Professional Documents
Culture Documents
@eotc Books by PDF
@eotc Books by PDF
ትችላለች⁉
➦እኛ በወር አበባ ጊዜ ንፁህ አይደለንም ብለን ሥጋዊ ምግብ እንደማንተው ሁሉ ጸሎት
የነፍስ ምግብ ነውና ነፍሳችን ለ7 /ሰባት/ ቀን ከውዳሴ ማርያም ፣ ከሰኔ ጎለጎታ
፣ከአርጋኖን፣ከሰይፈ ሥላሴ፣ከሰይፈ መለኮት እና ከተለያዩ የጸሎት ማዕድ እየከለከልን
ሕያዊት ነፍሳችንን ማስራብ የለብንም፡፡ ይልቁንም ዘወትር በመጸለይ ነፍሳችንን መመገብ
ይገባናል፡፡
አንዳንዶቹ እንኳን ሊጸለይ ቀርቶ የጸሎት መፅሐፍ አይነካም እያሉ እህቶቻችንን የሚያሳቅቁ
አሉ፡፡ እባካችሁ ሰው ከምታሳቅቁ እወቁ፣ ጠይቁ፣ ጠንቅቁ፣ ያለበለዚያ ለእህቶቻችን ፈተና
አትሁኑ፡፡ ባይሆን ጥሩ ስሜትና መንፈስ ካልተሰማችሁ ሰውነታችሁን መታጠብ፣አንቀጸ
👉
ሥጋችሁን/የከበረውን ቦታ/ ብቻ በመታጠብ ጸሎታችሁን መቀጠል ትችላላችሁ፡፡ ምናልባት
የስንፍና ምክር ሰምታችሁ ካልሆነ በስተቀር ከወር ወር ጸሎት፣የምትተዉበት ምክንያት የለም፡
ሌሎች በወር አበባ ጊዜ አይጾምም ይላሉ፣ ከየት እንዳገኙት ባይገባኝም ይህች በወር አበባ
አመካኝቶ፣ለመብላት አንኩቶ ይመስለኛል፡፡ በወር አበባ ጊዜ አንዳንድ እህቶቻችን ከፍተኛ
የሕመምና የስቃይ ስሜት የሚሰማቸው ብሎም እስከ ሕክምና የሚያደርሳቸው ከሆነ
ምናልባት መድሃኒት ሊወስዱ ስለሚችሉ እነርሱን አይመለከትም፡፡
➦ባለ ሁለት ግቢ የሆነበት ምክንያት ሴተችና ወንዶች ንፁህ በማይሆኑበት ፣ የሥጋ ድቀት
በሚያገኛቸው ጊዜና በጋብቻ ተወስነው ሕጋዊ ሩካቤ ሲፈጽሙ በእነዚህ ምክንያት ከቤተ-
ክርስትያን ደጅ እንዳይርቁና ኪዳን፣ቅዳሴ ጸሎት እንዲያደርሱበት ነው፡፡ ይህም የሚከናወነው
በመጀመሪያው ግቢ በመሆን ነው፡፡
ይሄ ጥያቄ በራሱ ተገቢነት የሌለው ትሕትና በማጣት ዲያብሎስ እየፈተነን መሆኑ ማስረጃ
ነው። አንድ ኦርቶዶክስ ከማንኛውም የዝሙት ተግባር እርቆ ከኖረ በኋላ ተክሊል ሊፈጸምለት
ሲል አረኸ አይገባኝም በማለት ራሱን ዝቅ ያደርጋል።
ከዚህ በተቃራኒው ራስን በራስ የማርካት የዝሙት ኃጢአት የኖረ ሰው ተክሊል ይገባሃል
ቢባል እንኳን አረኸ እኔ አይገባኝም ብሎ በተሰበረ ልብ ሊርቅ ሲገባው በማስተርቤሽን
ኃጢአት የዝሙትን ተግባር ሲፈጽም ከኖረ በኋላ ተክሊል ይገኛል ብሎ መጠየቅ ልባችን
በፈጸምነው ኃጢአት አለመሰበሩን ማረጋገጫ ነው።
አንዲት ሴት ራሷን የዝሙትን የኃጢአት እርካታ የመራቢያ አካሏን በመነካካት አያረካች ከኖረች
በኋላ እንዴት ባለ ድፍረት ነው ተክሊል ይገባኛል ብላ የምትጠይቀው?
ምንም ከወንድ ጋር በምንጣፍ አንድ ባትሆንም በኅሊና ወንድ በማሰብ አልፋ በፍቃዷ አፈ
ማኅፀኗን እየነካካች የዝሙትን ተግባር ስለፈጸመች ድንግል ተብላም አትጠራም።
በሉቃስ ወንጌል ላይ የሚገኝ አንድ ታሪክ አለ።
አባታችን አዳምን ግን የቤተ ፈት ልማድ አላገኘውም ማለትም ኃጢአት ሰርቶ ከገነት በተባረሩ
ጊዜ ፈጣሪዬን አስቀየምኩት ስለ በደሉ ያለቅስ ነበር።
ማለት ኃጥአቱን እያሰበ ቢያለቅስ በንስሐ አዳምን መስሎታልና የቤተ ፈት ፍቃድ ልማድ
አላገኘውም ይባላል።
አንዳንድ ሰዎች ማስተርቤሽን ሲፈጽሙ ከኖሩ በኋላ የንስሐ አባቴ ፈቅደውልኛል በማለት
ተክሊል ለመፈጸም ሲዳፈሩ ይታያል።
ተወዳጆች ሆይ ከድፍረት የሚገኝ ምንም አይነት መንፈሳዊ በረከት የለም። ድፍረት መንፈሳዊ
ኪሳራን ለዚህ ነው ቅዱስ ዳዊት እንደዚህ ያለው "የድፍረት ኃጢአት እንዳይገዛኝ ባርያህን
ጠብቀኝ ያን ጊዜ ፍጹም እሆናለሁ ከታላቁም ኃጢአት እነጻለሁ" መዝሙር 19፥13
ምን አልባት አንዳንድ ካህናት ስለዚህ አይነት ኃጢአት ግንዛቤ ሳይኖራቸው ቀርቶ ተክሊል
😔
ፈጽሚ ተክሊል ፈጽም ቢሉን እንኳን ራሳችንን ዝቅ አድርገን አይገባኝም ልንል ያስፈልጋል።
ሀ. አጋንንት የሰው ልጆችን በልዩ ልዩ መንገድ ክፋኛ ይዋጓቸዋል ። የሰው ልጆች ሲያንቀላፉ
አጋንንት ግን ለቅጽበት እንኳን አያሸልቡም ። ያንቀላፋው ሰው እስኪነቃ ድረስ እንኳን
አይጠብቁም ። አጋንንት የሰውን ልጅ በተኛበት ክፋ ክፋ ሕልም በማሳየት ይፈትኑታል ። አንድ
ጊዜ የተራቆተ የሴት ገላ ፣ በሌላ ጊዜ ደግሞ እንደ ወንድና ሴት ግንኙነት ሲያደርጉ በምትሐት
ያሳዩታል። በዚህ ጊዜ እርሱም በዝሙት ሐሳብ ይሳብና በሕልሙ ዝሙት ሲፈፅም ያድራል ።
መፅሐፈ መነኮሳት "ሰይጣናት የሰውን ልጅ ቀን ቀን ክፋ ሐሳብ በማሳሰብና በማሰራት
በሌሊት ደግሞ ዝሙት የሞላበት አስጸያፊ ሕልም በማሳየት ይዋጉታል " ይላል። በዚህ ጊዜ
ሰይጣናት ያቀረቡለትን ረቂቅ ፈተና ከመቃወም ፣ ከመፀፀትና ከመቆጨት ይልቅ ደስ እያለው
የሚያጣጥም ከሆነ ፤ በደስታ ስለ ዝሙት የሚያሰላስል ፣ የሚዳራ ፣ የሚዛለል ፣ ወደ ዝሙት
ከሚያመሩ ማናቸውም ነገሮች የማይሸሽ ሰው እነዚህን ነገሮች ነቅቶ ሳለ ያልተቃወማቸውን
ተግባራት በሕልሙ በፈፀማቸው ጊዜ በተግባር እንደ ፈፀማቸው ይቆጠራል ።ሌላው ከሥራ
ብዛት ሕልም እንዲታይ ጠቢቡ ሰሎሞን[ " ሕልም በሥራ ብዛት ይታያል " በማለት የተናገረው
ያስረዳል (መክ5:3) እንደዚሁም ሁሉ ከምኞት ብዛትም ሕልም ሊከሰት ይችላል። ክፋ ምኞት
በሕልምም ማርከሱ አይቀርም ። ሐዋርያው ይሁዳ " እያለሙ ሥጋቸውን ያረክሳሉ " ያለው
ለዚህ ይጠቀሳል ። (ይሁዳ 1:8) እንደሚታወቀው ነፍስ አትተኛም ። ስለዚህ ነፍስ በእንቅልፍ
ልቤ ነው ብላ ማመካኘት አትችልም ። ነፍስ በረከሰ ሕልም ምክንያት ከተጠያቂነት ነጻ መሆን
የምትችለው ሥጋ ከእንቅልፍ ውጭ በሚሆንበት ጊዜ ተግባረ ዝሙትን በመቃወምና
በመጥላት ከእግዚአብሔር ጋር መሆኗን ስታስመሰክር ብቻ ነው ። ሌላው ሕልመ ለሊትን
እንደ ኀጢአት የሚያስቆጥረው ሁኔታ አብዝቶ መመገብ ነው ። ጾም ለፅድቅ ስራ ሁሉ መሰረት
እንደሆነው እንደዚሁም አብዝቶ መመገብ የኀጢአት ሁሉ መሰረት ነው ። "እህል ጉልበትን
ያጠነክራል ተብሏልና ።ሰው ሁሉ ለቁመተ ስጋ ያህል ብቻ መመገብ ያሻዋል ። ከዛ ውጭ ግን
አብዝቶ መመገብ "ሆዳቸው አምላካቸው " እንደ ተባለው ለህልመ ለሊት ያጋልጠናል ።
ሕልመ ሌሊት መታን ማለት በቤት እና በቅጽረ ቤተ-ክርስትያን ሆኖ መጸለይ አይቻልም ማለት
አይደለም።በሱባኤም ሆነን ሕልመ ሌሊት ቢመታን ሰውነታችን ታጥበት ሱባኤው መቀጠል
እንጂ ማፍረስ የለብንም።
እዚህ ላይ አንድ መረሳት የሌለበት ነገር አለ። አንዳንዴ ሕልመ ሌሊት (ዝንየት) በሰይጣን
ፈተና ብቻ ላይከሰት ይችላል።ምናልባት ከምንጠቀማቸው ምግብና መጠጥ እንዲሁም
ከሥጋ ባህርያችን ሊከሰት ይችላል።ምክንያቱም ሰውነታችን ሲስማማው በራሱ ጊዜ ፈሳሽ
ሊወጣ ይችላል።ይህ ደግሞ ተፈጥሮ ነው፤ ምንም ማድረግ አይቻልም በጸጋ መቀበል
ነው።ለምሳሌ ማታ ትኩስ ነገር ሙቅ፣ሻይ አብዝተን የምንጠጣ ከሆነ በዘር ከረጢጣችን
ያለው አባለ ዘር በራሱ ጊዜ ሊፈስ ይችላል።
አለብን
#ፆር_የለመዱ (የሰይጣንን የፈተና ስልት በደንብ ለይተው ያወቁ ) አበው ቅዱሳን ግን ሽንገላ
የሞላበትን የሰይጣንን ፈተና አሸንክላ ምን እንደሚመስል መጪ ትውልድ እንዲያውቀው
በሕይወታቸው ያዪትንና መንፈስ ቅዱስ ያቀበላቸውን ፅፈው አስቀምጠዋል ። ለምሳሌ
ሰይጣነ ዝሙት የሰውን ልጅ ወደ ዝሙት ተግባር ከሚስብባቸው መንገዶች አንዱና ዋነኛው
ገሢሥ ነው ። #ገሢሥ ማለት ማሻሸት፣ መነካካት ፣ መዳበስ ማለት ነው ። ነብዩ ሕዝቅኤል
"ግልሙትናቸውንም አፍስሰውባት ነበር " (ሕዝ 23:3) በማለት እንደተናገረው ለዘር የደረሱ
ወንዶች ከሴቶች ጋር ሲላፋና ሲዳሩ ሩካቤ ሳይፈፅሙ ዘራቸው የሚፈስበት ጊዜ አለ ። ይህን
ድርጊት እንደ ተድላ በመቁጠር ብዙ ወጣቶች ሆን ብለው ያደርጉታል
በቅዱስ መፅሐፍ "የድንግልናዋንም ጡቶች ዳብሰው ነበር " እንደተባለው ቦታ ሳይመርጡና
ሰው ሳይለዩ የሴት ልጅን ገላ በመዳበስ "ግልሙትናን ማፍሰስ " ያሳፍራል ። ይህ መጥፎ
ልማድ የተጠናወታቸው ሰዎች ግርግርና በሰው ብዛት የተጨናነቀ ስፍራ የሴቶችን ገላ እንደ
ሐሳባቸው ለመነካካት ምቹ ሁኔታን ይፈጥርላቸዋል። ከነዚህ ውስጥ አንዳንዶቹ ሰው
ስራቸውን አይቶ እንዳይነቅፋቸው የተለያዪ ዘዴዎችን ይፈጥራሉ። ለምሳሌ አንዳንዶቹ ምንም
ሳያውቁና በእንቅልፍ ልባቸው ያደረጉት ለማስመሰል እንደ ተኛ ሰው እየተገላበጡና እያንኮራፋ
በልዩ አጋጣሚ አጠገባቸው የተኛችውን ሴት ገላ ሲዳብሱ ያድራሉ
ሌሎች ደግሞ ውጫዊ ይዘታቸው ሲታይ በዚህ ዓይነት ዘርን በማፍሰስ የመርካት ተግባር
የማይጠረጠሩ አይነት ናቸው ። ለምሳሌ እድሜያቸው በጣም የገፋ ፣ በአስተሳሰብ የበሰሉ ፣
በአለባበስና በምጣኔ ሀብት የተከበሩ የሚመስሉ ወይም አስተማሪ የሆነ መንፈሳዊ አቋምና
መልካም ስም የያዙ ናቸው ። እንደዚ ያሉት ሰዎች የሌሎችን ህዋሳት ለመነካካት
የሚያደርጉት ጥረት "ይህን አስበው አይደለም " እየተባለ ብዙ ጊዜ በበጎ ይተረጎምላቸዋል
ግብረ_አውናን(Masterbation)#ተገቢ_ነውን_?
#ግብአውናን የተባለበት ምክንያት አውናን የተባለው ሰው ከሚስቱ ጋር ግንኙነት እየፈፀመ
ሳለ ዘሩን ከማህፀን ውጪ ያፈሰው ስለነበር ነው ። ግብረ አውናን/Masterbation (ሴጋ)
በመፅሐፍ ቅዱስ ስንመዝነው ተገቢ ነገር አለመሆኑን እንረዳለን ። አንድ ገበሬ ለዘር
የሚያስቀረው ዘር ራሱ ከሚመገበው እንኳን የተሻለውን ምርጥ ዘር ነው ። ስለሆነም ከዘር
ወቅት በፊት ተጠንቅቆ በጎተራ ያስቀምጠዋል። በዘር ወቅት ደሞ አውጥቶ በመልካም ማሳ
ላይ ይዘራዋል እንጂ ያለ ቦታው አይበትነውም ። እንደዚሁም የሰው ዘር ከእህል ዘር
ይከብራልና በመልካም ጎተራ ማለትም በሰውነት ተጠብቆ መቆየት አለበት ። ከጋብቻ ቡሃላ
ባልና ሚስት ሩካቤ ሲፈፅሙ ደግሞ በመልካምዋ ማሳ በሚስት ማኀፀን መዝራት እንጂ ሆን
ብሎ እራስን በራስ በማርካት በየቦታው ማፍሰስ ተገቢ አይደለም ። እራስን በራስ ማርካት /
ሴጋ መፈፀም ተገቢ አለመሆኑን የሚያስረዱ በልዩ ልዩ አገባብ የተጠቀሱ ጥቅሶች አሉ
ከግብረ_አውናን (Masterbation)
#እንዴት_መላቀቅ_ይቻላል?
#ሀ. ግብረ አውናን እንደ ማር ጠብታ ነው ። የማር ጠብታ ልብስ ላይ የወደቀ እንደሆነ
በፍፁም የሚለቅ አይመስልም ፣ ነገር ግን ትንሽ ለቅለቅ ያደረጉት እንደሆነ ወዲያውኑ
ይለቃል። ይህ ክፋ ልማድም እንደማር በቀላሉ ባይሆንም ከልብ በመፀፀት በጠንካራ
መንፈስ ከተነሱ ሊያስወግዱት ይቻላል። በመጀመሪያ የሚያስፈልገው ከዚ ነገር
መቼም መላቀቅ አልችልም ብሎ ተስፋ አለመቁረጥ ነው ። ከፍተኛ ትግልና ጥረት
ይጠይቃል ። ስለዚህ ተስፋ መቁረጥ ፈፅሞ አይገባም
#ሠ. "ሁለት ሁለት አድርጎ ላካቸው " የሚለውን የወንጌል ቃል አስብ ። በዚህ ክፋ
ልማድ ተጠምደህ ሳለ ለብቻህ መሆንን አትውደድ ። ቢቻልህ አኗኗርህና መኝታህ
ከምታፍረውና ከምታከብረው ሰው ጋር ይሁን ። ይህም ጓደኛህ ወይም ከቤተሰብህ
አንዱ ሊሆን ይችላል። በፀሎት ከሚረዱህ መንፈሳውያን መምህራን አባቶች ጋር ጊዜ
ማሳለፍን ውደድ
#ሀ. ግብረ አውናን እንደ ማር ጠብታ ነው ። የማር ጠብታ ልብስ ላይ የወደቀ እንደሆነ
በፍፁም የሚለቅ አይመስልም ፣ ነገር ግን ትንሽ ለቅለቅ ያደረጉት እንደሆነ ወዲያውኑ
ይለቃል። ይህ ክፋ ልማድም እንደማር በቀላሉ ባይሆንም ከልብ በመፀፀት በጠንካራ
መንፈስ ከተነሱ ሊያስወግዱት ይቻላል። በመጀመሪያ የሚያስፈልገው ከዚ ነገር
መቼም መላቀቅ አልችልም ብሎ ተስፋ አለመቁረጥ ነው ። ከፍተኛ ትግልና ጥረት
ይጠይቃል ። ስለዚህ ተስፋ መቁረጥ ፈፅሞ አይገባም
#መ. ዘወትር ልቡናህ የሚጠመድበትን ነገር ፈልገህ አድርግ ። ቦዘኔ አትሁን ትጉህ
ሰራተኛ ሁን ።ስራህም አይምሮህን የሚያሰራ ቢዚ የሚያደርግ ይሁን ። ትርፍ ሰአት
አይኑርህ ። የሚነበብ ወይም ሌላ የሚሰራ ስራ ፈጥረህ ሥራ
#ሠ. "ሁለት ሁለት አድርጎ ላካቸው " የሚለውን የወንጌል ቃል አስብ ። በዚህ ክፋ
ልማድ ተጠምደህ ሳለ ለብቻህ መሆንን አትውደድ ። ቢቻልህ አኗኗርህና መኝታህ
ከምታፍረውና ከምታከብረው ሰው ጋር ይሁን ። ይህም ጓደኛህ ወይም ከቤተሰብህ
አንዱ ሊሆን ይችላል። በፀሎት ከሚረዱህ መንፈሳውያን መምህራን አባቶች ጋር ጊዜ
ማሳለፍን ውደድ
#ሸ. እንዲህ ያለ ፈተና ሲነሳብህ /አድርግ አድርግ ሲልህ / ከቻልክ ስገድ ።ወይም የሆነ
እንቅስቃሴ /ስፖርት / ስራ ። ሽንት መሽናትም ጥሩ መፍትሄ ነው አይምሮህ ሽፍት
እንዲያደርግ ያደርገዋል። በየጊዜው ፀበል መጠመቅን ቸል አትበል ። የሴት ገላን
ሳታይ
#ቀ. ሰውነትህን አትነካካ ቢበላህ እንኳን አትከከው ። ስታክና ስትነካካው በዛው
አድርግ አድርግ ሊልህ ይችላልና ። ንፁህ ሁን ፣ ሻወር ውሰድ ፣ ወክ አድርግ ፣ አንብብ ።
ከምንም በላይ አጥብቀህ ፀልይ ። ሁላችንንም እግዚአብሔር ይርዳን ።
#ሸ. እንዲህ ያለ ፈተና ሲነሳብህ /አድርግ አድርግ ሲልህ / ከቻልክ ስገድ ።ወይም የሆነ
እንቅስቃሴ /ስፖርት / ስራ ። ሽንት መሽናትም ጥሩ መፍትሄ ነው አይምሮህ ሽፍት
እንዲያደርግ ያደርገዋል። በየጊዜው ፀበል መጠመቅን ቸል አትበል ። የሴት ገላን
ሳታይ
🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔻
t.me/Orthodox_Addis_Mezmur
t.me/orthodox_spiritual_poems
t.me/Eotc_Books_By_Pdf
t.me/Lesangeez128
🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 🔺