Professional Documents
Culture Documents
1. ባለሥልጣኑ የሠራተኞችን የደመወዝ ስኬል በማጥናትና ለመንግሥት አቅርቦ በማስወሰን ተግባራዊ ያደርጋል፡፡ 2
2. . ተመሣሣይ ወይም አንድ ዓይነት ተፈላጊ ችሎታና መመዘኛ የሚጠይቁ እኩል ደረጃ ያላቸው ሥራዎች እኩል
መነሻ ደመወዝ ይኖራቸዋል።
3. የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (2) ድንጋጌ ቢኖርም የሙያተኛ እጥረት በሚያጋጥምባቸው የሥራ መደቦች
ባለሥልጣኑ ከመነሻ ደመወዝ እስከ ሦስት እርከን ገባ ብሎ በመክፈል ሠራተኛን መቅጠር ይችላል፡፡ 4. በየሁለት
ዓመቱ የሥራ አፈፃፀም አማካኝ ውጤታቸው አጥጋቢ ወይም ከአጥጋቢ በላይ ለሆነ ሠራተኞች የደመወዝ
እርከን ጭማሪ ይደረጋል፡፡