Professional Documents
Culture Documents
Amharic Training Manual On How To Establish and Manage Community Learning Centres
Amharic Training Manual On How To Establish and Manage Community Learning Centres
አዘጋጆች፤
የራስወርቅ መገርሳ በዳዳ
ኤርሚያስ ፀሐይ ብርሃኑ
ትዝታ ለማ መልካ
ጥሩወርቅ ዘለዓለም ወርቅነህ
1
2
ምስጋና
ይህ በማኅበረሰብ መማማሪያ ማእከላት ምንነት፣ አመሰራት እና አስተዳደር ዙሪያ የተዘጋጀው
የባለሙያዎች ማሠልጠኛ ማኑዋል እንዲዘጋጅ እና ታትሞ እንዲሰራጭ የሆነው ከእንግሊዝ ሀገር
መንግሥት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ሲተገበር በቆየ የቤተሰብ መማማር እና ሀገር-በቀል ዕውቀት
ላይ ባተኮረ ፕሮጀክት አማካኝነት ነው፡፡ ይህ ፕሮጀክት በዩኒቨርስቲ ኦፍ ኢስት አንግሊያ ውስጥ
የሚገኝ ሌላ ትልቅ ፕሮጀክት አካል ሲሆን የዚህ ፕሮጀክት መለያ ቁጥር (ref. EP/T015411/1)
ነው፡፡
Acknowledgement
This Training Manual on Community Learning Centres (CLCs) is prepared and duplicated as part
of and as one of the outcome documents of the project entitled "Family Literacy, Indigenous
Learning and Sustainable Development", which is part of a bigger project - Meeting the SDGs:
creating innovative infrastructures and policy solutions to support sustainable development in
Global South communities (GS-DEV) which is the title of University of East Anglia's Global
Research Translation Award (ref. EP/T015411/1). The award is funded by United Kingdom
Research and Innovation (UKRI) through the Global Challenges Research Fund (GCRF), part of
the UK's Official Development Assistance (ODA).
The team members who prepare this training manual are members of the University of East
Anglia's (UEA) UNESCO Chair in Adult Literacy and Learning for Social Transformation in
which Bahir Dar University is a member.
3
4
ማውጫ
ማውጫ ............................................................................................................................. 5
ምዕራፍ ሁለት................................................................................................................. 16
5
ምዕራፍ አራት ................................................................................................................. 24
ምዕራፍ ዘጠኝ.................................................................................................................. 46
ዋቢ መፃህፍት ................................................................................................................. 56
7
መግቢያ
ማኅበረሰብን መሰረት ያደረገ ትምህርት ለዘላቂ ልማት እንዲሁም ንቁ ዜጋ ለማፍራት ጠቀሜታው
የጎላ ነው። በፍጥነት እየተቀየረ ባለው የዓለም ሥርዓት የሚፈጠሩ ችግሮችን ለመቅረፍ ሰዎች
ቀጥተኛና ተግባራዊ እርምጃ እንዲወስዱ ያስችላቸዋል። እንዲሁም ሰዎች ሕይወታቸውን
በዘላቂነት ለማሻሻል አዳዲስ ዕውቀቶችን እና ክህሎቶችን እንዲያገኙ ይረዳቸዋል፡፡
የአንድን ማኅበረሰብ የዕለት ከዕለት ችግሮች ለመፍታት የሚያስችል እሴት፣ ዕውቀት፣ ክህሎት፣
ጥበብ የሚያገኙበትን ሁኔታ ለማመቻቸት የማኅበረሰብ መማማሪያ ማዕከላት ጉልህ ሚና
ይጫወታሉ፡፡ በተለይም ዝቅተኛ የማንበብና የመፃፍ ባሕል ባለበት ማኅበረሰብ ውስጥ
የማኅበረሰቡን የማንበብና የመፃፍ ክህሎት ለማሳደግና የተቀናጀ ተግባር ተኮር የክህሎት
ሥልጠናዎችን ለመስጠት አስተዋጿቸው የላቀ ነው፡፡ በተጨማሪም የማኅበረሰብ መማማሪያ
ማዕከላት ህፃናትና ጎልማሶች በጋራ የሚማሩበት የሚወያዩበትና ቤተሰባዊ መማማርን ተግባራዊ
የሚያደርጉበት ማዕከልም በመሆን ሊያገለግል ይችላል፡፡ በመሆኑም የማኅበረሰብ መማማሪያ
ማዕከላትን ማስፋፋትና ዐቅማቸውን ማሳደግ አስፈላጊነቱ የሚያጠያይቅ አይደለም፡፡
8
ምዕራፍ አንድ
1. የማኅበረሰብ መማማሪያ ማዕከል (ማ.መ.ማ.) ጽንሰ-ሀሳብ
የዚህ ምዕራፍ ዓላማዎች
የኢትዮጵያ ትምህርት ሚኒስቴር፣ (2016 እ.ኤ.አ.) ባወጣው ረቂቅ ስትራተጂ የማ.መ.ማ. ማለት
ማኅበረሰቡን የበለጠ ጠንካራ ለማድረግ በማኅበረሰቡ ውስጥ ላለ ማኛውም ሰው መረጃና ዕድሜ
ልክ የመማር ልምድ የሚያገኝበት ማዕከል ነው ሲል ተርጉሞታል፡፡ ይህ የማ.መ.ማ. አብዛኛውን
ጊዜ በማኅበረሰቡ አባላት ወይም በመንግሥት፣ መንግሥታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም በግሉ
ዘርፍ ድጋፍ የሚቋቋሙና የሚተዳደሩ ማኅበረሰብ-ተኮር ተቋማት ናቸው። መረዳት (ሊትሬሲ)፣
9
ድህረ- መረዳት (ፖስት ሊትሬሲ)፣ የገቢ ማስገኛ፣ የሕይወት ክህሎት ፕሮግራሞች እና ሌሎች
መሰረታዊ ትምህርቶች በማ.መ.ማ. ውስጥ ይሰጣሉ።
10
ለማጠቃለል የማ.መ.ማ. ዓላማዎች፡-
የአካባቢው ሰዎች በራሳቸው እንዲተማመኑ ለማድረግ
የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል
የማኅበረሰብ ልማትን ለማነቃቃት
የኅብረተሰቡን የተለያዩ ፍላጎቶች ለመለየትና መፍትሄ መስጠት
የማኅበረሰቡን ሰብአዊና ቁሳዊ ኃብት ለይቶ ለመጠቀምና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ወዘተ.
ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ ናቸው፡፡
በመቀጠልም በ2016 እ.ኤ.አ. በሞሮኮ በተካሄደው የተቋሙ የልምድ ልውውጥ መርኃ ግብር ላይ
የተገኙ ተሞከሮዎችን በማዳበር ዲቪቪ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የማ.መ.ማ
ፅንሰ ሃሳብን ለማስተዋወቅ ችሏል፡፡ በመቀጠልም በአማራ፣ በኦሮሚያና በደቡብ ብሔሮች፣
ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልሎች ከየክልሎቹ የትምህርት ቢሮዎች ጋር በመተባበር የማ.መ.ማ.
የሙከራ ፕሮጀክቶችን ሲሠራ የቆየ ሲሆን በሒደትም ወደአዲስ አበባና ትግራይም ለማስፋት
ችሏል፡፡ ከ2016 እ.ኤ.አ. ጀምሮ እስካሁን ድረስ ዲቪቪ ኢንተርናሽናል በመላ ሀገሪቱ ባለ 11
ወረዳዎች የማ.መ.ማ በመገንባትና ወደ ሥራ በማስገባት በየደረጃው ካሉ የመንግሥት ተቋማት
ጋር ተባብሮ እየሠራ ይገኛል፡፡
በመንግሥት ደረጃ የማ.መ.ማ ስትራቴጅ ረቂቅ (የኢትዮጵያ ትምህርት ሚኒስቴር፣ 2016 እ.ኤ.አ.)
የተዘጋጀ ቢሆንም እስካሁን ወደ ተግባር አልገባም፡፡
11
በመንግሥት በኩል የተቀናጀ ተግባር ተኮር የጎልማሶች ትምህርት ፕሮግራም ትግበራ ትኩረት
ተሰጥቶት በመሠራቱ ምክንያት በርካታ ጎልማሶች ማንበብና መፃፍ ችለዋል፡፡ ነገር ግን እነዚያ
ማንበብና መጻፍ የቻሉ ጎልማሶች የሁለት ዓመት መርኃ ግብር ካጠናቀቁ በኋላ በተለያየ ዘርፍ
ትምህርታቸውን ለመቀጠል ፍላጎት እንዳላቸው ጠይቀዋል። አንዳንዶቹ በየአካባቢያቸው የንባብ
ማዕከላት እንዲኖራቸው ሲፈልጉ ሌሎች ደግሞ ወደ መደበኛው ትምህርት ቤት መግባት
ይፈልጋሉ፡፡ አሁንም አብዛኞቹ ተመራቂ ጎልማሶች ኑሮአቸውን መሰረት አድርገው የተለያዩ
ዓይነት ክህሎት የሚማሩበት የማ.መ.ማ. እንዲቋቋም ጠይቀዋል።
ከላይ የተገለጹትን የተመራቂ ጎልማሶችን ፍላጎት ከግምት ውስጥ በማስገባት በሁሉም ክልሎች
እና ከተማ አስተዳደሮች የማ.መ.ማ. እንዲቋቋም በትምህርት ሚኒስቴር በኩል ተቀባይነት ያገኘ
ሲሆን ይህም ስትራቴጂ ተጀምሮ የማስፈጸሚያ ሰነዶች እየተዘጋጀ ነው።
12
1.5. የማኅበረሰብ መማማሪያ ማዕከላት (CLC) ጥቅሞች
የኢትዮጵያ ትምህርት ሚኒስቴር (2016 እ.ኤ.አ.) ባዘጋጀው ረቂቅ እስትራቴጅ እንደተገለፀው
የማ.መ.ማ. የሚከተሉት ጠቀሜታዎች አሏቸው፡፡
13
የአመለካከትን ማዘመን፡- አንዳንድ ማ.መ.ማ.ዎች የአካባቢውን ሕዝቦች ለሌሎች ብሄር
ብሄረሰቦች እና ብሄረሰቦች መቻቻል ያዳበሩ እና የበለጠ ሰላማዊ አብሮ መኖር ያስገኙ
እንደሆኑም ይታወቃል። በተጨማሪም በማ.መ.ማ. ሥልጠና የብዙ ሴቶችን ማብቃት
በሥርዓተ-ፆታ እኩልነት ላይ የበለጠ የዳበረ አረዳድ አስገኝተዋል፡፡
በአካባቢ አስተዳደር ውስጥ መሳተፍ፡ የዴሞክራሲ ሒደቶችን ማሳደግ፣ ትኩረት
የተነፈጋቸው ሰዎችን ከማብቃት ጎን ለጎን በአካባቢ አስተዳደር መዋቅሮችና በአካባቢ ውሳኔ
አሰጣጥ ላይ ከፍተኛ ተሳትፎ እንዲኖር አድርጓል።
14
5. ጤና እና ንፅህና፡- የማኅበረሰቡ አባላት ጤናማ ሆነው በመቆየት የማኅበረሰብን ደህንነት
ማጠናከር ይችላሉ። ስለዚህ የማ.መ.ማ. ሰዎች ስለ በሽታ መከላከል፣ መሰረታዊ ንፅህና
እና የተሻለ የአመጋገብ ሥርዓት የሚማሩበት ቦታ ሊሆን ይችላል፡፡
6. የኑሮ ደረጃ ማሻሻል፡- አንዳንድ የማኅበረሰቡ አባላት የራሳቸውን ልዩ ፍላጎት የሚጠቅም
ዕውቀትን ለማግኘት ራሳቸውን በትናንሽ ቡድኖች ማደራጀት ይችላሉ። እነዚህ ቡድኖች
ሴት፣ ወጣቶች፣ አረጋውያን እና አካል ጉዳተኞች ይገኙበታል። እነዚህ ቡድኖች የቡድኑን
አባላት የኑሮ ሁኔታ በሚያሻስሉ ተግባራት ላይ ለመሰማራት አማራጭ ሃሳቦች የሚገኙበት
በመሆን ያገለግላሉ፡፡
7. የሀይማኖት እና የአካባቢ ባሕል፡- በማኅበረሰቡ የሚገኙ ጥበበኛና አስተዋይ አረጋውያን
ልዩ ዕውቀታቸውን፣ ጥበባቸውን፣ እሴታቸውን፣ ለአዲሱ (ለቀጣዩ) ትውልድ ማስተላለፍ
ይችላሉ። ይህ ተግባር በኅብረተሰቡ ውስጥ ያለውን ዕውቀት በመጠቀም ሁሉም ሰው
በአስተሳሰብ ፣በውሳኔ እና በድርጊት የመሳተፍ ዕድል ስላለው የማኅበረሰቡ የመጨረሻ ግብ
ማኅበረሰብ አቀፍ ዐቅም ግንባታ ላይ ለመድረስ የሚያስችል የሕይወት ዘመን ትምህርት
እንዲኖር የሀገሪቱን ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ አስተዋጽኦ ያደርጋል።
15
ምዕራፍ ሁለት
2. በማኅበረሰብ መማማሪያ ማዕከላት የሚከናወኑ ተግባራት
የማነቃቂያ ጥያቄ
ዓላማ
16
የማ.መ.ማ. እንቅስቃሴዎችን በማደራጀት እና በመተግበር ረገድ ድጋፍ ለማግኘት
ከመንግሥት መስሪያቤቶችና ከአካባቢ ልማት አጋሮች ጋር ግንኙነት መፍጠር፣ ዋና
ዋናዎቹ ናቸው፡፡
17
የስኬት ታሪኮችና የፈጠራ ሥራዎች የልምድ ልውውጥና ስርጭት፣
የገበያ መረጃን ጨምሮ የተለያዩ መረጃዎችን ለማሳየት በማ.መ.ማ. ውስጥ የማስታወቂያ
ሰሌዳን ማዘጋጀት፣
ለመረጃ ማከማቻና ስርጭት ኮምፒተር መጠቀም እንዲሁም ለመቅዳት፣ ለማሳየትና መረጃ
ለመለዋወጥ ግንኙነት ሌሎች የአይሲቲ መሳሪያዎችን መጠቀም ወዘተ… ያካትታል፡፡
18
እንደ ማንበብ፣ መጻፍ፣ ሙዚቃ፣ ጥበብ ወዘተ ያሉ የተለያዩ ውድድሮችን ማዘጋጀት፣
በተለያዩ አጋጣሚዎች የአካባቢና ሀገር በቀል ባሕላዊ ሁነቶችን ማዘጋጀ፣
የመጽሐፍ ኤግዚቢሽኖችን እንዲሁም የመጽሃፍ ልውውጥ መርኃ ግብሮችን ከሌሎች
ተቋማትና የማ.መ.ማ. ጋር ማደራጀት፣
ባሕላዊ ውዝዋዜዎችን፣ ባሕላዊ ጥበቦችንና ባሕላዊ ዘፈኖችን ያደራጁ፣
እነዚህን አጠቃላይ ግቦች በግልፅ ግምት ውስጥ በማስገባት የማ.መ.ማ. አስተባባሪዎች ከማኅበረሰቡ
አባላት ጋር የሚከተሉትን የማ.መ.ማ. ዕቅድ እና አስተዳደር ባህሪያትን ግምት ውስጥ ማስገባት
አለባቸው፡-
1. ድርጅታዊ መዋቅር፣
2. በዕቅድ እና በአስተዳደር ዑደት ውስጥ የተወሰኑ ተግባራት፣
3. የኃብት ልማት ስልቶች፣ እና
4. የኃብት ማሰባሰብ እና ከሌሎች ድርጅቶች ጋር መገናኘት ።
19
ምዕራፍ ሦስት
3. የማኅበረሰብ መማማሪያ ማዕከላትን ማቋቋም
የማነቃቂያ ጥያቄዎች
ዓላማ
20
3.1.2. በማኅበረሰቡ ውስጥ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ
በማንኛውም ማኅበረሰብ ውስጥ በትክክል መሥራት ከመጀመሩ በፊት የማኅበረሰቡ አባላት ስለ
ማ.መ.ማ. ዓላማ እና ግብ እንዲያውቁ ማድረግ በጣም አስፈላጊ ነው። የኅብረተሰቡን ተሳትፎ
ለማረጋገጥ የማኅበረሰቡን ነዋሪዎች ማ.መ.ማ ደጋፊና ተጠቃሚ ማወቅ ወሳኝ ነው። የት/ቤት
መምህራን፣ የማኅበረሰቡ መሪዎች፣ መነኮሳት እና የአካባቢ መንግሥት ተወካዮች ለማ.መ.ማ.
ድጋፍ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ ላይ ወሳኝ ሚና መጫወት ይችላሉ። የመንደር ስብሰባዎችን
ማካሄድ፣ የባሕል ፕሮግራሞችን ማደራጀት፣ በሃይማኖት ተቋማት መልዕክት ማስተላለፍ፣
በትምህርት ቤትና በገበያ ቦታዎች ሕዝባዊ ቅስቀሳ ማካሄድ ስለማ.መ.ማ. ሰዎችን ለማሳወቅ
ውጤታማ ዘዴዎች ሊሆኑ ይችላሉ።
21
3.1.3. በማ. መ.ማ. ምስረታ ሒደት የማኅበረሰቡን ተሳትፎን ማሳደግ
የማኅበረሰቡን ሰዎች ለማ.መ.ማ. ሥራዎች ለማነሳሳት፣ ስለማ.መ.ማ. ሚና፣ እንቅስቃሴዎቹ እና
ውጤቶቹ ጠቃሚነቱን እንዲያውቁ እና እሱን እንዴት መደገፍ እንደሚችሉ እንዲያውቁ ግንዛቤ
መፍጠር አለብን። ስለዚህ ሁሉንም ሰዎችን የማ.መ.ማ. ገጽታዎች በሚመለከት ዕውቀትና መረጃ
ማስታጠቅ አስፈላጊ ነው። የማኅበረሰቡ ሰዎች በማ.መ.ማ.ተግባራት ፍላጎቶቻቸው እና
ስጋቶቻቸው እየተስተናገዱ መሆኑን ሲመለከቱ በማ.መ.ማ.እንቅስቃሴዎች ለመሳተፍ ፍላጎት
ይኖራቸዋል።
በማኅበረሰብ ሥራዎች የሰዎችን ተሳትፎ ለማረጋገጥ አንዱ ምርጥ ስልት የብዙ ሰዎችን
መስተጋብር እና ድርጊት የሚጠይቁ ተግባራትን መንደፍ ነው። የማኅበረሰብ ልማት እውነተኛ
ተሳትፎ በእያንዳንዱ አባል ትብብር ላይ የተመሰረተ ነው። በገንዘብ እጥረት ምክንያት ብዙ
የማኅበረሰቡ አባላት ለማኅበረሰብ ልማት ሥራዎች የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ አይችሉም፡፡ ነገር
ግን አስተዋፅዖ እንዲያበረክቱ ዕድል ከተሰጣቸው በጥበባቸው፣ በተሞክሮአቸውና በሙያቸው
ጠንካራ ድጋፍ ሊያደርጉ ይችላሉ። ሰዎችን ለማነሳሳት ቁሳዊ ሽልማቶች ሁልጊዜ አስፈላጊ
እንዳልሆኑ ግምት ውስጥ ማስገባት አስፈላጊ ነው፤ ምክንያቱም ተሳታፊወቹ ጎልማሶች
እንደመሆናቸው መጠን ውስጣዊ ተነሳሽነት ከቁሳዊ ሽልማት የላቀ ያበረታታቸዋል፡፡ እውቅና
መስጠት ከሽልማት የበለጠ ውጤታማ ነው። ሰዎች በውስጣቸው የሚያሳድጉት ተነሳሽነት
በእምነታቸው ላይ የተመሰረተና የበለጠ ረጅም ጊዜ የሚቆይ ነው::
22
አስተዳደር ኮሚቴ አባላት መምረጥ ያስፈልጋል። የማ.መ.ማ. ኮሚቴ ሰብሳቢ፣ ምክትል ሰብሳቢ፣
አባላትና ቋሚ ጸሃፊ ያሉት ሆኖ ሊደራጅ ይችላል፡፡ ነገር ግን በማኅበረሰቡ አባላት ድጋፍ መመረጥ
አለባቸው፡፡ እንደ ማኅበረሰብ መማማሪያ ማዕከላት ዓይነትና ተፈጥሮ የሚከናወኑ ተግባራትን
የሚያግዙ ልዩ ልዩ ንዑሳን ኮሚቴዎችን ማደራጀትም ሊያስፈልግ ይችላል፡፡
23
ምዕራፍ አራት
4. የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት
የማነቃቂያ ጥያቄዎች
ዓላማ
24
ይቻላል፡፡ አስተማማኝ መረጃ ለማግኘት የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎችን እና መሳሪያዎችን በአግባቡ
መጠቀም በጣም አስፈላጊ ነው:: የፍላጎት መመዘኛ ዘዴዎችን እና መሳሪያዎችን መምረጥ እና
መጠቀም ከመንግሥት እና መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም ከትምህርት ቤት
መምህራን ድጋፍ ማግኘት እንችላለን። ፍላጎቶችን ለመገምገም አንድ ወይም ብዙ ዘዴዎችን እና
ተስማሚ የሆኑትን መሳሪያዎች መምረጥ እንችላለን:: የበርካታ ዘዴዎች እና መሳሪያዎች
ምሳሌዎች ከዚህ በታች ተብራርተዋል (የካምቦዲያ ትምህርት ሚኒሰቴር፣ 2014 እ.ኤ.አ.)፡፡
25
ግላዊ መረጃቸውን ለመጠበቅ ምላሻቸው እንዴት ጥቅም ላይ እንደሚውል ለጠያቂው ግልጽ
ማድረግ አለብን። መጠይቆችን ካስሞላን በኋላ ሁሉንም መረጃዎች በማሰባሰብ መተንተን
ይገባናል፡፡ ፡
26
ምዕራፍ አምስት
5. የማኅበረሰብ የመረጃ ቋት (Database) ማቋቋም
ዓላማ፡
የማነቃቂያ ጥያቄዎች
ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ
የማኅበረሰቡ ታሪክ
የተፈጥሮ ኃብት፣
ከሕዝብ ጋር የተያያዙ መረጃች (ቁጥር/ብዛት፣ በፆታ፣ በዕድሜ፣ በኑሮ ደረጃ፣ በሥራ
መስክ፣ ወዘተ.)
የሚገኙ ተቋማት (ትምህርት ቤት፣ ኮሌጅ፣ የሃይማኖት ተቋማት፣ ክሊኒኮች፣ የማኅበረሰብ
አዳራሾች፣ የአርሶ አደር ማሰልጠኛ ማዕከላት፣ ወዘተ…)
የኢኮኖሚ ሁኔታ (ሙያ፣ ሥራ፣ የኢኮኖሚ ፀጋዎች፣ የድህነት ደረጃ፣ ወዘተ)፣
የአመራር ዘይቤ
የመኖሪያ ቤት ንድፍ;
የመንገድ ግንኙነት
27
የመብራት፣ የሚዲያ እና የኢንተርኔት አገልግሎት
አገልግሎት ሰጭ ኤጀንሲዎች እና አገልግሎቶቻቸውን በተመለከተ
የትምህርት ሁኔታ (የትምህርት ደረጃ፣ በዕድሜ፣ በፆታ፣ እንዲሁም ድምር መረጃ)
የፋይናንስ ተቋማት
የጤና እና የንፅህና አጠባበቅ ሁኔታ
የማኅበረሰብ መሠረተ ልማት
የሀገር ውስጥ ድርጅቶች፣ ማኅበራት፣ ክለቦች ወዘተ
የማኅበረሰቡ ችግሮች እና ተግዳሮቶች
በማኅበረሰቡ ውስጥ የሚገኙ ግብዓቶች
የመንግሥት የሚቀርቡ የድጋፍ ዓይነቶች
ሀገር በቀል ዕውቀቶችና ጥበቦች
የኅብረተሰቡ ጥንካሬ እና ድክመቶች፣
የልማት አጋጣሚዎችና ስጋቶች፣ ወዘተ…
28
5.3. የመረጃ አሰባሰብ ሒደት
ከመንግሥታዊ ምንጮችና ሰነዶች መረጃ ማግኘት እንችላለን፡፡ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች
እና የማኅበረሰብ ድርጅቶች ጠቃሚ መረጃ ሊሰጡ ይችላሉ። በማኅበረሰብ የምክክር ስብሰባዎች፣
ቃለ-መጠይቆችን በማካሄድ ወይም የትኩረት ቡድን ውይይቶች የማኅበረሰብ የመረጃ ቋት
ለማዘጋጀት መረጃ ማግኘት እንችላለን። እንደ መጠይቆች፣ ፎርማት፣ ቼክ ሊስት ወዘተ የመሳሰሉ
መረጃዎችን ለመሰብሰብ ተገቢ መሳሪያዎች መዘጋጀት አለባቸው። የመንግሥት ባለሥልጣናት፣
የትምህርት ቤት መምህራንና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ኃላፊዎች መረጃ ለመሰብሰብ
ተገቢ መሳሪያዎችን በማዘጋጀት ሊረዱን ይችላሉ። የማኅበረሰብ የመረጃ ቋት ለማ.መ.ማ. ዕቅድ
ማውጣት እና ውሳኔ መስጠት በጣም አስፈላጊ ስለሆነ ሁሉም መረጃዎች ተጠብቀው በማ.መ.ማ.
ውስጥ መታየት እና በየጊዜው መዘመን አለባቸው።
29
ምዕራፍ ስድስት
6. የማኅበረሰብ መማማሪያ ማዕከላት አደረጃጀትና አስተዳደር
ዓላማ
ለማ.መ.ማች ውጤታማ ዕቅድ ማውጣትና ማስተዳደር ተገቢ የሆነ የድርጅት መዋቅር መፍጠር
አስፈላጊ ነው። ይህ መዋቅር ከማኅበረሰቡ የአስተዳደር ሥርዓት፣ የአካባቢ ኢኮኖሚ እና ማኅበራዊ-
ባሕላዊ ባህሪያት ጋር የሚስማማ እና ተቀባይነት ያለው መሆን አለበት፡፡ የማኅበረሰብ መማማሪያ
ማዕከላትን በየጊዜው ማጠናከር እና አስተዳደሩን ማሻሻል አለበት፡፡ እሸቱ እና አማኑኤል (2017
እ.ኤ.አ.) እንደገለፁት ለትልቅ የማ.መ.ማ. ተስማሚ ሊሆን የሚችል የድርጅታዊ መዋቅር ዓይነተኛ
ምሳሌ የሚከተለውን ይመስላል፡፡
30
የወረዳ ትምህርና ስልጠና ቦርድ
አመቻች
31
በዚህ ረገድ የተቀናጀ ተግባር ተኮር የጎልማሶች ትምህርትን ተግባራዊ ለማድረግ የተዋቀረው
ቦርድና የቴክኒክ ኮሚቴ የታየበት ዓይነት መፋዘዝና የሥራ መገፋፋት በማ.መ.ማ ሊደገም
አይገባውም፡፡ ሁሉም ባለድርሻ የየድርሻውን ተግባር ቆጥሮ መረከብ ያለበት ሲሆን ወደ ትግበራ
ከመገባቱ በፊትም ሁሉም የማ.መ.ማ የኮሚቴ አባላት፣ አስተባባሪዎች፣ አመቻቾች፣ ንብረት
ክፍል እና ጸሐፊ ማን ምን መሥራት እንዳለባቸው የሚያሳይ ዝርዘር የሥራ መግለጫ ሊሰጣቸው
ይገባል፡፡
32
6.4. የማኅበረሰብ መማማሪያ ማዕከል ዕቅድ ዝግጅት
ወጪ ቆጣቢ መሆናቸውንና ማኅበረሰቡን ተጠቃሚ እያደረጉ መሆናቸውን ለማረጋገጥ
የማኅበረሰብ መማማሪያ ማዕከላት ተግባት በአግባቡ ማቀድና በተደራጀ አግባብ መተግበር እጅግ
አስፈላጊ ነው፡፡ ይህንም ለማድረግ የማኅበረሰብ መማማሪያ ከመመስረቱ በፊት የማኅበረሰቡ
አጠቃላይ አባላት ስለ መማማሪያ ማዕከሉ ራዕይና ግብ እንዲኖረው ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ይህንን
ለማድረግም የማኅበረሰቡን አጠቃላይ ገጽታ እንዲሁም ዐቅም ማወቅ የሚጠይቅ ሲሆን ይህንንም
የማኅበረሰብ አቀፍ ንቅናቄና የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
የማነቃቂያ ጥያቄዎች
1. የተለመዱ የማህበረሰብ መማማሪያ ማዕከል የእቅድ ክፍሎች ምን ምን ናቸዉ?
2. በማ.መ.ማ ምን ምን ተግባራት ሊከናወኑ ይችላሉ ብላችሁ ታስባላችሁ?
3. በማ.መ.ማ ውስጥ የማዕከሉን እቅድ የማዉጣት ኃላፊነት የማን ይመስላችኋል?
የማ.መ.ማ.ን ዕቅድ ማዘጋጀት የማዕከሉ አስተዳደር ኮሚቴ ዋና ተግባር ነው፡፡ የማ.መ.ማ. ዕቅድ
ሲዘጋጅ የማኅበረሰቡ ፍላጎት፣ ማኅበራዊና ባሕላዊ ሁኔታ እንዲሁም የማ.መ.ማ. ተሳታፊ
የሚሆኑ ሰዎች የኢኮኖሚያዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ መግባት ይኖርበታል፡፡ በተጨማሪም
የሚጠበቀው የማኅበረሰብ ተሳትፎ ደረጃና በፕሮግራም ትግበራ ውስጥ ሊያጋጥሙ የሚችሉ
እንቅፋቶችን ግምት ውስጥ ማስገባት አስፈላጊ ነው፡፡
33
በቀል ዕውቀትን ከፍ ለማድረግ የማዕከሉን ዕቅድ ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ማቀናጀት
ያስፈልጋል።
1. የማ.መ.ማ. መርኃ ግብር ግብና ዓላማ ማውጣት፡ የማ.መ.ማ. መርኃ ግብር ፕሮግራሞች
ግብና ዓላማ ከማኅበረሰቡ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት በተገኘ መረጃ መሰረት መቀረፅ አለባቸው።
2. የመርኃ ግብር አተገባበር አጠቃላይ ስልቶችን መወሰን፡ ጥንካሬዎችን፣ ድክመቶችን፣
ዕድሎችን ስጋቶችን ከግምት ውስጥ በማስገባት የማ.መ.ማ. ኮሚቴ አባላት የማ.መ.ማ.
መርኃ ግብር አተገባበር አጠቃላይ ስትራቴጂዎችን በመወሰን በተገኘው መንገድ ተፈላጊ
ውጤቶችን ማግኘት አለባቸው። የማ.መ.ማ. ዋና ዋና መርኃ ግብሮች እንዴት ተግባራዊ
እንደሚያደርግ መወሰን አለበት።
34
መርኃ ግብሮችን ውድቀቶችና ስኬቶች መገምገም የተሻለ ነው። ካለፈው ልምድ የተገኙ
ትምህርቶችን መተንተንና መመርመር እንዲሁም የተከተሉትን ስትራቴጂዎች
ውጤታማነት ማረጋገጥ በጣም ውጤታማ ነው። እነዚህ ግንዛቤዎች ስህተቶችን
ለማስወገድ እና ተገቢ የአተገባበር ስልቶችን ለመለየት ይረዱናል.
4. የተወሰኑ የአተገባበር ስልቶችን መወሰን፡ እያንዳንዱ ፕሮግራም የራሱ ባህሪያት አሉት።
በእያንዳንዱ መርኃ ግብር ዓላማዎችና ተግባራት ላይ በመመስረት, ልዩ የትግበራ ስልቶች
መወሰን አለባቸው፡፡ ለምሳሌ፡ የማ.መ.ማ. የአስተዳደር ኮሚቴዎች ተሳታፊዎችን
በማ.መ.ማ. ለማሰልጠን በማ.መ.ማ. የክህሎት ሥልጠናዎችን ከማደራጀት ይልቅ
በአካባቢው ካለ የክህሎት ማሰልጠኛ ተቋም (ቴክኒክና ሙያ) ጋር ግንኙነት መፍጠር
አማራጭ ሊሆን ይችላል፡፡
5. ከሀገራዊ ፖሊሲዎችና ዕቅዶች ጋር መጣጣም፡ የማ.መ.ማ. መርኃ ግብሮች ከሀገራዊና
ከአካባቢያዊ ልማት ዕቅዶች ጋር ወጥነት ባለው መልኩ መቀረጽ አለባቸው። ሌሎች
ባለድርሻ አካላት የማይሠሩባቸውን ተግባራት ማቀድ እንችላለን። በዚህ ረገድ ከመንግሥት
አካላት እና ከአካባቢው ባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር ማድረግ በጣም አስፈላጊ ነው።
6. ዋና እና ንዑስ ተግባራትን መወሰን፡ መርኃ ግብሩን ለመተግበር የተለያዩ ተግባራትን
ማከናወን ያስፈልጋል። የማ.መ.ማ. አስተዳደር ኮሚቴ በእያንዳንዱ እንቅስቃሴ ውስጥ
የተካተቱ ተግባራትንና ንዑስ ተግባራትን መወሰን አለበት።
7. የሰው ኃብት ዕቅድ ማውጣት፡- ለማንኛውም መርኃ ግብር ትግበራ የሰው ኃይል በጣም
አስፈላጊ ነው። ለምሳሌ የመረዳት (ሊትሬሲ) ማሰልጠኛ መርኃ ግብር ለመጀመር
በማኅበረሰብ መማማሪያ ማዕከሉ ምን ያህል አመቻቾችና አሠልጣኞች ለምን ያህል ጊዜ
እንደሚያስፈልጉ መወሰን አለበት። እንዲሁም የትምህርት ብቃታቸውና ዕውቀታቸው ምን
እንደሚሆን፣ እንዴት እንደሚቀጠሩና ምን ዓይነት ሥልጠና እንደሚሰጣቸው ወዘተ…
መወሰን አለበት፡፡
8. የበጀትና የግብአት ዕቅድ ማዘጋጀት፡- ለማኅበረሰብ መማማሪያ ማዕከላት ምን ዓይነት
የበጀት ድጋፍ እንደሚያስፈልግ፣ ከየትኞቹ ምንጮች እንደሚገኝ እንዲሁም ገንዘቡ እንዴት
እቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚውል በግልፅ መታቀድ አለበት።
9. የሰው ኃይል ልማት ዕቅድ ማውጣት፡ ዋና ዋና ተግባራትን የሚያከናውኑ እንዲሁም
የድጋፍ ሥርዓቱን የሚመሩ ሰዎች ተለይተው ሊሠለጥኑ ይገባል። የፈፃሚዎችና የድጋፍ
ሰጪ ባለሙያዎች ሥልጠና በዝርዝር ሊታቀድ ይገባል፡፡
35
10. የድርጊት መርኃ ግብር ማዘጋጀት፡- የድርጊት መርኃ ግብሩን ለማስፈጸም የሚከናወኑ
ተግባራትን በዝርዝር ይገልፃል፡ በዚህ ፕሮግራም ውስጥ መተግበር ያለባቸው ዋና ዋና
ተግባራት ምን ምን እንደሆኑ፣ እነዚህ ተግባራት መቼ እንደሚከናወኑ እና እነዚህን
ተግባራት ለማከናወን ኃላፊነቱን የሚወስደው ማን እንደሆነ የሚገልፅ ዝርዝር የድርጊት
መርኃ ግብር ማዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡
11. አስተዳደራዊ ስልቶችን (Management strategies) ማዘጋጀት፡- ዕቅድ ስናወጣ አጠቃላይ
የመርኃ ግብሩን አፈፃፀም ሒደት እንዴት እንደምንቆጣጠርና እንደምንመራ መወሰን
አለብን። የማ.መ.ማ. መርኃ ግብሮችን ውጤታማ በሆነ መንገድ ተግባራዊ ለማድረግ
በተለያዩ ኤጀንሲዎች መካከል ትክክለኛ ቅንጅትና ትስስር ዘዴዎች መወሰንና በዕቅዱ
ውስጥ ማካተት አስፈላጊ ነው።
12. የመርኃ ግብሩን ዘላቂነት ማቀድ፡- ዘላቂነት ያለው ዕቅድ ለፕሮግራሙ የመጨረሻ ስኬት
በጣም አስፈላጊ ነው። የማ.መ.ማ. የማኔጅመንት ኮሚቴ የመርኃ ግብሮቹን ዘላቂነት
የሚያረጋግጡ ስልቶች መቀየስ አለበት።
13. የግምገማ ዕቅድ ማዘጋጀት፡- በዚህ የዕቅድ ደረጃ የተግባር ክንውኖች ስኬትና ግስጋሴን
እንዴት እንደምንከታተል፣ እንደምንቆጣጠር እንዲሁም መቼ ምን ዓይነት የማስተካከያ
እርምጃዎች እንደምንወስድ እና የመርኃ ግብሮቹ ተፅዕኖዎች መቼና እንዴት
እንደሚገመገሙ መወሰን አለብን። ተግባራት ከመጀመራቸው በፊት የክትትል፣ የግምገማ
እና የሪፖርት አቀራረብ ሒደት መነደፍ አለበት።
36
ምዕራፍ ሰባት
7. የማ.መ.ማ፣ ሠራተኞችን ዐቅም መገንባት
የማነቃቂያ ጥያቄ
37
ከዐቅም ግንባታ ጋር የተያያዙ ተግባራትን በየጊዜው መከታተልና መገምገም አስፈላጊ ነው።
የዐቅም ግንባታ ተግባራትን ተፅእኖ በማሳደግ በማኅበረሰብ ደረጃ የዐቅም ማጎልበቻ ተግባራትን
ውጤታማነት ለማሳደግ ልንጠቀምባቸው የምንችላቸው ቴክኒኮች አሉ (የካምቦዲያ ትምህርት
ሚኒሰቴር፣ 2014 እ.ኤ.አ.)። እነዚህም፡-
የምዕራፉ ዋና አላማ፡
የማነቃቂያ ጥያቄዎች
1
የማመማ ቀጣይነትን በተመለከተ በመጨረሻዉ ምዕራፍ በዝርዝር እንመለከታለን፡፡
39
እንደ እሸቱ እና አማኑኤል (2017 እ.ኤ.አ.) ገለፃ በማኅበረሰብ አቀፍ እንቅስቃሴዎች ውስጥ
የማኅበረሰቡ አባላት የተሳትፎ ደረጃ በሦስት ይከፈላል፡፡ እነዚህ የተሳትፎ ደረጃዎችም
እንደሚከተለው ተብራርተው ቀርበዋል፡፡
40
የማ.መ.ማ. አስተባባሪዎች ስለእነዚህ የተለያዩ የተሳትፎ ደረጃዎች ማወቅና ሁሉም በማኅበረሰቡ
ውስጥ ያሉ ሰዎች በመጨረሻ የውሳኔ አሰጣጡ አካል እንዲሆኑ ለማድረግ መሞከር አለባቸው
(እሸቱ እና አማኑኤል, 2017 እ.ኤ.አ.)።
41
የቤት ለቤት ዘመቻዎች፣ የእግር ጉዞዎች እና ሒደቶች፣
የሬዲዮ ማስታወቂያዎች፣ የመንገድ ዳር ጨዋታዎች፣
የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች፣ በራሪ ወረቀቶች ስርጭት ወዘተ…
የዘፈን፣ የሥዕል፣ የታሪክ፣ የስነ- ግጥም፣ ፉከራ፣ ሽለላ፣ ውዝዋዜ፣ ወዘተ. ዓይነት
ውድድሮች፣
42
ማኅበረሰቡን በራሳቸው ማኅበራዊ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ እንዲሰጡ ማበረታታት፣
በማኅበረሰብ ልማት እንቅስቃሴዎች ውስጥ የሕዝብ ተሳትፎና ባለቤትነትን ማረጋገጥ፣
የአካባቢ ፀጋዎችን መለየትና መጠቀም፣
በማ.መ.ማ. እንቅስቃሴዎች ውስጥ የመሪነት ሚና እንዲጫወቱ የአካባቢውን ሰዎች ዐቅም
ማጎልበትና ማበረታታት፣
የማኅበረሰብ ባለቤትነትን ማዳበር፣
የማኅበረሰብ ልማት ተነሳሽነቶችን እና ተግባራትን ማስቀጠል።
43
አስፈላጊ ነው። የሰዎችን ፍላጎትና ዐቅም ግምት ውስጥ በማስገባት የገንዘብ ማሰባሰብ ተግባራትን
በማ.መ.ማ አስተዳደር ኮሚቴ አባላት መካከል ሊከፋፈሉ ይችላሉ። ከማ.መ.ማ አስተዳደር ኮሚቴ
አባላት በተጨማሪ የአካባቢው አስተዳደር እና የልማት አጋሮች ለማ.መ.ማ. ሀብቶችን በማሰባሰብ
ረገድ ወሳኝ ሚና መጫወት ይችላሉ። የማ.መ.ማ አስተዳደር ኮሚቴ ኃብት ማሰባሰብ
የሚችልባቸው አንዳንድ ምንጮች የሚከተሉት ናቸው።
44
የማ.መ.ማ. መርኃ ግብሮችን ተግባራት በማስተባበርና ኃብት በ፣ስተዳደር በንቃት
ለሚሳተፉ ሰዎች ሥልጠና መስጠት፣
በጣም ተስማሚ መሳሪያዎችን እና ቴክኖሎጂዎችን ብቻ መግዛትና መጠቀም፣
የማኅበረሰቡ አባላት ውሳኔ እንዲወስኑና ለራሳቸው መርኃ ግብሮች ኃላፊነት እንዲወስዱ
ዕድሎችን መስጠት፣
ያጋጠሙ ወጪዎችን ለመከታተል ትክክለኛውን የሂሳብ አያያዝና የኦዲት ሒደቶችን
መጠቀም፣
የማ.መ.ማ ተግባራትን እና የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴዎችን በመምራት በውጫዊ ዕውቀት
ላይ ጥገኛ ከመሆን ይልቅ በአካባቢው ያሉ ባለሙያዎችንና ጥበባቸውን ጥቅም ላይ
ማዋል፣
ያሉትን ሀብቶች በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋል እና ለወደፊት ጥቅም ላይ የሚውሉ
መሆናቸውን ለማረጋገጥ ህገ ደንብ አዘጋጅቶ ተግባራዊ ማድረግ፣
የአካባቢው ሰዎች ለማ.መ.ማ. እና ለማኅበረሰቡ ዕድገት አስፈላጊ ናቸው ብለው
የሚሏቸውን ሀብቶች እንዲቆጣጠሩና የአካባቢ ሀብቶችን እንዲያስተዳድሩ ኃላፊነት
መስጠት፣
ሁሉም ሰው እንዲያየው የማ.መ.ማ የውስጥ በጀት ማጠቃለያ በማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ
መለጠፍ። ይህ የማ.መ.ማ. መርኃ ግብር ተግባራትና የፋይናንስ ግልጽነት እንዲኖራቸው
ያደርጋል፣
የማ.መ.ማ እንቅስቃሴዎችን በተለይም ሂሳብ አያያዝ ጉዳዮች ላይ መደበኛ ክትትልና
ግምገማ ማካሄድና ውጤቱን በማ.መ.ማ. ውስጥ ማሳየትና ውጤቱን ለመርኃ ግብሩ
ሥራዎችን ለማሻሻል ዓላማ መጠቀም፡፡
45
ምዕራፍ ዘጠኝ
9. ባለድርሻ አካላትን ማቀናጀት፣ ማስተሳሰርና ማገናኘት
የምዕራፉ ዓላማ፡-
46
የማይክሮ ፋይናንስ ብድር ከሚሰጡ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር ሊያገናኝ (ሊንኬጅ
ሊፈጥር) ይችላል።
በማህበረሰቡ ውስጥ ማንበብና መጻፍ እንዲሁም ቀጣይነት ያለው የትምህርት እንቅስቃሴን ውጤታማ
ለማድረግ የማ.መ.ማ አስፈላጊ መሳሪያወች ቢሆኑም አገልግሎታቸው በእነዚህ ተግባራት ብቻ መገደብ
የለበትም። የማ.መ.ማ. የመማርያና የማህበረሰቡን ጉዳዮች መወያያ ቦታ ተብሎ የሚታወቅበት ስለሆነ
ተግባራቶቹንና አገልግሎቶቹን በማስፋፋት በሌሎች በርካታ መንገዶች ለማህበረሰቡ ጥቅም ሊሰጥ ይችላል።
ነገር ግን ይህ እንዲሆን ማ.መ.ማ.ን ዘርፈ ብዙ እንቅስቃሴዎች ለመደገፍ አስፈላጊውን እውቀት፣ ግንኙነትና
ግብዓቶች ያላቸዉን አጋሮችና ተባባሪዎች መለየት አስፈላጊ ነው። ስለሆነም ከአጋሮች ጋር ትስስር
መፍጠርና እንደዚህ አይነት ትስስሮችን መዘርጋት ያስፈልጋል፡፡ የማ.መ.ማ. ማህበረሰቡን ለማገልገል፣
ችግሮቹን ለመፍታት እና ፍላጎቶቹን ለማሟላት ትክክለኛ የመማማሪያ ማዕከላትና የተለያዩ ተግባራትን
ለማከናወን የተግባራት ሁሉ የስበት ማዕከል (ማግኔት) ማድረግ ያስፈልጋል።
47
በእያንዳንዱ ማኅበረሰብ ውስጥ የጋራ ዓላማ ያላቸው እና እንደ ማ.መ.ማ. ተመሳሳይ ተጠቃሚዎች
ያላቸው የመንግሥት ክፍሎች፣ ተቋማት፣ ኤጀንሲዎች እና ድርጅቶች አሉ። የማ.መ.ማ.
አስተዳደር ኮሚቴ መርኃ ግብሮችን በመንደፍና በመተግበር ሒደት ላይ ሙሉ በሙሉ ወይም
በከፊል ጥቅም ላይ ሊውሉ የሚችሉትን የሌሎች ተቋማትን ሀብቶች ግምት ውስጥ በማስገባት
ማቀድና መሥራት አለበት፡፡
የትስስር ግንኙነቶች በጣም ጠቃሚ ሊሆን ይችላል፡፡ ምክንያቱም ትስስር የሚከተሉትን ማድረግ
ይችላል (የካምቦዲያ ትምህርት ሚኒሰቴር፣ 2014 እ.ኤ.አ.)፡፡
48
ምዕራፍ አስር
10. የማኅበረሰብ መማማሪያ ማዕከላት ክትትል፣ ግምገማና
ቀጣይነትን ማረጋገጥ
10.1. ክትትልና ግምገማ
ክትትልና ግምገማ ልምድና ችሎታ የሚጠይቅ ሙያዊ ሥራ ነው። በማ.መ.ማ ውስጥ የመርኃ
ግብሩን ተጠቃሚዎች በማሳተፍ አሳታፊ ክትትልና ግምገማ ማድረግ እንችላለን። ይህንን
ለማድረግ የክትትልና ግምገማ አመልካቾችን መለየትና መረጃና ማስረጃዎችን ለመሰብሰብ
ተስማሚ የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎችን (data collection tools) ማዘጋጀት አለብን:: በዚህ
ሒደት ከመንግሥት ኃላፊዎችና ከልማት አጋሮች ድጋፍ ማግኘት እንችላለን፡፡
ክትትልን ከመጀመራችን በፊት የሚከተሉትን ጉዳዮች ያካተተ የክትትል ዕቅድ ማዘጋጀት አለብን።
የክትትል ዓላማዎች
ክትትል ሊደረግባቸው የሚገቡ ተግባራት
ለክትትል ጥቅም ላይ የሚውል ጊዜ
ክትትልየሚደረግባቸው የፕሮጀክቱ ተግባራትና የሚጠበቁ ውጤቶች
የሚሰበሰበው መረጃ
የመረጃ አሰባሰብ ዘዴዎች
የክትትል ቡድን
የክትትል ድግግሞሽ (በወር ወይም በዓመት)
49
ዘዴው ምን ያህል ውጤታማ እንደሆነና እሱን ለመጠቀም ምን ያህል ጊዜ እና ዕውቀት
እንደሚያስፈልግ ለማረጋገጥ የክትትልና የግምገማ ዘዴዎች አስቀድመው መሞከር
አለባቸው።
የማ.መ.ማ. ተግባራት ስንገመግም የማ.መ.ማ መርኃ ግብር ዓላማዎች በጊዜ ሒደት ምን ያህል
እንደተሳኩ ማወቅ አለብን። በግምገማ የፕሮጀክቶቹን ወጪ ቆጣቢነት እና ለታለመላቸው
ተሳታፊዎች የሚጠበቀውን ለውጥ ስለማምጣታቸው መረጃ ማግኘት እንችላለን። በግምገማው
ውጤት መሰረት፣ የማ.መ.ማ የማኔጅመንት ኮሚቴ የማ.መ.ማ ተግባራትን መቀጠል ወይም
ማሻሻልን በተመለከተ ውሳኔ ሊሰጥ ይችላል። የሚከተለው ለዓላማ ተኮር ግምገማ ሊሰበሰቡ
የሚችሉ የመረጃ ዓይነቶች ናሙና ነው። እንደ አውዱ ጥያቄዎችን ማከል ወይም መቀነስ
እንችላለን።
50
ሰዎች አዲሱን ዕውቀትና ችሎታ እንዴት እየተጠቀሙበት ነው?
አመለካከታቸው ተለውጧል ወይ?
እነዚህ ለውጦች በሰዎች ሕይወት ላይ ምን ተጽእኖ አምጥተዋል?
2
ስለመረጃ ቋት ዝግጅትና አጠቃቀም በምዕራፍ አምስት በዝርዝር ተገልጿል፡፡
51
አስፈላጊ የደብዳቤ ልውውጦች፣
የሚዲያ ዘገባዎች፣
የቃለ መጠይቅ መዝገቦች፣
በማ.መ.ማ. ተሳታፊዎች (ሰልጣኖች) የተሰሩ ቁሳቁሶች ናሙናዎች፣
በጋዜጣና በመጽሔት ላይ ስለማ.መ.ማ. እንቅስቃሴዎች የታተሙ ጽሑፎች፣ እና
የተማሪዎችን የቃለ መጠይቅና የመማር ግኝቶች፡፡
የማ.መ.ማ.ተግባራትን የምንመዘግበው፡
52
መረጃዎቻችንን (ሰነዶቹን) በሚከተሉት መንገዶች ማሰራጨት እንችላለን (የካምቦዲያ ትምህርት
ሚኒሰቴር፣ 2014 እ.ኤ.አ.)።
53
የማ.መ.ማ.ን መርኃ ግብሮችን በመተግበር ላይ ለማኅበረሰቡ ተሳትፎ ተጨማሪ ቦታ
መስጠትና የባለቤትነት ስሜት እንዲፈጥሩ ማድረግ ያስፈልጋል፣
በባለድርሻ አካላትና በልማት አጋሮች መካከል የተሳትፎ፣ ትብብርና የኃብት መጋራት
ዕድሎችን መፍጠር፣
ተአማኒ የሆነ የመርኃ ግብር በጀት ማዘጋጀት፣
የገቢ ማስገኛ መርኃ ግብሮችን በማዘጋጀትና የተሳታፊዎችን የአገልግሎት ክፍያ
በመሰብሰብ የበጀት ዘላቂነት ማረጋገጥ፣
ከታማኝ ተቋማት የትብብርና የአጋርነት ድጋፍ ማግኘት፣
የአካባቢ አስተዳደር፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የሃይማኖት መሪዎች እና በማኅበረሰቡ
ተሰሚነት ያላቸውን ሰዎች ድጋፍ ማግኘት፣
በተቻለ መጠን ቁርጠኛ የሆኑ በጎ ፈቃደኞችን መመልመልና የአካባውን ሰዎች
በሠራተኝነት መቅጠር፣
ራሳቸውን ችለው እንዲቀጥሉ የማ.መ.ማ ሠራተኞችን ዐቅም መገንባትና ማብቃት፣
የማኅበረሰቡን ጥበብ ለመጠቀምና ሀብቶቹን ለማንቀሳቀስ የማኅበረሰቡን ዐቅም ማጎልበትና
ግንኙነትን ማሳደግ፣
የአካባቢያዊ ሁኔታን የመረዳትና አዊዳዊ ተግባራትን ለመጠቀም ከማኅበረሰቡ ውጭ
የሚመጡ የመርኃ ግብሩ ፈፃሚዎችን ዐቅም ማጎልበትና የመረዳ ክፍተትን መቀነስ፣
የማ.መ.ማ.ን መርኃ ግብሮች በማኅበረሰቡ አባላት የመታየት ወይም የመጎብኘት ዕድል
እንዲኖረው ማድረግ አስፈላጊ ነው፡፡
54
የማ.መ.ማ. የራሳቸውን ገቢ እንዲያመነጩ፣እና ሥራቸውን እንዲቀጥሉ ተገቢ የሆነ
ቴክኒካዊ ድጋፍ በወረዳ አስተዳደር፣በቀበሌ አመራር፣በማእከል አስተዳደር ኮሚቴዎች፣
በመንግሥት ሴክተር ተቋማት እና ሌሎች በጎ አድራጎት ድርጅቶች እንዲቀጥል ማድረግ።
55
ዋቢ መፃህፍት
እሸቱ አባተ፣ እና አማኑኤል ሃደራ. (2017). Manual for CLC Establishment and
Implementation.
እሸቱ አባተ፣ እና አማኑኤል ሃደራ. (2021). Expanding Community Learning Centres in
Ethiopia. Asqual.
ዩኔስኮ ኢንስቲትዩት ፎር ላይፍ ሎንግ ለርኒንግ. (2016). Synthesis Report on the State
of Community Learning Centres in Six Asian Countries Bangladesh, Indonesia,
Mongolia, Republic of Korea, Thailand and Viet Nam (Issue December 2016).
https://uil.unesco.org/literacy/community-learning/synthesis-report-state-
community-learning-centres-six-asian-countries
56