Professional Documents
Culture Documents
አቶ ሙሉቀን አየሁ
የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ኮሚሽነር
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
ማውጫ
መመሪያ 1. የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች
የምልመላና መረጣ መመሪያ...........................................................................................................17
መግቢያ፣.....................................................................................................................................18
ክፍል 1. ጠቅላላ፣.......................................................................................................................19
1.2. ትርጓሜ፣.........................................................................................................................19
i
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ii
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
4.10. የሥራ መደብ ሲታጠፍ ወይም መ/ቤት ሲዘጋ የሚደረግ የሠራተኛ ድልድል...............72
ክፍል 5. ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች፣.................................................................................................73
መግቢያ፡..........................................................................................................................................88
ክፍል 1. ጠቅላላ፡........................................................................................................................89
1.2. ትርጓሜ፡..........................................................................................................................89
3.3. በተከታታይ ሶስት ዓመትና ከስድስት ዓመት በታች ያገለገሉ ተሿሚዎች አመዳደብና
ደመወዝ አከፋፈል፡......................................................................................................................96
3.5. በተከታታይ 10 ዓመትና በላይ በሹመት ያገለገሉ አመራሮች አመዳደብና ክፍያ አፈፃፀም
በተመለከተ ፣..............................................................................................................................99
መግቢያ፡.......................................................................................................................................102
ክፍል 1. ጠቅላላ፡.....................................................................................................................102
1.2. ትርጓሜ፡............................................................................................................................103
ክፍል 3. ልዩ ልዩ ጉዳዮች፡.....................................................................................................106
መግቢያ፡.......................................................................................................................................109
ክፍል 1. ጠቅላላ......................................................................................................................109
iv
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
1.2. ትርጓሜ.............................................................................................................................109
ክፍል 3. ልዩ ልዩ ጉዳዮች......................................................................................................116
መግቢያ........................................................................................................................................118
ዓላማ........................................................................................................................................118
ክፍል 1. ጠቅላላ......................................................................................................................119
1.2. ትርጓሜ.........................................................................................................................119
ክፍል 6. ልዩ ልዩ ጉዳዮች......................................................................................................132
መግቢያ........................................................................................................................................139
ክፍል 1. ጠቅላላ......................................................................................................................140
1.2. ትርጓሜ.........................................................................................................................140
ክፍል 5. ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች.................................................................................................147
æ9u=Ám....................................................................................................................................152
1.2. hCGT@........................................................................................................................152
ክፍል 2. ¯STm.......................................................................................................................153
ክፍል 3. ¾fiø~ ኃብት ›4†4PC †9v^hS በአንድ Tbh6 5ThTøS ¾†k£Ò ¾›t^C
WC¯hm 153
ክፍል 4. uFST uø£4 P£9 u†ØØæ~ ’ÖS ¾fiø~ ኃብት አስተዳደር ቡድን ø~4T
¾T˛hTø’~ W^ዎkm................................................................................................................154
ክፍል 5. በ†ÖQT˛ æ/u?ek ø~fiT የT˛æPw ¾fiø~ ኃብት አስተዳደር ሰራተኛ ›ThV’h
¾T˛hTø’~ ተግባራት m.............................................................................................................155
ክፍል 6. በ ¾P£9ø~ u†ØØæ~ ¾’ÖS ¾fiø~ ኃብት አስተዳደር ቡድን ›ThV’h ¾T˛hTø’~
ተግባራት m 156
ክፍል 14. †ÖQT˛ æ/u?ek ø~4T uT˛æPw የሰው ኃብት አስተዳደር ሰራተኛ ›ThV’h
vii
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
mGb!Ã.......................................................................................................................................165
ክፍል 1. -Q§§.........................................................................................................................166
1.3. TRÙ».........................................................................................................................166
2.1. x@C.xY.Ũ!¼x@DS yS‰ ߬ãC CGR mçn#N bmqbL tGƉDE XRM© mWsD
170
2.6. প mS9|J r2t9k bir h2k hይŨ˛/h2IM 9mr)ይ6 t929tW b2M h2G
P992äk /SA˛SSúSM~ ¥Ir9.......................................................................................172
viii
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
3.4. h2k.h ይ.Ũ˛ b9¥9W WMT ÃMÆ9WG পh2IM Iœ¥S r2t9k t9ÆCG
)1@CJ....................................................................................................................................176
5.1. QTC.............................................................................................................................179
5.2. I6I6..........................................................................................................................179
5.3. /I2J...........................................................................................................................179
5.4. GWWC.......................................................................................................................180
ix
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
መግቢያ........................................................................................................................................184
ክፍል 1. ጠቅላላ......................................................................................................................184
1.2. ትርጓሜ.........................................................................................................................184
ክፍል 7. ልዩ ልዩ ጉዳዮች......................................................................................................192
መግቢያ........................................................................................................................................194
ክፍል 1. ጠቅላላ......................................................................................................................194
1.2. ትርጉም.........................................................................................................................194
3.1. ምደባ.............................................................................................................................202
3.4. ተጠያቂነት........................................................................................................................206
3.5. ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች........................................................................................................206
መመሪያ 11. በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የቀበሌ ስራ አስኪያጆች የዝውውር አፈጻጸም
መመሪያ 209
መግቢያ........................................................................................................................................210
ክፍል 1. ጠቅላላ......................................................................................................................210
3.1. የወረዳው የሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ዋና ጽ/ቤት የስራ ድርሻ..................218
መመሪያ 12. በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የአካል ጉዳተኞች የሥራ ስምሪት መመሪያ፣
221
xii
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
መግቢያ........................................................................................................................................222
1.2. ትርጐሜ........................................................................................................................222
ክፍል 4. ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች.................................................................................................226
æ9u=Ám....................................................................................................................................229
ክፍል 1. ÖpSS........................................................................................................................229
1.2. hCGT@m.....................................................................................................................229
xiii
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
2.1.3. pTር..........................................................................................................................231
2.1.4. ዝውውር....................................................................................................................232
ክፍል 3. 6¿ 6¿ 9SÒÑ@bk...............................................................................................234
መግቢያ........................................................................................................................................237
1.2. ትርጓሜ፣......................................................................................................................238
ክፍል 3. ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች.................................................................................................241
መመሪያ 15. የተሸሻለው የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያዎች አሰጣጥና
አጠቃቀም መመሪያ......................................................................................................................242
መግቢያ........................................................................................................................................243
ክፍል 1. ጠቅላላ......................................................................................................................243
1.2. ትርጓሜ.........................................................................................................................243
ክፍል 4. ልዩ ልዩ ጉዳዮች......................................................................................................251
xv
አባሪዎች
አባሪ 1 የፈተና ዝግጅትና አሰጣጥ፣...............................................................................................76
xv
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
xvi
xvi
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
ሰኔ 2013 ዓ.ም
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ባህር ዳር፣ ኢትዮጵያ
17
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
መግቢያ፣
ስለሆነም ሲቪል ሰርቫንቱን በተገቢው መንገድ በመጠቀም የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚሻ
በመሆኑ የስምሪት አፈፃፀሙ የሜሪት ስርአትን የተከተለ ፣ ግልፅ የሆነ አሰራርን መሠረት ያደረገ
ይሆን ዘንድ የምልመላና መረጣ አፈፃፀም መመሪያ ወጥቶ ሲተገበር ቆይቷል ።
ሆኖም ከዚህ በፊት በ 2010 ዓ/ም ተሻሽሎ የወጣው የአፈጻፀም መመሪያ የነጥብ ስራ ምዘና ዘዴ ጥናት
ተግባራዊ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ መመሪያው ከጥናቱ ጋር የተዛመዱ እንዲሆን ለማድረግ
፣ የመንግስት ሰራተኛው በመመሪያው ላይ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ፤ ወቅታዊ
ነባራዊ ሁኔታውን ያማከለ እንዲሆን ማድረግ በማስፈለጉ ይህ የተሻሻለው የምልመላና መረጣ መመሪያ
የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በተሻሻለው የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ
ቁጥር 253/2 ዐ 1 ዐ አንቀጽ 96 ንዑስ አንቀጽ 2 በተሰጠው መመሪያ የማውጣት ስልጣን መሠረት
እንዲሻሻል ተደርጓል ።
18
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
• ከነጥብ የስራ ምዘናና ደረጃ አወሳሰን ጥናት ጋር የተዛመደ የመመሪያ ማሻሻያ ማድረግ
በማስፈለጉ ፡
• ስራ ላይ ያለው የምልመላና መረጣ መመሪያ ያሉበትን ክፍተቶች ማስተካከል አስፈላጊ
ሆኖ ተገኝቷል።
ክፍል 1. ጠቅላላ፣
1.1. አጭር ርዕስ፣
1.2. ትርጓሜ፣
1.2.1. “የመንግስት ሠራተኛ” ማለት በመንግስት መ/ቤት ውስጥ በቋሚነት ተቀጥሮ የሚሠራና
፣ በጊዜያዊ ሠራተኞች ቅጥር አፈጻጸም መመሪያ መሰረት ተቀጥሮ የሚሰራ ሰው ነው።
1.2.2. “ኮሚሽን” ማለት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ነው፣
1.2.3. “የመንግስት መ/ቤት” ማለት ራሱን ችሎ በአዋጅ ወይም በደንብ የተቋቋመና ሙሉ
በሙሉ ወይም በከፊል በመንግስት በጀት የሚተዳደር መስሪያ ቤት ነው፣
1.2.4. “የሰው ኃብት አስተደደር ዳይሬክተር/ ቡድን መሪ” ማለት በእያንዳንዱ መ/ቤት ውስጥ ወይም
በአንድ የጋራ ማዕከል ከመነሻ እስከ መድረሻ የሰው ኃብት አስተዳደር ተግባራትን
የሚያከናውኑ የሰው ኃብት አስተዳደር ባለሙያዎችን የሚመራ/የሚያስተባብር ነው፣
1.2.5. “የሰው ኃብት አስተዳደር ባለሙያ ወይም ባለሙያዎች” ማለት እንደ አስፈላጊነቱ በእያንዳንዱ
መስሪያ ቤት ውስጥ ወይም በአንድ የጋራ ማዕከል ተደራጅተው የሰው ኃብት አስተዳር
ሥራዎችን ከመነሻ እስከ መድረሻ የሚያከናውኑ ባለሙያዎች ስብስብ ወይም አንድ
ባለሙያ ነው፣
1.2.6. “ዳይሬክቶሬት” ማለት በነጥብ የሥራ ምዘናና ደረጃ አወሣሰን ዘዴ በክልል ደረጃ ባሉ ተቋማት
ላይ ሥራዎችን ከመነሻ እስከ መድረሻ የሚያከናውኑ ባለሙያዎች ስብስብ
19
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
20
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
1.2.14. “ምልመላ” ማለት በአንድ መሥሪያ ቤት ውስጥ ባለ ወይም ወደፊት ሊኖር በሚችል
ክፍት የሥራ መደብ ላይ ሠራተኛ በቅጥር፣ በዝውውር፣ በደረጃ ዕድገት ለመመደብ ብቃት
ያላቸው ተወዳዳሪዎችን ለይቶ ማወቅና ለውድድር የመጋበዝ ሂደት ነው፣
1.2.15. “መረጣ” ማለት በአንድ መሥሪያ ቤት ውስጥ ባለ ክፍት የሥራ መደብ ላይ ብቃት ያላቸው
ሆነው በቅጥር፣ በዝውውር፣ በደረጃ ዕድገት ለመመደብ ተወዳዳሪዎችን አወዳድሮ የመለየት
ሂደት ነው፣
1.2.16. “ዝውውር” ማለት አንድን ሠራተኛ ከአንድ የሥራ መደብ ወደ ሌላ የሥራ መደብ አዛውሮ
መመደብ ነው፣
1.2.17. “የውስጥ ዝውውር” ማለት በአንድ መ/ቤት አደረጃጀት ውስጥ አንድን የመንግሥት ሠራተኛ
ከአንድ የሥራ መደብ ወደ ሌላ የሥራ መደብ አዛውሮ መመደብ ነው፣
1.2.18. “የውጭ ዝውውር” ማለት አንድን የመንግሥት ሠራተኛ ከአንድ የሥራ መደብ ወደ ሌላ
የሥራ መደብ በየትኛውም የአስተዳደር እርከን ከአንድ መ/ቤት ወደ ሌላ መ/ቤት አዛውሮ
መመደብ ነው፣
1.2.19. “ቅድሚያ በመስጠት የሚፈጸም ዝውውር” ማለት አንድ ሠራተኛ በመንግስት ሥራ ምክንያት
ከትዳር በመነጣጠል፣ በህመም፣ በጋብቻና በአካል ጉዳት ዝውውር ሲጠየቅ ከሌሎች
ዝውውር ፈላጊዎች ቅድሚያ በመስጠት አዛውሮ ማሠራት ነው።
1.2.20. “በህመም ምክንያት የሚደረግ ምደባ” ማለት ከመንግስት ሪፈራል ሆስፒታሎች የህክምና
ቦርድ ማስረጃ የሚያቀርቡ ሠራተኞችን በየደረጃው በሚገኝ የሲቪል ሰርቪስ መ/ቤት በኩል
የተሰጣቸውን ምክረ ሀሳብ መነሻ በማድረግ ተስማሚ ወደ ሆነ ቦታ አዛውሮ መመደብ
ነው።
1.2.21. “በደህንነት ስጋት የሚደረግ ምደባ ማለት” በህይወት ለመኖር የደህንነት ስጋት ምክንያት
ወይም የህግ ከለላ የሚያስፈልጋቸውን ሠራተኞች በየደረጃው በሚገኝ የሲቪል ሰርቪስ
መ/ቤት በኩል የተሰጣቸውን ማረጋገጫ መነሻ በማድረግ ተስማሚ ወደ ሆነ ቦታ
አዛውሮ መመደብ ነው።
1.2.22. “በክብር የተመለሰ “ ማለት ከሀገር መከላከያ ሰራዊትነት በክብር የተመለሰ ስለመሆኑ ከሀገር
መከላከያ ተቋም ማስረጃ የሚያቀርብ የሰራዊት አባል ነው።
1.2.23. “የደረጃ ዕድገት” ማለት አንድን የመንግስት ሠራተኛ ከያዘው የሥራ ደረጃና ደመወዝ ከፍ
ወዳለ የሥራ ደረጃ ወይም ደረጃና ደመወዝ ማሣደግ ነው።
21
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
1.2.24. “ድልድል” ማለት አንድ የመንግሥት መ/ቤት በከፊል/ሙሉ በሙሉ የአደረጃጀት ለውጥ
በሚያደርግበት ጊዜ በሚወጣ የማስፈፀሚያ መመሪያ ላይ በተቀመጡ የማወዳደሪያ
መስፈርቶች መሠረት የመ/ቤቱን ሠራተኞች በተፈቀዱ የሥራ መደቦች ላይ አወዳድሮ
መመደብ /መደልደል ነው።
1.2.25. “ምደባ” ማለት ከላይ በንኡስ አንቀጽ 1.2.24 በተገለጸው መሰረት በሚደረግ ድልድል ምደባ
የማያገኙ ሰራተኞች፡ መ/ቤት ሲዘጋ እንዲዘጋ የተደረገው መ/ቤት ሰራተኞች፡ የስራ
መደብ ሲታጠፍ በታጠፈው ስራ መደብ ላይ የሚሰሩ ሰራተኞች፡ ከሃላፊነት የሚነሱ
ተሸሚዎች፡ ትምህርታቸውን አጠናቀው የሚመለሱ ሰራተኞችና በተለያየ ምክንያት
ይዘውት የነበረውን የስራ መደብ የሚለቁ ሰራተኞች ሲኖሩ ክፍት የስራ መደብ
በማፈላለግ ምደባ የመስጠት ሂደት ነው።
1.2.26. "አካል-ጉዳተኛ” ማለት ለዚህ መመሪያ አፈጻጸም በደረሰበት የአካል፣የአእምሮ ወይም የስሜት
ሕዋሣት ጉዳትን ተከትሎ በሚመጣ የኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ መድሎ ሣቢያ በሥራ
ስምሪት የእኩል ዕድል ተጠቃሚ ያልሆነ ሰው ሲሆን አንድ ሰው የአካል ጉዳተኛ
ተደርጐ የሚወሰደው ሙሉ በሙሉ አይነ ስውር ወይም ሙሉ በሙሉ መስማት
የተሣነው ወይም በተጨማሪ ድጋፍ የሚንቀሣቀስ ወይም በተጨማሪ ድጋፍ
ባይንቀሳቀስም በግልጽ በሚታይ ሁኔታ በተፈጥሮ ወይም በሰው ሰራሽ አደጋ ምክንያት
በአጋጠመው ጉዳት የተነሳ የአንቅስቃሴ ችግር ያለበት ሰው ነው።
1.2.27. “የነጥብ የስራ ምዘና” ማለት ሥራዎችን ለመመዘን የሚያስችሉ መስፈርቶችን በመጠቀም
ሥራዎችን መዝኖ በሚያገኙት አጠቃላይ ነጥብ መሠረት በደረጃ የማስቀመጥ ዘዴ ነው።
1.2.28. በዚህ መመሪያ በወንድ ፆታ የተገለፀው ሁሉ ሴትንም ይጨምራል።
22
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
23
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
የትምህርት ደረጃ መነሻ ደመወዝ ጋር አቻ የሆነ ክፍት የሥራ መደብ ከተገኘ ሌሎች
ስምሪቶች ከመፈፀማቸው በፊት እንዲመደቡ ማድረግ፣
1.3.8. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 1.3.7 የተጠቀሱት ከተስተናገዱ በኋላ ያለትምህርት ዝግጅታቸው
ተመድበው የሚገኙ ሠራተኞች ትምህርት ዝግጅታቸው የሚጋብዛቸው ከሆነና ከያዙት
የሥራ ደረጃ ጋር አቻና ተፈላጊ ችሎታውን የሚያሟሉት ክፍት የሥራ መደብ ከተገኘ
ሌሎች ስምሪቶች ከመካሄዳቸው በፊት በቋሚነት እንዲመደቡ ማድረግ ።ይህም ሆኖ
የትምህርት ዝግጅታቸው ተጋብዞ በስራ ልምድ የማያሟሉት ከሆነ በጊዚያዊነት
እንዲመደቡ ማድረግ፣ ያለትምህርት ዝግጅታቸው ተመድበው የሚገኙ ሠራተኞች
የሚያሟሉት ክፍት የሥራ መደብ ከጠፋ የያዙትን ደመወዝ እንደያዙ አንድ ደረጃ ከፍ
ወይም ዝቅ አድርጐ ትምህርት ዝግጅታቸው ወደ ሚገኝበት የሥራ መደብ በጊዚያዊነት
እንዲመደቡ ማድረግ፣
1.3.9. ከላይ ከንዑስ አንቀጽ 1.3.5 — 1.3.8 በተገለጸው መሠረት የሚመደቡ ሠራተኞች ቁጥር
ከአንድ በላይ ሆኖ ከተገኘ እንደቅደም ተከተላቸው ምደባው የሚፈፀመው ማስታወቂያ
ወጥቶ በውስጥ ዝውውር መስፈርቶች አግባብ በውድድር ሆኖ በክልል ደረጃ መ/ቤቱ በፑል
የታቀፈ ከሆነ በፑል መ/ቤቶች፣ በፑል ያልታቀፈ ከሆነ በራሱ መ/ቤት፣ በዞን እና
በሬጆፖሊታን ከተሞች፣ በዞን እና በሬጆፖሊታን ከተሞች ደረጃ በሚገኙ ሁሉም መ/ቤቶች
እንዲሁም በወረዳ፣ በወረዳ ደረጃ በሚገኙ በሁሉም መ/ቤቶች በአነስተኛና መካከለኛ
ከተማ አስተዳደር ደግሞ በአነስተኛና መካከለኛ ከተማ አስተዳደር ደረጃ በሚገኙ በሁሉም
መ/ቤቶች፣ በክፍለ ከተማ በክፍለ ከተማ ደረጃ በሚገኙ ሁሉም መ/ቤቶች፣ በቀበሌ ደረጃ
ደግሞ በሁሉም ቀበሌዎች ሠራተኞች ተወዳድረው እንዲመደቡ ይደረጋል።
1.3.10. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 1.3.9 የተጠቀሰው ቢኖርም አንድ ሠራተኛ እየሠራ ባለበት መ/ቤት
ሊመደብበት የሚችል ክፍት የሥራ መደብ መኖሩ እስከተረጋገጠ ድረስ በመ/ቤቱ ውስጥ
ያሉ ተመሣሣይ ምደባ ያላገኙ ሠራተኞች ካሉ በመ/ቤቱ ውስጥ ያሉት ብቻ በውስጥ
ዝውውር ማወዳደሪያ መስፈርት መሠረት ተወዳድረው በቅድሚያ እንዲመደቡ የተደረገ
መሆኑን ማረጋገጥና በቅድሟያ እንዲመደቡ ይደረጋል።
24
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
2.1.1. በክፍት የሥራ መደቦች ላይ ሠራተኛ ለመቅጠር ሲፈለግ ግልፅ የቅጥር ማስታወቂያ
በማውጣት እጩ ተወዳዳሪዎችን መጋበዝ ያስፈልጋል፣
2.1.2. መስሪያ ቤቶች የቅጥር ማስታወቂያ ሲያወጡ በማስታወቂያው ላይ የፈተና መለያ ዘዴዎችንና
የፈተናውን ቀን ማስታወቂያው ላይ መግለፅ አለባቸው፣
2.1.3. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 2.1.1 ላይ የተመለከተው ቢኖርም መስሪያ ቤቶች በስልጠና
መመሪያ በተገለፀው መሠረት አስቀድመው በዕቅድ ይዘው በቅድመ ስራ ስልጠና
የሚያሰለጥኗቸውን ሰልጣኞች ስልጠናቸውን እንዳጠናቀቁ ያለ ማስታወቂያ በቀጥታ ቅጥር
የሚፈፀምላቸው ይሆናል።
2.1.4. መ/ቤቶች የሚያወጧቸውን የቅጥር ማስታወቂያዎች በህዝብ አደባባዮችና ሠፊ ህዝብ
ይንቀሣቀስባቸዋል ተብለው በሚገመቱ ሌሎች ቦታዎች በመለጠፍ አመልካቾችን መጋበዝ
ይኖርባቸዋል።
2.1.5. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 2.1.4 ላይ የተመለከተው ቢኖርም መ/ቤቶች የቅጥር
ማስታወቂያዎችን በጋዜጦች ወይም በኤሌክትሮኒክስ መገናኛ ብዙሃን እንዲወጡ ማድረግ
ይችላሉ። ሆኖም አይገደዱም።
2.1.6. የክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ ይዘት በዚህ መመሪያ አባሪ ሁለት ላይ ተመላክቷል።
2.2.1. የቅጥር ማስታወቂያ በአየር ላይ ተለጥፎ የሚቆየው ለሰባት ተከታታይ የሥራ ቀናት ብቻ
ይሆናል፣
2.2.2. ማስታወቂያው የወጣበት ቀን አንድ ተብሎ የሚቆጠረው አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ
ሲሆን በማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ አየር ላይ የሚውለውም በፕሮቶኮል መዝገብ ወጭ
በሆነበት ቀን ይሆናል።
2.2.3. ማስታወቂያው ከተለጠፈበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ ምዝገባ ይካሄዳል፤ ተወዳዳሪዎች በአካል
በመቅረብ፣ በፋክስ መልዕክት፣ ማስረጃ አስይዞ ሰው በመላክ መመዝገብ
25
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
26
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
2.4.1. የመ/መስሪያ ቤቶች ሠራተኛ ለመቅጠር የተለያየ መጠሪያ ላላቸው የሥራ መደቦች
ማስታወቂያ ሲያወጡ፣ ለአንድ ስራ መደብ የተመዝጋቢዎች ቁጥር ከሰላሳ የማይበልጥ ከሆነ
በቀጥታ ለፈተና እንዲቀርቡ ያደርጋሉ፤ ቁጥራቸው ከሰላሳ በላይ ሲሆን ለፈተና የሚቀርቡ
ሰላሳ አመልካቾች በዕጣ ተለይተው ለፈተና እንዲቀርቡ ይደረጋል፤ ቁጥራቸው ከአንድ
በላይ ለሆኑ አንድ ዓይነት መጠሪያ ላላቸው የሥራ መደቦች ለእያንዳንዳቸው ተጨማሪ
አስር አስር አመልካቾች በእጣ ተለይተው ወይም የተወዳዳሪዎች ቁጥር ከሚፈለገው በታች
ከሆነ በቀጥታ ያለእጣ ለፈተና እንዲቀርቡ ይደረጋል።
2.4.2. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 2.4.1 የተገለፀው ቢኖርም በማንኛውም የትምህርት ደረጃ በወጣ
የተግባር ፈተና በሚያስፈልጋቸው የተለያየ መጠሪያ ያላቸው ሥራ መደቦች ላይ ለአንድ
የሥራ መደብ እስከ 10 እና ከዚያ በታች አመልካቾች ሲኖሩ በቀጥታ ለፈተና እንዲቀርቡ
ይደረጋል። ቁጥራቸው ከ 10 በላይ ሲሆን ለፈተና የሚቀርቡ 10 አመልካቾች በዕጣ
ተለይተው ለፈተና እንዲቀርቡ ይደረጋል፤ ቁጥራቸው ከአንድ በላይ ለሆኑ አንድ ዓይነት
መጠሪያ ላላቸው የሥራ መደቦች ለእያንዳንዱ ተጨማሪ የሥራ መደብ አምስት አምስት
አመልካቾች በእጣ ተለይተው ወይም የተወዳዳሪዎች ቁጥር ከሚፈለገው በታች ከሆነ
በቀጥታ ያለእጣ ለፈተና እንዲቀርቡ ይደረጋል።
2.4.3. አካል ጉዳተኛ የሆኑ እና ከመከላከያ ሠራዊት፣ ከፖሊስ ሠራዊት አባልነት እና
ከሚሊሻነት በክብር የተመለሱና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ በቀጥታ ያለ ዕጣ
ይሣተፋሉ፤ ሆኖም ያለ ዕጣ ለፈተና የሚቀርቡት ለአንድ ጊዜ አዲስ ቅጥር ለመፈፀም ብቻ
ይሆናል።
2.4.4. ከላይ በንኡስ አንቀፅ 2.4.3 የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ በአንድ በወጣ የቅጥር ማስታወቂያ
የተመዘገቡ በክብር ተመላሾች ለፈተና እንዲቀርቡ ከተቀመጠው ቁጥር በላይ ከሆነ ለፈተና
ከሚቀርቡት ውስጥ 50% ለክብር ተመላሾች የሚሰጥ ሆኖ ቁጥራቸው ከተሰጣቸው ኮታ
በላይ ከሆነ እርስ በርሳቸው እጣ እንዲያወጡ በማድረግ ለፈተና እንዲቀርቡ ይደረጋል።
እንዲሁም 50% ደግሞ ለሌሎች ተወዳዳሪዎች የሚተው ይሆናል ።
2.4.5. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 2.4.4 የተጠቀሰው ቢኖርም በመንግስት ሠራተኛነት ተቀጥረው እያገለገሉ
ያሉ ወይም ሲያገለግሉ ቆይተው ስራቸውን የለቀቁ አካል ጉዳተኞችም ሆነ
27
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
2.5.1. ለአንድ ክፍት የሥራ መደብ የቀረቡ እጩ ተወዳዳሪዎች ምርጫ የሚፈፀመው በሰው
ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ቡድን ውስጥ በሚመደቡ ባለሙያዎች አማካኝነት ይሆናል፤
ቅጥሩም የሚፀድቀው በሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ቡድን ወይም የማስተባበሩን
ሥራ ደርቦ እንዲሠራ በተወከለ ባለሙያ ይሆናል። ሆኖም ቅጥሩን የሚያፀድቀው
በመረጣው ሂደት መሣተፍ የለበትም፣
2.5.2. በሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ ቡድን ውስጥ የተመደቡት ባለሙያዎች ቁጥር ሁለት
እና በላይ ከሆነ ዳይሬክተር/ቡድን መሪው ወይም የማስተባበሩን ሥራ ደርቦ እንዲሠራ
የተወከለ ፈፃሚ አንድ ባለሙያ በሰብሣቢነት ይመድባል፤ ዳይሬክተር/ቡድን መሪ የሌለው
አንድ ባለሙያ ብቻ ከሆነ ግን ሰብሣቢ ሳያስፈልገው ሥራውን ይሠራል ሆኖም ቅጥሩን
የሚያፀድቀው የመ/ቤቱ ኃላፊ/ምክትል ኃላፊ/ተወካይ ይሆናል፣
2.5.3. በተለያዩ አስገዳጅ ምክንያቶች ዳይሬክተር/ቡድን መሪ/ተተኪ በምልመላና መረጣ ሂደት
ከተሣተፈ ቅጥሩን የሚያፀድቀው የመ/ቤቱ ኃላፊ/ምክትል ኃላፊ/ተወካይይሆናል። መ/ቤቱ
በፑል የሚመራ ከሆነ ፑሉን በሚያስተባብረው መ/ቤት ኃላፊ/ም/ኃላፊ/ተወካይ ይሆናል።
28
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
29
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
30
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
አሸናፊውን ለይቶ ካሳወቀ መቀበል ይገባል። በአንድ ወረዳ ወይም ዞን የሚገኝ የቴክኒክና
ሙያ ኮሌጅ ወይም መ/ትራንስፖርት ላይ የሚሰሩ ሠራተኞች በተደጋጋሚ ፈተና
እንዲያዘጋጁ የሚጋበዙ ከሆነና የፈተና አሰጣጡ ላይ ጥያቄ የሚያስነሳ ከሆነ ከሌላ አካባቢ
ፈተኝ በመጋበዝ ፈተናውን መስጠት ይቻላል።
2.7.2.1. በአንድ የሥራ መደብ ላይ ለመወዳደር ከሚጠየቁ ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታዎች በላይ ማስረጃ
ይዘው የሚቀርቡ ቢኖሩ ማስረጃው ተጨማሪ ነጥብ አያስገኝላቸውም ወይም የትምህርት
ደረጃና የአገልግሎት ዘመን የሚጠቅሙት ለመመዝገቢያነት ብቻ ነው፣
2.7.2.2. በሴቶች ልዩ ድጋፍ እርምጃ መመሪያ ላይ ለሴቶች የተሰጡ ልዩ ድጋፎች እንደተጠበቁ
ሆኖ ሴቶች ከወንዶች ጋርም ሆነ ሴቶች ከሴቶች ጋር ሲወዳደሩ ከፈተና በፊት
ለኃላፊነት ቦታዎች 5 ነጥብ ለሌሎች የሥራ መደቦች 3 ነጥብ ይሰጣል፤ ይህም ሆኖ
ሴቶች ከወንዶች ጋር ተወዳድረው እኩል ከመጡ ቅድሚያ ለሴቷ ይሰጣል፣
2.7.2.3. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 2.7.2.2 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ ሁለት ተመሣሣይ ፆታ ያላቸው
ተወዳዳሪዎች እኩል ነጥብ ካመጡ ለሥራ መደቡ አግባብ ያለው የትምህርት ዝግጅት ሆኖ
ከፍ ያለ የትምህርት ደረጃ ላለው ቅድሚያ ይሰጣል። ይህም ሆኖ እኩል ከመጡ ሥራ ልምድ
ይዘው የተመዘገቡ ከሆነ ለሥራ መደቡ አግባብ ያለው የሥራ ልምድ ብልጫ ላለው
ቅድሚያ ይሰጣል፤ ይህም ሆኖ እኩል ከመጡ አግባብ ያለውና የሌለው ሣይባል በቁጥር
የአገልግሎት ብልጫ ላለው ቅድሚያ ይሰጣል፤ ይህም ሆኖ እኩል ከመጡ አሸናፊው በዕጣ
ይለያል፤ከፍ ያለ የትምህርት ደረጃም ሆነ የስራ ልምድ በማስረጃነት የሚያዘው በምዝገባ
ወቅት በቀረበ ማስረጃ ላይ ብቻ ተመስርቶ ይሆናል
።
2.7.2.4. በአባሪ ሦስት የተገለፁት የሥራ መደቦች የተግባር ፈተና የሚያስፈልጋቸው መሆኑ
እንደተጠበቀ ሆኖ ከእነዚህ በተጨማሪ የተግባር ፈተና ያስፈልጋቸዋል ተብለው
የሚታመንባቸው የሥራ መደቦች በሚያጋጥሙበት ጊዜ የተግባር ፈተና
የሚያስፈልጋቸው መሆኑን የመለየት ወይም የመወሠን ኃላፊነት የቅጥር ጥያቄውን
ያቀረበው አካል እና የሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ ቡድን በጋራ ይሆናል፣
2.7.2.5. የተግባርና የፀሑፍ ወይም የፅሑፍ ውጤቱ ለቀጣይ ውድድር የሚጋብዘው የጽሑፍ ፈተና
ብቻ ለሚጠይቅ 40 እና ከዚያ በላይ ነጥብ ካስመዘገበ፣ የጽሑፍና የተግባር
31
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
32
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
33
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
2.7.2.13. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 2.7.2.12 የተጠቀሰው ቢኖርም የቅጥር ማስታወቂያ ከመውጣቱ አንድ
ወር በፊት በእጁ ህጋዊ መልቀቂያ የያዘ ማንኛውም የመንግስት ሠራተኛ እየሠራ
ባለበት መ/ቤት ውስጥ ተመልሶ በቅጥር አግባብ ተወዳድሮ ሊቀጠር ይችላል፣
2.7.2.14. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 2.7.2.11 የተገለፀው ቢኖርም ከፍተኛ የትምህርት ደረጃ ይዘው
ከትምህርት ደረጃቸው መነሻ ደመወዝ በታች የተቀጠሩ ሠራተኞች የሙከራ ቅጥራቸውን
ሳያጠናቅቁ ለቀው ወደ ሌላ መ/ቤት የያዙት የትምህርት ደረጃ መነሻ ደመወዝ እና ከዚያ
በላይ የሚያስከፍል የሥራ መደብ ላይ ሊቀጠሩ ይችላሉ፣
2.7.2.15. በመንግስት ስፖንሰር አድራጊነት የረዥም ጊዜ የትምህርት ዕድል አግኝተው እየተማሩ
ያሉ እንዲሁም በአንድ የመንግስት መ/ቤት በቋሚነት የተቀጠረ የመንግስት ሰራተኛ
በተመሳሳይ ጊዜ በሌላ የመንግስት መ/ቤት በቋሚነት በመቀጠር በሁለት የመ/ቤቶች ላይ
መስራት አይችልም።
2.7.2.16. የዕድገት መሰላል ተጠቃሚ በሚያደርጉ የስራ መደቦች ላይ ባለሙያዎች /ሰራተኞች ሲቀጠሩ
በየሙያ ተዋረዳቸው ደረጃና ደመወዝ ላይ ቅጥር የሚፈፀም ይሆናል።
2.7.2.17. የጤና ባለሙያዎች ቅጥር በሚፍጸምበት ጊዜም የጤና ባለሙያው በመንግስታዊም ሆነ
መንግስታዊ ባልሆኑ ተቋም አገልግሎ ወደ መንግስታዊ መስሪያ ቤት ወይም ጤና
ተቋም ሲገባ በሰለጠነበት የጤና ሙያ አገልግሎት ስለመስጠቱና የመንግስት ግብር
ስለመክፈሉ ማረጋገጫ ካቀረበ አገልግሎቱ ተይዞ ባለው ክፍት የስራ መደብ ላይ
ሊቀጠር ይችላል።
2.7.2.18. በተለያዩ ምክንያቶች ደርሶበት ከነበረው ከፍ ያለ የሥራ ደረጃ ሥራ ለቆ እንደገና በአንድ
ዓመት ጊዜ ውስጥ ዝቅ ብሎ በሌላ የመንግስት መሠሪያ ቤት ሥራ የተቀጠረ የጤና ባለሙያ
የሙከራ ቅጥር ጊዜውን እንዳጠናቀቀ ቀድሞ ደርሶበት ወደነበረው ደረጃ ከፍ ተደርጎ
ደመወዙ እንዲስተካከል ይደረጋል።
2.7.2.19. የቀበሌ ልማት ባለሙያዎች የስራ መደብ ክፍት ሆኖ ለስምሪት የሚፈለግ ከሆነ በስራ መደቡ
ተዋረድ ስምሪት እንዲፈጸም ይደረጋል።
2.8.1. መ/ቤቶች አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኙት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ዲፕሎማና ከዚያ በላይ
የትምህርት ደረጃ ያላቸው እና ምንም የስራ ልምድ የሌላቸውን አመልካቾችን በታሳቢ
ቀጥሮ ማሰራት ይቻላል። ሆኖም ዲፕሎማ የትምህርት ደረጃ ያላቸውን አመልካቾችን
34
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
35
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
2.10.1. የሰው ኃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ ቡድን ምዝገባው በተጠናቀቀ በሦስት የሥራ
ቀናት ውስጥ ፤ የሥራ መደቡ ተያዥ የሚያስፈልገው ከሆነ ደግሞ በአምስት የሥራ
ቀናት የቅጥር ሂደቱን አጠናቆ ለተቀጣሪው የቅጥር ደብዳቤ በመስጠት ሥራ እንዲጀምር
ያደርጋል፤ ሆኖም ተወዳዳሪዎች በሌላ የመንግስት መስሪያ ቤት እየሠሩ ያሉ ከሆነ ግን
በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ መልቀቂያ እንዲያመጡ ይደረጋል። ይህም ሆኖ አንድ
የመንግሥት ሠራተኛ በማንኛውም ጊዜ የአንድ ወር ቅድሚያ ማስጠንቀቂያ በመስጠት
ሥራውን ሊለቅ ይችላል። ሆኖም መ/ቤቱ ሠራተኛውን በቀላሉ ሊተካው የሚችል ከሆነ
የአንድ ወሩን ጊዜ ሣይጠብቅ መልቀቂያውን ሊሰጠው ይችላል። ይሁን እንጅ ሠራተኛው
ለሥራው እጅግ አስፈላጊና በቀላሉ ለመተካት የማይቻል ሆኖ ሲገኝ የሚሰራበት መ/ቤት
ወደፊት ከሚቀጠርበት መ/ቤት ጋር በመስማማት የመልቀቂያውን ጥያቄ ከሶስት ወር
ለማይበልጥ ጊዜ ማራዘም የሚችለው ሰራተኛው ፍቃደኝነቱ ሲገልፅ
36
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
37
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
38
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
መ/ አንድ መ/ቤት ባወጣው የቅጥር ማስታወቂያ በተደረገ ውድድር አሸናፊው በሌላ የመንግስት
መ/ቤት ሲሰራ የቆየና የተወዳደረበት የሥራ መደብ ቀደም ብሎ ሲከፈለው ከቆየው ደመወዝ
ዝቅ ያለ ከሆነ የሚከፈለው የወር ደመወዝ በቅጥር ማስታወቂያው ላይ የተገለፀው ደመወዝ
ይሆናል፤ የሥራ መደቡ ደረጃ ተመሣሣይ ቢሆንም በእርከን አገኘው የነበረ ጥቅም ነው በሚል
በአዲሱ መ/ቤት እንዲከበርለት መጠየቅ አይችልም፣
ረ/ በከባድ የዲሲፕሊን ጥፋት የተከሰሰ የመንግስት ሠራተኛ በራሱ ፈቃድ ሥራውን በመልቀቁ
አገልግሎቱን አቋርጦ በሌላ በማናቸውም የክልል የመንግስት መ/ቤት ተመልሶ
39
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
40
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
ሰ/ በቋሚነት ቀጥረው እያሠሯቸው የነበሩ ሠራተኞች በሌላ መ/ቤት በመቀጠራቸው ምክንያት የግል
ማህደራቸው ወደ አዲሱ መ/ቤት እንዲተላለፍ ቀጣሪው መ/ቤት ሲጠይቅ ነባሩ መ/ቤት የሚፈልገው
ማስረጃ ካለ ኮፒውን በማስቀረት የመላክ ግዴታ አለበት፣
ሸ/ በውድድር አሸናፊ የሆኑት የማህበራዊ ዋስትና ሽፋን ተጠቃሚ በሆኑ የመንግስት ልማት
ድርጅቶች በቋሚነት ያገለገሉ ሠራተኞች የነበሩ ከሆኑ ቃለ-መኃላና የጣት አሻራ ማቅረብ
ይጠበቅባቸዋል፤ ሆኖም ማህደራቸውን ማስመጣት እስከተቻለ ድረስ የህይወት ታሪክ ፎርም
እንዲሞሉ አይገደዱም፤ ለዚህም ሠራተኞች ከመቀጠራቸው በፊት የህይወት ታሪክ ፎርም የሞሉና
ያላቸው መሆኑን መ/ቤቱ ማረጋገጥ ይኖርበታል።
መ/ በአንድ መ/ቤት ውስጥ እንደ አዲስ የሚቀጠሩ፣ ከሌላ መ/ቤት በውጭ ዝውውር፣ በምደባ፣ በደረጃ
ዕድገት በአንድ መ/ቤት ከአንድ ዳይሬክቶሬት/ቡድን ወደ ሌላ ዳይሬክቶሬት/ቡድን በውስጥ ዝውውር፣
በደረጃ ዕድገት፣ በድልድል የሚመደቡ ሠራተኞች፣
41
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
2.15.1. በሙከራ ቅጥር ወቅት ሠራተኞች ስለ ሥራው በቂ እውቀት እንዲያገኙ ተገቢው ስልጠናና
ድጋፍ በተቀጠሩበት መ/ቤት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር/ቡድን መሪ አማካይነት
ይሰጣቸዋል፤ ሥራውን በአግባቡ ስለማከናወናቸው ክትትል እየተደረገ የእቅድ
አፈፃፀማቸው ይሞላል፣
2.15.2. ሠራተኞች በሙከራ የሚቆዩበት ጊዜ ስድስት ወር ሆኖ የእቅድ አፈፃፀማቸው የሚመዘነው
በየ 3 ወሩ ይሆናል፣
2.15.3. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 2.15.2 የተገለፀው ቢኖርም ሠራተኛው በየ 3 ወሩ የሚሞላለት
የ 2 ጊዜ የእቅድ አፈፃፀም ውጤት አጥጋቢና በላይ ከሆነ ከሚሰራበት መ/ቤት በሚቀርበው
የእቅድ አፈፃፀም ውጤት መሠረት በሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ቡድን የቋሚ
ቅጥር ደብዳቤ ይሰጠዋል። ውጤቱ ከአጥጋቢ በታች ከሆነ ግን የሙከራ ጊዜው ለተጨማሪ
የሶስት ወር ሙከራ ጊዜ እንዲራዘምለት ይደረጋል።
2.15.4. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 2.15.3 የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ በዘጠኝ ወሩ በሚሞላ ሶስት የሙከራ
ጊዜ የእቅድ አፈፃፀም ውጤቱ አጥጋቢና በላይ ከሆነ ሠራተኛው ከሚሰራበት መ/ቤት
በሚቀርበው የእቅድ አፈፃፀም ውጤት መሠረት በሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ ቡድን
የቋሚነት ደብዳቤ ይሰጠዋል። ይህም ሆኖ የእቅድ አፈፃፀሙ ከአጥጋቢ በታች ከሆነ
ከአሰሪው መ/ቤት በሚቀርበው የእቅድ አፈፃፀም ውጤት መሠረት ያለ ተጨማሪ ስነ-
ስርዓት በሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ቡድን አማካኝነት እንዲሰናበት ይደረጋል።
42
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
2.15.5. ከላይ ከንዑስ አንቀጽ 2.15.2 - 2.15.4. የተገለፀው ቢኖርም በሙከራ ቅጥር ላይ የሚገኝ
ሠራተኛ የእቅድ አፈፃፀም ምዘና ውጤቱ ጊዜውን ጠብቆ ካልተሞላለት የሚመለከተው
የሥራ ኃላፊ የሚኖርበት ተጠያቂነት እንደተጠበቀ ሆኖ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ የእቅድ
አፈፃፀም እንዲሞላለት የሚደረግ ሲሆን ዘግይቶ በተሞላ የሥራ አፈፃፀም ሠራተኞችን
ማሰናበት አይቻልም፣
2.15.6. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 2.15.3 - 2.15.5 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ የሥራ አፈፃፀም
የሚሞላው አሰሪ መ/ቤት በወቅቱ ሞልቶ ለሰው ኃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ ቡድን
ማቅረብ ግዴታ ሲሆን የሰው ኃብት ሥራ አመራር ዳይሬክቶሬት/ቡድን በሙከራ ቅጥር ላይ
ያለን ሠራተኛ እቅድ አፈፃፀሙ በወቅቱ ተሞልቶ ስለመላኩ የመከታተል ግዴታና ኃላፊነት
አለበት፣
2.15.7. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 2.15.6 የተመለከተው ቢኖርም የሙከራ ጊዜያቸውን አጥጋቢ
እና በላይ በሆነ የእቅድ አፈፃፀም ውጤት ካጠናቀቁ በኋላ ደብዳቤ ሳይሰጣቸው በሌላ
መ/ቤት የሚመደቡ ሰራተኞች ቢኖሩ እንደ አዲስ የተመደቡበት ወይም የተረከባቸው
መ/ቤት ማህደራቸውን በመመርመር የቋሚነት ደብዳቤ ይሰጣቸዋል፤ ይህም በሰው ሃብት
አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ ቡድን አማካኝነት ይከናወናል።
2.15.8. የሙከራ ጊዚያቸውን አጥጋቢ እና በላይ በሆነ የእቅድ አፈፃፀም ውጤት ያጠናቀቁ ሰራተኞች
የሚሰጣቸው የቋሚነት ደብዳቤ ከተቀጠሩበት ቀን ጀምሮ ይሆናል።
3.1.1. ማንኛውም መ/ቤት በዝውውር የሚሸፈን ክፍት የሥራ መደብ ሲኖረው ማስታወቂያ
በማውጣት እጩ ተወዳዳሪዎችን መጋበዝ ይኖርበታል።
3.1.2. መ/ቤቶች የዝውውር ማስታወቂያዎችን በውስጥ የማስታወቂያ ሰሌዳዎች፣ በህዝብ አደባባዮች
በመለጠፍ አመልካቾችን መጋበዝ ይኖርባቸዋል። ሆኖም የውስጥ ዝውውር ማስታወቂያዎች
የሚለጠፉት በውስጥ የማስታወቂያ ሰሌዳ ብቻ ይሆናል።
3.1.3. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 3.1.2 ላይ የተገለፀው ቢኖርም መ/ቤቶች የውጭ ዝውውር
ማስታወቂያዎችን በጋዜጦች ወይም በኤሌክትሮኒክስ መገናኛ ብዙሃን እንዲወጡ ማድረግ
ይችላሉ። ሆኖም አይገደዱም።
43
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ሀ/ የውስጥ ዝውውር ከሆነ ማስታወቂያው ለ 2 ተከታታይ የስራ ቀናት ተለጥፎ ይቆያል። ሆኖም
ውድድሩን ያወጣው አካል ቅርንጫፍ መስሪያቤቶች ካሉት የማስታወቂያው የቆይታ ጊዜ ለ 7
ተከታታይ የስራ ቀናት ይሆናል።የሚወጡ የውስጥ ዝውውር ማስታወቂያዎችን የበታች ቅርንጫፍ
መ/ቤት ያላቸው የክልል ፣ የዞን ፣የሬጆፖሊታን ከተማ፣ የወረዳ ወይም የከተማ አስተዳደር መ/ቤቶች
የራሳቸውን አደረጃጀት መሰረት በማድረግ የሚወጡ የውስጥ ዝውውር ማስታወቂያዎችን
ለቅርንጫፎቻቸው በየደረጃው በሚገኘው የሲቪል ሰርቪስ መ/ቤት ወይም ስምሪቱን በሚፈጽመው
አካል አማካኝነት እንዲደርሳቸው ይደረጋል ። በተመሣሣይ ቅርንጫፍ
/ተጠሪ መ/ቤቶች ለእናት መ/ቤቶቻቸው የሚያወጧቸውን ማስታወቂያወች በየደረጃው በሚገኘው
የሲቪል ሰርቪስ መ/ቤት ወይም ስምሪቱን በሚፈጽመው አካል አማካኝነት እንዲደርሳቸው ይደረጋሉ
።
3.1.6. ከንዑስ ቁጥር 3.1.1 – 3.1.5 ድረስ የተገለፀውን ተግባራት በአግባቡ መፈፀሙን ስምሪቱ
እንዲፈፀምለት የጠየቀው መ/ቤት/ ዳይሬክቶሬት/ ቡድን ክትትል ማድረግ አለበት።
44
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
3.3.1. ለአንድ ክፍት የሥራ መደብ የቀረቡ እጩ ተወዳዳሪዎች ምርጫ የሚፈፀመው በዚህ መመሪያ
አንቀጽ 2.5 በተደነገገው አግባብ ይሆናል።
3.4.1. በዝውውር ጊዜ የሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ ቡድን ባለሙያ በዚህ መመሪያ ክፍል
ሁለት አንቀጽ 2.6 የተዘረዘሩት ተግባርና ኃላፊነቶች ይኖሯቸዋል።
ሐ/ የማህደር ጥራት 5%
45
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
3.5.2. ከላይ በአንቀጽ 3.5 ንዑስ አንቀጽ 3.5.1 በፊደል ተራ “ሀ” በውጤት ተኮር ማወዳደሪያ
መስፈርት መሠረት የሁለት ጊዜ የሠራተኞች የዕቅድ አፈፃፀም አማካይ ውጤት በ 0.6
ተባዝቶ የሚያዝ ሆኖ በስራ ላይ ሁነው ለሚቀጠሩት ግን የሙከራ ጊዚያቸውን
ከማጠናቀቃቸው በፊት በሌላ የመንግስት ተቋም የተሞላላቸውና የሙከራ ጊዚያቸውን
ሲያጠናቅቁ የተሞላላቸው የየሶስት ወሩ እንደ ስድስት ወር የእቅድ አፈጻጸም ውጤት
ተወስዶ የሚያዝላቸው ይሆናል። እንዲሁም በፊደል ተራ “ለ” የተገለፀው የሥራ ልምድ
የማወዳደሪያ መስፈርት አግባብ ያለው የሌለው ሳይባል የአንድ ዓመት አገልግሎት በ 0.875
ተባዝቶ የተገኘው ውጤት ይያዛል። ሆኖም የስራ አፈፃፀም ነጥብ አያያዙ በደረጃ እድገት
አፈፃፀም መመሪያ ክፍል 4 አንቀጽ 4.4.1 ከፊደል ተራ “ለ” እስከ ፊደል ተራ “ረ” ድረስ
ያሉትን አንድ በአንድ ተከትሎ ይፈጸማል። የማህደር ጥራት አያያዝ ደግሞ በአንቀጽ
4.4.2 በተመላከተው ሠንጠረዥ ከተራ ቁጥር አንድ እስከ አምስት የተደነገጉ ጉዳዮች
ተፈፃሚ ይሆናሉ። በዝውውሩ አሸናፊ የሚሆነው ሠራተኛ በአጠቃላይ ውጤት ቢያንስ
50%ና በላይ ማምጣት ይጠበቅበታል።
3.6.1. በአንድ መ/ቤት አደረጃጀት ውስጥ ከአንድ የስራ መደብ ወደሌላ የስራ መደብ ወይም ከአንድ
ዳይሬክተር/ቡድን ወደሌላ ዳይሬክተር/ቡድን ወይም ከዞን፣ከማዕከል፣ ከሬጆፖሊታን
ከተሞች ወደ ክልል፣በተመሣሣይም ከክልል ወደ ዞን፣ ማዕከል፣ ሬጆፖሊታን ከተሞች እኩል
ወደሆነ የሥራ ደረጃና ደመወዝ ዝውውር መፈጸም ይቻላል።
3.6.2. አንድን የመንግሥት ሠራተኛ በተመሣሣይ የሥራ ደረጃና ደመወዝ ከአንድ የሥራ መደብ
እኩል ደረጃ ወዳለው ተመሣሣይ የስራ ደረጃና የደመወዝ መጠን አዛውሮ መመደብ
ይቻላል። ሆኖም ዝውውር ጠያቂው ሠራተኛ ደረጃው ተመሳሳይ ሆኖ አሁን የሚከፈለው
ደመወዝ ከስራ መደቡ መነሻ ደመወዝ ከፍ ያለ ከሆነ እስከ ሦስት እርከን ያለውን የደመወዝ
ልዩነት እንደያዘ ተቀባይ መ/ቤቱ ተቀብሎ ዝውውሩን የመፈፀምና ልዩነቱንም የመክፈል
ግዴታ ይኖርበታል። ሆኖም በእርከን የተገኘን ጥቅም ካልሆነ በስተቀር አንድን ሠራተኛ
ከያዘው የሥራ ደረጃ ከፍ ወይም ዝቅ አድርጐ ዝውውር መፈፀም አይቻልም፡
46
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
3.6.3. ከላይ በንዑስ አንቀፅ 3.6.2 የተገለፀው ቢኖርም አንድ የመንግሥት መሥሪያ ቤት ኃላፊ
ለሥራው አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው አንድ የመንግሥት ሠራተኛን በዚያው በመስሪያ ቤት
ውስጥ እኩል በሆነ የሥራ ደረጃና ደመወዝ ወደ ሌላ የሥራ መደብ ወይም ክፍት የስራ
መደብ መኖሩ ተረጋግጦ የያዘውን ደመወዝ እንደያዘ እስከ አንድ ደረጃ ዝቅ ወይም ከፍ
ባለ ደረጃ ከአንድ ዳይሬክተር/ቡድን ወደ ሌላ ዳይሬክተር/ቡድንና ከአንድ የሥራ መደብ
ወደ ሌላ ሥራ መደብ በማዛወር ሊያሠራ ይችላል ። ሆኖም ግን ዝውውር የሚፈፀምለት
ሰራተኛ ለሚዛወርበት የስራ መደብ ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታውን ማሟላት ይጠበቅበታል።
ነገርግን ከዳይሬክተር/ቡድን መሪ ወደ ባለሙያ ወይም ከባለሙያ ወደ ዳይሬክተር/ቡድን
መሪ አዛውሮ ማሰራት አይቻልም።
3.6.4. የመንግሥት ሠራተኛ በጤና መታወክ ምክንያት በያዘው የሥራ መደብ ወይም ባለበት የሥራ
ቦታ ላይ ሊሠራ አለመቻሉ በመንግስት ሪፈራል/ስፔሻላይዝድ/ ሆስፒታል የህክምና
ማስረጃ ሲረጋገጥ፣
ሀ) በቅድሚያ በተመሳሳይ ደረጃ ሊመደብበት የሚችል ክፍት የሥራ መደብ ካለ በያዘው ደረጃና ደመወዝ
፣
3.6.5. ከዞን ወደ መካከለኛ ከተማ(አነስተኛ ከተማና ወረዳ) ዝውውር መፈፀም ይቻላል። ከወረዳ፣
ከአነስተኛ ከተማና ከመካከለኛ ከተማ ወደ ዞን ዝውውር መፈፀም ይቻላል። ከሬጆፖሊታን
ከተማ ወደ ክፍለ ከተማ ዝውውር መፈፀም ይቻላል። ከሳተላይት ከተሞች ወደ
ሬጆፖሊታንት እናት መ/ቤታቸው ዝውውር መፈፀም ይቻላል። ከክፍለ ከተማ ወደ
ሬጆፖሊታን ከተማ ዝውውር መፈፀም ይቻላል።
47
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ቀበሌ ተቋማት ወደ ወረዳ ጽ/ቤት ዝውውር መፈፀም ይቻላል። ከመሪ ማዘጋጃ ወደ ወረዳ
ከተማ ልማትና ቤቶች ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ፤ዞን ወይም ሬጆፖሊታን ከተማ ዝውውር
መፈፀም ይቻላል። ከሬጆፖሊታን ከተማ ወይም ከዞን ወደ መሪ ማዘጋጃ ዝውውር
መፈፀም ይቻላል። ከንዑስ ማዘጋጃና ከታዳጊ ከተማ ወደ ወረዳ ከተማ ልማትና ቤቶች
ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት እንዲሁም የወረዳ ከተማ ወዳለው መሪ ማዘጋጃ ቤት ዝውውር
መፈፀም ይቻላል።
3.6.6. በት/ቤትና በጤና ጣቢያ የሚሰሩ የሰው ሃብት አስተዳደር ሠራተኞች ሊወዳደሩ የሚችሉት
በራሳቸው ተመሣሣይ ስራ መደብና ደረጃ ወደ ወረዳ፣መካከለኛ ከተማ አስተዳደር ፣
አነስተኛ ከተማ አስተዳደሮች ወደ ክፍለ ከተማ ሲቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት ይሆናል።
3.6.7. በት/ቤትና በጤና ጣቢያ የሚሰሩ የግዥ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ሠራተኞች
ሊወዳደሩ የሚችሉት ወደ ግዥ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ቡድን ሲሆን
በሬጆፖሊታን ከተሞች ላይ ካሉ ት/ቤቶችና ጤና ጣቢያዎች ወደ ክፍለ ከተማ ገንዘብና
ኢኮኖሚ ትብብር ጽ/ቤት ፣ በወረዳ ደረጃ ካሉ ት/ቤቶችና ጤና ጣቢያዎች ወደ ወረዳ
ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ጽ/ቤት ፣ በመካከለኛ ከተማ አስተዳደር ደረጃ ወደ መካከለኛ
ከተማ አስተዳደሩ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ጽ/ቤትና አገልግሎት ጸ/ቤት ላይ ወደ
ተደራጀው የግዥ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ቡድን፣ በአነስተኛ ከተማ አስተዳደሮች ላይ
ያሉት ደግሞ ወደ አነስተኛ ከተማ አስተዳደሩ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብርር ጽ/ቤት ይሆናል።
3.6.8. በት/ቤትና በጤና ጣቢያ ላይ የሚሰሩ ሌሎች ድጋፍ ሰጭ ሠራተኞች ሊወዳደሩ የሚችሉት
በተመሣሣይ ደረጃ ሲሆን በሬጆፖሊታን ከተሞች ላይ ካሉ ት/ቤቶችና ጤና ጣቢያዎች
ወደ ሬጆፖሊታን እናት መ/ቤታቸው ፣ በወረዳ ደረጃ ካሉ ት/ቤቶችና ጤና ጣቢያዎች ወደ
ወረዳው እናት መ/ቤታቸው ፣ በመካከለኛ ከተማ አስተዳደር ደረጃ ወደ መካከለኛ ከተማ
አስተዳደሩ እናት መ/ቤታቸው፣ በአነስተኛ ከተማ አስተዳደሮች ላይ ያሉት ደግሞ ወደ
አነስተኛ ከተማ እናት መ/ቤታቸው ፤ ከት/ቤት ወደ ሌላ ት/ቤት ፣ ከጤና ጣቢያ ወደ ሌላ
ጤና ጣቢያ ዝውውር የሚፈፀመው በክፍለ ከተማ ውስጥ ብቻ ሲሆን በገጠር ወረዳና
ከሬጆፖሊታን ያሉ ከተሞች ውጭ ያሉ ከተማ አስተዳደሮች ውስጥ ያሉት ድጋፍ ሰጭ
ሰራተኞች ግን በወረዳው ውስጥ ባሉት ት/ቤትና ጤና ጣቢያ ዝውውር የሚፈፀም
ይሆናል።
48
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
3.6.9. ከላይ ከንዑስ አንቀጽ 3.6.1 እስከ 3.6.8 የተገለፀው ቢኖርም ከወረዳ ወረዳ እና ከዞን ወደ
ዞን፣ ከአንድ ከተማ አስተዳደር ወደ ሌላ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም አነስተኛና
መካከለኛ ከተማ አስተዳደሮች፣ ከወረዳ፣ ከአነስተኛና መካከለኛ ከተማ አስተዳደሮች
ወደ ክልል፣ ከሬጆፖሊታን ከተሞች ወደ ዞን፣ ከዞን ወደ ሬጆፖሊታን ከተሞች፣
ከአነስተኛና መካከለኛ ከተሞች ወደ ሬጆፖሊታን ከተሞች እንዲሁም ከወረዳ፣
ከአነስተኛና መካከለኛ ከተማ አስተዳደር፣ክፍለ ከተማ በታች ከሚገኙ ተቋማት ወደ ዞን
ወይም ሬጆፖሊታን ከተሞች በውስጥ ዝውውር አግባብ ስምሪት መፈፀም አይቻልም።
3.6.10. ከንዑስ አንቀጽ 3.6.1 እስከ 3.6.9 የተመለከተው ቢኖርም የጋራ አገልግሎት እንዲሰጡ
በተደራጁ የስራ ዘርፎች ስር የሚገኙ ሠራተኞች/ባለሙያወች ዝቅተኛ ተፈላጊ
ችሎታውን እስካሟሉ ድረስ የጋራ አገልግሎት ወደሚሰጧቸው መ/ቤቶች እንዲሁም
በተጠቃሚ መ/ቤቶች ስር የሚገኙ ሁሉም ሠራተኞች/ባለሙያወች የጋራ አገልግሎት
በሚሰጡ የስራ ዘርፎች በውስጥ ዝውውር አግባብ ተመድበው ሊሰሩ ይችላሉ። ሆኖም
በተጠቃሚ መ/ቤቶች ውስጥ ያሉ ሁሉም ሠራተኞች/ባለሙያወች በየራሳቸው መ/ቤት
ካልሆነ በስተቀር ከአንዱ መ/ቤት ወደ ሌላ መ/ቤት በውስጥ ዝውውር አግባብ ተወዳድረው
ሊመደቡ አይችሉም።
3.6.11. በዞንና ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ ስር የተደራጀውን የሰው ሃብት አስተዳደር ቡድንን ለማገዝ
ሲባል በፑል አስተባባሪ መ/ቤቶች የተመደቡ የሰው ኃብት አስተዳደር ሠራተኞች
በውስጥ ዝውውር አግባብ መወዳደር የሚችሉት ወደ ሲቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት እና የጋራ
አገልግሎት ወደ ሚሰጡባቸው መ/ቤቶች መዛወር ይችላሉ ።
3.6.12. በዞንና ወረዳ ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት ስር የተደራጀውን የግዥ ፋይናንስና
ንብረት አስተዳደር ቡድንን ለማገዝ ሲባል በፑል አስተባባሪ መ/ቤቶች የተመደቡ የጠቅላላ
አገልግሎት ኃላፊዎችና እና እቃ ግምጃ ቤት ኃላፊ ወደ ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት
እና የጋራ አገልግሎት ወደ ሚሰጡባቸው መ/ቤቶች መዛወር ይችላሉ።
3.6.13. የአንድ የሰው ኃብት አስተዳደር ሰራተኛ የስራ መደብ ክፍት ቢሆንና ቦታውን በውስጥ
ዝውውር ለማስያዝ ከተፈለገ የስራ መደቡ የሰው ሃብት አስተዳደር ሠራተኛ ከሆነ
የሚወዳደሩት ሲቪል ሰርቪስ ውስጥ የሚሰሩ ሠራተኞች፣ ሌሎች የሰው ሃብት
አስተዳደር ሠራተኞችእና በፑል ተጠቃሚ መ/ቤቶች ውስጥ ያሉ ሠራተኞች፤
እንዲሁም የስራ መደቡ የእቃ ግምጃቤት ኃላፊ ወይም የጠቅላላ አገልግሎት ኃላፊ
49
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
50
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
2. የማህደር ጥራት 5%
2. የማህደር ጥራት 5
ለ/ ከላይ በዝርዝር የተቀመጡትን መስፈርቶች መሠረት በማድረግ አሸናፊው ቢያንስ 50% ውጤት
ማምጣት ይጠበቅበታል።
51
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
አሸናፊው ይለያል ። በአንድ ወረዳ ወይም ዞን የሚገኝ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ወይም መ/ትራንስፖርት
ላይ የሚሰሩ ሠራተኞች በተደጋጋሚ ፈተና እንዲያዘጋጁ የሚጋበዙ ከሆነና የፈተና አሰጣጡ ላይ
ጥያቄ የሚያስነሳ ከሆነ ከሌላ አካባቢ ፈታኝ በመጋበዝ ፈተናውን መስጠት ይቻላል።
3.7.2. በአንድ የሥራ መደብ ላይ ለመወዳደር ከሚጠየቁ ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታዎች በላይ
ማስረጃ ይዘው የሚቀርቡ ቢኖሩ ማስረጃው ተጨማሪ ነጥብ አያስገኝላቸውም ወይም
የትምህርት ደረጃና የአገልግሎት ዘመን የሚጠቅሙት ለመመዝገቢያነት ብቻ ነው።
3.7.3. በውጭ ዝውውር ውድድር ጊዜም ለሴቶች 3 ፤ ለሴት አካል ጉዳተኞች 5 እና ለወንድ
አካል ጉዳተኞች 4 ነጥብ ይሰጣል። ይህም ሆኖ ሴቶች ከወንዶች ጋር እኩል ነጥብ ካገኙ
ቅድሚያ ለሴቶች ይሰጣል። ሆኖም ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው ተወዳዳሪዎች እኩል ነጥብ
ካመጡ አሸናፊው በዚሁ መመሪያ አንቀጽ 2.7 ንዑስ አንቀጽ 2.7.2.3 በተገለፀው መሠረት
ይለያል።
3.7.4. በአባሪ ሦስት የተገለፁት የሥራ መደቦች የተግባር ፈተና የሚያስፈልጋቸው መሆኑ
እንደተጠበቀ ሆኖ ከተገለፁት ሙያዎች ጋር ተመሣሣይ የሥራ መደብ በሚያጋጥምበት
ጊዜ የተግባር ፈተና የሚያስፈልጋቸው የሥራ መደቦች የመለየት ወይም የመወሰን
ሃላፊነት የዝውውር ጥያቄውን ያቀረበው አካል እና የሰው ሃብት አስተዳደር ቡድን
በጋራ ይሆናል።
3.7.5. የሥራ መደቡ ካልታጠፈ ወይም መ/ቤቱ ካልተዘጋ በስተቀር በሙከራ ላይ ያለ
ሠራተኛ ከመ/ቤት መ/ቤት ሊዛወር አይችልም።
3.8.1. በጤና ችግር ምክንያት ከመንግሥት ሪፈራል/ ስፔሻላይዝድ/ ሆስፒታል በሀኪሞች ቦርድ
በተረጋገጠ ማስረጃ የካንሰር፣ የኤችአይቪ ኤድስ ፣ የኩላሊት እጥበት የሚደረግላቸው
ህሙማን ፣ የአዕምሮ እና የልብ ህሙማን ስለመሆናቸው ማረጋገጫ የሚያቀርቡ ሠራተኞች
ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታውን እስካሟሉ ድረስ ከማንኛውም ዝውውር ፈላጊ ቅድሚያ
ይሰጣቸዋል። ይህም ሆኖ ከሁለቱ አንዱ ባለትዳር ከሆነ ቅድሚያ ለባለትዳሩ ይሰጣል።
ከባለትዳሮች መካከል አካል ጉዳተኞች ካሉ ለአካል ጉዳተኛ ተወዳዳሪ ቅድሚያ ይሰጣል።
ከአካል ጉዳተኞቹ መካከል የተለያየ ጾታ ያላቸው ከሆነ ለሴት ተወዳዳሪ አካል ጉዳተኛ
ቅድሚያ ይሰጣል።ሆኖም የሚቀርበው የህክምና
52
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
53
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
3.8.6. ከላይ ከንዑስ አንቀጽ 3.8.1 እስከ 3.8.5 ላይ የተመለከቱት ዝውውር ጠያቂዎች በሌሉበት
ሁኔታ ለአካል ጉዳተኞች ቅድሚያ ይሰጣል። የተለያየ ጾታ ያላቸው ከሆነ ለሴት
ተወዳዳሪ አካል ጉዳተኞች ቅድሚያ ይሰጣል።
3.8.7. የሚቀርበው የጋብቻ ማስረጃ ህጋዊ ከሆነ የመንግስት ተቋም ወይም የሀይማኖት ተቋም
ወይም ከሀገር ሽማግሌዎች የተሰጠ እና መረጃው የዝውውር ማስታወቂያው ከመውጣቱ
በፊት ቢያንስ ከ 6 ወር አስቀድሞ ዝውውሩ ከሚፈፀምለት ሰራተኛ የግል ማህደር የተያያዘ
ስለመሆኑ ማረጋገጫ ማቅረብ ይኖርበታል። ለተጋቢዎች የቅድሚያ እድል ሲሰጥ
በመጀመሪያ ባለትዳሮችን በጋራ እንዲኖሩ ለማድረግ የሚለው የሚቀድም ሲሆን ቀጥሎም
ለማቀራረብ ስራም ያገለግላል።
3.8.8. በጋብቻ ዝውውር ሲፈፀም አመልካቾች የትዳር አጋራቸው የመንግሥት ሠራተኛ በመሆን
ባለመሆን ልዩነት ሳይደረግ ለመወዳደር እኩል ተጠቃሚነት ይኖራቸዋል። የትዳር አጋራቸው
በከተማው/በቀበሌው ነዋሪ ስለመሆናቸው የመንግሥት ሠራተኛ ከሆኑ ከሚሰሩበት
መ/ቤት የመንግሥት ሠራተኛ ካልሆኑ ከሚኖሩበት የቀበሌ አስተዳደር ህጋዊ ማስረጃ
ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡
3.8.9. ዝውውር ጠያቂዎች በሹመት ምክንያት ከትዳራቸው የተለያዩ ባለትዳሮች ከሆኑ
ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታውን ማሟላታቸው እየተረጋገጠ ማስታወቂያ ማውጣት
ሳያስፈልግ በተመሳሳይ የሥራ ደረጃ ወይም ተመሳሳይ የስራ ደረጃ ከጠፋ እስከ አንድ ደረጃ
ክፍና ዝቅ በማድረግ የያዙትን ደመወዝ እንደያዙ በየደረጃው ባለው ሲቪል ሰርቪስ
መ/ቤት በኩል እንዲዛወሩ ይደረጋል። ሆነም በአንድ ደረጃ ከፍታ ዝውውር የሚፈፀምለት
የስራ ደረጃውን ጥቅም የሚያገኘው ከሌሎች ሰራተኞች ጋር ተወዳድረው በደረጃ እድገት
አግባብ ሲያሸንፉ ብቻ ይሆናል።
3.8.10. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 3.8.9 የተገለፀው ቢኖርም የተሿሚ የትዳር አጋር የሆነ ባለቤቱ
በወረዳው በሚገኙ ቀበሌዎች የምትሰራ ከሆነ ለተሿሚ የትዳር አጋር የተሰጠ የቅድሚያ
እድል ተጠቃሚ ይሆናል። ቁጥራቸው ከአንድ በላይ በሚሆንበት ጊዜ ግን በውጭ ዝውውር
መስፈርት መሠረት እርስ በርሳቸው ተወዳድረው አሸናፊው ቅድሚያ የሚሰጠው ይሆናል።
3.8.11. ከላይ በንዑስ አንቀፅ 3.8.7 የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ የቅድሚያ እድል የተሰጣቸው
ሠራተኞች ከሌሎች የቅድሚያ እድል ካልተሰጣቸው ሠራተኞች ጋር ለዝውውር
ውድድር ሲቀርቡ ያለ ፈተና በቀጥታ የሚዛወሩ ይሆናል። ሆኖም የቅድሚያ እድል
54
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
ሀ) በቅድሚያ በተመሳሳይ ደረጃ ሊመደብበት የሚችል ክፍት የሥራ መደብ ካለ በያዘው ደረጃና
ደመወዝ ፣
ለ) በተመሳሳይ ደረጃ ሊመደብ የሚችልበት ክፍት የሥራ መደብ ከሌለና ሠራተኛው ዝቅ ባለ ደረጃ
ላይ ለመሥራት በጹህፍ ስምምነቱን የገለፀ ከሆነ እስከ ሁለት ደረጃና ደመወዝ ተቀንሶ፣ ወደ
ሚስማማው የሥራ መደብ ወይም የሥራ ቦታ ተዛውሮ ሊሰራ ይቻላል። በአንድ ዞን ውስጥ
ከሚሰራበት ወረዳ ወደ ሌላ ወረዳ ወይም ከሚሰራበት ከተማ ወደ ሌላ ከተማ አስተዳደር በዞን ሲቪል
ሰርቪስ መምሪያ በኩል ተመድበው እንዲሰሩ ይደረጋል፣ ከአንድ ዞን ወደ ሌላ ዞን የሚደረግ ምደባ ግን
በክልሉ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በኩል ይፈፀማል፡
55
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
3.9.2. በጤና ችግር ምክንያት ባሉበት ቀበሌ መስራት እንደማይችሉ በ 3 ሐኪሞች የተረጋገጠ
የህክምና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉም ካሉ ከቀበሌ ወደ ወረዳ መዛወር ይቻላል።
3.9.3. በህይወት ለመኖር የደህንነት ስጋት ምክንያት ወይም የህግ ከለላ የሚያስፈልጋቸው
ሰራተኞች/ባለሙያወች ከ 3 ቱ ተቋማት ማለትም፡- ከዞን/ከወረዳ/ከተማ አስተዳደር/
ፖሊስ ጽ/ቤት፣ አስተዳደር ጽ/ቤት እና ሲቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት የተጣራና የተረጋገጠ ማስረጃ
ማቅረብ የሚችሉ ሠራተኞችን በአንድ ዞን ውስጥ ከሚሰራበት ወረዳ ወደ ሌላ ወረዳ
ወይም ከሚሰራበት ከተማ ወደ ሌላ ከተማ አስተዳደር በዞን ሲቪል ሰርቪስ መምሪያ በኩል
ተመድበው እንዲሰሩ ይደረጋል፣ ከአንድ ዞን/ሬጆፖሊታን ከተማ ወደ ሌላ
ዞን/ሬጆፖሊታን ከተማ የሚደረግ ምደባ ግን በክልሉ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በኩል
ይፈፀማል፡ ምደባ የሚካሄደው በተመሳሳይ ባለበት የአስተዳደር እርከንና ከዚያ በታች
የአስተዳደር እርከን የሚፈፀም ይሆናል።
3.9.4. አንድ ሰራተኛ በራሱ ፍላጎት ዝቅ ባለ ደረጃ ላይ ለመሥራት በጹህፍ ስምምነቱን
የገለፀ ከሆነ እስከ አንድ የስራ ደረጃና ደመወዝ ተቀንሶ፣ ወደ ሚስማማው የሥራ
መደብ ወይም የሥራ ቦታ ተዛውሮ ሊሰራ ይቻላል። በአንድ ዞን ውስጥ ከሚሰራበት ወረዳ
ወደ ሌላ ወረዳ ወይም ከሚሰራበት ከተማ ወደ ሌላ ከተማ አስተዳደር በዞን ሲቪል
ሰርቪስ መምሪያ በኩል ተመድበው እንዲሰሩ ይደረጋል፣ ከአንድ ዞን/ሬጆፖሊታን ከተማ
ወደ ሌላ ዞን/ሬጆፖሊታን ከተማ የሚደረግ ምደባ ግን በክልሉ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
በኩል ይፈፀማል።
3.10.1. በታሳቢ የተቀጠሩ ወይም የተመደቡ ሠራተኞች የሚከፈላቸውን ደመወዝ እንደያዙ ከአንድ
መስሪያ ቤት ወደ ሌላ መስሪያ ቤት በታሳቢ እስከተቀጠሩበት ወይም እስከተመደቡበት የስራ
ደረጃ ድረስ ሊዛወሩ ይችላሉ። ሆኖም የሚዛወሩበት የስራ መደብ የሚጠይቀው
የትምህርት ደረጃና ዝግጅት ሊኖራቸው ይገባል።
3.10.2. በካርየር የታቀፉ ሠራተኞች ከካርየር ውጭ ወደሆኑ የስራ መደቦች የሚዛወሩ ከሆነ ለዝውውሩ
በተሰጠው አቻ የስራ ደረጃ መነሻ ደመወዝ ላይ ብቻ ይሆናል፡-
56
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
ሀ/ መምህራን ፤ር/መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች ካላችው የስራ ኃላፊነት አንፃር የስራ ደረጃቸው በልዩ
ሁኔታ የተመዘነ ስለሆነ በተመደቡበት የስራ ቦታ ውጤታማ ሁነው እንዲሰሩ ይጠበቃል ። ሆኖም
የተመደቡበትን ቦታ ለቀው መ/ቤቶች በሚያወጠቸው የዝውውር ማስታወቂያ ተወዳድረው ወደ ጽ/ቤት
መግባት የሚፈልጉ ካሉ ለር/መምህራንና ሱፐር ቪዘሮቸ ከያዙት የስራ ደረጃ ሶስት ደረጃ ተቀንሶ
እንዲዛወሩ ይደረጋል ። መምህራን ደግሞ ከያዙት የስራ ደረጃ ሁለት ደረጃ ተቀንሶ እንዲዛወሩ ይደረጋል
።
ለ/ የቀበሌ ልማት ባለሙያወች ማለትም የቀበሌ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊወች ፤ የእንስሳት ሀብት ልማት፣
የሰብል ልማት፣ የተፈጥሮ ሀብት፣ የመስኖ፣ የእንስሳት ህክምና፤የእንስሳት አዳቃይ ቴክኒሻኖች ፤
ኀብረት ስራ ማኀበራት አደራጅ እና የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ባለሙያዎችን ያካተተ
ሲሆን የእነዚህ ሰራተኞችና ባለሙያዎች የስራ ደረጃ የተመዘነው በልዩ ሁኔታ ያለባቸውን የስራ
ጫናና የሚሰሩበትን አካባቢ ግምት ውስጥ ያስገባ በመሆኑ በተመደቡበት ቦታ ላይ ሆነው እንዲሰሩ
ይጠበቃል። ሆኖም የተመደቡበትን ቦታ ለቀው መ/ቤቶች በሚያወጧቸው የዝውውር ማስታወቂያ
ተወዳድረው ወደ ጽ/ቤት መግባት የሚፈልጉ ካሉ የጽ/ቤት የሥራ ደረጃዎችን ከግምት ውስጥ
በማስገባት መፈጸም ያለበት በመሆኑ የቀበሌ ግብርና ባለሙያዎች ደረጃ XIV እና ደረጃ XV ላይ
የተመደቡ ሠራተኞች ወደ ደረጃ XII መዘዋወር የሚችሉ ሲሆን ደረጃ XII ላይ የተመደቡ ግን
በቀጣይ የእድገት መሠላል ተጠቃሚ ሆነው ደረጃ XIV ሲደርሱ ብቻ የሚስተናገዱ ይሆናል።
3.10.3. ሁለት የመንግስት ሠራተኞች በተመሳሳይ የስራ ደረጃ የሚገኙ ከሆነና አሰሪ መ/ቤቶች
እስከተስማሙ ድረስ ማስታወቂያ ማውጣት ሳያስፈልግ በፈቃደኝነት እርስ በእርስ መዛወር
ይችላሉ። ሆኖም ዝውውሩ በቅድሚያ ከመፈፀሙ በፊት ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታውን
ማሟላታቸው በሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ ቡድን በኩል መረጋገጥ ይኖርበታል።
3.10.4. ከደረጃ I እስከ ደረጃ V የትምህርት ደረጃ ይዘው በማንኛውም የስምሪት ዓይነት እስከ ባለሙያ
III የስራ ደረጃ የተመደቡ ባለሙያወች የተመደቡበትን የስራ ደረጃ ይዘው በተመሳሳይ
ደመወዝና ደረጃ ከቦታ ቦታ በውጭ ዝውውር መዛወር ይችላሉ።
3.10.5. በውጭ ዝውውር በወጣ ማስታወቂያ የተመዘበገ ብቸኛ ተወዳደሪ ሆኖ ከቀረበ ያለፈተና
በቀጥታ ማዘወር ይችላሉ። ነገር ግን በልዩ ሙያ ሆኖ የተግባር ፈተና በሚጠይቁ መደቦች
ላይ ግን ዝውውሩ የሚፈፀመው በፈተና ይሆናል።
57
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
58
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
3.11.6. ከንዑስ አንቀጽ 3.11.1 እስከ 3.11.5 የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ በውጭ ዝውውር
በሚወጡ ማስታወቂያዎች መስፈርቶችን እና ለሥራ መደቡ የተጠየቀውን ዝቅተኛ
ተፈላጊ ችሎታ እስካሟሉ ድረስ መወዳደር ይችላሉ።
3.11.7. የስራ ተዋረድ የተለያየ ቢሆንም የስራ መደቡ ደረጃው አንድ እስከሆነ ድረስ እና ዝቅተኛ
ተፈላጊ ችሎታውን እስካሟሉ ድረስ ዝውውር መፈፀም ይቻላል።
59
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
3.12.4. በትውስት የተዛወረው ሠራተኛ የውጤት ተኮር እቅድ አፈፃፀም ውጤት በትውስት ወስዶ
በሚያሰራው መ/ቤት አማካኝነት ተሞልቶ ለቀጣሪው መ/ቤት እንዲተላለፍ ይደረጋል።
3.12.5. በትውስት የተዛወረ ሠራተኛ በሄደበት መ/ቤት ጥፋት ቢፈጽም የዲስፕሊን ክሱ የሚታየው
በቀጣሪው መ/ቤት አማካኝነት ይሆናል። በትውስት የወሰደው መ/ቤት ደግሞ ተገቢ
ማስረጃዎችን አደራጅቶ ለቀጣሪው መ/ቤት በወቅቱ የማስተላለፍ ግዴታ አለበት።
3.12.6. ሰጭና ተቀባይ መ/ቤቶች በተለየ ሁኔታ ካልተስማሙ በስተቀር የሠራተኛው ደመወዝም
ሆነ ሌሎች ጥቅማጥቅሞች በተቀባዩ መ/ቤት የሚሸፈን ይሆናል።
3.12.7. በትውስት ሄዶ የቆየ ሠራተኛ ጊዜውን አጠናቆ ሲመለስ በነበረበት የስራ ደረጃና ሙያ ወይም
አቻ በሆነ ሙያ ተመድቦ እንዲሰራ ይደረጋል። ቀጣሪው መ/ቤትም ይህንኑ በማሰብ
ቅድሚያ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል።
3.12.8. በትውስት የተዛወረ ሠራተኛ በቀጣሪው መ/ቤት በሚወጣ የደረጃ እድገት ስልጠና ወዘተ
… ተሳታፊ ይሆናል።
60
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
3.14.1. የዚህ ዓይነት ዝውውር የሚፈጸመው አስቀድሞ በወጣ የውጭ ዝውውር ማስታወቂያ
መሠረት ሠራተኛው የሥራ መደቡን ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታ እስካሟላ ድረስ የስራ
ደረጃ ተመሳሳይነት ባይኖረውም እንደማንኛውም ሠራተኛ በዚህ መመሪያ የውጭ
ዝውውር የማወዳደሪያ መስፈርቶች መሠረት ተወዳድሮ ሲያሸንፍ ይሆናል።
3.14.2. ሠራተኞው በነበረበት ህጋዊ ዕውቅና ያለው የግል፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆነ መ/ቤት
ውስጥ በቋሚነት የሚታወቅና ቋሚ ደመወዝ የሚከፈለው መሆን አለበት።
3.14.3. ሠራተኛው ይዞት የመጣው ደመወዝ ከሚዛወርበት የስራ መደብ ደመወዝ ጋር የማይጣጣም
/ከፍ ወይም ዝቅ/ ያለ ከሆነ ከተዛወረበት ጊዜ ጀምሮ
ሀ) ተቀባይ መ/ቤት በቂ በጀት ያለው ከሆነ ከሶስት እርከን ሳይበልጥ ወደሚቀጥለው እስኬል አስተካክሎ
መክፈል ይችላል።
ለ) ተቀባይ መ/ቤቱ በበጀት እጥረት ምክንያት የተቸገረ ከሆነና የሚዛወረው ሠራተኛ ፈቃደኛ መሆኑን
በጽሁፍ ካረጋገጠና መ/ቤቱም ይህንኑ ካረጋገጠ በስራ መደቡ መነሻ ደመወዝ ብቻ ማዛወር ይቻላል።
61
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
4.1.1. ማንኛውም ክፍት የስራ መደብ በደረጃ እድገት የሚሸፈነው በግልጽ ማስታወቂያ
አማካኝነት ይሆናል።
4.1.2. የደረጃ እድገት ማስታወቂያ የሚለጠፈው እንደ አስፈላጊነቱ በቅርንጫፍ መ/ቤቶችና
በተጠሪ ተቋማት በውስጥ የማስታወቂያ ሰሌዳዎች ይሆናል።
4.1.3. የደረጃ እድገት ማስታወቂያ ይዘት በዚህ መመሪያ ቅጽ ሁለት ላይ ተያይዟል።
4.1.4. ማስታወቂያው በአየር ላይ የሚቆይበት ጊዜ
62
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
ሐ/ ማስታወቂያው አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ የስራ ቀናት ምዝገባው ይካሄዳል።
4.1.5. ከንዑስ ቁጥር 4.1.1 – 4.1.4 ድረስ የተገለፀውን ተግባራት በአግባቡ መፈፀሙን ስምሪቱ
እንዲፈፀምለት የጠየቀው መ/ቤት/ዳይሬክቶሬት/ቡድን ክትትል ማድረግ አለበት።
63
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
4.3.1. ለአንድ ክፍት የሥራ መደብ የቀረቡ እጩ ተወዳዳሪዎች ምርጫ የሚፈፀመው በዚህ
መመሪያ አንቀጽ 2.5 በተደነገገው አግባብ ይሆናል።
ሠ/ በዚህ ንዑስ አንቀጽ ፊደል ተራ”ለ” እስከ “መ” ላይ ተመለከተው ቢኖርም አንድ ሠራተኛ ለደረጃ
እድገት ለመወዳደር የሚያበቃው የዕቅድ አፈፃፀም አጥጋቢ እና በላይ መሆን ይኖርበታል።
ረ/ በዚህ ንዑስ አንቀጽ ፊደል ተራ “ለ” እስከ “ሠ” የተመለከተው ቢኖርም እያንዳንዱ የዕቅድ
አፈፃፀም አጥጋቢ እና በላይ እስካልሆነ ድረስ አማካይ ነጥቡ አጥጋቢና በላይ ቢሆንም ለደረጃ
እድገት ውድድር መቅረብ አይቻልም።
64
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
የሚቀነስ የሚሰጥ
ተ.ቁ የተወሰደው የዲስፕሊን እርምጃ ነጥብ ነጥብ
እስከ 2 ዓመት ለሚደርስ ጊዜ ከደረጃና
1 ደመወዝ ዝቅ ማድረግ 5 0
እስከ ሦስት ወር ደመወዝ የሚደርስ የደመወዝ
2 ቅጣት 4 1
እስከ አስራ አምስት ቀን የሚደርስ የደመወዝ
3 ቅጣት 3 2
4 የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ቅጣት 2 3
የቃል ማስጠንቀቂያ ቅጣት በጽሁፍ ከተቀመጠ
5 1 4
6 ምንም የቅጣት ሪከርድ የሌለበት 0 5
65
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ሐ/ ከላይ ከንዑስአንቀጽ 4.4.1 እስከ 4.4.3 ድረስ በተቀመጡት ዝርዝር የማወዳደሪያ መስፈርቶች
መሠረት አሸናፊ የሚሆነው ተወዳዳሪ በአጠቃላይ ውጤት 50% እና በላይ ማምጣት ይጠበቅበታል።
ሆኖም በአጠቃላይ ውጤት 50% ባለማምጣታቸው ምክንያት ከውድድር ውጭ የሚሆኑ እጩዎች
መ/ቤቱ የደረጃ እድገቱን በድጋሚ የሚያወጣው ከሆነ ከመወደደር አይታገዱም።
4.4.4. በንዑስ አንቀጽ 4.4.1 ፊደል ተራ ለ የተጠቀሰው ቢኖርም በተለያየ ምክንያት የአንድ
ጊዜ የዕቅድ አፈፃፀም ውጤት 3 ወርና በላይ ነገር ግን ከ 6 ወር ባነሰ ጊዜ የተሞላላቸው
ሠራተኞች ቢኖሩ በነዚህ ጊዜያት የተሞላላቸው የዕቅድ አፈፃፀም ውጤት እንደ አንድ
ጊዜ የዕቅድ አፈፃፀም ውጤት ተይዞ ከሌላ የ 6 ወር የዕቅድ አፈፃፀም ውጤት ጋር ተደምሮ
ውጤቱ ለውድድር ሊያዝላቸው ይችላል።
4.4.5. በንዑስ አንቀጽ 4.5.1 ፊደል ተራ ለ እና በንዑስ አንቀጽ 4.4.4 የተጠቀሰው ቢኖርም
በትምህርት ላይ የነበሩ ወይም በሹመት የቆዩ ሠራተኞች ወደ ትምህርት ከመግባታቸው
ወይም ከመሾማቸው በፊት በሥራ ላይ ባለው የዕቅድ አፈፃፀም ምዘና መመሪያ መሠረት
የአንድ ወይም የሁለት ጊዜ የእቅድ አፈፃፀም ውጤት ካላቸው የተሞላላቸው የዕቅድ
አፈፃፀም ውጤት ተይዞላቸው እንዲወዳደሩ ይደረጋል። ሆኖም ግን በሥራ ላይ ባለው
የእቅድ አፈፃፀም ምዘና መመሪያ መሠረት የአንድም ጊዜ የዕቅድ አፈፃፀም ውጤት
ከሌላቸው የአንድ ጊዜ የስራ አፈፃፀም ውጤት እስከሚሞላላቸው ድረስ የዕቅድ አፈፃፀም
ሳያስፈልጋቸው በሌሎች መስፈርቶች ወደ 100% ተቀይሮ እንዲወዳደሩ ይደረጋል።
4.4.6. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 4.4.4 እና 4.4.5 የተጠቀሰው ቢኖርም በትምህርት ማሻሻል
እና በተናጠል በስራ መደብ ደረጃ መሻሻል ምክንያት ከሚገኝ ጥቅም በስተቀር በደረጃ
እድገት ከአንድ እርከን በላይ ጥቅም ያገኘ ሠራተኛ ከሆነ ጥቅም ካገኘበት ጊዜ አንስቶ አንድ
ዓመት ሳይሞላው የደረጃ ዕድገት መወዳደር አይችልም።
4.4.7. የመንግሥት ሠራተኛ የነበረም ሆነ ያልነበረ በአንድ መ/ቤት ውስጥ ካደገበት ደረጃ በላይ
የደረጃ እድገት ለመወዳደር አንድ ዓመት መቆየቱ እንደተጠበቀ ሆኖ በሙከራ
66
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
67
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
68
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
69
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
4.4.24. ለአስተዳደር አመችነት ሲባል በአንድ መ/ቤት ውስጥ የተለያየ ተግባርና ኃላፊነት
ይዘው በተለያዩ ቡድኖች ውስጥ የሚሠሩ ሠራተኞች በተደራጁበት መ/ቤት ውስጥ
በሚወጡ የደረጃ ዕድገት ማስታዎቂያዎች ተወዳድረው ሊያድጉ ይችላሉ። ሆኖም ዝቅተኛ
ተፈላጊ ችሎታውን ግን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
4.4.25. በወረዳ፤በከተማ አስተዳደሮችና በክፍለ ከተሞች ስር በሚገኙ ት/ቤቶችና ጤና ጣቢያወች
ላይ ያሉ ድጋፍ ሰጭ ሰራተኞች በያሉበት የአስተዳደር እርከን ስር በየራሳቸው ተቋም
ወደ ሚገኙ ት/ቤቶችና ጤና ጣቢያወች በሚወጡ የደረጃ እድገት መወዳደር ይችላሉ ።
4.4.26. አንድ ባለሙያ ደመወዙ ከያዘው ደረጃ መነሻ በላይ ቢሆንና በያዘው ደመወዝ ትይዩ የደረጃ
እድገት ማስታወቂያ ቢወጣ የያዘውን ደመወዝ እንደያዘ ለደረጃው ብቻ መወዳደር
የሚችል ይሆናል።
4.4.27. ከትምህርት ደረጃው መነሻ ደመወዝ በታች በሚያስከፍል የዕድገት መሰላል ተጠቃሚ
ከሚያደርጉ የስራ መደቦች ውጭ በሆነ የስራ መደብ ላይ የሚሰራ ሰራተኛ ዝቅተኛ ተፈላጊ
ችሎታውን ካሟላ የትምህርት ደረጃውን መነሻ ደመወዝ በሚያስከፍል የካርየር ስራ መደብ
ላይ በደረጃ እድገት ሊወዳደር ይችላል።
4.4.28. የቀበሌ ስራ አስኪያጆች ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታውን አሟልተው እስከተገኙ ድረስ
በምልመላ መረጣ መመሪያ ክፍል 4 የደረጃ እድገት አፈጻጸም መመሪያ መሰረት የገጠር
ቀበሌ ስራ አስኪያጆች ወደ ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት ፣ የከተማ ቀበሌ ስራ አስኪያጆች ወደ
ከንቲባ ጽ/ቤት ፣ በሪጆፖሊታን ከተሞች ስር ባሉ የከተማ ቀበሌ ስራ አስኪያጆች ወደ ክፍለ
ከተማ ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ባሉ ሁሉም የስራ መደቦች ደረጃ እድገት እንዲወዳደሩ
ይደረጋል።
4.5.1. የደረጃ እድገት ፈተናዎች ዝርዝር አፈፃፀም በዚህ መመሪያ ክፍል ሁለት አንቀጽ 2.9
መሠረት ይሆናል።
4.5.2. በሴቶች ልዩ ድጋፍ እርምጃ መመሪያ ላይ ለሴቶች በተሰጡ ልዩ ድጋፎች መሠረት
ሴቶች ከወንድች ጋርም ሆነ ሴቶች ከሴቶች ጋር ሲወዳደሩ ከፈተና በፊት ለኃላፊነት
ቦታዎች 5 ነጥብ ለሌሎች የሥራ መደቦች 3 ነጥብ መሰጠቱ እንደተጠበቀ ሆኖ ሴቶች
ከወንዶች ጋር ተወዳድረው እኩል ከመጡ ቅድሚያ ለሴቷ ይሰጣል። የአካል
70
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
4.8.1. የደረጃ እድገት ያገኘ ሠራተኛ ክፍያ የሚታሰብለት የደረጃ እድገቱ ከፀደቀበት ቀን ጀምሮ
ይሆናል። ሆኖም የደረጃ እድገቱ በተለያየ ምክንያት ቅሬታ ቢቀርብበት ቅሬታዉ ተጣርቶ
አግባብ ያለው ሆኖ ከተገኘ ክፍያው ሊታሰብ የሚችለው ውሣኔ ከተሰጠበት ጊዜ ጀምሮ
ይሆናል። ሆኖም የቀረበው ቅሬታ አግባብ ሆኖ ካልተገኘ ክፍያው የደረጃ እድገት ውጤቱ
ከተገለፀበት ጊዜ ጀምሮ ይሆናል።
71
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
4.9.1. በእንደገና ሥራ ደረጃ ምደባ ወይም በልዩ ምክንያት ከተቋሙ ውስጥ የተወሰኑ ሠራተኞች
የያዟቸው የስራ መደቦች ተነጥለው ከፍ ወዳለ ደረጃ አድገው ሲመጡ በመደቡ ላይ የነበሩት
ሠራተኞች ለደረጃው የሚያስፈልገውን ዝቅተኛ የተፈላጊ ችሎታ የሚያሟሉ መሆኑ በሰው
ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ ቡድን ሲረጋገጥ ያለምንም ውድድር ከፍ ያሉትን
ደረጃዎች እንዲይዙ በማድረግ የደረጃውን ጥቅም እንዲያገኙ ይደረጋል። ሆኖም በሙከራ
ቅጥር ላይ የሚገኝ ባለሙያ/ሰራተኛ የተሸሻለው ደረጃውን ጥቅም የሚያገኘው የሙከራ
ጊዜውን ካጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ ይሆናል።
4.9.2. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 4.9.1 በተገለጸው መሠረት ሠራተኞች የያዟቸው የሥራ መደቦች
ተነጥለው ከፍ ወዳለ ደረጃ አድገው ሲመጡ ሌሎች የተፈላጊ ችሎታ መመዘኛዎችን
አሟልተው የተሻሻለውን የስራ መደብ ደረጃ ለማሟላት እስከ አንድ ዓመት ጊዜ ድረስ ብቻ
የሥራ ልምድ የሚቀራቸው ከሆነ በመደቡ ላይ በተጠባባቂነት እንዲመደቡ በማድረግ
ሠራተኞቹ የተመደቡበትን የስራ መደብ የስራ ልምድ እንዳሟሉ በዚህ አንቀጽ ንዑስ
አንቀጽ 4.9.1 መሠረት የተሻሻሉትን የሥራ መደቦች ጥቅም ያለውድድር እንዲያገኙ
ይደረጋል።
4.9.3. የተሻሻሉትን የሥራ መደቦች ደረጃ ለማሟላት ከአንድ ዓመት በላይ የስራ ልምድ
የሚቀራቸውን ሠራተኞች ቀድሞ ከነበረው የሥራ ደረጃ ጋር እኩል ወደሆኑ ሌሎች
የሥራ መደቦች በማዛወር ክፍት የሥራ መደቦች በውድድር እንዲሞሉ ይደረጋል።
4.9.4. በአንድ መ/ቤት በቋሚነት ተመድቦ ሲሰራ የነበረ ሰራተኛ በመንግስት ስፖንሰር
አድራጊነት በመደበኛ ፕሮግራም ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ከገባ በኋላ ይዞት የነበረው
የስራ ደረጃ ቢሻሻል ትምህርት ላይ እያለ የተሻሻለውን የስራ ደረጃ ዝቅተኛ ተፈላጊ
ችሎታውን እስካሟላ ድረስ የተሻሻለው የስራ ደረጃ ጥቅም እንዲያገኝ ይደረጋል።
4.10. የሥራ መደብ ሲታጠፍ ወይም መ/ቤት ሲዘጋ የሚደረግ የሠራተኛ ድልድል
4.10.1. አንድ መ/ቤት ሲዘጋ፣ የስራ መደብ ሲታጠፍ ወይም በሌሎች ተጨባጭ ምክንያቶች ተንሣፋፊ
የሆኑ ሠራተኞች/ባለሙያወች ሲኖሩ በክልል ደረጃ ሲቪል ሰርቪስኮሚሽን ምደባ የመስጠት
ኃላፊነት አለበት።
72
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
4.10.2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 4.10.1 የተገለፀው ቢኖርም በዞን፣ በወረዳ፣ በክፍለ ከተማ
እና በከተማ አስተዳደር ደረጃ የሚኖሩ ተንሣፋፊ ሠራተኞች/ባለሙያወች ምደባ በዞን፣
በወረዳ፣ በክፍለ ከተማ እና በከተማ አስተዳደር ሲቪል ሰርቪስ መ/ቤቶች አማካኝነት
ይከናወናል።
4.10.3. ተንሣፋፊ ሠራተኞች ለመመደብ በክፍትነት የተገኙ የሥራ መደቦች ሠራተኞቹ
ከያዙት የሥራ ደረጃ ዝቅ ያሉ ከሆኑ የነበራቸውን ደመወዝ እንደያዙ እስከ ሁለት ደረጃ
ድረስ ዝቅ ወይም የስራ መደቡ ከፍ ያለ ከሆነ እስከ ሁለት ደረጃ ከፍ ብለው በጊዜያዊነት
እንዲመደቡ ይደረጋል። የተመደቡት ከፍ ወዳለ ደረጃ ከሆነ የሥራ ደረጃውን ጥቅም
የሚያገኙት ከሌሎች ሠራተኞች ጋር በደረጃ እድገት አግባብ ተወዳድረው ሲያሸንፉ ብቻ
ይሆናል።
4.10.4. ማንኛውም መ/ቤት ከፍት የሥራ መደብና በጀት እስካለው ድረስ የሚመደብለትን
ሠራተኛ ተቀብሎ የማሰራት ግዴታ አለበት።
4.10.5. በአንድ መ/ቤት በቋሚነት ተመድቦ ሲሰራ የነበረ ሰራተኛ በመንግስት ስፖንሰር አድራጊነት
በመደበኛ ፕሮግራም ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ከገባ በኋላ ይዞት የነበረው የስራ ደረጃ
ቢታጠፍ ፤ የስራ መደቡ መጠሪያና የስራ ተግባሩ ቢቀየር ፤ መ/ቤቱ ቢዘጋ ቀደም ሲል
ሲከፈለው በነበረው ደመወዝና ደረጃ ትይዩ እንዲመደብ ይደረጋል።
4.10.6. አንድ መ/ቤት የመዋቅር ክለሳ የሚያደርግ ከሆነ የመ/ቤቱ ሁሉም ሠራተኞች እኩል
ተወዳድረው የሚደለደሉ ሲሆን ከፍ ብለው የሚደለደሉ ሠራተኞች ጥቅም የሚሰጠውም
በደረጃ ዕድገት ሥነ-ስርዓት ተወዳድሮ ለሚያሽንፍ ሠራተኛ ብቻ ይሆናል።
ክፍል 5. ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች፣
5.1. ማንኛውም የሥራ ኃላፊ ወይም ሠራተኛ ባለው ሥልጣን ከህግ ውጭ ለሚፈጽማቸው
የምልመላና መረጣ ተግባራት ሁሉ በህግ ተጠያቂ ይሆናል።
5.2. ተወዳዳሪዎች እስከ ሁለት ደረጃ የሚቆጠር የስጋ ዝምድና/የጋብቻ ዝምድና ከሰው ሃብት
አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ቡድን ባለሙያዎች ወይም ከመ/ቤቱ ኃላፊዎች ጋር ካላቸው
ባለሙያዎች ወይም ኃላፊዎች በሰው ኃይል ስምሪቱ ላይ መሳተፍ የለባቸውም።ማለትም
ፈፃሚ ሠራተኛው/ባለሙያ/ቡድን መሪ/ዳይሬክተር ወንድ
73
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
74
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
ደረጃ ዝቅ ያለው ክፍት የስራ መደብ ካልተገኘ በአንድ ደረጃ ዝቅታ የሚከፈላቸውን
ደመወዝ እንደያዙ በተገኘው ክፍት የስራ መደብ ላይ በጊዚያዊነት ይመደባሉ።
በዚህ መመሪያ አፈፃፀም ላይ የሚነሣ ቅሬታ ቢኖር በሥራ ላይ ባለው የቅሬታ አቀራረብ ሥነ- ሥርዓት
መሠረት ተፈፃሚ ይሆናል። ይሁን እንጅ ምንም ስራ ያልነበራችው አዲስ ተቀጣሪዎች በቅጥር
አፈፃፀም ሂደት የሚያነሱት ቅሬታ ቢኖር ክልልና ዞን በተደራጀው የሰው ኃብት ስራ አመራር
አፈፃፀም ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬትና ቡድን የሚታይ ይሆናል።
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 253/2010 አንቀጽ
96 ን/አንቀጽ 2 መሠረት ይህን መመሪያ የመለወጥ፣ የማሻሻል ወይም በሥራ ላይ በሚውልበት ጊዜ
ማብራሪያ ወይም ትርጉም የመስጠት ኃላፊነት የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ነው።
ሀምሌ 2010 ዓ.ም ወጥቶ ሥራ ላይ ያለው የምልመላና መረጣ መመሪያ እና ይህን ተከትሎ
በተለያዩ ጊዜያት የወጡ ሰርኩላሮችና ማብራሪያዎች በዚህ መመሪያ ተተክተዋል።
አቶ ሙሉቀን አየሁ
የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ኮሚሽነር
75
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
76
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
77
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ጊዜውን፣
የሚሰጥበትን ቦታ እና ሌሎችም ካሉ፣
ሰ/ የቃለ-መጠይቅ አቀራረብ፣
በሰላምታ መጀመር እና፣
የቃለ-መጠይቁን ዓላማ ለተጠያቂው መግለፅ ናቸው።
1.3.3 ቃለ-መጠይቁን ማከናወን፣
ተወዳዳሪዎች ተመቻችተው እንዲቀመጡ መጋበዝ፣
ከውይይቱ አብዛኛውን ጊዜ ተወዳዳሪዎቹ እንዲናገሩ ማድረግ፣
የውይይቱ ሂደት አቅጣጫ በጥሞና መቆጣጠር መቻል፣
በሚገባ ማዳመጥና አእምሮን ክፍት አድርጐ የሚሰጡ መረጃዎችን በጥሞና መቀበል፣
ውሣኔ መስጠት ያለበት ቃለ-መጠይቁ ከተጠናቀቀ በኋላ ቢሆንም የሚመዛዘነው ተግባር ግን
ከሂደቱ ጋር የተቆራኘ መሆኑን መገንዘብ ከቃለ-መጠይቅ ፈታኞች ይጠበቃል።
1.3.4 መዝጊያ፣
ውጤቱ የሚገለፅበትን ወይም ሁኔታ መግለጽ፣
ቃለ-መጠይቁ መጠናቀቁን በግልፅ በማሣወቅ ተነስቶ ወይም በር ከፍቶ በትህትና እና
በመልካም ምኞች መግለጫ ማሰናበት ያስፈልጋል፣
የቃል ጥያቄ ፈተና እና መልስ እንደ ፅሑፍና ተግባር ፈተና ሁሉ ጥያቄውና መልሱ
በመረጃነት መያዝ ይኖርበታል።
78
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
ሀ/ አንድ ሊታመንና ሊሆን የሚችል ክስተትን የሚገልፅና ከፈታኞች የቀን ተቀን ህይወት ጋር
ግንኙነት ወይም አጋጣሚነት የሌለው ወይም ለውድድር ክፍት ከሆነው የሥራ መደብ ላይ
በምሣሌነት ሊቀርብ የሚችል ጉዳይ በፅሑፍ ማዘጋጀት፣
ለ/ ፅሑፍ ችግሮችን ለማሣየት የሚረዱ በቂ መረጃዎችን እንዲያካትትና ግልፅ የሆነ መልስ ወይም
መፍትሄ የሌለው የተለያዩ ሃሣብ ሊቀርብበት የሚችል መሆኑን ማረጋገጥ፣
ሐ/ ፈታኞች የሥራው ዝርዝር ተግባርና ኃላፊነት በሚጠይቀው ተፈላጊ ችሎታ መሠረት
በውይይቱ ወቅት የሚገመገምበት መመዘኛዎች ምን እንደሚሆኑ ስምምነት ላይ
መድረስ፣
መ/ ፀጥታ ባለው ክፍል የእያንዳንዱን ተፈታኝ /አባል/ገፅታ በሚገባ እንዲያዩ በሚያስችል
አቀማመጥ፣ በምቹ ወንበሮችና ጠረጴዛ እንዲቀመጡ ማድረግ፣
ሠ/ በእያንዳንዱ ተፈታኝ ፊት የስም ዝርዝር በማዘጋጀት ፈታኞቹ እያንዳንዱን ተፈታኝ
በስም ለይተው እንዲያው ማድረግ፣
ረ/ የውይይት ፅሑፍን ማደልና ፅሑፍ ላይ ከተገለፀው መመሪያ በስተቀር ሌላ ምንም ዓይነት
ገለፃ ለተፈታኞች አለመስጠት ያስፈልጋል።
1.4.3 የፈተናው ሂደት፣
ሀ/ ተፈታኞች ለተወሠኑ ደቂቃዎች ፅሑፉን እንዲያነቡ ይደረጋል፣ በዚህ ወቅት ፈታኞቹ
ከተወዳዳሪዎች ምንም ዓይነት ጥያቄ አይቀበሉም፣
ለ/ ተፈታኞች በፅሑፍ ላይ ውይይት እንደጀመሩ እያንዳንዱ ፈታኝ ከወጣው መስፈርት
አኳያ ማስታወሻ በመያዝ እያንዳንዱን ተፈታኝ ይገመግማል።
1.4.3.1 የእያንዳንዱ ተፈታኝ ከሰዎች ጋር በሚደረገው ግንኙነት ክህሎትና ሰብዓዊ
ባህሪያት የሚገመገምበት መለኪያዎች፣
ሀ/ በውይይቱ ላይ የሚደረግ ተሣትፎ ብዛት የሃሣብ ጥረትና አስተዋፅኦ፣
ለ/ እነዚህ አስተዋፅኦዎች በውይይት ቡድኑ ያገኙት ተቀባይነትና በቡድኑ አባላት በሥራ
ላይ የማዋላቸው መጠን፣
ሐ/ እያንዳንዱ ግለሰብ የሌላውን የቡድን አባል ሃሣብ ጣልቃ ባለመግባት የማዳመጥ መጠን፣ መ/
እያንዳንዱ አባል ለሌላው አባል አስተዋፅኦ የሚሰጠው ትኩረት፣
ሠ/ እያንዳንዲ ግለሰብ ያሣየው የአመራር ብቃት መጠን፣
79
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
80
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
81
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ቅጽ አንድ
ክፍት የሥራ መደቡ በሠራተኛ እንዲሟላ መጠየቂያ ቅጽ፣
ቁጥር ---------------------
ቀን -----------------------
በ-------------------------------ቢሮ/ኤጀንሲ/ኢንስቲትዩት/ተቋም/ኮሚሽን/ባለስልጣን/መምሪያጽ/ቤት
ለሰው ኃብት ሥራ አመራር ደጋፊ የሥራ ሂደት
-------------------------፣
1. የሥራ መደቡ መጠሪያ -------------- ደረጃ ------ ደመወዝ -------- ብዛት ------ የመ/መ/ቁጥር -----
2. ክፍት የሥራ መደቡ፡-
አዲስ የተፈቀደ የተለቀቀ
3. ክፍት የሥራ መደቡ፡-
ሀ/ የሚሟላበት የስምሪት ዓይነት በቅጥር/በውስጥ ዝውውር/በውጭ ዝውውር/በደረጃ ዕድገት ------------------------
--- በቅጥር ከሆነ
በ ሣቢ ቋሚ
ለ/ ፈተና የሚጠይቅ/የማይጠይቅ መሆኑን ------------------- ሚጠይቅ ከሆነ የተግባር እና የፅሑፍ ወይም
የፅሑፍ
4. ለሥራ መደቡ ከ ----------- ቀን/20 --------- ዓ.ም ጀምሮ በወር ብር -------- በጀት የተያዘለት መሆኑን፣
5. ከሥራ ዝርዝሩ ወይም ከጥናት ሠነዱ በመነሣት ለሠራ መደቡ የሚፈለገው ዕውቀት፣ ክህሎት፣
ችሎታና ሌሎች ፈላጊ ባህሪያት፣
---------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------- -
-------------------------ጥያቄውን ያቀረበው ኃላፊ/የሂደትመሪ/አስተባባሪ ጥያቄውን ያፀደቀው
የመ/ቤት ኃላፊ/ም/ኃላፊ ተወካይ
ስም ------------------------------------------- ስም ---------------------------------------
ፊርማ ------------------------ ፊርማ ---------------------------
የሥራ ኃላፊነት ---------------------------- የሥራ ኃላፊነት --------------------------
6. የሰው ኃብት ሥራ አመራር ደጋፊ የሥራ ሂደት ውሣኔ/አስተያየት፣
---------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------------- -
---------------------------------------------------------
ስም ------------------------------------------
ፊርማ ---------------------------------------
የሥራ ኃላፊነት ----------------------------------- ቀን --------- ወር---------------ዓ.ም
82
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
ቅጽ ሁለት
የክፍት ሥራ መደብ ማስታወቂያ ቅጽ ይዘት፣
ቁጥር -------------------------------
ቀን -------------------------------
83
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
84
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ
85
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
አቶ ሙሉቀን አየሁ
የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ኮሚሽነር
86
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
ከኃላፊነት የሚነሱ የመንግስት ተሿሚዎች ምደባ አሰጣጥና የደመወዝ ክፍያ አፈጻጸም መመሪያ
(የተሻሻለ)
ሰኔ 2013 ዓ.ም
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ባህር ዳር፣ ኢትዮጵያ
87
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
መግቢያ፡-
መንግስት የያዛቸውን የልማት፤ የዲሞክራሲ እና የሰላም ፖሊሲዎችን በአግባቡ እንዲፈጸሙ በማድረግ
የሕዝቡን ሁለንተናዊ ጥቅም ማስከበር ግንባር ቀደም አላማው ነው:: ይህን ዓላማ ለማሳካት ቆረጥ እና
ብቁ የመንግስት ተቐምን የሚመራ አመራር መመደብ ያስፈልጋል:: በመሆኑም ለኃላፊነት የሚሾሙ
አካላት ሲመደቡ በህግ የተሰጣቸውን ህዝባዊና መንግስታዊ ኃላፊነትን በአግባቡ መፈጸም ይገባቸዋል::
88
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
ከኃላፊነት የሚነሱ የመንግስት ተሿሚዎች ምደባ አሰጣጥና የደመወዝ ክፍያ አፈጻጸም መመሪያ
(የተሻሻለ)
ክፍል 1. ጠቅላላ፡-
1.1. አጭር ርዕስ፡-
1.2. ትርጓሜ፡-
1.2.1. “የመንግስት ሠራተኛ” ማለት በመንግስት መ/ቤት ውስጥ በቋሚነት ተቀጥሮ የሚሠራ ሰው
ነው፣
1.2.2. “ኮሚሽን” ማለት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ነው፣
1.2.3. “የመንግስት መ/ቤት” ማለት ራሱን ችሎ በአዋጅ ወይም በደንብ የተቋቋመና ሙሉ
በሙሉ ወይም በከፊል በመንግስት በጀት የሚተዳደር መስሪያ ቤት ነው፣
1.2.4. “ተሿሚ” ማለት በየትኛውም የሲቪል ሰርቪስ መዋቅር ላይ በክልሉ ም/ቤት ፣
በብሔረሰብ ዞን አስተዳደር ም/ቤቶች ወይም በክልል ርዕሰ መስተዳድር፣ ም/ርዕሰ
መስተዳድር፣ በወረዳ ፣ በቀበሌ ም/ቤቶች እና የመሾም ስልጣን በተሰጠው አካል በሹመት
የሚመደብ ሰው ማለት ነው። እንዲሁም የመንግስት ሰራተኛ እያሉ በቀጥታ ወደ ልማት
ድርጅቶችና ብዙሃን ማህበራትና ሙያ ማህበራት የተሾሙትን ያካትታል። ሆኖም ግን
በሲቪል ሰርቪስ መዋቅር ሳይልፉ በቀጥታ ወደ መንግስት ልማት ድርጅቶችና ብዙሃን
ማህበራት የተሾሙትን ለዚህ መመሪያ አተገባበር እንደ ተሿሚ አይቆጠሩም ።
1.2.5. “የአስተዳደር እርከን ከፍተኛ ደረጃ” ማለት የክልል የመንግስት ተቋማት ኃላፊዎችና
ም/ኃላዎች እንዲሁም በእነዚህ ተሿሚዎች ማዕረግ በአቻ የተሸሙ፤የዞን ዋናና ምክትል
አስተዳዳሪዎችንና የሦስቱ ሬጆፖሊታን ከንቲባና ም/ከንቲባዎችን፤የብሄረሰብ አስተዳደር
ም/ቤት ዋና አፈ-ጉባዔዎችና ም/አፈ-ጉባዔዎችን ጨምሮ ደረጃ XVIII በዞንና
በሬጆፖሊታን ከተማ አስተዳደር ፤በወረዳ፣ በአነስተኛና መካከለኛ ከተማ አስተዳደሮች፤
በክፍለ ከተሞች ፤ በመሪ ማዘጋጃ ቤት ደረጃ XV ፤ንዑስ ማዘጋጃ ቤት ደረጃ XIV ;ታዳጊ
ከተማ እና በከተማ አስተዳደር ስር የሚገኙ ቀበሌዎች ላይ ደረጃ XIII ነው።
89
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
3.1.1. የመንግስት ሰራተኛ ያልነበር ሰው ወደ ሲቭል ሰርቪስ መዋቅር መጦ የሚሾም ከሆነ ከተሾሙበት
ቀን ጀምሮ በየደረጃው ባሉ ሲቭል ሰርቪስ መ/ቤት አማካኝነት የሂይወት
90
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
ከኃላፊነት የሚነሱ የመንግስት ተሿሚዎች ምደባ አሰጣጥና የደመወዝ ክፍያ አፈጻጸም መመሪያ
(የተሻሻለ)
91
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
92
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
ከኃላፊነት የሚነሱ የመንግስት ተሿሚዎች ምደባ አሰጣጥና የደመወዝ ክፍያ አፈጻጸም መመሪያ
(የተሻሻለ)
93
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
94
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
ከኃላፊነት የሚነሱ የመንግስት ተሿሚዎች ምደባ አሰጣጥና የደመወዝ ክፍያ አፈጻጸም መመሪያ
(የተሻሻለ)
3.2.1. ምንም የስራ ልምድ ሳይኖራቸው ወደ ሹመት የተሳቡ አመራሮች ከኃላፊነት በሚነሱበት
ጊዜ ባላቸው የትምህርት ደረጃ መነሻ ደመወዝ እየተከፈላቸው በሚመጥናቸው የስራ
መደብ እንዲመደቡ ይደረጋል።
3.2.2. ከሦስት ዓመት በታች ያገለገሉ ተሿሚዎች በአዲሱ የሥራ ምዘናና ደረጃ አወሣሠን ጥናት
መሠረት ደረጃ በተሠጣቸው የሥራ መደቦች ከተደለደሉ በኋላ በአመራርነት ቆይተው
ከኃላፊነታቸው የተነሱ ተሿሚዎች ከመሾማቸው በፊት የተመደቡበት ደረጃና ጥቅም
ተከብሮላቸው እንዲመደቡ ይደረጋል።
3.2.3. በአዲሱ የሥራ ምዘናና ደረጃ አወሣሠን ጥናት መሠረት ደረጃ በተሠጣቸው የሥራ
መደቦች ሳይመደቡ ከተሾሙ በኋላ ከኃላፊነት በሚነሱበት ጊዜ ከመሾማቸው በፊት ይዘውት
የነበረው የሥራ መደብ መጠሪያ በአዲሱ የሥራ ምዘናና ደረጃ አወሣሠን ጥናት መሠረት
በተመዘነበት ደረጃ ትይዩ እንዲመደቡ ይደረጋል። ሆኖም በሹመት ላይ በነበሩበት
ወቅት የተደረገ አገር አቀፍ የደመወዝ ማሻሻያ ካለ እንዲያገኙ ይደረጋል።
3.2.4. ደረጃ በተሠጣቸው የሥራ መደቦች ሳይመደቡ ከተሾሙ በኋላ ከኃላፊነት በሚነሱበት ጊዜ
ከሹመት በፊትና የሹመት የስራ ልምዳቸው ተደምሮ ሁለት ዓመት እና ከሁለት ዓመት በላይ
ከአራት ዓመት በታች ከሆነ የያዙት የትምህርት ደረጃ ከሚያስከፍለው መነሻ ደመወዝ
በአንድ ደረጃ ከፍ ያለው ደመወዝ እየተከፈላቸው እንዲመደቡ ይደረጋል። ይህም ማለት
በባለሙያ II በክፍትነት ወደ ሚገኘው የሥራ መደብ ደረጃ IX ወይም X እንዲመደቡ
የሚደረግ ሲሆን በቅድሚያ የደረጃ X ክፍት የሥራ መደብ ከተገኘ በዚሁ ደረጃ ይመደባሉ
የደረጃ X ክፍት የሥራ መደብ ከጠፋ ግን በደረጃ IX እንዲመደቡ ይደረጋል። ነገር ግን
በቀበሌ ደረጃ በአመራርነት ሲያገለግሉ የቆዩ ተሿሚወች ከደረጃ 9 በላይ አይመደቡም።
ሆኖም አመራሩ ከመሾሙ በፊት በነጥብ የስራ ምዘና ዘዴ ተመዝኖ ደረጃ ከተሰጠው በኃላ
ወደ አመራርነት የተሳበ ከሆነ ከላይ በንዑስ አንቀጽ 3.1.14 በተገለፀው መሰረት
የሚስተናገዱ ይሆናል።
3.2.5. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 3.2.3 የተገለጸው ቢኖርም ከሹመት በፊትና የሹመት የስራ ልምዳቸው
ተደምሮ አራት አመት እና በላይ ከሆነ የያዙት የትምህርት ደረጃ ከሚያስከፍለው መነሻ
ደመወዝ በሁለት ደረጃ ከፍ ያለው ደመወዝ እየተከፈላቸው እንዲመደቡ ይደረጋል።
ሆኖም ባለሙያ III ተሿሚዎች እንደሚያሟሉት የሥራ
95
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ደረጃና በክፍትነት ወደ ሚገኘው የሥራ መደብ ደረጃ XI ወይም XII እንዲመደቡ የሚደረግ
ሲሆን በቅድሚያ ደረጃ XII የሆነ ክፍት የሥራ ደረጃ ከተገኘ በዚሁ ደረጃ ይመደባሉ
ከጠፋግን በደረጃ XI እንዲመደቡ ይደረጋል። ነገር ግን በቀበሌ ደረጃ በአመራርነት
ሲያገለግሉ የቆዩ ተሿሚወች ከደረጃ X በላይ አይመደቡም።ሆኖም አመራሩ ከመሾሙ
በፊት በነጥብ የስራ ምዘና ዘዴ ተመዝኖ ደረጃ ከተሰጠው በኃላ ወደ አመራርነት የተሳበ
ከሆነ ከላይ በንዑስ አንቀጽ 3.1.14 በተገለፀው መሰረት የሚስተናገዱ ይሆናል።
3.2.6. ቀደም ሲል የመንግስት ሰራተኛ ያልነበሩም ሆነ ቀደም ሲል የመንግስት ሰራተኛ ሆነው
ነገር ግን በተለያዩ የልማት ድርጅቶችም ሆነ በሌሎች የግል ልዩ ልዩ ተቋማት ላይ
በመስራት ላይ እያሉ ወደ መንግስት ተቋም ተሹመው ቆይተው ከሃላፊነት ሲነሱ ከሹመት
በፊትና የሹመት ልምዳቸው ተደምሮ በንዑስ አንቀጽ 3.2.3 እና 3.2.4 መሰረት በአዲሱ
የስራ ምዘና ደረጃ አወሳሰን ጥናት የደመወዝ ስኬል የተፈቀደውን ጥቅም እያገኙ
እንዲመደቡ ይደረጋል።
3.2.7. ከሹመት በፊት ርዕሰ መምህር፣ ም/ርዕሰ መምህርና ሱፐርቫይዘር የነበሩ ተሿሚዎች
በማንኛውም ጊዜ ከሹመት ተነስተው ወደ መምህርነት የሚመደቡ ከሆነ በመርሱ ቡድን
አማካኝነት ምደባ የሚሰጣቸው ሲሆን ከ 3 ዓመት በታች በሹመት ቆይተው ከሃላፊነት
ተነስተው ወደ ጽ/ቤት የሚመደቡ ከሆነ አቻ መምህራን ጉደኞቻቸው ከደረሱበት ደመወዝ
ላይ ካረፉ በኋላ ወደ ጽ/ቤት መዛወሪያ ትይዩ ደረጃና ደመወዝ ላይ እንዲመደቡ
ይደረጋል።ሆኖም ከ 3 ዓመት እና በላይ በሹመት ያገለገሉ እና ወደ ጽ/ቤት የሚመደቡ ከሆነ
በተሿሚዎች አመዳደብና ክፍያ አፈጻጸም መመሪያ መሰረት እንዲመደቡ
ይደረጋል።ይሁንእንጅ ምደባው ለአስተዳደር እርከኑ ከተፈቀደው ከፍተኛ የሥራ ደረጃና
ደመወዝ በላይ መመደብ አይቻልም። ይህ የሚፈጸመው በየደረጃው ባለው የሲቪል
ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት መ/ቤት አማካኝነት ይሆናል።
3.3. በተከታታይ ሶስት ዓመትና ከስድስት ዓመት በታች ያገለገሉ ተሿሚዎች አመዳደብና
ደመወዝ አከፋፈል፡-
3.3.1. የክልል ተቋማት ኃላፊዎችና ም/ኃላፊዎች በቢሮ ኃላፊ ወይም ም/ኃላፊ ደረጃ የተሾሙ
አመራሮች በክልል መ/ቤት ም/ኃላፊ ደረጃ በህዝብ ግንኙነት የተሾሙ፣ የዞን
አስተዳዳሪዎች፣ ም/አስተዳዳሪዎች በዞን ም/አስተዳደር ማዕረግ የተሾሙ ሌሎች
96
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
ከኃላፊነት የሚነሱ የመንግስት ተሿሚዎች ምደባ አሰጣጥና የደመወዝ ክፍያ አፈጻጸም መመሪያ
(የተሻሻለ)
97
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
3.4.1. የክልል ተቋማት ኃላፊዎችና ም/ኃላፊዎች በቢሮ ኃላፊ ወይም ም/ኃላፊ ደረጃ የተሾሙ
አመራሮች በክልል መ/ቤት ም/ኃላፊ ደረጃ በህዝብ ግንኙነት የተሾሙ፣ የዞን
አስተዳዳሪዎች፣ ም/አስተዳዳሪዎች በዞን ም/አስተዳደር ማዕረግ የተሾሙ ሌሎች
አመራሮች እና የሦስቱ ሬጅዮሮፖሊታን ከንቲባና ም/ከንቲባዎች በእነዚህ ማዕረግ የተሾሙ
ሌሎች ኃላፊዎች የብሔረሰብ ዞንና ሬጅዮሮፖሊታን ከተማ አፈ-ጉባዔዎችና ምክትል አፈ-
ጉባዔዎች ከኃላፊነት ሲነሱ የሥራ መደቡ እስካለና ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታውን እስካሟሉ
ድረስ ደረጃ XVIII እንዲመደቡ ይደረጋል፤ ደረጃ XVIII በክፍትነት ካልተገኘ ደረጃ XVII
እንዲመደቡ ይደረጋል። ደረጃ XVII በክፍትነት የማይገኝ ከሆነ ግን የደረጃ XVII ጥቅም
እያገኙ በተገኘው ክፍት የሥራ መደብ እንዲመደቡ ይደረጋል።
3.4.2. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 3.4.1 የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ በአዲሱ የሥራ ምዘናና
ደረጃ አወሣሠን ጥናት መሠረት በዞን/ሬጅዮሮፖሊታን ከተማ / ፣ በመካከለኛ ከተማ
አስተዳደር፣ በወረዳ ፣ በአነስተኛ ከተማ አስተዳደር፤ በክፍለ ከተማ ደረጃና መሪ ማዘጋጃቤት
ደረጃ XV ላይ እንዲመደቡ ይደረጋል። ይህ የሥራ መደብና ደረጃ በክፍትነት ካልተገኘ
ደረጃ XIV ላይ እንዲመደቡ ይደረጋል ። ደረጃ XIV በክፍትነት የማይገኝ ከሆነ ግን የደረጃ
XIV ጥቅም እያገኙ በተገኘው ክፍት የሥራ መደብ እንዲመደቡ ይደረጋል።
3.4.3. በንዑስ ማዘጋጃ ቤት ላይ የሚያገለግሉ ተሿሚዎች ከሀላፊነት በሚነሱበት ጊዜ ክፍት
የስራ መደብ እስከተገኘ ድረስ ደረጃ XIV ይህ የስራ መደብና ደረጃ በክፍትነት ካልተገኘ
ደረጃ XIII ላይ ይመደባሉ። ይህም ሆኖ ደረጃ XIII በክፍትነት ካልተገኘ የደረጃ XIII ጥቅምን
በመስጠት በተገኘው ክፍት የስራ መደብ ላይ ይመደባሉ ።
3.4.4. በከተማ አስተዳደሮች ስር በሚገኙ ቀበሌወችና በታዳጊ ከተማ ደረጃ ተሿሚ ሆነው
ሲያገለግሉ ቆይተው ከሀላፊነት የሚነሱ ተሿሚዎች ደረጃ XIII ላይ ይመደባሉ:: ይህ የስራ
መደብና ደረጃ በክፍትነት ካልተገኘ ደረጃ XII ላይ ይመደባሉ።ይህም ሆኖ ደረጃ XII
የሥራ መደብ በክፍትነት የማይገኝ ከሆነ የደረጃ XII ጥቅምን እያገኙ በተገኘው ክፍት
የስራ መደብ ላይ እንዲመደቡ ይደረጋል።
3.4.5. ከላይ የተገለፁ ቢኖርም ተፈላጊ ችሎታውን ባለማሟላታቸው ሊመደቡ የማይችሉ
ከሹመት የተነሱ ኃላፊዎች በሚኖሩበት ጊዜ በሚያሟሉት የስራ ደረጃ ላይ
98
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
ከኃላፊነት የሚነሱ የመንግስት ተሿሚዎች ምደባ አሰጣጥና የደመወዝ ክፍያ አፈጻጸም መመሪያ
(የተሻሻለ)
3.5.1. የክልል ተቋማት ኃላፊዎችና ም/ኃላፊዎች በቢሮ ኃላፊ ወይም ም/ኃላፊ ደረጃ የተሾሙ
አመራሮች በክልል መ/ቤት ም/ኃላፊ ደረጃ በህዝብ ግንኙነት የተሾሙ፣ የዞን
አስተዳዳሪዎች፣ ም/አስተዳዳሪዎች በዞን ም/አስተዳደር ማዕረግ የተሾሙ ሌሎች
አመራሮች እና የሦስቱ ሬጅዮሮፖሊታን ከንቲባና ም/ከንቲባዎች በእነዚህ ማዕረግ የተሾሙ
ሌሎች ኃላፊዎች የብሔረሰብ ዞንና ሬጅዮሮፖሊታን ከተማ አፈ-ጉባዔዎችና ምክትል አፈ-
ጉባዔዎች ተሿሚዎች ከኃላፊነት ሲነሱ የሥራ መደቡ እስካለና ዝቅተኛ ተፈላጊ
ችሎታውን እስካሟሉ ድረስ ደረጃ XVIII እንዲመደቡ ይደረጋል፤ ደረጃ XVIII
በክፍትነት ካልተገኘ የደረጃ XVIII ጥቅም እያገኙ በተገኘው ክፍት የሥራ መደብ
እንዲመደቡ ይደረጋል።
3.5.2. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 3.5.1 የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ በነጥብ የሥራ ምዘናና ደረጃ
አወሣሠን ጥናት መሠረት በዞን/ሬጅዮሮፖሊታን ከተማ / ፣ በመካከለኛ ከተማ አስተዳደር፣
በወረዳ ፣ በአነስተኛ ከተማ አስተዳደር፤ በክፍለ ከተማ ደረጃና መሪ ማዘጋጃቤት ደረጃ XV
ላይ እንዲመደቡ ይደረጋል። የደረጃ XV በክፍትነት የማይገኝ ከሆነ ግን የደረጃ XV ጥቅም
እያገኙ በተገኘው ክፍት የሥራ መደብ እንዲመደቡ ይደረጋል።
3.5.3. በንዑስ ማዘጋጃ ቤት ላይ የሚያገለግሉ ተሿሚዎች ከሀላፊነት በሚነሱበት ጊዜ ክፍት
የስራ መደብ እስከተገኘ ድረስ ደረጃ XIV ይህ የስራ መደብና ደረጃ በክፍትነት ካልተገኘ
የደረጃ XIV ጥቅምን በመስጠት በተገኘው ክፍት የስራ መደብ ላይ ይመደባሉ ።
3.5.4. በከተማ አስተዳደሮች ስር በሚገኙ ቀበሌዎችና በታዳጊ ከተማ ደረጃ ተሿሚ ሆነው
ሲያገለግሉ ቆይተው ከሀላፊነት የሚነሱ ተሿሚዎች ደረጃ XIII ላይ ይመደባሉ:: ይህ
የስራ መደብና ደረጃ በክፍትነት ካልተገኘ ደረጃ XIII ጥቅምን እያገኙ በተገኘው ክፍት
የስራ መደብ ላይ እንዲመደቡ ይደረጋል።
99
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
100
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
ትምህርታቸውን ያሻሻሉ አመዳደብና ደመወዝ አከፋፈል የአፈጻጸም መመሪያ
መመሪያ 3. ትምህርታቸውን
ያሻሻሉ ኃላፊዎች አመዳደብና
ደመወዝ አከፋፈል የአፈጻጸም
መመሪያ (የተሻሻለ)
ቁጥር 03/2013
ሰኔ 2013 ዓ.ም
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ባህር ዳር፣ ኢትዮጵያ
101
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
መግቢያ፡-
ትምህርት የአንድን አገር ልማት ለማፋጠን እጅግ ጠቃሚ በመሆኑ በአገር ደረጃም ሆነ በክልላችን
ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራባቸው ከሚገኙ ዘርፎች ውስጥ በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው። ስለሆነም
በተለያዩየ ደረጃ የሚገኙ የትምህርት ተቋማትን በመጠቀም ተሿሚዎች የረጅም ጊዜ ስልጠና
እንዲያገኙ በማድረግ እና የመፈጸም አቅም በማጎልበት በሲቪል ሰርቪሱ ተቋማት የሚታየውን
የአፈጻጸም ክፍተት በመሙላት ጠንካራ ሲቪል ሰርቪስ ተቋማት ለመገንባት ይቻላል፣፣ በመሆኑም
የትምህርት ደረጃቸውን አሻሽለው የሚመለሱ የመንግስት ተሿሚዎችን በአግባቡ ምደባ ለመስጠትና
ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያሥችል መመሪያ ተሻሽሎ ከህዳር 2010 ዓ፣ም ጀምሮ ስራ ላይ እንዲውል
የተደረገ ቢሆንም እንደገና ማሻሻል አስፈልጓል።
ክፍል 1. ጠቅላላ፡-
102
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
ትምህርታቸውን ያሻሻሉ አመዳደብና ደመወዝ አከፋፈል የአፈጻጸም መመሪያ
1.2. ትርጓሜ፡-
የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ መመሪያ ውስጥ፣
1.2.1. "የመንግሥት መ/ቤት" ማለት በየትኛውም የአስተዳደር እርከን እራሱን ችሎ በአዋጅ ወይም
በደንብ የተቋቋመ እና ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ከመንግስት በሚመደብለት በጀት
የሚተዳደር የክልል መንግስት መስሪያ ቤት ነው።
1.2.2. "ኮሚሽን" ማለት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሲቪል ሰርቪስኮሚሽን ነው።
1.2.3. .“ተሿሚ” ማለት በየትኛውም የሲቪል ሰርቪስ መዋቅር ላይ በክልሉ ም/ቤት ፣ በብሔረሰብ
አስተዳደር ም/ቤቶች ወይም በክልል ርዕሰ መስተዳድር፣ ም/ርዕሰ መስተዳድር እንዲሁም
በወረዳ እና በቀበሌ ም/ቤቶች እንዲሁም የመሾም ስልጣን በተሰጠው አካል በሹመት
የሚመደብ ሰው ማለት ነው። እንዲሁም የመንግስት ሰራተኛ እያሉ በቀጥታ ወደ ልማት
ድርጅቶችና ብዙሃን ማህበራትና ሙያ ማህበራት የተሾሙትን ያካትታል። ሆኖም ግን
በሲቪል ሰርቪስ መዋቅር ሳይልፉ በቀጥታ ወደ መንግስት ልማት ድርጅቶችና ብዙሃን
ማህበራት የተሾሙትን ለዚህ መመሪያ አተገባበር እንደ ተሿሚ አይቆጠሩም ።
1.2.4. “መደበኛ ፕሮግራም “ ማለት በመንግስት ድጋፍም ይሁን በግል ስፖንሰር አድራጊነት ከመደበኛ
ስራቸው ውጭ ሆኖ ትምህርቱን ለመከታተል የመረጠው መርሀ-ግብር ነው።
1.2.5. “በርቀት፤በማታ፤በክረምት ፕሮግራም”ማለት በመንግስትድጋፍምይሁንበግልስፖንሰር
አድራጊነት መደበኛ ስራውን እያከናወነ ትምህርቱን ለመከታተል የመረጠው መርሀ- ግብር
ነው።
103
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
104
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
ትምህርታቸውን ያሻሻሉ አመዳደብና ደመወዝ አከፋፈል የአፈጻጸም መመሪያ
የሚመደብ ከሆነ ከነበረበት አስተዳደር እርከን ከፍተኛ የስራ ደረጃ በላይ ሊመደብ
አይችልም።
2.1.6. ከተሿሚነት በቀጥታ ወደ ከፍተኛ ትምህርት በመግባት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ቆይተው
በተለያየ ምክንያት በቋሚነት አቋርጠው የተመለሱ ኃላፊዎች የነበሩ ከኃላፊነት የሚነሱ
የመንግሥት ተሿሚዎች ምደባ አሰጣጥና የደመወዝ ክፍያ አፈጻጸም መመሪያ መሠረት
ቋሚ ምደባ ይሰጣቸዋል። ሆኖም ከሹመት ተነስተው ወደ ትምህርት ቤት በመግባት
ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ቆይተው በተለያዩ ምክንያቶች ትምህርታቸውን በጊዜያዊነት
ያቋረጡ ከሆነ ወደ ት/ቤት እስከሚመለሱ ድረስ ወደ ትምህርት ሲገቡ ይዘውት የነበረውን
ደመወዝ እንደያዙ ጊዜያዊ ምደባ ተሰጥቷቸው በተገኘው የስራ መደብ እየሰሩ እንዲቆዩ
ይደረጋል።
2.1.7. ከላይ በንዑስ አንቀፅ 2.1.5 እና 2.1.6 በተገለጸው አግባብ ምደባ የሚሰጣቸው ተሿሚዎች
ትምህርታቸውን ያቋረጡበትን ምክንያት የሚገልጽ ማስረጃ ከዩኒቨርስቲው ሪጅስትራር
ጽ/ቤት በማምጣት ወደ ትምህርት ለላካቸው መ/ቤትና በየደረጃው ለሚገኘው ሲቪል
ሰርቪስ መ/ቤትም ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
2.1.8. ቀደም ሲል ተሿሚ ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩና በመንግስት ድጋፍ ከመደበኛ ስራቸው ተለይተው
የዕድገት መሰላል በሚያስጠቅም የትምህርት ደረጃና ዝግጅት አሻሽለው ሲመለሱ ክፍት
የስራ መደብ እስካለ ድረስ በዕድገት መሰላል የስራ ደረጃ መነሻ ላይ ሊመደቡ ይችላሉ።
ሆኖም ከትምህርት ተመልሰው በተሿሚዎች ምደባ አሰጣጥና ክፍያ አፈፃፀም መመሪያ
መሰረት ሲመደቡ ሊያገኙ የሚችሉት ደመወዝ የሚበልጥ ከሆነ ከኃላፊነት የተነሱ
ተሿሚዎች ምደባ አሰጣጥና ክፍያ አፈፃፀም መመሪያ መሰረት ይስተናገዳሉ ። በዕድገት
መሰላል የሚያስጠቅም የስራ መደብ ላይ የሚመደቡ ከሆነም የቀጣይ ዕድገት መሠላል
ማግኛ ጊዚያቸው በዕድገት መሰላል አፈፃፀም መመሪያ መሰረት ይስተናገዳሉ ።
105
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ክፍል 3. ልዩ ልዩ ጉዳዮች፡-
3.1. ትምህርታቸውን በመንግስት ስፖንሰር አድራጊነት ሲከታተሉ ቆይተው በተለያየ
ምክንያት አቋርጠው የሚመለሱና ትምህርታቸውን አጠናቀው የሚመለሱ ተሿሚዎች
ከትምህርት ስለመመለሳቸው ትምህርት ለላካቸው መ/ቤትና በየደረጃው ለሚገኘው ሲቪል
ሰርቪስ መ/ቤትም ሪፖርት ያደርጋሉ ። የትምህርት ጊዜው ከአንድ ዓመት በላይ
የሚወስድ ከሆነ በየ አመተ ምህረቱ ለላካቸው መ/ቤት ሪፖርት ያርጋሉ።
3.2. ከትምህርት መልስ ምደባ የተሰጣቸው ተሿሚዎች በሥራ ላይ ባለው የሥራ አፈፃፀም ምዘና
መመሪያ መሠረት የአንድም ጊዜ የሥራ አፈፃፀም ውጤት ከሌላቸው ለተለያዩ
የሥምሪትና የስልጠና ውድድሮች በሌሎች መስፈርቶች ወደ 100 % ተቀይሮ
እንዲወዳደሩ ይደረጋል።
3.3. ከትምህርት መልስ ምደባ የተሰጣቸው ተሿሚዎች በትምህርት መሻሻል ባገኙት
ጥቅም ምክንያት መ/ቤቱ በሚያወጣው የደረጃ እድገት ላይ ለመወዳደር አንድ ዓመት
እንዲጠብቁ አይደረጉም ።
3.4. በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 253/2010 አንቀጽ 96
ን/አንቀጽ 2 መሠረት ይህን መመሪያ የመለወጥ፣ የማሻሻል ወይም በሥራ ላይ
106
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
ትምህርታቸውን ያሻሻሉ አመዳደብና ደመወዝ አከፋፈል የአፈጻጸም መመሪያ
አቶ ሙሉቀን አየሁ
የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ኮሚሽነር
107
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
መመሪያ 4. ትምህርታቸውን
ያሻሻሉ መንግስት ሠራተኞች/
ባለሙያዎች አመዳደብና
ደመወዝ አከፋፈል አፈፃፀም
መመሪያ /የተሸሻለው/
ቁጥር 04/2013
ሰኔ 2013 ዓ.ም
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ባህር ዳር፣ ኢትዮጵያ
108
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
ትምህርታቸውን ያሻሻሉ መንግስት ሠራተኞች/ ባለሙያዎች አመዳደብና ደመወዝ አከፋፈል አፈፃፀም መመሪያ /የተሸሻለው/
መግቢያ፡-
ትምህርት የአንድን አገር ልማት ለማፈጠን እጅግ ጠቃሚ በመሆኑ በአገር ደረጃም ሆነ በክልላችን
ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራባቸው ከሚገኙ ዘርፎች ውስጥ በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው። ስለሆነም
የትምህርት ተቋማትን በመጠቀም የፈጻሚውን አቅም ማጎልበት በሲቪል ሰርቪሱ የሚታየውን
የመፈጸም አቅም ክፍተት መሙላት ስለሚያስችል የትምህርት ደረጃቸውን አሻሽለው የሚመለሱ
የመንግስት ሠራተኞችን/ባለሙያዎችን በአግባቡ ምደባ ለመስጠትና ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያሥችል
መመሪያ ተሻሽሎ ከሰኔ 2011 ጀምሮ ስራ ላይ እንዲውል የተደረገ ቢሆንም እንደገና ማሻሻል
አስፈልጓል። ስለሆነም
በተለያዩ ጊዚያት የወጡ ሰርኩላሮችን የዚህ መመሪያ አካል በማድረግ ለተጠቃሚው ምቹ ሁኔታ
ለመፍጠርና በአፈጻጸም የታዩ ግድፈቶችን ለማረም በማስፈለጉ፣
ከነጥብ የስራ ምዘናና ደረጃ አወሳሰን ጥናት ጋር የተዛመደ የመመሪያ ማሻሻያ ማድረግ
በማስፈለጉ።
በየደረጃው ትምህርታቸውን አጠናቀው ለሚመለሱ ባለሙያዎች የትምህርት
ዝግጅታቸውን መሠረት ያደረገ ምደባ በወቅቱ መስጠት በማስፈለጉ፣
በሃገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሃገር በመንግስት ድጋፍ ትምህርታቸውን አሻሽለው ለሚመለሱ
ባለሙያዎች ተገቢ የስራ ምደባና አቅምን ያገናዘበ ማበረታቻ በመስጠት አቅማቸውን አሟጠው
እንዲጠቀሙ ማስቻል በማስፈለጉ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በተሻሻለው የመንግስት ሠራተኞች
አዋጅ 253/2010 አንቀጽ 96 ንዑሥ አንቀጽ 2 በተሰጠው መመሪያ የማውጣት ስልጣን
መሰረት ይህን መመሪያ አውጥቷል።
ክፍል 1. ጠቅላላ
1.2. ትርጓሜ
የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ መመሪያ ውስጥ፣
109
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
1.2.1. "የመንግሥት መ/ቤት" ማለት በየትኛውም የአስተዳደር እርከን እራሱን ችሎ በአዋጅ ወይም
በደንብ የተቋቋመ እና ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ከመንግስት በሚመደብለት በጀት
የሚተዳደር የመንግስት መስሪያ ቤት ነው።
1.2.2. "ኮሚሽን" ማለት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ነው።
1.2.3. “የመንግስት ሠራተኛ ” ማለት በመንግሥት መሥሪያ ቤት ውስጥ በቋሚነት ተቀጥሮ የሚሠራ
ሰው ነው ።
1.2.4. “መደበኛ ፕሮግራም “ ማለት በመንግስት ድጋፍም ይሁን በግል ስፖንሰር አድራጊነት ከመደበኛ
ስራቸው ውጭ ሆኖ ትምህርቱን ለመከታተል የመረጠው መርሀ-ግብር ነው።
1.2.5. “በርቀት፤በማታ፤በክረምት ፕሮግራም”ማለት በመንግስትድጋፍምይሁንበግልስፖንሰር
አድራጊነት መደበኛ ስራውን እያከናወነ ትምህርቱን ለመከታተል የመረጠው መርሀ- ግብር
ነው።
1.2.6. ማንኛውም በወንድ ፃታ የተገለፀው የሴት ፆታንም ያካትታል።
110
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
ትምህርታቸውን ያሻሻሉ መንግስት ሠራተኞች/ ባለሙያዎች አመዳደብና ደመወዝ አከፋፈል አፈፃፀም መመሪያ /የተሸሻለው/
111
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ልምድ የተሻሻለው ትምህርት ደረጃ መነሻ ደመወዝና ከዚያ በላይ ደመወዝ ሊያስከፍል
በሚችል ደረጃ ያለው ስራ መደብ ላይ ይመደባሉ። ሆኖም ግን ሊመደቡ የሚችሉበት የስራ
መደብ ከሌለ እየሰሩ ባሉበት የስራ ደረጃ ላይ የትምህርት ዝግጅት መነሻ ደመወዝ
እንዲያገኙ በማድረግ በጊዚያዊነት ይመደባሉ።
2.1.7. ከላይ በን/አንቀጽ 2.1.2 - 2.1.6 የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ ባለሙያው ከሄደበት መ/ቤት
የሚመደብበት ክፍት የሥራ መደብ ከጠፋ ብቻ በየደረጃው ባለው የሲቪል ሰርቪስ መ/ቤት
አማካኝነት ባለሙያው ይሰራበት የነበረው መ/ቤት ባለበት የአስተዳደር አርከን ባሉ ሌሎች
ሴክተር መ/ቤቶች ባሉ ክፍት ስራ መደቦች ላይ እንደአስፈላጊነቱ በጀቱን እንደያዘ ወይም
ሳይዝ እንዲመደቡ ይደረጋል።
2.1.8. ከላይ በን/አንቀጽ 2.1.7 በተገለጸው መልኩ ምደባ መስጠት ካልተቻለ የሚመጥናቸው ክፍት
የሥራ መደብ እስከሚገኝ ድረስ በተላኩበት የአስተዳደር እርከን ውስጥ በጊዜያዊነት
በማንኛውም ስራመደብ ላይ ተመድበው እንዲሰሩ ይደረጋል። ይህም ሆኖ ጊዚያዊ የስራ
መደብ ከጠፋ የወረዳና ከተማ አስተዳደር ሠራተኞችን በዞን በኩል ዞን ሴክተሮች ላይምሆነ
በዞኑ ውስጥ ባሉ ወረዳዎች ወይም ከተማ አስተዳደሮች ላይ እንዲመደቡ ይደረጋል። የዞን
ሴክተር መ/ቤት ሠራተኞች ምደባ ግን በዞን ሲቪል ሰርቪስ መ/ቤት አማካኝነት
ይጠናቀቃል።
2.1.9. ከላይ በን/አንቀጽ 2.1.8 የተገለጸው ቢኖርም ሠራተኛው የሚመደብበት ክፍት የስራ
መደብ ባለመገኘቱ ከነበረበት የአስተዳደር እርከን ወደ ላይኛው አስተደር እርከን ተስቦ
የሚመደብ ሠራተኛ ቢኖር ከነበረበት አስተዳደር እርከን ከፍተኛ የስራ ደረጃ በላይ ሊመደብ
አይችልም።
2.1.10. የካርየር ተጠቃሚ የሆነ ሠራተኛ በመንግስት ድጋፍ በማንኛውም ፕሮግራም ከሁለተኛ ዲግሪ
በታች በሆነ የትምህርት ደረጃ ትምህርቱን አጠናቆ ሲመለስ ለትምህርት ከመሄዱ በፊት
ያገኝ የነበረው ደመወዝ ካሻሻለው የትምህርት ዝግጅት መነሻ ደመወዝ በታች ከሆነ በካርየሩ
መነሻ ደመወዝ የሥራ ደረጃ ላይ እንዲመደብ ይደረጋል። ሆኖም ግን ለትምህርት ከመሄዱ
በፊት ያገኝ የነበረው ደመወዝ ካሻሻለው የትምህርት ዝግጅት መነሻ ደመወዝ በላይ
ከሆነ በሚያገኘው ደመወዝ ትይዩ ባለው የካርየር ሥራ ደረጃ ላይ ከመመደብ በስተቀር
የሚደረግለት ጭማሪ አይኖርም ።
2.1.11. ከላይ በንኡስ አንቀጽ 2.1.10 የተገለጸው ቢኖርም ደመወዙ በካርየር መመሪያው ለትምህርት
ደረጃው ከተወሰነው መነሻ ደመወዝ እኩል ወይም የሚበልጥ ከሆነ
112
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
ትምህርታቸውን ያሻሻሉ መንግስት ሠራተኞች/ ባለሙያዎች አመዳደብና ደመወዝ አከፋፈል አፈፃፀም መመሪያ /የተሸሻለው/
113
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ተመዝኖ ደረጃ የወጣለት የጤና ሙያ የሥራ መደብ መኖሩን በቅድሚያ ተቋሙ ማረጋገጥ
ይኖርበታል። በተቋሙ ፍላጎት አንድ የጤና ባለሙያ ሙያውን አሻሽሎ ሲመለስ ቢያንስ
ለትምህርት ከመሄዱ በፊት ደርሶበት ከነበረው ደረጃ በታች አይመደብም ። በዚህ መሠረት
የትምህርት ደረጃ ያሻሻለ የጤና ባለሙያ፡-
ሀ) በሰለጠነበት የሙያ መስመር የትምህርት ደረጃውን አሻሽሎ ሲመለስ ለትምህርት ከመሄዱ በፊት
ደርሶበት የነበረው ደረጃ ዝቅ ያለ ከሆነ በሰለጠነበት ሙያ የመጀመሪያ ተዋረድ ወይም ዕድገት
መሰላል ላይ ተመድቦ ለደረጃው የተወሰነው ደመወዝ ይከፈለዋል።
ለ) በሰለጠነበት የሙያ መስመር ትምህርት ደረጃውን አሻሽሎ ሲመለስ ለትምህርት ከመሄዱ በፊት
ደርሶበት ከነበረው ደረጃ እኩል ወይም በላይ ከሆነ የሚከፈለውን ደመወዝ እንደያዘ በአዲሱ ሙያው
በትይዩ ባለ አቻ ደረጃ ላይ ይመደባል
ሐ) የትምህርት ማሻሻያ ያደረገ የጤና ባለሙያ ባሻሻለው የትምህርት ደረጃ ተመድቦ ሥራ የጀመረበት
ቀን መነሻ ሆኖ የሥራ ልምዱ ለመደበኛ የደመወዝ ጭማሪ እና ለደረጃ ዕድገት ይያዝላታል።
114
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
ትምህርታቸውን ያሻሻሉ መንግስት ሠራተኞች/ ባለሙያዎች አመዳደብና ደመወዝ አከፋፈል አፈፃፀም መመሪያ /የተሸሻለው/
115
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ክፍል 3. ልዩ ልዩ ጉዳዮች
3.1.1. በመንግስት ስፖንሰር አድራጊነትም ሆነ በግል ወጫቸው ትምህርታቸውን አሻሽለው ምደባ
የሚያገኙ ባለሙያዎች በስራ ላይ ያለው የምልመላና መረጣ መመሪያ የሚጋብዛቸው
ከሆነ ተጨማሪ የመቆያ ጊዜ ሳያስፈልጋቸው ለከፍተኛ የስራ ደረጃዎች በደረጃ እድገት
አግባብ ሊወዳደሩ ይችላሉ። በውድድር ወቅትም ወደ ትምህርት ከመሄዳቸው በፊት
ባለው አንድ ዓመት ውስጥ የተሞላላቸው ሥራ አፈፃፀም ይያዝላቸዋል።
3.1.2. በመንግስት ስፖንሰር አድራጊነት 2 ኛ ዲግሪና ከዚያ በላይ የትምህርት ደረጃቸውን
የሚያሻሽሉ ባለሙያዎች የሶስት እርከን ጭማሪ የሚያገኙት ትምህርታቸውን ጀምረው
እስከ ሚያጠናቅቁ ድረስ ባስተማራቸው መ/ቤት ከቆዩ ብቻ ይሆናል። ሆኖም የነበሩበትን
መ/ቤት በደረጃ ዕድገት፤ በዝውውርና በምደባ የለቀቁ ሰራተኞች/ባለሙያዎች
የተመደቡበት ፤ያደጉበት ወይም የተዛወሩበት መ/ቤት በጀት ይዞ እንዲከፍል ይደረጋል።
ሆኖም ግን ሰራተኛው ሲመደብ ፣ ሲዛወርና ደረጃ እድገት ሲያድግ የነበረበት መ/ቤት
ለተቀባይ መ/ቤት በመንግስት ስፖንሰር አድራጊነት ትምህርቱን እየተከታተለ የነበረ
ስለመሆኑ ማሳወቅ አለበት። ከላይ የተገለፀው ቢኖርም በራሱ ፈቃድ መልቀቂያ ጠይቆ
የለቀቀን ባለሙያ/ሰራተኛ አይመለከተውም።
3.1.3. በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 253/2010 አንቀጽ 96
ን/አንቀጽ 2 መሠረት ይህን መመሪያ የመለወጥ፣ የማሻሻል ወይም በሥራ ላይ በሚውልበት
ጊዜ ማብራሪያ ወይም ትርጉም የመስጠት ኃላፊነት የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ነው።
3.1.4. ሰኔ 2011 ዓ/ም ወጥቶ በሥራ ላይ የነበረው ትምህርታቸውን ያሻሻሉ ባለሙያዎች አመዳደብና
ደመወዝ አከፋፈል አፈጻጸም መመሪያና ይህንን አስመልክቶ የተላለፉ ሰርኩላሮች በዚህ
መመሪያ ተተክተዋል።
3.1.5. ይህን መመሪያ በተዛባ መልኩ ወይም ያለአግባብ የሚያስፈጽም ማንኛውም አካል ወይም
የስራ ኃላፊ አግባብ ባለው ህግ ተጠያቂ ይሆናል
3.1.6. በዚህ መመሪያ ላይ አፈፃፀም ላይ የሚኖር ቅሬታ በስራ ላይ ባለው የቅሬታ ዓቀራረብ ስነ-
ሥርዓት ተፈፃሚ ይሆናል።
3.1.7. ይህ መመሪያ ከሰኔ /2013 ዓ/ም ጀምሮ የፀና ነው።
አቶ ሙሉቀን አየሁ
የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ኮሚሽነር
116
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የፈቃድ አሰጣጥና የህክምና ማስረጃ አቀራረብ መመሪያ/የተሻሻለው/
ሰኔ 2013 ዓ.ም
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ባህር ዳር፣ ኢትዮጵያ
117
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
መግቢያ
የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 265/2011 ሲቋቋም ሊያከናውናቸው የሚገቡ
ተግባራትን መሰረት ያደረገ ተግባርና ኃላፊነት ተላብሶ እንዲንቀሳቀስ መሆኑ ይታወቃል።
ስለሆነም በተግባር ላይ ካሉት መመሪያዎች መካከል አንዱ የአመት ዕረፍት ፍቃድ አሰጣጥ የህክምና
ማስረጃ አቀራረብ መመሪያ ነው ። ሆኖም ግን ከአሁን በፊት ተግባራዊ ሲደረግ የነበረው የአመት
ዕረፍት ፍቃድ አሰጣጥ የህክምና ማስረጃ አቀራረብ መመሪያ በአግባቡ ተግባራዊ ሲደረግ የቆየ ቢሆንም
ለአፈፃፀም ግልፀኝነት የጎደላቸውና መስተካካል ያለባቸው ጉዳዮች ያሉ በመሆኑና የሰራተኞችን
ተጠቃሚነት ይበልጥ ያረጋገጠ መመሪያ ማውጣት በማስፈለጉ ይህ መመሪያ ማሻሻያ ተደርጎበታል ።
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አዋጅ 253/2010 በሚተዳደሩ መስሪያ ቤቶች ውስጥ
የሚሰሩ የመንግስት ሠራተኞች የተጣለባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት እንዲችሉ እና
በስራ የደከመ አእምሯቸው እንዲታደስ የአመት እረፍት ፈቃድ እንዲያገኙ ለማድረግ
የሕክምና ፈቃድ፣ የዓመት እረፍት ፈቃድና የልዩ ልዩ ፈቃዶች አሰጣጥና ማስረጃ
አቀራረብን ለተገልጋይ ተደራሽ ለማድረግ በማስፈለጉ፣
የመንግሥት ሠራተኞች ህመም በሚያጋጥማቸው ጊዜ ከመንግሥስትና ከግል ጤና ተቋማት
እንዲሁም ከውጭ ሐገር የሚሰጥን የህክምና ማስረጃ ተቀባይነት ላይ የነበረው አሰራር ያሉበትን
ክፍተቶች መሙላት በማስፈለጉ፣
ዓላማ
118
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የፈቃድ አሰጣጥና የህክምና ማስረጃ አቀራረብ መመሪያ/የተሻሻለው/
ክፍል 1. ጠቅላላ
1.1. አጭር ርዕስ
ይህ መመሪያ “የፈቃድ አሰጣጥና የህክምና ማስረጃ አቀራረብ መመሪያ ቁጥር 05 /2013” ተብሎ
ሊጠቀስ ይችላል።
1.2. ትርጓሜ
1.2.1. “የመንግስት መ/ቤት” ማለት ራሱን ችሎ በአዋጅ ወይም በደንብ የተቋቋመና ሙሉ በሙሉ
ወይም በከፊል በመንግስት በጀት የሚተዳደር መስሪያ ቤት ነው፣
1.2.2. “ኮሚሽን” ማለት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ነው፣
1.2.3. “የመንግስት ሠራተኛ” ማለት በመንግስት መ/ቤት ውስጥ በቋሚነት/በጊዚያዊነት ተቀጥሮ
የሚሠራ ሰው ነው፣
1.2.4. “የዓመት እረፍት ፈቃድ” ማለት አንድ የመንግሥት ሠራተኛ በስራ ወቅት የደከመ
አዕምሮውን ለማደስ እንደ አገልግሎቱ መጠን የሚሰጠው ፈቃድ ነው።
1.2.5. “ የበጀት ዘመን” ማለት ከሐምሌ 1 ቀን ጀምሮ እስከ ቀጣዩ ሰኔ 30 ቀን ድረስ ያለውን የሥራ
ዘመን የሚያመለከት ነው።
1.2.6. “የአገልግሎት ዘመን” ማለት አንድ የመንግሥት ሠራተኛ ከተቀጠረበት ቀን ጀምሮ አገልግሎት
መስጠት እስከሚያቋርጥበት ቀን ድረስ ያለውን የአገልግሎት ጊዜ ነው።
1.2.7. “የአገልግሎት ዘመን መቋረጥ” ማለት የመንግሥት ሠራተኛው አገልግሎት በጡረታ፣
በራስ ፈቃድ፣ በህመም፣ በችሎታ ማነስ፣ በእስራት ፣ በቅነሣ ፣ በሞት ምክንያት
ስራን ማቋረጥ ነው።
119
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
1.2.8. “በራስ ፈቃድ የአገልግሎት ዘመን መቋረጥ” ማለት ሠራተኛው ከሚሠራበት መ/ቤት መልቀቂያ
ጠይቆ መልቀቂያ የወሰደ ወይም በስራ ገበታው ላይ ባለመገኘቱ በጥሪ ማስታወቂያ
እንዲሰናበት የተደረገ ሰው ነው።
1.2.9. “ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት” ማለት በህመም፣ በእሥራት፣ ወይም በሌላ ምክንያት መደበኛ
ሥራን ለማከናወን አለመቻል ነው።
1.2.10. “የህክምና ማስረጃ’’ ማለት በሀገር ውስጥና ከውጪ ሀገር ህጋዊ ፈቃድ ከተሰጠው የህክምና
ተቋም የሚሠጥ የህክምና የምስክር ወረቀት ነው።
1.2.11. “የመንግሥት የጤና ተቋም” ማለት ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል በመንግሥት በጀት
የሚተዳደር የጤና አገልግሎት መስጫ ተቋም ነው።
1.2.12. “የሕክምና ቦርድ ማስረጃ ” ማለት ታካሚዎች በሪፈራል/ስፔሻላይዝድ/ ወደ መንግስት
ሆስፒታሎች ተልከው ከታከሙ በኋላ በህክምና ቦርድ በሦስት ሀኪሞች ፊርማ ተደግፎ
የሚሰጥ ማስረጃ ነው።
1.2.13. “የሕመም ፈቃድ” ማለት አግባብ ካለው የጤና ተቋም ተኝቶ ወይም በተመላላሽ ለመታከምና
ለማገገም እንደበሽታው ሁኔታ የሚሰጥ የህመም ፈቃድ ነው።
1.2.14. “የግል የጤና ተቋም” ማለት ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ወይም ከክልሉ ጤና ጥበቃ ቢሮ
በተሰጠ ፈቃድ የህክምና አገልግሎት የሚሰጥ የጤና ድርጅት ነው።
1.2.15. “የአሳካሚ የህመም ፈቃድ“ ማለት አንድ ሴት የመንግሥት ሠራተኛ አንድ ዓመት ያልሞላው
ጨቅላ ህፃን ሲታመምባት ማስረጃ የሚቀርብበት የአሳካሚ ፈቃድ ነው።
1.2.16. “የዓመት እረፍት ፈቃድ ማዛወር” ማለት በመንግስት መ/ቤቶች የስራ ጫና ምክንያት/ከአቅም
በላይ የሆነ ችግር ሲያጋጥም/ የነበረውን የዓመት እረፍት ፈቃድ ወደ ቀጣዩ በጀት
ዓመት ማዛወር ነው።
1.2.17. “አስገዳጅ የሆነ ምክንያት” ማለት መ/ቤቱ ባጋጠመው አስቸኳይ ስራ ምክንያት ሰራተኛው
የዓመት ዕረፍት እንዳይወስድ የሚከለከልነት ነው።
1.3. ማንኛውም በወንድ ፃታ የተገለፀው የሴት ፆታንም ያካትታል።
1.4. የመመሪያው ተፈጻሚነት ወሰን፡- ይህ መመሪያ ተፈፃሚነት የሚኖረውበአማራ ብሄራዊ
ክልላዊ መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 253/2010 በሚተዳደሩ መ/ቤቶችና
ሰራተኞች ላይ ነው።
120
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የፈቃድ አሰጣጥና የህክምና ማስረጃ አቀራረብ መመሪያ/የተሻሻለው/
2.1.1. ማንኛውም አዲስ ተቀጣሪ የመንግሥት ሠራተኛ የአስራ አንድ ወራት አገልግሎት
ከመስጠቱ በፊት የዓመት እረፍት ፈቃድ የማግኘት መብት የለውም።
2.1.2. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 2.1.1 የተገለጸዉ ቢኖርም በአንድ የሲቪል ሰርቪስ ተቋም ከአንድ
አመት በላይ አገልግሎ እንደ አዲስ ወደ ሌላ የሲቪል ሰርቪስ ተቋም የተቀጠረ እና
ያልተጠቀመበትን ህጋዊ የአመት እረፍት ፈቃድ ከነበረበት መስሪያ ቤት ያቀረበ ሠራተኛ
አዲስ በተቀጠረበት መስሪያ ቤት የ 11 ወር ቆይታ ሳይጠበቅበት የሙከራ ጊዜውን
እንዳጠናቀቀ ከመቀጠሩ በፊት የነበረውን የመጨረሻ የአንድ አመት ፈቃድ ብቻ
መጠቀም ይችላል::
2.1.3. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 2.1.1 የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ አንድ የመንግሥት ሠራተኛ
አሥራ አንድ ወሩን ካጠናቀቀ በኋላ በተቀጠረበት በጀት ዓመት ለሰጠው አገልግሎት
የዓመት እረፍት ፈቃዱ በአገልግሎቱ መጠን ተሰልቶ እንዲሰጠው ይደረጋል።
2.1.4. አንድ አመት ያገለገለ የመንግስት ሠራተኛ 20 የስራ ቀናት የአመት እረፍት ፈቃድ
ያገኛል። ከአንድ ዓመት በላይ ያገለገለ ሠራተኛ ለእያንዳንዱ ተጨማሪ ዓመት አንድ የሥራ
ቀን እየታከለበት የዓመት እረፍት ፈቃድ ያገኛል። ሆኖም ለአንድ የበጀት ዓመት
የሚሰጠው የዓመት ዕረፍት ፈቃድ በጠቅላላው ከ 30 የሥራ ቀናት መብለጥ የለበትም።
2.1.5. ከላይ በንኡስ አንቀፅ 2.1.4 የተገለፀው ቢኖርም አንድ የመንግስት ሠራተኛ የተዛወረ
(የተጠራቀመ) የአመት እረፍት ፈቃድ ካለው በአንድ የበጀት አመት ከ 30 ቀን በላይ
መጠቀም ይችላል።
2.1.6. አንድ ጊዜያዊ ሠራተኛ ለቋሚ የመንግሥት ሠራተኛ የተፈቀደውን የዓመት እረፍት
ፈቃድ የማግኘት መብት አለው።
2.2.1. ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ የዓመት እረፍት ፈቃድ የመጠየቅ እና የመውሰድ መብት
አለው።
121
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
2.3.1. የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ ቡድን በየበጀት አመቱ መጀመሪያ እስከ ሐምሌ 30
ቀን ባለው ጊዜ የመንግሥት ሠራተኛው የዓመት እረፍት ፈቃዱን የሚጠቀምበት
ፕሮግራም መሙያ ቅጽ ለኃላፊ ወይም ም/ኃላፊ/ ለእያንዳንዱ ዳይሬክቶሬት/ቡድን
በመላክ ተሞልቶ እንዲላክለት ያደርጋል ።
2.3.2. ተጠሪነታቸዉ ለመ/ቤት ኃላፊ ወይም ም/ኃላፊ የሆኑ ሠራተኞች በኃላፊያቸዉ/
ም/ኃላፊያቸው/በተወካይ ኃላፊያቸው አማካኝነት፣ በዳይሬክቶሬት/በቡድን የታቀፉ
ሠራተኞች ደግሞ በዳይሬክተራቸው/ቡድን መሪያቸው አማካኝነት ሠራተኞች የዓመት
እረፍት ፈቃዳቸውን የሚጠቀሙበትን ጊዜ እንዲሞሉ በማድረግ ስምምነት ላይ
የደረሱበትን አማራጭ ከሠራተኞቻቸው ጋር በመፈራረም መረጃውን የሰው ሀብት
አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ ቡድን እስከ ሐምሌ 30 ድረስ እንዲደርስ ያደርጋሉ ።
2.3.3. ሠራተኞች ባቀረቡት ፕሮግራም መሠረት የዓመት እረፍት ፈቃድ ጥያቄያቸውን ማቅረብና
መጠቀም ቢችሉም አስቀድመው ያሳወቁትን ፕሮግራም ከአቅም በላይ በሆነ ችግር
ምክንያት መለወጥ ቢፈልጉ ተጠሪነታቸዉ ለመ/ቤት ኃላፊ/ም/ኃላፊ የሆኑ ሠራተኞች
ከኃላፊያቸዉ/ተወካይ ኃላፊያቸዉ፣ በዳይሬክቶሬት/በቡድን የታቀፉ ሠራተኞች ደግሞ
ከዳይሬክተራቸው/ቡድን መሪያቸው ጋር በመስማማት የበጀት
122
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የፈቃድ አሰጣጥና የህክምና ማስረጃ አቀራረብ መመሪያ/የተሻሻለው/
አመቱ ሳይቀየር የዓመት እረፍት ፈቃድ መውጫ ጊዜያቸውን ሊቀይሩ ወይም ሊያሻሽሉ
ይችላሉ።
2.3.4. አስገዳጅ በሆነ ምክንያት የአንድ በጀት አመት ወደ ሁለተኛው ፣ የሁለተኛው በጀት
ዓመት ፈቃድ ወደ ሶስተኛው ዓመት የተላለፈለት ሰራተኛ እየሰራበት ያለውን የበጀት
ዓመት ጨምሮ የሁለት/የሶስት ተከታታይ ዓመታት ፈቃዱን በአንድ ዓመት ውስጥ
በፕሮግራም የመጠቀም መብት አለው። ሆኖም ከሦስቱ አመት የመጀመሪያውን ዓመት(ወደ
4 ኛው በጀት ዓመት የማይዛወረውን) የአመት እረፍት ፈቃድ መጠቀም የሚችለው
በመጨረሻው በጀት ዓመት እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ ብቻ ነው።
2.3.5. በመንግሥት መ/ቤት ውስጥ የሚገኙ የመንግሥት ሠራተኞች የዓመት እረፍት ፈቃዳቸውን
በፕሮግራም መጠቀም አለባቸው።
2.3.6. የዓመት ዕረፍት የወሰደው ሰራተኛ የዕረፍት ቆይታውን ሳይጨርስ መ/ቤቱ ለአስቸኳይ ስራ
ቢፈልገው ዕረፍቱን አቋርጦ እንዲገባ ይደረግና የተፈለገበት ስራ ሲጠናቀቅ ሰራተኛው
የዓመት ዕረፍት መውሰድ ከፈለገ የዓመት ዕረፍቱ የሚቀጥል ይሆናል ። ሆኖም ግን
ሰራተኛው የዓመት ዕረፍት መውሰድ ካልፈለገ ያልተጠቀመበት የዓመት ዕረፍት ቀናት
የሚመለስለት ይሆናል ።
2.3.7. ሠራተኛው ፈቃዱን በሚወስድበት ጊዜ በእረፍት ላይ የሚቆይበትን የወር ደመወዝ በቅድሚያ
ሊወስድ ይችላል።
2.3.8. የበጀት ዓመቱ ከመጠናቀቁ በፊት ፈቃድ ወስዶ አገልግሎቱን በገዛ ፈቃዱ ያቋረጠ የመንግሥት
ሠራተኛ አገልግሎት ያልሰጠበት ጊዜ ታስቦ በፈቃድ ላይ እያለ የተከፈለውን ደመወዝ
እንዲመልስ ይደረጋል።
2.3.9. ተሿሚዎች ከኃላፊነት ተነስተዉ የመንግስት ሠራተኛ ሆነዉ ከተመደቡበት እና
መ/ራን፣ር/መ/ራንና የትምህርት ሱፐርቫይዘሮች በዝውውር ወደ ጽ/ቤት ከመጡበት ጊዜ
ጀምሮ የአመት እረፍት ፈቃድ የማግኘት መብት አላቸዉ። የአመት እረፍት ፍቃድ
አሰጣጡም በበጀት አመቱ የሚያገለግሉበትን ጊዜ ያህል ታስቦ ይሆናል።
2.4.1. የዓመት እረፍት ፈቃድ ወደ ሚቀጥለው በጀት ዓመት የሚዘዋወረው ሠራተኛው የዓመት
እረፍት ፈቃዱን በሥራ ጫና ምክንያት መጠቀም ባለመቻሉ ተጠሪነታቸዉ ለመ/ቤት
ኃላፊ የሆኑ ሠራተኞች የመ/ቤቱ የበላይ ኃላፊ ወይም ምክትል ኃላፊ
123
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
124
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የፈቃድ አሰጣጥና የህክምና ማስረጃ አቀራረብ መመሪያ/የተሻሻለው/
ዓመት እረፍት ፈቃድ ሙሉ በሙሉ በገንዘብ ተለውጦ እንዲሰጠው የመጠየቅ መብት ያለው
ሲሆን አሰሪው መ/ቤቱም የሠራተኛውን የዓመት እረፍት ፈቃድ ጥያቄውን ተቀብሎ
ማስተናገድ ይኖርበታል። በስራ ጫና ምክንያትም ወደ 3 ኛው የበጀት ዓመት የተዛወረውን
የአንድ ዓመት የዓመት እረፍት ፈቃድ በገንዘብ ተለውጦ የሚሰጠው ይሆናል ። ሆኖም
ግን ከስራ ጫና ውጭ ወደ 3 ኛው የበጀት ዓመቱ የተዛወረ የዓመት ዕረፍት ፈቃድ ወደ
ገንዘብ ተቀይሮ እንዲሰጥ አይደረግም።
3.1.3. አገልግሎቱ የተቋረጠ የመንግስት ሠራተኛ የዓመት እረፍት ፈቃዱ ለአንድ ወይም ለሁለት
ተከታታይ የበጀት ዓመት በመንግሥት ሥራ ምክንያት በመ/ቤቱ የበላይ ኃላፊ ወደ
ሁለተኛው ወይም ሶስተኛ የበጀት ዓመት የተላለፈ ከሆነ የዓመት እረፍት ፈቃዱ ሙሉ
በሙሉ በገንዘብ ተቀይሮ ለራሱ ወይም ለተተኪዎች እንዲሰጥ ይደረጋል። ሆኖም
ሥራውን በገዛ ፈቃዱ ለቆ ወደ ሌላ የሲቪል ሰርቪስ መ/ቤት የተቀጠረ ሠራተኛ ከሆነ ግን
ፈቃዱን በገንዘብ ተቀይሮ የሚሰጠው የዓመት እረፍት ፈቃድ አይኖርም። ነገር ግን ወደ
ሌላ የሲቪል ሰርቪስ መ/ቤት የማይቀጠር ከሆነ ያልተጠቀመበት ዓመት እረፍት ወደ
ገንዘብ ተቀይሮ ይሰጠዋል።
3.1.4. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 3.1.3 የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ ሠራተኛው በዝውውር ወይም
በምደባ ወይም በድልድል ወይም በደረጃ እድገት ይሰራበት የነበረውን መ/ቤት ለቆ ወደ ሌላ
መ/ቤት የሚዛወር ወይም የሚመደብ ወይም የሚያድግ ከሆነ ሠራተኛው ወደ ተዛወረበት
ወይም ወደ ተመደበበት ወይም ወደ አደገበት ያልተጠቀመበትን የዓመት እረፍት ፈቃድ
ከማስተላለፍ ባሻገር የዓመት እረፍት ፈቃዱ በገንዘብ የሚቀየርበት አግባብ አይኖርም።
3.1.5. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 3.1.4 የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ ሠራተኛው የሞላው የፈቃድ
ፕሮግራም ሳይደርስ ወይም ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት አሳልፎት እያለ ስራው ከተቋረጠ
በበጀት ዓመቱ ውስጥ የሰራበት ጊዜ ታስቦ በገንዘብ ተቀይሮ ይሰጠዋል። ነገር ግን
ሠራተኛው በራሱ ፈቃድ መልቀቂያ ጠይቆ በሌላ የሲቪል ሰርቪስ ተቋም የሚቀጠር ከሆነ
በመስሪያ ቤቱ የበላይ ኃላፊ ውሳኔ የአመት እረፍት ፈቃዱ ወደ ሚቀጥለው በጀት ዓመት
የተዛወረ ስለመሆኑ በክሊራንሱ ላይ መገለፅ ይኖርበታል።
3.1.6. አገልግሎቱ የተቋረጠ የመንግስት ሰራተኛ የዓመት እረፍት ፈቃዱ ወደ ገንዘብ ሲቀየር
ለሠራተኛው የሚከፈለው ያልተጣራ የወር ደመወዙ በ 30 ቀኖች በማካፈል ሰራተኛው
ባለው የዓመት እረፍት በስራ ቀኖች ብቻ ተባዝቶ የሚገኘው ገንዘብ ነው።
125
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
3.1.7. የአንድ የዓመት ዕረፍት ፈቃዱ ወደ ሦስተኛው በጀት ዓመት የተዛወረለት በስራ ላይ ያለ
መንግሥት ሠራተኛ ፈቃዱ በገንዘብ ሲለወጥ ወደ የ 3 ኛው በጀት ዓመት የአንድ ዓመት
እረፍት ቀናቱ ብቻ ያልተጣራ የወር ደመወዙ በ 30 ቀኖች በማካፈል ሰራተኛው ባለው
የዓመት እረፍት በስራ ቀኖች ብቻ ተባዝቶ የሚገኘው ገንዘብ ነው።
3.1.8. በአንቀጽ 2.4 ንዑስ አንቀጽ 2.4.2 መሠረት ወደ 3 ኛ በጀት ዓመት የተዛወረው የአንድ ዓመት
እረፍት ፈቃድ ሙሉ በሙሉ በገንዘብ ተለውጦ ለሰራተኛው እንዲሰጥ ለማድረግ መ/ቤቱ
በበጀት ዓመቱ በጀት መያዝ ይጠበቅበታል። ሆኖም ግን በበጀት ዓመቱ ለዚሁ ጉዳይ የተያዘ
በጀት ከሌለ በሚቀጥለው በጀት ዓመት ታስቦ ለሰራተኛው የሚከፈል ይሆናል።
3.2.1. የመንግሥት ሠራተኛው በሞት ሲለይ በህጋዊ መንገድ እየተዛወረለት ያልወሰደው የዓመት
እረፍት ፈቃድ እና በሞት በተለየበት አመት ያልወሰደው የአመት እረፍት በሞት
እስከተለየበት ድረስ ያለው ታስቦ በሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ ቡድን
እየተረጋገጠ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ወደ ገንዘብ ተቀይሮ በህይወት ሳለ በጽሁፍ
ላሳወቃቸው የትዳር ጓደኛው ወይም በስሩ ይተዳደሩ ለነበሩ ቤተሰቦቹ የሚከፈል
ይሆናል። ሆኖም በጽሁፍ ያሳወቃቸው በሌሉበት ሁኔታ ለህጋዊ ወራሾች እንዲሰጥ
ይደረጋል።
3.2.2. በሞት የተለየ የመንግሥት ሠራተኛ በዓመት እረፍት ላይ የነበረ ከሆነ እና የዓመት እረፍት
ሲወጣ በቅድሚያ የወሰደው የወር ደመወዝ ካለ ለቤተሰቦቹ ከሚከፈል የ 3 ወር ደመወዝ
ላይ እንዲመለስ አይጠየቅም።
126
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የፈቃድ አሰጣጥና የህክምና ማስረጃ አቀራረብ መመሪያ/የተሻሻለው/
3.3.1.2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (3.3.1.1) የተመለከተው ፈቃድ እንደ ህመም ፈቃድ
አይቆጠርም።
3.3.1.3. ነፍሰጡር የሆነች የመንግሥት ሠራተኛ መውለጃዋ ሲደርስ እወልዳለሁ ብላ ከገመተችበት
ቀን በፊት 30 ተከታታይ ቀናት የቅድመ ወሊድ ፈቃድ፣ እንዲሁም ስትወልድ ከወለደችበት
ቀን ጀምሮ 90 ተከታታይ ቀናት፣ በአጠቃላይ 120 ተከታታይ ቀናት ደመወዝ የሚከፈልበት
የወሊድ ፈቃድ ይሰጣታል።
3.3.1.4. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (3.3.1.3) መሠረት ሠራተኛዋ የተሰጣት የቅድመ ወሊድ ፈቃድ
ከማለቁ በፊት ከወለደች ያልተጠቀመችበትን ቀሪ የቅድመ ወሊድ ፈቃድ ከወለደች በኋላ
እንድትጠቀምበት ይደረጋል።
3.3.1.5. ሠራተኛዋ የወሰደችው የቅድመ ወሊድ ፈቃድ ሲያልቅ ያልወለደች እንደሆነ እስከ
ምትወልድበት ቀን ድረስ ባሉት የሥራ ቀናት የምትቆይበት ዕረፍት በበጀት ዓመቱ ካላት
የዓመት ዕረፍት ፈቃድ ወይም በበጀት ዓመቱ የዓመት ፈቃድ የሌላት እንደሆነ ከሚቀጥለው
የበጀት ዓመት የዕረፍት ፈቃዷ ይተካል።
3.3.1.6. ሠራተኛዋ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (3.3.1.3) የተወሰነውን የወሊድ ፈቃድ ከጨረሰች
በኋላ ብትታመምና ተጨማሪ ፈቃድ የሚያስፈልጋት መሆኑ በሀኪም ከተረጋገጠ በአዋጅ
ቁጥር 253/2010 አንቀጽ 42(1) በተደነገገው መሠረት የሕመም ፈቃድ መውሰድ
ትችላለች።
3.3.1.7. ማንኛዋም ስድስት ወር የሞላት ነፍሰጡር የሆነች የመንግስት ሠራተኛ የቅድመ
ወሊድ ፈቃድ ከመውሰዷ በፊት ጽንሱ የተቋረጠባት ከሆነ ይህንኑ የሚያረጋግጥ የህክምና
ማስረጃ ስታቀርብ የ 60 ቀን የድህረ ወሊድ ፈቃድ ይሰጣታል።
3.3.1.8. የቅድመ ወሊድ ፈቃድ ከወሰደች በኋላ የጽንስ መቋረጥ ካጋጠማት የወሰደችው የቅድመ
ወሊድ ፈቃዷ ተቋርጦ በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ (3.3.1.3) የተመለከተው የ 90 ቀን
የድህረ ወሊድ ፈቃድ ይሰጣታል።
3.3.1.9. ከሦስት እስከ ስድስት ወር ባለው የእርግዝና ጊዜ ውስጥ የፅንስ መቋረጥ ያጋጠማት
የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ የሚከፈልበት 30 ተከታታይ ቀን ፈቃድ ይሰጣታል።
3.3.1.10. ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ የትዳር ጓደኛው ስትወልድ ደመወዝ የሚከፈልበት
10 የሥራ ቀን ፈቃድ ይሰጠዋል።
127
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
3.3.2.1. ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ ሲያገባ 3 የሥራ ቀናት የጋብቻ ፈቃድ ከደመወዝ ጋር
ይሰጠዋል።
3.3.2.2. ማንኛውም የጊዜያዊ ሠራተኛ ሲያገባ ለቋሚ የመንግሥት ሠራተኛ የተሰጠው መብት
ይኖረዋል።
3.3.3.1. ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ የትዳር ጓደኛ፣ተወላጅ፣ ወላጅ ወይም እስከ ሁለተኛ ደረጃ
የሚቆጠር የሥጋ ወይም የጋብቻ ዘመድ የሞተበት እንደሆነ ደመወዝ የሚከፈልበት 3
ተከታታይ ቀናት የሐዘን ፈቃድ ይሰጠዋል።
3.3.3.2. ሠራተኛው በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ /1/ ከተመለከቱት ውጭ የቅርብ ዘመድ ወይም
ወዳጅ የሞተበት እንደሆነ ደመወዝ የሚከፈልበት የአንድ ቀን የሐዘን ፈቃድ ይሠጠዋል።
ሆኖም በዚህ ምክንያት የሚሠጥ የሐዘን ፈቃድ በአንድ የበጀት ዓመት ውስጥ ከ 6 ቀናት
መብለጥ የለበትም።
3.3.3.3. ማንኛውም የጊዜያዊ ሠራተኛ የትዳር ጓደኛ፣ተወላጅ፣ ወላጅ ወይም እስከ ሁለተኛ
ደረጃ የሚቆጠር የሥጋ ወይም የጋብቻ ዘመድ የሞተበት እንደሆነ ለቋሚ የመንግሥት
ሠራተኛ የተሰጠው መብት ይኖረዋል።
128
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የፈቃድ አሰጣጥና የህክምና ማስረጃ አቀራረብ መመሪያ/የተሻሻለው/
4.1.1. የመንግሥት ክሊኒኮች በክልል ደረጃ ያለው የፖሊስ ክሊኒክ የማረሚያ ቤት ክሊኒክ
እና በዚሁ ደረጃ በመንግስት መ/ቤት ያሉ ክሊኒኮች፡-
በተቋማቸው ለታየ ታካሚ ቢበዛ እስከ 3 ቀናት ፈቃድ ሊሰጡ ይችላሉ። ህመምተኛው
ካልተሻለውና ተጨማሪ የህመም ፈቃድ ማስረጃ መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከበቂ
ማብራሪያ ጋር 3 ቀናት ተጨማሪ ፈቃድ ሊሰጡ ይችላሉ።
4.1.2. ጤና ጣቢያዎች/ የቤተሰብ መምሪያ ክሊኒኮች/ሜሪስቶፕስ፡-
የህክምና አገልግሎት ለተሰጠው ታካሚ የህመም ፈቃድ መስጠት ካስፈለገ ቢበዛ እስከ 1 ዐ ቀናት
የሚደርስ ፈቃድ ሊሰጡ ይችላሉ። ህመምተኛው ካልተሻለውና ተጨማሪ የህመም ፈቃድ ማስረጃ
መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከበቂ ማብራሪያ ጋር ለተከታታይ 5 ቀናት ፈቃድ በመጨመር በድምሩ
የ 15 ቀናት ፈቃድ ሊሰጡ ይችላሉ።ይሁን እንጅ፡-
ሀ. በጤና ጣቢያው የሚሰጠው የሕመም ፈቃድ በጤና መኮንን ቢ.ኤስ.ሲ ነርስ ወይም ሃኪም
ባለበትና ክትትል ባደረገበት ሁኔታ ሊሆን ይገባል።
129
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
በተቋማቸው ለታዬ ታካሚ ቢበዛ የሶስት ቀናት ፈቃድ መስጠት የሚችሉ ሲሆን ለታካሚው ተጨማሪ
ፈቃድ መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ሌላ ተጨማሪ ሦስት ቀናት መስጠት ይችላሉ፣
የህክምና አገልግሎት ለተሰጠው ታካሚ የህክምና ፈቃድ መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ እስከ 5
ቀናት የሚደርስ የህመም ፈቃድ ሊሰጡ የሚችሉ ሲሆን ታካሚው ሊሻለው ካልቻለና ተጨማሪ ፈቃድ
መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ከበቂ ማብራሪያ ጋር ሌላ 3 ቀናት በማከል በድምሩ እስከ
8 ቀናት ድረስ መስጠት ይችላሉ
አገልግሎት ለሰጡት ታካሚ የመንግሥት ሠራተኛ የህመም ፈቃድ መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ
እስከ 1 ዐ ቀናት የሚደርስ የህመም ፈቃድ ሊሰጡ የሚችሉ ሲሆን ታካሚው ሊሻለው ካልቻለና
ተጨማሪ ፈቃድ መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ 5 ቀናት በመጨመር በድምሩ እስከ 15 ቀናት
ድረስ ሊሰጡ ይችላሉ፣
ለታከመ የመንግሥት ሠራተኛ የህመም ፈቃድ መስጠት አስፈላጊ ከሆነ እስከ 15 ቀን የሚደርስ የህመም
ፈቃድ መስጠት ይቻላል። ህመምተኛው ካልተሻለውና ተጨማሪ የፈቃድ ማስረጃ መስጠት አስፈላጊ
ሆኖ ከተገኘ ከበቂ ማብራሪያ ጋር በተከታታይ 15 ቀናት ፈቃድ በመጨመር በጠቅላላው 3 ዐ ቀናት
ፈቃድ መስጠት የሚቻል ሲሆን በተጨማሪ የሚሰጠው የህመም ፈቃድ ተቀባይነት የሚኖረው
በስፔሻሊስት ወይም በቋሚ የሆስፒታሉ ሀኪም ሲፈረም ብቻ ነው።
አገልግሎት ለተሰጠው ታካሚ የህመም ፈቃድ መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በመንግስት ሰራተኞች
አዋጅ ቁጥር 253/2010 አንቀጽ 43 ንዑስ አንቀጽ 1 መሠረት የህክምና ፈቃድ መስጠት ይችላሉ።
አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኙትም ታማሚው በጡረታ እንዲገለል ውሳኔ አስተላልፈው ለአሰሪ መስሪያ ቤቱ
ማሳወቅ ይችላሉ።
130
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የፈቃድ አሰጣጥና የህክምና ማስረጃ አቀራረብ መመሪያ/የተሻሻለው/
4.1.8. በውጭ ሀገር የሚገኙ የጤና ተቋማት የሚሰጧቸው የህክምና ማስረጃዎች የጤና ጥበቃ
ሚ/ር በሚሰጠው አቻ ግመታ መሰረት በአገር ውስጥ ካሉ የመንግስትም ሆነ የግል ጤና
ተቋማት የሚሰጧቸው የህክምና ማስረጃዎች በሚስተናገዱበት አግባብ እኩል ተቀባይነት
ይኖራቸዋል።
131
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ክፍል 6. ልዩ ልዩ ጉዳዮች
6.1 በዕረፍት ላይ ያለ የመንግስት ሰራተኛ ካልሆነ በስተቀር የህክምና ማስረጃ ተቀባይነት ሊኖረው
የሚችለው በቅድሚያ የመንግስት ሰራተኛው በሚሰራበት የስራ ቦታ አቅራቢያ ከሚገኝ
የመንግስት የህክምና ተቋም ሪፈር ተደርጎ ወደ መንግስት ከፍተኛ የህክምና ተቋም ህክምና
አገልግሎት እንዲያገኝ ሲደረግ ነው።
6.2 በዚህ መመሪያ ውስጥ ያልተካተቱ ፈቃዶች በመንግሥት መ/ቤቶች ተቀባይነት አይኖራቸውም።
6.4 ሀሰተኛ የህክምና ማስረጃ የሚያቀርብ ሰራተኛ ማስረጃው ከመሰረዙ በተጨማሪ ተጠያቂ
የሚሆን ሆኖ ከሙያው ሥነ-ምግባር ውጭ ተገቢ ያልሆነ የህክምና ማስረጃ የሚሰጥ የጤና
ባለሙያ ተጠያቂ ያደርጋል።
132
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የፈቃድ አሰጣጥና የህክምና ማስረጃ አቀራረብ መመሪያ/የተሻሻለው/
6.6 የሚሰጠው የሕክምና ፈቃድ ተከታታይና ቅዳሜና እሁድን እንዲሁም ሌሎች የበዓላት
ቀናትን ያካትታል።
6.7 ታካሚዎች የሚያቀርቡት የህክምና ማስረጃ የሰራተኛው የቅርብ ሀላፊ ካየው በኋላ በክልል
በሰው ኃብት አስተዳደር ዳይሮክተሬት በሬጆፖሊታን ከተሞች፣በዞን፣ በወረዳ፣ በመካከለኛ
ከተማ በአንስተኛ ከተማ፣ በክ/ከተማና በሌሎች ከተማ አስተዳደሮች ደግሞ በሰው ኃብት
አስተዳደር ሠራተኞች አማካኝነት ተረጋግጦ ከሠራተኛው የግል ማህደር እንዲቀመጥ
ይደረጋል።
6.8 በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 253/2010 አንቀጽ 96
ንዑስ አንቀጽ 2 መሠረት ይህን መመሪያ የመለወጥ፣ የማሻሻል ወይም በሥራ ላይ
በሚውልበት ጊዜ ማብራሪያ ወይም ትርጉም የመስጠት ኃላፊነት የሲቪል ሰርቪስ
ኮሚሽን ነው።
6.9 በሰኔ ወር 2011 ዓ/ም ወጥቶ በሥራ ላይ የነበረው የፈቃድ አሰጣጥና ማስረጃ አቀራረብ
መመሪያና ይህንን አስመልክቶ የተላለፉ ሰርኩላሮች በዚህ መመሪያ ተተክተዋል።
6.10 ይህን መመሪያ በተዛባ መልኩ ወይም ያለአግባብ የሚያስፈጽም ማንኛውም አካል ወይም የስራ
ኃላፊ አግባብ ባለው ህግ ተጠያቂ ይሆናል
6.11 በዚህ መመሪያ አሰራር ላይ የሚኖር ቅሬታ በስራ ላይ ባለው የቅሬታ አቀራረብ
ሥርዓት መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል::
አቶ ሙሉቀን አየሁ
የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ኮሚሽነር
133
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
አባሪ 4 ተቀጽላ-1
የሠራተኞች የዓመት ፈቃድ መጠየቂያ ቅጽ፣
ሀ/ ፈቃድ ጠያቂ፣
ስም የአገልግሎት ዘመን ቀደምሲል ለመ/ቤቱ
ባቀረብኩት የዓመት እረፍት ፈቃድ መውጫ ፕሮግራም መሠረት ከ ዓ.ም
የዓመት እረፍት ፈቃዴ ከ ዓ/ም እስከ ዓ.ም ድረስ ለ-------ቀናት
የሙሉ ቀን/የግማሽ ቀን ፈቃድ እንዲሰጠኝ እጠይቃለሁ። ለስራ ብፈለግ በ-------------
------ ከተማ----------------------------ቀበሌ ----------------------- ስልክ ቁጥር አድራሻ
የምገኝ መሆኔን እገልፃለሁ።
የጠያቂው ፊርማ ቀን
ለ/ ፈቃድ ሰጪ
ሠራተኛው ያቀረቡት የዓመት እረፍት ፈቃድ ጥያቄ አስቀድመው ባሣወቁት ፕሮግራም
መሠረት ስለሆነ ከ ቀን ዓ.ም ጀምሮ የ
ቀን የዓመት እረፍት የሙሉ ቀን/የግማሽ ቀን ፈቃዳቸው እንዲሰጣቸው ተስማምቻለሁ።
የቅርብ ኃላፊ /ሂደት መሪ/አስተባባሪ ስም ፊርማ ቀን
ሐ/ ሠራተኛው ያቀረቡት የዓመት እረፍት ፈቃድ ጥያቄ አስቀድመው ባሣወቁት
ፕሮግራም መሠረት ቢሆንም የሥራ ሂደቱ ካለበት ወቅታዊና አስቸኳይ ሥራ አኳያ
የዓመት እረፍት ፍቃዳቸውን መጠቀም ስለማይችሉ በዚህ የበጀት ዓመት ወደ-----
------------ ወር/----------------ዓ.ም እንዲዛወርላቸው ወስኛለሁ።
የቅርብ ኃላፊ /ሂደት መሪ/አስተባባሪ ስም ፊርማ
ቀን
መ/ ሠራተኛው ያቀረቡት የዓመት እረፍት ፈቃድ ጥያቄ አስቀድመው ባሣወቁት ፕሮግራም
መሠረት ቢሆንም የሥራ ክፍሉ ካለበት ወቅታዊና አስቸኳይ ሥራ አኳያ የዓመት
እረፍት ፍቃዳቸውን መጠቀም ስለማይችሉ ወደ ሚቀጥለው የበጀት አመት
ቢዛወርላቸው የሚል የውሳኔ አስተያየት አለኝ።
የቅርብ ኃላፊ/ሂደት መሪ/አስተባባሪ ስም ፊርማ ቀን
134
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የፈቃድ አሰጣጥና የህክምና ማስረጃ አቀራረብ መመሪያ/የተሻሻለው/
135
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
አባሪ 5 ተቀጽላ-2
ቁጥር ---------------------
ቀን -------------------------
-
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
የ ቢሮ/ኮሚሽን/ጽ/ቤት/ኤጀንሲ/ባለስልጣን/መምሪያ
የሠራተኞች የዓመት እረፍት ፈቃድ መውጫ ፕሮግራም ማሻሻያ ቅጽ
እኔ አቶ/ወ/ሮ/ወ/ሪት የተባልኩ የዚሁ
መ/ቤት ባልደረባ
ሀ/በ
ሐ/ በ
መ/ ከላይ የቀረበውን ምክንያት ከግምት ውስጥ በማስገባት የዓመት እረፍት ፈቃድ መውጫ ፕሮግራማቸው
ወደ -----------------------በጀት ዓመት እንዲዛወር ወስኛለሁ።
የመ/ቤት ኃፊ/ምክትል ኃላፊ/ተወካይ ስም
ፊርማ
ቀን
136
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የፈቃድ አሰጣጥና የህክምና ማስረጃ አቀራረብ መመሪያ/የተሻሻለው/
አባሪ 6 ተቀጽላ-3
የሠራተኛው /ዋ/ ስም
የ ……………………………….
የ ……………………………….
የ ……………………………….
137
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ሰኔ 2013 ዓ.ም
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ባህር ዳር፣ ኢትዮጵያ
138
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የሥራ ተያዥ ማቅረብ የሚያስፈልጋቸው የመንግሥት ሠራተኞች አፈጻጸም መመሪያ
መግቢያ
የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 265/2011 ሲቋቋም ሊያከናውናቸው የሚገቡ
ተግባራትን መሰረት ያደረገ ተግባርና ኃላፊነት ተላብሶ እንዲንቀሳቀስ መሆኑ ይታወቃል። ስለሆነም
በአዋጅ 253/2010 በሚተዳደሩ የመንግስት መ/ቤቶችና የመንግስት ሰራተኞች ላይ ተግባራዊ ሊደረጉ
የሚችሉ የተለያዩ ማስፈፀሚያ መመሪያዎችን ማዘጋጀትና ተግባራዊ ሲደረጉ የነበሩ መመሪያዎችን
ማሻሻል በአዋጅ ቁጥር 253/2010 አንቀፅ 96 ን/አንቀፅ 2 በተሰጠው ስልጣን መሰረት አዳዲስ
መመሪያዎችን እያዘጋጀ ለመንግስት መ/ቤቶች በማውረድ ተግባራዊነቱን በመከታተል በመደገፍ በርካታ
ስራዎችን እየሰራ ይገኛል። ስለሆነም በተግባር ላይ ካሉት መመሪያዎች መካከል አንዱ የስራ ተያዥ
ማቅረብ የሚያስፈልጋቸው የመንግሥት ሠራተኞች አፈጻጸም መመሪያ ነው ። ሆኖም ግን ከአሁን በፊት
ተግባራዊ ሲደረግ የነበረው የስራ ተያዥ ማቅረብ የሚያስፈልጋቸው የመንግሥት ሠራተኞች
አፈጻጸም መመሪያ በአግባቡ ተግባራዊ ሲደረግ የቆየ ቢሆንም ለአፈፃፀም ግልፀኝነት የጎደላቸውና
መስተካካል ያለባቸው ጉዳዮች ያሉ በመሆኑና የሰራተኞችን ተጠቃሚነት ይበልጥ ያረጋገጠ መመሪያ
ማውጣት በማስፈለጉ ይህ መመሪያ ማሻሻያ ተደርጎበታል ።
139
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ክፍል 1. ጠቅላላ
1.1. አጭር ርዕስ
1.2. ትርጓሜ
1.2.1. “የመንግሥት መ/ቤት” ማለት በየትኛውም የአስተዳደር እርከን ራሱን ችሎ በአዋጅ ወይም
በደንብ የተቋቋመ እና ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ከመንግስት በሚመደብለት በጀት
የሚተዳደር መ/ቤት ነው።
1.2.2. “የመንግስት ሠራተኛ” ማለት በየአስተዳደር እርከኑ በሚገኙ የመንግሥት መ/ቤቶች ውስጥ
በቋሚነት ወይም በጊዜያዊነት ተቀጥሮ የሚሰራ ሰው ነው።
1.2.3. “ውል ሰጭ” ማለት የዋስትና ግዴታ የሚሰጥ በየደረጃው የሚገኝ መሥሪያ ቤት ነው።
1.2.4. “ውል ተቀባይ” ማለት በውል ሰጭው መሥሪያ ቤት በዋስትና ግዴታ መቀበያ ሰነድ መሰረት
ስምምነት የሚወስድ ግለሰብ/ አካል/ ነው።
1.2.5. “ዋስ/ተያዥ” ማለት ውል ተቀባይ ሠራተኛ በውል ውስጥ በገባው ግዴታ መሠረት ሳይፈጽም
ቢቀር ወይም አፍርሶ ቢገኝ ውል ተቀባዩን ተክቶ እንደውለታው ግዴታውን ለመፈፀም
የሚገደድ ግለሰብ ወይም አካል ነው።
1.2.6. “የዋስትና መቀበያ ሰነድ” ማለት በውል ሰጭ መ/ቤት እና ውል ተቀባይ ባለሙያ/ሠራተኛ/
መካከል የሚደረገው ውል አንድ አካል ሆኖ ውል ተቀባይ በገባው ውል መሠረት ግዴታውን
በአግባቡ ሳይፈጽም ቢቀር ዋሶች በተናጠል ወይም በጋራ ዋስ የሆኑበትን የገንዘብ መጠን
ለውል ሰጭ መ/ቤት ገቢ ለማድረግ ተስማምተው የሚፈርሙበት ቅጽ ነው።
1.2.7. “የጋራ ዋስ” ማለት አንድ ባለሙያ/ሠራተኛ/ ለሚረከበው ንብረት ወይም ለሚያንቀሳቅሰው
ንብረት እንደ መያዣ የሚያገለግሉና ለሚጠፋውም ጥፋት በጋራ የሚጠየቁ የግለሰቦች ስብስብ
ማለት ነው።
1.2.8. “የተናጠል ዋስ” ማለት አንድ ሠራተኛ ከገንዘብና ንብረት ጋር ተያያዥነት ባላቸው
የስራ መደቦች ላይ ለሚረከበው ንብረት ወይም ለሚያንቀሳቅሰው ገንዘብ እንደመያዣ
140
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የሥራ ተያዥ ማቅረብ የሚያስፈልጋቸው የመንግሥት ሠራተኞች አፈጻጸም መመሪያ
141
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
2.2. በክልሉ በየደረጃው በሚገኙ የመንግሥት መ/ቤቶች ውስጥ በዋና ገንዘብ ያዥ ፣ ገንዘብ
ያዥ፣ ረዳት ገንዘብ ያዥ፣ የእለት ገንዘብ ሰብሳቢ/ተቀባይ/ ፣ ግዥ ባለሙያ ፣ ሹፌሮች/ለመኪና
ብቻ/ የስራ መደብ ላይ የሚቀጠሩ፣ የሚዛወሩና ደረጃ እድገት የሚያድጉ
ባለሙያዎች/ሰራተኞች የሚሠሩ ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ ለሚረከበው ገንዘብ
ለብር 80‚000 (ሰማንያ ሺህ ) የጋራ ዋስ የሚሆኑ የእያንዳንዳቸው የወር ደመወዝ ብር
4000 /አራት ሺህ / እና በላይ የሆኑ 2 ቋሚ ሠራተኞች/ባለሙያ/ ወይም የወር ደመወዙ
ብር 6500 /ስድስት ሺህ አምስት መቶ / እና በላይ የሆነ 1 ቋሚ
ሠራተኛ/ባለሙያ/ ወይም ግምቱ ብር 80‚000 (ሰማንያ ሺህ ) የሆነ የራሱን ወይም የሌላ
ግለሰብ ቋሚ ወይም ተንቀሳቃሽ ንብረት በዋስትና ማቅረብ /ማስያዝ/ አለበት።
2.3. በክልሉ በየደረጃው በሚገኙ የመንግሥት መ/ቤቶች ውስጥ በጥበቃ ሠራተኝነት እና በሞተረኝነት
ተሠማርቶ የሚሠራ ሠራተኛ ለብር 50‚000 ( ሃምሣ ሺህ ) የጋራ ዋስ የሚሆኑ
የእያንዳንዳቸው የወር ደመወዝ ብር 3000 /ሶስት ሺህ/ እና በላይ የሆኑ 2 ቋሚ
ሠራተኞች ወይም የወር ደመወዙ ብር 6000 /ስድስት ሺህ / እና በላይ የሆነ 1
142
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የሥራ ተያዥ ማቅረብ የሚያስፈልጋቸው የመንግሥት ሠራተኞች አፈጻጸም መመሪያ
ቋሚ ሠራተኛ ወይም ግምቱ ብር 50‚000 (ሃምሣ ሺህ ) በላይ የሆነ የራሱን ወይም የሌላ
ግለሰብ የቋሚ ወይም ተንቀሳቃሽ ንብረት በዋስትና ማቅረብ/ማስያዝ አለበት።
2.4. በክልሉ በየደረጃው በሚገኙ የመንግሥት መ/ቤቶች ውስጥ በቤተ - መፃህፍት ሠራተኝነት
የስራ መደብ ላይ ተቀጥሮ ወይም ተመድቦ የሚሠራ ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ
ለሚረከበው ንብረት ለብር 10000 (አስር ሽህ) የጋራ ዋስ የሚሆኑ የእያንዳንዳቸው
የወር ደመወዝ ብር 2500 /ሁለት ሺህ አምስት መቶ ብር/ እና በላይ የሆኑ 2 ቋሚ
ሠራተኞችን ይህ ካልሆነ የወር ደመወዙ 5000 /አምስት ሺህ ብር/ የሆነ 1 ቋሚ
ሠራተኛ ወይም ግምቱ ብር 1 ዐዐዐዐ (አስር ሺህ) የሆነ የራሱን ወይም የሌላ ግለሰብ የቋሚ
ወይም ተንቀሳቃሽ ንብረት በዋስትና ማቅረብ/ማስያዝ አለበት።
2.5. በክልሉ በየደረጃው በሚገኙ የመንግሥት መ/ቤት ውስጥ በቀያሽነት ፣ የኢ.ኮ.ቴ.
(ICT)ሰርቨር አንቀሳቃሽ ባለሙያዎች ፣ የምስልና ድምፅ ቀረፃ ሠራተኛ፣ የህትመት
ሠራተኛ፣ የሙዝየም ኃላፊ/ባለሙያ/ ተሠማርቶ የሚሠራ ሠራተኛ ለብር 60000 (
ስልሣ ሽህ) የጋራ ዋስ የሚሆኑ የእያንዳንዳቸው የወር ደመወዝ ብር 4000 /አራት ሺህ
ብር/ እና በላይ የሆኑ 2 ቋሚ ሠራተኞች ወይም የወር ደመወዙ ብር 7000 /ሰባት ሺህ
ብር/ እና በላይ የሆነ 1 ቋሚ ሠራተኛ ወይም ግምቱ ብር 60000 ( ስልሣ ሽህ) የሆነ
የራሱን ወይም የሌላ ግለሰብ ቋሚ ወይም ተንቀሳቃሽ ንብረት በዋስትና
ማቅረብ/ማስያዝ/ አለበት።
3.1.1. በዋስትና መቀበያ ሠነድ /ቅጽ/ ላይ የቀረቡት ዋሶች ውል ሰጭና ተቀባይ ባሉበት በውዴታ
እንዲፈርሙ ማድረግ አለበት።
3.1.2. የዋስትና መቀበያ ሰነዱ ከመፈረሙ በፊት ዋሶች ማሟላት ያለባቸውን ቅድመ ሁኔታዎች
ማሟላታቸውን ማረጋገጥ አለበት።
3.1.3. ባለሙያዉ/ሠራተኛው/ በስሙ የተረከበውን ገንዘብ ወይም ንብረት ያጠፋ ወይም ይዞ የተሰወረ
እንደሆነ ቀጣሪው መ/ቤት ሁኔታውን እንዳወቀ ወዲያውኑ ለዋሶች የማሳወቅ ግዴታ
አለበት።
143
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
3.2.1. ዋስ ለመሆን ፈቃደኛ የሆኑ ሰዎች በውል ሰጭ/በቀጣሪ መ/ቤት/ በኩል የተዘጋጀውን የዋስትና
መቀበያ ሰነድ /ቅጽ/ ውል ተቀባይና ውል ሰጭ ባሉበት በሙሉ ፍቃደኝነት የመፈረም ግዴታ
አለባቸው።
3.2.2. ውል ተቀባይ በስራው አጋጣሚ በእጁ የሚገባውን ንብረትም ሆነ ገንዘብ ሆነ ብሎ ይሁን
በሥራው አጋጣሚ ቢጠፋበት ወይም ይዞ ቢሰወር ዋሶች ዋስ የሆኑበትን የገንዘብ መጠን
በጋራ ወይም በተናጠል ገቢ የማድረግ ግዴታ አለባቸው።
3.2.3. ዋሶች ዋስ ስለሆኑት ባለሙያ/ሠራተኛ/ በየጊዜው እየተከታተሉና የተለየ ሁኔታ
በሚኖርበት ወቅትም ለቀጣሪው /ውል ሰጭ/ መ/ቤት የማሳወቅ ግዴታ አለባቸው።
3.2.4. ማንኛውም ዋስ መሆን የሚችል ሰው በህግ እገዳ ያልተጣለበት፣ የአእምሮ ችግር የሌለበትና
በራሱ አመዛዝኖ መወሰን የሚችል መሆን አለበት፣
3.2.5. ዋስ የሚሆነዉ ሰዉ ቋሚ ሠራተኛ የሆነና ጡረታ ለመውጣት ቢያንስ 5 ዓመት የቀረው
መሆን አለበት።
3.2.6. ዋስ የሚሆነው ሰው ቋሚ ሠራተኛ ከሆነ ደመወዙ በማንኛውም የዋስትና እዳ ያልተያዘ
መሆኑን ከሚሰራበት መ/ቤት ወይም ማስረጃ እንዲሰጥ ከተፈቀደለት ተቋም የጽሁፍ
ማረጋገጫ ማቅረብ አለበት።
3.2.7. ለዋስትና የሚቀርበው ቋሚም ሆነ ተንቀሳቃሽ ንብረት ከማንኛውም እዳ ነፃ መሆኑን በህግ
ስልጣን በተሰጠው አካል በጽሁፍ ማረጋገጫ ማቅረብ አለበት።
3.2.8. ማንኛውም ግለሰብ ለትዳር ጓደኛው/ዋ ዋስ ሆኖ መቅረብ አይችልም።
3.2.9. ለውል ተቀባይ አካል ዋስ ሆነው የሚቀርቡ ግለሰቦች ባለትዳር ከሆኑ ባለቤቶቻቸው
አብረው እንዲፈርሙ ይደረጋል።
3.2.10. ተያዥ ለሚያስፈልጋቸው የስራ መደቦች ዋስ ወይም ተያዥ የሚሆነው ሠራተኛ
ወይም ግለሰብ ከውል ሰነዱ ጋር ጉርድ ፎቶ ግራፍ ማያያዝ አለበት።
144
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የሥራ ተያዥ ማቅረብ የሚያስፈልጋቸው የመንግሥት ሠራተኞች አፈጻጸም መመሪያ
145
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
146
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የሥራ ተያዥ ማቅረብ የሚያስፈልጋቸው የመንግሥት ሠራተኞች አፈጻጸም መመሪያ
ክፍል 5. ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
5.1.1. ይህ መመሪያ ዋስትናን በሚጠይቁ የስራ መደቦች ላይ የተቀጠሩ ጊዜያዊ ቅጥር
ሠራተኞችንም ይመለከታል።
5.1.2. በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 253/2010 አንቀፅ
96/2/ መሠረት ይህን መመሪያ የመለወጥ፣ የማሻሻል ኃላፊነት ለሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
የተሰጠ ነው።
5.1.3. ዋስትና በሚጠይቁ የስራ መደቦች ላይ ተያዥ የሆነ ሰራተኛ /ባለሙያ/ የደመወዝ ለውጥ
እንዳገኙ ደብዳቤ ማስፃፍ ሳይጠበቅባቸው በአዲሱ የደመወዝ ስኬል መጠን ዋስ/ተያዥ ሆነው
እንዲቀጥሉ ይደረጋል።
5.1.4. ይህ መመሪያ ከመውጣቱ በፊት በነበረው መመሪያ ዋስ አስይዘው ስምሪት የተፈጸመላቸው
ባለሙያዎች/ሠራተኞች ሌላ አዲስ ዋስ እንዲያቀርቡ አይጠየቁም።
5.1.5. በሐምሌ ወር 2011 ዓ/ም ወጥቶ በሥራ ላይ የነበረው የሥራ ተያዥ ማቅረብ
ለሚያስፈልጋቸው የመንግሥት ሠራተኞች የወጣ መመሪያና ይህን አስመልክቶ የተላለፉ
ሰርኩላሮች በዚህ መመሪያ ተተክተዋል።
5.1.6. ይህን መመሪያ በተዛባ መልኩ ወይም ያለአግባብ የሚያስፈጽም ማንኛውም አካል ወይም
የስራ ኃላፊ አግባብ ባለው ህግ ተጠያቂ ይሆናል
5.1.7. በዚህ መመሪያ ›A99U ላይ የሚኖር p_ታ በስራ ላይ ባለው ¾p_ታ ›k^£w 4’-
ሥርዓት æt£h †A9T˛ SJT6::
5.1.8. ይህ መመሪያ ከሰኔ 2013 ዓ/ም ጀምሮ የፀና ነው።
አቶ ሙሉቀን አየሁ
የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ኮሚሽነር
147
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
በተመደቡበት የስራ መደብ ላይ በሥራ አጋጣሚ በእጃቸው የገባውን የመንግሥት ንብረት ወይም ገንዘብ
ቢያጠፋ ወይም ሌላ ጥፋት ቢሰሩ ለብር------------/
--------------------------------------------------------------------------------------------------------------------
/
ለመክፈል ግዴታ ገብቻለሁ ። ለዚህም ዋስትና የግል ንብረቴ የሆነውን -------
ተሸከርካሪ/የተሸከርካሪው ዝርዝር መረጃ ይገለጻል/ወይም መኖሪያ ቤት አድራሻ በ----------------ከተማ
ቀበሌ-------የቤት ቁጥር ---------የሆነው ንብረት በዋስትና እንዲመዘገብ ከባለቤቴ ጋር ሆነን
ተስማምተናል። ዋስትና የተሰጠበት የዚህ ውል ኮፒ አግባብ ላለው የመንግሥት መ/ቤት ወይም አካል
እንዲደርሰው ይደረጋል። /ከመኪናና ከቤት ውጭ የሆነ ንብረት በማስያዣነት ሊቀርብ ይችላል።
149
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
150
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የሰው ኃብት አስተዳደር ተግባራትን በአንድ ማዕከል አፈፃፀም መመሪያ
ሰኔ 2013 ዓ.ም
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ባህር ዳር፣ ኢትዮጵያ
151
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
æ9u=Ám
5æ/u?ek u›D9 ¾†fiÖø~ W6×ST †9vC £Sfl^£õ uFST uø£4 P£9 ¾fiø~ ኃብት
›4†4PC W^ዎ kS ›Th5A እ S4=æ^ 5†P^9ø~ የነጠላ ፑል ¾fiø~ ኃብት አስተዳደር
¾t^†2 pTC m Eø~ø~CT æt6 ¾fiø~ ኃብት ›4†4PC W^k uk5Aታ m u96î’hT
h›9 ሎ ’9 uI’ ø~99C SS †æ4Ce በነጠላ ፑል ¾fiø~ ኃብት አስተዳደር ›ThV’h
እS4=hTøን ይፈለጋል ።
እንዲሁም ¾t^†ኞችን ¾96 TUPር m የ æ£9 ›ÁÁET ›Övup እና 5?5Ak ¾fiø~ ኃብት
አስተዳደር Ñ~4PkS ›4æ6he ግልጽ ›t^Cን በ TæShh መሠረታዊ የስራ ሂደት ለውጥ ጥናትና
ለውጡን ተከትሎ እየተተገበረ ያለውን የነጥብ ስራ ምዘና ጥናት ለማስፈጸም የወጡ ደንቦችንና
የአፈጻጸም መመሪያዎችን æt£ታф æCU 1S5p የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሲቪል
ሰርቪስ ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 253/2010 አንቀፅ 96 ን/አንቀፅ 2 በተሰጠው ስልጣን መሰረት
ይህን ¾fiø~ ኃብት ›4†4PC †9v^hS በአንድ ማዕከል 5ThTøS ¾†kÒ9 የአሰራር መመሪያ
ማሻሻያ አድርጓል።
SU ææsÁ በዞንና በወረዳ ደረጃ ¾fiø~ ኃብት ›4†4PC †9v^hS በአንድ ማዕከል 5ThTøS
¾†kÒ9 ¾›ሠራር ææsÁ ቁጥር 07/2013 †w5A 5=Ök4 SkS6 ::
1.2. hCGT@
152
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የሰው ኃብት አስተዳደር ተግባራትን በአንድ ማዕከል አፈፃፀም መመሪያ
ክፍል 2. ¯STm
2.1. ¾fiø~ ኃብት ›4†4PC W^ዎ k u†øfi’~ ¾›P£99h እ Chffk w} እS4=hTø’~
uT9£9 ø~4S ¾I’ø~S ¾fiø~ ኃብት ø~Ö?ታ TT k6×@ uI’ æ6h~ uæÖkU
¾›Ñ695Ah ›fi×TS Tflfl6::
2.2. ¾W^ Sd ዎ kS TQpS hI’~ ¾fiø~ ኃብት ›4†4PC W^ዎ k uTSkp
4h^b9hф øPI’~ ›4†£fihk እS4=Ák’w5~ T9£9::
2.3. ›S9 øT ¾I’ ¾Ukk ›†£GkU እ S4=ffC uT9£9 u¾æ/u?ek ¾’u£ø~S
¾›A99U hõ†h T4k£hT ¾T@sh WC¯hS u†fl5 æ6h~ T4AS::
153
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
3.2. uFS P£9 ^£1ø~S k5ø~ ¾†Ølæ~ æ/u?ek uk=U ææsÁ ¾†k£kGh
¾fiø~ ኃብት ›4†4PC W^ዎ k ¾T˛hTø’~S1ø~ uFS P£9 v5ø~ የሲቪል
ሰርቪስ መምሪያ ø~4T u†ØØæø~ ነጠላ የሰው ኃብት አስተዳደር ቡድን ›ThV’h
’ø~ ::
3.3. uø£4 P£9 ^£1ø~S k5ø~ ¾†Ølæ~ æ/u?ek uk=U ææsÁ ¾†k£kGh
¾fiø~ ኃበት ›4†4PC W^ዎ k ¾T˛hTø’~S1ø~ uø£4 P£9 v5ø~ የሲቪል
ሰርቪስ ጽ/ቤት ø~4T u†ØØæ¨ ነጠላ የሰው ኃብት አስተዳደር ቡድን ›ThV’h
’ø~ ::
3.4. u¾P£9ø~ ¾†ØØæ~ ¾’ÖS ¾fiø~ ኃብት አስተዳደር ቡድን 5†ÖQT˛ æ/u?ek
5T˛ÁhTø~ኑት ¾fiø~ ኃብት ›4†4PC W^ ¾T˛Áስፈልጋቸው u9h በሲቪል
ሰርቪስ መስሪያቤት በኩል እየቀረበ ¾T˛ፈቀድ SIT6 ::
3.5. uk=U ææsÁ ›Sk9 6 ¾†k£kGhST 5?5Ak †æ££S ¾fiø~ ኃብት ›4†4PC
W^ዎ kS እS4=ÁhTø~S u¾†ÖQT˛ æ/u?ek ¾T˛æPuø~ የሰው ኃብት
አስተዳደር ሰራተኛ በነበረው ¾T6 ›P£99h ተከትሎ በነበረው የፑል አስተባባሪ መስሪያ
ቤት ሆኖ 5b5h hb5h 4^ዎ 1 ›Ò» ¾I’~ l£lfkm በጀት m ¾4^ hõ6/u=a/ እና
የመሳሰሉትን አገልግሎቶች በዚሁ መስሪያ ቤት አማካኝነት ያገኛል:: ውጤት ተኮርም
የሚታቀድለትና የሚሞላት ግን በነጠላ የሰው ኃብት አስተዳደር ቡድን መሪ ይሆናል ።
154
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የሰው ኃብት አስተዳደር ተግባራትን በአንድ ማዕከል አፈፃፀም መመሪያ
155
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
5.1.3. በተመደበበት መስሪያቤት ውስጥ የዲስፕሊን ግድፈት ያደረሰ ሰራተኛ ሲኖር ከሀላፊው ወይም
ከቡድኑ የደረሰውን መረጃ መሰረት በማድረግ ክስ በመመስረት ለተከሳሹ ያሳውቃል m
5.1.4. የሰው ኃብት አስተዳደር ቡድን የቅጥር፣ የዝውውር የደረጃ እድገትና የስልጠና ማስታወቂያ
ሲያወጣ የሰው ኃብት አስተዳደር ሰራተኛ ሆኖ ከሚያገለግልበት መስሪያቤት ተወዳዳሪ
ሲኖር በመመዝገብ ለቡድኑ ያሳውቃል m
5.1.5. ከተመደበበት መስሪያ ቤት ወይም ፑል ሰራተኞች የህክምና ማስረጃ ሲቀርብ
ስለትክክለኛነቱ እያረጋገጠ መረጃውን ይይዛል
5.1.6. ሰራተኛ ያለፈቃድ ከስራ ገበታው ላይ ሲጠፋ በመመሪያው መሰረት ማስታወቂያ ያወጣል
ካልተመለሰም ህጉን ጠብቆ እንዲሰናበት በማድረግ መረጃውን ለቡድኑ ያሳውቃል
5.1.7. በቡድኑ ስምሪት ተሰጥቷቸው ወደ ተመደቡበት መስሪያቤት ወይም ፑል ለሚመጡ ሰራተኞች
ሰራተኛው ከተመደበላቸው የቡድን መሪዎች ጋር በመሆን የማስተዋወቂያ ስልጠና ይሰጣል
5.1.8. በቅጥር ወይም በዝውውር ወይም በደረጃ እድገት የሚሸፈኑ መደቦችን በጀት ያላቸው
ስለመሆኑ ከመስሪያቤቱ ሀላፊና ከቡድን መሪዎች ጋር በመወሰን ስምሪቱ እንዲፈጸም
ለነጠላ አስተዳደሩ ያስተላልፋል
156
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የሰው ኃብት አስተዳደር ተግባራትን በአንድ ማዕከል አፈፃፀም መመሪያ
u¾P£9ø~ 5†ØØæø~ ¾’ÖS ¾fiø~ ኃብት አስተዳደር ቡድን ¾fiø~ ኃበት æÖ¾mÁ
pî V6†ø~ u ሰው ኃብት አስተዳደር ሠራተኛ ›ThV’h Á1ø~Q5~ ::
6.3. u¾P£9ø~ ¾†ØØæ~h ¾’ÖS ¾fiø~ኃብት አስተዳደር ቡድን ¾k£uø~S TÁ%
uææCæCT እ SP ›4ASÑ˛’ß h†ÖQT˛ æ/u?ek ÒC uææhhC hõh
¾W^ æPu~ upTC ወይም uEø~ø~C ወይም በደረጃ እድገት እ S4=TES ÁPCÒ5~
::
6.4. ¾hõh ¾W^ æPhk T4 ታømÁ ¾’ÖS ¾fiø~ኃብት አስተዳደር ቡድን ›ThV’h
†kÒ9e እ SP ›4ASÑ˛’ß u†ÖQT˛ æ/u?ek ¾ø~4T T4ታømÁ fi5?4 øSU
u5?5Ak h ታ kT k8k እ S4=ø× SP£Ò6 ::
157
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
158
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የሰው ኃብት አስተዳደር ተግባራትን በአንድ ማዕከል አፈፃፀም መመሪያ
159
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
14.1.1. u’ÖS ¾fiø~ ኃብት አስተዳደር ቡድን †ÖQT˛ æ/u?ek ø~4T ¾T˛ÑZ~ t^†Pk
S5~uh æ/u?h øSU 55?S †æ££S æ/u?h uø× pTC ወይም Eø~ø~C ወይም
የደረጃ እድገት እS4=ø4PG fi=Òuk~ ሰው ኃበት አስተዳደር ሰራተኛ uT4ታømÁø~
æt£h UEÑv uTht@9 ECEC æ£9ø~S uøpß 4UsßS 5æAìU
T4ømÁø~S Sø×ø~ ¾’ÖS ¾fiø~ ኃብት አስተዳደር ቡድን T£øp
SÖupuታ6::
160
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የሰው ኃብት አስተዳደር ተግባራትን በአንድ ማዕከል አፈፃፀም መመሪያ
16.2. የሰው ኃብት አስተዳደር የዲስፕሊን ክሱን ካጣራ በኋላ የውሳኔ ሀሳቡን ሰራተኛው ለሚሰራበት
መስሪያቤት የበላይ ሃላፊ ያሳውቃል:: በመስሪያቤቱ የበላይ ሀላፊ ውሳኔ ከተሰጠበት በኋላ
ውሳኔውን ተከታትሎ ያስፈጽማል::
161
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
162
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የሰው ኃብት አስተዳደር ተግባራትን በአንድ ማዕከል አፈፃፀም መመሪያ
20.4. ¾h65~ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 253/2010 አንቀፅ 96 ን/አንቀፅ 2
መሰረት ææsÁ ማውጣትና እንደ አስፈላጊነቱ 5=ÁflGል SkS6 ::
20.5. SU ææsÁ ከጸደቀበት ከሰኔ/2013 ዓ.ም 9Ua ¾ìT SIT6::
አቶ ሙሉቀን አየሁ
የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ኮሚሽነር
163
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ሰኔ 2013 ዓ.ም
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ባህር ዳር፣ ኢትዮጵያ
164
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የኤች አይቪ አድስ መከላከል መቆጣጠሪያ አፈፃፀም መመሪያ
m9b˛Ã
¥SFWM r2tF bh¥2 m/22D˛ ी61D˛ mS9MJ I2 mS9MJ hSSÀ S~TC
42/2/መሰረት m2G¥G h9) প¥Ã9CM প|2 hीÆb˛ প¥9ZJ mmJ ÃMW mRC~S
bmrAJ½
165
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ክፍል 1. mQ11
1.1. h+C C:M
1.3. JCG»
166
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የኤች አይቪ አድስ መከላከል መቆጣጠሪያ አፈፃፀም መመሪያ
1.3.8. “প h2IM ImMtF” ¥MJ bh2k.hይ.Ũ˛ úb˛Ã MWCt~ btAT9 ÃMWS প bF¬
প mk1k6 kMÖ¬ mAkM পtCú bфkMt~ পtMÃ9 bF¬Dk প tÃU ImMtF
MW CW::
1.3.9. “প h2k .h ይ.Ũ˛. MCm2” ¥MJ hSI MW b9œ WMT h2k h ይ Ũ˛ ÃMbJ
mRS w ይ M hMmRC~S M¥r)2T প ф9r9 9rPWS প mbS পMWCJ AúF
MCm2 59J CW::
1.3.10. “QIm MCm2 প MीC h269MÖJ” ¥MJ Mh2k.hይ.Ũ˛. MCm2 bA”9CCJ
প Srb MW MCm2 k¥Ir2~ b@J MMCm2W পtCNbJS 91¥ mrrJ
b¥Ir9 প MCm2W Wm2J SG ይ hይwt~ 1 ይ hM~¬D˛ tÀ/ñ /SAÃMkJ6
tmC¥sW |C 6ßGD˛ G99J /SA˛Ã9C9 প фrA প ÆMœÃ MीC CW::
1.3.11. “IIr MCm2 প MीC h269MÖJ” ¥MJ bA”9CCJ প h2k.h ይ Ũ˛. MCm2
19r2 MW প MCm2 Wm2t~S mrrJ b¥Ir9 bÆMœÃ প фMT প MीCG
প|C 6ßG I)G CW::
1.3.12. “প hÆMUC bF¬” ¥MJ b9mr |) 9SZ~CJ wQJ khSR MW w9 M21 MW
brS˛Q IDM w ይ M bCM h¥ीCCJ প фt1MG h˛S$ी¹S M˛RS½ =mTS½
kCीCS½ ÆMb~M2S½ S˛TCS /G প múMM~JS ÃीJ¬6::
1.3.13. “I)GG እንीmीb2” ¥MJ ቫይረሱ b9¥9W WMT˛ያለባቸው ½ በቫይረሱ MीSÃJ
w1P}9WS Ãm~ IθGJ /G পh2IM Iœ¥S r2t9k h ይ w¬9WS btšM
J~C2¬ /SA˛Ãú6ûG ŨይrM~S bmSCM r2I প bk~19WS hMtDÀh
/SA˛Ãbrीt~ প фÃ9G MmhD˛½mSAúD˛½MC 6ßGD˛½¥Ib2D˛G h˛lñфÃD˛
t9ÆC CW::
1.3.14. “MMm˛C” ¥MJ পhSI MW প h2k.h ይŨ˛. MCm2 Wm2J w ይ M পImœ
J~C2¬ kh2IM )C ÃMWS GMIG btmMkt পIीMG መረጃው 96À
প¥ይwGbJ |C9J ¥MJ CW::
1.3.15. “የ mk1k6 t9ÆC” ¥MJ প hSI প m2G k9C w ይ M bF¬ mSMh2 প RC tIDM
w9 m2CFW MW /SAይLmJ t2b˛ TS”S& প¥Ir9 t9ÆC M˛RS bF¬WS
Mmk1k6 পф9r9 ¥SFWM প¥Mt¥CG M2MÖk t9Æ9kS ÃीJ¬6::
1.3.16. “möGmC” ¥MJ পhSIS t11@ bF¬ MC+J /G M˛ÃMkJ6 পфkMWS
2~AJ ÆMbJ M¥öM পфwMI পीJJ6 /CMP ¥MJ CW::
1.3.17. “M9~ প|2 J~C2¬” ¥MJ b9¥9W WMT প h2k h ይŨ˛ Ũ ይrM ÃM ባቸው
প mS9|J r2t9k /G ቫይረሱ በደማቸው ያለ mRG9W bhीMG M˛r)2T
167
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
168
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የኤች አይቪ አድስ መከላከል መቆጣጠሪያ አፈፃፀም መመሪያ
1.4.5. M|2 QTCG প|2 DMJG M¥úGJ M˛Æ6 পф9r9 প MWCJ AúF MCm2
ी6k1
1.4.6. MMm˛2D˛CJ
169
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
1.4.10. hGዳ@CJ
170
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የኤች አይቪ አድስ መከላከል መቆጣጠሪያ አፈፃፀም መመሪያ
171
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
172
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የኤች አይቪ አድስ መከላከል መቆጣጠሪያ አፈፃፀም መመሪያ
173
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
174
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የኤች አይቪ አድስ መከላከል መቆጣጠሪያ አፈፃፀም መመሪያ
175
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
176
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የኤች አይቪ አድስ መከላከል መቆጣጠሪያ አፈፃፀም መመሪያ
প ir h2k.hይ.Ũ˛/h2IM 9mr)ይ6 ፣
177
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
178
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የኤች አይቪ አድስ መከላከል መቆጣጠሪያ አፈፃፀም መመሪያ
5.2. I6I6
5.3. /I2J
179
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
5.4. GWWC
h2k.hይ.Ũ˛ b9¥9W WMT ÃMG প h2IM hœ¥S r2t9k MM2MÖk tGAC bF¬Dk
bфÃ)6m~ ߬Dk 1 ይ tLWrW m|2J পMÆ9WM::ከሌሎች ሰራተኞች ጋር ሲወዳደሩም
በምልመላና መረጣ መመሪያው ላይ የተደረገላቸው ድጋፍ ተፈጻሚ ይሆናል::
180
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የኤች አይቪ አድስ መከላከል መቆጣጠሪያ አፈፃፀም መመሪያ
181
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
አቶ ሙሉቀን አየሁ
የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ኮሚሽነር
182
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የመንግስት ሠራተኞች በመ/መስሪያ ቤት ውስጥ ህፃናት ማቆያ አገልግሎት መስጫ መመሪያ
መመሪያ 9. የመንግስት
ሠራተኞች በመ/መስሪያ ቤት
ውስጥ ህፃናት ማቆያ
አገልግሎት መስጫ መመሪያ
ቁጥር 09/2013
ሰኔ 2013 ዓ.ም
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ባህር ዳር፣ ኢትዮጵያ
183
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
መግቢያ
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አዋጅ ቁጥር 253/2010 በሚተዳደሩ መስሪያ ቤቶች ውስጥ
የሚሰሩ ሴት የመንግስት ሠራተኞች የተጣለባቸውን ተግባርና ኃላፊነት በአግባቡ በመወጣት ለክልላቸው
ብሎም ለአገራቸው ልማት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ያበረክቱ ዘንድ ስራዎቻቸውን ከተጽዕኖ ተላቀው
በሙሉ ልብ ማከናወን የሚጠበቅባቸው በመሆኑ፣ የሚወለዱ ጨቅላ ህፃናት ጤንነታቸው ተጠብቆ
በአካልና በአዕምሮ የዳበሩ ሆነው በማደግ ብቁ ዜጋ እንዲሆኑ ተገቢ እንክብካቤ ድጋፍ
የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ፣
በተሻሻለው የአብክመ መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 253/2010 ለሴት ሠራተኞች የሚጠበቁ
የስራ ሁኔታዎችን በተመለከተ በአንቀጽ 48 ንዑስ አንቀጽ 6 ማንኛውም የመንግስት መ/ቤት ሴት
የመንግስት ሠራተኞች ህፃናት ልጆቻቸውን የሚያጠቡበትና ህፃናቱን የሚንከባከቡበት የህፃናት ማቆያ
ማቋቋም እንዳለበት የተደነገገውን መሠረት በማድረግ ዝርዝር መመሪያ በማውጣት ለተጠቃሚዎች
ተደራሽ ማድረግ በማስፈለጉ፣
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በመንግሥት ሠራተኞች አዋጅ አንቀጽ
96 ንዑስ አንቀጽ 2 በተሰጠው መመሪያ የማውጣት ስልጣን መሠረት ይህን መመሪያ አውጥቷል፡
ክፍል 1. ጠቅላላ
1.1. አጭር ርዕስ
ይህ መመሪያ “የመንግስት ሠራተኞች ጨቅላ ሕፃናት በመንግስት መስሪያ ቤት ውስጥ ማቆያ መመሪያ
ቁጥር 09/2013” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል።
1.2. ትርጓሜ
1.2.1. “ጨቅላ ሕፃን” ማለት እድሜው ከ 4 ወር በላይና ከአራት ዓመት በታች የሆነ ነው።
1.2.2. “የጨቅላ ህፃናት ማቆያ” ማለት በመንግስት መ/ቤት/ተቋም ውስጥ ለዚሁ ተግባር
የሚገነቡ ክፍሎች ናቸው።
1.2.3. “የመንግስት ሠራተኛ” ማለት ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል በመንግስት በጀት
በሚተዳደር መ/ቤት ተቀጥሮ የሚሰራ የተፈጥሮ ሰው ነው።
184
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የመንግስት ሠራተኞች በመ/መስሪያ ቤት ውስጥ ህፃናት ማቆያ አገልግሎት መስጫ መመሪያ
1.2.4. “ሞግዚት” ማለት የመንግስት ሠራተኞችን ጨቅላ ሕፃናት በስራ ሰዓት ተቀብላ የምትንከባከብ
የኮንትራት ሠራተኛ ናት።
1.2.5. “የህፃናት ማቆያ አገልግሎት” ማለት በመንግስት መ/ቤቶች ውስጥ በፑል ወይም በተናጠል
አገልግሎት እንዲሰጥ ተደርጎ የተዘጋጀ የጋራ ወይም በተናጠል መጠቀሚያ አገልግሎት
ነው።
1.2.6. በዚህ መመሪያ በወንድ ፆታ የተገለፁ ሁሉ ሴቶችንም ያጠቃልላል።
185
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
3.5.1. የህፃናት ማቆያዉ ሲቋቋም የቦታ መረጣው በህፃናቱ ጤናና አካል ላይ ጉዳት ሊያደርሱ
የሚችሉ ኬሚካሎች፣ ብናኞች፣ ጨረሮችና ሽታ የሌለበት፣ የድምፅ ብክለት
እንዳይኖረው ከመኪና መንገድና ድምፅ ካላቸው የማምረቻ ቦታዎች የራቀ ሊሆን ይገባል።
3.5.2. በማቆያዉ ህፃናት ጊዜያቸውን በጨዋታ የሚያሳልፉበት ክፍል ዋነኛው አስፈላጊ ክፍል
ሲሆን ይዘቱም ደህንነቱ የተጠበቀና በህፃናት ላይ ጉዳት ሊያደርሱ ከሚችሉ ነገሮች
የፀዳ ሊሆን ይገባል።
3.5.3. ክፍሉ ለተንከባካቢዎች በማንኛውም ሰዓት በነፃነት ክትትል ሊያደርጉ የሚችሉበትን ሁኔታ
የሚፈጥርላቸው ሊሆን ይገባል።
3.5.4. የክፍሉ አቀማመጥ ለህፃናት ነፃነት፣ ደህንነትና ምቾት ሊሰጣቸው የሚችል ሆኖ ሊዘጋጅና
በቂ የተፈጥሮ ብርሃንና አየር ሊያገኝ በሚችል መልኩ ሊዘጋጅ ይገባል።
3.5.5. በማቆያዉ የሚገኙት ክፍሎች የተለያዩ አገልግሎቶችን የሚሰጡ ሲሆን ለህፃናቱ እንደ
ዕድሜ ደረጃቸው የመጫወቻ ክፍሎች፣ የመኝታና የማረፊያ ክፍሎችን፣ የምግብ
ማዘጋጃና ማከማቻ ክፍል፣ የመመገቢያ ክፍልና የልብስና የመፀዳጃ ዕቃዎች
ማስቀመጫና መቀየሪያ ክፍልን ያካተተ ሊሆን ይገባል።
3.5.6. የመኝታና ማረፊያ ክፍሉ ከህፃናቱ የመጫወቻ ክፍል ጋር ተጎራባች ሆኖ በመጫወቻ
ክፍሉ ውስጥ በሚፈጠረው የህፃናት ጩኸት እንዳይረበሽ ድምፅ በማያሳልፍ ቁስ
/ማቴሪያል የተሰራና በከፊል በመስታወት የተከለለ ሊሆን ይገባል።
3.5.7. የመኝታ ክፍሉ ለተንከባካቢዎች ዕይታ አመቺ ሆኖ በቂ የተፈጥሮ ብርሃን የሚያስገባና ቀጥታ
የፀሐይ ጨረር የሚያስገባ ሳይሆን በጥላ የተጋረደ መሆን አለበት
3.5.8. የክፍሉ ሙቀት የተመጣጠነ እንዲሆን ንፁህ አየር ሊዘዋወርበት የሚችልና የተፋፈነ
እንዳይሆን ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል።
186
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የመንግስት ሠራተኞች በመ/መስሪያ ቤት ውስጥ ህፃናት ማቆያ አገልግሎት መስጫ መመሪያ
3.5.9. አካባቢው ሞቃት ከሆነ ክፍሉ ሰው ሰራሽ የሙቀት መቆጣጠሪያ እንዲገጠም ተደርጎ የመኝታ
ክፍሎቹ ለጨቅላና ለሚውተረተሩ ህፃናት በተመሳሳይ መልኩ የሚዘጋጁ መሆን
አለባቸው።
3.5.10. በማቆያው የሚስተናገዱ ጨቅላ ህፃናት ዕድሜያቸዉ ከ 4 ወር በላይና ከ 4 ዓመት በታች
ዕድሜ ክልል ዉስጥ የሚገኙ ህፃናትን የሚያጠቃልል ሲሆን ወላጆች/አሳዳጊዎች ምቹ የስራ
አካባቢ ለመፍጠር እና ህጻናትም ማግኘት የሚገባቸውን ሁለንተናዊ ድጋፍና እንክብካቤ
ማገኘት እንዲችሉ ለማድረግ የሚረዳ መሆን አለበት።
3.5.11. የመኝታ ክፍሎቹ ከ 10 ያልበለጡ ጨቅላ ህፃናትን የሚይዙ ሆነው የክፍሎቹ ስፋት እንደ
ህፃናቱ አልጋ የሚለያዩ ይሆናሉ።
3.5.12. ክፍሉ ለህፃናቱ በቂ የመዘዋወሪያ ቦታ ያለውና ቀጥታ የፀሐይ ጨረር የማያስገባ
ሊሆን ይገባል።
3.5.13. የክፍሉ ሙቀት የተመጣጠነና ንፁህ አየር ሊዘዋወርበት የሚችል ሆኖ ወይም ሰው ሰራሽ
የሙቀት መቆጣጠሪያ የተገጠመ መሆን አለበት
3.5.14. የመጫወቻ ክፍሉ ወለል ለስላሳና በግጭት ወቅት ጉዳት ሊያስከትል የማይችል ሊሆን ይገባል።
3.5.15. አዋቂዎች ወደ ህፃናት መጫወቻ ክፍል ከመግባታቸው በፊት ንፅህናቸውን ስለመጠበቃቸውና
ህፃናቱን ለበሽታ ከሚዳርጉ ነገሮች ስለመፅዳታቸው ማስጠንቀቂያና ጥቆማ የሚሰጥ
ምልክት ከክፍሎቹ በተወሰነ ሜትር ርቀት ላይ በግልፅ ሊቀመጥ ይገባል።
3.5.16. የሚዘጋጁ የመጫወቻ ክፍሎች ደህንነታቸውና ምቾታቸው የተጠበቀ አሻንጉሊቶችና ልዩ
ልዩ የመጫወቻ ቁሳቁሶች ለህፃናቱ ግልፅና ምቹ የሆነ ክፍት ቦታ ላይ ማስቀመጥና
የክፍሉ ግድግዳዎች የሀገርን ባህላዊ እሴቶች የሚያሳዩ ሆነው ሊዘጋጁ ይገባቸዋል።
3.5.17. በክፍሉ ውስጥ የሚዘጋጁ ወንበሮች፣ ጠረጴዛዎችና ሼልፎች የማይንቀሳቀሱና ከወለሉ ወይም
ከግድግዳው ጋር የተያያዙ መሆን ይኖርባቸዋል።
3.5.18. አንድ የመጫወቻ ክፍል ከ 10 ያልበለጡ ጨቅላ ህፃናትን ለማስተናገድ እንዲቻል እና
ለአንድ ህፃን ነፃ የመጫወቻና የመንቀሳቀሻ ቦታ 2.8 ሜ 2 ታሳቢ በማድረግ መዘጋጀት
ይኖርባቸዋል።
3.5.19. የሚውተረተሩ ህፃናት ለእነዚህ ህፃናት የሚዘጋጁ የመጫወቻ ክፍሎች ለህፃናቱ ነፃነትን
የሚሰጡና የሚያበረታቷቸው ሆነው ሊዘጋጁ ይገባቸዋል።
187
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
3.5.20. የክፍሉ ግድግዳዎች በመማሪያ ፊደላት፤ በእንስሳትና በተክል ስዕሎች የተሞላና የህፃናቱን
ቀልብ ሊስቡ የሚችሉ ሆነው ብሎም የማወቅና የመማር ፍላጎታቸውን የሚያነሳሳና
ዕውቀት የሚቀስሙባቸው መሆን ይገባቸዋል።
3.5.21. የክፍሉ ውስጣዊ ሁኔታ ህፃናቱን በቡድን ሆነው እንዲጫዎቱ ሆኖ መዘጋጀት አለበት።
3.5.22. ለህፃናቱ መፀዳጃና መታጠቢያ የሚያገለግል ከተፀዳዱ በኋላ ልብሳቸውን የሚቀይሩበትና
የመፀዳጃ ቁሳቁሶችና አልባሳቶቻቸው የሚቀመጡበት ክፍል ንፁህ መሆን አለበት።
3.5.23. ጡት የሚጠቡ ህፃናት እናቶቻቸው ለማጥባት በሚመጡበት ወቅት አረፍ ብለው ሊያጠቡ
የሚችሉበት ቦታና ተጨማሪ ምግብ የሚጠቀሙ ህፃናት ምግባቸው የሚዘጋጅበትና
ከተዘጋጀም በኋላ በወላጅ እናቶቻቸው ወይም በተንከባካቢያቸው አማካኝነት ሊመገቡበት
የሚያስችላቸው ቦታ ሊሆን ይገባል።
3.5.24. ሁሉም የሚገነቡ ክፍሎች አየር የሚዘዋወርባቸው፣ ከቀጥታ የፀሐይ ጨረርና ንፋስ
የተጠበቁ ሊሆኑ ይገባዋል።
4.2.1. የመኝታ ክፍል ውስጥ በቂ ቁጥር ያለው የህፃናት አልጋና ፍራሽ፣ የተለያዩ ተንጠልጣይ
ቅርፃቅርፆች፣ የሙቀት መቆጣጠሪያ መሣሪያ ሊኖረው ይገባል።
4.2.2. የመጫወቻ ክፍል ውስጥ የመማሪያና የመጫወቻ ቁሳቁስ፣ ቴሌቪዥን፣ አሻንጉሊት፣
የህፃናት ወንበርና ጠረጴዛ፣ የፊደል ገበታ፣ ለህፃናት የተዘጋጁ ባህላዊ ስዕሎችና
ቅርፃቅርፆችና ሌሎች ለህፃናት የሚሆኑ የመጫወቻ ቁሳቁሶች የያዘ መሆን ይኖርበታል።
188
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የመንግስት ሠራተኞች በመ/መስሪያ ቤት ውስጥ ህፃናት ማቆያ አገልግሎት መስጫ መመሪያ
4.2.3. የንፅህና መጠበቂያ ክፍሉ፡- የዕቃ መደርደሪያ ሳጥን፣ የልብስ መቀየሪያ ጠረጴዛ፣ የህፃናት
ማጠቢያ ገንዳ፣ የኤሌክትሪክ ውሃ ማሞቂያ፣ የህፃናት መፀዳጃ ፖፖ፣ የመጀመሪያ ዕርዳታ
መስጫ ሳጥን፣ የህፃናት ንፅህና መጠበቂያ ዳይፐር፣ የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ቅርጫትና
ሌሎች የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን የያዘ መሆን አለበት።
4.2.4. የምግብ ማብሰያና መመገቢያ ክፍሎቹ፡- የምግብ ማብሰያ ምድጃ (የኤሌክትሪክ እና ሲሊንደር)፣
ፍሪጅ፣ የውሃ ማጣሪያና ማሞቂያ፣ የማብሰያና የመመገቢያ ቁሳቁሶችን ማጠቢያ ቦታ
(ሲንክ) እና ማስቀመጫ/መደርደሪያ ሳጥን የያዘ መሆን ይገባዋል።
4.2.5. የመመገቢያ ክፍሉ፡- የህፃናት መመገቢያ ጠረጴዛና ወንበር የአዋቂ ወንበር የያዘ ሊሆን ይገባል።
4.2.6. በማቆያዉ የማብሰያና የመመገቢያ ቁሳቁሶች ለህፃናቱ በቂና ጤናማ ምግብ ለማቅረብ
እንዲያስችላቸውና በአጠቃላይ የተሟላ አገልግሎት ማግኘት እንዲችሉ መሆን አለበት።
189
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
190
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የመንግስት ሠራተኞች በመ/መስሪያ ቤት ውስጥ ህፃናት ማቆያ አገልግሎት መስጫ መመሪያ
5.1.5. ወላጅ ልጁን ይዞ ሲመጣ ንፁህ እንዲሆን አጥቦና ንፁህ ልብስ አልብሶ እንዲሁም በማቆያዉ
የቆይታ ጊዜው የሚሆን በቂ የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁስ አቅም በፈቀደ መልኩ ጨምሮ
በማዘጋጀት አያይዞ መምጣት ይኖርበታል።
5.1.6. ወደ ማቆያዉ አገልግሎት ፈልገው የሚመጡ ወላጆችና ህፃናት ለተላላፊ በሽታዎች የተጋለጡ
አለመሆናቸውን ማረጋገጥ የሚኖርባቸው ሲሆን ከተላላፊ በሽታዎች ነፃ ሲሆኑ ብቻ
አገልግሎቱን የሚያገኙ ይሆናሉ። ለምሳሌ ስሜታቸው በዓይን የሚታይ እንደ ጉንፋን፣
እከክ፣ ትክትከ…..
191
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ክፍል 7. ልዩ ልዩ ጉዳዮች
7.1.1. በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት በተሻሻለው የመንግስት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር
253/2010 መሠረት ይህን መመሪያ የመለወጥ፣ የማሻሻል ወይም በሥራ ላይ በሚውልበት
ጊዜ ማብራሪያ ወይም ትርጉም የመስጠት ኃላፊነት የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ነው።
7.1.2. ይህን መመሪያ በተዛባ መንገድ የሚፈጽም የሚያስፈጽም ማንኛውም የስራ ኃላፊ አግባብ
ባላቸው የፍትሐብሔርና የወንጀል ሕግ ተጠያቂ ይሆናል።
7.1.3. በዚህ መመሪያ አተገባበር ላይ የሚኖር ቅሬታ በስራ ላይ ባለው የቅሬታ አቀራረብ ስርዓት
መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል::
7.1.4. ይህ መመሪያ ከታኅሳስ ወር 2012 ዓ/ም ጀምሮ የጸና ይሆናል።
አቶ ሙሉቀን አየሁ
የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ኮሚሽነር
192
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የቀበሌ ልማት ሰራተኞች/ ባለሙያዎች/ የጽ/ቤት ኃላፊዎች የዝውውርና ምደባ አፈጻጸም
ሰኔ 2013 ዓ.ም
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ባህር ዳር፣ ኢትዮጵያ
193
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
መግቢያ
የቀበሌ ግብርና ባለሙያዎች/ሰራተኞች የአርሶ አደሩን ችግር በቅርበት በመረዳት የክልሉን ብሎም
የሀገሪቱን የልማት ፖሊሲ ለማስፈጸም እንዲችሉ ማበረታታት ስለሚገባ፣ ከቀበሌ ወደ ቀበሌ
የባለሙያዎች የዝውውር መመሪያ ተዘጋጅቶ በስራ ላይ ተግባራዊ መደረጉ ጠቀሜታዉ በመረጋገጡና
ባለሙያዎች በስራ ቦታቸዉ ተረጋግተዉ እንዲሰሩ ለማስቻል ።
በክልላችን ውስጥ በስራ ላይ የነበረው የቀበሌ ባለሙያዎች የዝውውር አፈጻጸም መመሪያ የነበሩበትን
የግልጸኝነት ችግርና የሚነሱ አቤቱታዎችን መቀነስ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤ የቀበሌ ግብርና
ሰራተኞች/ባለሙያዎች የግብርና ተግባርን የተሳለጠ ማድረግ እንዲችሉ ማነሳሳት፣ ታታሪና
ውጤታማ ሁነው ሠራተኞች/የጽ/ቤት ኃላፊዎች እንዲበረታቱ ለማድረግ፤
በተለያዩ ጊዜያት በተደረጉ የመስክ ጉብኝቶች፣ ከዞን ግብርና መምሪያና ከወረዳ ግብርና ጽ/ቤቶች እንዲሁም
ከራሳቸው ከቀበሌግብርና ባለሙያዎች በሚቀርብ ቅሬታ በስራ ላይ የነበረው መመሪያ ለአፈፃፀም
የሚያስቸግር በመሆኑ የወጣውን የቀበሌ ግብርና ባለሙያዎች የሰው ኃይል ስምሪት መመሪያ መከለስ
አስፈልጓል።
በመሆኑም የአፈፃፃም ችግሮችን በመለየት የአብክመ ሲቨል ሰርቪስ ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 253/2010
አንቀጽ 96 ን/አንቀጽ 2 በተሰጠው ስልጣን መሰረት ይህን የተሻሻለው የቀበሌ ግብርና ባለሙያዎች
የዝውውርና ምደባ መመሪያ አዘጋጅቷል ፡
ክፍል 1. ጠቅላላ
1.1. አጭር ርዕስ
ይህ መመሪያ የቀበሌ ልማት ሰራተኞችና ባለሙያዎች /የቀበሌ ሰብል ልማትና ጥበቃ፣ የቀበሌ
የእንስሳት ሀብት ልማት፣ የተፈጥሮ ሀብት ልማትና ጥበቃ፣ የቀበሌ መስኖ፣ የእንስሳት ጤና ጥበቃ
ባለሙያዎች፤የእንስሳት አዳቃይ ቴክኒሽያኖች ፣ የቀበሌ ኀብረት ስራ አደራጆች እና የቀበሌ ገጠር
መሬት አጠቃቀምና አስተዳደር ሠራተኞች እንዲሁም የቀበሌ ጽ/ቤት ኃላፊዎች የዝውውር
አፈጻጸም መመሪያ ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል።
1.2. ትርጉም
194
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የቀበሌ ልማት ሰራተኞች/ ባለሙያዎች/ የጽ/ቤት ኃላፊዎች የዝውውርና ምደባ አፈጻጸም
1.2.1. “የቀበሌ ግብርና ልማት ሰራተኞችና ባለሙያዎች” ማለት፡- በቀበሌ ተመድበው እያገለገሉ
ያሉ የእንስሳት ሀብት ልማት፣ የሰብል ልማት፣ የተፈጥሮ ሀብት፣ የመስኖ፣ የእንስሳት
ህክምና፤የእንስሳት አዳቃይ ቴክኒሻኖች ፣ የቀበሌ ገጠር መሬት አጠቃቀምና አስተዳደር
ሠራተኞች እና ኀብረት ስራ ማኀበራት ባለሙያዎችን ያካተተ ነው።
1.2.2. “የቀበሌ ግብርና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ” ማለት፡- በቀበሌው ውስጥ የሚያገለግል የቀበሌ
ግብርና ልማት ሰራተኞችንና ባለሙያዎችን የሚያስተባብር፣ የሚደግፍ፣ የሚከታተልና
የሚቆጣጠር ማለት ነው።
1.2.3. “አገልግሎት ዘመን” ማለት፡- በግብርና ልማት ጽ/ቤት ከተቀጠረ በኋላ ወይም ከመቀጠሩ
በፊት በመንግሥት ሠራተኞች የምልመላና መረጣ አፈጻጸም መመሪያ መሠረት ሊያዝ
የሚገባው የስራ ልምድ እና በየትኛውም ደረጃ የሰራበትን የአገልግሎት ዘመን ያጠቃልላል።
1.2.4. “የጋብቻ ማስረጃ” ማለት፡- በማዘጋጃ ቤት ወይም በወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ወይም በሃይማኖት
ተቋም ወይም በባህላዊ ጋብቻ /የአገር ሽማግሌ/ የሚሰጥ የምስክር ወረቀት/ውል ማለት
ነው።
1.2.5. “ዝውውር” ማለት አንድ የቀበሌ ግብርና ልማት ሰራተኛ/ባለሙያ/ጽ/ቤት ኃላፊ ከሚሰራበት
ቀበሌ ወደ ሌላ ቀበሌ፤ ወይም ወደ ሌላ ወረዳ/ዞን ቀበሌ አዛውሮ ማሰራት ማለት ነው።
1.2.6. “የሕክምና ቦርድ ማስረጃ” ማለት በመንግሥት ሪፈራል ሆስፒታል ደረጃ በሐኪሞች ሜዲካል
ቦርድ ታማሚው ያለበትን የጤና ሁኔታና ምን ሊደረግለት/ሊታገዝ እንደሚገባ የሚገለጽ
የሕክምና ማስረጃ ማለት ነው።
1.2.7. “ምደባ” ማለት የቀበሌ ግብርና ልማት ሰራተኛ/ባለሙያ/ጽ/ቤት ኃላፊ በመንግሥት ወጭ
ትምህርቱን አሻሽሎ ሲመለስ፤ከጽ/ቤት ኃላፊነት ሲነሳ፤በጤናና በህይወት የመኖር
የደህንነት ስጋት ችግር ምክንያት መመደብ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ሠራተኛው/ዋ ካለው/ላት
ሙያና ደረጃ አኳያ ታይቶ አገልግሎት የሚሰጡበትን ቦታ ማሳወቅ ወይም መደልደል ነው።
1.2.8. “የሥራ ቦታ ምድብ ደረጃ” ማለት በአየር ጠባይ ተስማሚነት ደረጃ እና በመሠረተ ልማት
ደረጃ ከወረዳው ርዕሰ ከተማ ያለው ርቀትና በሌሎችም መስፈርቶች ስልጣን ባለው አካል
የተሰጠ የቦታ ደረጃ ማለት ነው።
195
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
1.3.1. ይህ መመሪያ በክልሉ ውስጥ ተመደበው በሚሰሩ የቀበሌ ግብርና ልማት ጣቢያ
ሰራተኞች/ባለሙያዎችና ጽ/ቤት ኃላፊዎች በሙሉ ተፈጻሚ ይሆናል።
2.1.1. በየዓመቱ የሚደረገው ዝውውር ክፍት በሆኑ ቀበሌዎችና ፍላጐትን መሠረት ያደረገና በውድድር
የሚፈጸም ሲሆን አንድ የቀበሌ ግብርና ሰራተኛ /ባለሙያ/ ጽ/ቤት ኃላፊ ከቀበሌ ቀበሌ
ለመዛወር በተመደበበት ቀበሌ ሁለት ዓመት ማገልገል ይጠበቅበታል።
2.1.2. የቀበሌ ባለሙያዎች ዝውውር ከተጠናቀቀ በኋላ አንድ የቀበሌ ባለሙያ አዲስ ተቀጥሮ ወይም
በዝውውር ከሌላ ወረዳ ከመጣ ፤በመንግሥት ወጭ ትምህርቱን አሻሽሎ ሲመለስ፤ከጽ/ቤት
ኃላፊነት ሲነሳ፤በጤናና በህይወት የመኖር የደህንነት ስጋት ችግር ምክንያት መመደብ
አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በወረዳው ውስጥ ባሉት ክፍት ቀበሌዎች በጊዜያዊነት ተመድቦ
እንዲሰራ ይደረጋል። ሆኖም ግን ከጊዜ በኋላ የቦታ ክፍተት ከተፈጠረ በጊዜያዊነት ተመድቦ
የነበረውን ወደ ሚመጥነው ቀበሌ ወይም ቦታ ለመመደብ የግድ 2/ሁለት/ ዓመት
እንዲያገለግል አይጠበቅም።
2.1.3. የዝውውር ማስታወቂያ ለሁሉም የቀበሌ ሰራተኞች/ባለሙያዎች በሚያመች መንገድ
እንዲለጠፍ/እንዲደርስ/ እና የቀበሌ ሰራተኞች/ባለሙያዎች/ጽ/ቤት ኃላፊዎች
የዝውውር መጠየቂያ ፎርሙን በመሙላት ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት
7/ሰባት/ ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የሚፈልጓቸውን ሦስት ቀበሌዎች ከ 1 ኛ እስከ
3 ኛ ደረጃ በመዘርዘር ለዚሁ ዓላማ በተዘጋጀው የመጠየቂያ ፎርም ሞልተው በወረዳ ግብርና
ጽ/ቤት በኩል እንዲቀርብ ይደረጋል። ሆኖም ግን አንድ ባለሙያ የዝውውር ፍላጎቱን በደረጃ
ዘርዝሮ ካቀረባቸው ቀበሌዎች ውስጥ በውጤቱ ምክንያት ማግኘት ባይችል፣ በቋሚነት
ተመድቦበት በነበረው ቀበሌ እንዲቀጥል ይደረጋል።
2.1.4. አንድ የቀበሌ ባለሙያ ካለበት ቀበሌ መዛወር ካልፈለገ ይህንኑ ሀሳቡን ዝውውሩ ከመሰራቱ
በፊት በጽሑፍ ማመልከቻ ለጽ/ቤቱ ሊያሳውቅ ይችላል።
196
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የቀበሌ ልማት ሰራተኞች/ ባለሙያዎች/ የጽ/ቤት ኃላፊዎች የዝውውርና ምደባ አፈጻጸም
ሐ. የጋብቻ ሁኔታ 5%
መ. የማኀደር ጥራት 5%
ሠ. ለስራ ቦታ 15%
ረ. ለሴቶች 3
2.2.1. ዝውውሩ ከመታየቱ በፊት ባሉት ሁለት ተከታታይ ዓመታት የመጨረሻ የዕቅድ አፈጻጸም
መገምገሚያ ወቅት የተሞላ የ 4 ተከታታይ ጊዜ የስራ አፈጻጸም ምዘና አማካይ
ውጤት 50% የሚያዝ ሆኖ /የተገኘው ውጤት በ 0.5 እየተባዛ ይያዛል።
197
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ለአብነት በስራ አፈጻጸም ውጤት ከፍተኛ ሆኖ አማካይ ውጤቱ 80 ቢሆን 80 ሲባዛ በ 0.5
= 40 ይሆናል።ሆኖም ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ማለትም በህመም፤
በወሊድ፤በእስራት፤በትምህርት፤ከኃላፊነት በመነሳት በእነዚህ ደረጃ ሊወሰዱ በሚችሉ
ምክንያቶች ውጤት ያልተሞላለቸው የቀበሌ ግብርና ሰራተኞች፤ ባለሙያዎችና ጽ/ቤት
ኃላፊዎች ቀደም ሲል ተሞልቶ ማህደራቸው ላይ በተያያዘው ተከታታይ የሁለት ጊዜ
ስራ አፈጻጸም ውጤት መሰረት እንዲወዳደሩ ይደረጋል።
2.2.2. የአገልግሎት ዘመን ከ 25 የሚያዝ ሆኖ 25 ዓመት እና በላይ አገልግሎት ያላቸው ከሆነ
25 ነጥብ የሚያገኝ ይሆናል። ሆኖም ከ 25 ዓመት በታች አገልግሎት ያላቸው የቀበሌ
ሰራተኞች፤ባለሙያዎችና ጽ/ቤት ኃላፊዎች ተወዳዳሪ ሆነው ሲቀርቡ በዚሁ ስሌት
ውጤቱ ተሰልቶ ይሰጣቸዋል። /ለምሣሌ 12 ዓመት ያገለገለ/ለች 12 ሲባዛ በ 25 ሲካፈል
25 =12 ይሆናል ማለት ነው።
2.2.3. ለትዳር የሚሰጥ ነጥብ 5% ይሆናል።
2.2.4. የቀበሌዎች ለኑሮ ተስማሚነት ደረጃ 15 የሚይዝ ሆኖ ቀበሌዎችን በ 3 ምድብ ወይም ደረጃ
በመክፈል ማለትም በከፍተኛ ደረጃ ለኑሮ አስቸጋሪ፣ በመካከለኛ ደረጃ ለኑሮ አስቸጋሪና
በዝቅተኛ ደረጃ ለኑሮ አስቸጋሪ በሚል በየአራት ዓመት የወረዳው ሲቪል ሰርቪስ እና
የግብርና ጽቤት በጋራ የገጠር መሠረተ ልማት መስፋፋት እና የአየር ንብረት ሁኔታ
አስቸጋሪነትና ቀበሌው ከወረዳው ርዕሰ ከተማ ያለው ርቀት ግምት ውስጥ በማስገባት
ደረጃ በማዘጋጀት ለወረዳ አስተዳደር ም/ቤት በማቅረብ ደረጃው እየተወሰነ ከዚህ በታች
በተዘረዘረው መሰረትለደረጃ ነጥብ ይሰጣል።
2.2.5. የማኀደር ጥራት 5 የሚያዝ ሆኖ ከዚህ በታች በተቀመጠው ሠንጠረዥ መሠረት የሚያዝ
ይሆናል።
198
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የቀበሌ ልማት ሰራተኞች/ ባለሙያዎች/ የጽ/ቤት ኃላፊዎች የዝውውርና ምደባ አፈጻጸም
የሚቀነስ የሚሰጥ
ተ.ቁ የተወሰደው የዲስፕሊን እርምጃ
ነጥብ ነጥብ
እስከ 2 ዓመት ለሚደርስ ጊዜ ከደረጃና
1 5 0
ደመወዝ ዝቅ ማድረግ
እስከ ሦስት ወር ደመወዝ የሚደርስ
2 4 1
የደመወዝ ቅጣት
እስከ አስራ አምስት ቀን የሚደርስ
3 3 2
የደመወዝ ቅጣት
4 የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ቅጣት 2 3
የቃል ማስጠንቀቂያ በጽሑፍ
5 1 4
ከተቀመጠ
6 ምንም የቅጣት ሪከርድ የሌለበት 0 5
2.2.6. ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው የዝውውር ተወዳዳሪዎች እኩል ውጤት ካስመዘገቡ በመንግስት
ሠራተኞች የምልመላና መረጣ መመሪያ ንዑስ አንቀጽ 2.7.2.3 መሰረት ውጤታቸው
እንዲለይ ይደረጋል።
ሀ. ከቀበሌ ወደ ቀበሌ
ለ. ከወረዳ ወደ ወረዳ
አዲስ ምሩቃን ወደ ግብርና ተቋም ከመቀላቀላቸው በፊት፣ ነባር የቀበሌ ግብርና ባለሙያዎች በውድድር
ከነበሩበት ቀበሌ፣ ወረዳ፣ ዞን ወደ ሌላ ቀበሌ፣ ወረዳ፣ ዞን ተዘዋውረው እንዲሰሩ የሚደረግበት ሥርዓት
የተዘረጋ ሲሆን ዝውውሩ በሚከተለው መንገድ እንዲፈጸም ይደረጋል።
199
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
2.4.1.2. ከዞን - ዞን፤ከወረዳ ወረዳ የተዛውሩ የቀበሌ ግብርና ልማት ሰራተኞች /ባለሙያዎች
/ጽ/ቤት ኃላፊዎች በተዛወሩበት ዞን/ወረዳ ውስጥ በዚያው ዞን/ወረዳ ውስጥ ካሉና ዝውውር
ከሞሉ የቀበሌ ግብርና ልማት ሰራተኞች/ባለሙያዎች/ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር እኩል
የመወዳደር መብት ያላቸው ሲሆን ተወዳድረው በተመደቡበት ቦታ የመሰማራት ግዴታ
አለባቸው።
2.4.1.3. ህጋዊ የጋብቻ ማስረጃ የሚያቀርቡት ባለትዳሮች ዝውውር የሚጠይቁት አንድ ላይ ለመኖር
ወይም ለመቀራረብ ሊሆን ይችላል ።
2.4.1.4. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 2.4.1.3 የተደነገገው ቢኖርም፣ አንድ የቀበሌ ግብርና
ሰራተኛ/ባለሙያ/ጽቤት ኃላፊ የዝውውር ጥያቄ ፎርም ሲሞላ ወይም ስትሞላ ለትዳር
የተሰጠውን ነጥብ ማግኘት የሚችሉት የጋብቻ ማስረጃ በሠራተኛው/ዋ/ የግል ማህደር
ላይ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ቢያንስ ከስድስት ወርና በፊት የተያያዘ መሆን አለበት።
2.4.1.5. የትዳር አጋሩ/ሯ/ የመንግስት ሠራተኛ ቢሆኑም ባይሆኑም የጋብቻ ማስረጃው ከላይ በአንቀጽ
2.4.1.4 መሠረት የተያያዘና የመንግሥት ሠራተኛ ከሆኑ ከሚሰሩበት መ/ቤት የመንግስት
ሠራተኛ ካልሆኑ ደግሞ ከሚኖሩበት ቀበሌ የኗሪነት ማረጋገጫ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፤
ይህም ከሌሎች ሠነዶች ጋር ወደ አወዳዳሪ ተቋም መላክ አለበት።
2.4.1.6. ባለሙያው/ዋ/ ለመዛወር ሲጠይቅ ወይም ስትጠይቅ፣ የባልና ሚስት አገልግሎት ተደምሮ
ሲካፈል በሚኖረው አማካይ የአገልግሎት ዘመን ተይዞ እንዲወዳደር ወይም እንድትወዳደር
ይደረጋል። ሆኖም የራሱ/ሷ/ የአገልግሎት ዘመን ከአማካይ ውጤቱ የተሻለ ከሆነ በቀጥታ
ይኸው የግል የአገልግሎት ዘመን ለውድድሩ እንዲያዝ ይደረጋል።
2.4.1.7. ባለሙያው/ዋ/ በዝውውር መጠየቂያ ቅጽ ላይ መረጃውን በትክክል መሙላት
ይጠበቅበታል/ይጠበቅባታል፣ መረጃውን ሳይሞሉ ቀርተው ዝውውሩ በተናጠል ከታየ በኋላ
የሚቀርብ የዝውውር ጥያቄ ተቀባይነት አይኖረውም።
200
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የቀበሌ ልማት ሰራተኞች/ ባለሙያዎች/ የጽ/ቤት ኃላፊዎች የዝውውርና ምደባ አፈጻጸም
201
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
3.2.1.1. ከዞን ሲቪል ሰርቪስ መምሪያ የሚመጣውን የተጠቃለለ መረጃ መሠረት በማድረግ ከዞን
ወደ ዞን መዛወር የሚፈልጉ የቀበሌ ግብርና ልማት ሰራተኞች/ ባለሙያዎች
/ጽ/ቤት ኃላፊዎች ዝውውር ይሰራል።
3.2.1.2. በስሩ ያሉ ተጠሪ ተቋማት የሚያስተዳድሯቸዉን የቀበሌ ሰራተኞች/ባለሙያዎችን መረጃ
በማሰባሰብ በየደረጃዉ ዝዉዉር እንዲያካሂዱ ያስተባብራል።
3.2.1.3. ከሲቭል ሰርቪስ ኮሚሽን ጋር በጋራ በመሆን ለዞን ሲቪል ሰርቪስ መምሪያና እና ግብርና
፣ የገጠር መሬት እና የህብረት ስራ መምሪያዎች በመመሪያው ላይ ግልጽነት ይፈጥራል።
3.2.1.4. ሥራውን የሚከታተል ባለሙያ/Focal Person/ ይመድባል።
202
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የቀበሌ ልማት ሰራተኞች/ ባለሙያዎች/ የጽ/ቤት ኃላፊዎች የዝውውርና ምደባ አፈጻጸም
3.2.3.1. ከዞን ሲቪል ሰርቪስ መምሪያ የሚፈለግ መረጃ ሲኖር መረጃውን ተቀብሎ ለግብርና፣ የገጠር
መሬት ቢሮ እና የህብረት ስራ ኤጀንሲ ያስተላልፋል።
3.2.3.2. ከወረዳ ወረዳ መዛወር የሚፈልጉ የቀበሌ ግብርና ልማት ሰራተኞች/ ባለሙያዎች/ጽ/ቤት
ኃላፊዎች የዝውውር ፎርም በወቅቱ መረጃው ተሞልቶ በወረዳ ግብርና፣ የገጠር መሬት እና
የህብረት ስራ ጽ/ቤት በኩል እንዲላክለት በማድረግ እና ትክክለኛነቱን በማረጋገጥ ከሲቪል
ሰርቪስ መምሪያ ጋር በመሆን ዝውውሩን ይሰራል።
3.2.3.3. በስሩ ያሉ ተጠሪ ተቋማት የሚያስተዳድሯቸዉን የቀበሌ ሰራተኞች/ባለሙያዎችን መረጃ
በማሰባሰብ ዝዉዉር እንዲያካሂዱ ያስተባብራል።
3.2.3.4. በተቀመጠው የማወዳዳሪያ መስፈርት መሠረት የተወዳዳሪዎች ውጤቱን ይፋ ያደርጋል።
3.2.3.5. ስራውን የሚከታተል ባለሙያ /focal person/ ይመደባል።
3.2.3.6. በሲቪል ሰርቪስ መምሪያ ተሰርቶ የሚቀርብለትን ዝውውር፣ የግብርና፣ የገጠር መሬት እና
የህብረት ስራ መምሪያ ኃላፊ ወይም ምክትል ኃላፊው ወይም ተወካይ ዝውውሩን
ያጸድቃል።
203
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
3.2.5.1. ከቀበሌ ቀበሌ መዛወር የሚፈልጉ የቀበሌ ግብርና ልማት ሰራተኞች/ ባለሙያዎች/ጽ/ቤት
ኃላፊዎች የዝውውር ፎርም በወቅቱ በማስሞላትና መረጃውን በማጠቃለል ለወረዳ ሲቪል
ሰርቪስ ጽ/ቤት ይልካል።
3.2.5.2. በስሩ ያሉ ተጠሪ ተቋማት የሚያስተዳድሯቸዉን የቀበሌ ሰራተኞች/ባለሙያዎችን መረጃ
በማሰባሰብ በወቅቱ ዝዉዉር እንዲያካሂዱ ያስተባብራል።
3.2.5.3. ከሲቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት ጋር አብሮ ዝውውሩን የሚሰራ አንድ ሠራተኛ ይወክላል።
3.2.5.4. የዝውውር ደብዳቤ የደረሳቸው ሁሉም የቀበሌ ግብርና ልማት ሰራተኞች/
ባለሙያዎች/የጽ/ቤት ኃላፊዎች ደብዳቤው በደረሳቸው በ 1 ዐ/አስር/ የስራ ቀናት ውስጥ
በእጃቸው ያሉ ዝርዝር መረጃዎችን ወይም የተሰሩ ስራዎችን፣ ፋይሎችንና
ንብረቶችን ለቀበሌው ጽ/ቤት ርክክብ በመፈፀም አዲስ ወደ ተመደበበት/ችበት/ ቀበሌ
በመሄድ ሥራ እንዲጀምሩ ክትትል ያደርጋል።
204
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የቀበሌ ልማት ሰራተኞች/ ባለሙያዎች/ የጽ/ቤት ኃላፊዎች የዝውውርና ምደባ አፈጻጸም
3.2.5.5. በሲቪል ሰርቪስ ተሰርቶ የሚቀርብለትን ዝውውር የግብርና፣ የገጠር መሬት እና የህብረት
ስራ ጽ/ቤት ኃላፊው ወይም ምክትል ኃላፊው ወይም ተወካይ ለየተቋማቸው የተሰራውን
ዝውውር ያጸድቃሉ።
3.2.5.6. ዝውውር የተሰራላቸው የቀበሌ ግብርና ልማት ሰራተኞች/ባለሙያዎች/ጽ/ቤት
ኃላፊዎች የዝውውር ደብዳቤ እንዲደርሳቸውና የርክክብ ስርዓቱ በአግባቡ መፈጸሙን
በሁሉም ቀበሌ ተገኝተው ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል።
3.2.6.1. የዝውውር ፎርም በሚሞላበት የጊዜ ገደብ ውስጥ በወቅቱ በትክክል ሞልቶ ማቅረብ።
3.2.6.2. ዝውውሩ ከመሰራቱ በፊት የመረጃ ስህተት ያለበት ከሆነ በ 10 የስራ ቀናት ውስጥ
በማመልከቻ ቅሬታቸውን ለሲቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት ማቅረብ።
3.2.6.3. የቀበሌ ግብርና ልማት ሰራተኞች፤ባለሙያዎችና የጽ/ቤት ኃላፊዎች የዝውውር
ደብዳቤ ከደረሳቸው በኃላ ዝውውሩን መሰረዝ እንደማይቻል ማሳወቅ።
205
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
3.4. ተጠያቂነት
3.4.1. ለቀበሌ ግብርና ልማት ሰራተኞች/ባለሙያዎች/ጽ/ቤት ኃላፊዎች የዝውውር ቅጽ
መሙያ ጊዜን የተቋማት ኃላፊዎች የማሳወቅ ግዴታ አለባቸው። የቀበሌ ግብርና ልማት
ሰራተኞች/ባለሙያዎች/ጽ/ቤት ኃላፊዎች ሳያውቁት የዝውውር ጊዜው ቢያልፍባቸው
በየደረጃው ያሉ የግብርና ተቋማት ኃላፊዎች ወይም ተወካዮች ተጠያቂ ይሆናሉ።
3.4.2. ማንኛውም የቀበሌ ግብርና ልማት ሰራተኛ/ባለሙያ/ጽ/ቤት ኃላፊ ሕጋዊ ባልሆነ
ወይም በተጭበረበረ /የሐሰት/ ማስረጃ ጋብቻ እንዲፈፀም ቢያደርግ ወይም የሕክምና
ማስረጃ ወይም በሌላ ምክንያት እንዲዛወር/እንድትዛወር ያደረገ ወይም ያቀረበ መሆኑ
ሲረጋገጥ በዲስፕሊን ስነ-ሥርዓት አፈጻጸም መመሪያ መሠረት ይጠየቃል። ሆኖም ጉዳዩ
በሕግ የሚያስጠይቅ ሆኖ ከተገኘ አግባብ ባለው የወንጀል ሕግ ይጠየቃል። የተፈፀመው
ዝውውርም ይሰረዛል።
3.4.3. ማስረጃ ሳያቀርብ እንደቀረበ አድርጎ ዝውውር የፈፀመ ወይም ያስፈፀመ ባለሙያ ወይም
የስራ ኃላፊ በዲስፕሊን አፈጻጸም መመሪያ መሠረት ይጠየቃል። የተፈፀመውም
ስምሪት ይሰረዛል።
3.4.4. ይህን የዝውውር መመሪያ በተዛባ መልኩ ወይም ያለአግባብ የሚፈጽም የሚያስፈጽም አካል
ወይም ኃላፊ አግባብ ባለው ሕግ ተጠያቂ ይሆናል።
3.4.5. በየደረጃው ተሞልቶ ለሚመለከታቸው አካላት በሚላከው የቀበሌ ግብርና ልማት
ሰራተኞች/ባለሙያዎች/ጽ/ቤት ኃላፊዎች የግል መረጃ ላይ አላግባብ ተሞልቶ
ለሚፈፀመው ችግር መረጃውን የሞላው ባለሙያ ወይም ኃላፊ ተጠያቂ ይሆናል።
3.5. ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
3.5.1. በዚህ መመሪያ ያልተሸፈኑ ሌሎች የዝውውር ጉዳዮች በመንግስት ሠራተኞች አዋጅ
253/2010 እና ደንብ ቁጥር 75/2003 እና በምልመላ መረጣ መመሪያ መሠረት ተፈጻሚ
ይሆናል።
3.5.2. በማንኛውም ደረጃ ዝውውር የተሰራለት የቀበሌ ግብርና ልማት ሰራተኛ/ባለሙያ/ጽ/ቤት
ኃላፊ በመንግስት እውቅና በመደበኛ ትምህርት በክረምት ተከታታይ ትምህርት /ኮርስ/
ወይም የርቀት ትምህርት ፕሮግራም ወይም ተመሣሣይ
206
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሻሻለው የቀበሌ ልማት ሰራተኞች/ ባለሙያዎች/ የጽ/ቤት ኃላፊዎች የዝውውርና ምደባ አፈጻጸም
207
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
አቶ ሙሉቀን አየሁ
የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ኮሚሽነር
208
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የቀበሌ ስራ አስኪያጆች የዝውውር አፈጻጸም መመሪያ
ሰኔ 2013 ዓ.ም
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ባህር ዳር፣ ኢትዮጵያ
209
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
መግቢያ
የህብረተሰቡን ግንዛቤ ለማዳበርና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን በተዋረድ ከተቋቋሙት የዞንና የወረዳ
አስተዳደር ጽ/ቤት አደረጃጀቶች በተጨማሪ በቀበሌ ደረጃ ጉዳዩን በባለቤትነት ለማስፈጸም ይረዳ ዘንድ
በሁሉም የክልላችን የገጠር ቀበሌዎች አንድ አንድ የቀበሌ ስራ አስኪያጆች ተመድበው በማገልገል ላይ
ይገኛሉ።
እነዚህ የገጠር ቀበሌ ስራ አስኪያጆች በተመደቡበት ቀበሌ ህብረተሰቡን የሚጠቅም የልማትና የመልካም
አስተዳደር ተግባራትን እንዲያከናውኑ ለማስቻልና ሀላፊነታቸውን በብቃት፣ በከፍተኛ ተነሳሽነትና
ኃላፊነት ስሜት እንዲወጡ ለማድረግ የሚያነሷቸውን ጥያቄዎች ትኩረት በመስጠት ችግሩን
ለመፍታት ጥረት ሲደረግ የቆየ ቢሆንም አሁንም መፈታት የሚገባቸውና ጥያቄዎች እንዳሉ
የሚታዎቅ ሲሆን በተለይም ከዝውውር ጋር የተያያዘው ችግር ጎልቶ እየተነሳ ያለ ችግር ነው።
በመሆኑም በክልላችን ውስጥ በአስተዳደር ጽ/ቤት የገጠር ቀበሌ ስራ አስኪያጆች የዝውውር መመሪያ
ወጥነት ባለው መልኩ ባለመኖሩና መፈታትም ያለበት መሆኑ ታምኖበት ፤ በዚህ ዙሪያ የሚታዩትን
ችግሮች ለመፍታት ግልጽ የሆነና የማያሻማ መስፈርት በማስቀመጥ መፍታትና የመዛወር መብታቸውን
በአግባቡ ሊጠቀሙበት የሚያስችል ስርአት መዘርጋት አስፈላጊ በመሆኑ ይህን የገጠር ቀበሌ ስራ
አስኪያጆች የዝውውር መመሪያ ማውጣት አስፈልጓል።
ክፍል 1. ጠቅላላ
1.1. አጭር ርእስ
ይህ መመሪያ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የገጠር ቀበሌ ስራ አስኪያጅ የዝውውር አፈጻጸም
መመሪያ ቁጥር 11/2013 ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል።
1.2.1. ጽ/ቤት ፦ ማለት የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ነው።
1.2.2. የቀበሌ ስራ አስኪያጅ ፦ ማለት ከህዝቡ የሚነሱ አቤቱታዎችን አዳምጦ ተገቢ ምላሽ
የሚሰጥና ህብረተሰቡ የሚያደርገውን የልማትና የመልካም አስተዳደር እንቅስቃሴ
የሚያስተባብርና ቴክኒካዊ ድጋፍ የሚሰጥ ባለሙያ ነው።
210
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የቀበሌ ስራ አስኪያጆች የዝውውር አፈጻጸም መመሪያ
ይህ መመሪያ በክልሉ በሚገኙ ሁሉም የገጠር ወረዳ ቀበሌዎች ላይና በከተማ አስተዳደር ስር ባሉ
የገጠር ቀበሌዎች ላይ በገጠር ቀበሌ ስራ አስኪያጅነት እያገለገሉ በሚገኙ ሰራተኞች ላይ ተፈጻሚነት
ይኖረዋል።
2.1.1. አንድ የገጠር ቀበሌ ስራ አስኪያጅ ካለበት ቀበሌ ወደ ሌላ ቀበሌ ለመዛወር ባለበት ቀበሌ
ቢያንስ 2 አመት ማገልገል ይኖርበታል።
2.1.2. አንድ የገጠር ቀበሌ ስራ አስኪያጅ መደበኛ ዝውውር ከተጠናቀቀ በኋላ በቅጥር ወይም
በዝውውር ከሌላ ወረዳ ከመጣ በወረዳው ውስጥ ባሉት ክፍት ቦታዎች በጊዜያዊነት
ተመድቦ እንዲሰራ ይደረጋል።
2.1.3. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 2.1.2 የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ አንድ የገጠር ቀበሌ ስራ
አስኪያጅ በጊዜያዊነት ከተመደበ መደበኛ ዝውውር እስከሚታይ ድረስ በተመደበበት
ቀበሌ እንዲቆይ ይደረጋል።መደበኛ ዝውውር በሚፈጸምበት ጊዜ የያዘው ቦታ በሌሎች
211
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ነባር ዝውውር ጠያቂዎች የሚሸፈን ከሆነ ከቦታው ተነስቶ በተገኘው ክፍት ቦታ በቋሚነት
እንዲመደብ ይደረጋል።
2.1.4. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 2.1.3 በተገለጸው ሁኔታ በቋሚነት የሚመደቡ ስራ አስኪያጆች በወረዳው
ወይም በከተማ አስተዳደሩ 2 አመት እስካገለገሉ ጊዜ ድረስ ለቀጣይ ዝውውር በአንድ
ቀበሌ 2 አመት የመቆየት ግዴታ የለባቸውም።በጊዜያዊነት ተመድበው የነበሩ ስራ
አስኪያጆች በምደባ ወቅት ቁጥራቸው ከ 1 በላይ ከሆኑ ባላቸው ጠቅላላ አገልግሎት ቅደም
ተከተል መሰረት እንዲመደቡ ይደረጋል።
2.1.5. ለመዛወር የሚፈልጉ የገጠር ቀበሌ ስራ አስኪያጆች መዛወር የሚፈልጉባቸውን በሚሰሩበት
ወረዳ/ከተማ አስተዳደር ውስጥ ከሚገኙ ሶስት ቀበሌዎች በደረጃ ከ 1 ኛ እስከ 3 ኛ ድረስ
በመዘርዘር ለዚሁ አላማ በተዘጋጀው የመጠየቂያ ፎርም ሞልቶ በወቅቱ ለወረዳ
አስ/ጽ/ቤት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።ሆኖም ግን አንድ ስራ አስኪያጅ የዝውውር ፍላጐቱን
በደረጃ ዘርዝሮ ካቀረባቸው ቀበሌዎች በውጤቱ ምክንያት ማግኘት ባይችል በነበረበት
ቀበሌ ይቆያል።
2.1.6. ተመሳሳይ ፆታ ያላቸዉ የገጠር ቀበሌ ሰራ አስኪያጆች በቀበሌዉ ወይም በወረዳዉ
መቆየት የሚገባቸዉን የአገልግሎት ጊዜ አሟልተዉ ሲወዳደሩ እኩል ነጥብ ኑሯቸዉ አንድ
ተመሳሰይ ቀበሌ ቢመርጡ ቅድሚያ የሚሰጠዉ የተሻለ የስራ አፈፃፀም ዉጤት ያለዉ
ሲሆን ዉጤቱም በቅርብ ጊዜ የተሞላለት ከአንድ ዓመት በላይ ያገለገለ ከሆነ
የአመቱ፤ከአንድ አመት በታች የሰራ ከሆነ የስድስት ወራት ይሆናል።
2.1.7. ተቃራኒ ፆታ ያላቸዉ የቀበሌ ሰራ አስኪያጆች እኩል ነጥብ ኑሯቸዉ አንድ ተመሳሰይ ቀበሌ
ቢመርጡ ቅድሚያ የሚሰጠዉ ለሴቷ ነዉ።
2.1.8. በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ 2.1.7 ላይ የተጠቀሰው እንዳለ ሆኖ አንድ የገጠር ቀበሌ ስራ
አስኪያጅ አስቀድሞ የዝውውር ፍላጎቱን ካሳወቀ በኋላ ካለበት ቀበሌ መዛወር ካልፈለገ
ዝዉዉር ከመሰራቱ በፊት በማመልከቻ ለወረዳው/ለከተማ አስተደደር አስተደደር ጽ/ቤት
ማሳወቅ አለበት። ይሁን እንጅ ጥያቄው ተቀባይነት አግኝቶ ባለበት እንዲቆይ ከተደረገ ሌላ
ዝውውር ሊታይለት የሚችለው ከ 1 አመት ቆይታ በኋላ ሲሆን የሚያዝለትም
የመጨረሻዉ የአንድ አመት አማካይ የስራ አፈጻጸም ውጤት ነው።
2.1.9. ከወረዳ ወደ ወረዳና ከዞን ወደ ዞን የሚደረግ ዝውውር በመደበኛው የሲቪል ሰርቪስና የሰው
ሀብት ልማት ቢሮ ባወጣው የምልመላና መረጣ የውጭ ዝውውር መመሪያ መሰረት ሆኖ
ጽ/ቤቱ በጀት እስካለው ድረስ ሁሉንም የገጠር ቀበሌ ስራ አስኪያጆች
212
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የቀበሌ ስራ አስኪያጆች የዝውውር አፈጻጸም መመሪያ
213
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
2.3.1. የጋብቻ ማስረጃ የመደበኛ ዝውውር ከመደረጉ ከስድስት ወራት በፊት ከዝውውር
ተጠቃሚዎች ከግል ማህደራቸው ተያይዞ መገኘት አለበት።
2.3.2. የጋብቻ ማስረጃው ተቀባይነት የሚኖረው ህጋዊ ከሆነ ማዘጋጃ ቤት ወይም የሀይማኖት ተቋም
ወይም የሀገር ሽማግሌዎች የተሰጠ ስለመሆኑ በቅድሚያ ሲረጋገጥ ነው።
2.3.3. ባለትዳሮች ትዳርን መሰረት ያደረገ ዝውውር ሊጠይቁ የሚችሉት የባልና ሚስት
አገልግሎት ተደምሮና አማካይ ተወስዶ ከሌሎች ተወዳዳሪዎች በነጥብ በልጠው ሲገኙ
መሆን ይገባዋል።ሆኖም የባለትዳሮች ነጥብ ከሌሎች የቀበሌ ስራ አስኪያጆች እኩል ከመጣ
ለባለትዳሮች ቅድሚያ እንዲሰጥ ይደረጋል።
2.3.4. ባለትዳሮች ዝውውር የሚጠይቁት ለመቀራረብ እስከሆነ ድረስ ባለትዳሮችን የማቀራረብ
ሁኔታ በዝውውር ወቅት ትኩረት ሊሰጠው ይገባል።ይህም ማለት መደበኛ ዝውውሩ
እንደተጠናቀቀ አንድ የቀበሌ ስራ አስኪያጅ የትዳር ጓደኛው/ዋ ወዳለበት ቅርብ የገጠር
ቀበሌ ለመዛወር ጠይቆ/ቃ በውጤት ምክንያት ባይሳካ ለትዳር ጓደኛ
214
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የቀበሌ ስራ አስኪያጆች የዝውውር አፈጻጸም መመሪያ
ቅርብ በሆነ የገጠር ቀበሌ በዚሁ ወቅት ክፍት ቦታ ካለ ለትዳር በተሰጠ ነጥብ መዛወር
ይቻላል።
2.3.5. በተለያዩ ሁለት የገጠር ቀበሌዎች የሚኖሩ ባለትዳር የገጠር ቀበሌ ስራ አስኪያጅ ወደ አንዳቸው
አቅራቢያ ቀበሌ ለመዛወር ሁለቱም በዝውውር መጠየቂያ ፎርም ላይ የመጠየቅ መብት
አላቸው።
2.3.6. ባለትዳሮች ዝውውር የሚጠይቁት ለመቀራረብ እስከሆነ ድረስ ባለትዳሮቹ በአንድ ወረዳ
/ ከተማ አስተዳደር / ስር ባይሆኑም የምትመርጠው / የሚመርጠው ቀበሌ / ወደ
አጐራባች ወረዳ ቀበሌ የሚቀርብ ከሆነ ለጋብቻ የሚሰጠው ነጥብ ተጠቃሚ ይሆናሉ ።
2.4. በዝውውር ወቅት ትኩረት የሚሹ ጉዳዩች
2.4.1. ለሴቶች ብቻ ባገኙት ነጥብ ላይ የሚደመር 3 ነጥብ ይሰጣል።ነገር ግን በትዳር ምክንያት ነጥብ
የተሰጣቸውን ሴቶች ይህ ነጥብ አይመለከታቸውም።
2.4.2. የኤች አይ ቪ ኤድስ ህሙማን ስለመሆናቸው ህጋዊ የህክምና ማረጋገጫ የሚያቀርቡ የገጠር
ቀበሌ ስራ አስኪያጆች ከማንኛውም ዝውውር ፈላጊ ቅድሚያ ለህክምና አመች በሆነ ቦታ
ይመደባሉ።ችግሩ ያለባቸው ከአንድ በላይ ከሆኑ ባለትዳር ለሆነ/ች/ቅድሚያ
ይሰጣል።ባለትዳር ካልሆኑ በስራ አፈጻጸም ውጤት እንዲለዩ ይደረጋል።
2.4.3. የኤች አይ ቪ ኤድስ ህሙማን ስለመሆናቸው ህጋዊ የህክምና ማረጋገጫ የሚያቀርቡ ዝውውር
ፈላጊዎች እስከሌሉ ድረስ በጤና ችግር ምክንያት በሶስት ሀኪም የተፈረመ የህክምና
ማስረጃ ለሚያቀርቡ ስራ አስኪያጆች ቅድሚያ ይሰጣል።የሚቀርበው የህክምና ማስረጃ
ስራ አስኪያጁ/ጇ በበሽታው/ዋ/ምክንያት አሁን በሚሰራበት/በምትሰራበት/ ቦታ ላይ
ሊቀጥል/ልትቀጥል/የማይችሉበት ሁኔታና ሌሎች መሰል ጉዳዩችን የሚገልጽ መሆን
ይኖርበታል።
2.4.4. ከላይ በተራ ቁጥር 2.4.2. እና 2.4.3 ከተጠቀሰዉ ዉጭ በጤና ችግር ምክንያት ከመንግስት
ዞናል ወይም ሪፈራል ማስረጃ መቅረብ አለበት።
2.4.5. በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ 2.4.2 እና 2.4.3 እና ከተመለከተው ውጪ ያሉ የገጠር
ቀበሌ ስራ አስኪያጆች ባላቸው የዝውውር ድምር ውጤት መሰረት የሚገባቸውን ቀበሌ
እንዲይዙ ይደረጋል።የተለያየ ጾታ ያላቸው ተወዳዳሪዎች እኩል ነጥብ ካመጡ ቅድሚያ
ለሴቷ ይሰጣል።ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው እኩል ነጥብ ካመጡ በስራ አፈጻጸም ከሚሰጠው
ውጤት ብልጫ ነጥብ ያለው ቅድሚያ ይሰጠዋል።
215
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
2.5.2. በውጤት ተኮር ምዘና ስርአት መሰረት የሁለት አመት ስራ አፈጻጸም አማካይ ነጥብ
ከ 65%ይያዛል።ይህም የቀበሌ ስራ አስኪያጆችን በቀጣይ የበለጠ ለስራ እንዲነሳሱና
ውጤታማ እንዲሆኑ ከማስቻሉም በላይ ጤናማ የሆነ የውድድር መንፈስ ይፈጥራል።
በመሆኑም አንድ የገጠር ቀበሌ ስራ አስኪያጅ በተመደበበት ቀበሌ በተጨባጭ ያመጣው
ለውጥ መነሻ ተደርጐ የተሰጠው የ 2 አመት የስራ አፈጻጸም አማካይ ውጤት ከ 65%
ይያዛል።ወይም የስራ አፈጻጸም ውጤቱ በ 0.65 ተባዝቶ ይቀመጥለታል።ይህም ማለት
የሁለት አመት አማካይ ውጤት 80%ላመጣ የቀበሌ ስራ አስኪያጅ
80x0.65=52%ይሰጠዋል ማለት ነው።ሆኖም ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት የ 2 አመት
የስራ አፈጻጸም ከሌለው የአስተዳደር ጽ/ቤት ሀላፊ ካመነበትና ለዚህም ማረጋገጫ
ከሰጠ ያለውን የስራ አፈጻጸም አማካይ ውጤት መውሰድ ይቻላል።
2.5.3. የስራ ልምድ/አገልግሎት ዘመን/ ከ 20% ይያዛል።የቀበሌ ስራ አስኪያጁ ለመስሪያ ቤቱ ወይም
ለሀገሩ በሰጠው የአገልግሎት ዘመን ሊበረታታ የሚገባው በመሆኑ በየትኛውም ቦታና
በማንኛውም የስራ መስክ የሰራበትና በህጋዊነት የሚያዝለት የአገልግሎት ዘመን/የስራ
ልምድ/እንደ አንድ መመዘኛ ተወስዶ ከ 20%የሚያዝ ሆኖ 20 አመትና በላይ የአገልግሎት
ዘመን /የስራ ልምድ/ያለው የቀበሌ ስራ አስኪያጅ 20% ይሰጠዋል።ሆኖም ከ 20 አመት
በታች አገልግሎት ያላቸው ስራ አስኪያጆች የሚሰጣቸው ነጥብ በአገልግሎት
ዘመናቸው ልክ ይሆናል።ይህም ማለት 20አመት
216
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የቀበሌ ስራ አስኪያጆች የዝውውር አፈጻጸም መመሪያ
217
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
2.6.1. የአስተዳደር ጽ/ቤት የቀበሌ ስራ አስኪያጆች ተግባራት አመቱን በሙሉ የሚከናወኑ ቢሆንም
በስራ አፈጻጸም ላይ የሚኖረውን ተጽእኖ ማገናዘብ በማስፈለጉ ዝውውር ጠያቂዎች
ጥያቄያቸውን አመታዊ የስራ ግምገማና የውጤት ተኮር ምዘና ከተፈጸመ በኋላ በየአመቱ
ከጥቅምት 1 ቀን ጀምሮ ባሉት ሰባት ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ በዝውውር መጠየቂያ
ቅጽ መሰረት ጥያቄያቸውን ያቀርባሉ።ዝውውሩም እስከ ጥቅምት 30 ይፈጸማል።
2.6.2. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 2.6.1 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ የዝውውር ፎርም ሞልተው
እድሉን ያላገኙ ስራ አስኪያጆች ባሉበት ቀበሌ 2 አመት መቆየት ሳይጠበቅባቸው ዝውውሩ
በተሰራበት ቀጣይ አመት የዝውውር ፎርም በድጋሜ በመሙላት የእድሉ ተጠቃሚ መሆን
ይችላሉ።
3.1.1. የሁሉንም የቀበሌ ስራ አስኪያጅ ባለሙያዎች መረጃ በአግባቡ አጠናቅሮ ለዚሁ በተዘጋጀው
ፎርም መሰረት ማስሙላት፣
3.1.2. የመደበኛ ዝውውር ማስታወቂያ ለሁሉም የቀበሌ ስራ አስኪያጅ እንዲደርስ አመች በሆኑ
ቦታዎች ሁሉ እንዲለጠፍ ማድረግና በደብዳቤ ማሳወቅ፣
3.1.3. ከቀበሌ ስራ አስኪያጆች የሚመጣውን የመደበኛ ዝውውር መጠየቂያ ፎርም በመረከብ ለምደባ
ማመቻቸት፣
3.1.4. የቀበሌ ስራ አስኪያጆችን የዝውውር ዝርዝር መረጃና የጠየቁትን ቀበሌ ግልጽ በሆነ ቦታ
እንዲለጠፍና በአስተዳደር ጽ/ቤት አማካኝነት እንዲያውቁት በማድረግ የመረጃ መዛባት
ያለበት ስራ አስኪያጅ ካለ እንዲስተካከል ማድረግ፣
3.1.5. በወረዳው / ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት ሀላፊ ከፀደቀ በኋላ የዝውውር ውጤቱን ለሁሉም
የቀበሌ ስራ አስኪያጆች ግልጽ በሆነ ቦታ በመለጠፍ ስራ አስኪጆች እንዲያውቁት
ማድረግና የተመደቡበትን የስራ ቦታ በደብዳቤ ማሳወቅ ይሆናል።
218
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የቀበሌ ስራ አስኪያጆች የዝውውር አፈጻጸም መመሪያ
219
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
የቀበሌ ስራ አስኪያጆች
220
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የአካል ጉዳተኞች የሥራ ስምሪት መመሪያ፣
ሰኔ 2013 ዓ.ም
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ባህር ዳር፣ ኢትዮጵያ
221
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
መግቢያ
አካል ጉዳተኞች እንደማንኛውም ዜጋ መድሎ ሣይደርስባቸው በማህበራዊና ኢኮኖሚው ዘርፎች ላይ
እኩል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ የሚያስችል ራሱን የቻለ የማስፈጸሚ ያደንብ አለመኖሩን
በመረዳት፣
የአካል ጉዳተኞች ስምሪት ከተፈጸመ በኋላ ለሥራ መሣሪያ ስለሚገለገሉባቸው ቁሣቁሶች ጉዳይ በግልፅ
ያልተቀመጠ በመሆኑ፤ በክልሉ የሚገኙ የአካል ጉዳተኞችን በህግ ለማስተናገድ እንዲቻል ግልፅ የሆኑ
መመዘኛዎችን አውጥቶ በሥራ ላይ ማዋል በማስፈለጉ፣በፌደራል ደረጃ ስለ አካል ጉዳተኞች የስራ
ስምሪት መብት የወጣው አዋጅ ቁጥር 568/2008 ላይ የተመለከቱ ድንጋጌዎችን ማካተት በማስፈለጉ፣
የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ተሻሽሎ በወጣው የአብክመ መንግስት
ሰራተኞች አዋጅ 253/2010 አንቀጽ 50 መሠረት ይህንን መመሪያ አውጥቷል።
ይህ መመሪያ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የአካል ጉዳተኞች የሥራ ስምሪት መመሪያ ቁጥር
12/2013 ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል።
1.2. ትርጐሜ
ሀ. "አዋጅ" ማለት በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 253/2010 ዓ/ም
ነው።
222
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የአካል ጉዳተኞች የሥራ ስምሪት መመሪያ፣
በሚታይ ሁኔታ በተፈጥሮ ወይም በሰው ሰራሽ አደጋ ምክንያት በአጋጠመው ጉዳት የተነሳ
የአንቅስቃሴ ችግር ያለበት ሰው ነው።
ሠ. ”ምቹ የስራ አካባቢ” ማለት የአካል ጉዳተኛ ሠራተኛን የሥራ ሁኔታ ለማመቻቸት
ሲባል መሣሪያዎች በሥራ ይዘት መዘርዘር፣ በሥራ ስዓት፣በሥራ አደረጃጀትና የሥራ አካባቢ ላይ
የሚደረግ ለውጥ ወይም ማስተካከያ ነው።
ረ. "የሥራው ፀባይ የማይፈቅድ" ማለት ተፈላጊውን ችሎታ የሚያሟላ አካል ጉዳተኛ ተመጣጣኝ
ማመቻቸት ተደርጐለትም ቢሆን ሊያከናውነው የማይችል ሥራን ያመለክታል
223
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
የሥራው ፀባይ የማይፈቅድ ካልሆነ በስተቀር የተፈላጊ ችሎታ መመዘኛዎችን አሟልቶ የተገኘና
በውድድር ውጤቱ ብቁ ሆኖ የተገኘ አካል ጉዳተኛ በምንም አይነት መልኩ መድልዎ አይደረግበትም፣
በስራው ፀባይ አካል ጉዳተኛ የማይሰማራባቸውን የሥራ መደቦች የመለየትና የመወሰን ስልጣን፣
በየደረጃው የሚገኘው የሰው ኃብት ሥራ አመራር ዳይሬክቶሬት/ቡድን/እና ስምሪቱ የሚፈጽምለት
ዳይሬክቶሬት/ቡድን/ የጋራ ኃላፊነት ይሆናል። በግልጽ የሚታይ የአካል ጉዳት አይነትንም የመወሰን
ወይም የመፈረጅ ስልጣን የሰው ኃብት ሥራ አመራር ዳይሬክቶሬት/ቡድን/ ይሆናል።
3.2.1. ማንኛውም አካል ጉዳተኛ የሥራው ፀባይ ካላገደው በስተቀር በማንኛውም መ/ቤት
ውስጥ በሚወጡ የቅጥር ማስታወቂያዎች ተወዳድሮ የመቀጠር መብቱ የተጠበቀ ሆኖ
224
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የአካል ጉዳተኞች የሥራ ስምሪት መመሪያ፣
225
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
አካል ጉዳተኞች ወደ ሲቪል ሰርቪስ ከተቀላቀሉ በኋላ በደረጃ ዕድገትና በድልድል የሚወዳደሩ ከሆነ
ለወንድ አካል ጉዳተኞች ከፈተና በፊት 4 ነጥብ የሚሰጥ ይሆናል ። ተወዳዳሪ አካል ጉዳተኞች
ሴቶች ከሆኑ ሴቶች ከሴቶች ጋርም ሆነ ሴቶች ከወንዶች ጋር ሲወዳደሩ ለኃላፊነት ቦታዎች 6
ነጥብ፤ ለሌሎች የሥራ መደቦች 5 ነጥብ ይሰጣቸዋል።
አካል ጉዳተኞች በውስጥም ሆነ በውጭ ዝውውር ውድድር ወቅት ለሴት አካ ጉዳተኞች 5 ነጥብ ለወንድ
አካል ጉዳተኞች 4 ነጥብ ይሰጣል ። ይህም ሆኖ ሴቶች ከወንዶች ጋር እኩል ነጥብ ካመጡ
ቅድሚያ ለሴቶች ይሰጣል ። ሆኖም ተመሳሳይ ፆታ ያላቸው ተወዳዳሪዎች እኩል ነጥብ ካመጡ
አሸናፊው በዕጣ ይለያል ።
ክፍል 4. ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
4.1. የአካል ጉዳት ያለበት ሠራተኛ ግዴታዎች
ማንኛውም የመንግስት መ/ቤት አካል ጉዳት ላለበት የመንግስት ሠራተኛ በዚህ መመሪያ በትርጓሜው
ላይ እንደተገለፀው ተመጣጣኝ ማመቻቸት በሚለው መሠረት ምቹ የሥራ ሁኔታ የመፍጠር ግዴታ
ተጥሎበት፤የሚከተሉትንም መፈጽም ይኖርበታል።
ሀ. አካል ጉዳተኛው ዐይነ ስውር ከሆነ ከሌሎች ሠራተኞች ጋር ያለውን የሥራ መስተጋብር
ለማሳለጥና የተሰጠውን ተግባርና ኃላፊነት በአግባቡ ይወጣ ዘንድ ረቂቅ አንባቢ እና ፀሀፊ
በኮንትራት የመቅጠር ግዴታ አለበት። መስማት ለተሳናቸውም እንደዚሁ የምልክት ቋንቋ
አስተርጓሚ ይቀጠርላቸዋል።
226
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የአካል ጉዳተኞች የሥራ ስምሪት መመሪያ፣
ማንኛውም አካል ጉዳት ያለበት ሠራተኛ አድሎ የተፈፀመበት መስሎ ከተስማማው ወይም ያለ አግባብ
አስተዳደራዊ በደል የደረሰበት እንደሆነ እንደማንኛውም የመንግስት ሠራተኛ ሁሉ ቅሬታውን
በየደረጃው ለሚገኝ የቅሬታ ማስተናገጃ ባለሙያ በቅሬታ አቀራረብ ስነ- ስርዓት የማቅረብ መብት
አለው።
4.4. ማንኛውም የስራ ኃላፊ ወይም ሰራተኛው ባለው ስልጣን መሰረት ከህግ ውጭ ለሚፈፅማቸው
የምልመላ መረጣ ተግባራት ሁሉ በህግ ተጠያቂ ይሆናል።
4.5. መመሪያው በሥራ ላይ የሚውልበት ጊዜ
አቶ ሙሉቀን አየሁ
የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ኮሚሽነር
227
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ሰኔ 2013 ዓ.ም
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ባህር ዳር፣ ኢትዮጵያ
228
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የሴቶች ልዩ ድጋፍ እርምጃ አፈፃፀም
æ9u=Ám
fi?ek høS9k ÒC እ h~6 †£ታ d እ S4=I’~ 5T9£9 በህገ-መንግስቱና ሌሎች ህጎች ላይ
ትኩረት ተሰጥቶት ወደ ተግባር የተገባ ቢሆንም uእ h~6’h SS ¾†æt£† USU ›96b
¾5?5uhm Á5†îbff 5እh~6 W^ የእh~6 hõÁ †ÖQT˛ ¾æIS æwታ1ø~ እንዲረጋገጥ T
tÑ^фT h6Sф ¾fi?ek Ñ~4S þ5=fi=bk በመቅረፅ ¾ ጾታ 4wTCS በ Tæ×ÖS uJ~5~U
የመ/መቤቶች ተግባራዊ ይደረጋል ።
ስለሆነም uæS94 ት መ/ቤቶች uTS2ø~U የስራ P£9 ¾æቀጠርm የመዛወር m የደረጃ ዕድገትና
ስልጠና ¾T9Z@h፤ ኃ Sd’h የሚጠይቁ የስራ h ታዎች S ÚUa የልዩ ድጋፍ እርምጃ ተጠቃሚ
እንዲሆኑ በመደረጋቸዉ ከአሁን በፊት ከነበረው ዝቅተኛ አፈፃፀም በአሁኑ ወቅት ከክልላችን ጠቅላላ
የመንግስት ሰራተኛ 41% ተሳትፎ የደረሰ ቢሆንም በቀጣይ የተጠናከረ ስራ በመስራት 50% እና በላይ
እንዲደርስ ለማድረግ ሁሉም የመንግስት ተቋማት የሴቶች ልዩ ድጋፍ እርምጃ መመሪያ በአግባቡ ወደ
ተግባር በመቀየር የሴቶችን ተሳትፎ ተግባራዊ ማድረግ ያለበት በመሆኑ ና በአፈፃፀም ላይ ያጋጠሙ
ክፍተቶችን እና ግልፅነት የጎደላቸውን አንቀፆች ላይ ማሻሻያ ማድረግ በማስፈለጉ የአማራ ብሔራዊ
ክልላዊ መንግስትሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 253/2010 አንቀፅ 96 ን/አንቀፅ 2 በተሰጠው
ስልጣን መሰረት ይህን ¾fi?ek 6¿ 9Òõ እ CU9bk T4A9T˛Á ææs ያ አውጥቷል።
ክፍል 1. ÖpSS
1.1. ݧC Cb4m
1.2. hCGT@m
¾Q5~ ›Ñvw 5?S hCÑ~U ¾T˛ÁfiÖø~ h6I’ u4†kC uk=U ææsÁ ø~4T
1.2.1. «¾fi?ek ¾6¿ 9Òõ እ CU9» T5h ufi=W=6 fiCW=fi~ ø~4T u¾P£9ø~ um
†£hö Á6’u^1ø~S fi?ek uhUUChT W6ÖT እ S4=J~U uk=J~ ›ThV’h
wQታ 1ø~S ›4w£ø~ fi=ÑZ~ upTCm uEø~ø~CT uP£9 b9Ñh 6¿ 9Òõ
uæ4Öh ¾T˛ታ¾ø~S ¾8ታ 4wTC 6¿’h 5TTuw ¾T˛øfi9 ’ø~:፡
229
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
1.2.2. «¾æS94h æWsÁ u?h» T5h ^fi~S k5A u›D9 øSU uPSw ¾†ØØæT
æ~5~ uæ~5~ øSU uhd6 hæS94h uT˛æPw5h u9h ¾T˛†4PC ¾h66
æS94h æWsÁ u?h ’ø~::
1.2.3. « ¾£»U Ñ˛k? W6ÖT » T5h ›S9 ¯æhT hk=ÁU Ñ˛k? uSS ¾T˛A9
W6ÖT Iff ¾T˛Á4ÑZø~ ¾hUUCh P£9 tChdh?hm 4=†5ATm ¾æ9æsÁ
ዲ 9s øSU hk=Á uSS 5=IS ¾T˛k6 ’ø~::
1.2.4. « ¾›ßC Ñ˛k? W6ÖT » T5h 5›W^ ›U4h kST hk=ÁU uSS ’ÑC 9S
ከአንድ ዓመት S’fi Ñ˛k? ¾T˛fiTm ›S9 A9T˛ ¾T˛ÁhTø~’ø~S †9vC
¾›A99U wQh 5T£P9 ታ 4h ¾T˛kÒ9 uøpß እ ¾†t^ h5ø~ †9vC ÒC ¾†
%^Z W6ÖT ’ø~ ::
1.2.5. “የኃላፊነት ቦታ” ማለት በነጥብ የሥራ ምዘናና ደረጃ አወሣሰን ጥናት በመንግስት
ተቋማት ላይ ሥራዎችን ከመነሻ እስከ መድረሻ የሚያከናውኑ ባለሙያዎች ስብስብ በመያዝ
በዳይሬክተር/በቡድን መሪ ደረጃ የተሰጠ የስራ ቦታ ነው ።
1.2.6. “አካል-ጉዳተኛ” ማለት ለዚህ መመሪያ አፈጻጸም በደረሰበት የአካል፣
የአእምሮወይምየስሜትሕዋሣት ጉዳትን ተከትሎ በሚመጣ የኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ
መድሎ ሣቢያ በሥራ ስምሪት የእኩል ዕድል ተጠቃሚ ያልሆነ ሰው ሲሆን አንድ ሰው
የአካል ጉዳተኛ ተደርጐ የሚወሰደው ሙሉ በሙሉ አይነ ስውር ወይም ሙሉ በሙሉ
መስማት የተሣነው ወይም በተጨማሪ ድጋፍ የሚንቀሣቀስ ወይም በተጨማሪ ድጋፍ
ባይንቀሳቀስም በግልጽ በሚታይ ሁኔታ በተፈጥሮ ወይም በሰው ሰራሽ አደጋ ምክንያት
በአጋጠመው ጉዳት የተነሳ የአንቅስቃሴ ችግር ያለበት ሰው ነው።
SU ¾fi?ek ¾6¿ 9Òõ እ CU9 ææsÁ Ep†2 †ASÑ˛ k5Aታø~S ›TE6†ø~ uæS94h
æWsÁ u?ek ø~4T 5pTCm ለዝውውር m ለደረጃ እድገት m 5W6ÖTT †1T9 ለሆኑ
¾fiø~ ኃብት ›4†4PC hSD’@bk 5T˛kCu~ fi?ek J~5~ †A9T˛ SIT6::
230
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የሴቶች ልዩ ድጋፍ እርምጃ አፈፃፀም
በዚህም መሠረት 5›ßC Ñ˛k? uT˛fiT ¾æ~Á TflflÁ W6ÖT SS ሴቶች እርስ በእርሳቸውም
ሆነ ከወንዶች ጋር ሲወዳደሩ ለሴቶች ተጨማሪ 10 ነጥብ ይሰጣል :: ከወንዶች ጋር ተወዳድረው እ h~6
uT˛æÖ~uh Ñ˛k? ደግሞ 5fi?ቷ p9T˛Á Sfi×6:: እንዲሁም ሴት አካል ጉዳተኞች 11 ነጥብ
ይሰጣል።
2.1.3. pTር
ሀ) ክፍት የስራ መደቦችን በሰው ኃብት ለመሙላት በመስሪያ ቤቶች የሚወጡ የቅጥር ማስታወቂያዎች
ደረጃ V እና ከዚያ በታች የትምህርት ደረጃ የሚጠይቁ ሲሆኑ ለመቅጠር ከታቀደው መካከል 20%
ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታውን አሟልተው የሚመዘገቡ ሴቶች እርስ በእርሳቸው ተወዳድረው
እንዲይዙት ይደረጋል ።ቀሪውን 80% ወንዶችና ሴቶች ይወዳደሩበታል
o ዲግሪና ከዚያ በላይ የትምህርት ደረጃ የሚጠይቁ የስራ መደቦች ላይ ደግሞ 25% ዝቅተኛ
231
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ተፈላጊ ችሎታውን አሟልተው የሚመዘገቡ ሴቶች እርስ በእርሳቸው ተወዳድረው እንዲይዙት ይደረጋል
። ቀሪውን 75% ወንዶችና ሴቶች ይወዳደሩበታል ከወንዶች ጋር ሲወዳደሩም በአገኙት ውጤት
ላይ ለኃላፊነትቦታ 5 ነጥብና ከኃላፊነት ውጭ ላሉ የስራ መደቦች የሚደመር 3 ነጥብ ይሰጣቸዋል
። ይህም ሆኖ እኩል በሚመጡበት ጊዜ ለሴቷ ቅድሚያ የሚሰጥ ይሆናል።
ሐ).ቅጥሩ የሚፈጸመው በፑሉ ውስጥ በታቀፉ መ/ቤቶች፤ በፑል ያልታቀፈ ከሆነ ደግሞ በመ/ቤቱ
የሚፈጸሙ ቅጥሮች እየተቆጠሩ በተከታታይ ከሚፈፀሙ ቅጥሮች መካከል ደረጃ V እና ከዚያ በታች
የትምህርት ደረጃ የሚጠይቁ ከሆነ ከአምስቱ አንዱ ወይም ዲግሪ እና ከዚያ በላይ የትምህርት ደረጃ
የሚጠይቁ ከሆነ ከአራቱ አንዱ ሴቶች ብቻ እንዲወዳደሩበት ይደረጋል። በዞንና በወረዳ በነጠላ
አደረጃጀት ቅጥር የሚፈፀም በመሆኑ እንደ ወረዳ ወይም ዞን የሚፈፀመው የሁሉም ተቋማት ቅጥሮች
እየተቆጠሩ በተከታታይ ከሚፈፀሙ ቅጥሮች መካከል ዲግሪ እና ከዚያ በላይ የትምህርት ደረጃ
የሚጠይቁ ከሆነ ከአራቱ አንዱ ወይም ደረጃ V እና ከዚያ በታች የትምህርት ደረጃ የሚጠይቁ
ከሆነ ከአምስቱ አንዱ ሴቶች ብቻ እንዲወዳደሩበት ይደረጋል።
2.1.4. ዝውውር
232
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የሴቶች ልዩ ድጋፍ እርምጃ አፈፃፀም
ለሌሎች የሥራ መደቦች 3 ነጥብ መሰጠቱ እንደተጠበቀ ሆኖ ሴቶች ከወንዶች ጋር ተወዳድረው እኩል
ከመጡ ቅድሚያ ለሴቷ ይሰጣል። አካል ጉዳተኞች ወደ ሲቪል ሰርቪሱ ከተቀላቀሉ በኋላ በደረጃ እድገት
የሚወዳደሩ ከሆነ ሴቶች ከሴቶች ጋርም ሆነ ሴቶች ከወንዶች ጋር ሲወዳደሩ ለኃላፊነት ቦታዎች 6
ነጥብ፤ ለሌሎች የሥራ መደቦች 5 ነጥብ ይሰጣቸዋል።ሆኖም ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው ተወዳዳሪዎች
እኩል ነጥብ ካመጡ አሸናፊው በምልመላ መረጣ መመሪያ አንቀጽ
2.7.2 ንዑስ አንቀጽ 2.7.2.3 በተገለፀው መሠረት ይለያል።
2.2.1. «u9 ታ እ h~6’h ›Uff እ h~6 ¾W^ b96 †ÖQT˛’hS T4huC» የሚለውን
መርህ በባለቤትነት ይዞ ማራመድ ፣
2.2.2. fi?ek ufi=W=6 fiCW=fi~ ø~4T ወደ ›æ^C መምጣት ይችሉ ዘንድ ¾†5Á¿
¾W6ÖT †a9^VkS TkT9hm
2.2.3. ¾fi?h ¾æS94h t^†PkS ¾6¿ 9Òõ እ CU9bk uT£ÒÑT £Ñ9 ›bS ታ ф
T˛T 5=Ýbß hT˛k5~T u¾P£9ø~ hT˛ÑZ~ 6¿ 6¿ ¾fi?ek æS94 ታ ф ›hShT
233
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
234
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የሴቶች ልዩ ድጋፍ እርምጃ አፈፃፀም
2.2.4. ¾fi?ekS ¾6¿ 9Òõ እ CU9 መመሪያ †A9T˛’h 5T£ÒÑTT ¾ø~£’@ fiß’h
9Cfl 5TÖThC ¾T˛Á9E u9h uum J~ኔታ ææPwm æS94 ታ ф h6I’~
9C9ekU 9Òõ TæSÚhm
2.2.5. fi?ekS ›4æ6he ufi=W=6 fiCW=fi~ ø~4T ¾†P’ÑÑ~ hÑAkS PShkንT
ææsÁbkS u†fl5 hh~£h æAìU እና በየሩብ አመቱ አፈፃፀሙን መገምገም፤
2.2.6. ¾†fl5 lTC ÁS1ø~S fi?ek ከቴክኒካል W^bk øP ø~£’@ ሰ ß’h TU×hm
2.2.7. ufi=W=6 fiCW=fi~ ø~4T fi?ekS ዝቅ አድርጎ ¾T¾h ›æ5hhh
5æp£õT u^4 ¾æ†TæS æSA4S TÑA6uhm
2.2.8. JÑCS 5T1P9T 9U’hS 5æp£õ fi?h ¾æS9Wh t^†Pk
¾T˛Öupv1ø~S 9Cfl TæShh m
2.2.9. fi?h ¾æS94h t^†Pk 56Th ና ለውጤታማ ስራ uT˛ÁPCÑ~h T£h
እ Sp@h 5=I’~ ¾T˛k5~ TUu^ф k9akS T4øÑ9 m
2.2.10. fi?ekT ¾W^ J~’@ታ1ø~S ¾†æ5hß TThT UCUakS Tht@9m
2.2.11. ¾†fl5~hS TTek uæU£T 5fi=Uþk=¾VkT 5hhæh uTwQh ¾ዕC4
u ዕ C4 æTTCS TkSÖõm
2.2.12. በስርዓተ ፆታ ዙሪያ ለሠራተኞች በቂ ግንዛቤ ማስጨበጥ፣
2.2.13. የሰው ኃብት ስምሪትን እንዲሁም ስልጠናን በተመለከተ በእቅድ ሂደት ውስጥ የሴቶችን
ተሳትፎ ማረጋገጥና የሚጠናቀሩ የሰው ሀይል መረጃዎችም በፆታ ተለይተው እንዲቀመጡ
በማድረግ መረጃ በሚጠየቅበት ጊዜ ለሚመለከተው አካል በወቅቱ እንዲደርስ ማድረግ።
ክፍል 3. 6¿ 6¿ 9SÒÑ@bk
3.1. ማንኛውም የሥራ ኃላፊ ወይም ሠራተኛ ባለው ሥልጣን ከህግ ውጭ ለሚፈጽማቸው
የሴቶች ልዩ ድጋፍ መመሪያና መመሪያውን ወደ ጎን በመተው ለሚከናወኑ ስምሪቶች
ተግባራት ሁሉ በህግ ተጠያቂ ይሆናል።
3.2. በዚህ የሴቶች ልዩ ድጋፍ መመሪያ በተፈቀዱ የስምሪት መብቶች ተግባራዊ
የማያደርግ ተቋም ሁሉ በህግ ተጠያቂ ይሆናል።
235
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
በዚህ መመሪያ አፈፃፀም ላይ የሚነሣ ቅሬታ ቢኖር በሥራ ላይ ባለው የቅሬታ አቀራረብ ሥነ- ሥርዓት
መሠረት ተፈፃሚ ይሆናል፣
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 253/2010 አንቀጽ
96 ን/አንቀጽ 2 መሠረት ይህን መመሪያ የመለወጥ ወይም የማሻሻል ኃላፊነት የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ኮሚሽን ነው።
ሀምሌ 2002 ዓ.ም ወጥቶ ሥራ ላይ ያለው የሴቶች ልዩ ድጋፍ ዕርምጃ ዓፈፃፀም መመሪያ እና
ይህን ተከትሎ በተለያዩ ጊዜያት የወጡ ሰርኩላሮችና ማብራሪያዎች በዚህ መመሪያ ተተክተዋል።
አቶ ሙሉቀን አየሁ
የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ኮሚሽነር
236
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የሴቶች ልዩ ድጋፍ እርምጃ አፈፃፀም
ሰኔ 2013 ዓ.ም
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ባህር ዳር፣ ኢትዮጵያ
237
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
የሥራ ስንብትና ወደ ስራ መመለስ ጥያቄ ማስፈጸሚያ መመሪያ
መግቢያ
የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በአዋጅ ቁጥር 265/2011 ሲቋቋም ሊያከናውናቸው የሚገቡ
ተግባራትን መሰረት ያደረገ ተግባርና ኃላፊነት ተላብሶ እንዲንቀሳቀስ መሆኑ ይታወቃል። ስለሆነም
በአዋጅ 253/2010 በሚተዳደሩ የመንግስት መ/ቤቶችና የመንግስት ሰራተኞች ላይ ተግባራዊ ሊደረጉ
የሚችሉ የተለያዩ ማስፈፀሚያ መመሪያዎችን ማዘጋጀትና ተግባራዊ ሲደረጉ የነበሩ መመሪያዎችን
ማሻሻል ለኮሚሽኑ በተሰጠው ስልጣን በአዋጅ ቁጥር 253/2010 አንቀፅ
96 ን/አንቀፅ 2 መሰረት አዳዲስ መመሪያዎችን እያዘጋጀ ለመንግስት መ/ቤቶች በማውረድ
ተግባራዊነቱን በመከታተል በመደገፍ በርካታ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል። ስለሆነም በተግባር ላይ
ካሉት መመሪያዎች መካከል አንዱ የሥራ ስንብትና ወደ ስራ የመመለስ ጥያቄ ማስፈጸሚያ መመሪያ
ነው ። ይህም መመሪያ አንድ የመንግስት ሠራተኛ በስራ ገበታው ላይ መገኘት ሳይችል ሲቀር እንዴት
ከስራ እንደሚሰናበት እንደሁም ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ያጋጠመው ሠራተኛ ያጋጠመው ችግር
እንደተወገደ እንዴት ወደ ስራ የመመለስ ጥያቄ ማቅረብ እንደሚችል ከሰኔ 2011 ዓ.ም ጀምሮ
የስራ ስንብትና ወደ ስራ የመመለስ ጥያቄ ማስፈጸሚ መመሪያ ወጥቶ ሲሰራበት መቆየቱ
ይታወቃል። ይሁን እንጅ ለአፈፃፀም ግልፀኝነት የጎደላቸውና መስተካካል ያለባቸው ጉዳዮች ያሉ
በመሆኑና የሰራተኞችን ተጠቃሚነት ይበልጥ ያረጋገጠ መመሪያ ማውጣት በማስፈለጉ ይህ መመሪያ
ማሻሻያ ተደርጎበታል ።
የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በተሻሻለው የመንግስት ሠራተኞች አዋጅ 253/2010 አንቀጽ 96 ንዑስ
አንቀጽ 2 በተሰጠው ስልጣን መሰረት ይህን የስራ ስንብትና ወደ ስራ የመመለስ ጥያቄ ማስፈጸሚያ
መመሪያ አውጥቷል።
237
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
1.2. ትርጓሜ፣
1.2.1. “የመንግሥት ሠራተኛ” ማለት በክልሉ የመንግሥት መ/ቤት ውስጥ በቋሚነት ተቀጥሮ
የሚሰራ ሰው ነው ።
1.2.2. “ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት” ማለት በህመም፣ በእሥራት፣ ወይም በሌላ በድንገት በሚከሰት
ችግር ምክንያት በስራ ገበታ ላይ ተገኝቶ ሥራን ለማከናወን አለመቻል ነው።
1.3. ማንኛውም በወንድ ፃታ የተገለፀው የሴት ፆታንም ያካትታል።
1.4. የተፈጻሚነት ወሰን
ይህ መመሪያ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በየትኛውም የአስተዳደር ዕርከን በአዋጅ ቁጥር
253/2010 በሚተዳደር ማንኛውም የመንግስት መ/ቤት ላይ ተፈፃሚ ይሆናል።
2.1.1. አንድ የመንግስት ሠራተኛ መ/ቤቱ ባላወቀው ሁኔታ በልዩ ልዩ ምክንያቶች ከሥራ ቦታው
ከጠፋ ከጠፋበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 10 ቀናት ተጠብቆ ለአስር ተከታታይ ቀናት
የሚቆይ የመጀመሪያ ጥሪ ማስታወቂያ ይወጣል። በመጀመሪያ ጥሪ ማስታወቂያ መቅረብ
ካልቻለ ለተጨማሪ 10 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ድጋሚ የጥሪ ማስታወቂያ ይወጣል።
ሁለተኛው የጥሪ ማስታወቂያ ከመጠናቀቁ በፊት መቅረብ ካልቻለ እንዲሰናበት
ይደረጋል። ሆኖም መ/ቤቱ ባለሙያዉ/ሠራተኛው/ ከሥራ ገበታው
238
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የሥራ ስንብትና ወደ ስራ መመለስ ጥያቄ ማስፈጸሚያ መመሪያ
239
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
2.2.1. ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ከምድብ ሥራው በመለየቱ ከሥራ የተሰናበተ ሠራተኛ
ተቀባይነት ያለው ማስረጃ ቀደም ሲል ይሰራ ለነበረበት መሥሪያ ቤት በማቅረብ ወደ ስራ
የመመለስ ጥያቄ ሊያቀርብ ይችላል።
2.2.2. ወደ ስራ የመመለስ ጥያቄውን ማቅረብ ያለበት ከአቅም በላይ የሆነው ምክንያት ከተወገደበት
ቀን ጀምሮ ባሉት አስር ተከታታይ የስራ ቀኖች ውስጥ መሆን አለበት።
2.2.3. በእስራት ምክንያት ከስራ ገበታቸው ተለይተዉ ከቆዩ በኋላ በነፃ የተለቀቁ፣ በዋስ የተለቀቁ
እንዲሁም በሌላ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ከስራ ገበታቸው የተለዩ ሠራተኞች የስራ
መመለስ ጥያቄ የሚያቀርቡት ሰራተኞች የተሟላና ህጋዊ ማስረጃ ሲያቀርብ ወደ ስራ
እንዲመለስ ይደረጋል።
2.2.4. ባለሙያዉ/ሠራተኛው/ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ሥራ ላይ የተለዬ መሆኑን የሚያረጋግጥ
ህጋዊ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅበታል።
2.2.5. የቀረበው ማስረጃ ሕጋዊነትና ባለሙያዉ/ሰራተኛው/ በስራው ላይ ያልተገኘበት ሙሉ
ጊዜ የሚሸፍን መሆኑን፤ እንዲሁም ሠራተኛው ይዞት የነበረው የሥራ መደብ ወይም
ሌላ ተመሳሳይ ስራ መደብ በክፍትነት ያለ መሆኑ በሰው ሀብት አስተዳደር
ዳይሬክቶሬት/ቡድን ተረጋግጦ ወደ ስራ የሚያስመልሰው ከሆነና ውሳኔው በመስሪያ ቤቱ
ኃላፊ ወይም ተወካይ ሲፀድቅ ሰራተኛው ቀደም ሲል ሲከፈለው የነበረውን ደመወዙን
እንደያዘ ምደባ እንዲሰጠው ይደረጋል።
2.2.6. መስሪያ ቤቱ ምደባ የሚሰጥበት ክፍት የስራ መደብ ከሌለው በየደረጃው ባለ የሲቪል ሰርቪስ
መ/ቤት አማካኝነት በየደረጃው ባሉ ሌሎች ሴክተር መ/ቤቶች ባሉ ተመሳሳይ ስራ መደቦች
ላይ ምደባ እንዲያገኝ ይደረጋል።
2.2.7. ሥራቸዉን በገዛ ፈቃዳቸዉ የለቀቁ ሠራተኛች በዚህ መመሪያ አይስተናገዱም፣
2.2.8. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 2.2.7 የተገለፀው ቢኖርም በሥራ ላይ እያሉ በሌላ መ/ቤት ለቅጥር
ተወዳድረዉ በማለፋቸው ምክንያት ህጋዊ መልቀቂያ/ክሊራንስ/ ይዘው የተቀጠሩ
ሠራተኞች በተቀጣሪው ማስረጃ ምክንያት ሳይሆን በቀጣሪው መ/ቤት የአፈጻጸም ስህተት
በኢንስፔክሽን ወይም በመ/ቤቱ ጥረት ቅጥሩ የተሰረዘባቸዉ ሠራተኞች ቀድሞ ወደ
ነበሩበት መ/ቤት በተሰረዘባቸው በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ የስራ መመለስ ጥያቄያቸውን
ያቀርባሉ። መልቀቂያ የወሰዱበት መ/ቤትም ወደ ቀድሞ ስራቸው ይመልሳቸዋል። ሆኖም
ሠራተኞች ቀደም ሲል ይዘውት የነበረው የሥራ
240
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የሥራ ስንብትና ወደ ስራ መመለስ ጥያቄ ማስፈጸሚያ መመሪያ
መደብ በሠራተኛ ከተያዘና ሌላ ተመሣሣይ ክፍት የሥራ መደብ ካልተገኘ የሰው ሀብት
አስተዳደር ዳይሮክተሬት/ቡድን ወይም ተቋሙ በሁሉም መ/ቤቶች ሌላ ክፍት የሥራ
መደብ በማፈላለግ እንዲመደቡ ያደርጋል።
2.2.9. ከላይ በንዑሥ አንቀጽ 2.2.8 የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በተሳሳተ መንገድ ስምሪት የፈጸሙ
አካላት በተሻሻለው የመንግስት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 253/2010 አንቀጽ
93 ንዑስ አንቀጽ 3 መሠረት ለጥፋቱ ተጠያቂ ይሆናሉ።
2.2.10. በዚህ መመሪያ መሠረት ወደ ስራ የመመለስ ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቶ ወደ ስራው የተመለሰ
ሠራተኛ በስራ ላይ ላልተገኘበት ጊዜ የደመወዝም ሆነ ሌሎች ጥቅማጥቅሞችን
የመጠየቅ መብት የለውም።
ክፍል 3. ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
3.1. በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 253/2010 አንቀጽ 96 ን/አንቀጽ
2 መሠረት ይህን መመሪያ የመለወጥ፣ የማሻሻል ወይም በሥራ ላይ በሚውልበት ጊዜ
ማብራሪያ ወይም ትርጉም የመስጠት ኃላፊነት የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ነው።
3.2. ይህ መመሪያ ተፈፃሚነት የሚኖረው በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ሠራተኞች
አዋጅ ቁጥር 253/2010 በሚተዳደሩ መ/ቤቶችና ባለሙያዎች/ሠራተኞች/ ላይ ብቻ
ነው።
3.3. በሰኔ ወር 2011 ዓ/ም ወጥቶ በሥራ ላይ የነበረው ሥራ ስንብትና ወደ ስራ የመመለስ ጥያቄ
ማስፈጸሚያ መመሪያና ይህን አስመልክቶ የተላለፉ ሰርኩላሮች በዚህ መመሪያ ተተክተዋል።
3.4. ይህን መመሪያ በተዛባ መልኩ ወይም ያለአግባብ የሚያስፈጽም ማንኛውም አካል ወይም
የስራ ኃላፊ አግባብ ባለው ህግ ተጠያቂ ይሆናል
3.5. በዚህ መመሪያ ›A99U ላይ የሚኖር p_ታ በስራ ላይ ባለው ¾p_ታ ›k^£w ስነ
ሥርዓት æt£h †A9T˛ SIT6::
3.6. ይህ መመሪያ ከሰኔ 2013 ዓ/ም ጀምሮ የፀና ነው።
አቶ ሙሉቀን አየሁ
የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ኮሚሽነር
241
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ሰኔ 2013 ዓ.ም
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ባህር ዳር፣ ኢትዮጵያ
242
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሸሻለው የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያዎች አሰጣጥና አጠቃቀም መመሪያ
መግቢያ
ሐምሌ 2002 ዓ/ም የወጣው የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ልብስ እና የሥራ መሣሪያዎች አጠቃቀም
መመሪያ አገልግሎት እየሰጠ ቢሆንም፣
በሥራ ላይ ያለው መመሪያ በየጊዜው ከተደረጉ የአደረጃጀት ለውጥ ጋር ተያይዞ እንደ አዲስ
የተፈጠሩና አደረጃጀታቸውን የከለሱ ተቋማት በመኖራቸው በዚህ ሂደት አንዳንድ የሥራ
መደቦች በመታጠፋቸው በመጣመራቸውና የመጠሪያ ለውጥ በማድረጋቸው የተደረገውን
ለውጥ ተከትሎ ማሻሻያ ማድረግ በማስፈለጉ
በአዲስ በተካተቱ የሥራ መደቦች የተፈቀዱ የሥራ ልብሶችና መሣሪያዎች እንዲሻሻሉና
እንዲጨመሩ ከመ/ቤቶች ተደጋጋሚ ጥያቄዎች በመቅረባቸው ፣ ከቴክኖሎጅ ዕድገትና
ከወቅቱ የገበያ ሁኔታ ጋር ተቀራራቢ የሆነ የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያ ዋጋን ማሻሻል
በማስፈለጉ፣
የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያዎች ግዥ፣አጠቃቀምና አወሳሰን ሥርዓትን በባለቤትነት
የሚከታተለውን አካል ተግባር በውል ለይቶ ማስቀመጥ በማስፈለጉ፣
በመመሪያው ውስጥ ያሉ ሌሎች ችግሮችን በማረምና ወቅታዊ የሆኑ ጉዳዮችን በማካተት
መመሪያውን ማውጣት በማስፈለጉ የክልሉ ሲቪል ሰርቪስ ከሚሽን በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ
መንግሥት የመንግሥት ሠራተኞች አዋጅ 253/2010 አንቀጽ 96 ንዑስ አንቀጽ
2 መመሪያ የማውጣት ሥልጣን መሰረት ይህ የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ልብስና የሥራ
መሣሪያ አሰጣጥና አጠቃቀም መመሪያ እንዲወጣ ተደርጓል ።
ክፍል 1. ጠቅላላ
1.1. አጭር ርዕስ
1.2. ትርጓሜ
243
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
1.2.1. "የመንግሥት መ/ቤት" ማለት በየትኛውም የአስተዳደር እርከን እራሱን ችሎ በአዋጅ ወይም
በደንብ የተቋቋመ እና ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ከመንግስት በሚመደብለት በጀት
የሚተዳደር የመንግስት መስሪያ ቤት ነው።
1.2.2. "ኮሚሽን" ማለት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ነው።
1.2.3. "የሥራ ልብስ" ማለት አንድ የመንግሥት ሠራተኛ ሥራውን በሚያከናውንበት ጊዜ
እንደየሥራው ፀባይ ለሠራተኛው ደህንነት ወይም ንጽህናውን ለመጠበቅና ለመለያነት
እንዲያገለግለው የሚሰጠው ልብስና ጫማ ነው።
1.2.4. "የሥራ መሣሪያ" ማለት ሠራተኛው ሥራውን በጋራ ወይም በግል ለማከናወን
እንዲጠቀምበት የሚሰጥና ሥራውን ሲጨርስ በሥራ ቦታው የሚቀመጥ ልዩ ልዩ የሥራ
መሣሪያ ወይም እቃ ማለት ሆኖ መነጽር ፣ጠመንጃ ፣ማጭድ፣ የአይን መሸፈኛ ጎግል፣
የአፍ መሸፈኛ ፊልተር፣ አካፋ፣ መዶሻ፣ መርቴሎ፣ የአትክልት መቀስ የመሳሰሉትን
የሚያጠቃልል ሲሆን ከእነዚህ ውጭ ያሉትን እንደየተቋሙ ባህሪ እያንዳንዱ መ/ቤት
በራሱ እየወሰነ የሚሰጠው ነው።
1.2.5. “ብትን የልብስ ጨርቅ" ማለት የሱፍ ምርት ያልሆነና የቀለሙ ልዩነት ሣይወሰን ከጥጥ
ወይም የጥጥና የሲንተቲክ ድብልቅ ወይም ከሌላ ተመሣሣይ ከሆነ ጥሬ እቃ የተሠራ
ተመሣሣይ ደረጃ ያለው ያልተሰፋ ጨርቅ ነው።
1.2.6. “አንድ ወጥ ሸሚዝና ሱሪ” ማለት ከጥጥ ወይም የጥጥና የሲንተቲክ ድብልቅ ወይም ከሌላ
ተመሣሣይ ከሆነ ጥሬ እቃ ከተሰራ አንድ ዓይነት ቀለም ካለው ጨርቅ የተሰፋ ሆኖ ያለ
ኮት ሊለበስ የሚችል ሸሚዝና ሱሪ ነው።
1.2.7. “ሸሚዝ” ማለት ቀለሙ እንደተፈለገው ሆኖ ከጥጥ ወይም የጥጥና የሲንተቲክ ድብልቅ ወይም
ከሌላ ተመሣሣይ ከሆነ ጥሬ እቃ ከተሰራ የሴንቴትኩ መጠን ዝቅ ካለና የጥጡ መጠን ከፍ
ካለ ለሸሚዝ እንዲሆን ከተመረተ ጨርቅ ተሠፍቶ የተዘጋጀ ነው።
1.2.8. “ቀሚስ” ማለት ቀለሙ እንደተፈለገው ሆኖ ከብትን የልብስ ጨርቅ የሚዘጋጅ ሆኖ ሙሉ
በሙሉ ከጥጥ ወይም የጥጥና የሲንተቲክ ድብልቅ ወይም ከሌላ ተመሣሣይ ከሆነ
ተመሣሣይ ጥሬ እቃ ተሰርቶ የተሠፋ ነው።
1.2.9. "ጋዋን ወይም ሙሉ የሥራ ካፖርት ወይም 3/4 ኛ ካፖርት" ማለት ቀለሙ እንደተፈለገው
ሆኖ ከብትን ልብስ ጨርቅ የሚሰፋ ገበር የሌለው ጋዋን ወይም ሙሉ የሥራ ካፖርት
ወይም 3/4 ኛ ካፖርት ነው።
244
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሸሻለው የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያዎች አሰጣጥና አጠቃቀም መመሪያ
1.2.10. "ካፖርት" ማለት ከሱፍ የተሰራ ወይም ሙቀት እንዲሰጥ ገበር ያለው ሆኖ ከጥጥ
ወይም ከሲንተቲክ የተሰራ የብርድ መከላከያ ልብስ ነው።
1.2.11. "የዝናብ ልብስ" ማለት በጥጥ ገበር ወይም ያለገበር ከሲንተቲክ ወይም ከፕላስቲክ
የተሰራ የዝናብ መከላከያ ልብስ ነው።
1.2.12. "ጃንጥላ" ማለት ለዝናብ ወይም ለፀሐይ መከላከያ የሚያገለግል ነው።
1.2.13. "ካባ" ማለት በችሎት ወቅት ዳኞች የሚለብሱት ከበትን ልብስ ጨርቅ የተሰፋ ጥቁር
ልብስ ነው።
1.2.14. "ሽርጥ" ማለት እንደ የሥራ ባህሪው ብትን ልብስ ጨርቅ ወይም ከሌላ ተስማሚ ጥሬ
እቃ የተሰራ ሆኖ የልብስን መቆሸሽ ለመከላከል የሚለበስ የሥራ ልብስ ነው።
1.2.15. "ቱታ" ማለት ከብትን የልብስ ጨርቅ ወይም ከሌላ ጥሬ እቃ የተሠራና ሱሪው ከጃኬት
መሰል ልብስ ጋር ተያይዞ የተሰፋ ሆኖ የልብስን መቆሸሽ ለመከላከል በልብስ ላይ ተደርቦ
የሚለበስ የሥራ ልብስ ነው።
1.2.16. "አጭር ቆዳ ጫማ" ማለት ማሠሪያ ያለው ወይም የሌለው ሆኖ ለሲቪል ሥራ
አገልግሎት የሚውልና ቁመቱ ከቁርጭምጭሚት የማያልፍ ከቆዳ የተሠራ ጫማ ነው።
1.2.17. "አጭር ቡትስ ቆዳ ጫማ" ማለት ማሠሪያ የሌለው ሆኖ ለሲቪል ሥራ አገልግሎት የሚውልና
ቁመቱ ከቁርጭምጭሚት የሚያልፍ ከቆዳ የተሠራ ጫማ ነው።
1.2.18. "የላስቲክ ቡት ጫማ" ማለት ከተፈጥሮ ጐማ የተሠራ ገበር ያለው ሆኖ በክረምትና ጭቃ
በሚበዛበት ወቅት የሚደረግና በቀላሉ የሚፀዳ ጫማ ነው።
1.2.19. "ፊልድ ጃኬት" ማለት ከጥጥ ወይም ከሌላ ተመሣሣይ ጨርቅ የተሠራ ሆኖ ሙቀት የሚሰጥ
ገበር ያለው ልብስ ነው።
2.1.1. ለየሥራ መደቦች የተፈቀደው የሥራ ልብስ ዓይነትና መጠን የሚሰጠው በሥራ መደቡ ላይ
ተመድበው በመሥራት ላይ ለሚገኙ ቋሚና የሙከራ ቅጥር እንዲሁም ጊዜያዊ/ ኮንትራት
ቅጥር ሠራተኞች ነው። ሆኖም የሥራ ልብስ በተፈቀደበት የሥራ መደብ
245
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
246
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሸሻለው የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያዎች አሰጣጥና አጠቃቀም መመሪያ
3 ወርና በላይ ካገለገለ ግማሹን ያገኛል። ሆኖም በዓመት አንድ ጊዜ የሥራ ልብስ የሚያስገኝ
ከሆነ 6 ወርና ከዚያ በላይ ማገልገል ይጠበቅበታል።
2.1.8. ሴት የስራ ልብስ ተጠቃሚዎች የስፌት ዓይነትን የመምረጥ መብት ያላቸው ሲሆን አንድ
ወጥ ሸሚዝና ሱሪ ወይም ጃኬትና ጉርድ አሰፍተው ሊለብሱ ይችላሉ። ለምሣሌ ሸሚዝና
ሱሪ የነበረን ወደ ቀሚስ ወይም ወደ ጉርድና ሸሚዝ መቀየር ቢፈልግ የሥራ ልብሱ
መጠንና ዋጋ ልዩነት እስከሌለው ድረስ ሊፈቀድለት ይችላል።
2.1.9. በሞቃታማና በውርጭ አካባቢዎች የተመደቡና የሥራ ልብስ በተፈቀደባቸው የሥራ መደቦች
ላይ ተመድበው በመሥራት ላይ ለሚገኙ ሠራተኞች በመመሪያው ላይ ለተፈቀዱት
የጨርቅና የጫማ ዓይነቶች ለአካባቢው የአየር ጠባይ ተስማሚ የስራ ልብስ መስጠት
ይቻላል። ሆኖም ዋጋው ተመጣጣኝ ስለመሆኑና ለስራው ያለው አስፈላጊነት በየደረጃው
በሚገኝ የሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ቡድን ተጠንቶ በዞን ለዞን ገንዘብና ኢኮኖሚ
ትብብር መምሪያና በወረዳ ለወረዳ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ጽ/ቤት ኃላፊ ቀርቦ
ሲጸድቅ ይሆናል።
2.1.10. በሥራ ልብስ ግዥ አፈጻጸምና በስራ ልብስ ጥራት ጉዳዮች ዙሪያ የሚታየውን ችግር ለመቅረፍ
እንዲቻል ግዥ ከመፈፀሙ በፊት ከግዥ ፋይናንስና ንብረት አሥተዳደር
ዳይሬክቶሬት/ቡድን እንዲሁም ከሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ቡድን አንድ ባለሙያ
ከተጠቃሚ ሠራተኞች ቢያንስ አንድ ተወካይ ተመርጦ በልብስ ዓይነትና ጥራት መረጣና
የማማከር ተግባር ላይ ይሳተፋሉ።
2.1.11. በንዑስ አንቀጽ 2.1.11 የተገለፀው ኮሚቴ የጨርቅ ናሙና ከመረጠ በኋላ ብትን የልብስ
ጨርቁ በግዥ መመሪያ መሠረት ግዥው ይፈጸማል።
2.1.12. አንድ ሰራተኛ በህመም ምክንያት በበጀት ዓመቱ ለተወሰኑ ወራት ስራውን ባይሰራ
የተመደበበት የስራ መደብ በአመት አንድ የሥራ ልብስ የሚያስገኝ ከሆነ 6 ወር በታች
በህመም ላይ ከቆየ የስራ ልብሱን ያገኛል። ከስድስት ወር በላይ ከቆየ ግን ለስራ መደቡ
የተፈቀደው የሥራ ልብስ አይሰጠውም።የሥራ መደብ በዓመት ሁለት የሥራ ልብስ
የሚያስገኝ ከሆነ 3 ወርና በላይ ካገለገለ ግማሹን ያገኛል።
2.1.13. አንድ ሰራተኛ ማግኘት እየተገባው በተለያየ ምክንያት ሳይሰጠው ከዚህ ዓለም በሞት ቢለይ
ሕይወቱ ያለፈበትን ዓመትና ሌላ ያልወሰደው የሥራ ልብስ ካለ ወደ ገንዘብ ተቀይሮ ለህጋዊ
ወራሾቹ ይሰጣል። በተመሳሳይ በጡረታ የተለየ ሠራተኛም ወደ ገንዘብ ተቀይሮ
ይሰጠዋል።
247
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
2.2.1. የሥራ ልብሱን ስፌት በተመለከተ ለወንድ ለአንድ ኮትና ሱሪ ከብር 500 ያልበለጠ
፣ ለሴት ጃኬትና ጉርድ ከብር 150 ያልበለጠ፣ ለሴት አንድ ወጥ ሸሚዝና ሱሪ ከብር
350 ያልበለጠ እንዲሁም ለ ¾ ኛ ካፖርትና ገዋን እና ቱታ ከብር 100 ያልበለጠ
የማሰፊያ ዋጋ ለእያንዳንዱ ተጠቃሚ በጥሬ ገንዘብ የሚሰጥ ሆኖ የተሰጠውን ብትን ጨርቅ
በተሰጠው ገንዘብ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ አሰፍቶ በስራ ገበታው ላይ ለብሶ መገኘት
አለበት።የማሰፊያው ዋጋው ወቅታዊ የገቢያ ሁኔታ እየታየእንደአስፈላጊነቱ ሊሻሻል
ይችላል።
2.2.2. ለአንድ ወጥ ሸሚዝና ሱሪ፣ ለጃኬትና ጉርድ ቀሚስ፣ ለኮትና ሱሪ፣ የሚሰጠው ሱፍ
ያልሆነ ከጥጥ ወይም የጥጥና የሲንተቲክ ድብልቅ ወይም ከሌላ ተመሣሣይ ከሆነ ጥሬ
እቃ የተሠራ ብትን የልብስ ጨርቅ ጥራቱን የጠበቀና የዋጋ መጠኑ በሜትር ከብር 300
ያልበለጠ ይሆናል። ለቱታ፣ ለጋዋንና ለሽርጥ፣ ለሙሉ ካፖርት፣ ለ 3/4 ካፖርት፣
የሚሰጠው ሱፍ ያልሆነ ብትን የልብስ ጨርቅ ጥራቱን የጠበቀና የዋጋ መጠኑ በሜትር
ከብር 150.00 ያልበለጠ ይሆናል።
2.2.3. ከረባት እንዲሰጣቸው ለተፈቀደላቸው ሠራተኞች ጥራቱን የጠበቀና ዋጋው ተመጣጣኝ የሆነ
ከብር 200.00 ያልበለጠ ተገዝቶ የሚሰጥ ይሆናል።
2.2.4. ለካፖርት የሚሰጠው የጨርቅ ዓይነት ሙቀት የሚሰጥና ገበር ያለው ሆኖ የጥጥ ወይም
የሲንተቲክ ወይም ከጥጥና ከሲንተቲክ ጥሬ እቃ የተሰራ ይሆናል። ይህ የማይገኝ ከሆነ
በምትኩ ሙቀት የሚሰጥና ገበር ያለው ፊልድ ጃኬት ከመንግስት ወይም ከግል ድርጅቶች
በማወዳደርና በወቅቱ ያለውን የካፖርት ዋጋ ከግምት ውስጥ በማስገባት ገዝቶ መስጠት
ይቻላል።
2.2.5. የሚሰጠው የዝናብ ልብስ ከጥጥና ከሴንተቲክ የተሰራ የዝናብ ልብስ ነው። የዝናብ ልብሱ
የማይገኝ ከሆነ በምትኩ ጃንጥላ ይሰጣል።
2.2.6. ለካባና ለፈረጅያ የሚሰጠው ብትን የልብስ ጨርቅ ሱፍ ያልሆነ ማንኛውም የጥራት ደረጃ
ያለው ጥቁር ጨርቅ ነው።
248
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሸሻለው የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያዎች አሰጣጥና አጠቃቀም መመሪያ
249
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
3.1. ተጠሪነታቸው ለዳይሬክቶሬት/ ቡድን ለሆኑ የሥራ መደቦች ዳይሬክተሩ/ ቡድን መሪው የሥራ
ልብሱ አስፈላጊ ስለመሆኑ ከበቂ ማብራሪያ ጋር ለሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/
ቡድን ያቀርባል።
3.2. ተጠሪነታቸው ለሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ ቡድን ላልሆኑ የሥራ መደቦች የመ/ቤቱ
ኃላፊ የሥራ ልብሱ አስፈላጊ ስለመሆኑ ከበቂ ማብራሪያ ጋር ለሰው ሃብት አስተዳደር
ዳይሬክቶሬት/ቡድን ያቀርባል።
3.3. የሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ቡድን የቀረበውን አዲስ ወይም የማሻሻያ ጥያቄ
በመመርመር አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ተጨማሪ መረጃዎችን በማሰባሰብ ተገቢው ውሣኔ
እንዲሰጥበት የውሳኔ ሃሳቡን የክልል በቀጥታ ፣ዞኖች፣ ወረዳዎችና ማዕከላት በእናት መስሪያ
ቤታቸው በኩል ለሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን እንዲደርስ ያደርጋሉ። የክልሉ ሲቪል ሰርቪስ
ኮሚሽንም በየተቋሙ ተቀባይነት አግኝቶ የቀረበውን ጥያቄ በመመርመር አስፈላጊውን
ውሣኔ ይሰጣል።
3.4. በመመሪያው ላይ ሊካተትላቸው ሲገባ ያልተካተተላቸው የስራ መደቦች፤በነጥብ የስራ ምዘና
ዘዴ በተሰጠው መጠሪያ ያልተካተተላቸው ወይም በበፊቱ የስራ መደብ መጠሪያ
የተካተተላቸው የስራ መደቦች ያሉ በመሆኑ፤ ከተቋማት በአዲስ እንዲፈቀድ የተጠየቁ የስራ
መደቦች ወደፊት ምላሽ የሚያገኙ ይሆናል ።
3.5. አንዳንድ የስራ መደቦች በተደጋጋሚ የተለያዬ የስራ ልብስና የስራ መሳሪያ የተፈቀደ እና
ከመመሪያው ከመውጣቱ በፊት ከተፈቀደው የስራ ልብስና የስራ መሳሪያ ዓይነትና መጠን
የተቀነሰባቸው እንዳለ የተገነዘብን በመሆኑ ማስተካከያ መስጠት በማስፈለጉ ወደፊት
ማስተካከያ እስከሚደረግ ድረስ ከተሻሻለው መመሪያ በፊት በነበረው መመሪያ ተፈፃሚ
እንዲሆን ።
3.6. በዚህ መመሪያ ያልተገለፀ የስራ ልብስና የስራ መሳሪያ የመግዥያ እና የማሰፊያ የዋጋ
ተመን መጠን እና በመመሪያ የተገለፀው የመግዥያ እና የማሰፊያ የዋጋ ተመን መጠን
ከወቅታዊ የገበያ ሁኔታ ጋር የማይጣጣም ሆኖ ሲገኝ በጨረታ በማውጣ አሸናፊ
የሆነውን የዋጋ ተመን እንዲተገበር ይደረጋል።
250
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሸሻለው የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያዎች አሰጣጥና አጠቃቀም መመሪያ
ክፍል 4. ልዩ ልዩ ጉዳዮች
4.1. አፈፃፀሙን የመከታተልና የመቆጣጠር ተግባር
251
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
4.2.1. በክልል መ/ቤቶችና ተቋማት የሚገኙ የሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ቡድን በዓመቱ
መጨረሻ ላይ የሥራ ልብስ የተሰጣቸውን ሠራተኞች ቁጥር በየሥራ መደቡ በመለየትና
የተሰጠውን የልብስና የስራ መሳሪያ ዓይነትና ብዛት የሚገልጽ መረጃ አዘጋጅተው ይይዛሉ።
ከሚመለከተው አካል ሲጠየቁም መረጃውን ያቀርባሉ።
4.2.2. በዞንና በወረዳ ደረጃ የሚገኙ የሰው ሃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ ቡድን በፑልና በሴክተር
መ/ቤቶች በመለየት በዓመቱ መጨረሻ ላይ የሥራ ልብስ የተሰጣቸውን ሠራተኞች
በቁጥር፣ በፆታና በየሥራ መደቡ በመለየትና የተሰጣቸውን የልብስና የሥራ መሳሪያ
ዓይነትና ብዛት የሚገልጽ መረጃ አዘጋጅተው ይይዛሉ። ከሚመለከተው አካል ሲጠየቁም
መረጃውን ያቀርባሉ።
በዚህ መመሪያ ከተፈቀደላቸው በስተቀር የሥራ ልብስን በገንዘብ ቀይሮ መሥጠት አይፈቀድም። ይህን
ድርጊት የፈጸመ ኃላፊ ወይም ባለሙያ አግባብ ባለው ህግ ይጠየቃል።
ይህ መመሪያ ተፈፃሚነት የሚኖረው በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ በሚተዳደሩ
መ/ቤቶች ተቀጥረው የሚሰሩ ቋሚ ሠራተኞች እና በእነዚህ ተቋማት ላይ የሚቀጠሩ ጊዜያዊ/ኮንትራት
ሠራተኞን ይጨምራል ።
252
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሸሻለው የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያዎች አሰጣጥና አጠቃቀም መመሪያ
ሐምሌ 2002 ዓ/ም ወጥቶ በሥራ ላይ የነበረው የሥራ ልብስ እና የሥራ መሣሪያዎች አጠቃቀም
መመሪያና ይህን አስመልክቶ የተላለፉ ሠርኩላሮች በዚህ መመሪያ ተተክቷል።
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ 253/2010 አንቀጽ 96 ን/አንቀፅ 2 መሠረት
ይህን መመሪያ የመለወጥ፣ የማሻሻል ወይም በሥራ ላይ በሚውልበት ጊዜ ማብራሪያ ወይም ትርጉም
የመስጠት ኃላፊነት የኮሚሽኑ ነው።
253
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
አባሪ 8 የተፈቀደ የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያ ዓይነትና መጠን የሚያሳይ ሠንጠረዥ
ተቁ የሥራ መደቡ መጠሪያ የሚሰጠው የሥራ ብዛት
ልብስ ዓይነት
1 ኮትና ሱሪ በዓመት ሁለት
የጥበቃ ሰራተኛ ወንድ ሸሚዝ በዓመት ሁለት
አጭር የቆዳ ጫማ በዓመት ሁለት
ጥንድ
ካፖርት በመጀመሪያ አንድ
ተሰጥቶ በየ3
ዓመቱ አንድ
የዝናብ ልብስ በመጀመሪያ አንድ
ተሰጥቶ በየ3
ዓመቱ አንድ
2 የጥበቃ ሰራተኛ ሴት ጃኬትና ጉርድ በዓመት አንድ
ቀሚስ
አንድ ወጥ ሸሚዝና በዓመት አንድ
ሱሪ
ሸሚዝ በዓመት ሁለት
የቆዳ ጫማ አጭር በዓመት ሁለት
ጥንድ
ካፖርት በመጀመሪያ አንድ
ተሰጥቶ በ3
ዓመት አንድ
የዝናብ ልብስ በመጀመሪያ አንድ
ተሰጥቶ በየ3
ዓመቱ አንድ
3 ኮትና ሱሪ በዓመት ሁለት
የእንስሳት እርድ ሰራተኛ /ወንድ/ አጭር የቆዳ ጫማ በዓመት ሁለት
ሥነ ሥርዓት አስከባሪ/ወንድ/ ጥንድ
ሸሚዝ በዓመት ሁለት
4 ጃኬትና ጉርድ በዓመት አንድ
ሥነ ሥርዓት አስከባሪ/ሴት/ ቀሚስ
የእንስሳት እርድ ቁጥጥር ባለሙያ/ሴት/ አንድ ወጥ ሸሚዝና በዓመት አንድ
ሱሪ ወይም ቀሚስ
ሸሚዝ በዓመት ሁለት
አጭር የቆዳ ጫማ በዓመት ሁለት
ጥንድ
5 ጥበቃና አትክልተኛ ወንድ ኮትና ሱሪ በዓመት ሁለት
ቱታ በዓመት አንድ
ሸሚዝ በዓመት ሁለት
አጭር የቆዳ ጫማ በዓመት ሁለት
ጥንድ
የላስቲክ ቡት ጫማ በዓመት አንድ
ጥንድ
254
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሸሻለው የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያዎች አሰጣጥና አጠቃቀም መመሪያ
255
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
256
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሸሻለው የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያዎች አሰጣጥና አጠቃቀም መመሪያ
257
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
258
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሸሻለው የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያዎች አሰጣጥና አጠቃቀም መመሪያ
259
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
260
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሸሻለው የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያዎች አሰጣጥና አጠቃቀም መመሪያ
261
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
262
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሸሻለው የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያዎች አሰጣጥና አጠቃቀም መመሪያ
263
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
264
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሸሻለው የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያዎች አሰጣጥና አጠቃቀም መመሪያ
265
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
266
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሸሻለው የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያዎች አሰጣጥና አጠቃቀም መመሪያ
267
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
268
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሸሻለው የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያዎች አሰጣጥና አጠቃቀም መመሪያ
269
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
270
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሸሻለው የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያዎች አሰጣጥና አጠቃቀም መመሪያ
271
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
272
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሸሻለው የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያዎች አሰጣጥና አጠቃቀም መመሪያ
273
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
274
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!
የተሸሻለው የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ልብስና የሥራ መሣሪያዎች አሰጣጥና አጠቃቀም መመሪያ
275
በአገልግሎታችን፡- ተደራሽ መሆን፣ በትህትና ማስተናገድ፣ ፈጣንና ፍትኃዊ ምላሽ መስጠት!
አብክመ ሲቪል ሰርቪስ
ማስታወሻ
የህትመት ወጭው በኢፌዲሪ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በኩል ከእንግሊዝ ተራድዖ ድርጅት (UK-Aid) እና የተባበሩት መንግሥታት በተገኘ
276
ማገልገል ክብር ነው። በቅንነት ማገልገል ደግሞ ድርብ ክብር ነው!