Professional Documents
Culture Documents
Sample Tahsas21
Sample Tahsas21
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ልጆቿን ሰብስባ ከምታከብራቸው የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
በዓላት መካከል ፩ዱ የሆነዉ ኖላዊ በመባል የሚታወቀውና ጌታችን በበግ ጠባቂ (እረኛ) አምሣል የተገለጠበት ዕለት ታሕሳስ
፳፩ ነው ።
"ኖላዊ" ማለት ጠባቂ፣ እረኛ ማለት ነዉ። አዳም ከክብሩ ዝቅ ባለና በተዋረደ ጊዜ ቸር መድኃኒታችን ክርስቶስ
ከእመቤታችን ከስጋዋ ስጋ ከነፍሷ ነፍስን ነስቶ በቤተልሔም በግርግም ተወለደ፤ በእረኞችና መላእክትም ምስጋና
መድኀኒትነቱን ገለጠ። እረኛም ነፍሱን ለበጎቹ አሳለፎ እንደሚሰጥ ክርስቶስም ለኛ ወገኖቹ በመስቀል ዋጋ ከፍሎ አዳነን።
እረኛ በጎቹን ከተኩላ( ከጠላት) እንደሚያስጥል ጌታችንም ከዲያብሎስ ባርነት ማስጣሉን ቤተክርስቲያን በልዮነት
የምታስብበት እንዲሁም
“ዮሴፍን እንደ መንጋ የምትመራ፥ የእስራኤል ጠባቂ ሆይ፥ አድምጥ፤ በኪሩቤል ላይ የምትቀመጥ፥ ተገለጥ።”
— ዮሐንስ ፲፥፲፩
፫, በርናባስ ሐዋርያ
ቅዱስ በርናባስ ምንም በትውልዱ እሥራኤላዊ ቢሆንም ተወልዶ ያደገው በቆዽሮስ ነው:: እስከ ወጣትነት ጊዜውም የቆየው
እዚያው ነው::የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው የመሆኑ ዜና ሲሰማ ግን ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ መድኅን ክርስቶስን
ተመለከተ:: ጌታውንም ሊከተል በልቡ ቆረጠ:: የፈጠረን ሁሉን ሚያውቅ ክርስቶስም እንዲጠቅም አውቆ: የመጀመሪያ
ስሙ "ዮሴፍ" ሲሆን "በርናባስ" ያለው መድኃኒታችን ክርስቶስ ነው:: ትርጉሙም "ወልደ ኑዛዜ-የመጽናናት ልጅ" እንደ
ማለት ነው:: ስሙንም ቀይሮ አስከተለው:: ከ72ቱ አርድእትም ደመረው::ቅዱስ በርናባስ በአገልግሎት ዘመኑ መጀመሪያ
ከቅዱስ ዻውሎስ ጋር: ቀጥሎ ደግሞ ቅዱስ ማርቆስን አስከትሎ ብዙ አሕጉራትን አስተምሯል። ቅዱሱም ከብዙ ትጋት
በሁዋላ በዚህች ቀን አረማውያንና አይሁድ ገድለውታል(ሰማዕትነት ተቀብሎ አርፏል):: ቅዱስ ማርቆስም ገንዞ ቀብሮታል::
ስዕል: ቅዱስ በርናባስ
ማጠቃለያ
ቤተክርስቲያን ከማንም እና ከምንም ነገር በላይ አምላክ ፈጣሪ ብላ እግዚአብሔርን ታመልካለች
ቅድስት ድንግል ማርያምን አመ አምላክ (አምላክ እናት) ብላ ሐዋርያትን፣ ነቢያትን፣ ቅዱሳን አባቶቻችን እና እናቶቻችን
ፃድቃን ሰማዕታትን ደሞ እግዚአብሔር እንዳከበራቸዉ መጠን ታመሰግናቸዋለች።
ጥያቄዎች