Professional Documents
Culture Documents
0
ማ ው ጫ
የምዕራፉ አላማዎች
የወንጀል ህግ ምንነት፣ አላማውን ግቡን ይረዳሉ፣
የሰው ልጅ ሠላማዊ ህይወትን ለመምራት ከወንጀል የፀዳ ህብረተሠብ መፍጠር አለበት፡፡ ለዚህ
ደግሞ ያለው አማራጭ የወንጀል ፍትህ አስተዳደርን መዘርጋት ነው፡፡ ይህ የወንጀል ፍትህ
አስተዳደር እንዲኖር ህግ አውጭ፣ ህግ ተርጓሚና አስፈፃሚ አካላት መኖር አለባቸው፡፡ በዚሁ
መሠረት ህግ አውጪው እንደ ወንጀል አድርጐ የሚቆጥራቸው ድርጊቶች እና ተገቢ ብሎ
ያመነባቸውን ቅጣቶች ዘርዝሮ በህግ ያወጣል፤ ህግ ተርጓሚው ወንጀል ፈፅመዋል ተብለው
የተከሰሱ ሠዎችን ሲቀርቡለት ማስረጃውን አዳምጦ ተገቢውን ውሣኔ ይሰጣል፡፡ አስፈፃሚው
አካል በፖሊስ አማካኝነት ወንጀል እንዳይፈፀም ይከላከላል ተፈፅሞም ከሆነ ተጠርጣሪዎች ይዞ
ለፍርድ ያቀርባል፡፡ ዓቃቤ ህግ መንግስትን በመወከል ክስ ያቀርባል፡፡ ማረሚያ ቤቶች ቅጣት
የተወሰነባቸውን ጥፋተኞች ተቀብለው ያሰራሉ ሌሎች ቅጣቶችም ተወስነው ከሆነ ያስፈፅማሉ፡፡
5
ግንኙነት መሠረት ድርጊታቸውን ማስተካከል የሚችሉ ህጉ ተፈፃሚ የማይሆንባቸው ሲሆን
ይህን ማድረግ የማይቻላቻው በህጉ መሠረት ይዳኛሉ፡፡
ኢትዮጵያ ከላይ የተጠቀሰውን አላማ ለማሣካት በተለያዩ ጊዜያት የወንጀል ህጐች ድንግጋ
በተግባር ላይ አውላለች፡፡ በ1923 ዓ.ም የተደነገገው ለመጀመሪያ ጊዜ በስራ ላይ የዋለው
የወንጀል ህግ ነው፡፡ 1949 ዓ.ም የወጣው ደግሞ ሁለተኛውና ከ40 ዓመት በላይ በስራ ላይ
የነበረ የወንጀል ህግ ነው፡፡ በየመሃሉም ተጨማሪና ያለውን ከፍተት ሊሞሉ የሚችሉ ህጐች
በስራ ላይ ነበሩ፡፡
የወንጀል ህግ አላማና ግብ
አ ንቀ ፅ 1
7
የወንጀል ህግ አላማ
የወንጀል ህጉ ግብ
የሰው ህይወት አካል እና ጤንነት፣ ነፃነት እና ክብር (አምስተኛ መፅሃፍ አንቀፅ 538-
661)
9
የወንጀል ህግ ከሌሎች ህጐችና ኢ-ሞራላዊ ድርጊቶች የሚለይበት ሁኔታ
10
እንዳየነው ግለሰብን ወክሎ በፍትሐብሔር ጉዳይ አይከራከርም፡፡ ምክንያቱም የፍትሐብሔር
ክርክር በግለሰቦች መከላከል የተፈጠረ አለመግባባት ነው፡፡
ከላይ ለመግለፅ እንደተሞከረው አንድ ድርጊት ወይም ያለማድረግ እንደ ወንጀል የሚቆጠረው
ህግ አውጭው በግልፅ ጉዳዩን ወንጀል መሆኑን ሲደነግግ ብቻ ነው፡፡ ሆኖም ግን ጥሩም ሆነ
መጥፎ ሞራላዊ እሴቶች ምንጫቸው ሃይማኖት ወይም ከውስጥ በሚመነጭ የማክበር ሰሜት
ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ሃይማኖታዊ ግበረ-ገብነት ሊመነጭ የሚችለው ግለሰቡ ለሃይማኖቱ መርሆች
ያለው መንፈሣዊ አመለካከት ነው፡፡ ግብረ-ገብነት ቤተሠብን፣ ታላላቆችን፣ አለቆችን እና
አመለካከቶችን በማክበር ሊመነጭ ይችላል፡፡ በተለያዩ የሃገራችን ክፍሎች እንዳሚታየው
የቤተሠብ አመለካከትን ማክበር፣ ታላላቆች የሚሉትን መፈፀም ምንጩ ለጉዳዩ የሚሰጠው
ጥልቅ ስሜት ነው፡፡
11
የግብረገብ ወይም ሞራላዊ እሴቶች ሊኖሩና ሊቀጥሉ የሚችሉት ህብረተሠቡ የሚሰጣቸው
ክብር እና ጥልቅ ስሜት እንጂ መደበኛ ተጠያቂነትን ስለማያስከትሉ አይደሉም፡፡
በህገ መንግስቱ አንቀፅ 15 መሠረት ማንም ሰው በህይወት የመኖር መብት አለው ማንኛውም
ሰው የሌላውን ሰው ህይወት ያጠፋ እንደሆነ በወንጀለኛ ህግ ይቀጣል፡፡ በአንቀፅ 15 ስር
የተደነገገው በህይወት የመኖር መብት አለው ሲል መንግስት በማናቸውም ምክንያት የሰውን
ህይወት ሊያጠፋ አይችልም፡፡ ይህ መብት እንደተጠበቀ ሆኖ ሰው ህይወቱን ሊያጣ የሚችልበት
ሁኔታ ይኖራል መንግስት የሰው ህይወት ሊያጠፋ የሚችለው የሚከተሉትን መሠረት አድርጐ
ነው፡፡
የአካል ደህንነት መብት የተላለፈ ማንኛውም የመንግስት አካል ወይም ግለሰብ ህገ መንግስቱን
እንደጣሰ ይቆጠራል፡፡ ስለዚህ ማንኛውም ሰው የወንጀል ድርጊት መፈፀሙ ከተረጋገጠበት
እንደነገሩ ሁኔታ ወይ በእስራት ወይም በሞት ሊቀጣ ይችላል እንጂ አካሉን በማሰቃየት ሊቀጣ
አይችልም፡፡ እንዲሁም አንድ ሰው ወንጀል ፈፅሟል ተብሎ በበቂ ምክንያት ተጠርጥሮ እያለ
ማስረጃው ግን በበቂ ሁኔታ ካልተገኘ ተጠርጣሪው ይለቀቃል እንጂ ወንጀሉን እንዲያምን
አይደበደብም፡፡ በማናቸውም ሁኔታ የሰው አካል ደህንነት መብት የተጠበቀ ነው፡፡ ይህንን
የፈፀመ ካለ በወንጀል ህጉ መሠረት ተጠያቂ ይሆናል፡፡
የነፃነት መብት
ከቦታ ቦታ መዘዋወር
14
ከህብረተሠቡ ነጥሎ በማስቀመጥ ሌሎች ወንጀሎች እንዳይፈፅሙ መከላከል ነው፡፡ በዚህም
መሠረት አንድ ወንጀለኛ እሰራት ቢፈረድበት እስሩን እስኪጨረሰ ድረስ ሌላ ወንጀል በመፈፀም
የህብረተሠቡን ሠላም አያናጋም የሚል ግምት ስላለ በህገ መንግስቱ እውቅና የተሠጠው
የነፃነት መብት ሊያጣ ይችላል፡፡
የመወያያ ጥያቄዎች
15
የጋራ መብት ቅድሚያ መሠጠቱ የግለሰብ መብት በወንጀል ህጉ ጥበቃ
አይደረግለትም ማለት ነው?
“ሰላም”
“ደህንነት”
“ስርዓት”
“መብት”
16
ምዕራፍ ሁለት
የምዕራፉ አላማዎች
1. የህጋዊነት መርህን ምንነት በዝርዝር ይረዳሉ፣
አ ንቀ ፅ ሁለ ት
17
2. ፍርድ ቤት ሕገወጥነቱ በሕግ ያልተደነገገን ድርጊት ወይም ግድፈት እንደወንጀል
ሊቆጥረው እና ቅጣት ሊወስንበት አይችልም፡፡
ሀ. በህግ በግልፅ ካልተደነገገ በስተቀር ወንጀል የለም፡፡ በአንቀፅ 2(1) እንደተቀመጠው ወንጀል
መሆኑ በግልፅ ካልተቀመጠ ማንኛውም ሰው ለፈፀመው ድርጊት ምንም እንኳን ድርጊቱ
ግብረ-ገብነት የጐደለው ቢሆን ተጠያቂ አይደለም፡፡
18
ለ. በህጉ በግልፅ የተቀመጠውን ወንጀል ድርጊት የፈፀመው ሰው የሚቀጣው ህጉ ባስቀመጠው
መሠረት ነው፡፡ ለተላለፈው ድርጊት የተቀመጠው ቅጣት ብቻ ይቀጣል፡፡ ሁለት አባባሎች
በአጭር ሲቀመጡ፡-
የህግ አውጭው ህጐች ሲደነግግ በተቻለ መጠን ግልፅና የማያሻማ መሆን አለበት፡፡ ሆኖም ግን
በተለያዩ ምክንያቶች የተዘጋጁት ህጐች ግልፅነት ሊጐድላቸው ይችላል፡፡ በዚህም መሠረት
አንዳንድ ቃላቶች ግልፅነት ሊጐድላቸው ይችላል ወይም የተለያዩ አሻሚ ትርጐም ይሰጣሉ፡፡
20
የወንጀል ህግ ወደ ኋላ ተመልሶ የማይሰራ ስለመሆኑ
አንቀፅ አምስት
21
አንድ ድርጊት ከተፈፀመበት ጊዜ በፊት “ወንጀል ሆኖ ያስቀጣል” ተብሎ ቀደም ሲል ተደንግጐ
ካልቆየና ተከሣሹም ለፍርድ የሚቀርብበት ህግ በድርጊቱ ፍፃሜ በፊት በህግ መልስ ተቀርፆ
ካልቆየና ድርጊቱን ከፈፀመ በኋላ አድሪጊውን ለመቅጣት ሲባል ሌላ ህግ ከወጣ በህገ መንግስቱ
መሠረት ተፈፃሚነት የለውም፡፡
22
የሚለው እንጂ ድርጊቱ ከተፈፀመ በኋላ የወጣ (አዲስ) ህግ የሚደነገገው የቅጣት ጣሪያ የት
ድረስ ነው? የሚለው አይደለም፡፡
ልዩነቶች (Exceptions)
አንቀፅ ስድስት
23
ለምሳሌ፡- አንድ ሰው በቀድሞው ህግ መሠረት በ6 አመት ፅኑ እስራት የሚያስቀጣ
ወንጀል ቢፈፅምና በአሁኑ ህግ መሠረት ይሄው ተመሣሣይ ወንጀል በ6
አመት ቀላል እስራት የሚያስቀጣ ቢሆን ምንም እንኳን ወንጀሉ የተፈፀመው
የቀድሞው ህግ በስራ ላይ በነበረበት ጊዜ ቢሆንም አዲሱ ህግ መሠረት የ6
አመት ቀላል እስራት ተፈፃሚ ይሆንበታል፡፡
የመወያያ ጥያቄዎች
አንቀፅ ሰባት
ለምሣሌ፡- አንድ “X” የተባለ የንግድ ድርጅት ሰራውን በሚያካሂዱበት ወቅት በወንጀል
ህጉ የተከለከለ እና የሚያስጠይቅ ድርጊት ከፈፀመ ጉዳዩን ያየው ፍርድ ቤት
ሁለት አይነት ውሣኔ ይሰጣል፡፡
25
የይረጋ ዘመን አፈፃፀም
አንቀፅ ስምንት
በህጉ አንቀፅ 8 መሠረት የክስ አቀራረብና የቅጣት አፈፃፀም ይርጋ ዘመን በዚህ ህግ
እንደሚመራ ይገልፃል፡፡ ይህ ማለት ወንጀሉ የተፈፀመው የቀድሞው ህግ በስራ ላይ በነበረበት
ጊዜ ይሁን ወይም በአሁኑ ህግ ይርጋ የሚሳራው እና የሚፈፀመው በአዲሱ ህግ መሰረት ብቻ
ነው፡፡
26
የፍርዶች አፈፃፀም
አንቀፅ ዘጠኝ
27
አንቀፅ 9 የሚያመለክተው በተሻረው ህግ መሠረት የተሰጡ ፍርዶች አፈፃፀማቸው የሚመራው
በስራ ላይ ባለው ህግ መሠረት ይመራል፡፡ ይህ አንቀፅ በስሩ የተለያዩ ድንገጌዎችን ስለያዘ
ዝርዝር አድርገን እንመለከተው፡፡
28
የእኩልነት መርህ
አንቀፅ አራት
ከዚህ መርህ ለማየት እንደሚቻለው በህግ ፊት እኩል የመሆን መብት ሚዛናዊና ፍትሐዊ
ፍርድ የማግኘት መብት ከሌሎች ነገሮች መሃል ዘርንና ቀለምን ሣይለይ ሰዎች በአጠቃላይ
የሚጐናፀፉት ነው፡፡ ህገ መንግስቱ አንቀፅ 25 ላይ እንደተገለፀው ህጉ ”ዜጐች ሁሉ” ሣይሆን
“ሰዎች ሁሉ” በማለት ይጀምራል፡፡ በዚህም ምክንያት በአንድ ኢትዮጵያዊና በአንድ የውጭ
አገር ዜጋ መካከል የወንጀል ወይም የፍትሐብሔር (የብድር፣ የውል፣ የጋብቻ፣ የንብረት
ወዘተ) ክርክር ሲነሣና ህግ ፊት (ፍርድ ቤት ወይም አስተዳደር) ቢቀርብ ኢትዮጵያዊው
ተከራካሪ ከዜግነቱ የሚመነጭ አንዳች የተለየ ፍርድ አያገኝም፡፡ የውጭ አገር ዜጋም ለእርሱ
ሲባል ከህግ ውጭ የተለየ ፍርድ አይሰጠውም፡፡ ፍትህ የሰዎችን ዜግነት አትለይም ዓለም
29
አቀፋዊ ናት፡፡ ይህ ህግ የአለም መንግስታት የተቀበሉት በመሆኑ በውጭ አገር የሚኖሩ
ኢትዮጰያዊያንም የዚህ መብት ተጠቃሚዎች ናቸው፡፡
“እኩል የህግ ጥበቃ” ስንል ምን ማለታችን ነው? ከላይ እንደጠቀስነው በህግ ፊት እኩል
የመሆን መብት የሚረጋገጠው በትክክለኛ ዳኝነት ወይም የአስተዳደር ስርዓት ነው፡፡ እኩል
የህግ ጥበቃ የሚረጋገጠው ደግሞ ህጉ ተረቶ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ነው፡፡ ሰዎች ሁሉ በህግ
ፊት እኩል መሆናቸው የሚረጋገጠው የፍትህ አካላት ህግ አስፈፃሚው ህግን
በሚተረጉሙበትና በስራ ላይ በሚያውሉበት ጊዜ ሲሆን ሁሉም ሰዎች እኩል የህግ ጥበቃ
የሚያደርግላቸው ደግሞ ህግ አውጭው የመንግስት አካል ነው፡፡ የኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ
ህግ ይሄን መሠረታዊ መርሀ በአንቀፅ አራት ላይ በግልፅ አስቀምጧል፡፡ ሁሉም ሰዎች በህግ
እንደምን እኩል ጥበቃ ይደረግላቸዋል?
የህግ ዋንኛ አላማ የህብረተሠቡን የሀብት የአስተሣሠብ የእምነትና የሃይል ሚዛን በመቆጣጠር
ሰዎች እለታዊ ኑሮአቸው ያለ ሰጋት እንዲያካሂዱ ማድረግ ነው፡፡ የህግ ትልቁ ዓላማ ሠላምን
መፍጠረና ሠላምን ማረጋገጥ ነው ማናቸውም ህግ ሲወጣ የእያንዳንዱን ሰው ህይወት
በአጠላይ ደግሞ የህብረተሠቡን ህይወት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንካቱ አይቀርም፡፡ የህግ
አይነተኛ ጠባይ ደግሞ ሁሉን አቀፍነት ነው፡፡ የሃገሪቱን ህዝቦች በአጠቃላይ የሚነካ ህግ
ሊወጣ ይችላል፤ ወይም የአገሪቱ አጠቃላይ ህብረተሠብ የተወሰነውን ክፍል ብቻ የሚነካ ሊሆን
ይችላል፤ ወይም በአንድ በተወሰነ ሞያ የተሠባሠቡ ሰዎችን ብቻ የሚነካ ሊሆንም ይችላል፡፡
ለአንድ ሰው ወይም ለተወሰኑ ሰዎች ብቻ ተብሎ የሚሰራ ህግ የለም፡፡
30
ይህ ከዚህ በላይ ከተገለፀው የእኩልነት መርህ ጋር ይቃረናል? መልሱ አይቃረንም ነው፡፡
ምክንያቱም ሁለት ወንጀል አድሪጊዎች በህግ ፊት እኩል ናቸው ማለት ሁለቱም በአንድ
አይነት የህግ ስነ ስርዓት አካሄድ መሠረት ይዳኛሉ ወይም ይቀጣሉ ማለት አይደለም፡፡ ይህ
ጉዳይ የክስ አቀራረብ፣ የፍርድ ቤት ነገሩን የማየት ስልጣንና የመሣሠሉት የህግ ስነ ስርዓት
ጉዳዮች ናቸው፡፡ እንዴት እንደሆነ ቀጥለን እንመልከት
31
የተዋዋለው አባታቸው ቢሆንም እንኳን ወራሾች ባለተዋዋሉት ውል በወረሱት ልክ
እንዲፈፅሙ ሊጠሩ ይችላሉ፡፡ የዚህ አይነቱ አሰራር በወንጀል ህግ ተነባራዊ ማድረግ
አይቻልም፡፡ ተጠየቂው ፈፃሚው ብቻ ነው፡፡
የመወያያ ጥያቄዎች
32
ምዕራፍ ሶስት
በወንጀል ህግ ተጠያቂነት
የምዕራፉ አላማዎች
1. የወንጀል ህግ ተጠያቂ የሚያደርጉትን ቅድመ ሁኔታዎች ይገነዘባሉ፣
ሀ. ህጋዊ ፍሬ ነገር
ለ. ግዙፋዊ ፍሬ ነገር
33
ሐ ሞራላዊ ፍሬ ነገር በአንድ ላይ ተሟልተው ሲገኙ ብቻ ነው አንድ
ሰው ወንጀል አድርጓል ተብሎ ተጠያቂ የሚሆነው ሁሉንም ተራ
በተራ እንመልከታቸው፡፡
አ ንቀ ፅ 2 3 (2 )
ህጋዊ ፍሬ ነገር
አ ንቀ ፅ 2 3 (1 )
ግዙፉዊ ፍሬ ነገር
በዚህ ቅድመ ሁኔታ መሠረት አንድ ሰው ወንጀል የመፈፀም ሃሣብ ካለው በድርጊት
እስካልተገለፀ ድረስ ተጠያቂነትን አያስከትልም፡፡ ምክንያቱም አንድ ሰው ወንጀል የመፈፀም
ሃሣብ ኖሮት በድርጊት አስካልገደጸው ድረስ ማንም ሊያውቀው አይችልም፡፡ አንድ ሰው
ወንጀል ለመስራት አስቦ በድርጊት ካልገለፀው አይቀጣም የሚለው ድንጋጌ መሠረታዊ የሆነ
34
የወንጀል መርህ ነው፡፡ ወንጀል በድርጊት ወይም ከሃሣብ በመነጨ አካላዊ እንቅስቃሴ
መፈፀም መቻል አለበት፡፡ ሃሣብ በሚታይ አካላዊ እንቅስቃሴ ካልተደገፈ ወንጀል ፈፃሚው
ያሠበውን ነገር ራሱ ብቻ ስለሚያውቀው ተጠያቂ ማድረግ አይቻልም፡፡
ግዙፋዊ ቅድመ ሁኔታ የሚባለው ፍሬ ነገር በስሩ የተለያዩ ጉዳዮችን የያዘ ነው፡፡
ድርጊት
በድርጊት የተፈፀመ ወንጀል ማለት አንድ እንዳይፈፀም ክልከላ ወይም እገዳ የተደረገበትን
ድርጊት መፈፀም ማለት ነው፡፡ ለምሳሌ በአንቀፅ 538 መሠረት ማንም ሰው አሳቦ ወይም
በቸልተኝነት በማናቸውም አይነት መሣሪያ ወይም ዘዴ ሌላውን ሰው የገደለ እንደሆነ
ነፍስ ገዳይ እንደሆነና ተጠያቂ እንደሚሆን ይገልፃል፡፡ በዚህም መሠረት አንድ ሰው ለብዙ
ጊዜ ለመግደል ሲያስብ የቆየውን ጐረቤቱን ጠመንጃ ገዝቶ በጥይት መቶ ቢገድለው ወይም
በሴንጢ ወግቶ ቢገድለው የወንጀል ህጉ እንዳይፈፀም ክልከላ ያደረገበትን ነገር ስለፈፀመ
ይቀጣል፡፡
አለማድረግ
ይህ ከላይ ከተገለፀው ጋር ተቃራኒ ነው አለማድረግ ማለት በወንጀል ህጉ ላይ እንዲያደረግ
የታዘዘውን ነገር አለመፈፀም ማለት ነው፡፡ በርግጥ በህጉ ከተዘረዘሩት የወንጀል አይነቶች
አብዛኛዎቹ በድርጊት አማካኘነት የሚፈፀሙ ናቸው፡፡ ሆኖም ግን እንዳንዶቹ የሚፈፀሙት
በህጉ የታዘዘን ጉዳይ ባለመፈፀማቸው ነው፡፡
35
ሀ. በሞት ወይም በዕድሜ ልክ ፅኑ እሥራት የሚያስቀጣ ወንጀል
መፈፀሙን ወይም የወንጀለኛውን ማንነት እየወቀ ለሚመለከታቸው
ባለሥልጣኖች ሳያስታውቅ የቀረ እንደሆነ፤ ወይም
አንድ የወንጀል ድርጊት ጉዳት ወይም አደጋ አስከትሎ ከሆነ በድርጊቱና በውጤት መሃከል
የምክንያትና የውጤት ግንኙነት አለ ማለት ይቻላል፡፡ ይሄን የምክንያትና ውጤት ግንኙነት
ማረጋገጥ ከተቻለ ድርጊቱን የፈፀመው ሰው ለደረሰው ጉዳት በወንጀል ተጠያቂ ነው፡፡
ሆኖም ግን ለውጤቱ ምክንያት የሆነው ጉዳይ ግልፅ ካለሆነ እጅግ ውስብስብ ችግሮች
ሊፈጠሩ ይችላሉ፡፡
በዚህ ዙሪያ በተለያዩ ሙህራኖች ሁለት አይነት የምክንያትና ውጤት ንድፈ ሃሣብ
ያቀርባሉ፡፡ የመጀመሪያው በርቀት ያለ ምክንያት ነው፡፡ በዚህ ንድፈ ሃሣብ መሠረት “ይህ
ባይሆን ኖሮ” ውጤት አይከተልም ነበር በሚል ውጤቱ ከመከሠቱ በፊት ያሉ ድርጊቶች
ወይም ክስተቶችን በሙሉ ምክንያት አድርጐ የሚወስድ ነው
36
ለምሳሌ ፡- “ሀ” በቅርብ የሚያውቀው ጓደኛው “ለ”ን የልደት በአሉ ላይ እንዲገኝ ጥሪ
አድርጐለት በቀጠሮው መሠረት ልደቱ ላይ ለመገኘት “ለ” መኪናውን
እያሽከረከረ ሲሄድ አደጋ አጋጥሞት ቢሞት ለሞቱ ምክንያት “ሀ” ነው፡፡
በዚህ ንድፈ ሃሢብ መሠረት “ሀ” “ለ”ን የልደት በዓሉ ላይ እንዲገኝ ጥሪ ባያደርግለት ኖሮ
መኪና አያሽከረክርም ነበር ቢያሽከረክር ደግሞ አይሞትም ነበር በማለት ከውጤቱ በፊት
የተፈጠሩ ክስተቶች በሙሉ ምክንያት አድርገው ይቆጠራሉ፡፡
አ ንቀ ፅ 2 4 (1 )
ለምሳሌ፡- 494 እንመልከት በዚህ አንቀፅ መሠረት የእሳት ቃጠሎ ማድረስ ወንጀል
እንዲኖር አንድ ሰው በንብረት ላይ አደጋ ለማድርስ አስቦ በንብርቶቹ ላይ
ከሣት መለኮስ አለበት፡፡ ግለሰቡ እሣቱን በንብርቱ ላይ መለኮሱ ምክንያት
37
ሲሆን የንብረቱ ቃጠሎ ደግሞ ውጤት ነው፡፡ በዚህም መሠረት በአደጋውና
በድርጊቱ መካከል የምክንያትና ውጤት ግንኙነት አለ ማለት ይቻላል፡፡
1. “ሀ” ተማሪው “ሐ” ያልተገባ ባህሪ ስላናደደው በጥፊ መታው፤ ተማሪው ወዲያው
ሞተ፡፡
38
አ ንቀ ፅ 2 4 (2 )
ተከሳሹ ከፈፀመው ድርጊት በፊት እንግዳ የሆነ የሌላ ሰው አድራጐት፣ ፍጥረታዊ ነገር ወይም
አጋጣሚ ሁኔታ የተነሣ በህግ ጥበቃ የተደረገለት መብት ጉዳት ሲደርስበት ነው፡፡
ለምሣሌ፡-
“ሀ” “ለ” በተባለ ባላጋራው ክፉኛ በጥይት ቢመታና በድጋሚ “ሐ” በተባለ ሰው በጥይት
ተመቶ ቢቆስልና ቢሞት “ሐ” የተኮሰው ጥይት በህክምና ለሞት የማያደርስ መሆኑ
ከተረጋገጠ “ሀ” ለሞት ያበቃው ምክንያት የመጀመሪያው በ”ለ” የተተኮሰው ጥይት
ይሆናል፡፡ ስለሆነም በ”ሐ” ተመስርቶ የነበረው ሰው የመግደል ወንጀል ተጠያቂነት ወደ
መግደል መከራ ይቀየራል፡፡
ለ. ተደራራቢ ምክንያት
በዚህ መሠረት ለአንድ ውጤት መድረስ ከአንድ በላይ የሆኑ ምክንያቶች ሲኖሩና እነዚህም
ምክንያቶች በአንድ ጊዜ የተፈፀሙ ድርጊቶች ከሆኑ ነው፡፡
ለ ምሣ ሌ
“ሀ” “ለ” መንገድ ላይ ያገኙትን ነጋዴ ለመዝረፍ አስበው በአንድ ጊዜ በጥይት ተኩሰው
ቢገድሉት ለሞቱ ተደራራቢ ምክንያት እንዳለ ይገመታል፡፡
ለምሳሌ፡- “ሀ” “ለ”ን በጥይት ከመታው በኋላ መብረቅ ቢመታውና ቢሞት ጣልቃ የገባው
መብረቅ በ”ሀ” ድርጊት እና በ”ለ” መሞት መካከል ያለውን የምክንያት ውጤጥት
ግንኙነት ያቋርጣል፡፡
የመወያያ ጥያቄዎች
2. 24(3) አዲስ የገባ አንቀፅ ነው፡፡ በዚህ አንቀፅ መሠረት የተለያዩ ምክንያቶች
እያንዳንዳቸው ራሣቸውን ችለው አንድ ውጤት ማምጣት ባይችሉም ተደምረው
ውጤት ካስገኙ ሁሉም ለውጤቱ ምክንያቶች ናቸው ይላል ምን ማለት ነው?
በምሣሌ አብራራ፡፡
40
ጥያቄ ፡- በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ የምክንያትና ውጤት ግንኙነት መኖሩን
አለመኖሩን በዝርዝር አስረዳ
የሃሣብ ክፍል
ይህ ሶስተኛው ከዚህ በፊት ከተዘረዘሩት በአንድ ጋር መገኘት ያለበት የወንጀል ቅድመ ሁኔታ
ነው፡፡ በዚህ መሠረት አንድ ሰው በህግ ጥበቃ የተደረገለት መብት ላይ ድርጊቱን የፈፀመው
በወንጀል አጥፊነት መንፈስ መሆን አለበት፡፡ አንድ ሰው የደረሰውን ጉዳት አስቦ ወይም
በቸልተኝነት መፈፀሙ ካልተረጋገጠ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ወይም በድንገተኛ አጋጣሚ
ነገር የተፈፀመ ተደርጐ ስለሚታይ በወንጀል ህግ ሊፈርድበት እንደማይገባ አንቀፅ 57
ያሣያል፡፡ ስለሆነም ይህ ቅድመ ሁኔታ እንዲሟላ በወንጀል አጥፊነት መንፈስ ድርጊቱ
መፈፀሙን ማረጋገጥ አለብን፡፡
አ ንቀ ፅ 5 7 (1 ) (2 )
41
በኢትዮጵያ የወንጀል ህግ መሠረት የሃሣብ ክፍል ለሁለት ይከፈላል፡፡ እነዚህም አስቦ ወንጀል
ማድረግ እና በቸልተኝነት ወንጀል ማድረግ ተብለው የራሣቸውን ንኡሣን ክፍል ይዘው
ይገኛሉ፡፡
በአንቀፅ 58(1)(ሀ) መሠረት እውቀትና ፍላጐት ሁለት የቀጥተኛ የሆነ አጥፊነት ቅድመ
ሁኔታዎች እንደሆኑ ያሣያል፡፡
እውቀት
ለምሳሌ “ሀ” የተባለው የአዲስ አበባ ነዋሪ የኤች አይ ቪ ቫይረስ በደሙ ውስጥ እንዳለ
እያወቀና ሆን ብሎ የፍቅር ጓደኛውን ለመጉዳት አስቦ ያለጥንቃቄ የግብረ ስጋ
ግንኙነት ቢፈጽምና ጓደኛው የኤች አይ ቪ ቫይረስ ቢገኝባት “ሀ” የኤች አይ ቪ
42
ቫይረስ በግብረ ስጋ ግንኙነት እንደሚተላለፍ አላውቅም ብሎ ሊከራከር
አይችልም፡፡ ይህ በተለይ አዲስ አበባን በመሰለና የመገናኛ ብዙሃን በየቀኑ ስለ
በሽታው መተላለፊያ መንገድ በሚሰብኩበት ከተማ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
43
ፍላጐት
አንድ ወንጀል አድራጊ ፍላጐት ነበረው ለማለት የድርጊቱን መፈፀም ወይም በድርጊቱ ምክንያት
የሚገኘውን ውጤት ፈልጐ በፍቃደኝነት ሲፈፅም ነው በዚህም መሰረት ከወንጀል ድርጊቱ
የተነሳ የደረሱት ውጤቶች አስቀድመው የታዩ እና የተፈለጉ ናቸው፡፡
ቸልተኝነት ከስሙ እንደምንረዳው አንድ ሰው ጥንቃቄ ማድረግ ሲገባው ሣያደርግ ሲቀር ነው፡፡
በዚህም የጥንቃቄ ጉድለት ምክንያት ያልተፈለገ እና ሊወገድ የሚችል ጉዳት ሲደርስ ነው፡፡
አንቀፅ 59(1) የቸልተኝነት አይነት ሁለት ናቸው፡፡
44
የታወቀ ቸልተኝነት
በ59 (1) (ሀ) መሠረት አንድ ሠው በታወቀ ቸልተኝነት ሊቀጣ የሚችለው ድርጊቱ በወንጀል
የሚያስቀጣ ውጤት ሊያስከትል እንደሚቻል እያወቀ አይደርስም በሚል ግምት ወይም
ባለማመዛዘን የፈፀመ እንደ ሆነ ነው፡፡ በሌላ አነጋግር ድርጊቱ ጉዳትን እንደሚያስከትል
ያውቃል ሆኖም ግን የድርጊቱን ውጤት አይቀበልም፡፡ ምክንያቱም ድርጊቱ ጉዳት ያደርሣል
ብሎ አያምንም ወይም ጉዳት ለመከላከል እያደረገ ያለው ጥንቃቄ በቂ በመሆኑ ጉዳት
አይደርስም የሚል ግምት አለው፡፡
አንድ የታከሲ ሹፌር ባለቤቱ ስልክ ደውላ ስታናግረው የመኪናውን መፍጠን ተረድታ “ረጋ
ብለህ ሂድ” ብላ ብትጠይቀውና እሱም፡፡ 15 አመት መኪና የመንዳት ልምድ አለኝ አታሰቢ
ቢል” እና ከ2 ደቂቃ በኋላ ሰው ገጭቶ ቢገድል በዚህ አንቀፅ ይታያል
ያልታወቀ ቸልተኝነት
አ ንቀ ፅ 5 9 (1 ) (ለ )
45
በአንቀፅ 59(1) (ለ) መሠረት ያልታወቀ ቸልተኝነት የሚባለው ወንጀል ፈፃሚው ድርጊቱ
ጉዳት እንደሚያስከትል ሳያውቅ ሲቀር ወይም ጥንቃቄ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ባለመገንዘቡ
ጉዳት ሲያደርስ ነው፡፡
ቸልተኝነት እና ቅጣት
አ ንቀ ፅ 5 9 (2 )
በዚህ በአንቀፅ መሠረት ቸልተኝነት በህጉ ላይ በተለይ ያስቀጣል ተብሎ ካልተደነገገ በቀር
በቸልተኝነት የተፈፀመ ወንጀል አያስቀጣም ስለሆነም አንድ ድርጊት ወይም ያለማድረግ
በቸልተኝነት ቢፈፀሙ ሊያስቀጡ የሚችሉት ህጉ በግልፅ የወንጀል ተጠያቂነት መኖሩን
ካስቀመጠ ነው፡፡
የመወያያ ጥያቄዎች
46
ሲፈፀም የሚያስቀጣ እንደሆነ አይገልፁም፡፡ እነዚህ በግልፅ የሃሣብ ክፍሉን
የማይገልፁ አንቀፆች ቢያጋጥምህ/ሽ በየትኛው መመደብ አለበት?
ሌላ?
አ ንቀ ፅ 3 4 (1 )
በዚህ አንቀፅ መሠረት በህግ የሰውነት መብት ያላቸው ድርጅቶች የመንግስት አስተዳደር
አካላትን ሣይጨምር ወንጀል ፈፅመው በተገኙ ጊዜ እንደሚከሰሱና እንደሚቀጡ በአዲስ መልክ
እንዲገባ ተደርጓል፡፡ ይህ እስከአሁን የተመለከትነውን ሦስቱ የወንጀል ቅድመ ሁኔታዎች ጋር
በልዩነት የተቀመጠ ድንጋጌ ነው፡፡ ስለሆነም በአንቀፅ 513፣ 716፣ 777 መሠረት በህግ
47
የሰውነት መብት ያላቸው ድርጅቶች የተፈፀመ ወንጀል አንቀፅ 23(3) ላይ የተጠቀሰው የሃሣብ
ክፍል በቅድመ ሁኔታነት አይታይም፡፡
ጥያቄዎች፡-
1. በህግ ሰውነት የተሰጠው አካል ወንጀል ፈፅሞ ቢገኘና ለዚህ ለፈፀመው ወንጀል
በህጉ ላይ የተቀመጠው ቅጣት እሰራት ቢሆን ምን ማድረግ አለበት?
የመሠናዳት ተግባሮች
መቼ መግደል እንዳለበት?
ከዚያም አለፎ ያስበውን ለመፈፀም መሣሪያዎችን ቢገዛ ወይም ሌሎች ምቹ ሁኔታዎች ቢፈጥር
በአንቀፅ 26 መሠረት አያስቀጣም፡፡
የወንጀል ሙከራ
አ ንቀ ፅ 2 7 (1 )
49
መጨሻው ተከታትሎ አስፈላጊ የሆነውን ውጤት ያላገኘ ቢሆንም በመሞከሩ ብቻ
ጥፋተኛ ይሆናል፡፡
ሀ . ሃ ሣብ
አንድ የወንጀል ድርጊት ተጀመረ የሚባለው መቼ ነው? ለምሣሌ “ሀ” በግጦሽ መሬት ምክንያት
ከ”ለ” ጋር ስለተጣላ ለመግደል ወስኖ ህገ ወጥ ጠመንጃ ከዘመዱ ላይ ገዛ፡፡ ያስበውን ለመፈፀም
ዛሬ ከምሽቱ 12 ሠዓት ሲሆን ወደ “ለ” ቤት አመራ በዚህ ምሣሌ መሠረት”ሀ” የወንጀለ
ድርጊቱን የጀመረው መቼ ነው
ጠመንጃ ሲገዛ?
“ለ”ን ሲያየው?
ሲተኩስ?
ወይስ ሌላ?
50
አንድ ሊሰርቅ ያሰበ ሰው እና ሰው ለመግደል ያሰበ ሰው ወንጀሉን ጀመረ የሚባልበት ጊዜ
የተለያየ ነው፡፡ የወንጀል አጀማመር ከጉዳይ ጉዳይ ይለያያል፡፡ ይሄንን ለመመለስ የቀረበልንን
ጉዳይ በጥንቃቄ ማየት ይጠይቃል፡፡ ጊዜውን መለየት ከቻልን ተጠርጣሪው በዝግጅት ላይ ነው
ወይንስ በሙከራ የሚለው መልስ ያገኛል፡፡
ሌላው መታየት ያለበት ጉዳይ የወንጀል ድርጊቱ መፈፀም የለበትም፡፡ የታሰበው ወንጀል
ከተፈፀመ ሙከራ ሳይሆን ፍፃሜ ያገኘ ወንጀል ነው፡፡ የወንጀል ህጉ አንቀፅ 27(1) ላይ
እንደተመለከተው ሙከራ ሁለት አይነቶች ናቸው፡፡
ሀ. ፍፃሜ ያላገኘ
ከዚሁ ጋር ተያይዞ ያለው ሌላው ፈፅሜ ያላገኘው ሙከራ ወንጀል አድራጊው እስከ መጨረሻው
ለመከታተል ያልቻለው ነው፡፡ ይህ ሙከራ ፍፃሜ ያለገኘው በራሱ ፈቃድ ሣይሆን በሌላ
ውጫዊ ምክንያት ነው፡፡ ወንጀል ፈፃሚው ያሰበውን ለመፈፀም ፈቃደኛ ሰለሆነ ጀምሮታል፡፡
ሆኖም ግን እንቅፋት አጋጠመው፡፡ በቅድሙ ምሣሌ መሠረት “ሀ” ወንጀሉን ለመፈፀም
ጠመንጃውን ካነጣጠረ በኋላ በአከባቢው የሚያልፍ ሰው ስላየው አቋረጠ፤ ይህ ከራሱ ፍላጐት
የመጣ አይደለም፡፡ ሰው ባያየው ንኖ ወንጀሎን መጨረሻ የማድረስ እቅድ ነበረው፡፡
51
ለ. ፍፃሜ ያገኘ
በአንቀፅ 27(2) መሠረት በህጉ ላይ ተቃራኒ ድንጋጌ ከሌለ በስተቀር የወንጀል ሙከራ ሁል
ጊዜም የሚያስቀጣ ነው፡፡ አድራጊው በመደቡ ለመፈፀም በፈለገው ወንጀል የተደነገገውን ቅጣት
ይቀጣል፡፡ ሆኖም ግን ፍርድ ቤቱ ሙከራው የተፈለገውን ውጤት ያላስገኘበትን ምክንያት
ከርምት ውሰጥ በማስገባት ቅጣቱን ሊቀንስ ይችላል፡፡ ቅጣቱ ሊ ቀ ንስ የሚቻልበባቸው
ምክንያቶች አንቀፅ 28 ላይ ተዘርዝረዋል፡፡
አ ንቀ ፅ 2 8 (1 )
አድራጊው ሊፈጽመው የነበረውን የወንጀል ድረጊት በገዛ ፍቃዱ የተወ እንደሆነ፤ የነገሩ
ሁኔታዎች የሚገቡ ምክንያቶችን ሲያስገኙ ፍርድ ቤት በሕግ በተፈቀደው ወሰን
መሠረት (አንቀፅ 179) ወይም እንደመሰለው (አንቀፅ 180) ቅጣቱ ያቃልልለታል፡፡
የወንጀል ድርጊቱን የተወው በሐቀኝነት ወይም ከፍ ባለ የሕሊና ስሜት በመነሳሳት
ምክንያት እንደሆነ፤ ፍርድ ቤቱ ከቅጣት ነፃ ያደርጋዋል፡፡
52
ሊፈፀም የማይቻል ወንጀል
አ ንቀ ፅ 2 9
ለምሣሌ፡- “ሀ” “ለ”ን ለመግደል አስብ መረዝ በመስጠት ፋንታ ተሣስቶ ስኳር
ወንጀሉ ሊፈፀም ያልቻለበት ሁለተኛው ምክንያት ወንጀል ሊፈፀምበት የተሳበው ነገር ወይም
ጣባይ ነው፡፡ ለረጅም ጊዜ ጐረቤቱን ለመግደል ሲያስብ የነበረ ሰው ከለታት አንድ ቀን መንገድ
ላይ ሞቶ ቢያገኘውና በጥይት ቢመታው ያሰበውን ውጤት ማግኘት አይቻልም፡፡ ምክንያቱም
የሞተን ሰው መግደል ማሰብ ሊፈፀም የማይቻል ወንጀል ስለሆነ ነው፡፡
53
የመወያያ ጥያቄዎች
54
ምዕራፍ አራት
የምዕራፉ አላማዎች
በወንጀል አፈፃፀም ላይ ተከፋይ መሆን ማለት በአንድ የወንጀል ድርጊት ከአንድ ሰው በላይ
ከአጀማመሩ እስከ ፍፃሜው ባለ ው ሂደት ውስጥ በተለያዩ ደረጃዎች መሣተፋቸውን
ያመለክታል፡፡ ወንጀል በአንድ ሰው የወንጀል ሃሣብ ጠንሣሽነት ተጀምሮ በዚሁ ሰው ድርጊቶች
ፍፃሜ ሊያገኝ እንደሚችል ሁሉ የሌሎች ሠዎች የተለያየ ችሎታና ተሣትፎ ተጨምሮበት
ሊጠናቀቅ ይችላል፡፡
በ1949 ዓ.ም በወጣው የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ቁጥር 32 ስያሜ “ስለዋና ወንጀል አድራጊው
እና ግብረአበሮቹ” የሚል የነበረው በአሁኑ ስያሜ በዋና ወንጀል አድራጊነት በሚል ተቀይሯል፡፡
ይህ አሁን በስራ ላይ ያለው የወንጀል ህግ አንዱና መሠረታዊ ለውጥ ነው፡፡ ይህ የሆነበትን
55
ምክንያት ፍትህ ሚኒስቴር ባተመው ሃተታ ዘምክንያት ላይ እንደተገለፀው የቀድሞው ህግ
ድንጋጌ ስያሜ አንድ ቀንደኛ ወንጀል አድራጊ እንዳለና ሌሎቹ ግን ከርሱ ያነሰ ሚና ያላቸው
ረዳቶች እንደሆኑ ያሳያል፡፡ ከዚህም ሌላ ሁለት ወንጀል አድራጊዎች በወንጀል አድሪጊዎች
በወንጀሉ አፈፃፀም ላይ በግብር ወይም በድርጊት ላይሣተፉ ይችላሉ፡፡ አንዳንዶቹ በቀጥታ
በድርጊት ተካፋይ ቢሆኑም ሌሎቹ ሀሣብ ወይም መመሪያ በመስጠት ብቻ ተሣታፊ ሊሆኑ
ይችላሉ፡፡ ግብረ አበሮች የሚለው ግን በግብር ወይም በድርጊት ተካፋይ የሆኑትን ብቻ
ያመለክታል ሆኖም ይሄንንና ሌሎች በንዑስ ቁጥር አንድ መግቢያ እንደሚያስረዳው በፊደል
ከ(ሀ)(ለ) እና (ሐ) የተዘረዘሩት ወንጀል አድራጊዎች ሁሉ እንደ ዋና ወንጀል አድራጊ እንጂ
አንዱን እንደ አብይ ወንጀለኛ ሌሎቹን እንደ አነስተኛ ወንጀለኞች የሚቆጥረውን በማሶገድ
በስያሜውም ሆነ በይዘቱ እንዲስተካከል ተደርጓል፡፡ ዋና ወንጀል አድራጊነት በተለያዩ ገፅታዎች
ሊከሰት ይቻላል፡፡
በቀጥታ ወይም በእጅ አዙር በተለይም በእንስሳ ወይም በተፈጥሮ ኃይል አማካይነት
በእርግጥ ወንጀሉን አድርጐ እንደሆነ፤
በአንቀፅ 32(1)(ሀ) መሠረት ማንም ሠው በዋና ወንጀል አድራጊነት ወንጀል እንዳደረገ ተቆጠሮ
የሚቀጣው በቀጥታ ወይም በእጅ አዙር በተለይም በእንሰሣ ወይም በተፈጥሮ ኃይል አማካኝነት
በርግጥ ወንጀሉን አድርጐ እንደሆነ ነው ይላል፡፡ የዚህ ዋና ወንጀል አድራጊነት ገፅታዎች
ሁለት ናቸው፡፡ እነኚህም በቀጥታ የሚለው በግል ድርጊት ወይም አካላዊ እንቅስቃሴ በቀጥታ
መፈፀም እና በተዘዋዋሪ ተብለው የተቀመጡት በእንሰሳና በተፈጥሮ አማካኝነት መፈፀም ናቸው
ለምሳሌ ፡-
56
o በተመሣሣይ “ሀ” “ለ”ን ለመግደል አሰቦ “ሀ” በቤት ውስጥ መተኛቱን እያወቀ
እሣት ለኩሶ ቢያቃጥለውና በእሣቱ ምክንያቱ “ለ” ቢሞት አሁንም “ሀ”
ወንጀሉን በቀጥታ ፈፅሞታል፡፡
አ ንቀ ፅ 3 2 (1 ) ( ለ )
ለምሳሌ ፡-
ምን እንደሚዘርፍ አቀደ
57
በሌላ ሰው ወንጀሉን መፈፀም
አንቀፅ 32(1) (ሐ)
አ ንቀ ፅ 3 2 (2 )
የተደረገው ወንጀል ከአድሪጊው አሳብ በላይ ያለፈ እንደሆነ፤ ጉዳዩ የሚታየው በአንቀጽ
58(3) በተመለከተው መሰረት ነው፡፡
እነዚህ አንቀፆች እንደሚያሣዩት በዋና ወንጀል አድሪጊነት የተሣተፉት ሁለት ሰዎች ምንም
እንኳን ማናቸው የተለያየ ቢሆንም ተጠየቂነታቸው እኩል ነው፡፡ በዚህ ረገድ በሞራል
ወንጀለኛው እና ቀጥታ በአካል ወንጀሉን በፈፀመው ሰው መካከል ምንም ልዩነት አይደረግም፡፡
ሆኖም ግን ቅጣቱ የሚላከው እያንዳንዱ ወንጀለኛ ሊፈፅም ባሰበው ልክ ነው፡፡ በአንቀፅ 58(3)
መሠረት አንድ ሰው በላወቀው ባልፈለገው ወይም በቀጥታ ወይም በአጋጣሚ ከሃሣቡ በላይ
በሆነው ነገር ሊፈረድበት አይቻልም፡፡
58
ለምሣሌ፡- “ሀ” የተባለው የሞራል ወንጀለኛ “ለ” እና “ሐ” ባንክ እንዲዘረፉ ሁሉንም
አቅድ አውጥቶ ቢልካቸውና ሆኖም ግን “ለ” የባንኩ ዘበኛ አላስገባ ሲለው
በጥይት ዘበኛውን ቢገድል፤ በግድያው ለይ “ሀ” ተጠያቂ አይደለም፡፡
ምክንያቱም በእቅዱ የሌለ እና ያላሰበው ስለሆነ ነው፡፡ በዘበኛው መሞት
ያልፈለገው እና ከሃሣቡ በላይ ነው፡፡
የመወያያ ጥያቄዎች
3. በአንቀፅ 32(1) (ሐ) ላይ “ህፃንን” ተብሎ የተገለፀው እድሜው ስንት አመት የሆነውን
ነው?
5. “ሀ” አንድ የመንግስት ባንክ እንዲዘርፍ እቅድ ያወጣና መሣሪያ ይገዛል፣ ጊዜ ይወስንና
ለጓደኞቹ ለ “ሐ” እና “መ” ያዋያቸዋል፡፡ እነሱም ሃሣቡን ይቀበሉና ትናንት ምሽት
ዘረፋውን ለማከናወን “መ” እና “ሐ” ወደ ባንኩ በ “ሀ” እቅድ መሠረት ይሄዳሉ፡፡
የባንኩን በር ሰብረው ወደ ጊቢው ከገቡ በኋላ “መ” እኔ በዚህ ሃሣብ አልስማማም ወደ
ቤቴ እሄዳለሁ ብሎ “ሐ” እዛው ትቶት ይሄዳል፡፡ “ሐ” በወጣለት እቅድ መሠረት
ዘረፋውን አከናውኖ ይመለሣል፡፡ ሁሉም ዋና ወንጀል አድራጊ ናቸው? እኩልስ
ይጠየቃሉ፡፡
59
ሌሎች ተካፋይነት
ወንጀሎች ከፀባያቸው የተነሣ በሁሉም ሰዎች ሊፈፀሙ አይችሉም፡፡ አንድ አንድ ወንጀሎች
የተለዩ ሰዎች ብቻ ይፈፀማሉ፡፡ በአንቀፅ 33 መሠረት ወታደራዊ ወንጀሎችን ለመፈፀም
ወታደር መሆንን ይጠይቃል፡፡ ከመንግስት ስራ ጋር የተያያዙ ወንጀሎችን ለመፈፀም
የመንግስት ሠራተኛ ብቻ መሆንን ሊጠይቅ ይችላል፡፡ ሆኖም ግን ወንጀል አድራጊው የተባለው
ልዩነት ባይኖረውም በሙሉ ፈቃድና እውቀቱ የወንጀሉ ተካፋይ ከሆነ በዋና ወንጀል አድራጊነት
ተጠያቂ ይሆናል፡፡
ማነሣሣት
አ ንቀ ፅ 3 6 (1 )
60
ለወንጀል ቀጥተኛ ወይም ተዘዋዋሪ አስተዋፅኦ ሊያደርጉ ከሚችሉ ተሣታፊዎች አንዱ አነሣሽ
ነው፡፡ አንድ ሰው ወንጀሉን ራሱ በተለያየ መልኩ በቀጥታ ተሣትፎ ባይፈፅመውም ሌሎች
እንዲፈፅሙት እና የተፈለገውን ውጤት እንዲገኝ ሊያደርግ ይችላል፡፡ በአንቀፅ 36 መሠረት
ሌሎች ሰዎችን በመሣሪያነት በመጠቀም ወንጀል ሊፈፀም ከሚቻልባቸው መንገዶች አንዱ
ወንጀልን በአካል የሚፈፅመው ሰው ማነሣሣት ነው ሆኖም ግን አንድ ሰው ሌላውን በተለያዩ
ዘዴዎች ወንጀል እንዲፈፅም አነሣስቷል ከማለታችን በፊት የሚከተሉትን ነጥቦች በጥንቃቄ
ማየት ይገባል፡፡
ማነሣሣት ምን ጊዜም በአውቆ አጥፊነት መፈፀም ያለበት ወንጀል ነው፡፡ ሰለሆነም አነሣሹ
የማነሣሣት ድርጊቱን የሚፈፅመው አውቆ ፈልጐና ውጤት እንዲገኝ በማሰብ ነው፡፡
ለምሳሌ አንድ የህክምና ባለሞያ ከጓደኛው ጋር በሻይ ሰዓት ሲወያይ ስለተማረው ትምህርት
እና ለሞት የሚያበቁ የመድሃኒት አይነቶች ቢያጫውተው እና ሠው ለመግደል ሃሣብ
የነበረው ጓደኛው ውሣኔ ላይ ደርሶ የግድያ ወንጀል ቢፈፅም የህክምና ባለሞያው ድርጊቱን
በአውቆ አጥፊነት ስላልፈፀመው ወይም ድርጊቱ እንዲፈፀም ፍላጐት ስላልነበረው በአነሣሽነቱ
ሊጠየቅ አይገባውም፡፡
አ ንቀ ፅ 3 6 (2 )
በአንቀፅ 36(2) መሠረት አነሣሹ ለአነሣሣው ወንጀል የሚቃጣው ቢያንስ ተሞክሮ እንደሆነ
ነው፡፡ ሊነሣሣ የታሰበው ሰው ወንጀሉን ካልሞከረ ወይም ካልፈፀመ በስተቀር ስለማይቀጣ
የማነሣሣት ተግባር የፈፀመውም ሰው አይቀጣም፡፡ ቅጣቱም የሚወሰነው ሊደረግ ለታሰበው
ወንጀል ህጉ በተደነገገው ቅጣት ልክ ነው፡፡
አባሪነት
አ ንቀ ፅ 3 7 (1 )
62
ወንጀል የሚያደርግበትን ዘዴ ወይም መሣሪያ ወይም ግዙፋዊ እርዳታ በመስጠት
ወይም ለወንጀሉ አፈፃፀም በሚጠቅም በማናቸውም ሌላ ዓይነት መንገድ አስቦ የረዳው
እንደሆነ ነው፡፡
አባሪነት የወንጀል ተሣትፎ አንድ ገፅታ ሲሆን ዋናው ወንጀል አድራጊ በተለያየ ጊዜ ከሌሎች
ሰዎች የሚያገኘው እገዛ ነው፡፡ የአባሪነት እርዳታ በተለያየ መልክ ሊሰጡ ይችላሉ፡፡
እርዳታዎቹ ቁሣዊ ወይም ሞራላዊ ወይም አካላዊ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ወንጀሉን የሚፈፅምበት
መሣሪያ መስጠት ቁሣዊ እርዳታ ነው፤ ስለወንጀሉ አፈፃፀም የሚመለከት መረጃ መስጠት
ሞራላዊ ድጋፍ ሊሆን ይችላል፡፡ ወንጀሉ በሚፈፀምበት አከባቢ ሰዎች እንዳይደርሱ ማድረግ
አካላዊ እርዳታ ነው ማንም ሰው በሰጠው እርዳታ በወንጀል ድርጊት አባሪ ነው ተብሎ ተጠያቂ
የሚሆነው የሚከተሉትን ግርምት ውስጥ በማስገባት ነው፡፡
የሃሣብ ክፍል
አባሪነት ምን ጊዜም ቢሮን በአወቆ አጥፊነት የሚፈፀም ወንጀል ነው፡፡ አንድ አባሪ የሚሰጠው
እርዳታ የወንጀሉ ስራ እንዲቃና በማሰብ የተሰጠ መሆን አለበት፡፡ ስለሆነም እርዳታ
በቸልተኝነት ከተሠጠ አባሪነት የለም፡፡
የአባሪነት ጊዜ
የአባሪነት እርዳታ ወንጀሉ ከመፈፀም በፊት ወይም በመፈፀም ላይ እንዳለ የተሰጠ መሆን
አለበት፡፡ ስለሆነም ወንጀሉ ከተፈፀመ በኋላ የሚሰጥ እርዳታ የአባሪነት እርዳታ ሊሆን
አይችልም፡፡ ወንጀሉ ከመፈፀሙ በፊት እርዳታ የሚሰጥ ሰው ዋና ወንጀል አድራጊ ወይም
አነሳሽ አድርጐ መመደብ አይቻልም፡፡ ምክንያቱም ማንንም እንዲወሰን አላነሣሣም፡፡ ያደረገው
ነገር ቢኖር ወንጀል ለመስራት ወስነው የመጡ ሰዎችን የሚያስፈልጋቸውን እርዳታ ማቅረብ
ነው፡፡
63
የእርዳታ አይነቶች
እርዳታው በተለያዩ መልኩ ሊሰጥ ይችላል፡፡ ቁሣዊ ሊሆን ይችላል ለምሣሌ የሚዘረፈውን ቤት
ቁልፍ፡፡ ሞራላዊ ሊሆን ይችላለ ለምሣሌ ምክር መለገስ እና የተለያዩ መረጃዎችን ማቀበል፡፡
በአካል ተኝቶ መርዳትም ሊሆን ይችላል፡፡ ለምሣሌ ወንጀሉ በሚፈፀምበት አከባቢ የሚያልፍ
ሰው መኖሩን እና አለመኖሩን መከታተል፡፡ ሆኖም ግን ሁል ጊዜ የሚያከራክሩ ጉዳዮች
በአባሪነት ላይ ይነሣሉ
የአባሪነት ውጤት
አ ንቀ ፅ 3 7 (2 ) ( 3 )
በዚህ አንቀፅ መሠረት አባሪ በተሞከረው ወንጀል ልክ ይቀጣል፤ ከላይ ስለአነሣሽነት በቀረበው
ማብራሪያ ላይ አነሣሽነት እንደሚያስቀጣና የተነሣሣው ሰው ቢያንስ ወንጀሉን መሞከር
እንደለበት አነሣሹ ለተሞከረው ወይም ለተፈፀመው ወንጀል በተደነገገው ቅጣት አንደሚቀጣ
ተገለፆል፡፡ ተመሣሣይ ስለሆነ መንግድም አያስፈልግም፤ ሆኖም ግን በህጉ ልዩ ክፍል ውስጥ
64
በግልፅ ያስቀጣል ተብሎ ከተደነገገ እርዳታ የሰጠው ሰው አባሪ ሣይሆን ዋናው ወንጀል
አድራጊ ይሆናል፡፡
የመወያያ ጥያቄዎች
2. ማነሣሣት በስልክና በደብዳቤ ይቻላል? በሶስተኛ ወገንሰ? ለምሣሌ “ሀ” “ለ”ን በአካል ወይም
በስልክ አግኝቶ ማነሣሣት ስላልቻለ “መ” የተባለ ጓደኛውን እንዲያነሣሣለት ጠይቆ
የማነሣሣቱ ስራ ተሣካለት፡፡ ማነው አነሣሽ? ተወያዩ
ሰው መግደል
የወንጀል ድርጊቶች ከሚያደርሱት ጉዳት አንፃር ደረጃ ይውጣላቸው ከተባለ በመጀመሪያ ደረጃ
የሚመደበው ወይም መመደብ ያለበት በሰው ህይወት ላይ የሚፈፀም ወንጀል ነው፡፡ በሌሎች
ወንጀሎች የተጐዳ ሰው ሊያጣ የሚችለው የተወሰነ ነገር ሲሆን ህይወቱ የጠፋ ሰው ግን
የሚያጣው ሁሉንም ነገሩን ነው፡፡
በህይወት መኖር የሰው ልጅ ሰብአዊ መብቱ ነው፤ ሰብዓዊ መብት ስንል ሰው ሰብዓዊ ፍጡር
በመሆኑ ብቻ የሚኖረው መብት ነው፡፡ የኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀፅ 10(1) ላይ “ከሠው
ልጅ ተፈጥሮ የሚመነጩ” ሲል ሰው ሰው ሆኖ በመወለዱ ብቻ ማናቸውም ቅድም ሁኔታ
ሣያስፈልግ የሚኖሩት መብቶች ለማለት ነው፡፡
የኢትዮጵያ የወንጀል ህግ ይሄንን መሠረታዊ የሰው ልጆች መብት ጥበቃ ለማድረግ አምስተኛ
መፅሃፍ ላይ ከአንቀፅ 538 ጀምሮ ደረጃ በደረጃ አስቀምጧል፡፡ እነዚህም እንደ ቅደም
65
ተከተላቸው ከባድ አገዳደል ተራ የሆነ አገዳደል እና ቅጣትን የማያቀል አገዳደል ተብለው
ተለይተው ተቀምጠዋል፡፡ አንቀፅ 539 ቅጣትን የሚያከብዱ ምክንያቶች የየዘ ሲሆን አንቀፅ
541 ደግሞ የማቅለያ ምክንያቶችን ይዟል፡፡ ሆን ተብሎ የሚፈፀም የሰው መግደል ወንጀል
በአንቀፅ 539 ከተገለፀው የቅጣት ማክበጃ ወይም በህጉ አንቀፅ 541 ከተገለፀው የቅጣት ማቅለያ
ውጭ ከሆነ ደግሞ ድርጊቱ የሚሸፈነው በአንቀፅ 540 ነው፡፡
1. ማንም ሰው፡-
በሞት ይቀጣል፡፡
በዚህ አንቀፅ መሠረት ከባድ ስለሆነ የሰው ግድያ ይዘረዘራል፡፡ ሰዎች በማህበራዊ ኑሮ ውስጥ
ከሚፈፅሟቸው ተግባራት ጨካኝ ነውረኛ አደገኛ የሚያሰኛቸው ሰው ከገደሉ ነው፡፡ ሆኖም ግን
በአንቀፅ 539 መሠረት ጨካኝ ነውረኛ የሚያሰኘው ሰውን መግደል ብቻ ሣይሆን በአፈፃፀሙ
ረገድ የሚደረገው ክንውን ለማሳየት ይመስላል፡፡ ስለሆነም ጨካኝነት፣ ነውረኛነት እና አደገኛነት
66
ለማቋቋም ሊኖር የሚገባው መመዘኛ መሠረት የሚደረገው ምክንያት ምንድን ነው? ይህ
የህብረተሠቡን ማህበራዊ እድገትና ባህላዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ አስገብቶ ትርጉም ለማስጠት
መሻት አስቸጋሪ ነው፡፡ እንቁላል ሌባን በሚኮንነው እና የአባትን ገዳይ መግደል በሚያሞግሰው
ህብረተሠብ ባህል ውስጥ በተፈጠረ ስነ ልቦና የነውረኛነት መስፈሪያ መነሻ የሚያደርገው
ምንድን ነወ? ይህ በጥንቃቄ መታየት የሚገባውና የህጉ መንፈስ እና አላማን ከግምት ወስጥ
ያስገባ ትርጉም መስጠት አሰአላጊ ነው፡፡
በንኡስ አንቀፅ ቁጥር 2 መሠረት ግድያ የፈፀመ ሰው የሞት ቅጣት የሚፈረድበት አስቀድሞ
ለፈፀመው ወንጀል የእድሜ ልክ ጽኑ እስራት የተፈረደበት ወንጀለኛ ሁሉ ሣይሆን የእድሜ ልክ
ጽኑ እስራት ተፈርዶበት ቅጣቱን በመፈፀም ላይ እያለ ከባድ የግድያ ወንጀል የፈፀመ ብቻ
ነው፡፡ የዚህ አይነቱን ወንጀለኛ በሞት እንዳይቀጣ የሚያደርግ ምንም ማቀለያ ምክንያት
የሌለው በመሆኑ ምንጊዜም ቢሆን የሞት ቅጣት ሊፈርድበት ይገባል፡፡ የእድሜ ልክ ፅኑ
እስራት ቢፈረድበትም ቅጣቱን በመፈፀም ላይ ያልሆነ ወንጀለኛ ግን ሰው በሚገድልበት ጊዜ
የእድሜ ልክ አስራት በመፈፀም ላይ የሚገኘውን ወንጀለኛ ያህል አደገኛ ነው የማይባልበት ጊዜ
ሊኖር ይችላል፡፡ ሁኔታው እየታየ የሞት ቅጣት ወይም የእድሜ ልክ ፅኑ እስራት ሊፈረድበት
ይችላል፡፡
ሆኖም ግን የእድሜ ልከ እሰራት ተፈርዶበት ቅጣቱን በመፈፀም ላይ እያለ በንዑስ ቁጥር አንድ
ለይ የተመለከተው ከባድ ግድያ ብቻ ሲፈፅም፤ የሞት ቅጣት ይፈረድበታል እንጂ ከዚህ ውጭ
አስቦም ይሁን በቸልተኝነት ወይም በህጋዊ መከልከል በሚገድልበት ጊዜ መሆን ያለበትም፡፡
67
በአንቀፅ 540 ላይ ስለ ተራ የሆነ የሰው ግድያ ተመልክቷል “ተራ” የሚለው ቃሉ የግድያውን
ቀላልነት የሚያሣይ ሣይሆን በከባድ ግድያ በቀላል ግድያ መካከል የሚገኘውን የግድያ አይነት
ነው፤ ምን አይነት ናቸው፡፡
በአንቀፅ 541 ላይ ቀላል ስለሆነው የሰው ግድያ ተመልክቷል፡፡ ይህ አንቀፅ በቅድሞው 524
ላይ በተደነገገው መሠረት ቀላል ግድያ የሚባለው በመኖሪያ ቤቱ ወይም በአጥሩ ግቢ ሌላ ሰው
ከገባ በተንኮል የገባውን ሰው ሊያስግድል በሚጥርበት ጊዜ ሰው የገደለ እንደሆነ ነበር፡፡
68
ማጥፋቱ እየታወቀ ቀላል የእስራቱ መነሻ እስር ቀን የመቀጫውን ደግሞ አንድ ብር ብሎ
መደንገጉ ፈፅሞ ተቀባይነት የሌለው ጉዳይ ነበር፡፡
ንዑስ አንቀፅ (2) መሠረት የሚያስቀጣው ሙያዊ ሆኖ ጥንቃቄ መውሰድ ሲገባው በከባድ
ቸልተኝነት ሰው የገደለ እንደሆነ ነው፡፡ ለዚህ አይነቱ ወንጀል የቅጣት መነሻው ከፋ ቢል ሰው
ተጠንቅቆ የሞያ ግዲታውን ይወጣል ተብሎ ስለሚገመት ቅጣቱ ከፍ ተደርጐ ተደንግጓል፡፡
ንዑስ አንቀፅ (3) መሠረት ብዙ ጊዜ ከአንድ በላይ በሆነ ሰዎች ላይ በጠንቃቄ ጉድለት የተነሣ
ስለሚደርስባቸው ጉዳት ነው፡፡
አ ንቀ ፅ 2 6 9
69
ለ. የማኅበረሰብቡ አባላት በዘር እንዳይራቡ ወይም በሕይወት እንዳይኖሩ ለማድረግ
ማናቸውንም ዘዴ በሥራ ላይ ያዋለ እንደሆነ፤ ወይም
ከዚህም አንፃር የዘር ማጥፋት ተግባር አለም አቀፋዊ ወንጀል በመሆኑ በአገራችን የወንጀለኛ
መቅጫ ህግ ውስጥ አቀማመጡ ይህን ይዘት በሚያካትት መልክ ነው፡፡
70