሳሪያዎች፣ ጊዜና በጀት ናቸው፡፡ በጀት ስንል
ለፕሮግራሙ የሚያስፈልግ አጠቃላይ የማቴሪያልና የገንዘብ መጠንን ያጠቃልላል፡፡
4. ፎርማትን መምረጥ
5. ስክርፕት መጻፍ
71
የምንጠቀምባቸው ዓረፍተ ነገሮች አጭር መሆን ይኖርባቸዋል፤ ተከታታይ
አጭር ግን አይሆኑም ምክንያቱም ግጥም ነው የሚመስሉት፤
የምንጠቀምባቸው ዓረፍተ ነገሮች ቀላል መሆን አለባቸው፣
የምንጠቀምባቸው ዓረፍተ ነገሮች ግልጽና ቀጥተኛ ሊሆኑ ይገባል፤
የተወሳሰቡ ለአነባብ አስቸጋሪና ለአድማጭ ግልጽ ያልሆኑ ቁጥሮችን
ማጠጋጋትና በአሃዝ መፃፍ፣
በአዕምሮ ውስጥ ምስል መሳል፤
ፅሁፍን ለአንድ ሰው እንደማውራት መፃፍ
6. ተሰጥዖና ድምፅ መረጣ
ተሰጥዖ ያላቸውን አንባቢዎች መምረጥ የቅድመ ዝግጅት ምዕራፍ አንዱ ተግባር ሲሆን
በዋናነት የሚከተሉት ብቃትና ተሰጥዖ ያሏቸውን አንባቢዎች ማግኘት ደግሞ
የፕሮግራሙን አቀራረብ ውጤታማ ያደርገዋል፡፡
ጥሩ የኮሚዩኒኬሽን ክህሎት
ስሜትን የመግለፅ ብቃት
በራስ መተማመን
የጊዜ አጠቃቀም
የፅሁፍን ውስጠት የመረዳትና በተረዱት መጠን የማቅረብ ብቃት
ልምድ
72
3.4.2 የዝግጅት ምዕራፍ
73
3.4.1 የድህረ ዝግጅት ምዕራፍ
ዋናው የሥቱዲዮ የቀረጻ ፕሮግራም ከተጠናቀቀ በኋላ ያለውን ጊዜ ያጠቃልላል፡፡ በዚህ ምዕራፍ
ውስጥ የኤዲቲንግና የሥርጭት ሥራዎች ይከናወናሉ፡፡ ኤዲቲንግ ማለት አንድ የተቀረጸን
ድምፅ ውስጥ አስፈላጊ ያልሆኑትን የማስወገድ፣ አስፈላጊ ድምጾችን ደግሞ የማስገባትና
ቦታቸውን የማስተካከል ሂደት ነው፡፡ ኤዲቲንግ ሲሰራ የሚከተሉት ጥቅሞች አሉት፡፡
የተቀረፀው ድምፅ በትክክል ለማስቀመጥ/ ለማስተካከል፤
የሚያስፈልጉ ወይም የቴክኒክ ብልሽት ያለባቸውን ድምፆች ለማጋድ፣
የፕሮግራሙን ግብዓቶች ከፕሮግራሙ ሰዓት ጋር ለማጣጣም፣
ሙዚቃና የድምፅ ኢፌክቶችን ለመጨመር
ማጠቃለያ
አንድን የሬዲዮ ፕሮግራም ከቅድመ ዝግጅት (ፕሮፖዛል ቀረፃ) እስከ ድህረ ዝግጅት የሚከናወኑ
ተግባራትን መለየት ለአንድ የፕሮግራም አዘጋጅ ወሳኝ ሆኑ ፋይዳዎች አሉት፡፡ ምክንያቱም
የሬዲዮ ፕሮግራም በሚዘጋጅበት ጊዜ ስኬታማነቱ የሚወሰነው በየምዕራፉ በምናከናውናቸው
ተግባራት ነው፡፡ ስለሆነም በየአንዳንዱ ምዕራፍ የምንሰራቸው ሥራዎች ጥራታቸውን የጠበቁና
ሙያውን ያማከሉ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
74
ዋቢ መፅሐፍት
75
“የምሁራን ጨዋታ”
(የሬዲዮ ፕሮግራም ትልም)
76
ማውጫ
ይዘት ገፅ
1. .............................................................................................................................................. መግቢያ
..................................................................................................................................... 78
2. ............................................................................................................. የፕሮግራሙ አጠቃላይ መግለጫ
..................................................................................................................................... 79
2.1 ስያሜ ....................................................................................................................................... 79
2.2 ዓላማ ...................................................................................................................................... 79
2.3 አድማስ .................................................................................................................................... 79
2.4 አዘጋጆች................................................................................................................................... 80
5 የሚቀርብበት ቋንቋ ....................................................................................................................... 80
2.6 ርዝመት (ቆይታ) ......................................................................................................................... 80
2.7 መቼት ..................................................................................................................................... 80
2.8 ይዘት ....................................................................................................................................... 80
2.8.1 የምሁራን ትንታኔ .................................................................................................................. 80
2.8.2 የሙዚቃ ግብዣ .................................................................................................................. 81
2.8.3 የአድማጮች ጥያቄ................................................................................................................ 81
2.8.4 ጥያቄና መልስ .......................................................................................................................... 81
3. አቀራረብ ....................................................................................................................... 81
4. የፕሮግራሙ ጊዜያዊ የጨዋታ አጀንዳዎች .................................................................................. 83
5. ........................................................................................................................... የሚያስፈልጉ ግብዓቶች
..................................................................................................................................... 84
5.1 የሰው ሃይል ................................................................................................................................ 84
5.2 ቁሳቁስ ..................................................................................................................................... 84
5.3 ገንዘብ ...................................................................................................................................... 85
6......................................................................................................................... የገንዘብ ማግኛ መንገዶች
..................................................................................................................................... 85
7. ......................................................................................................... የፕሮግራሙ ማስተዋወቂያ መንገዶች
..................................................................................................................................... 85
77
መግቢያ
የብዙሃን መገናኛ እንደወግ ይከተሏቸው የነበሩ ንድፈ ሃሳቦች በአብዛኛው የብዙሃን መገናኛ
ከመንግስት ጋር ባላቸው ግንኙነት ላይ መሠረት ያደረጉ ነበሩ፡፡ ይህ አስተሳሰብ ከጊዜ ወደ ጊዜ
እየተቀየረ መጥቶ ህዝብን መሠረት ያደረጉ፤ የመረጃ ፍሰታቸውን ከህዝብ ወደ ህዝብ በማድረግ
ትኩረታቸውን ህዝብ ላይ ያደረጉ ንድፈ ሃሳቦች እየቀረቡ ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህ ንድፈ ሃሳቦች
አንዱ የሆነው የልማታዊ ጋዜጠኝነት ንድፈ ሃሳብ ደግሞ በሶስተኛው ዓለም ላለው የሚድያ
ተቋም ምርጥ ፍልስፍና በመሆን ድምፅ አልባ ለነበሩት ዜጎች ድምፅ በመሆን አማራጭ የመረጃ
ማግኛና ማስተላለፊያ መንገዶችን በማቅረብ ሚናውን እየተጫወተ ነው፡፡ በዚህ ፍልስፍና ውስጥ
ሚዲያ የህዝብ ወገን በመሆን የልማቱ ተጠቃሚ የሆነውን ሰፊ ህዝብ የማገልገል ሚና
ይጫወታል፡፡ ህዝቡ በራሱ አንደበት ለራሱ መናገር የሚችልበት ሁኔታ እያመቻቸ የሚሄድ
የብዙሃን መገናኛ ንድፈ ሃሳብ ልማታዊ ጋዜጠኝነት ነው፡፡ ልማታዊ ጋዜጠኝነት በታዳጊ አገራት
ህዝቦችን ንቃተ ህሌናቸውን በማሳደግ ለልማት እና ለዲሞክራሲያዊ ግንባታ የሚያበረክተው
አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው፡፡
78
ይህ የማህበረሰብ ሬዲዮ የማህበረሰቡ ድምፅ እንደመሆኑ መጠን ማህበረሰቡን ያሳተፉ
ፕሮግራሞችን በራሳቸው የማህበረሰቡ አባላት በመጠቀም ማከናወን ወሳኝ ሚና እንዳለው
ይታመናል፡፡ ስለሆነም የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው
የማህበረሰብ ሬዲዮ የአየር ሰዓት ወስደው ፕሮግራም መስራት አስፈላጊ እንደሆነ ስለታመነበት
ይህ “የምሁራን ጨዋታ” የተሰኘ የሬዲዮ ፕሮግራም ትልም ቀርቧል፡፡
በዚህ ትልመ ሃሳብ ውስጥ ስለፕሮግራሙ አጠቃላይ መግለጫ ማለትም ስያሜ፣ ዓላማ፣
አድማስ፣ አዘጋጅ፣ ቋንቋ፣ ርዝመት (ቆይታ)፣ መቼት፣ ይዘት እና አቀራረብ እንዲሁም
ለፕሮግራሙ አስፈላጊ የሆኑ ዋና ዋና የቁሳቁስና የገንዘብ ግብዓቶች ቀርበዋል፡፡
2.1 ስያሜ
የዚህ ፕሮግራም ስያሜ “የምሁራን ጨዋታ” ይሰኛል፡፡ የምሁራን ጨዋታ ከሌላው ዜጋ ጨዋታ
የተለየ ሲሆን በዋናነት የንድፈ ሃሳብና የተሞክሮ ተኮር ጨዋታዎች ይገኙበታል፡፡ የዚህ ስያሜ
የተሰጠው ፕሮግራሙ በውስጡ ከሚሰራቸው የጨዋታ አርዕስቶች ወይም የጨዋታ አጀንዳና
የተጫዋቾች የጨዋታ ሥርዓት አንፃር የሚዘጋጅ ስለሆነ ነው፡፡
2.2 ዓላማ
ይህ ፕሮግራም ዓቢይና ንዑስ ዓላማዎች አሉት፡፡ የፕሮግራሙ ዓበይት ዓላማ ለደብረ ማርቆስ
ዩኒቨርሲቲና የአካባቢው ማህበረሰብ መረጃ የመስጠት፣ ማስተማርና ማሳወቅ ነው፡፡ ይህም
ሲተነተን የሚከተሉትን ንዑስ ዓላማዎችን የያዘ ይሆናል፡፡
2.3 አድማስ
79
አካላት ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ሲሆን ዓለም ዓቀፍ የሆኑ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ወቅታዊ
ጉዳዮችም በምሁራን ጨዋታ ፕሮግራም አድማስ ውስጥ ይዳሰሳሉ፡፡
2.4 አዘጋጆች
ሀ) ዋና አዘጋጅ፡-
ለ) ተባባሪ አዘጋጆች፡-
5 የሚቀርብበት ቋንቋ
የምሁራን ጨዋታ ፕሮግራም በሳምንት አንድ ቀን ለአንድ ሰዓት የሚቆይ ፕሮግራም ነው፡፡
ስለዚህ የፕሮግራሙ አጠቃላይ 1 (አንድ) ሰዓት የአየር ላይ ቆይታ ይኖረዋል፡፡ የዚህ ፕሮግራም
በየንዑስ ፕሮግራሞች ተከፋፍሎ በአቀራረብ ላይ ቀርቧል፡፡
2.7 መቼት
ዘወትር ማክሰኞ ከምሽቱ 11፡00 ጀምሮ እስከ 12፡00 በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲና የአካባቢው
ማህበረሰብ ሬዲዮ ኤፍ ኤም 97.7 የሚተላለፍ ፕሮግራም ነው፡፡
2.8 ይዘት
80
በአገራችን፣ በአህጉራችንና በመላው ዓለም የተከናወኑትና የብዙሃን መገናኛዎችን ቀልብ መሳብ
የቻሉ ጉዳዮች ከምሁራን ሙያዊ ትንታኔ በመስጠት መጨዋወት፡፡
በዚህ ንዑስ ፕሮግራም የተለያዩ የጠቅላላ ዕውቀት ጥያቄዎች እየቀረቡ ቀድመው ለሚመልሱ
አድማጮች በየሳምንቱ የተለያዩ ሽልማቶች የሚያበረክት ሲሆን የዩኒቨርሲቲውና የአካባቢው
ማህበረሰብ ጠቅላላ ዕውቀት ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል፡፡
3. አቀራረብ
81
11፡05-11፡08 የጨዋታ አጀንዳ የዕለቱን የጨዋታ አጀንዳ ከዓለም አቀፍ እስከ አካባቢ
ያለበትን ሁኔታ በመግለጽ የጨዋታውን ፈር ማስያዝ፣
በአካሄዱ ላይ መነጋገር
82
4. የፕሮግራሙ ጊዜያዊ የጨዋታ አጀንዳዎች
2 የትምህርት ጥራት
5 ባህልና ወግ
6 የማህበረሰብ ጤና
8 የግብርና ዘመናዊነት
9 የኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች
12 የከተሞች ዘመናዊነት
83
የሚያስፈልጉ ግብዓቶች
84
5.3 ገንዘብ
ለዚህ ፕሮግራም ወጪ ሊሸፍን የሚችል ገንዘብ በተለያየ መንገድ ማግኘት የሚቻል ሲሆን
የሚከተሉትን አማራጮች የፕሮግራሙ አዘጋጆች ሊጠቀሙባቸው ይችላሉ፡፡
ከሬዲዮ ጣቢያው
በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ካሉ የሥራ ሂደቶች ስፖንሰር በመጠየቅ፣
ከውጭ አካላት ስፖንሰር በመጠየቅ፣
በማህበረሰብ ሬዲዮ
በውስጥ ማስታወቂያ
በበራሪ ፅሁፎች አማካኝነት ለአድማጮች የማስተዋወቅ ሥራ ይሰራል፡፡
85