You are on page 1of 47

ቢቤትትሬዲንግ የእምነ በረድና ግራናይት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖ

ግምገማ ጥናት የወሰን ልየታ (SCOPPING) ሪፖርት

የፕሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ ስም:- ቢኒያም አእምሮ


አድራሻ፡- ባህር ዳር ስ/ቁ: +251- 918-37-57-57
ፕሮጀክቱ የሚገኝበት ቦታ:- ደብረ ማርቆስ ከተማ መንቆረር ክፍለ ቀተማ
ቀበሌ 11

ጥናቱ የሚቀርበዉ፡- ለደብረ ማርቆስ ከተማ አካባቢ ጥበቃ ጽዳትና

ዉበት አረንጓዴ ልማት ተ/ጽ/ቤት

ጥናቱን ያዘጋጀዉ፡- ኢትዮ ግሪን የአካባቢ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ

ጉዳዮች አማካሪ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

ስልክ፡- 0913411527/0961894478 /Email: - tiruneh242@gmail.com

ህዳር/2016

ደብረ ማርቆስ

ማውጫ

1
መግቢያ..........................................................................................................................................................5

1.2. የአከባቢ እና ማህበራዊ ተፅዕኖ ጥናቱ አላማ.............................................................................................6

1.3. የፕሮጀክቱ መገኛ ቦታ.......................................................................................................................7

1.4. የፕሮጀክቱ ጥቅል ዓላማ....................................................................................................................8

1.4.1. የፕሮጀክቱ ዝርዝር አላማዎች፡-................................................................................................8

1.5. የአከባቢ እና ማህበራዊ ተፅዕኖ ጥናቱ አላማ.............................................................................................8

1.6. የሪፖርቱ አስፈላጊነት......................................................................................................................8

1.7. የጥናቱ ስልት (ዘዴ)...........................................................................................................................9

2. የፕሮጀክቱ ገለፃ.....................................................................................................................................10

2.2. ግብዓቶች......................................................................................................................................10

2.3. የቴክኖሎጅ አይነትና የቴክኖሎጅ አጠቃቀም ገለጻ...............................................................................11

2.4. የግንባታ ወጪ................................................................................................................................11

2.7. በምዕራፎች የተከፋፈለ የፕሮጀክቱ የትግበራ የጊዜ ሰሌዳ.....................................................................12

2.7.1. በግንባታ ምእራፍ የሚከናወኑ ተግባራት........................................................................................12

2.7.2. በአገልግሎት ምዕራፍ የሚከናወኑ ተግባራት......................................................................................13

2.7.3. በፕሮጅት መዝጊያ ምዕራፍ የሚከናወኑ ተግባራት.........................................................................13

3. የአማራጮች ትንተና..............................................................................................................................13

3.1. አማራጭ አልቦ (Zero alternatives).................................................................................................13

3.1.1. የጥሬ እቃ ምንጭ አማራጭ.....................................................................................................14

4. የባዮፊዚካልና ማህበረ ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ መሠረታዊ መረጃዎች..................................................................15

4.1. የአፈር አይነትና ሁኔታ.....................................................................................................................16

4.2. የመልክዓ ምድር ሁኔታ....................................................................................................................16

የደብረማርቆስ ከተማ መልክአምድራዊ አቀማመጥ....................................................................................16

4.3. ማህበረ-ኢኮኖሚያዊ መሰረታዊ መረጃዎች ትንተና.............................................................................16

4.3.1. የደብረማርቆስ ከተማ የንፁህ መጠጥ ዉሃአቅርቦት ሁኔታ.......................................................16

4.3.2. የከተማዋ የጤና አገልግልት ሁኔታ...........................................................................................17

4.3.3. የህዝብ አሰፋፈር፣ሃይማኖት፤ቋንቋናባህል..................................................................................18

4.3.4. አርኪኦሎጂ፣ሃይማኖታዊና ማህበራዊ ተቋማት ሁኔታ...............................................................18

5. የአካባቢ ተፅዕኖ ትንተና.............................................................................................................................18

2
5.1. በፕሮጀክቱ ትግበራ ወቅት የሚጠበቁ አሉታዊና አዋንታዊ ተጽኖዎች.........................................................18

5.1.1. አዋንታዊ ተጽኖዎች....................................................................................................................18

5.1.2. አገልግሎትን ለማህበረሰቡ በፍትሃዊነት መስጠት...............................................................................18

5.2. አሉታዊተፅዕኖዎች..........................................................................................................................19

5.2.1 በግንባታ ጊዜ የሚከሰቱ................................................................................................................19

5.2.2. በአገልግሎት ምዕራፍ የሚከሰቱ ተፅዕኖዎች......................................................................................20

5.2.3. በፕሮጀክት ማጠናቀቂያ ወቅት የሚከሰቱ ተፅዕኖዎች........................................................................21

6. የህብረተሰብ ተሳትፎ..................................................................................................................................21

7. በጥናቱ የሚዳሰሱ ቁልፍ ጉዳዮች..................................................................................................................22

7.1. ፕሮጀክቱ በአከባቢው በሚኖሩ እንስሳት እና እፅዋት ላይ ሊኖረው የሚችለውን ተፅዕኖ..................................22

8. የጥናት እቅድ /የአከባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርት ዝግጅት ቅደም ተከተል............................................................22

8.1. አጠቃላይ መግለጫ..............................................................................................................................22

8.2. መግቢያ.............................................................................................................................................23

8.3. የአከባቢ ተፅዕኖ ጥናት አላማ.................................................................................................................23

8.4. የጥናት ወሰን......................................................................................................................................23

8.5. የጥናቱ ስልት ወይም ዘዴ......................................................................................................................23

8.6. በጥናት ወቅት የተወሰዱ ታሳቢዎችና የነበሩ የእውቀት ክፍተቶች..............................................................23

8.7. የፖሊሲ፣የህግና የአስተዳደር ማዕቀፎች..................................................................................................23

8.8. ዝርዝር የፕሮጀክት ገለፃ ማድረግ...........................................................................................................23

8.9. የባዮፊዚካልና ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ መሠረታዊ መረጃዎች............................................................24

8.10. የአከባቢ ተፅእኖ ትንተና ማካሄድ..........................................................................................................24

8.11. የተፅዕኖ ማቅለያ እርምጃዎች.............................................................................................................24

8.12. የአካባቢ አያያዝ እቅድ........................................................................................................................24

8.13. የአከባቢ ክትትል/ምርመራ እቅድ.........................................................................................................25

8.14. ማጠቃለያና ምክረ ሀሳብ....................................................................................................................25

ዕዝል 2 በአካባቢና ማህበራዊ ተጽዕኖዎችን ለመለየት የሚያገለግል ቸክሊስት.........................................................26

8.15. ዋቢ ማጣቃሻዎች.............................................................................................................................27

8.16. እዝሎች...........................................................................................................................................27

9. የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናት ሰነድ ይዘት.............................................................................................................27

3
10. የአካባቢና ማህበራዊ ተጽእኖ ግምገማ ጥናት የሚካሄድበት የጊዜ ሰሌዳ.....................................................28

ሰንጠረዦችና ስዕሎች

ሰንጠረዥ 1፡ የፕሮጀክቱ መገኛ ቦታ በኬክሮስና በኬንትሮስ መስመሮች...................................................................7

ሠንጠረዥ 2፡ በጥናቱ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ስብጥር........................................................................................10

ሠንጠረዥ 3፡ ለእምነ በረድ የማዕድን አለት መቁረጫ ማሽነሪዎች.......................................................................11

ሠንጠረዥ 4 ፡ የሰው ኃይል........................................................................................................................11


ሠንጠረዥ 5፡ የፕሮጀክት ትግበራ እና የሚካሄድበት ጊዜ ሰሌዳ.......................................................................12
ሠንረተዥ 6፡ የፕሮጀክቱ አማራጮች..............................................................................................................15
ሰንጠረዥ፡ 7 በከተማው 10 ዋናዋና በሽታዎችን የሚያሳይ..................................................................................17
ሰንጠረዥ 8 ፡- የአካባቢና ማህበራዊ ተጽእኖ ግምገማ ጥናት ለማካሄድ የተዘጋጀ የድርጊት መርሃ ግብር.....................28

ስዕል 1. በአማካሪ ድርጅቱ የተሰራ የፕሮጀክቱ የመሬት አቀማመጥ........................................................................7

4
መግቢያ

ቢቤት ትሬዲንግ የእምነ በረድና ግራናይት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማህበር በአማራ ክልል በደብረ ማርቆስ ከተማ እየተገነቡ

ካሉ ፋብሪካዎች መካከል አንዱ ነዉ፡፡ ቢቤት ትሬዲንግ የእምነ በረድና ግራናይት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማህበር በአማራ

ክልል በደብረ ማርቆስ ከተማ በመንቆረር ክፍለ ከተማ ቀበሌ 11 በ 25,283,726.93 ብር ከፒታል በመመደብ በእምነ

በረድና ግራናይት ፋብሪካ ለመሰማራት 2 ሄክታር ቦታ ጠይቆ ከተማ አስተዳደሩ ይሁንታ ሰጥቶታል፡፡ ፕሮጀክቱ በግንባታ

ወቅትና ስራ በሚጀምርበት ወቅት ከ 143 በላይ ስራ ፈላጊዎችን በጊዜያዊና በቋሚነት የሥራ እድል ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የእምነ በረድና ግራናይት ፋብሪካ በተለያየ መጠን ጥራቱን የጠበቀ ምርት ለአገር ዉስጥ እና 60%

ለዉጭ ገበያ በማቅረብ በግንባታዉ ዘርፍ ለተሰማሩ የማህበረሰብ ክፍሎች በግብአትነት በማቅረብ የበኩሉን ድርሻ

ይወጣል በዚህም የባለሃብቱን ገቢ ያሳድጋል::

በመሆኑም የዚህ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ቢኒያም አእምሮ ይህንን የአቅርቦትንና የፍላጎትን ክፍተት

ለመሙላት ካለው ጥልቅ ራዕይ የተነሳ ይህንን የእምነ በረድና ግራናይት ፋብሪካን አቋቁመዉ ለመስራት በዝግጅት ላይ

ይገኛሉ፡፡ ፕሮጀክቱን ከማቋቋም ጎን ለጎን ከፕሮጀክቱ ጋር ተያይዞ የሚመጡ ጉልህ የአከባቢ ተፅዕኖዎችን ለይቶ እነዚህ

ተፅዕኖዎች በፕሮጀክቱ አከባቢ በስነምህዳር፣ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ከመፍጠራቸው በፊት ተፅእኖዎችን

ለመከላከል የተፅዕኖዎችን የማቅለያ እቅድ እና የአፈፃፀም ስልት በባለሙያ አስጠንተው እና በሚመለከተው የአከባቢ

ጥበቃ መስሪያ ቤት አስፀድቀው መተግበር ይጠበቅባቸዋል፡፡

ባለሃብቶቹ በኘሮጀክቱ ግብዓት፣ተግባራትና ውጤት የተነሳ የሚከሰቱ ተጽዕኖዎችን ለመከላከልና ለመቀነስ የሚከናወኑ

ተግባራት በመፈጸም ተፅዕኖውን መቀነስ ካልቻሉ ለተጽዕኖው የካሳ ክፍያ እንዲፈፅሙ በአዋጅ ቁጥር 181/2 ዐዐ 3

ያስገድዳል፡፡ የአካባቢ አያያዝ እቅድ ተግባራትን/ግዴታዎችን በተቀመጠላቸው መጠን፣ የአፈጻጸም ጥራትና የጊዜ መርሃ

ግብር በማከናወን በየስድስት ወሩ የአፈጻጸም ሪፖርት ለሚመለከተው የአካባቢ መስሪያ ቤት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

ከዚህ በላይ የተዘረዘሩትን ግዴታዎች አለመወጣቱ በአካባቢ ምርመራ፣ ክትትልና ቁጥጥር ከተረጋገጠ በአዋጅ ቁጥር

181/2 ዐዐ 3 አንቀጽ 25/4 መሰረት ብር 2 ዐ,ዐዐዐ /ሃያ ሺ ብር/ ቅጣት ያስቀጣል፡፡ ስለሆነም እነዚህን ስራዎች ለመስራት

እንዲመች ይህ የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሰነድ አማካሪ ድርጅት በሆነው ኢትዮ ግሪን የአከባቢ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ

ጉዳዮች አማካሪ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የተዘጋጀ ነው፡፡

ሪፓርቱ የተዘጋጀው በአማራ ክልል የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ መመሪያ ቁጥር 01/2010 አንቀጽ 11፣ ንኡስ አንቀጽ 11.1

እና 11.2 መሰረት ነው፡፡ ጥናቱ ከመጀመሩ በፊት ከፕሮጀክቱ ባለቤት ጋር ስምምነትና የስራ ውል ተወስዷል፡፡ ይህ ሪፓርት

5
ከመዘጋጀቱ በፊት አማካሪ ድርጅቱ የጥናት ቡድን በማቋቋም ስለፕሮጀክቱ የሚገልጹ መረጃዎችን ከባለቤቱ በመጠየቅና

ከኢንተርኔት በማፈላለግ፣ እንዲሁም ፕሮጀክቱ የሚካሄድበትን ቦታ በማየት አስፈላጊ የመስክ መረጃዎች ተሰባስበዋል፡፡

ይህ ሪፓርት በዋናነት ሊካሄድ ስለታሰበው ፕሮጀክት አጠቃላይ መግለጫ፣ መግቢያ፣የፕሮጀክት አማራጮች፣

የአካባቢያዊና ማህበራዊ ነባራዊ ሁኔታዎች፣ የጥናት ስልትና የአካባቢውን ነዋሪዎች ተሳትፎን ያካተቱ መረጃዎችን

ይዟል፡፡ ለሪፓርቱ አጋዥና ተጨማሪ መረጃዎች በእዝል የተያያዙ ሲሆን ሪፓርቱ ሲዘጋጅ ጥቅም ላይ የዋሉ

ማጣቀሻዎችንም ይዟል፡፡ ሪፖርቱ በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር አካባቢ ጥበቃ አረንጓዴ ልማት ጽዳትና ዉበት

ተጠሪ ጽቤት በኩል ተቀባይነት እንዳገኘ የፕሮጀክት ትግበራ ስራው ይጀመራል፡፡

የፕሮጀክቱ ጥቅል አላማ በከተማዉ እና በአካባቢዉ የሚስተዋለውን የግራናይት እና እምነ በረድ ፍላጎትና አቅርቦት

ክፍተት በመሙላት ለፕሮጀክቱ ባለቤት ገቢንና ለአካባቢው ማህበረሰብ የስራ እድልን መፍጠር ሲሆን ዝርዝር አላማው፣

1. ገቢን እና የስራ እድልን በመፍጠር ለአከባቢው ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ለውጥ አስተዋፅኦ ማበርከት

2. ጥራት ያለው የእምነ በረድና የግራናይት ምርት በማምረት በግንባታዉ ዘርፍ መሻሻል አስተዋፅኦ ማበርከት

3. አገራችን ወደ ኢንዱስትሪ ልማት የሚደረገውን ሽግግር ለመደገፍ

1.2. የአከባቢ እና ማህበራዊ ተፅዕኖ ጥናቱ አላማ


ፕሮጀክቱ ወደ ስራ ከመግባቱ በፊት ዝርዝር ጥናት በማካሄድ በአካባቢና ማህበረሰቡ ላይ ለሚደርሱ ተጽእኖወች

ለአወንታዊ ተጽእኖወች የማጎልበቻ እርምጃ እንዲሁም ለአሉታዊ ተጽእኖወች የማቅለያ እርምጃወች

በመዉሰድ ፕሮጅቱ ከአካባቢዉና ማህበረሰቡ ጋር ተጣጥሞ የሚቀጥልበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ነው፡፡

1.2.1. የዚህ ጥናትዝርዝር አላማዎች፡-


 ፕሮጀክቱን ገለልተኛ በሆነ አካል ከአካባቢና ከማህበራዊ እይታ አኳያ በመዳሰስ ሊከሰቱ የሚችሉ ተፅዕኖዎችን

በመለየትና ተፅዕኖዎችን የሚያስወግዱ ወይም የሚያቃልሉ እርምጃዎችን ለማስቀመጥ፣

 ብክለቶች እንዳይከሰቱ ለማድረግ፣ ካልተቻለም ጉዳታቸውን ለመቀነስ፣

 የተለዩ የአካባቢ ተጽእኖዎችን በአግባቡ ለመያዝ የሚያስችል የማቅለያ መሳሪያ /እርምጃዎችን/ ለማቅረብ፣

 የአካባቢ ተቆጣጣሪው መስሪያ ቤት በፕሮጀክቱ ትግበራ ላይ ትክክለኛ ውሳኔ እንዲሰጥ ለማስቻል

1.3. የፕሮጀክቱ መገኛ ቦታ


ፕሮጀክቱ በደብረ ማርቆስ ከተማ በመንቆረር ክፍለ ከተማ ቀበሌ 11 በኢንዱስትሪ መንደር ምድብ ዉስጥ የሚገኝ ሲሆን

የፕሮጀክቱ ቦታ ሰሜን ኤርምያስ ንጉሴ ደቡብ ኤልሳቤት አለማየሁና ሶሎሞን አዲስ ምስራቅ መንገድ፣ ምዕራብ ክፍት

ቦታ ያዋስኑታል፡፡

ሰንጠረዥ 1፡ የፕሮጀክቱ መገኛ ቦታ በኬክሮስና በኬንትሮስ መስመሮች

6
ተ.ቁ ሰሜን ኬክሮስ ምስራቅ ኬንትሮስ
1 359831.59 1137707.047

2 359871.242 1137615.245

3 360052.587 1137700.116

4 360012.815 1137791.86

ስዕል 1. በአማካሪ ድርጅቱ የተሰራ የፕሮጀክቱ የመሬት አቀማመጥ

1.4. የፕሮጀክቱ ጥቅል ዓላማ


በከተማዉ እና በአካባቢዉ የሚስተዋለውን የእምነ በረድ እና የግራናይት ምርት ፍላጎትና አቅርቦት ክፍተት

በመሙላት ለፕሮጀክቱ ባለቤት ገቢንና ለአካባቢው ማህበረሰብ የስራ እድልን በመፍጠር የፕሮጀክት ባለቤቱን

ገቢማሳደግ እና የአካባቢዉን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ማድረግ ነዉ፡፡

7
1.4.1. የፕሮጀክቱ ዝርዝር አላማዎች፡-

 በአካባቢዉ የልማት እንቅስቃሴ ላይ የበኩሉን ድርሻ መወጣት፣

 በአካባቢዉ የሌሉና ለወደፊት አስፈላጊ በሆኑ የቢዝነስ እንቅስቃሴዎች ላይ በመሳተፍ ትርፋማ

በመሆን ለሌሎችም አርአያ መሆን፣

 ለአካባቢዉ ወጣቾች የስራ እድል መፍጠር፣

 የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማህበረሰቡ ማስረጽ እና

 የፕሮጀክቱን ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ ለአካባቢዉ ማህበረሰብ ማቅረብና 60% የሚሆነዉን ምርት

ለዉጭ ገብያ በማቅረብ የዉጭ ምንዛሬ ማስገኘት ናቸዉ፡፡

1.5. የአከባቢ እና ማህበራዊ ተፅዕኖ ጥናቱ አላማ


ፕሮጀክቱ ወደ ስራ ከመግባቱ በፊት ዝርዝር ጥናት በማካሄድ በአካባቢና ማህበረሰቡ ላይ ለሚደርሱ ተጽእኖወች

ለአወንታዊ ተጽእኖወች የማጎልበቻ እርምጃ እንዲሁም ለአሉታዊ ተጽእኖወች የማቅለያ እርምጃወች በመዉሰድ

ፕሮጅቱ ከአካባቢዉና ማህበረሰቡ ጋር ተጣጥሞ የሚቀጥልበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ነው፡፡

1.5.1. የዚህ ጥናትዝርዝር አላማዎች፡-

 ፕሮጀክቱን ገለልተኛ በሆነ አካል ከአካባቢና ከማህበራዊ እይታ አኳያ በመዳሰስ ሊከሰቱ የሚችሉ ተፅዕኖዎችን

በመለየትና ተፅዕኖዎችን የሚያስወግዱ ወይም የሚያቃልሉ እርምጃዎችን ለማስቀመጥ፣

 ብክለቶች እንዳይከሰቱ ለማድረግ፣ ካልተቻለም ጉዳታቸውን ለመቀነስ፣

 የተለዩ የአካባቢ ተጽእኖዎችን በአግባቡ ለመያዝ የሚያስችል የማቅለያ መሳሪያ /እርምጃዎችን/ ለማቅረብ፣

 የአካባቢ ተቆጣጣሪው መስሪያ ቤት በፕሮጀክቱ ትግበራ ላይ ትክክለኛ ውሳኔ እንዲሰጥ ለማስቻል

1.6. የሪፖርቱ አስፈላጊነት


ይህ የወሰን ልየታ/scopping/ ሪፖርት በአከባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ጥናት ወቅት መታየት ያለባቸው ከፕሮጀክቱ ጋር

ተያይዘው ሊመጡ የሚችሉ ጉልህ አውንታዊና አሉታዊ የአካባቢ ተፅዕኖዎችን ለመተንተን፣ የትንተና ዘዴዎችን፣ የተለዩ

አማራጮችን፣ የተፅዕኖ ማቅለያ እቅዶችንና የክትትልና ግምገማ እቅዶችን ለማመላከት ነው፡፡ ይህ የወሰን ልየታ ሪፖርቱ

በደብረ ማርቆስ ከተማ አካባቢ ጥበቃ አረንጓዴ ልማት ጽዳትና ዉበት ተጠሪ ጽ/ቤት ቀርቦ ከፀደቀ በኋላ ሙሉ የአከባቢ

ተፅዕኖ ግምገማ ጥናት ሰነድ የሚዘጋጅለት ይሆናል ፡፡ የአከባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርቱም ጉልህ የአከባቢ ተፅእኖ

ሊያመጡ የሚችሉ ነገሮችን ለመለየት፣ የማቅለያ ዘዴዎችን ለመጠቆምና የአከባቢ ተፅዕኖ እቅድን፣ የክትትልና ግምገማ

ስርዓትን ለማዘጋጀት ያስችላል፡፡

8
1.7. የጥናቱ ስልት (ዘዴ)
1.7.1. ጥናቱ በሚካሄድበት ጊዜ ጥቅም ላይ የዋሉት ስልቶች ወይም ዘዴዎች፡-

ሪፓርቶችና ጽሁፎችን ማንበብ፡- በፕሮጀክት ባለቤቱ የቀረቡ ስለፕሮጅቱ የተዘጋጀ ጽሁፎችን፣ በአገሪቱ በክልሉ የወጡ

የፓሊሲ፣ የህግና አስተዳደራዊ ማዕቀፎችን በሚመለከት የወጡ ሰነዶችና ከድረ-ገጾች የሚገኙ መረጃዎችን በማሰባሰብ

ለዚህ ሪፓርት ዝግጅት ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡ ይህ ዘዴ በዋናነት ስለፕሮጅቱ ምንነትና ምንግብአት ተጠቅሞ ምን ምርት

እንደሚያወጣ ለመረዳትና በፕሮጀክቱ መተግበሪያ ቦታ ላይ ምን ምን ሀብቶችና እንዳሉን ተፅዕኖን የመሸከም

አቅማቸውን ለመገመት ጥቅም ላይ ውሏል፡፡

በመስክ የፕሮጀክቱን ቦታና አካባቢውን መመልከት፡-ፕሮጀክቱ የሚካሄድበትን ቦታና አካባቢው ያለውን

ህይወታዊ፣ቁሳዊና ማህበራዊ ሀብቶች ሁኔታ በሚመለከት መረጃ ተሰብስቧል፡፡ በዚህም የመስክ እይታ ወቅት

ፎግራፎችን በማንሳት ለሪፓርት ዝግጅት ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የፕሮጅቱን መሬት መገኛ ኮርዲኔቶች

በጅ.ፒ.ኤስ. ለክቶ ከሳይት ፕላኑ ጋር በማረጋገጥ የኬንትሮስና ኬክሮስ መስመሮችን እንዲሁም ከባህር ጠለል ያለውን

ከፍታ በሚመለከት መረጃ ተወስዷል፡፡

የሳተላይት ምስሎችን መጠቀም፡- ከጎግል መሬት (Google Earth) ያለን የፕሮጀክቱን ቦታና አካባበውን የሚያሳይ ምስል

በመጠቀም የአካባቢው ሁኔታ፣ያላቸውን ርቀት፣ እንዲሁም የውሃ መውረጃዎችና ተዳፋታማነት ወዘተ. ለማወቅ ጥቅም

ላይ ውሏል፡፡ከዚህም በተጨማሪ በሪፓርቱ ውስጥ የፕሮጀክቱን መገኛ ለማመልከት ጥቅም ላይ ውሏል፡፡

መደበኛ ባልሆነ ቃለ ምልልስ በማድረግ፡-

በአካባቢው የሚገኙ ሰዎችን ማናገር (መደበኛ ያልሆነ ቃለ መጠይቅ በማካሄድ) መረጃ ማሰባሰብ፡ በመስክ ጉብኝት ወቅት

የተገኙ ሰዎችን በተለይም ከፕሮጀክቱ አቅራቢያ የሚገኙ ነዋሪዎችን በመስክ ጉብኝት ወቅት ያገኘናቸውን ኗሪዎች

መደበኛ ባልሆነ ቃለ ምልልስ ስለፕሮጀክቱ እና ፕሮጀክቱ ስለሚካሄድበት ቦታ መረጃ ተሰባስቧል፡፡

የተለያዩ የማወዳደሪያ መስፈርቶችን መጠቀም፡- ከፕሮጀክቱ አማራጮች ውስጥ የተሻለውን ለመምረጥ የሚያግዙ

መስፈርቶች የተዘጋጁ ሲሆን የአጥኝ ቡደኑ አባላት ለእያንዳንዱ አማራጭ ነጥብ እንዲሰጡ በማድረግ የተሻለው

እንዲመረጥ ተደርጓል፡፡ በተመሳሳይ ከተዘረዘሩ ተፅዕኖዎች መካከል ትኩረት የሚያስፈልጋቸውን ለመለየት መስፈርቶችን

ጥቅም ላይ እንዲውሉ ተደርጓል፡፡ የተባበሩት መንግስታት የአካባቢፕሮግራም (UNEP) ባዘጋጀው የስልጠና ማንዋል እና

የአማራ ክልል በቅርቡ ያወጣውን የአካባቢተፅዕኖ ግምገማ መመሪያ ቁጥር 001/2010 በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት

የተፅዕኖ መገምገሚያ መስፈርቶችን በማዘጋጀትና በማወዳደር ትኩረት የሚያስፈልጋቸው ወይም የማያስፈልጋቸው

መሆኑን ለመለየት ተችሏል፡፡ ምንም እንኳን መስፈርቶቹ የተፅዕኖ ግምገማውን ይዘት እንዳይለቅ ቢያደርጉትም

የባለሙያዎችን ሙያዊ ውሳኔ ጥቀም ላይ ማዋል የማይቀር ሆኗል፡፡

9
1.5. በጥናቱ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ስብጥር

በጥናቱ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች የተመረቁ እና በቂ ልምድ ያላቸው ባለሙያዎች የሚመደቡ ሲሆን

የባለሙያዎቹ ዝርዝር መረጃ እንደሚከተለው ይቀርባል፡፡

ሠንጠረዥ 2፡ በጥናቱ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ስብጥር

ተ.ቁ የባለሙያው ስም ሰርቲፊኬት ያገኘበት መስክ


1 ጥሩነህ እንግዳ በአከባቢ ብክለት ተንታኝ ከፍተኛ ባለሙያ
2 ባላገር አንተንህ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ተንታኝ ጀማሪ ባለሙያ
3 እሱባለዉ ደባስ የአካባቢ ጤና ተንታኝ ከፍተኛ ባለሙያ
4 ይታያል ወዳጀ የማህበራዊ ዘርፍ ጉዳዮች ተንታኝ ከፍተኛ ባለሙያ

2. የፕሮጀክቱ ገለፃ

2.1. የፕሮጀክቱ ስፋትና ባህሪ

የዚህ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ የሆኑት ቢኒያም አእምሮ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ደብረ ማርቆስ ከተማ

መንቆረር ክፍለ ከተማ ቀበሌ 11 በ 2 ሄክታር ቦታ ላይ የእምነ በረድና ግራናይት ፋብሪካ ፕሮጀክት በማቋቋም እየተገበሩ

ያሉ ሲሆን ፕሮጀክቱ በሙሉ አቅሙ ሲሰራ በአመት 20,500 ሜትር ስኩየር የሚሆን እምነ በረድ ማምረት አቅም ያለዉ

ፋብሪካ ለመገንባት መሰረት አድርጎ የሚቋቋም ፕሮጀክት ነዉ፡፡ የፕሮጀክቱ የኢንቨስትመንት ወጪ ብር 126,062,551

ለ 143 ዜጎች ቋሚእና ጊዚያዊ የስራ እድልን ይፈጥራል፡፡ ለዚህ ጥናት የመስክ መረጃ በተሰባሰበበት ወቅት ፕሮጀክቱ

ቀደም ባሉት አመታት ጀምሮ ከ 3 ኛ ወገን ጸድቶ የቆየ ሲሆን ባለሃብቱ ባቀረቡት የኢንቨስትመንት ጥያቄ መሰረት

የከተማ አስተዳደሩ የፕሮጀክቱን አስፈላጊነት ከግምት ዉስጥ በማስገባት ይሄንኑ ፕሮጀክት ሊፈቅድላቸዉ ችሏል፡፡

2.2. ግብዓቶች
ቢቤት ትሬዲንግ የእምነ በረድና ግራናይት ማምረቻ ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የሚጠቀማቸዉ ዋና ዋና ግብአቶች

ከሃገር ዉስጥ የሚገኙ እምነ በረድና ግራናይት ማዕድን እነዚህ ግብአቶች በፕሮጀክት ባለቤቱ ከህጋዊ ማዕድን አዉጭዎች

ተገዝተዉ የሚቀርቡ ይሆናል፡፡

እንደሚከተለው ይቀርባል፡፡

2.3. የቴክኖሎጅ አይነትና የቴክኖሎጅ አጠቃቀም ገለጻ

ፕሮጀክቱ የሚከተሉትን ማሺኖች በመግዛት ምርት ለማምረት ያቀደ ሲሆን የማሺኖቹ ጠቅላላ ዋጋ ብር

126,062,551 ብር ነዉ፡፡ለፕሮጀክቱ የ.ሚያስፈልጉት የማሺኖች አይነትና የዋጋ ዝርዝር እንደሚከተለው ይቀርባል፡፡

ሠንጠረዥ 3፡ ለእምነ በረድ የማዕድን አለት መቁረጫ ማሽነሪዎች

10
ተ. ዝርዝር HLQ_1600 HLQY-2300/2500
1. Max blade diameter mm 1600 230/250
2 Cross bram length mm 6000 7600/7800
3 Cutting length mm 3500 3500
4 Cutting width mm 2000 2000
5 Lifting strock mm 800 1350
5 Power of main monitor Kw 55(4p) 55(4p)
7 Power of pump motor Kw 4 4
8 Power of strock motor Kw 2.2 2.2
9 Power of vertical motor Kw 1.1 1.1
10 Gross power Kw 62.3 62.3
11 Gross weight Kg 10000 13000/14000
12 Diamenssion mm 65000*5000*4000 7800*5000*4500

ምንጭ፡- ከቢቤት ትሬዲንግ የእምነ በረድ እና ግራናይት ፋብሪካ የአዋጭነት ጥናት 2022 የተወሰደ

2.4. የግንባታ ወጪ

የፕሮጀክቱ ባለቤት ለፕሮጀክቱ ማቋቋሚያ በተፈቀደላቸዉ 2 ሄክታር ቦታ ላይ ግንባታዉን ጀምረዉ

ለማጠናቀቅ 25,539,000 ብር ተመድቧል፡፡ ግንባታዉ የአምነ በረድና የግራናይት ፋብሪካዉ የሚቀመጥበት

ክፍል፤ የቢሮ አገልግሎት የሚዉል ክፍል፣ የምርት ማከማቻ መጋዘን፣ መጸዳጃ ቤት እና የሰራተኞች የልብስ

መቀየሪያ ክፍሎችአሉት፡፡ ፕሮጀክቱ ለ 50 ቋሚእና ለ 25 ጊዚያዊ የሰው ኃይል የስራ እድል የሚፈጥር ሲሆን ብር
673,200 ብር አመታዊ ደመወዝ የሰው ኃይል ወጪ ተይዟል፡፡ ለፕሮጀክቱ የሚሰው ኃይል ብዛት እንደሚከተለው

ይቀርባል፡፡
ሠንጠረዥ 4 ፡ የሰው ኃይል

ተ.ቁ የስራ መደብ ብዛት የወር ደመወዝ የአመት ደመወዝ


1 ዋና ስራ አስኪያጅ 1 10,264.00 123,168.00
2 ፀሐፊ 1 2,181.00 26,173.00
3 የሽጭ ሰራተኛ 6 1925.00 1380,600.00
4 የሂሳብ ሰራተኛ 2 3079.00 73,896.00
5 ምርት ተቆጣጣሪ 2 1000 216,000
6 የማሽን ኦፕሬተር 15 2039 415,620.00
7 አነስተኛ የመቁረጫ ኦፕሬተር 15 2039 415,620.00
8 H/V መቁረጫ ኦፕሬተር 15 2039 415,620.00
9 የቀን ሰራሰኛ 30 1026 615,600
10 ንብረት ክፍል ሰራተኛ 7 2566 61,584
11 ሜካኒክ 7 2566 92,376
12 ኤሌክትሪክ ሰራተኛ 7 2566 92,376
13 የጽዳት ሰራተኛ 15 1026 147,744
14 ተላላኪ 4 1026 49,248
15 ሾፌር 7 1925 115,500

11
16 ጥበቃ ሰራተኛ 16 1026 196992
ልዩ ክፍያ 20 % 479640.20
ጠቅላላ ድምር 143 2877841.20

ምንጭ፡- የቢቤት ትሬዲንግ የእምነ በረድና ግራናይት ፋብሪካ ፕሮጀክት ፕሮፖዛል

2.7. በምዕራፎች የተከፋፈለ የፕሮጀክቱ የትግበራ የጊዜ ሰሌዳ


የቢቤት ትሬዲንግ የእምነ በረድና ግራናይትፋብሪካ ፕሮጀክት ግንባታ 2 አመት የሚፈጅ ሲሆን ግንባታዉን የተለያዩ

የግንባታ ዲዛይንና ሌሎች አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታዎችን አጠናቅቆ ከመጋቢት 2016 ዓ.ም ጀምሮ የግንባታ ስራዉን

የሚጀምር ሲሆን ከሚያዚያ 2018 ጀምሮ የምርት ማምረት ስራዉን ጀምራል፡፡ የፕሮጀክቱ የትግበራ ምዕራፎች

በጥቅሉ ቀጥሎ ባለው ሰንጠረዥ የተመለከተ ሲሆን በእያንዳንዱ ምዕራፍ ስር ያሉ ዝርዝር ተግባራት ደግሞ ከሰንጠረዡ

ቀጥሎ ተዘርዝረዋል፡፡
 ሠንጠረዥ 5፡ የፕሮጀክት ትግበራ እና የሚካሄድበት ጊዜ ሰሌዳ

ተ.ቁ የሚከናወንበት ጊዜ
የፕሮጀክት ምዕራፍ
ከ እስከ
1 የግንባታ ስራ ማካሄድ ከየካቲት 2016 ሚያዚያ /2018 ዓ.ም
በሙሉ አቅሙ ምርት ማምረት ከሚዚያ/ 2018 ዓ.ም የካቲት/2095.ም
2 የመዝጊያ ምእራፍ ከየካቲት/ 2095 ዓ.ም ሰኔ 2095 ዓ.ም

ይህ የእምነ በረድና የግራናይት ፋብሪካ ፕሮጀክት የግንባታ፤ትግበራ እና ምርት የፕሮጀክት ማጠናቀቂያ


ምእራፎች አሉት፡፡ በእያንዳንዱ ምዕራፍ የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ቀጥለው ተዘርዝረዋል፡፡
2.7.1. በግንባታ ምእራፍ የሚከናወኑ ተግባራት

 ቦታውን ለግንባታ ማዘጋጀት (በግንባታ ተቋራጩ የሚከናወን ተግባር)


 ለግንባታው የሚያስፈልጉ ጥሬ እቃዎችን መግዛትና ወደ ፕሮጀክቱ ቦታ ማጓጓዝ፣
 ሁለት ክፍል ያለው (አንድ ለሴትና አንድ ለወንድ) ጊዜያዊ መጸዳጃ ቤት ማዘጋጀት (በግንባታ ተቋራጩ
የሚከናወን ተግባር)
 የግንባታ ስራ ማካሄድ
 በግንባታው ምክንያት የተፈጠሩ ቆሻሻዎችን ማሰባሰብና በሚፈቀደው ቦታ አጓጉዞ መድፋት
 ሰራተኞችን መቅጠርና ማሰልጠን
 የሙከራ አገልግሎት መጀመር
 ከሚመለከተው የመንግስት መስሪያ ቤት አገልግሎቱን ለመስጠት ፈቃድ ማግኘት

2.7.2. በአገልግሎት ምዕራፍ የሚከናወኑ ተግባራት


 ሰራተኞችን መቅጠር

12
 የፋብሪካው ግብአቶችን መግዛትና ወደ ፋብሪካው ማስገባት
 የጥራት ምርመራ ማካሄድ
 የማስታወቂያ ስራ መሰራት
 ፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻዎችን ማስተዳደር
 ለመንግስት አስፈላጊውን ግብርና ሌሎች የአገልገሎት ክፍያዎችን መፈጸም

2.7.3. በፕሮጅት መዝጊያ ምዕራፍ የሚከናወኑ ተግባራት

 የተቀጠሩ የፕሮጀክቱ ሰራተኞች በሌላ ተመሳሳይ ወይም አማራጭ ስራ እንዲቀጠሩ ማድረግ ወይም
በውሉ መሰረት ካሳ በመክፈል ማሰናበት፣
 ፕሮጀክት የመዝጊያ እቅድ ማዘጋጀት ወይም/እና የአካባቢ አያያዝ እቅዱን መከለስ
 ማሽኖችና ሌሎች መስሪያ መሳሪያዎችን ለዳግም ኡደት ወይም ለሌላ ተመሳሳይ ስራ የሚፈልጋቸው
ካለ ማስታወቂያ በመንገር ከተገኘ ውል መያዝ፣
 ግንባታዎችና ማሽኖች ማፈራረስ አስፈላጊ ከሆነ (አስፈላጊ ፈቃድ/ዶች ያለውን የግንባታ አፍራሽ
መቅጠር) ፣
 ግንባታው ሲፈርስ ጉዳት ሊደርስባቸው የሚችሉ ንብረቶች ካሉ ቦታ መቀየር፣ በአጎራባች ለሚገኙ
ፕሮጀክቶችም ማስጠንቀቂያ መስጠት (በወቅቱ በሚኖረው ህግ መሰረት) ፣
 በግንባታዎች ላይ የተገጠሙና እንደገና ጥቅም የሚሰጡ ቁሳቁሶችን በጥቃቄ በማንሳት መሸጥ፣
 የማምረቻ፣ አስተዳደርና ሌሎችንም ግንባታዎችን ማፈራረስ፣
 የተተከሉ ማሽኖችንና ሌሎች መሳሪያዎችን መንቀል፣
 የውስጥ ለውስጥ መንገዶችን ማፈራረስ
 በግቢ ውስጥ የተፈጠሩ ጉድጓዶች በመድፈን ቦታውን በፊት እንደነበረው ማስተካከል፣
 ቦታውን ለማስተካከል ጥቅም ላይ ያልዋለውን ቆሻሻ የከተማ አስተዳደሩ በፈቀደው ቦታ ላይና ሁኔታ
መድፋት፣
 የፕሮጀክቱን ቦታ በማስተካከል ማስረከብ ወይም በሚመለከተው አካል ሲፈቀድ ለሌላ ፕሮጀክት
መጠቀም
 ስለ ፕሮጅቱ መዘጋትና የተወሰዱ ጥንቃቄዎች ወዘተ የሚገልጽ ሪፓርት ለተቆጣጣሪው መስሪያ ቤት
ማቅረብ

3. የአማራጮች ትንተና

ይህንን ፕሮጀክት ተግባራዊ ለማድረግ ከአካባቢ ተፅዕኖ መቀነስ አንጻር የሚከተሉት አማራጮች ተለይተዋል፡፡

3.1. አማራጭ አልቦ (Zero alternatives)


አማራጭ 1፡ ፕሮጀክት ሳይካሄድ ቢቀር፤ ፐሮጀክቱ ካልተካሄደ በግንባታ እና በሌሎች የፕሮጀክቱ ምዕራፎች

የሚኖሩ አሉታዊ ተጽዕኖዎች አይከሰቱም፡፡ ነገር ግን ተግባራዊ ካልተደረገ አውንታዊ ተጽዕኖዎች ማለትም

የፕሮጀክቱ ባለቤት የሚያገኘውና ለመንግስት የሚኖረው የግብር ገቢ ሊኖር አይችልም፡፡ ከዚህም በተጨማሪ

13
ፕሮጀክቱ ስራ ሲጀምር የሚኖረው የስራ እድል፣ ለአካባቢው የምጣኔ ሀብት እድገትና መሬቱን ለበለጠ

ጠቀሜታ የማዋል እድል አይኖርም፡፡

አማራጭ 2፡ ፕሮጀክቱ ተግባራዊ ቢደረግ፤ ፕሮጀክቱ ተግባራዊ ሲደረግ በዚህ ሪፓርት ውስጥ የተዘረዘሩት

አሉታዊ ተፅዕኖዎች የሚኖሩ ቢሆንም የፐሮጀክቱ ባለቤት ትርፍ ይጨምራል፣ መሬቱ የተሻለ አጠቃቀም

ይኖረዋል፣ የስራ እድል ይኖራል እንዲሁም የአካባቢውና የኢንዱስትሪ ክፍለ ኢኮኖሚ እድገት ላይ አወንታዊ

አስተዋጽኦ ይኖረዋል እንዲሁም የሚስማር ውጤቶች ምርት ለአካባቢው ማህበረሰብ በተመጣኝ ዋጋ

እንዲቀርቡ ያስችላል፡፡

3.1.1. የጥሬ እቃ ምንጭ አማራጭ

ለፕሮጀክቱ የሚሆነው ዋናው ጥሬ እቃ የእምነ በረድ ማዕድን ሲሆን ይህ ማዕድን ከምዕራብ ጎጃም ዞን ከሚገኙ

ወረዳዎች፣ከአዊ ዞን ከሚገኙ ወረዳዎችና ከቤኒሻንጉል ክልል አሶሳ በመግዛትና በማስመጣት ለማምረት የታሰበ መሆኑን

ከቢቤት ትሬዲንግ የፕሮጀክት አዋጭነት ጥናት የካቲት 2022 ለመረዳት ተችሏል፡፡

አማራጭ 1፤ የእምነበረድ እና ግራናይት ፋብሪካ ግብዓት የመግዛት አማራጭ፡- ይህ አማራጭ ግብዓቱ በአማራ ክልል
ከሚገኙ የማዕድን አዉጭዎች ጥሬ ማዕድኑን ስለሚገዛና በተለይ በምዕራብ ጎጃምና በአዊ ዞን ፍቃድ ያላቸዉ ጥራቱን

የጠበቀ እመነ በረድና ግራናይት ማዕድን አዉጭዎች ስለሚገዛ ጥራቱን ለማረጋገጥ የሚባክነውን ጊዜ እና ወደ ቆሻሻነት

የሚለወጠውን ተረፈ ምርት ስለሚቀንስ የተሻለ አማራጭ ነው፡፡

አማራጭ 1፡ ከአገሪቱ የኤሌክትሪክ ሀይል መረብ (ግሪድ) ሀይል ማግኘት፤ ፕሮጅከቱ የኤሌክትሪክ ሀይል በመጠቀም
ምርቱን ለማምረት አቅዶ እየተንቀሳቀሰ ሲሆን ይህ የሀይል ምንጭ አቅርቦት የሚመቻቸው የደብረ ማርቆስ ከተማ

ለኢንዱስትሪ መንደሩ ከሚዘረጋው መስመር ሲሆን የሃይል ምንጩ ካለው አካባቢያዊ ተዛማጅነት አኳያ ተመራጭ ስለሆነ

ይህም ለፕሮጀክቱ ባለቤትም ሆነ ለአካባቢው ስነ ምህዳር ደህንነት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፡፡ ነገርግን የፕሮጀክቱ ባለቤት

ካላቸው ተነሳሽነት እና ፍላጎት አኳያ የኤሌክትሪክ ማከፋፋያ መስመሩ ፈጥኖ ካልተዘረጋ ፕሮጀክቱ ግንባታውን ጨርሶና

ማሽን ተክሎ ወደ ምርት ሊገባ አይችልም፡፡

አማራጭ 2፡ ነዳጅ የሚጠቀሙ የኤሌክትሪክ ማመንጫዎችን መጠቀም፤ ፕሮጀክቱ የሚፈልገውን ኃይል


ለማመንጨት ነዳጅ መጠቀም ጥሩ አማራጭ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በየጊዜው የሚቆራረጥ የኤሌክትሪክ ሀይልን

ለመተካትና የከተማ አስተዳደሩ የሚያቀርበውን የኤሌክትሪክ ሀይል አቅርቦት ከመጠበቅ በነዳጅ የሚሰራ “ጀኔሬተር”

መጠቀም ጥሩ አማራጭ ነው፡፡ ይሁን እንጅ በነዳጅ የሚሰራ ጀኔሬተር የድምጽ ሁከት ከማስከተሉ በተጨማሪ

የሚያወጣው ጭስ አየር ይበክላል፤ እንዲሁም የነዳጅ ዋጋ ከኤሌክትሪክ ዋጋ በበለጠ ወጭ ያስወጣል፡፡ ከአካባቢ ብክለት

14
አይን ሲታይ ነዳጅ አካባቢን ሚበክልና የአለምን ሙቀት የሚጨምር ሲሆን በኢትዮጵያ የሚመረተውና የሚከፋፈለው

የኤሌክትሪክ ሀይል ግን ከውሃ የሚፈጠር ስለሆነ ታዳሽ በመሆኑ በአካባቢ ላይ የሚያሳድረው ብክለት አነስተኛ ነው፡፡

ከላይ በዝርዝር ከተመለከቱት አማራጮች መካከል ለታቀደው ፕሮጀክት የተሻለ የሆነውን ለመወሰን የጥናት ቡድኑ

አባላት ቀጥሎ በተቀመጠው የማወዳደሪያ መስፈርትና ሰንጠረዥ ተጠቅመው የተሻለውን መርጠዋል፡፡ የማወዳደሪያ

መስፈርቶች ምጣኔ ሀብታዊ ጠቀሜታ (የመነሻ እና ስራውን ለማስኬድ የሚያስፈልገው መዋእለ ንዋይ አነስተኛነት)፣

ለአካባቢ እንክብካቤ ያለው ጠቀሜት፣ እና ስራ ላይ ለማዋል ያለው ምቹነት ናቸው፡፡ በነዚህ የማወዳደሪያ መስፈርቶች

ስር ለእያንዳንዱ አማራጭ ከ 1 እስከ 10 ነጥብ እንዲሰጡ ከተደረገ በኋላ (10 ለጥሩ 1 ለመጥፎው አማራጭ) የአማካዩ

ነጥብ ድምር ለማወዳደሪያነት ተወስዷል፡፡

ሠንረተዥ 6፡ የፕሮጀክቱ አማራጮች

ጉዳይ አማራጭ ምጣኔ ሀብታዊ አካባቢ ለመጠቀ አጠቃላይ የተሻለው


ጠቀሜታ እንክብካቤ ም ነጥብ
ጠቀሜታ ያለውም አማራጭ
ቹነት
አማረጭ ፕሮጀክቱ ሳይተገበር ቢቀር 1 8 ጠ/አ 9

ፕሮጀክቱ ተግባራዊ ቢደረግ 7 4 5 16


የጥሬእቃምንጭ የእምነ በረድና ግራናይት ብሎክ ማእድን ከህጋዊ 8 8 9 27 
አማራጭ ማዕድን አዉጭዎች መግዛት
የኤሌክትሪክሀይ ከአገሪቱ የኤሌክትሪክ ሀይል መረብ ግሪድ) 9 8 10 27 
ልምንጭአማራ ሀይልማግኘት
ጭ ነዳጅ የሚጠቀሙ የኤሌክትሪክ ማመንጫዎችን 6 6 4 16
መጠቀም፤
የፍሳሽ ቆሻሻ የፍሳሽ ሽቆሻሻውን በፕሮጀክቱ ውስጥ በሴፕቲክ 8 9 7 24 
አያያዝ ታንክ በማጠራቀም ሲሞላ ወደ ህጋዊ የማስወገጃ
አማራጭ ቦታ በመጓጓዝ ማስወገድ፡፡

ፌሳሽ ቆሻሻውን ከፊብሪካዉ ዉጭ ወደ 3 4 9 16


አካባቢው የፍሳሽ መውረጃ መልቀቅ

ማሳሰቢያ፡- ለእያንዳንዱ ማወዳደሪያ መስፈርት ከ 1 እስከ 10 ነጥብ እንዲይዝ የተደረገ ሲሆን፣ 10 የሚሰጠው በጣም
ጠቃሚ ለሆነው ሲሆን 1 ደግሞ ለማይጠቅመው (ጉዳትላለው) ነው፡፡ በእያንዳንዱ ጉዳይ ስር ከተቀመጡት አማራጮች
ውስጥ አጠቃላይ ውጤቱ ከፍተኛ የሆነው ለፕሮጀክቱ በአጥኝ ቡድኑ የተመረጠው አማራጭ ሆኗል፡፡

4. የባዮፊዚካልና ማህበረ ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ መሠረታዊ መረጃዎች

እንደ ደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪ የደብረ ማርቆስ ከተማ ከባህር ወለለል በላይ

ከ 2350 እስከ 2500 ሜትር ከፍታ ላይ የምትገኝና 18 ዱግሪ ሴንቲግሬድ አማካይ የሙቀት መጠን ያላት ናት፡፡ ከዚህ

15
በተጨማሪ በከተማ አስተዳደሩ ግብርና ጽ/ቤት መረጃ መሰረት ከተማዋና አካባቢው ከ 1300 እስከ 1380 ሚሊ ሜትር

አማካይ አመታዊ የዝናብ መጠን አላት፡፡

4.1. የአፈር አይነትና ሁኔታ


ከከተማዋ ግብርና ጽ/ቤት በተገኘው መረጃ መሰረት በከተማዋ አብዛኛው ክፍል የሚገኘው ቀይ አፈር ሲሆን አሻልማ

አፈር አነስተኛውን ክፍል (ቀበሌ 05 እና 07) ሸፍኖ ይገኛል፡፡

4.2. የመልክዓ ምድር ሁኔታ


የደብረማርቆስ ከተማ መልክአምድራዊ አቀማመጥ

የደብረ ማርቆስ ከተማ በምስራቅ ጎጃም ዞን ካሉት 5 የከተማ አስተዳደሮች አንዷ ስትሆን ስትራቴጅክ መገኛ ያላትና

ከአዲስ አበባ በሰሜን ምእራብ አቅጣጫ በ 300 ኪሎ ሜትር ፣ ከክልሉ ዋና ከተማ ከባህር ዳር ደግሞ በ 265 ኪ.ሜ ርቀት

ሊይ የምትገኝና የዞኑ ርእሰ ከተማ ሆና በማገልገል ላይ ትገኛለች፡፡ ከከተማዋ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ የተገኘዉ

መረጃ እንደሚያሳየው ከተማዋ በከተማ አስተዳደር ደረጃ በ 4 ክፍለ ከተሞችና በ 20 የቀበሌ አስተዳደሮች የተከፈለች

ከተማ ናት፡፡ አንፃራዊ መገኛዋን በተመለከተም መረጃው እንደሚያሳየው በሰሜን ጎዛምን ወረዳ፣ በደቡብ ጎዛምን ወረዳ

፣ በምስራቅ አነደድ ወረዳ ፣ በምዕራብ ጎዛምን ወረዳ ያዋስኗታል፡፡ ጂኦግራፉያዊ መገኛዋም 100 170 እስከ 100 21'30'

ሰሜን ኬክሮስ እና 37 042'00'' እስከ 37 045'30'' ምስራቅ ኬንትሮስ ላይ ነው፡፡ የከተማዋ አጠቃላይ ስፊት 17000 ሄ /ር

ያህል ሲሆን ከከተማ አስተዳደ ግብርና ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው ከተማዋ ከባህር ወለል በላይ በ 2388

ሜትርና በ 2500 ሜትር ከፍታ ልዩነት መካከል ትገኛለች ፡፡ የከተማዋ የሙቀት መጠን ከፍተኛው 24 ዲግሪ ሴንቲግሬድ

ዝቅተኛው 18 ዲግሪ ሴንቲግሬድ እና አማካይ አመታዊ የሙቀት መጠን ደግሞ 21 ዱግሪ ሴንቲግሬድ መሆኑን የጽ/ቤቱ

መረጃ ያሳያል፡፡ ይህን መነሻ በማድረግ ወይና ደጋ አካባቢ ላይ የተከተመች ከተማ ናት፡፡ የከተማዋን የመሬት አቀማመጥ

ስናይ ሜዳማ ፣ተራራማና ተዳፊታማ ገጽታዎችን የተላበሰችና በውስጧ ጨሞጋ ፣ውትረን፣ውሰታ፣ የግምጅ፣አባሂም

እና ሌሎች ወቅታዊና አመታዊ የሚፈሱ ወንዞችን የያዘች ከተማ ስትሆን እንዲሁም የወንቃ እና ፣የራባ ጥብቅ ደን

ያለባት ከመሆኑም በላይ የጮቄ የውሀ ማማም በከተማዋ በቅርብ ርቀት የሚገኝባት ከተማ ናት

4.3. ማህበረ-ኢኮኖሚያዊ መሰረታዊ መረጃዎች ትንተና


4.3.1. የደብረማርቆስ ከተማ የንፁህ መጠጥ ዉሃአቅርቦት ሁኔታ
ከከተማዋ ውሀ ፍሳሽ አገልግሎት ጽ/ቤት በተገኘው መረጃ መሰረት ከ 1956 ዓ.ም ጀምሮ ከተማዋ የንፁህ የመጠጥ ውሃ አገልግሎት
ተጠቃሚ ስትሆን የውሀው ምንጭ ሰንተራ የሚገኙት ቁጥር ስድስት፣ቁጥር አስር እና ቁጥር 11 ጉድጓዶች እንዲሁም ሰላ
ምንጭ (ቀበሌ 11)፣አዲስ አምባ ምንጭና የብራጌ ምንጭ(ቀበሌ 08) መሆኑን መረጃው ያሳያል፡፡ በመረጃው መሰረት
ሶስቱ የውሀ ጉድጓዶች በ 2002 ዓ.ም ተቆፍረው አገልግሎት መስጠት የጀመሩ ሲሆን ሁሉም በጥሩ ሁኔታ አገልግሎት

16
እየሰጡ ይገኛሉ፡፡ የሚያመነጩትን የምርት መጠንም ቁጥር ስድስት፣ቁጥር 10 እና ቁጥር 11 እንደቅደም ተከተላቸው
30፣9፣እና 28 ሊትር/ሴኮንድ ነው፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ሶስቱ ምንጮች ደግሞ በ 2007 እና በ 2008 ዓ.ም ተቆፍረው አገልግሎት መስጠት የጀመሩ ሲሆን ሙሉ
በሙሉ ሳይሆን በከፊል አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙ መረጃው ያሳያል፡፡ በመረጃው መሰረት የውሀውን ጥራት
ለመጠበቅም በሳምንት ሶስት ጊዜ እንደሚመረመር እና ክሎሪን እንደሚጨመር ይደረጋል፡፡ የንፁህ መጠጥ ውሀ ሽፋኑ
67% ላይ እንደሚገኝም መረጃው ያሳያል፡፡ ክልሉ ያለበትን የንጹህ መጠጥ ውሀ ሽፋን ስናይ ደግሞ በገጠር 90.9%
በከተማ 75.05% መሆኑን ከፕላን ኮሚሽን የተገኘው መረጃ ያሳያል፡፡ በመሆኑም የከተማዋ የንጹህ መጠጥ ውሀ ሽፋን
ክልሉ በ 2011 ዓ/ም በከተማ ከደረሰበት 75.05% የውሀ ሽፋን ጋር ሲነጻጸር ዝቅተኛ ከመሆኑም በላይ 33 % ህዝብ
የንጹህ መጠጥ ውሀ ተጠቃሚ እንዳልሆነ ያሳያል፡፡ በአቅርቦት ዙሪያ ያሉትን ችግሮችን በተመለከተ የመብራት
መቆራረጥ በመኖሩ ምክንያት በተፈለገው መጠን ማምረት አለመቻሉን መረጃው ያሳያል፡፡

4.3.2. የከተማዋ የጤና አገልግልት ሁኔታ


ከደብረ ማርቆስ ከተማ ጤና ጽ/ቤት በተገኘዉ መረጃ መሰረት በከተማዋ ዉስጥ ይዞታቸዉ የመንግስት የሆኑ 1
ስፔሻሊይዝዴ ሆስፒታል፣ 3 ጤናጣቢያ ( ውሰታ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ 2004 ዓ.ም አገልግልት የጀመረ፣ህዳሴ ጤና
አጠባበቅ ጣቢያ በ 2001 ዓ.ም አገልግልት መስጠት የጀመረ፣ደብረ ማርቆስ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ በ 1961 ዓ.ም አገሌግልት
መስጠት የጀመረ) ፣7 ጤና ኬላ 21 ክሉኒክ 27 ፋርማሲዎች እንዱሁም 13 ባህላዊ ህክምና መስጫዎች ይገኛለ፡፡ ከዚህ
በተጨማሪ አንድ ተጨማሪ ሆስፒታል በመገንባት ላይ መሆኑንም መረጃው ያሳያል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የጎዛምን ወረዳ
ጤና አጠባበቅ ጣቢያም ለከተማዋ ህዝብና ለአካባቢው ህዝብ አገልግልት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ ከደብረ ማርቆስ ከተማ
ጤና ጽ/ቤት በተገኘዉ መረጃ መሰረት በከተማዉ የሚገኙ ዋና ዋና በሽታዎችን የሚያሳይ ሰንጠረዥ ከዚህ በታች
እንደሚከተለዉ ቀርቧል ፡፡
ሰንጠረዥ፡ 7 በከተማው 10 ዋናዋና በሽታዎችን የሚያሳይ

ተ.ቁ ዋናዋና በሽታዎች የህመምተኞች ብዛት


1 Acute upper resipiratory infection 12864
2 Dyspepsia 7550
3 Acute febrile illness 7284
4 Other unspecified infections andparasitic disease 5165
5 Urinary tract infection 4750
6 Other or un specified disease of eye 4690
7 Dental and gum diseases 4523
8 Typhoid fever 4412
9 Disease of the Musculo skeletal system and connective tissue 4185
10 Trauma( Injury,fracture) 3684

ምንጭ፡- የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት

17
4.3.3. የህዝብ አሰፋፈር፣ሃይማኖት፤ቋንቋናባህል

ከተሞች የተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማትእና መሰረተ ልማት አውታሮች ፣በርካታ የሰው ሀይል የሚጠይቁ
ኢንዱስትሪዎችና የመንግስት ተቋማት ፣የተሻለ የንግድ እንቅስቃሴና የስራእድል ያላቸው በመሆኑ ፈጣን የህዝብ እድገት
ይስተዋልባቸዋል፡፡ የደብረማርቆስ ከተማ ስነ-ህዝብ ሁኔታም ከላይ በተገለጹት ምቹ ሁኔታዎች እንዲሁም ባላት ምቹ
የአየር ንብረት ምክንያት ከገጠር ወደ ከተማ ከፍተኛ ፍልሰት በመኖሩ እና በከተማዋ ባለው ውልደት ምክንያት ፈጣን
የህዝብ እድገት ይስተዋልባታል፡፡ በመሆኑም በ 1999 ዓ.ም የተካሄደው ህዝብና ቤቶች ቆጠራ መረጃ የከተማዋን ህዝብ
ሊገልጽ ስለማይችል የከተማዋ አስተዳደር ከንቲቫ ጽ/ቤት የከተማዋ ህዝብ በ 2012 ዓ.ም ወንድ 102,933 ሴት 112,067
በድምሩ 215,000 ህዝብ እንደሚገኝ የተገኘዉ መረጃ ያረጋግጣል ፡፡

4.3.4. አርኪኦሎጂ፣ሃይማኖታዊና ማህበራዊ ተቋማት ሁኔታ

በፕሮጀክቱ ውስጥም ሆነ በቅርብ እርቀት ምንም አይነት የምርምር፣ አርኪኦሎጂና ሃይማኖታዊ ተቋማት የሉም፡፡

ስለሆነም ፕሮጀክቱ ተግባሩን በማካሄዱ ቀጥተኛ በሆነ መንገድ የሚፈጠር ተጽዕኖ አይኖርም፡፡

5. የአካባቢ ተፅዕኖ ትንተና

5.1. በፕሮጀክቱ ትግበራ ወቅት የሚጠበቁ አሉታዊና አዋንታዊ ተጽኖዎች


5.1.1. አዋንታዊ ተጽኖዎች

በቀጥታና በተዘዋዋሪ የስራ እድል መፈጠር ይህ የሚስማር ፋብሪካ ፕሮጀክት በስራ ላይ ሲውል ለ 143 ቋሚና

ጊዜያዊ ሰዎች የስራ እድል የሚፈጠርላቸው ሲሆን የስራ እድል ፈጣራው ቅድሚያ ለአከባቢው ነዋሪዎች

ለአካባቢው ኗሪዎች የሚሰጥ እድል ይሆናል፡፡ፕሮጀክቱ ከሚሰጠው ቀጥተኛ የስራ እድል በተጨማሪ

የፕሮጀክቶችን ምርቶች በማከፋፈል በሚሳተፉ አገልግሎት ሰጭዎች አማካይነት በተዘዋዋሪ የስራ እድል

ይፈጥራል፡፡

5.1.2. አገልግሎትን ለማህበረሰቡ በፍትሃዊነት መስጠት

ፋብሪካዉ ደረጃቸዉን የጠበቀ የእምነ በረድና ግራናይት ምርቶችን በማምረት በተለይም ለደብረ ማርቆስ

ከተማና በአካባቢዉ ለሚገኙ በኮንስትራክሽን ዘርፍ ለተሰማሩ የማህበረሰብ ክፍሎች በተመጣጣኝ ዋጋ

በማቅረብ ተጠቃሚ የሚያደርግ ሲሆን 60% የሚሆነዉን ምረቱን ደግሞ ወደ ዉጭ በመላክ የዉጭ
ምንዛሬ ያስገኛል፡፡

5.1.3. ለመንግስት ገቢ ማስገኘት

ድርጅቱ የገቢ ግብርና የትርፍ ግብር ለመንግስት ስለሚያስገባ የመንግስት ገቢ እንዲጨምር ያደርጋል፡፡

ይህም መንግስት ለአከባቢው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶችን ለማስፋፋት ያስችላል፡፡

18
5.1.4. ለባለሀብቱ ትርፍ ማስገኘት

ፋብሪካዉ ከመጀመሪያ አመት ጀምሮ ትርፋማ ስለሆነ ባለሃብቱ የሚያገኙትን ትርፍ በሌሎች ተመሳሳይ

የስራ ዘርፎች ላይ በመሰማራት ለአገሪቱ ሁለንተናዊ ልማት አስተዋፅኦ ያበረክታል፡፡

5.2. አሉታዊተፅዕኖዎች
5.2.1 በግንባታ ጊዜ የሚከሰቱ

የደረቅ ቆሻሻ መፈጠር፡- ፕሮጀክቱ በግንባታ ወቅት የላይኛው የአፈር ክፍል ለግንባታ ስለማይፈለግ ተቆፍሮ

በሚወጣበት ጊዜ ቆሻሻ ይፈጠራል፡፡ ይህ ቆሻሻ በአቅራቢያው በሚገኙ መንገዶች ወይም ወንዝ ወይም የጎርፍ

መፋሰሻዎች ላይ ከተደፋ የትራፊክ እንቅስቃሴን ያውካል ፣መንገዶችን ያቆሽሻል እንዲሁም በክረምት ወቅት

የጎርፍ መፋሰሻዎችን በመዝጋት መጥለቅለቅን ያስከትላል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የተከመረ አፈር የአካባቢው

መልካም እይታ ያበላሻል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ይህ አፈር የሚደፋበት ቦታ በውሃ አካላት ውስጥ ወይም አጠገብ

ወይም በእርሻ ወይም ለሌላ አገልግሎት በተዘጋጁ ቦታዎች ላይ ከተደፋ የአፈር ብክለትን ይፈጥራል፣ የወንዝ

ደለልን ይጨምራል፣ ወንዞች ወይም ወራጅ ውሃዎች የሚፈሱበትን መስመር ሊያስቀይር ይችላል፡፡

በግንባታ ጊዜ ከሚፈጠሩ የደረቅ ቆሻሻዎች ውስጥ እንደ ሲሚንቶ፣ ቀለም ፣ጅፕሰም ፣ ሚስማር፣ወዘተ

መያዣዎች ጥቅም ከሰጡ በኋላ በመጠራቀም የአካባቢውን መልካም ገጽታ ከማበላሸታቸው በተጨማሪ

በቀላሉ በነፋስ የሚወሰዱት ቆሻሻዎች የጎርፍ መፋሰሻዎችን በመዝጋት የጎርፍ መጥለቅለቅን ሊያስከትሉ

ይችላሉ፡፡ በተለይ የፕላስቲክነትና ብረታ ብረት ባህሪ ያላቸው ቆሻሻዎች በቀላሉ ስለማይቀልዙ የተክሎች ስር

ውሃ እንዳያገኙ በማድረግ፣ በክረምት ውሃ በማቆር የበሽታ አስተላላፊ ተህዋስያን እንዲራቡና መጥፎ ሽታ

እንዲፈጠር በማድረግ የወንዝ መፋሰሻዎችን በመዝጋት ችግር መፍጠር ፡፡

ከመጸዳጃ ቤት ውጭ በመጸዳዳት አካካቢን ማቆሸሽ፡- በግንባታ ምዕራፍ በግምት እስከ 143 የሚደርሱ

ሰራተኞች በአንድ ጊዜ ሊሰማሩ ይችላሉ፣ እነዚህ ሰዎች በስራ ሰዓት የሚጸዳዱበት ሽንት ቤት ከሌለ በየክፍት

ቦታው በመጸዳዳት አካባቢ እንዲበከል ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡

በግንባታ ሰራተኞች ላይ አደጋ ወይም የጤና ችግር መከሰት፡- ፕሮጀክቱ በሚገነባበት ጊዜ በጉድጓድ ውስጥ

በመግባት፣ከከፍተኛ ቦታዎች ላይ በመውደቅ፣ በግንባታ መሳሪያዎች በመቆረጥ ወይም ከፍተኛ ክብደት

በመሸከም አደጋ ሊደርስባቸው ይችላል፡፡ በተመሳሳይ ለግንባታ ጥቅም ላይ ያልዋለ ቆርቆሮ ወይም ሚስማር

በሰራተኞች ላይ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል፡፡

19
5.2.2. በአገልግሎት ምዕራፍ የሚከሰቱ ተፅዕኖዎች

የደረቅ ቆሻሻ መፈጠር፡- ጥቅም በማይሰጡ የምርት መጠቅለያዎች፣ጥቅም ላይ የዋሉ የውሃ መያዣ

ፕላስቲኮች፣ ከአስተዳደር ክፍል የሚፈጠሩ ወረቀትና የመሳሰሉ የጽህፈት መሳሪያዎች፣ ወዘተ የቆሻሻ

ምንጮች ናቸው፡፡በገቁፋሮ ወቅት የሚወጣ አፈር ወደወንዝ በመግባት ብክለትን ሊያስከትል ይችላል፡፡

የደረቅቆሻሻ አያያዝ ደካማ ከሆነ በየቦታው በመበታተን የአካባቢውን ውበት ከመቀነሱ በተጨማሪ እንደ አይጥና

ሌሎች ጉዳት የሚያስከትሉ እንስሳትና ተባይ መደበቂያና መራቢያ በመሆን በሰውን ንብረትና ጤና ላይ ጉዳት

ያስከትላል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በነፋስና በዝናብ ውሃ በመጓዝ የውሃ መፋሰሻዎችን በመዝጋት በክረምት የውሃ

ጥለቅለቅ ከማስከተሉም በላይ የውሃ አካላትን በመበከል ለሰው ልጅ ጤና ተስማሚ እንዳይሆን ያደርጋል፡፡

የፍሳሽ ቆሻሻ መፈጠር፡ ከፋብሪካዉ የሚወጣ አገልግሎት የሰጠ የዉሃ ፍሳሽ፣ ከመጠዳጃ ቤቶች ፤

መታጠቢያ ክፍሎች የሚፈሰው ፍሳሽ ቆሻሻ፣ በአግባቡ ካልተወገደ አፈርን፣ የከርሰምድርንና የገፀ

ምድር ውሃ ላይ ብክለትን ያስከትላል፡፡ ከሰራተኞች መመገቢያ ቤቶች እና ከመጸዳጃ ቤቶች የሚፈጠር

ቆሻሻ በመሬት ላይ ከፈሰሰ አካባቢን በመበከል ለሰው እና ለእንስሳት ጤና ጠንቅ ከመሆኑ በተጨማሪ

መጥፎ ሽታን ይፈጥራል ፡፡

የድምጽ ሁከት፡- ከፕሮጀክቱ ማሽኖች የሚወጣ ድምጽ በድርጅቱ ሰራተኞች ላይ ወቅታዊ የመረበሽ

ስሜትን ጨምሮ የጤና ችግር ይፈጥራል፡፡

የእሳትአደጋ፡- በአገልግሎት ወቅት በሚፈጠር ከፍተኛ ሙቀት እና የኤሌክትሪክ ብልሽት ምክንያት

የእሳት አዳጋ ሊፈጠር ይችላል፡፡

የብዝሀ ህይወት መመናመን፡- ፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ በአግባቡ ቁጥጥር ካልተደረገባቸው በአካባቢዉ ስነ

ምህዳር ላይ ተዕዕኖ ያስከትላል ፡፡

በፕሮጀክቱ ሰራተኞች ላይ የሚደርስ የጤና ተፅዕኖ፡- የፕሮጀክቱ ሰራተኞች በስራ ደህንነት ማነስ

ምክንያት የጤና ጉዳት ሊደርስባቸው ይችላል፡፡ በዚህ ምዕራፍ ከላይ በተገለጹት በድምጽ ሁከት፣

በመጥፎ ሽታ፣ በእሳት ቃጠሎና በሌሎች አደጋዎች ምክንያት የጤና ችግር የሚገጥማቸው ሲሆን

ከነዚህ በተጨማሪ ቀጥሎ በተዘረዘሩት ምክንያቶች የጤና ተጽእኖ ይደርሳል፡፡

20
የኤሌክትሪክ ንዝረትና በእሳት መቃጠል፡-የኤሌክትሪክ መስመሮች ያልተሸፈኑ ከሆነና ሰራተኞች

ሊደርሱባቸው የሚችሉ ከሆነ በኤሌክትሪክ በመያዝ ጉዳት ሊደርስባቸው ይችላል፡፡ በተጨማሪም የክር

ማምረቻ ፋብሪካው ጥብቅ ቁጥጥር ካልተደረገለት የእሳት አዳጋ ሊፈጠር ስለሚችል የድርጅቱ

ሰራተኞች እና በአካባቢዉ የሚገኙ ሌሎች ፋብሪካወች የእሳት አዳጋ ተጋላጭ ሊሆኑ ያችላሉ፡፡

በተላላፊ በሽታዎች መያዝ ፡- በፕሮጀክቱ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች ከተለያዩ ቦታዎች ከሚገኙ

ደንበኞች ጋር ስለሚገናኙ ለተላላፊ በሽታዎች እንደ ኤች አይቪ፣ ኮሌራ፣ የአባለዘር በሽታች፣ ኮረና

ቫይረስና ለሌሎች ተላላፊ በሽታዎች ሊያዙ ይችላሉ፡፡ ስለሆነም ተላላፊ በሽታዎች እንዳይተላለፉ

በፕሮጀክቱ በኩል የመከላከልና የመቆጣጠር እርምጃ ላልተወሰደ አጠቃላይ የጤና ተዕዕኖ ስለሆነ ከፍተኛ

ትኩረት መስጠት አስፈላጊ ነው፡፡

5.2.3. በፕሮጀክት ማጠናቀቂያ ወቅት የሚከሰቱ ተፅዕኖዎች

በፕሮጀክት መዝጊያ ምዕራፍ የሚከሰቱ ተፅዕኖዎች በሁለት መልኩ ማየት ይቻላል፡፡እነሱም አንዱ የፕሮጀክት

ባለቤቱ ግንባታዎች ናማሽኖች ወዘተ እንዳሉ ትቶ ሲሄድ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የፕሮጅት ባለቤቱ

ግንባታዎችን አፈራርሶ መሬቱን ወደነበረበት በመመለስ ሲያስረክብ ነው፡፡የዚህ ጥናት ቡድን ሁለተኛውን

ቢሆንስ ማለትም የፕሮጅቱ ባለቤት ፕሮጅቱን አፈራርሶ መሬቱን እንደነበረበ ማስተካከል ይመለሳል የሚለውን

በመውስድ ይህ በሚሆንበት ጊዜየሚኖሩ ተጽእኖዎች ቀጥሎቀርቧል፡፡

የሰራተኞች ከስራ መፈናቀል፡- ፕሮጀክቱ ስራውን በሚያጠናቅቅበት እና በሚዘጋበት ጊዜ ተቀጥረው የነበሩ

ቋሚና ጊዜያዊ ሰራተኞች ከስራ እንዲለቁ መደረግ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ሌላ ገቢ የሌላቸው ወይም ሌላ

ተመሳሳይ ስራ ያላገኙ ሰራተኞች ገቢ ስለማይኖራቸው እነሱን እና ቤተሰባቸው ችግር ውስጥ ይወድቃል፡፡

በተወሰነ መልኩም በከተማው የሚኖረው ስራ አጥነት ቁጥር እንዲጨምር ያደርጋል፡፡

የደረቅ ቆሻሻ መፈጠር፡ ማሽኖች ሲነቀሉ፣ ህንጻዎች ወይም ቤቶች ሲፈርሱ፣ በሲሚንቶ የተደለደሉ

መንገዶችና ሌሎች ግንባታዎች በሚፈርሱበት ጊዜ የተለያየ ባህሪ ያለው ቆሻሻ ይፈጠራል፡፡ ከነዚህም

ቆሻሻዎች ውስጥ የብረትነት ባህሪ ያላቸው (ማሽኖች፣ ቆርቆሮዎች፣ የአርማታ ብረቶች፣ በርና መስኮቶች፣

ወዘተ)፣ የድንጋይና አፈርነት ባህሪ ያላቸው፣ የፕላስቲክ፣ እንጨትናመስታውትነት ባህሪ ያላቸው ቆሻሻዎች

ይፈጠራሉ፡፡

21
በአቅራቢያ ያለንብረት ላይ ጉዳት ማድረስ፡- አንዳንድ ቁመታቸው ከፍተኛ የሆኑ ግንባታዎች በሚፈርሱበት

ጊዜ በአካባቢው በሚገኝ ንብረት ላይ በመውደቅ ጉዳት ሊያስከትሉ ይችላሉ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ

መሰረታቸው ወደ መሬት ዝቅ ያሉ ግንባታዎች በሚፈርሱበት ጊዜ በአቅራቢያ ያሉ እንደመንገድና ሌሎች

የፕሮጀክት ግንባታዎችን መሰረት በማናጋት በቀላሉ እንዲፈርሱ ምክንያት ይሆናሉ

6. የህብረተሰብ ተሳትፎ
የቢቤት ትሬዲን የእምነ በረድና ግራናይት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ፋብሪካ ፕሮጀክት አካባቢ ቦታ የወሰን ልየታ
ቪጋርና የአካባቢ ተፅዕኖ ሰነድ ለማዘጋጀት በቀን 27/02/2016 ዓ.ም ከቦታው በመሄድ ቅኝት በማካሄድ የታየ
ሲሆን ቦታው በኢንዱስትሪ መንደር የሚገነባ በመሆኑ ከመኖሪና ከድርጅት አካባቢ ብዙም ቅርበት የሌለዉ
በመሆኑ በመኖሪያ አካባቢ ይደርሳል ተብሎ የሚያሰጋ አሉታዊ ተፅዕኖ የለም፡፡ የእምነ በረድና ግራናይት ፋብሪካዉ
ግንባታ የሚካሄድበት መሬት ካሳ ተከፍሎበት በኢንደስትሪ መንደር የተከለለና ከማንኛዉም የግልም ሆነ
የመንግሰት ይዞታ ነፃ የሆነ በመሆኑ በግለሰብ ደረጃ የሚፈናቀልም ሆነ ንብረት የሚያጣና ቀጥተኛ አሉታዊ
ተፅዕኖ የሚደርስበት የማህበረሰብ አካልም ሆነ ድርጀት ባለመኖሩ የማህበረሰብ ዉይይት ማድረግ አላስፈለገም ፡፡

7. በጥናቱ የሚዳሰሱ ቁልፍ ጉዳዮች

7.1. ፕሮጀክቱ በአከባቢው በሚኖሩ እንስሳት እና እፅዋት ላይ ሊኖረው የሚችለውን ተፅዕኖ

 ፕሮጀክቱ በአከባቢው በሚኖሩ ውሃማ አካላት እና በውሃ ውስጥ በሚኖሩ እንስሳት እና እፅዋት ላይ

ሊኖረው የሚችለውን ተፅዕኖ

 በፕሮጀክቱ በታችኛው አከባቢ በሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ ሊኖረው የሚችለውን ተፅዕኖ

 ፕሮጀክቱ በመሬት አቀማመጥ፣በቅርሶች፣ በተፈጥሮ ሀብቶች፣በማህበረሰቡ ባህላዊ እሴቶች፣ በድምፅ

እና አየር ብክለት ዙሪያ የሚያመጣው ተፅዕኖ

 በፕሮጀክቱ አማካኝነት የሚፈጠረውን ፋሳሽና ደረቅ ቆሻሻ

 በፕሮጀክቱ ስራ ጋር ተያይዞ በሚመጡ የጤና ችግሮች እና የስራ ላይ ሊፈጠሩ የሚችሉ አዳጋዎች

 ፕሮጀክቱ በአከባቢው በሚኖረው አሉታዊና አውንታዊ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ

8. የጥናት እቅድ /የአከባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርት ዝግጅት ቅደም ተከተል

ኢትዮ ግሪን የአከባቢ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች አማካሪ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር

የፕሮጀክቱን ዝርዝር የአከባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ለማካሄድ በሚከተሉት ነጥቦች ላይ ትኩረት ለማድረግ

ታቅዷል፡፡ ስለሆነም የአከባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርት ቪጋሩም እንደሚከተለው ይቀርባል፡፡

22
8.1. አጠቃላይ መግለጫ

የፕሮጀክት ስምና አድራሻ፣ የፕሮጀክት ባለቤትስም፣ ጥናቱን ያጠናው የአማካሪ ድርጅት ስም፣የፕሮጀክቱ

ምንነት አጭርና ግልፅ ማብራሪያ፣ የፕሮጀክቱ ቦታ አጭርና ግልፅ መረጃ፣ የፕሮጀክቱ አማራጮች፣ በፕሮጀክቱ

ምክንያት ይከሰታሉ ተብሎ የሚገመቱ ዋና ዋና የአከባቢ ተፅዕኖዎች፣ የተለዩ የተፅዕኖ ማቅለያ ዘዴዎችና፣

የአከባቢ የክትትል ስርዓትና የማስተግበሪያ ስልት ወዘተ ይካተታሉ

8.2. መግቢያ

 የፕሮጀክቱ/የጥናቱ/ መነሻ ሀሳቦች

 የፕሮጀክት ፕሮፖዛል መግለጫ በአጭሩ(አላማ፣ የፕሮጀክት መገኛ ቦታ፣የተለያ

አማራጮች፣የሚጠይቀውን የሀይል አይነት፣ፍጆታና ምንጭ እንዲሁም የሌሎች ሀብቶች ፍላጎት

 የአከባቢ ተፅዕኖ ዘገባ አደረጃጀት

 የጥናት ዘገባው አላማና የባለሀብቱን ግዴታ፣የህግ ተጠያቂነትና በቀጣይ የሚከናወኑ ተግባራት


8.3. የአከባቢ ተፅዕኖ ጥናት አላማ

 ጥቅል አላማ
 ዝርዝር አላማ

8.4. የጥናት ወሰን

 የፕሮጀክቱ አከባቢያዊ፣ ማህበራዊ፣ ባህላዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ ይገለፃል


 የፕሮጀክቱን ክልል የሚያሳይ ካርታ ይገለፃል

8.5. የጥናቱ ስልት ወይም ዘዴ

 በጥቅም ላይ የዋለ የጥናት ስልት፣ግብዓቶች፣ የመረጃ አሰባሰብና ትንተና ዘዴዎች


 የማሳተፊያ ዘዴ ስልትና የተሳትፎ ደረጃ
 በጥናቱ የተሳተፉ የባለሙያዎች ብዛት፣የሙያ ስብጥር፣ ኃላፊነትና ሙሉ አድራሻ

8.6. በጥናት ወቅት የተወሰዱ ታሳቢዎችና የነበሩ የእውቀት ክፍተቶች

 በጥናት ወቅት ያጋጠሙ የእውቀት ክፍተቶችን፣ በይሆናል የተወሰዱ መረጃዎችንና የመረጃ


ምንጭ ያልተገኘላቸውን መረጃዎች መለየት
 መላምቶች ያልተሟሉበትን ምክንያት መዘርዘር
 የተገኙ የእውቀት ክፍተቶችና መላምቶች ውሳኔ አሰጣጥ ላይ የሚኖራቸው እንድምታ መግለፅ

23
 ያጋጠሙ እጥረቶችንና ውስንነቶችን ለማስወገድ የተወሰዱ የመፍትሄ እርምጃዎችን መግለፅ

8.7. የፖሊሲ፣የህግና የአስተዳደር ማዕቀፎች

 የፖሊሲ፣የህግና የአካባቢ ደረጃ ማዕቀፎች በጥናቱ ይዳሰሳሉ

8.8. ዝርዝር የፕሮጀክት ገለፃ ማድረግ

 የፕሮጀክትን ስፋትና ባህሪ


 ለፕሮጀክቱ የተለያ አማራጮች ገለፃ ማብራሪያ
 የጥሬ እቃዎች ምንጭ፣አይነት ባህሪና መጠን
 የፕሮጀክቱ የጊዜ ሰሌዳ
 የቴክኖሎጂ አይነትና የቴክኖሎጂ ገለፃ
 የአመራረት ሂደት፣የተረፈ ምርቶችና የዋና ዋና ምርቶች አይነትና መጠን
 የደረቅና ፍሳሽ ቆሻሻን የማፅዳትና የማስወገድ ሂደት
 የሰውና የግብዓት ፍጆታ ወጪዎች

8.9. የባዮፊዚካልና ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ መሠረታዊ መረጃዎች

 የአከባቢ የመሬት ስሪት ወይም የይዞታ ሁኔታ፣በዙሪያው የሚገኝ የመሬት ሁኔታ፣ በአከባቢው ያሉ ግልፅ የሚታዩ
ተግዳሮቶች፣በፕሮጅቱ አካባቢ ያለው የመሰረተ ልማት የአገልግሎት ሁኔታ
 አሀዛዊና አሃዛዊ ያልሆኑ ፊዚካላዊና ስነህይወታዊ መረጃዎች ለምሳሌ የአየር ንብረት፣ አፈር፣ የውሃ
ሀብት፣የስርዓተ ምህዳር፣የመሬት አቀማመት፣የእፅዋትና እንስሳት አይነት ስርችትና ብዛት
 የምጣኔ ሀብታዊ መረጃዎች ለምሳሌየህዝብ ቁጥርና ስርጭት፣የእድሜ ስብጥር፣ የኢኮኖሚያዊ እድገት
ሁኔታ፣የውልደት ሁኔታ፣ የቤተሰብ የገቢ ሁኔታ መረጃ፣የኑሮ ሁኔታ፣የመሰረተ ልማት አገልግሎት፣የቤቶች
ሁኔታ፣የሀይል ፍጆታ፣ የውሃ አቅርቦት
 ባህላዊና ታሪካዊ ቦታዎች ለምሳሌ ፓርከች፣ የዱር እንስሳት መጠለያ ቦታዎች፣ መህስብ ቦታዎችና ሀውልቶች፣
ትኩረት የሚሰጣቸው የሀይማኖት ቦታዎች
 ተፅዕኖ የሚደርስበትን ቦታ የሚያመላክቱ ኮርዲኔቶች፣ ከለርድ ፎቶ ግራፎች፣ ሰንጠረዦችና ሌሎች ገላጭ
መረጃዎች
 የፕሮጀክት ትግበራ ቦታን የሚያሳይ ካርታና የፕሮጀክት ሳይት ፕላን
 ፕሮጀክቱ ድንበር ተሸጋሪ ተፅዕኖ የሚያደርስ ከሆነ ተፅዕኖ የሚደርስበትን አካባቢ የፊዚካላዊና ስነህይወታዊ
እንዲሁም ማህበራዊና ምጣኔ ሀብታዊ መረጃዎች

8.10. የአከባቢ ተፅእኖ ትንተና ማካሄድ

 እያንዳንዱን ተፅዕኖ ማብራሪያና ትንታኔ ማየት


 በፕሮጀክት አካባቢ ተፅዕኖ የሚደርስባቸውን አካላት መተንተን
 ፕሮጀክቱን ለመተግበር የተለያ አማራጮች ንፅፅር (ስፋት/መጠን፣በገኛ ቦታ፣ ቴክኖሎጂ፣ ፕላን፣የኃይል ምንጭ፣
ቴክኒካዊ ተፈፃሚነት፣ አከባቢያዊና ማህበራዊ ችግሮች
 የተፅዕኖ ትንበያ እርግጠኝነት

24
8.11. የተፅዕኖ ማቅለያ እርምጃዎች

 ለእያንዳንዱተፅዕኖ በእያንዳንዱ የፕሮጀክት ትግበራ ደረጃ ሊተገበሩ የሚገባቸው የተፅዕኖ ማቅለያ


እርምጃዎች በአግባቡ ተዘርዝረው የሚያስፈልጋቸውም ወጪ በተገቢው ሁኔታ ይመደባል
 የተለያዩ የማቅለያ እርምጃዎችን በመለየትና በማደራጀት ከተዘረዘሩት አማራጮች ውስጥ ምክንያታዊ በመሆን
የተሻሉ የማቅለያ እርምጃዎችን ለማሳየት ጥረት ይደረጋል
 አውንታዊ ተፅዕኖዎችንም እንዴት ማሳደግ ወይም ማሻሻል እንደሚቻል ይገለፃል

8.12. የአካባቢ አያያዝ እቅድ

የሚከተሉት ነጥቦች ይካተታሉ

 የተፅዕኖዎች ዝርዝር

 በእያንዳንዱ ተፅዕኖ የታቀዱ የተፅዕኖ ማቅለያ ዝርዝር ተግባራት ዝርዝር

 በእያንዳንዱ ተፅዕኖ የታቀዱ የተፅዕኖ ማቅለያ ዝርዝር ተግባራት መለኪያ

 በእያንዳንዱ ተፅዕኖ የታቀዱ የተፅዕኖ ማቅለያ ዝርዝር ተግባራት መጠን

 በእያንዳንዱ ተፅዕኖ የታቀዱ የተፅዕኖ ማቅለያ ዝርዝር ተግባራት የተመደበ የገንዘብ መጠን

 በእያንዳንዱ ተፅዕኖ የታቀዱ የተፅዕኖ ማቅለያ ዝርዝር ተግባራትን የሚተገበሩበት የጊዜ ሰሌዳ
 በእያንዳንዱ ተፅዕኖ የታቀዱ የተፅዕኖ ማቅለያ ዝርዝር ተግባራትን የሚፈፅሙት አካላት ዝርዝር

8.13. የአከባቢ ክትትል/ምርመራ እቅድ

 ክትትል የሚደረግባቸው የማቅለያ ተግባራት ዝርዝር


 ክትትሉን የሚያደርገው ተቋም
 የክትትል ዘዴዎች
 ክትትል የሚደረግባቸው የተግባር አመላካቾች ጥቅም ላይ የሚውሉ ደረጃዎች /ስታንዳርዶች ወይም
የአሰራር መመሪያዎች
 ክትትል የሚደረግበት የድርጊት መርሃ ግብር ይዘጋጃሉ፡፡

8.14. ማጠቃለያና ምክረ ሀሳብ

 የቁልፍ ጉዳዮች ማብራሪያ


 ጉልህ አሉታዊ ተፅዕኖዎችን ለመቀነስ የሚወሰዱ እርምጃዎች
 አውንታዊና አሉታዊ ተፅዕኖዎችን ለማመዛዘን የፕሮጀክቱ አዋጪነት
 ሊተኩ የማይችሉ የአከባቢ ሀብቶችን የመጠቀም ወይም የሚያጠፋ መሆኑንና ያለመሆኑን
 ለክትትልና ቁጥጥር ስራዎች የሚያስፈልጉ የህግ ማዕቀፎች እና ሌሎች ወሳኝ የሆኑ ሀሳቦች

25
ዕዝል 2 በአካባቢና ማህበራዊ ተጽዕኖዎችን ለመለየት የሚያገለግል ቸክሊስት
ሊከሰቱ የሚችሉ ተፅዕኖዎች አሉታዊ ተፅዕኖ አዎንታዊ
ተፅዕኖዎች የለውም ተፅዕኖዎች
 በቁስአካላዊ አካባቢ ላይ የሚፈጠር ተፅዕኖ
1.1 ገፀ-ምድር
የአፈር ክለት X
የመሬት አጠቃቀም ለውጥ X
የመሬት ገደላማነትና ተዳፋትነት መፈጠር X
1.2 አየር
በብናኝ ምክንያት የአየር መበከል X
የመጥፎ ሽታ መፈጠር X
የአደገኛ አየር በካይና ኦዞንን የሚጎዱ ጋዞች ልቀት/CFC ጋዞች/ X
በዐየር ነፃ\ዝውውርና ሙቀት ላይ የሚፈጠር ተፅዕኖ X
1.3 የውሃ ሃብት
በተበከለ የውሃ ልቀት ምክንያት በውሃ ሃብቶችና ስርዓት ላይ የሚደርስ ብክለት X
በውሃ ስርገት፣ፍሰት ስርዓትና የጎርፍ መጠን ላይ የሚፈጠር ለውጥ X
በከርሰ ምድር ውሃ ጥራት ላይ የሚከሰት ለውጥ X
በገፀ-ምድር ውሃ ላይ የመልክ የሙቀትና መሰል የበሃሪ ለውጦች መከሰት X
በሰው ወይም በንብረት ላይ በጎርፍና መሰል ችግሮች የሚከሰት ችግር X
በውሃ አዘል መሬቶች ላይ በሚኖር ግንባታ የሚፈጠር ተፅዕኖ X
1.4 ቆሻሻ
ጉልህ የሆነ የደረቅና ፍሳሽ ቆሻሻ መፈጠር X
1.5 የድምፅ ብክለት X
በስነህይወታዊ አካባቢ ላይ የሚኖር ተፅዕኖ
2.1 ዕፅዋት
የዕፅዋት ዝርያ ብዝሃነትና ምርታማነት ላይ የሚፈጠር ተፅዕኖ X
በመናመን ላ እነደሆኑ በተለዩ የእፅዋት ዝርያዎችና መኖሪያቸው ላይ የሚደርስ X
ተፅዕኖ
መጤ የእፅዋት ዝርያዎችን የማስገባትና ነባሮችን የመገደብ ተፅዕኖ X
o . የእንስሳት ህይወት
በመናመን ላ እነደሆኑ በተለዩ የእንስሳት ዝርያዎችና መኖሪያቸው ላይ የሚደርስ X
ተፅዕኖ
በዱር እንስሳት መኖሪያና እንቅስቃሴ አኗኗር መረበሽ X
የዱር እንስሳትን መኖሪና አኗኗር ማናጋት
3. ማህበራዊና ምጣኔሃብታዊ አካባቢ X

26
ሊከሰቱ የሚችሉ ተፅዕኖዎች አሉታዊ ተፅዕኖ አዎንታዊ
ተፅዕኖዎች የለውም ተፅዕኖዎች
3.1 የተፈጥሮ ሃብቶች
የተፈጥሮ ሃበቶችን ለልማት የመጠቀም ሁኔታ መጨመር X
ታዳሽ ያልሆኑ ሃብቶች የመመናመን/የማለቅ X
ጥብቅ ቦታዎች ፓርኮች ወንዞች ፣ ሃይቆች ላይ የሚኖር ተፅዕኖ X
3.2 ሃይል
በካይ የሃይል ምንጮችን መጠቀም/ነዳጅ X
ባለው የሃይል ምንጭ ፍላጎት ላይ ጭማሪ ማሳየት X
3.3 የትራፊክ ፍሰትና ተሸከርካሪ ዝውውር
ባለው የትራፊክ ፍስት ላይ ተጨማሪ ጫና መፈጠር X
በወቅታዊ የሰዎችና ቁሳቁስ እንቅስቃሴ ላይ ለውጥ መፈጠር X
የትራፊክ አደጋ ክስተት በእግረኛና በተሽከርካሪ ላይ መጨመር X
የአዲስ መንገድ መከፈት/ መገንባት X
o የህዝብ ቁጥር
የህዝብ ቁጥር እና ስርጭት በአካባቢው መቀየር X
3.5 የድንገተኛ አደጋ ክስተት
ፍንዳታ፣እሳት ቃጠሎ፣ የኬሚካልና አሌክቲሪክ አደጋ፣ ህንፃ መደርመስ ክስተቶች X
3.6 የሰው ጤና
በስራ ላይ በሚከሰት አደጋ የሚፈጠሩ የጤና እክሎች X
በአባላዘርና ተዛማጅ በሽታዎች ሚከሰት የጤና ተፅኖዎች X
3.7 ምጣኔሃብት
በአካባቢውም ሆነ በክልላዊ ምጣኔ ሃብት ላይ የሚኖር አወንታዊ ተፅዕኖዎች/ ገቢ X
ማደግ፣ መሬት ዋጋ ማደግ ወዘተ.
ለአካባቢው ማህበረሰብ የስራ እድል መፈጠር X
3.8 የማህበረሰብ ምላሽ
ከአካባቢው እሴት ባህልና ወግ ጋር የሚፃረሩ ሁነቶች መከሰት X
4.ውበትና ዕይታ
በአካባቢውና ዙሪያው ውበትና እይታ ላይ የሚኖር አሉታዊ ለውጥ X
5. ታሪካዊ ሃይማኖታዊና ባህላዊ ቅርሶች
በቅርስነት በሚታወቁ ታሪካዊ ሃይማኖታዊ ባላዊና ተፈተሮአዊ ሃበቶች ላይ X
የሚደርስ ተፅዕኖ

8.15. ዋቢ ማጣቃሻዎች

 ለዚህ ጥናት ያገለገሉ ምንጮች ይገለፃሉ

8.16. እዝሎች
 የቦታው ካርታ
 የጥናት ቡድኑን የግል ሁኔታዎችን የሚገልፅ መረጃ
 የአማካሪ የሙያና የንግድ ፍቃዶች
 የፕሮጀክቱ ባለቤት ስለጥናቱ የሰጠው ትክክለኛ ማረጋገጫ
 በቀረበው የመጀመሪያ የተፅዕኖ ዘገባ ላይ ገምጋሚ ባለሙያዎች የሰጡት አስተያት

9. የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናት ሰነድ ይዘት

የሚዘጋጀዉ የአካባቢና ማህበራዊ ተፅእኖ ግምገማ ዘገባ የሚከተሉት ክፍሎች ይኖሩታል

27
 አጠቃላይ መግለጫ
 መግቢያ
 የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናቱ አላማ
 የጥነት ወሰን
 የጥናቱ ስልት ወይም ዘዴ
 በጥናቱ ወቅት የተወሰዱ ታሳቢዎችና የነበሩ የእዉቀት ክፍተቶች
 የፖሊሲ፣ የህግና የአስተዳደር ማዕቀፎች
 የፕሮጀክቱ ገለጻ
 የባዮፊዚካልና ሶሾኢኮኖሚ መሰረታዊ መረጃዎች ትንተና
 የአካባቢ ተፅዕኖ ትንተና
 የተፅዕኖ ማቅለያ እርምጃዎች
 የአካባቢ አያያዝ እቅድ
 የአካባቢ ክትትል እቅድ
 በፕሮጀክቱ ትግበራ ተፅዕኖ የሚደርስባቸዉና የሚመለከታቸዉ አካላት ምክክር
 ማጠቃላያ ምክረሃሳብ
 ዋቢ መጽሀፍት ወይም ማጣቀሻዎች

10. የአካባቢና ማህበራዊ ተጽእኖ ግምገማ ጥናት የሚካሄድበት የጊዜ ሰሌዳ

በኢትዮጲያ እንዲሁም በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በወጡ የአካባቢና ማህበራዊ ተጽእኖ ግምገማ

ጋይድላይን፣ አዋጆችና መመሪያዎች መሰረት ማንኛዉም ፕሮጀክት ወደትግበራ ከመግባቱ በፊት በአካባቢ

ተጽእኖ ግምገማ ሂደት ዉስጥ ማለፍ እንዳለበት ይደነግጋሉ፡፡ በዚህም መሰረት በደብረ ማርቆስ ከተማ

መንቆረር ክፍለ ከተማ ቀበሌ 11 ኢንዱስትሪ መንደር ዉስጥ ሊቋቋም ለታቀደው ፕሮጀክት የአካባቢ ተጽእኖ

ግምገማ ጥናት ለማካሄድ ይህ የጊዜ ሰሌዳ /ቢጋር/ተዘጋጅቷል፡፡ ይህ ቢጋር በፕሮጀክት ባለቤቱ በቢቤት

ትሬዲንግ እምነ በረድና ግራናይት ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እና በአማካሪ ድርጅቱ ኢትዮ ግሪን የአካባቢ

ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች አማካሪ ኃ/የተ/የግ/ማ/ እንዲሁም ሰነዱን ገምግሞ በፕሮጀክቱ ላይ ዉሳኔ

በሚሰጠዉ የአካባቢ ጥበቃ መስሪያቤት መካከል መግባባት እንዲፈጠር ያደርጋል፡፡


ሰንጠረዥ 8 ፡- የአካባቢና ማህበራዊ ተጽእኖ ግምገማ ጥናት ለማካሄድ የተዘጋጀ የድርጊት መርሃ ግብር

ተ.ቁ ዋና ዋና ተግባራት የሚካሄድበት ጊዜ ተግባሩን

የሚፈጽምአካል
1 የፕሮጀክቱን ቦታ በማየት መረጃዎችን ማሰባሰብ ዉይይት 27/02/2016 ዓ.ም በአጥኚ ቡድን
2 የአካባቢ ወሰን ልየታ ሪፖርት አዘጋጅቶ ማቅረብ 29/02/2016 ዓ.ም በአጥኚ ቡድን
ማካሄድ

28
3 የፕሮጀክት ባለቤቱ የአካባቢ ወሰን ልየታ ሪፖርቱን በደብዳቤ 02/03/2016 ዓ.ም በፐሮጀክቱ ባለቤት
ለደብረ ማርቆስ ከተማ አካባቢ ጥበቃ አረንጓዴ ልማት ጽዳትና
5 ዉበት ተጠሪ ጽ/ቤት ማቅረብ
የቀረበዉን የወሰን ልየታ ሪፖርት በመገምገም ግብረ መልስ 07/03/2016 ዓ.ም ገምጋሚ ቡድን
6 መስጠት
የአካባቢ ወሰን ልየታ ሪፖርት እንዲስተካከል ገምጋሚ ቡድኑ 03/03/2016 ዓ.ም በአጥኚ ቡድን
7 ግብረመልስ ከሰጠ አስተካክሎ በድጋሜ ለገምጋሚ ቡድኑ
የመጀመሪያዉን የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማ ዘገባ ረቂቅ 11/03/2016 ዓ.ም በአጥኚ ቡድን
8 በማዘጋጀት ለፕሮጀክት ባለቤቱ ማቅረብ
በረቂቅ የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማ ዘገባ ላይ ከፕሮጀክት ባለቤቱ 13/03/2016 ዓ.ም የፐሮጀክቱ ባለቤቱ
9 ግብረ-መልስ ካለ እንዲስተካከል ለአማከሪዉ መስጠት
የመጀመሪያዉን የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማ ዘገባ ረቂቅ 16/03/2016 ዓ.ም የፐሮጀክቱ ባለቤቱ
10 ለገምጋሚ ቡድኑ ማቅረብ
የቀረበዉ የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማ ዘገባ ገምጋሚ ቡድኑ 18/02/2016 ዓ.ም በአጥኚ ቡድን
የማስተ ካከያ አስተያየት ካለ ሰነዱን አስተካክሎ ማቅረብ
11 ተስተካክሎ የቀረበዉን ዘገባ መስተካከሉን መገምገም 20/03/2016 ዓ.ም ገምጋሚ ቡድን
12 በደ/ማ/ከ/አካ/ጥ/አረ/ል/ጽ/ዉ/ተ/ጽ/ቤት ፕሮጀክቱ ተግባራዊ 24/03/2016 ዓ.ም ገምጋሚ ቡድን
እንዲሆን ከተስማማ የይሁንታ ሰርቲፍኬት ለፕሮጀክት ባለቤቱ
ይሰጣል
11. የአማካሪ ድርጅቱ የንግድ ፈቃድ

29
30
31
32
33
 በዚህ ጥናት የተሳተፍ ባለሙያዎች ሲቪ (CV)

CURRICULUM VITAE
Name: Tiruneh Engida Worku

Address: Debre Markos

Telephone No: 0913411527/0961894478 E-Mail: tiruneh242@gmail.com

Date of birth; August 5/1974 E.C

Sex: Male, Marital Status: Married

Nationality: Ethiopian

Religion: Orthodox

Education Qualification

No Level Year University Field of Study


1 Master 2015 E.C Debre Markos Environmental Science
2 Degree 1996 E.C Bahir Dar University Geography
Work Experience
 From 01/11/1996 E.C-30/10/2003 E.C Debre Markos Nigus Tekle Haymanot Secondary
school Geography Teacher
 From 01/11/2003 E.c -24/4/2006 Urban Municipal Standardization and Monitoring
Expert at Debre Markos Urban Development and City Service Office
 From 25/4/2006 -30/4/2010 Socio Economist Expert at Debre Markos Urban
Development and City Service Office
 From 01/05/20010 E.C- 30/10/2015 Environment and Social Safe gourd Specialist at
Debre Markos Urban Infrastructure Development
 Generally, I have 18 years working experience more on Teachers in Geography Socio
Economist, Environment and Social safe gourd officer in Urban Infrastructure
Department and. I pursued post graduate studies in Debre Markos University in the
Department of Natural Resource Management, specialized in Environmental Science.
Language:

 Amharic
 English
Skill:

34
 Basic Computer Skill
 Basic SPSS soft wear Application skill
 Basic Auto Cad and GIS Soft wear Application Skill
Hobby:

 Reading Books
 Following and attending spiritual events and spiritual songs
 Watching T.V
Reference:

5. Dr.Getinet Assabu . (PHD.) Lecture of Environmental Economics and Geology at Debre


Markos University. (Mobile: +251911335038 or +251911267154)
6. Dr Kiros Getachew .(PHD) (Climate Change and Bio Diversity ) Lecture at DebreMarkos
University ( Tel:0913220584) Those teachers are my witness to testify my performance in
academic or practical work.

35
CURRICULUM VITAE

ESUBALEW DEBAS MIHIRETIE

Tel: - +251-964-56 46 46 /+251 -923-42 38 80 Email- esubalew127@Gmail.Com

PERSONAL DETAILS

Date of birth:- 20 August 1984 G.C Sex:- Male

Languages:- English and Amharic፣ Nationality:- Ethiopia

OBJECTIVE OR PROFILE

My qualification coupled with my career has led me to specialize in planning Monitoring and evaluation
of Hygiene and environmental health, global health and pollution, MBS, EIA, WASH HIV /ADIS IDSR,
ICCM, IMNCI, EPI, malaria, nutrition, hygiene and sanitation, TB, leprosy, supportive supervision,
communication skill, IEC/BCC vector biology, disease surveillance, reporting and response, project
management, Health service extension programs. And this opportunity helped me to take part in the
control of major communicable disease in our country in line with MDGs. My supervision experience has
left me skilled in with the function of Ethiopian health system reforms, organization structures, program,
and to preparing environmental impact assessment (EIA) and to suggested mitigation masseur for each
problem of the project.

EDUCATIONAL BACKGROUND
Debre Markos University:- Masters Degree in General Masters of Public Health on June 27/2015 G.C.

 Haromaya university:- BSC Degree in Environmental health science, on September 12/2012


G.C
 Jimma university :- College of Public Health, Diploma in environmental Health ,July Fifth
2003 G.C
Special Training and certification
TOT :-MBS and 0n Procurement, contract and financial management and budget
management 2022 at Gondor by SNV

 TOT ;- WASH on PHCU management and District Transformation and performance management
by FMOH 2018
 EIA;- and Inter personal communication skill and building the skill of health professional to
work with community and to protected environment, population (April 2009)
Courses , Training and certification

 TOT on TB and HIV integrated refresher training module for health extension professional
(October 2012)

36
 TOT on EIA , CLTSH and on inter personal communication skill And IEC/BCC (April 2009)
 TOT on accelerated implementation of health service extension program on EPI,RH, IMNCI, ENA
Malaria, Hygiene and environmental health, HIV/AIDS ,IEC ,Monitoring & Evaluation (July –
August 2006)
 TOT on maternal, neonatal, child and Adolescent health ,Malaria, hygiene &
sanitation ,Nutrition and communication for health extension professional (NOV 2011)
 TOT on ICCM and IMNCI ( Integrated Community Child Illness Management) September 2012
NGOs and Specia experience

 Participated in conducting training based on ENA,IMNCI,ICCM, hygiene and sanitation and


interpersonal communication skill organized and facilitated by IFHP and Guhion Development
Aid Organization
 Conduct ISS and Monitoring &Evaluation in collaboration with IFHP& Guhion Development Aid
Organization for about 3 years& 6 month
 Amahra Region Drought prevention and Food security coordination Biro Relief Regional
coordinator under WFO
I have Experience by consulting and training service especially by EIA,WASH, Sanitation and
environmental health ,market based sanitation.
PROFESSIONAL CAREER( RELEVANT EXPERIENCE)

Health service extensions program coordinator and Hygiene and environmental health officer
Gozamen district Health office November 2010 – to Present

Main duties and responsibilities

 Develop detail M&E monthly, quarterly and yearly action plan for programs
 Monitor and evaluate these program based on the stretched objective
 Follow up & evaluate the performance of health professional
 Provide technical support & capacity building for health professional
 Collect analyze and interpret the daily use of data
 Conduct facilitative supervision and provide feed back
 Recognize encourage and motivate health professional so as to maintain & improve
performance
 Facilitate experience sharing meetings in collaboration with district health office and
Disseminate lessons learnt
 Work in coordination with stake holders, NGOs supporting the health service delivery
system
 Inspect both Urban and Rural water and sanitation projects
 Take water sample and sent it for further lab analysis
 Take part in water, sanitation &Hygiene projects site selection
 Organize support and supervise school water sanitation and hygiene program
 Prepare a summary of the activity report

37
Amahra Region Drought prevention and Food security program coordination Biro Relief
Regional coordinator under WFO (October 2009 – October 2010)

Main duties and responsibilities

 Prepare detail M&E annually, quarterly & yearly action plan and identify risk and drought
areas
 Conduct supervision at zonal and district level stakeholder using designed checklist
 Give in service training for health and agriculture professional
 Regularly observe model households for graduation approval in collaboration with district
and health center staffs
 Strengthen the referral linkage & health extension programs to HC ,
 Prepare a detail monitoring and Evaluation of monthly, quarterly and yearly action plan
 Give new license for nongovernmental for profit health facilities those which meet
minimum requirements
Project planning, monitoring and evaluation officer, Enarji Enawga district health office

( October 2008- September 2009 )

Main duties & responsibilities

 Prepare annual and strategic plan


 Monitor and evaluate the health service programs based on the desired objectives
 Order procurements and approve statement of expenditures
 Conduct performance review meeting, quarterly, biannually & yearly focused on both
qualitative and quantitative indicators
 Evaluate department heads using a designed standard
 Motivate and encourage staffs who perform well
 Work in coordination with stake holders supporting the health service delivery system
Malaria and Other communicable disease control officer Enarj Enawga District health office,
August2003 – August 12/2005

Main duties and responsibilities

 Prepare detail M&E monthly quarterly & yearly action plan of a program
 Take part in malaria epidemic forecasting, preparedness and control
 Highly participate in indoor residual chemical spray for the control of malaria vector
 Provide technical support and capacity building for health professionals
 Conduct facilitative supervision & provide feed back
 Train health staffs on HIV/AIDS and malaria prevention and control
 Collect analyze and interpret the daily use of data and Produce and submit detail report
Other skills:- Computer literate, MS-Office Packages , XL
REFERENCES

38
1. Ato Ayalew Shiferaw Ayalaw Senior Program Officer at The Carter Center-Ethiopia (TCC),
ayalewsisu2003@gmail.com Tel. 09-13-49-13-65

2. Ato Wodosen Sige Amahra Region WASH Capacity building Advisor e-mail wendetsige@gmail.com Tel.
09-13-03-92-87

39
Curriculum vitae (CV)

I. Personal information
Name: Balager Anteneh Date of birth: May 16,1975 E.C

Sex: Male Nationality: Ethiopian

Age: 40 Current address: Debre Markos

Marital status: married Place of birth: Dembecha

Mobile: 09-13-26-40-04 Email: balageranteneh@gmail.com

II. Educational Background


Elementary: Abidender primary school (From Grade1-6) From 1980-85 E.C.

Junior: Shellel Junior secondary school (From Grade 7-8) From 1986-87 E.C.

High school: Dembecha senior secondary school (From Grade 9-12) From1988-92 E.C.

Degree: Bahir Dar University From 1997-2000 E.C.

MA: Debre Markos University From 2005-2007 E.C.

III. Qualification
B.Ed in Geography Minor Economics

MA Degree in Geography and Environmental studies

IV. Experience

From 1996-1997 Teaching Geography in Tenguma primary and junior school

From 1998-2001 Teaching Geography in Amanuel senior secondary and higher education

Preparatory school

From 2002-2007 Teaching Civics in Deber markos technical and vocational institute

From 2008- till now land use expert in East Gojam Zone.

v. Language

Types of language Listening Speaking Writing Reading

Amharic Excellent Excellent Excellent Excellent

40
English Excellent Excellent Excellent Excellent

VI. Skill

 Basic computer skill


 Basic Arc GIS skill
VII. Research Experience

 I published research in the Ethiopian Journal of Social Sciences Volume 6, Number 1,


May 2020 (Challenges of Irrigation Water Management on Smallholder Schemes:
Case Study in Dembecha Woreda, Northwest Ethiopia.

VI. Hobby

Reading different books and participating in voluntary activities.

VII. Reference

Mehretie Belay (PhD) Assistant professor in Debre Markos University

Phone number: 0913486862

41
Curriculum vitae (CV)

42
43
12. በዚህ ጥናት የተሳተፍ ባለሙያዎች የሙያ ፈቃድ

44
45
46
47

You might also like