Professional Documents
Culture Documents
ማውጫ
ክፍል አንድ ................................................................................................................................................... 1
አጠቃላይ መግቢያ ......................................................................................................................................... 1
1.1 መግቢያ .............................................................................................................................................. 1
1.2 የኮሚሽኑ የሰብአዊ መብቶች ክትትል ሥልጣን እና ኃላፊነት ......................................................... 1
1.3 የሥራ መምሪያው ዓላማ .................................................................................................................. 2
1.4 የሥራ መምሪያው የተፈጻሚነት ወሰን............................................................................................. 2
ክፍል ሁለት .................................................................................................................................................. 3
የሰብአዊ መብቶች ክትትል ተግባራት መሠረታዊ ሐሳቦች .......................................................................... 3
2.1 የሰብአዊ መብቶች ክትትል ትርጓሜ ................................................................................................. 3
2.2 የሰብአዊ መብቶች ክትትል ሥራ ዓላማዎች .................................................................................... 3
2.2.1 የሰብአዊ መብቶች ይዘት ሁኔታን መሰነድ እና የአፈጻጸም ደረጃዎችን ማሳየት ..................... 3
2.2.2 የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች እንዳይከሰቱ መከላከል ................................................................... 3
2.2.3 ለሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች አፋጣኝ እርምት እና ምላሽ እንዲሰጥ ማድረግ............................ 4
2.2.4 ለሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች መፍትሔ ማፈላለግ ...................................................................... 4
2.2.5 የሕግ፣ የፖሊሲ እና አሠራር ለውጦች እንዲመጡ ማድረግ ................................................... 4
2.2.6 በሰብአዊ መብቶች ላይ የአመለካከት ለውጥ ማምጣት ............................................................. 4
2.2.7 በሰብአዊ መብቶች ላይ የሕብረተሰቡን ግንዛቤ ማሳደግ ............................................................ 4
2.3 የሰብአዊ መብቶች ክትትል ዓይነቶች ................................................................................................ 5
2.3.1 በተለዩ ሰብአዊ መብቶች ዘርፍ ጉዳዮች ላይ የሚደረግ ክትትል (Thematic Monitoring) .... 5
2.3.2 በተለዩ ሕብረተሰብ ክፍሎች መብቶች ላይ የሚደረግ ክትትል (Target Group
Monitoring) .......................................................................................................................................... 5
2.3.3 ሁኔታዎችን/ኹነቶችን መሠረት ያደረገ የሰብአዊ መብቶች ክትትል (Event/Incident based
Monitoring) .......................................................................................................................................... 5
2.3.4 የመልክአ- ምድር ወሰንን መሠረት ያደረገ የሰብአዊ መብቶች ክትትል (Area based
Monitoring) .......................................................................................................................................... 5
2.3.5 የሕጎችን አፈጻጸም መሠረት ያደረገ ክትትል (Legislation Implementation Monitoring) . 6
2.4 በሰብአዊ መብቶች ክትትል እና በሰብአዊ መብቶች ጥሰት ምርመራዎች መካከል ያለው
መስተጋብር ................................................................................................................................................ 6
ክፍል ሦስት .................................................................................................................................................. 7
የሰብአዊ መብቶች የክትትል መርሆች.......................................................................................................... 7
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
ii
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
iii
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
1
ክፍል አንድ
አጠቃላይ መግቢያ
1.1 መግቢያ
ይህንን ዓላማ ለማስፈጸም ኮሚሽኑ በማቋቋሚያ አዋጁ መሠረት የተለያዩ ሥልጣን እና ኃላፊነቶች
የተሰጡት ሲሆን ሰብአዊ መብቶች መከበራቸውን ለማረጋገጥ ከሚያከናውናቸው ተግባራት
መካከል አንዱ የሰብአዊ መብቶች ክትትል ማድረግ ነው።
ኮሚሽኑ በማቋቋሚያ አዋጁ መሠረት የተለያዩ ሥልጣን እና ኃላፊነቶች የተሰጡት ሲሆን ከነዚህም
መካከል በአዋጁ አንቀፅ 6(1) የተጠቀሰው በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ
መንግሥት የተደነገጉ ሰብአዊ መብቶች በማንኛውም ዜጋ፣ በመንግሥት አካላት፣ በፖለቲካ
ድርጅቶች፣ በሌሎች ማህበራት እንዲሁም በባለስልጣኖቻቸው መከበራቸውን ማረጋገጥ
ይገኝበታል።
ይህንን ለማሳካት ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል አንዱ የሰብአዊ መብቶች ክትትል ማድረግ
ሲሆን ይህም ስልጣን የሚመነጨው ከዚሁ የአዋጁ ድንጋጌ እና ከተቋሙ ዓላማ ነው። በሕገ
መንግሥቱ ከታወቁት ሰብአዊ መብቶች በተጨማሪም የሕገ መንግሥቱ አንቀፅ 9(4)
እንደሚያስቀምጠው ኢትዮጵያ ያጸደቀቻቸው የዓለም አቀፍ ስምምነቶች የሀገሪቱ የሕግ አካል
በመሆናቸው እና በአንቀፅ 13 (2) መሠረት በሕገ መንግሥቱ የተደነገጉ የሰብአዊ መብቶች
ኢትዮጵያ ከተቀበለቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ስምምነቶች፣ ሰነዶች እና መርሆዎች
ጋር በተጣጣመ ሁኔታ መተርጎም እንዳለባቸው በሚደነግጉት አንቀጾች መሠረት የኮሚሽኑ
የክትትል ሥራዎች ከዓለም አቀፍ እንዲሁም አህጉራዊ የሰብአዊ መብቶች ስምምነቶች፣ መርሆች
እና ሕጎች አንጻርም የሚከናወኑ ናቸው። በተጨማሪም የብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች ተቋማትን
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
2
የዚህ የሥራ መምሪያ አጠቃላይ ዓላማ የኮሚሽኑን የሰብአዊ መብቶች የክትትል ሥርዓትን
ማዳበር እንዲሁም የሥራዎቹን ውጤታማነት፤ ሙያዊነት እንዲሁም ዘላቂ ተፅዕኖ (Impact)
ለማሳደግ ሲሆን የሚከተሉት ዝርዝር ዓላማዎች ይኖሩታል፡-
ይህ የክትትል የሥራ መምሪያ ኮሚሽኑ በአዋጅ የተሰጠውን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የማድረግ ሥልጣን
እና ኃላፊነትን የመፈፀም ድርሻ ባላቸው የኮሚሸኑ የሥራ ክፍሎች ሁሉ ተፈፃሚ ይሆናል።
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
3
ክፍል ሁለት
የሰብአዊ መብቶች ክትትል ተግባራት መሠረታዊ ሐሳቦች
2.1 የሰብአዊ መብቶች ክትትል ትርጓሜ
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
4
የክትትል ሥራዎች የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ሲከሰቱ አስፈላጊው አፋጣኝ ምላሽ እና ድጋፍ
ለማሰጠት ጠቀሜታ ይኖራቸዋል። ለምሳሌ ሰዎች በቁጥጥር ስር በሚውሉበት ጊዜ በቁጥጥር
ስር ሆነው ኢ-ሰብአዊ አያያዝ በሚደርስባቸው ወቅት ወይም ሌሎች የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች
መከሰታቸውን በክትትል ከተደረሰበት፤ ወዲያውኑ አስፈላጊው አፋጣኝ ምላሽ በመንግሥትም
ሆነ በሌሎች የሚመለከታቸው አካላት እንዲሰጥ ለማድረግ ያስችላል። ለምሳሌ ያለአግባብ
የታሰሩ ከሆነ እንዲፈቱ፣ፍርድ ቤት ያልቀረቡ ከሆነ በአፋጣኝ እንዲቀርቡ፤ የሕክምና
አገልግሎት የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ሕክምና እንዲያገኙ አስተዋጽዖ ያደርጋል።
የሰብአዊ መብቶች ክትትል ሥራ ሌላው ዓላማ ለተከሰቱ የመብት ጥሰቶች መፍትሔ ማፈላለግ
ነው። የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን መከታተል እና መሰነድ ከሚያስፈልግባቸው ዋና ዋና
ምክንያቶች ውስጥ አንዱ የመብት ጥሰቶች በሚገባ እንዲታወቁ እና ለተጎጂዎች ፍትህን፣
እንደየሁኔታው ሕክምናን፣ የመልሶ ማገገሚያን እና ካሳን በሚያካትት መልኩ የተሟላ
መፍትሔ እንዲያገኙ ለማገዝ እንዲሁም አጥፊዎች እንዲለዩ እና የሕግ ተጠያቂነት እንዲኖር
ለማስቻል ነው።
የሰብአዊ መብቶች ክትትል ግኝቶች የመብት ጥሰቶች የመነጩት ከሕገ መንግሥቱ፣ ከዓለም
አቀፍ፣ እና አህጉራዊ የሰብአዊ መብቶች ሕግ እና መርሆች ጋር ከማይጣጣሙ ሀገራዊ ሕጎች፣
ፖሊሲዎች ወይም አሠራሮች መሆኑን በሚያሳዩበት ጊዜ እነዚሁ ሕጎች፣ ፖሊሲዎች እና
አሠራሮች እንዲሻሻሉ እና እንዲለወጡ ግፊት ማድረግን ያስችላሉ። በዚህም ምክንያት
መንግሥት በተለያዩ የዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ የሰብአዊ መብቶች ስምምነቶች የገባቸውን
ግዴታዎችን እንዲወጣ የሚያግዝም ይሆናል።
የሰብአዊ መብቶች ክትትል ግኝቶችን በይፋ ማሳወቅ በሕብረተሰቡ ዘንድ ስለ ሰብአዊ መብቶች
ያለውን አመለካከት እና ግንዛቤ በማሳደግ መብትና ግዴታውን አክባሪ እና ለመብቶቹም ቀናዒ
የሆነ ሕብረተሰብ እንዲኖር፤ በዚህም የመብት ጥሰቶች እንዲቀንሱ የራሱን አስተዋጽዖ ያደርጋል
። ይህ የግንዛቤ ማስፋፋት ሥራ የሲቪል ማኅበራት፣ ሚዲያ እና የሕዝብ ተወካዮች ላይም በጎ
ተፅዕኖ በማሳደር በሰብአዊ መብቶች ላይ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት ያስችላል።
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
5
የሰብአዊ መብቶች የክትትል ሥራዎች በአንድ ወይም ከዚያ በላይ በሆኑ የሰብአዊ መብቶች
አፈጻጸም በተለዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች፣ ሰብአዊ መብቶች፣ የተመረጡ ኩነቶች ወይም ተቋሞች
በአንድ የተወሰነ አካባቢ ላይ ትኩረት አድርገው ሊከናወኑ ይችላሉ። በተጨማሪም የሕጎችን፣
ፖሊሲዎች ወይም አሠራሮች አፈጻጸም ደረጃ ለመፈተሽ ሊከናወኑ ይችላሉ። እነዚህ የክትትል
ዓይነቶች ብዙውን ጊዜ አንዱ ከሌላው ጋር ተወራራሽነት እና ተመጋጋቢነት ባለው መልኩ
የሚከናወኑ ናቸው።
የሰብአዊ መብቶች ክትትል አንድን የሰብአዊ መብት አይነት ወይም ዓይነቶች ላይ ትኩረት
በማድረግ ሊከናወን ይችላል። ወሰኑም በዚያው ልክ የሚሰፋ ወይም የሚጠብ ሊሆን ይችላል።
ለምሳሌ የሰብአዊ መብቶች ክትትል የጤና ወይም የትምህርት መብቶች ላይ ብቻ አተኩሮ
ሊከናወን የሚችል ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በሲቪል እና ፖለቲካ መብቶች ላይ አትኩሮ
በአንጻራዊ ስፋት ሊከናወን ይችላል።
2.3.4 የመልክአ- ምድር ወሰንን መሠረት ያደረገ የሰብአዊ መብቶች ክትትል (Area
based Monitoring)
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
6
የሰብአዊ መብቶች ክትትል የተወሰኑ ወይም የተለዩ ሕጎችን አተገባበር መሠረት በማድረግ
ሊከናወን ይችላል። ይህም ለምሳሌ የአንድን አዋጅ አተገባበር ወይም አፈጻጸም ተግባራዊ መሆን
አለመሆን በሚቀመጡ መሠረታዊ መረጃዎች በመመልከት የተወሰዱ እርምጃዎች፣ በአዋጁ
የመጡ ውጤቶችን፣ የፍርድ ቤት የዳኝነት ሂደትን መከታተል (Trial Monitoring)፣ የአንድ
ተቋም አሰራር የሕግና የሰብአዊ መብቶችን ያከበረ መሆኑን፣ ወ.ዘ.ተ… መከታተልን ሊያጠቃልል
ይችላል።
2.4 በሰብአዊ መብቶች ክትትል እና በሰብአዊ መብቶች ጥሰት ምርመራዎች መካከል ያለው
መስተጋብር
የሰብአዊ መብቶች ምርምራ በአንድ ወይም ከአንድ በላይ በሆኑ አቤቱታ በቀረበባቸው ጥቆማ
ወይም መረጃ በተገኘባቸው የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች ተፈጽሞበታል በተባለ ጉዳይ ላይ አትኩሮ
ጥሰቱ መፈጸም ወይም አለመፈጸሙን ለማረጋገጥ፤ የተፈጸመውን የመብት ጥሰት ዓይነት
ለመለየት የሚደረግ የምርመራ ሥራ ነው።
የሰብአዊ መብቶች ምርመራ እና ክትትል ሥራዎች የቅርብ ቁርኝት ያላቸው ከመሆኑ ባሻገር
አንዳንድ ጊዜ በአንድ ላይ ሊከናወኑ የሚችሉበት ወይም አንዱ ለሌላው መነሻ የሚሆኑበት
አጋጣሚም አለ። ለምሳሌ የክትትል ሥራ በማከናወን ላይ የሚገኙ የሰብአዊ መብቶች ባለሙያዎች
በክትትሉ ሂደት አንድ የተለየ የመብት ጥሰት መፈጸሙን ካመኑ ምርመራ እንዲከናወን ምክረ
ሃሳብ ሊያቀርቡ ወይም ራሳቸው ምርመራ ሊያከናወኑ ይችላሉ። በተመሳሳይ በምርመራ የታዩ
ጉዳዮች ዙሪያ ወደፊት ጥሰቶች እንዳይፈጸሙ ለመከላከል ክትትል ሊደረግ ይችላል።
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
7
ክፍል ሦስት
የሰብአዊ መብቶች የክትትል መርሆች
3.1 መግቢያ
የሰብአዊ መብቶች ክትትል ባለሙያዎች የሰብአዊ መብት ጥሰት ተጎጂ የሆኑ ሰዎችን
በሚያነጋግሩበት ወቅት የደረሰባቸውን የሰብአዊ መብቶች ጉዳት፣ በደል እና ስቃይ በሚገባ መረዳት
እና ተቆርቋሪነት እና ርህራሄ ማሳየት ይኖርባቸዋል። በተጨማሪም ከጉዳት ተጋላጭነት ጋር
ስለሚኖር የማኅበረ ሥነ ልቦና ጉዳት (trauma) በሚገባ ግንዛቤ መውስድ ይኖርባቸዋል።
በሚጠቀሟቸው ቃላትም ሆነ በአካላዊ ሁኔታቸው በተወሰኑ ሰዎች ወይም ቡድኖች ላይ አሉታዊ
እና የተዛባ አመለካከትን፣ ሚዛናዊነትን ወይም ገለልተኛነትን በሚጎዳ መልኩ እንዳይተረጎሙ
ጥንቃቄ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
8
ሁሉን አቀፍ መረጃ ተሰብስቦ እስኪያልቅ ስለሁኔታው ግልጽ እና የተሟላ ግንዛቤ እስኪያዝ ድረስ
የክትትል ባለሙያዎች ረዘም ላለ ጊዜ ሥራቸውን የሚቀጥሉ ይሆናሉ። በተለይም የመንግሥት
አካላትን እንዲሁም ሌሎች የሚመለከታቸው አካላትን በተከታታይ መወትወት ሊያስፈልግ
ይችላል። በመሆኑም ባለሙያዎች ያለመሰልቸት እና ተስፋ ባለመቁረጥ፣ ታታሪ በመሆን፣
በትዕግስት እና በጽናት ሥራዎቻቸውን ማከናወን ይኖርባቸዋል።
በማንኛውም ጊዜና ሁኔታ በሰብአዊ መብቶች የክትትል ሂደት ተጎጂዎች እንዲሁም መረጃ
የሚሰጡ ሰዎች በክትትሉ ሂደት ባላቸው ተሳትፎ ምክንያት የሕይወት፤ የአካል እና የስነ ልቦና
ጉዳት(ጥቃት) እንዳይደርስባቸው አስፈላጊውን ሁሉ ጥንቃቄ ማድረግ አስፈላጊ ነው። የክትትል
ባለሙያዎች መረጃ ከሚሰጡ ሰዎች ጋር ግንኙነት ከመጀመራቸው በፊት በዚህ ግንኙነት
ምክንያት በሰዎች ላይ ጉዳት ሊያደርስ የሚችል መሆን አለመሆኑን በሚገባ መመዘን
ይኖርባቸዋል። ባለሙያዎቹ ጉዳት እንዳይደርስ ማድረግ ወይም ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት
ዓይነት እና መጠን መገመት የማይችሉ ከሆነ፤ ከመረጃ ሰጪው ጋር ግንኙነት ከማድረግ መቆጠብ
ወይም አማራጭ ዘዴዎችን መሞከር አለባቸው። ለምሳሌ የመረጃ ምንጮቹን ለብቻ በሚስጥር
ማነጋገር ወይም እንደየሁኔታው ከሌሎች ሰዎች ተለይተው ትኩረት ውስጥ ሊገቡ በማይችሉበት
ሁኔታ ቃለመጠይቅ ለማድረግ መጣር ይኖርባቸዋል። የሰብአዊ መብቶች የክትትል ባለሙያው
ድርጊትም ሆነ የሚጠበቅበትን ባለማድረግ በተጎጂዎች፣ መረጃ ሰጪዎች ወይም ሌሎች በክትትሉ
ተባባሪ በሆኑ ሰዎች ላይ ጉዳት ሊያደርስ አይገባም።
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
9
ከመረጃ ሰጪዎች ጋር በሚደረግ የቃለ መጠይቅ ወይም ሌላ ማናቸውም የመረጃ ማሰባሰብ ወቅት
የክትትል ባለሙያዎች መረጃዎችን ለመቀበል፣ ለመጠቀምም ሆነ ለሌላ ሦስተኛ ወገን ለማጋራት
ሁል ጊዜ የመረጃ ሰጪዎችን ነጻ ፈቃድ በግልጽ ማግኘት ይኖርባቸዋል። ይህም ማለት የምስጢር
መጠበቅ መርሆችን የሚሰበሰበው መረጃ ለምን አገልግሎት ሊውል እንደታሰበ እንዲሁም
መረጃዎቹ እንዴት ጥበቃ እንደሚደረግላቸው ማስረዳትን ይጨምራል። መረጃው በጥቅም ላይ
በሚውልበት ወቅት በመረጃ ሰጪዎች ደኅንነት ላይ ጉዳት ሊያደርስ ወይም የጉዳት ስጋቶች
ሊፈጥር የሚችል ከሆነ መረጃ ሰጪዎች በራሳቸው ይህንን ሊያውቁ ወይም ሊገምቱ ያልቻሉ
ቢሆንም እንኳ የክትትል ባለሙያዎች ይህንኑ የማሳወቅ ግዴታ አለባቸው። የክትትል ባለሙያው
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
10
የሰብአዊ መብቶች የክትትል ባለሙያዎች የመረጃ ምንጭ ለሚሆኑ ሰዎች በሙሉ ማንነታቸው
እና አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ የተለየ ስምምነት እስካልተሰጠ ድረስ የተሰጠው መረጃ በምስጢር
እንደሚያዝ እና እንደሚጠበቅ ማረጋገጥ አለባቸው። የምስጢር መጠበቅ መርህ ከጉዳት
አለማድረስ መርህ ጋር ተያያዥነት ያለው መርህ ሲሆን፤ የክትትል ባለሙያዎች የመረጃ
ሰጪዎቹን ማንነት በምስጢር የመጠበቅ ግዴታን የሚያመላክት ነው።
የዚህ ምስጢር መጠበቅ መርህ መጣስ በተጎጂዎች ላይ እንዲሁም መረጃ ሰጪዎች እና ሌሎች
ተባባሪ አካላት፤ በባለሙያዎቹ ተዓማኒነት እና ደኅንነት ፤ ተቋሙ በሕብረተሰቡ ዘንድ ያለው
ተቀባይነት እና ተዓማኒነት፤ እንዲሁም በአጠቃላይ በሥራው ውጤታማነት ላይ ከፍተኛ የሆነ
አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድር በመሆኑ ከፍተኛ ጥንቃቄ ይሻል።
ስለሆነም የመረጃ ምንጭ የሆኑ ሰዎች ፈቃዳቸውን በግልጽ ካልሰጡ በስተቀር ሚስጥራዊነቱ
የሚጠበቅ መሆኑን የክትትል ባሙያዎች በሚገባ ማስረዳት ይኖርባቸዋል። በተጨማሪም
የክትትል ባለሙያዎች ግልጽ ፈቃድ የተሰጣቸው ቢሆንም እንኳ መረጃ ሰጪዎች እና ሌሎች
አካላት ላይ (ለምሳሌ በቤተሰብ አባሎቻቸው ላይ) ሊደርስ የሚችለውን አደጋ በሚገባ በመመዘን
አስፈላጊውን ጥንቃቄ ሁሉ የማድረግ እና አደጋውን ሊያስወግድ በሚችል መልኩ ሥራዎችን
የማከናወን ኃላፊነት አለባቸው። የመረጃ ሰጪዎች እንዲሁም ሌሎች ተባባሪ አካላት ደኅንነት
የክትትል ባለሙያዎች ዋነኛ ትኩረት ሊያደርጉበት የሚገባ እና ከሌሎች ጉዳዮች ሁሉ ቅድሚያ
የሚሰጠው ጉዳይ መሆን ይኖርበታል።
በዚህ መሠረት የተሰበሰቡ መረጃዎች በተለይም የመረጃ ሰጪዎችን ማንነት ሊያሳውቁ የሚችሉ
መረጃዎች (personally identifiable data) በከፍተኛ ጥንቃቄ መጠበቅ እና መቀመጥ
ይኖርባቸዋል። ይህም የጥንቃቄ ሂደት የተሰበሰቡትን መረጃዎች በሙሉ፤ የሚሰነዱበት
(የሚቀመጡበት) እንዲሁም ጥቅም ላይ የሚውሉበትን ሁኔታዎች ሁሉ ይመለከታል።
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
11
1
በኮሚሽኑ ጸድቆ በስራ ላይ ያለውን የሥርዓተ ፆታ አካታችነት ማንዋልን (2013) በተለይም የክትትል ሥራዎችን በሚመለከት የተዘረዘሩትን ተግባራትን በሚገባ
መገንዘብ እና ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል።
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
12
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
13
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
14
ክፍል አራት
የሰብአዊ መብቶች ክትትል ዘዴ እና ሂደት
የሰብአዊ መብቶች የክትትል ሥራው ከመጀመሩ አስቀድሞ የሚከተሉትን ያካተተ ዝክረ ተግባር
(ቢጋር /ToR) ይዘጋጃል፦
• የክትትሉ ዳራ (ከሁኔታ ትንተና የሚወሰድ)
• የክትትሉን ጥቅል እና ዝርዝር ዓላማዎች እና ወሰን
• የክትትሉ ስልት
• ከክትትሉ የሚጠበቁ ውጤቶች (Deliverables/Outputs)
• አስፈላጊ የሠው ሃይል ብዛት፣ የፆታና የብዝሃነት ስብጥር እና የተለያዩ ባለሙያዎች
ሚና
• ክትትሉን ለማጠናቀቅ የሚፈጀውን ጊዜ
• አስፈላጊ የሎጂስቲክስ ጉዳዮችን እና
• ሥራውን ለማከናወን የሚያስፈልገውን ወጪ እና የበጀት ምንጭ ማመላከት ይኖርበታል።
ዝክረ ተግባሩ (ቢጋሩ) በሚመለከተው ኃላፊ ከመጽደቁ በፊት በሥራው የሚካፈሉ ሌሎች የተቋሙ
የሥራ ክፍሎች ካሉ ተገቢው ውይይት ተደርጎበት እና ግብዓቶች ተካትተው ሊዘጋጅ ይገባል።
በተጨማሪም ክትትሉን ለማካሄድ የተመረጠው ሥነ ዘዴ ወይም ስልት ስለተመረጠበት
ምክንያት፣ ቃለ መጠይቅ ይደረጋሉ ተብለው የሚታሰቡ ሰዎች ብዛት ግምት እና የሚገኙበት
አካባቢ የመሰሉ መረጃዎች እና ማብራሪያዎች መገለጽ ይኖርበታል።
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
15
በክትትል ሂደት በሰፊው ጥቅም ላይ ከሚውሉ የመረጃ ማሰባሰቢያ ዘዴዎች አንዱ መጠይቅ
ነው። መጠይቆች በሕግ ትንታኔ እና የማገናዘቢያ ዝርዝሮች መሠረት የሚዘጋጁ ሲሆን በቅድሚያ
አጠቃላይ መረጃዎችን የሚመለከቱ ጥያቄዎችን በማስቀደም በሂደት ወደ ዝርዝር ጥያቄዎች
እንዲገቡ ሆነው መቀረጽ ይኖርባቸዋል። ጥያቄዎች ክፍት (open ended) ወይም ሰፊ ምላሽን
ለማሳጠር የተወሰኑ መልሶችን ብቻ የሚጋብዙ (ውስን) ሆነው ወይም የሁለቱንም ዓይነት
ጥያቄዎች ያቀናጁ ሆነው ሊዘጋጁ ይችላሉ። መጠይቆች በተቻለ መጠን ግልጽ እና አጭር ሆነው
የሚከተሉትን ዋና ዋና ጉዳዮች መያዝ ይኖርባቸዋል:-
• መግቢያ (የተቋሙን ስም፣ የተቋሙ ምንነት፣ የክትትሉን ዓላማ የሚያመላክት አጠቃላይ
መግቢያ)፤
• በመረጃ ሰጪዋ/ው ፍቃደኛነት የሚሞላ የተጠያቂው የግል መረጃ (ለምሳሌ ጾታ፣ ዕድሜ፣
አካል ጉዳት ሁኔታ፣ የጋብቻ ሁኔታ፣ ሥራ፣ ትምህርት፣ ወ.ዘ.ተ…)፤
• መረጃ ሰጪዋ/ው የሚሰጣቸውን መረጃዎች መጠቀምን ሆነ ለሦስተኛ ወገን ማጋራትን
በተመለከተ ነፃ ፍቃድ የሰጠ/ች ስለመሆኑ፤
• ጥያቄዎች፤
• መረጃ ሰጪዋ/ውን በተመለከተ ያለው የደኅንነት ሥጋት ዓይነት፤
• በመጠይቁ በመሳተፋቸው የሚቀርብ ምስጋና::
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
16
ጥሰት ተጋላጭ የሆኑ የሕብረተሰብ ክፍሎችን እንዲሁም ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆኑ የመረጃ
ምንጮችን ባካተተ መልኩ ሊከናወን ይችላል። ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆኑ የመረጃ ምንጮች
የመብት ባለቤቶች፣ ተጎጂዎች፣ መብቱን የማክበር እና የማስከበር ኃላፊነት ያለባቸው
የመንግሥት እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ወ.ዘ.ተ... የሚሰጧቸው መረጃዎችን ፣ የሰነድ
ማስረጃዎችን፣ የመንግሥት ይፋዊ ሪፖርቶችን፣ የባለሙያዎች ትንታኔ፣ የሲቪል ማህበራት
(ሀገር በቀልም ሆነ የውጭ አገሮችን ጨምሮ) እና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥናቶችን እና
ሪፖርቶችን፣ የመገናኛ ብዙሃን ዘገባዎችን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች መግለጫዎችን፣ ከማህበራዊ
ትስስር ገጾች የተገኙ መረጃዎችን፣ የቀረቡ አቤቱታዎች(ቅሬታዎችን)፣ የፍርድ ቤት መዝገቦችን፣
የፖሊስ የምርመራ መዝገቦችን እና የመስክ ምልከታዎችን ያካትታሉ።
በሰብአዊ መብቶች ክትትል ሂደት በጥንቃቄ የተዘጋጀ የመረጃ መሰብሰቢያ ስርዓትን በመዘርጋት
እውነተኛ እና ትክክለኛ የሆኑ መረጃዎችን መሰብሰብ ያስፈልጋል። የመረጃ ማሰባሰብ ሥራ ከዚህ
በታች የተጠቀሱትን አንዱን፣ የተወሰኑትን ወይንም ሁሉንም በጥቅም ላይ በማዋል ሊከናወን
ይችላል።
4.2.1 ቃለ-መጠይቅ
በሰብዓዊ መብቶች ክትትል ሂደት የሚከተሉት የቃለ መጠይቅ ዓይነቶች ጥቅም ላይ ሊውሉ
ይችላሉ። ለሕፃናትን ቃለ-መጠይቅ በልዩ ሁኔታ የሚዘጋጅ ይሆናል።
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
17
ይሆናል። በዚህ ሂደት ሌሎች በቃለ መጠይቁ ወቅት የሚነሱ ጉዳዮችን መመዝገብ እንደ ሁኔታው
አስፈላጊ ይሆናል።
ይህ የቃለ- መጠይቅ ሂደት በሌሎች ዘዴዎች የተገኙ መረጃዎችን ለማመሳከር እንዲሁም ዝርዝር
(አሃዛዊ ያልሆኑ) መረጃዎችን ለማግኘት የሚጠቅም ነው።
ለ. ሙሉ በሙሉ በጥያቄዎች መዘርዝር ላይ ተመስርቶ የሚደረግ ቀጥታ ቃለ- መጠይቅ
(structured interview)
በዚህ ሂደት የጥያቄዎች መዘርዝር ማዘጋጀት ሳያስፈልግ አጠቃላይ አቅጣጫን ሊያሳዩ የሚችሉ
መረጃዎችን ለማግኘት የሚያስችሉ ዘዴዎችን በመከተል ብቻ የሚካሄድ ሲሆን በዚህ ሂደት
በዝርዝር የሚዘጋጅ የጥያቄዎች መዘርዝር አይኖርም። በሌላ በኩል ግን በጥልቀት ሊጠኑ
የሚገባቸውን ጉዳዮች ለመለየት ከፍተኛ ጥቅም የሚኖረው ሂደት በመሆኑ በጥንቃቄ መከናወን
አለበት። የመረጃ ምንጮቹም በጠቅላላው አመላካች የሆኑ መረጃዎችን ሊሰጡ የሚችሉ አካላትን
በማካተት የሚካሄድ እና ተጎጂዎችወይም ቀጥተኛ መረጃ ሰጪዎች ላይ ብቻ የሚወሰኑ ሳይሆን
ስለ ጉዳዩ አጠቃላይ መረጃ እና ማስረጃ የሚኖራቸውን አካላት ሁሉ በማነጋገር መረጃ የሚገኝበት
ሂደት ነው።
የቡድን ውይይቱን የሚመራው የክትትል ባለሙያ ሲሆን በዋነኝነት በተዘጋጁ የጥያቄ መዘርዝሮች
መሠረት ጥያቄዎችን በማንሳት መረጃ የመሰብሰብ ሥራ ነው። የጥልቅ ቡድን ውይይት በሰብአዊ
መብቶች ክትትል በተለያዩ ደረጃዎች ላይ ሊከናወን የሚችል ሲሆን፤ የቡድኑ አባላት እንዲሁም
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
18
የጥያቄዎቹ ይዘት እንደ ጉዳዩ እና የክትትሉ ሂደት ደረጃ የሚወሰኑ ይሆናል። አጠቃላይ
መረጃዎችን ለመሰብሰብ የታሰበ ከሆነ የቡድን ውይይቱ ላይ የሚሳተፉት ሰዎችም ከተለያዩ
መስኮች እንዲውጣጡ ለማድረግ የሚቻል ሲሆን ዝርዝር ጉዳዮች ለመጠየቅ እና ለክትትሉ
ቀጥተኛ ግብዓት የሚሆኑ መረጃዎችን ለማግኘት የታሰበ ከሆነ ደግሞ የቡድን ውይይቱ
ተሳታፊዎች አስቀድሞ በተዘጋጁ ዝርዝር መስፈርቶች መሠረት የተመረጡ መሆን እና
ውይይቱም አስቀድመው በተዘጋጁ መጠይቆች መሠረት መከናወን ይኖርበታል። በተጨማሪም
የቡድን ውይይት በሌሎች የመረጃ ማሰባሰቢያ ዘዴዎች የተገኙ መረጃዎችን ለማረጋገጥ እንዲሁም
በተዘጋጀ ሪፖርት ላይ ተጨማሪ ግብዓት ለማግኘት ጥቅም ላይ ሊውል ይችላል።
የቡድን ውይይት በተቻለ መጠን ምቹ በሆነ እና ፀጥታ ባለው ስፍራ መከናወን ያለበት ሲሆን
ከሁለት ሰዓት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ እንዲጠናቀቅ ይመከራል። የቡድን ውይይቱን የሚመራው
የክትትል ባለሙያ ሁሉም ተሳታፊዎች ሃሳባቸውን እንዲያካፍሉ እድል መስጠት አለበት። በዚህ
ሂደት አንዳንድ ሂደቱን የሚቆጣጠሩ (dominant) የሆኑ ሰዎች ሊኖሩ ስለሚችሉ በሚነሱ ሃሳቦች
ምክንያት በተሳታፊዎች መካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን ባለሙያው በሚገባ መምራት
(ማመቻቸት) እና ሁሉም አስተያየቶች እና አመለካከቶች በነጻነት እንዲንሸራሸሩ የሚያስችል
ሁኔታን መፍጠር ይጠበቅበታል። የቡድን ውይይት ዕድሜን ፣ጾታን፣ አካል ጉዳትን እና ሉሎች
የብዝኃነት እና አከታችነት መርሆችን በተከተለ መልኩ መመቻቸት እና መመራት አለበት።
ሕፃናትን በተመለከተም የሕፃናት ተሳትፎ መመሪያዎች ልብ ሊባሉና በአግባቡ ሊተገበሩ ይገባል።
የቡድን ውይይቱ በቅድሚያ የእርስ በእርስ ትውውቅ በማድረግ የሚጀመር ሲሆን ሂደቱን
የሚመራው ባለሙያ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች ማንሳት ይኖርበታል፡-
• ተሳታፊዎችን እንኳን ደህና መጣችሁ ማለት እንዲሁም ለመሳተፍ ፈቃደኛ በመሆናቸው
ማመስገን፤
• የውይይቱን አጀንዳ እንዲሁም ዓላማ ማስተዋወቅ፤
• ውይይቱ የሚካሄድበትን ደንብ፣ ሕግ፣አሠራር ማስተዋወቅ (የሌሎችን ሃሳብ ማክበርን፤
በአንድ ጊዜ አንድ ሰው ብቻ እንዲናገር፤ ስህተት ተብሎ የሚጣል ሃሳብ የሌለ መሆኑን
እንዲሁም ሁሉም ሃሳቦች የራሳቸው ጠቀሜታ እና ዋጋ እንዳላቸው ወ.ዘ.ተ...)
የቡድን ውይይቶች ላይ በተቻለ መጠን ሁለት ባለሙያዎች ሊኖሩ ይገባል። አንደኛው ባለሙያ
ጥያቄዎችን በማንሳት እና እድል በመስጠት ውይይቱን ሲመራ ሌላኛው ባለሙያ ማስታወሻ
የመያዝ እና ፍቃድ በተገኘ ጊዜ ድምጽ ወይም ተንቀሳቃሽ ምስል የመቅዳት ኃላፊነት እንዲሁም
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
19
መ) ቋንቋ እና አስተርጓሚዎች
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
20
ቃለ መጠይቁን በሚያከናውነው ባለሙያ እና በመረጃ ሰጪው መካከል ጉልህ የሆነ የባህል ልዩነት
ካለ መግባባት ላይ የራሱ አሉታዊ ተጽእኖ ሊያደርስ ይችላል። እነዚህ የባህል ልዩነቶች በሥርዓተ
ጾታ አረዳድ ላይ፤ የደረሰ ጉዳት እና የጥሰት አይነት እንዲሁም በሚነሱ ርዕሶች ላይ ጎልተው
ሊወጡ ይችላሉ። ሌሎች ጉዳዮች ለምሳሌ አለባበስ፣ የአካል ንክኪ፣ የአይን ግንኙነት (eye
contact) ወ.ዘ.ተ… የራሳቸው የሆነ አለመግባባት ሊፈጥሩ ይችላሉ። መጠይቁን የሚያከናውነው
ባለሙያ እነዚህ የባሕል ልዩነቶች በሚገባ መረዳት እና በታጋሽነት መጠይቁን ማከናወን እንዲሁም
ስለ ባሕሎቹ የበለጠ ለመረዳት ጥረት ማድረግ ይኖርበታል።
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
21
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
22
ሰ. 2 የፎቶግራፍ መረጃዎች
የፎቶግራፍ መረጃዎች መውሰድ ከድምጽ በበለጠ አደጋ ወይም ችግር ሊፈጥር የሚችል ነው።
መረጃ ሰጪዎችን ፎቶግራፍ ከማንሳት በፊት ሊደርስባቸው የሚችልን ጥቃት በሚገባ ግንዛቤ
ውስጥ ማስገባት ያስፈልጋል። አንዳንድ መረጃ ሰጪዎች (ተጎጂዎች) የደረሰባቸውን ጉዳት
(ቁስል፣ ጠባሳ ወ.ዘ.ተ…) ለማሳየት ሲፈልጉ፤ ማንነትን በማያመላክት መልኩ (ፊትን እና ሌሎች
ልዩ መለያዎችን ሳይታይ) ፎቶግራፉን ማንሳት ያስፈልጋል።
ፎቶግራፍ ለመነሳት የመረጃ ሰጪዋ/ው ፈቃድ የተገኘ እንደሆነ ምስሉን በህትመት (ይፋዊ
ሪፖርቶች) ላይ ለመጠቀም ወይም ለማሰራጨት ፈቃደኛ መሆኑንም በተጨማሪነት መጠየቅ እና
ማረጋገጥ ያስፈልጋል።
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
23
ሸ) ቃለ መጠይቁን ማከናወን
መረጃ ሰጪው በድካም፣ በስሜታዊነት ወይም በሌላ ምክንያት መረጃዎችን ለመስጠት በተቸገረ
ጊዜ ሁሉ እረፍት እንዲያደርግ እና መንፈሱን ለማረጋገት እንዲችል የክትትል ባለሙያው ማገዝ
ይኖርበታል። ይህንንም ከጥቃት ተጎጂነት፣ ከዕድሜ፣ ከጾታ፣ አካል ጉዳት እና ሌሎች ሁኔታዎች
በማገናዘብ ልዩ ትኩረት መስጠት ያሻል።
መረጃ ሰጪው በቃለ መጠይቁ ሂደት ሃሳቡ ሳይቆራረጥ ለመናገር የሚችልበትን እድል መስጠት
እንዲሁም ከተገቢው በላይ በሌሎች ጥያቄዎች በተደጋጋሚ ማቋረጥ አያስፈልግም። መረጃ
ሰጪው ግልጽ ያልሆኑ፣ የተጋነኑ ወይም እውነት ያልሆኑ፡ የማይመስሉ መረጃዎች ቢሰጥም
እንኳ የክትትል ባለሙያው በፊት ገጹ፣ በድርጊቱም ሆነ በቃላቱ መረጃ ሰጪውን መጠራጠሩን
ወይም ያለማመኑን ማመላከት የለበትም። እንዲህ ያሉ መረጃዎች ሲሰጡ መረጃ ሰጪው ሃሳቡን
እንዲጨርስ እድል ከተሰጠ በኋላ በማጣሪያ ጥያቄ መልክ በድጋሚ እንዲብራራ መጠየቅ ተገቢ
ነው።
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
24
የክትትል ባለሙያዎች የተለያዩ መረጃ ሰጪዎች ለምሳሌ በእድሜ ወይም የማኅበረ ሥነ ልቦና
ጉዳት (trauma) ሰለባ በመሆናቸው ምክንያት የየራሳቸው ልዩ ባሕርይ ስለሚኖራቸው እነዚህን
ሰዎች ቃለ መጠይቅ ማድረግ አስቸጋሪ ሊሆን እንደሚችል መገንዘብ ያስፈልጋል። በመሆኑም
ልዩ ትኩረት ሊደረግላቸው የሚገባ የሕብረተሰብ ክፍሎች ቃለ-መጠይቅ በሚደረጉበት ወቅት
እንደየሁኔታው ለየት ያለ አቀራረብ እና ዘዴ መከተል አስፈላጊ ይሆናል። ለዚህም የበለጠ ዝግጅት
እና ትዕግስት አስፈላጊ ነው።
የማሰቃየት እና የጭካኔ ተግባር ተጎጂዎችን መጠይቅ ማድረግ እጅግ ጥንቃቄ ሊደረግበት የሚገባ
ሥራ ነው። መጠይቁን የሚያከናውን ባለሙያ የስቃይ ተጎጂዎች የሚኖርባቸውን የማኅበረ ሥነ
ልቦና ጉዳት (trauma) በሚገባ በመረዳት ቃለ መጠይቁን በሚያደርጉበት ወቅት በድጋሚ ለሌላ
የማኅበረ ሥነ ልቦና ጉዳት (secondary trauma) የማያጋልጥ መሆኑን መገንዘብ ይኖርበታል።
የክትትል ባለሙያዎች ይህንን ከግንዛቤ በማስገባት ቀድመው መዘጋጀት እንዲሁም ተጎጂዎቹም
ሆኑ መረጃ ሰጪዎች በሚናገሩበት ወቅት ማበረታታት፤ እረፍት ከፈለጉ ቃለ መጠይቁን
ማቆምን፤ ስሜታዊ ሲሆኑ ደጋፊ እና ተቆርቋሪ መሆን ወ.ዘ.ተ… ይኖርባቸዋል። ነገር ግን
የክትትል ባለሙያዎች የሰለጠኑ የስነልቦና ባለሙያዎች ስላልሆኑ፤ ሥራቸው ሕክምና ወይም
የሥነ ልቦና ድጋፍ ለመስጠት እንዳልሆነ መገንዘብ እና እንዲሁም በአቅራቢያ የሚገኙ የሥነ
ልቦና ሕክምና አገልግሎች ሰጪ ተቋማት እና ባለሙያዎችን በማጣራት መረጃውን ለተጎጂዎች
ማድረስ አለባቸው። የሚቻል ከሆነ የክትትል ቡድኑ አባል አግባብ ያለው የሕክምና እና የሥነ
ልቦና ባለሙያዎች ማካትተ አስፈላጊ ነው። የሕክምና ባለሙያው የምስክሩን የበፊት የሕክምና
ሪከርዶችን በመመልከት እና አሁን ካለው ጋር በማመሳከር የሙያ አስተያየት ሊሰጥ ይችላል።
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
25
ከዚህ በተጨማሪም ከፍተኛ የሥነ ልቦና ጉዳት የደረሰባቸው የጾታዊ እና ወሲባዊ ጥቃት
ተጎጂዎችን ቃለመጠይቅ ማድረግ በራሱ ለተደራራቢ የሥነ ልቦና ጉዳት የሚዳርግ በመሆኑ
ቃለመጠይቁ ከመደረጉ አስቀድሞ በተቻለ መጠን የማህበረ ሥነ ልቦና (psycho-social) እና
የሕክምና (medical) አገልግሎቶችን ማመቻቸት ተገቢ ነው።
እነዚህ የሕብረተሰብ ክፍሎች በከፍተኛ ችግር እና እንግልት ውስጥ ያለፉ እንደዚሁም የኢኮኖሚ
ችግሮች ያሉባቸው በመሆኑ የክትትል ባለሙያዎች ይህንኑ መረዳት እና ተቆርቋሪነትን ማሳየት
እንዲሁም ጥያቄዎችን ከስደተኝነት ወይም ሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ጋር ግንኙነት ካላቸው ሕጎች
እና ዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ ሰነዶች ጋር በተናበበ መልኩ መዘጋጀት ይኖርባቸዋል።
መ) ሕፃናት
ሕፃናት ነገሮችን የሚረዱበት እና የሚመለከቱበት እይታ አካለ መጠን ከደረሱ ሰዎች የተለየ
ሊሆን ይችላል። ቃለ-መጠይቁን የሚያደርገው ባለሙያ ይህንን በሚገባ በመረዳት መጠይቁ
የሕፃናትን እድሜ፣ ብስለት እና ግንዛቤ ግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ ማከናወን ይኖርበታል።
ቀላል ቃላትን በመጠቀም ከሕፃናቱ ጋር ቅርርብ እና መተማመንን ለማስፈን ረዘም ያለ ጊዜ
ሊወስድ እንደሚችል በመገንዘብ በትዕግስት መሥራት ያስፈልጋል። በተጨማሪም መረጃዎችን
ለማግኘትም ሆነ የተሰበሰበውን መረጃ ለማመሳከር ይረዳ ዘንድ የሕፃናቱን ወላጆች (አሳዳጊዎች)
ወይም የቤተሰብ አባላት፣ መምህራን፣ ወይም ሌሎች አገልግሎት ሰጪዎችን እንደሁኔታው
ማነጋገር አስፈላጊ ይሆናል።
በሁሉም የክትትል ሥራዎች የአካል ጉዳተኞች እና የአረጋውያን ሁኔታ ሊካተት ይገባል። አካል
ጉዳተኞች እና አረጋውያን መረጃ ለመስጠት ተነሳሽነት ላይኖራቸው ወይም ላያስታውሱ ወይም
በአካባቢው ማኅበረሰብ የተገለሉ ሊሆኑ ይችላል። ስለሆነም እነዚህን ሰዎች አግኝቶ ለማነጋገር
የተለየ ጥረት ማድረግ በተጨማሪም በማኅበሮቻቸው በኩል ማሳተፍ አስፈላጊ ነው። ጥያቄዎቹም
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
26
ከተጎጂዎች፣ ምስክሮች እና ሌሎች አካላት መረጃዎች ከተሰባሰቡ በኋላ ግዴታ ካለባቸው አካላት
በተገኙት መረጃዎች ላይ ያላቸውን ምላሽ መጠየቅ እና ማካተት አስፈላጊ ነው። በመሆኑም
ክትትል በሚደረግበት ጉዳይ ዙሪያ ተገቢነት ያላቸው የበላይ ኃላፊዎችን ቃለመጠይቅ ማድረግ
ይገባል። ለምሳሌ ክትትሉ የሚደረገው በፖሊስ ጣቢያ ወይም ማረሚያ ቤት ከሆነ የፖሊስ
ጣቢያውን አዛዥ ወይም የማረሚያ ቤቱን የበላይ ኃላፊ ወይም እነዚህ ሊገኙ ባልቻሉ ጊዜ
ተወካዮቻቸውን በማነጋገር ምላሾቻቸውን በአግባቡ መመዝገብ ያስፈልጋል።
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
27
ማንኛውም በወንጀል የሚያስጠይቅ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት መፈጸሙን የሚያሳዩ የቁስ ወይም
የፎረንሲክ ማስረጃዎችን በክትትል ሂደት መነካካትም ሆነ ከስፍራቸው ማንሳት ተገቢ አይደለም።
ነገር ግን በሥራቸው ምክንያት የክትትል ባለሙያዎች እነዚህን መረጃዎች እና ማስረጃዎች ያገኙ
እንደሆነ ወዲያውኑ ለሚመለከተው የወንጀል ምርመራ አካል ማሳወቅ ይኖርባቸዋል። ፖሊስ
መረጃዎችን በቅርበት ተገኝቶ መሰብሰብ ባለመቻሉ እና ሌሎች አማራጮች በሌሉ ጊዜ ጉዳዩ
የሚመለከተው የመንግሥት የወንጀል ምርመራ አካላት በሚሰጡት ፍቃድ እና ሙያዊ ምክር
መሠረት የክትትል ባለሙያው ማስረጃዎቹ በሚገባ እንዲሰበሰቡ (እንዲቀመጡ) በተገቢው ምልክት
እንዲደረግባቸው እና እንዲታሸጉ በማድረግ ከመጥፋት እና በንኪኪ ከመበላሸት እንዲጠበቁ
ማድረግ ይቻላል። ማስረጃዎችን በጥንቃቄ ፎቶግራፍ ማንሳት ወይም በተንቀሳቃሽ ምስል መቅረጽ
ይችላሉ። አስፈላጊ በሆነ ጊዜ የቁሶችን መጠን በትክክል ለመለየት እንዲቻል ለማነጻጸሪያነት
የሚያገልግሉ በተለምዶ የሚገኙ ዕቃዎችን (ለምሳሌ ማስመሪያ፣ እስክሪብቶ፣ ማስታወሻ ደብተር
ወ.ዘ.ተ...) የወንጀል ሥፍራውን በማይረብሽ አግባብ ከቁስ ማስረጃዎች አጠገብ በማስቀመጥ
ፎቶግራፍ ማንሳት ወይም በተንቀሳቃሽ ምስል ለመቅረጽ ይቻላል።
በተለይ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ከቴክኖሎጂ እድገት በተለይም የስማርት ተንቀሳቃሽ ስልኮች
መስፋፋት ጋር በተያያዘ የሰብአዊ መብቶች ክትትል ሥራ ለመከወን ከነጻ ምንጮች (Open
Source) የሚገኙ መረጃዎች የመጠቀም አስፈላጊነት እያደገ መጥቷል።
ከነጻ ምንጮች የሚገኙ መረጃዎች ስንል በማንኛውም ሰው በነጻ ወይም በግዥ ሊገኙ የሚችሉ
እና መረጃዎችን ለማግኘት ልዩ ሕጋዊ መብት ወይም ፍቃድን የማይጠይቁ በአብዛኛው ለብዙ
ሰዎች ተደራሽ ሆነው በተለይ በኢንተርኔት ቴክኖሎጂ ጭምር ሊገኙ የሚችሉ መረጃዎችን ማለት
ነው። ከነዚህ ምንጮች ዋንኛው በመረጃ መረብ የሚገኙ መረጃዎች ሲሆኑ በድረ ገጾች፣ ማኅበራዊ
ሚዲያዎች (ፌስ ቡክ፣ ትዊተር፣ ዋትስአፕ፣ ቴሌግራም ወ.ዘ.ተ...) የሚገኙ የጽሁፍ፣
የፎቶግራፍ፣ የቪዲዮ እና የድምጽ መረጃዎችን ያካትታሉ። በተጨማሪም የሰብአዊ መብቶች
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
28
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
29
ክፍል አምስት
የድህረ መስክ/ክትትል ሂደትና ሪፖርት ዝግጅት
5.1 መረጃን መመርመር እና መተንተን
በሰብአዊ መብቶች የክትትል ሥራ ትክክለኛ እና ተዓማኒ የሆነ መረጃ መሰብሰብ በጣም አስፈላጊ
ነው። የተሰበሰቡ መረጃዎችን መሠረት በማድረግ የሚከናወኑ ትንታኔዎች እና ድምዳሜዎች
ለምክረ ሃሳቦች መነሻ ሆነው ያገለግላሉ፤ ከመንግሥት አካላትም ሆነ ከሌሎች ግዴታ ያለባቸው
አካላት ጋር ለሚከናወኑ የውትወታ ሥራዎች መነሻ ይሆናሉ።
የመረጃ ትክክለኛነት በሁለት መልኩ ይመዘናል። የመጀመሪያው የተሰጠው መረጃ እርስ በእርሱ
የማይጋጭ ውስጣዊ ወጥነት (internal consistency) ያለው መሆኑን መመዘን ነው። ከአንድ
መረጃ ሰጪ የተገኘ ውስጣዊ ወጥነት ያለው መረጃ ይበልጥ ተዓማኒ ሊሆን ይችላል። ሆኖም
በተለይ መረጃ ሰጪው የቋንቋ ችግር፣ የእድሜው መግፋት ወይም ማነስ፣ በደረሰበት የመብት
ጥሰት ሳቢያ የተከሰተ የማኅበረ ሥነ ልቦና ጉዳት፣ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ወ.ዘ.ተ... ያሉበት
ከሆነ በሚሰጠው መረጃ ውስጣዊ ወጥነት ላይ የራሱን የሆነ አሉታዊ ተጽዕኖ ሊያሳድር የሚችል
መሆኑን ግምት ውስጥ ማስገባት እና በመረጃው ትክክለኛነት ምዘና ላይ ታሳቢ ማድረግ
ያስፈልጋል።
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
30
ቀጥተኛ ከሆኑ ምንጮች የተገኙ መረጃዎች ቀጥተኛ ካልሆኑ ምንጮች የተሻለ አስተማማኝነት
(ተአማኒነት) እንደሚኖራቸው ይጠበቃል። ሆኖም ቀጥተኛ መረጃ ምንጭ የሆኑ ሰዎች በሰጧቸው
መረጃዎች ውስጥም ቢሆን ከግል አመለካከት ወይም (personal bias) የሚመነጩ መረጃዎችን፣
እራሳቸው ካዩት፣ ከሰሙት እና ካሳለፉት ልምድ ውጪ የሆኑ መረጃዎችን ለይቶ ማውጣት
አስፈላጊ ነው።
የሰብአዊ መብቶች የክትትል ሪፖርት የክትትሉን ዓላማ፣ የመረጃ ማሰባሰቢያ ስልት፣ የክትትል
ሥራውን ወሰን፣ የሕግ እና የሁኔታ ትንተና፣ በክትትሉ ከሁሉም ወገኖች የተገኙ መረጃዎች፣
ለመብት ጥሰት ተጋላጭ የሆኑ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ሁኔታ (ሴቶች፣ ሕፃናት፣ አረጋውያን
እና አካል ጉዳተኞችን ጨምሮ) በግኝቶች እና ምክረ- ሃሳቦች ማካተት አለበት።
በተለይ ለሕዝብ ይፋ የሚደረጉ ሪፖርቶች በሚዘጋጁበት ወቅት አንባቢው የሕግ ወይም የሰብአዊ
መብቶች ባለሙያ እንደማይሆን ታሳቢ በማድረግ ሪፖርቱ በአጠቃላይ ለአንባቢ በቀላሉ እንዲረዳ
ወይም ተደራሽ እንዲሆን የሚከተሉትን ነጥቦች መሠረት በማድረግ ማዘጋጀት ያስፈልጋል፦
ጥሩ የሰብአዊ መብቶች ክትትል ሪፖርት አንጻራዊ በሆነ መልኩ አጭር ግልጽ እና መረዳት
የሚያስችል እንዲሁም መረጃዎችን እና ማስረጃዎችን አመክንዮን እንዲሁም መረጃዎቹ ላይ
በተገቢው መጠን አጠር ያለ ትንታኔ መስጠት የሚችል መሆን ይኖርበታል። የተወሰኑት
አንባቢዎች ብዙ ገጾችን ለማንበብ ጊዜ የሌላቸው መሆኑን በመገንዘብም፤ አጭር መልዕክቱን
ለማወቅ ለሚፈልጉ አንባቢዎች የሚረዳ አንኳር ክፍል ማዘጋጀትም አስፈላጊ ነው። ጥሩ ሪፖርት
አንድ ሃሳብን በፍጥነት እና በአጭር ጊዜ መረዳት በሚያስችል መልኩ ማቅረብ መቻልን
ይጠይቃል። በአንድ ጉዳይ ላይ የተሰበሰበ መረጃን ወይም የሚታወቅ ጉዳይን ሁሉ ከሚያስፈልገው
መጠን በላይ መዘርዘር አስፈላጊ አይሆንም።
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
31
በክትትል ሪፖርት ላይ የሚካተቱ ምክረ ሃሳቦች ቀረጻ ከፍተኛ ጥንቃቄን የሚጠይቅ ነው።
የክትትል ሪፖርት ላይ የሚካተቱ ምክረ ሃሳቦች የሚከተሉትን መስፈርቶች ታሳቢ በማድረግ
ሊቀረጹ ይገባል፦
የሰብአዊ መብቶች የክትትል ሪፖርት የታሰበለትን ውጤት ለማሳካት ያስችለው ዘንድ እንዲሁም
አስፈላጊ እርምጃዎች ይወሰዱ ዘንድ፤ ለታለመለት አካል እንዲደርስ እና ግንዛቤ እንዲወሰድበት
ማድረግ አስፈላጊ ነው።
2
ይህ ስራ የኮሚሽኑን የውትወታ እና ቪሲቢሊቲ ስትራቴጂን ታሳቢ በማድረግ መከናወን ይኖርበታል።
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ
32
የውትወታ ሥራ እራሱን የቻለ አሠራር ሥርዓት እና ስልት ያሉት ስለሆነ ለብቻው ዝርዝር
ስትራቴጂ ዕቅድ በማዘጋጀት የሚከናወን አስፈላጊ ሥራ ነው።
www.ehrc.org የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሰብአዊ መብቶች ክትትል የሥራ መምሪያ