Professional Documents
Culture Documents
Ethiopian Reporter Amharic
Ethiopian Reporter Amharic
Ethiopian Reporter Amharic
(https://www.facebook.com/EThReporter/) (https://twitter.com/ethioreporter)
(https://www.linkedin.com/in/%E1%88%AA%E1%8D%96%E1%88%AD%E1%89%B0%E1%88%AD-
%E1%88%AA%E1%8D%96%E1%88%AD%E1%89%B0%E1%88%AD-12341514)
(/)
(https://metropolitanaddis.com/)
መነሻ ገጽ (/index.php/) / እኔ የምለዉ (/index.php/ine-yemilewu) / የሲዳማ የፖለቲካ ኃይሎች አሠላለፍና የመንፃት አስተሳሰብ ፈተና
እኔ የምለዉ (/INDEX.PHP/INE-YEMILEWU)
በሀላሌ ሲዳማ
የሲዳማ ብሔር አሁን በሚኖርበት አካባቢ የሰፈረው በ16ኛው ክፍለ ዘመን እንደነበረ የተለያዩ ጸሐፊዎች ያነሳሉ (Brogger 1986፣ 26፣ Hamer
1987፣ Braukamper 1977, Haileyesus Seba 2003)። የሲዳማ ብሔር በዚህ አካባቢ ከሠፈረበት ጊዜ ጀምሮ በአካባቢው ከነበሩ ሌሎች
ማኅበረሰቦች ጋር መልካም ግንኙነት ነበረው። ሆኖም በ17ኛው ክፍለ ዘመን የራሱን የአስተዳደርና የአምልኮ ሥርዓት ለማከናወን በተደጋጋሚ
ሙከራ ቢያደርግም፣ በአከባቢው ይኖሩ የነበሩ ማኅበረሰቦች አዎንታዊ ምላሽ ባለመስጠታቸው ምክንያት ወደ ትግል ሊገባ ተገልዷል።
ባደረገው ትግልም በአሸናፊነት በመውጣት የራሱን የአስተዳደር ሥርዓት መመሥረቱ ይነገራል (ቤታና ሆጤሳ 2013፣ 63)።
በዚያን ጊዜ በትግሉ ግንባር ቀደም ነን ያሉና ትውልዳቸውን ከቡሼ የዘር ሐረግ የሚመዙት የሼቤዲኖ፣ ያናሴ፣ ዊጋ፣ ማልጋ፣ ሆሎ፣ ጋርብቾና
ሃርቤጎና ጎሳዎች “የመሬቾ” የተባለና በአንጋ (Anga) የመንፃት (Wolapho) ፍልስፍና የሚመራ የባህል፣ የሃይማኖትና የአስተዳደር ሥርዓት
እንደ መሠረቱ ይነገራል (Hamer 1987፣ 32)። በዚህ ሥርዓት ያልታቀፉ “የአለታ” ቡድን አባላት ይህን አደረጃጀት ተቃውመው የተሠለፉ ሲሆን፣
በሁለቱም ቡድን ያልተሳተፉ ሌሎች የሲዳማ ጎሳዎች በሦስተኛ ቡድንነት በመፈረጃቸው ምክንያት፣ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ በሲዳማ ውስጥ የሦስት
ቡድኖች ክፍፍል እንደ ተመሠረተ ይነገራል።
የየመሬቾ ኃይል በሲዳማ ውስጥ የባህል፣ የሃይማኖትና የአስተዳደር ሥርዓት ላይ ከፍተኛ ሚና የነበረው ቢሆንም በአለታ ቡድን ሊሸነፍ ችሏል።
ይህም ለሁለቱም ቡድኖች መፍረስና በፍልስፍናው ስም ለሚጠራ የወላዊቾ (Wolawichcho) ቡድን መመሥረት ምክንያት በመሆን የኃይል
አሠላለፉን ከሦስት ወደ ሁለት ማውረድ እንዳስቻለ ይነገራል። በዚህ መሠረት ወላዊቾ (Wolawichcho) ቡድን የገዥነቱን ቦታ ሲረከብ ሌሎች
የሲዳማ ጎሳዎች የተገዥነት ደረጃ እንዲይዙ ተደርጓል (Hamer 1987፣ 32)።
https://www.ethiopianreporter.com/index.php/article/18166?fbclid=IwAR08d0-BDwXcf3wT8BGBdIHD-zVa51X2TSLuo_di9KErGjry05l12FDTWfY 1/10
24/02/2020 የሲዳማ የፖለቲካ ኃይሎች አሠላለፍና የመንፃት አስተሳሰብ ፈተና | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharic
በዚህ መሠረት የመሬቾ ቡድን ጎሳዎች ቀደም ብሎ ሲዳማ በሠፈረበት አከባቢ ይኖር የነበረ የሆፋ ማኅበረሰብ መሸነፍ በኋላ የተገኘውን መሬት
ለራሳቸው የተከፋፈሉ ሲሆን፣ በኋላ ወደ ጥምረቱ የተቀላቀለው ወገን (በአለታ ስም የተሰየመው) ጋር እኩል የሲዳማ የአምልኮና የባህል ሥርዓት
(ለሞቱት ቅድመ አያቶች የሚቀርብ መስዋዕት “Xorishi’ra” ሥነ ሥርዓት) አስፈጻሚ መሆን ችለዋል። የአስተዳደር ሥርዓቱ ሁሉንም ጎሳ በጋራ
ማስተባበር ባይችልም፣ እያንዳንዱ ጎሳ የራሱ ሞቴ እንዲኖረው አድርጓል። የጎሳው የአስተዳደር ሥርዓት የሚመራው በሞቴ (Moote) ሲሆን፣
ቀጥሎ ያለው በምክትል (Ja’laawa) እና አስተዳዳሪ (Gashsho) ነበር።
በዚህ መሠረት የሲዳማ ባህላዊ አስተዳደር የፖለቲካ መዘውሩ ከ17ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በወላዊቾ ቡድን ስም በጋራ የሚመራ ሲሆን፣ ከዚህ
የሚለዩ ጉዳዮች ሲያጋጥሙም በመሬቾ የገዥ ቡድን ይዘወሩ ነበር። በዚህ ጽሑፍ በዋነኛነት ለመመልከት የተፈለገው የዚህን ቡድን ታሪካዊ
አመጣጥ ሳይሆን፣ ይህ ቡድን በሲዳማ ፖለቲካ ላይ ያለውን ሚናና በመልካም አስተዳደር ሥርዓት ግንባታ ላይ እያደረሰ ያለውን አሉታዊ
አስተዋጽኦ ነው።
ይህ ቡድን ከ19ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በአሁኑ ጊዜ በሲዳማ ውስጥ የሚታዩትን ሃይማኖታዊ፣ ባህላዊና አስተዳደራዊ (ፖለቲካዊ) ሥርዓቶችን
ተግባራዊ ሲያደርግ የቆየ ነው። የሥርዓቱ ፍልስፍና መነሻ የሚያደርገው “የአንጋ” (Anga) ሥርዓት ሲሆን፣ አንጋ ማለት የመንፃት ሥርዓት ነው።
ፍልስፍናው የየመሬቾ ምሥረታን ተከትሎ የተገኘውን መሬት ንፁህ ለተባሉ (Wolawichcho) ጎሳዎች ያከፋፈለ ሲሆን፣ በኋላም መሬት ብቻ
ሳይሆን የሃይማኖትና ባህላዊ ሥርዓቱም በእነዚሁ ጎሳዎች ብቻ እንዲመራ የሚያስገድድ ነበር።
ይህ ፍልስፍና በሒደት ወደ ባህላዊ አስተዳደር አድጎ የእያንዳንዱ ንፁህ ጎሳ የአስተዳደር ሥርዓት በዚሁ ፍልስፍና እንዲቃኝ አድርጓል። በኋላም
የተመሠረተው የወላዊቾ ቡድን ስያሜውን የወሰደው ከራሱ መንፃት (Wolapho) ከሚለው ከሲዳምኛ ቃል ሲሆን፣ በዚህ ፍልስፍና ራሱን በአዲስ
መልክ እንዲያደራጅ ተደርጓል።
ሆኖም ይህ የወላዊቾ (Wolawichcho) ባህላዊ የአስተዳደር ሥርዓት ከ20ኛው ክፍለ ዘመን በኋላ፣ ከዚህ በፊት እንደነበረው መቀጠል
አልቻለም። ምክንያቱም የመሬት ባለቤት የነበረው ወላዊቾ ቡድን መሬቱ እየተቀማ ለምኒልክ ጦር አበጋዞች በመሰጠቱና በኋላም በንጉሡ
ሥርዓት መሬት በፊውዳሉ እጅ በመውደቁ ምክንያት ወላዊቾ የነበረውን ገዥነት አጥቶ፣ እንደ ሌሎቹ የሲዳማ ጎሳዎች ጭሰኛ እንዲሆን
አስገድዶታል።
የመንፃት አስተሳሰብ በሲአን (ሲዳማ አርነት ንቅናቄ)
የፊውዳል ሥርዓት ጭቆና እየበዛ በመጣበት ወቅት የሲዳማ ሕዝብ አዲስ የትግል ሥልት ነድፎ ወደ ትግል እንዲገባ አድርጎታል። በዚህም
መሠረት ‹‹ሲዳማ አርነት ንቅናቄ›› (Sidaamu Wolaphote Millimmo) በሚል የፖለቲካ ፓርቲ መሥርቶ ወደ ትግል እንደገባ ይነገራል።
ንቅናቄው በደርግ ዘመን በዚህ ስያሜ ለበርካታ ዓመታት ትግል ሲያደርግ የቆየ ሲሆን፣ ከ1983 ዓ.ም. ጀምሮ አገር ውስጥ ገብቶ በመታገል ላይ
ይገኛል።
በዋነኛነት ለመመልከት የተፈለገው የፖለቲካ ፓርቲ መመሥረትን ሳይሆን የፓርቲውን ስያሜ ነው። ከስሙ እንደምንረዳው “Wolapho” ወይም
“መንፃት” የሚል ስያሜ የሲዳማን ነፃነት ለማረጋገጥ የሚደረግ ትግል አይመስልም። ይህ ስያሜ ከላይ እንዳነሳነው የሲዳማ ገዥው ኃይል
የነበረው የመሬቾ ቡድን ከሆፋ መሸነፍ በኋላ የተገኘውን መሬት በብቸኝነት ለመቆጣጠር፣ ሲዳማን በሦስት ቦታ ለመክፈል የፈለሰፈውን የአንጋ
ሥርዓት ለማስፈጸም የተጠቀመው ስያሜ ነው። ይህንን የመሬቾ ፈርሶ ወደ ወላዊቾ ሲቀየር በቀጥታ የአንጋ ሥርዓት ማስፈጸሚያ የነበረውን
የነፁ (Wolapho) የሚል ስም በመውሰድ ያቋቋመው የቡድኑ መጠሪያ የነፁ (Wolawicho) የሚል ነበር። በዚህ መሠረት መንፃት (Wolapho)
የሚለው ስያሜ በቀጥታ የሚገናኘው የሲዳማ ብሔር ከባርነት ማላቀቅ ወይም ከአርነት ማውጣት ሳይሆን ይህንን የየመሬቾ/የወላዊቾ ቡድን
ፍልስፍናን መልሶ ለማረጋገጥ የሚደረግ ትግል መሆኑን ነው።
በዚህ በመንፃት (Wolapho) ስያሜ ባለፉት 27 ዓመታት በሲዳማ ውስጥ መንግሥት ለመመሥረት ከፍተኛ ጥረት የተደረገ ቢሆንም ሊሳካ
አልቻለም። ሲአን በሲዳማ ሥልጣን እንዳይዝ ካደረጉት ምክንያቶች አንዱ ፓርቲው የሚከተለው ርዕዮተ ዓለም መነሻ ነው። ከስሙ
እንደምንረዳው መንፃት (Wolapho) የሚለው ስያሜ የመላው ሲዳማ ሕዝብ ሳይሆን፣ ከዚህ በፊት ከ17ኛ ክፍለ ዘመን ጀምሮ እስከ 20ኛው
ክፍለ ዘመን የተሸጋገረና ሲዳማን ሦስት ቦታ የከፈለ የየመሬቾ ቡድን አስተሳሰብ በመሆኑ ነው። በዚህ መሠረት ኢሕአዴግ አገሪቱን ከተቆጣጠረ
በኋላ ይህ አስተሳሰብ በሲዳማ ውስጥ ጎልቶ በመምጣቱ፣ መላው የሲዳማ ሕዝብ ባደረገው ጥረት ፓርቲው ሲዳማን መምራት ሳይችል
ቀርቷል።
በአሁኑ ጊዜ የተለያዩ አጋጣሚዎችን በመጠቀም ሲዳማን ለማሳመንና ወደ ሥልጣን መጥተው ርዕዮተ ዓለማቸውን ለማስፈጸም እንዲያስችለው
በሲዳማ ክልል ጥያቄ መነሻ በሰፊው እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ። በአሁኑ ጊዜ ፓርቲው በሁለት የተከፈለ ቢሆንም፣ የሁለቱም ፓርቲዎች መሠረታዊ
ዓላማቸው በሲዳማ ውስጥ መንፃት (Wolapho) የሚለውን የየመሬቾ አስተሳሰብ ለመተግበር እንደሆነ ከሚያደርጉት የፖለቲካ እንቅስቃሴ
መረዳት ይቻላል። የዚህ ፓርቲ የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም የ17ኛው ክፍለ ዘመን የሲዳማ ገዥ ኃይል አስተሳሰብን በ21 ክፍለ ዘመን ለማምጣት
የሚደረግ ትግል በመሆኑ፣ በዚህ በ21ኛው ክፍለ ዘመን በየትኛው መመዘኛ ተቀባይነት ያለው አይደለም።
የመንፃት አስተሳሰብ በኢሕአዴግ ፓርቲ
https://www.ethiopianreporter.com/index.php/article/18166?fbclid=IwAR08d0-BDwXcf3wT8BGBdIHD-zVa51X2TSLuo_di9KErGjry05l12FDTWfY 2/10
24/02/2020 የሲዳማ የፖለቲካ ኃይሎች አሠላለፍና የመንፃት አስተሳሰብ ፈተና | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharic
በኢሕአዴግ ውስጥ የሲዳማን ይወክል የነበረው ሲሕዴድ ነበር። ይህ ፓርቲ በርዕዮተ ዓለም ደረጃ ሲአንን በመቃወምና በሲዳማ ውስጥ
የነበረውን ክፍፍል በማጥበብ አንድ ሲዳማ ለመመሥረት የተቋቋመና ላለፉት በርካታ ዓመታት ሲዳማን የመራ ፓርቲ ነው። ከጅምሩ ይህ ፓርቲ
የመንፃት አስተሳሰብን የሚቃወምና አንድ ሲዳማን ለመፍጠር የሚደረገውን ትግል የሚደግፍ ነበር።
ሆኖም ይህ የሲሕዴድ አስተሳሰብ ብዙም መጓዝ አልቻለም። በኢሕአዴግም ሆነ በሕገ መንግሥቱ ላይ የተቀመጠውን ራስን በራስ የማስተዳደር
መብት በመጠቀም፣ ሲዳማ ራሱን የመምራት ወይም የማስተዳደር ሚናውን እንዲወጣ የተሰጠውን ተልዕኮ ወደ ጎን በመተው፣ የሲዳማ አመራር
ወደ መንፃት ፍልስፍና በመግባቱ የመሬቾ ሲያራምድ የነበረውን አስተሳሰብ ተግባራዊ አድርጎታል እየተባለ ይታማል። በዚህ ምክንያት ዳግም
በኢሕአዴግ ዘመን ተመልሶ ሲዳማ ወደ ሦስት ቦታ እንዲከፈል ምክንያት እንደሆነ ይነሳል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ (Lovise Aalen) በ2010 ዓ.ም. ባደረጉት ጥናትና (The politics of ethnicity in Ethiopia actor power and
mobilization under ethnic federalism) በሚለው መጽሐፋቸው ገጽ 137 ላይ እንዲህ ብለው አስቀምጠዋል። በሲዳማ ውስጥ በባህላዊ
አስተዳደር የተቀዳጁትን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሁለቱ የየመሬቾ ቡድንና የአለታ ቡድን እየተፎካከሩ መሆኑን ሲያስረዳ፣ አቶ አባተ ኪሾ የክልሉ
ፕሬዚዳንት ሆኖ በቆየበት አሥር ዓመት የመሬቾ ቡድን አባል ለሆኑ ግለሰቦች የትምህርት ዕድል በማመቻቸትና በተለያዩ ጥቅም በሚኖራቸው
ቦታዎች በመሾም መጥቀሙን በማንሳት አለታዎች እየተቃወሙ መሆኑን አውስቷል።
አባተ ኪሾ ከሥልጣን ከወረደ በኋላ የመሬቾ ቡድን አባል የሆኑና በሥልጣን ላይ ያሉ እንደተገፉ ባደረገው ቃለ መጠይቅ ማረጋገጡን
አሥፍሯል። በተመሳሳይ በዚህ ጊዜ በመጀመርያ ሲሕዴድ ሲመሠረት መሥራች የነበሩ የሃዲቾና ሌሎች የሲዳማ ጎሳዎች በአንዳንድ የመንግሥት
ሥልጣን ቦታዎች እንዳይሳተፉ እንደተደረገ ይነሳል። በተለይ የሃዲቾ ጎሳ አባላት በየአከባቢው በሚደርስባቸው በደል መነሻ የሃዲቾ ጎሳ የራሱን
ፖለቲካ ፓርቲ ያቋቋመበት ጊዜ መኖሩን (Lovise Aalen) በተጨማሪ ገጽ 155 ላይ አስፍሮ እንመለከታለን።
በዚህ መሠረት በኢሕአዴግ ዘመን
መንግሥት የየመሬቾ አስተሳሰብ በፓርቲ ደረጃ ሳይሆን በግለሰብ ተሿሚዎች በኩል የመንፃት አስተሳሰብና አመለካከት በሲዳማ ውስጥ
ተግባራዊ በመደረጉ ምክንያት፣ ሲዳማ ዳግም ወደ ክፍፍል እንደገባ መመልከት ይቻላል። በዚህም በሲዳማ ውስጥ ያለው ባህላዊ አስተሳሰብ
ወደ መንግሥታዊ አስተሳሰብ ያደገ ሲሆን፣ የትኛው ጎሳ የዞን አስተዳዳሪ እንደሚሆን ለይቶ እስከማስቀመጥ የደረሰበትንና ጎሳዎች ደረጃ
የወጣላቸው ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል።
በዚህም ምክንያት በፍትሕ ሥርዓት፣ በፖሊስና በአስተዳደራዊ ሥርዓት የመብት ረገጣ በቡድን የሚፈጸምበት፣ ተጠያቂነት የሌለበት ሥርዓት
እንዲፈጠርና ሥርዓት አልበኝነት እንዲሰፍን ምክንያት በመሆን ላይ ይገኛል። የመንፃት ፍልስፍና እንደማይሳካ የተረዱ የእዚህ ፍልስፍና
አቀንቃኞች በኢሕአዴግ ዘመነ መንግሥት በተለያዩ የሥልጣን እርከኖች ተሹመው ሥራቸውን ሲከውኑ ኖረዋል። እነዚህ ግለሰቦች የተሾሙት
የሲዳማ ሕዝብ የነበረበትን የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱ፣ ልማት እንዲያረጋግጡና በሕዝቦች መካከል አንድነትና መቀራረብ
እንዲፈጥሩ ቢሆንም፣ በተግባር ልዩነቶች እየሰፉና ወደ 17ኛው ክፍለ ዘመን አስተሳሰብ እየተመለሱ መምጣታቸው ታይቷል።
የመንፃት አስተሳሰብ በብልፅግና ፓርቲ
ይህ ፓርቲ ቀድሞ የነበረው ኢሕአዴግን በማክሰም እንደ አዲስ የተመሠረተ ነው። በፓርቲው ደረጃ ሊመዘን የሚገባው ፓርቲው የመደመር
ፍልስፍና የያዘ መሆኑ ነው። የመደመር ፍልስፍና አሁን ባለበት ደረጃ ለሲዳማ ብቻ ሳይሆን፣ ለመላው ኢትዮጵያ ጠቃሚ መሆኑን ብዙዎች
ያነሳሉ። መደመር የሚለው አንድነትን የሚያጎላ በመሆኑ፣ በተለይ ሲዳማ ውስጥ ያለውን ክፍፍል የሚያጠብ በመሆኑ ለሲዳማም ጠቃሚ
መሆኑን ማመን አይከብድም። ከዚህም ባለፈ ከሲዳማ ብሔር ውጪ በአካባቢው የሚኖሩ ሌሎች ጭቁን ሕዝቦች ለሚኖራቸው አብሮነት
ጠቃሚ መሆኑም ይነሳል። ይህ የመደመር ዕሳቤ ለመንፃት ቦታ የማይሰጥ በመሆኑ፣ በአሁኑ ጊዜ ብዙዎች የመንፃት አስተሳሰብ አራማጆች
ይህንን ፓርቲ ሲቃወሙ ይሰማል። የመቃወማቸው ሚስጥር ሌላ ሳይሆን በሲዳማ ውስጥ ያለውንና የኖረውን የ17ኛው ክፍለ ዘመን የመንፃት
አስተሳሰብ የመናድ አቅም እንዳለው መረዳታቸውን ያሳያል።
በሲዳማ ውስጥ አንዳንድ አካላት እያራመዱት ያለውን ያረጀ አስተሳሰብ መናድ የሚቻለው፣ በመደመር ዕሳቤ የሚያምንና አንድ ሲዳማን ሊፈጥር
የሚችል ርዕዮተ ዓለምን ተግባራዊ ሊያደርግ የሚችል የፖለቲካ ፓርቲ ሲኖር ብቻ ነው ብሎ የእዚህ ጽሑፍ አዘጋጅ ያምናል። ለሲዳማ
የሚያስፈልገውን አንድነት ተግባራዊ ለማድረግ ከመደመር ጽንሰ ሐሳብና ከብልፅግና ፓርቲ ጋር በመሥራት በቀጣይ ሲዳማዊና ኢትዮጵያዊ
አስተሳሰብ የተላበሰ ዜጋ መፍጠር የሚያስችል መደላደል ሊመቻች ይገባል።
በመሆኑም አሁን ያለውን ክፍፍል ማስቀረት የሁሉም ሲዳማ ግዴታ ነው። በአሁኑ ጊዜ በየቦታው የሚታዩ የጎሳ ፖለቲካ አስተሳሰብን በመናድ
ሲዳማን አንድ በማድረግ ጠንካራ ኢትዮጵያን ሊገነባ የሚችል በአመለካከቱ፣ በአስተሳሰቡና በድርጊቱ የተደመረ የሲዳማ ማኅበረሰብ መፍጠር
ያስፈልጋል። ከእዚህ ጋር በተያያዘ ጥንቃቄ ማድረግ የሚገባው የ17ኛው ክፍለ ዘመን አስተሳሰብ በምንም መልኩ መቀጠል እንደሌለበት ነው።
የመንፃት አስተሳሰብ በሲሕዴድ ፓርቲ
ይህ ፓርቲ የአንድ ጎሳ አስተሳሰብ ይዞ የተመሠረተ ሲሆን ዋናው በሲሕዴድ/ኢሕአዴግ አመራር በኩል የሚደርስበትን በደል ለመታገል የተቋቋመ
ድርጅት ነው። በወቅቱ በሃዲቾ ጎሳ አባላት ላይ የሚደርሰው ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ፣ ባህላዊና አስተዳደራዊ በደል እያየለ ሲመጣ ይህንን
በተደራጀ አግባብ ለመከላከል ሰፊ ትግል በማድረግ ላይ የቆመ ሲሆን፣ በ1992 ዓ.ም. በተደረገው ምርጫ በዳራ ወረዳ አሸናፊ ፓርቲ ሆኖ
https://www.ethiopianreporter.com/index.php/article/18166?fbclid=IwAR08d0-BDwXcf3wT8BGBdIHD-zVa51X2TSLuo_di9KErGjry05l12FDTWfY 3/10
24/02/2020 የሲዳማ የፖለቲካ ኃይሎች አሠላለፍና የመንፃት አስተሳሰብ ፈተና | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharic
(https://www.addtoany.com/share#url=http%3A%2F%2
https://www.ethiopianreporter.com/index.php/article/18166?fbclid=IwAR08d0-BDwXcf3wT8BGBdIHD-zVa51X2TSLuo_di9KErGjry05l12FDTWfY 4/10
24/02/2020 የሲዳማ የፖለቲካ ኃይሎች አሠላለፍና የመንፃት አስተሳሰብ ፈተና | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharic
ተጨማሪ ጽሑፎች
ማስታወቂያ
https://www.ethiopianreporter.com/index.php/article/18166?fbclid=IwAR08d0-BDwXcf3wT8BGBdIHD-zVa51X2TSLuo_di9KErGjry05l12FDTWfY 5/10
24/02/2020 የሲዳማ የፖለቲካ ኃይሎች አሠላለፍና የመንፃት አስተሳሰብ ፈተና | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharic
(https://www.ethiopianreporter.com/node/17612)
ማስታወቂያ
(http://www.amisoft.et/index.php?refer=reporter)
ማስታወቂያ
https://www.ethiopianreporter.com/index.php/article/18166?fbclid=IwAR08d0-BDwXcf3wT8BGBdIHD-zVa51X2TSLuo_di9KErGjry05l12FDTWfY 6/10
24/02/2020 የሲዳማ የፖለቲካ ኃይሎች አሠላለፍና የመንፃት አስተሳሰብ ፈተና | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharic
ለዜና መጽሔታችን ደንበኝነት ይመዝገቡ
የኢሜል አድራሻ
ዜና መጽሔት
ሳምንታዊ ዜና መጽሔት
ሰበር ዜና
ይመዝገቡ
ማስታወቂያ
ማስታወቂያ
ማስታወቂያ
https://www.ethiopianreporter.com/index.php/article/18166?fbclid=IwAR08d0-BDwXcf3wT8BGBdIHD-zVa51X2TSLuo_di9KErGjry05l12FDTWfY 7/10
24/02/2020 የሲዳማ የፖለቲካ ኃይሎች አሠላለፍና የመንፃት አስተሳሰብ ፈተና | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharic
የቅርብ ዜና
‹‹የፌዴራል መንግሥት በትግራይ ላይ ከፖለቲካ ሴራ እስከ ተዋጊ ጦር በመላክ ወደ ውጊያ እንድንገባ እየተፈታተነን ነው››
01 ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) የሕወሓት ሊቀመንበርና የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር (/article/18159)
መንግሥት በባለቤትነት በያዛቸው ድርጅቶች ቦርዶች ውስጥ የሴቶች ተሳትፎ 50 በመቶ እንዲሆን ተጠየቀ
06 (/article/18152)
ማስታወቂያ
https://www.ethiopianreporter.com/index.php/article/18166?fbclid=IwAR08d0-BDwXcf3wT8BGBdIHD-zVa51X2TSLuo_di9KErGjry05l12FDTWfY 8/10
24/02/2020 የሲዳማ የፖለቲካ ኃይሎች አሠላለፍና የመንፃት አስተሳሰብ ፈተና | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharic
ብዙ የተነበቡ
(/article/18124)
(/article/18123)
(/article/18056)
https://www.ethiopianreporter.com/index.php/article/18166?fbclid=IwAR08d0-BDwXcf3wT8BGBdIHD-zVa51X2TSLuo_di9KErGjry05l12FDTWfY 9/10
24/02/2020 የሲዳማ የፖለቲካ ኃይሎች አሠላለፍና የመንፃት አስተሳሰብ ፈተና | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharic
የሪፖርተር አድራሻ
ሪፖርተር
ሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
የሪፖርተር አገልግሎት
Reporter Tenders
https://www.reportertenders.com (https://www.reportertenders.com)
Reporter Jobs
https:\\www.ethiopianreporterjobs.com (https:\\www.ethiopianreporterjobs.com)
Goalgoogle
http://goalgoole.com/ (http://goalgoole.com/)
https://www.ethiopianreporter.com/index.php/article/18166?fbclid=IwAR08d0-BDwXcf3wT8BGBdIHD-zVa51X2TSLuo_di9KErGjry05l12FDTWfY 10/10