Professional Documents
Culture Documents
አማካሪ
ድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ
የኅብረተሰብ ሣይንስና ቋንቋዎች ኮሌጅ
የኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነፅሁፍ - አማርኛ ትምህርት ክፍል
የድህረ ምረቃ
ታህሳስ 2015
ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ
ማውጫ
ይዘት ገጽ
ምስጋና……………………………………………………………………………
አጠቃሎ………………………………………………………………………………………ii
ምዕራፍ አንድ:መግቢያ
1.1.የጥናቱ ዳራ………………………………………………………………………………..
1.2 .የጥናቱ አነሳሽ ችግር…………………………….……………………………….
1.3.የጥናቱ መሰረታዊ ጥያቄዎች
1.4. የጥናቱ ዓላማ…………………………………………………………………………..
1.5.የጥናቱ አስፈላጊነት…………………………………………………………………
1.6.የጥናቱ ወሰን…………………………………………………………………………
ምዕራፍ ሁለት፡- ክለሳ ድርሳ
2.1. ፍላጎት ምንድ ነው?.............................................................................................
2.2. የፍላጎት ጠቀሜታ………………………………………………………………………
2.3. ፍላጎትና የሁለተኛ ቋንቋ ትምህርት……………………………………
2.4.ፍላጎት በትምህርት ውስጥ ያለው ሚና………………………………………………….
2.5.ፍላጎትን ማጥናት ለምን አስፈለገ ?...........................................................................
2.6. የሁለተኛ ቋንቋ ትምህርት ላይ ተጽዕኖ የሚሳድሩ ተላውጦዎች……………
2.6.1. ተማሪው ለሁለተኛ ቋንቋ ትምህርት ባለው አመለካከት ሳቢያ የሚከሰት
ተፅዕኖ…………………………………………………………………………………
2.6.2 ተማሪው ለሁለተኛ ቋንቋ ትምህርት ባለው ተነሳሽነት ምክንያት የሚከሰት
ተጽዕኖ……………………………………………………………………………….
2.6.3. በስነ ልቦና ችግር ምክንያት የሚከሰት ተጽዕኖ………………………………
2.6.4. በቤተሰብ በኩል የሚመጣ ተጽዕኖ…………………………………………….....
2.6.5. በተማሪው ጓደኞች በኩል የሚከሰት ተጽእኖ
2.6.6.ተማሪው ከሚኖርበት ህብረተሰብ በኩል የሚመጣ ተጽዕኖ
2.6.7. በቋንቋ መምህራን ስብእና እና በማስተማሪያ ዘዴ ምክንያት የሚከሰት
ተጽዕኖ
2.6.8. በመማሪያ መጽሀፉ ምክንያት የሚከሰት ተጽዕኖ
2.7. በፍላጎትና በተማሪው ውጤት ጋር ያለው ዝምድና
2.8.የቀደምት ስራዎች ቅኝት………………………………………………………
1
ምዕራፍ ሦስት………………………………………………………………………….
የአጠናን ዘዴ………………………………………………………………………….
3.1 የጥናቱ ንድፍ………………………………………………………………………
3.2. የናሙና አመራረጥ ዘዴ……………………………………………………………
3.2.1.የመስተዳድር አመራረጥ……………………………………………………………
3.2.3.የትምህርት ቤት አመራረጥ
3.2.4.የክፍልና የምድብ አመራረጥ
3.2.5.የተማሪዎች አመራረጥ………………………………………………………………
3.2.6.የመምህራን አመራረጥ……………………………………………………………
3.3. የመረጃ መሰብሰቢ መሳሪዎች…………………………………………………………
3.3.1. የጽሁፍ መጠይቅ
3.3.2. ቃለ መጠይቅ
3.3.3. ሰነድ ፍተሻ……………………………………………………………………………
3.4. የመረጃ አተናተን ዘዴ………………………………………………………
ዋቢ መፅሀፍት
ግምታዊ የጊዜ ሰሌዳ
ግምታዊ የበጀት ሰሌዳ
ምዕራፍ አንድ
መግቢያ
1.1 የጥናቱ ዳራ
ቋንቋ የሰው ልጅ ዋነኛ መግባቢያ ነው፡፡ በቋንቋ ላይ የሚደረጉ ጥናቶችና ምርምሮች የተሻለ የቋንቋ
አጠቃቀም ሁኔታዎችን በማመቻቸት ረገድ ጠቀሜታቸው የጎላ ነው፡ በጥናት ላይ የተደገፈ አሰራር
2
እንዲሁም የመማር ማስተማር ተግባር ደግሞ የተሳሳተውን አካሄድ ለማቃናት፣ መልካም ጎኑን ይበልጥ
ለማጠናከር እንዲቻል ይረዳል፡፡ስለዚህ የቋንቋ ትምህረት ለአፍ-ፈትም ሆነ ለኢ-አፍ-ፈት ተማሪዎች
ሲቀርብ በጥናት የተደገፈ መረጃን መሰረት ያደረገ መሆን አለበት፡፡ይህን ተግባር ለማከናወንም የተማሪዎቹን
ፍላጎት፣ ባህላዊ ዳራን ፣የተነሳሽነት ሁኔታ፣ አካባቢያዊ ተጽዕኖን፣አመለካከትን፣ የእውቀት ደረጃን ማወቁ
ወሳኝ እንደሆነ Harmer(1991) እና Brown (2007) አስረድተዋል ፡፡
ከላይ ከተዘረዘሩ ተላውጦዎች ውስጥ ፍላጎት በቋንቋ ትምህርትም ሆነ በሌላ ትምህርት ዙሪያ አብይና
መሰረታዊ ጉዳይ ነው፡፡የፍላጎት መኖር ያለመኖር ለአንድ ተግባር ስኬታማ መሆን ያለመሆን ወሳኝ ጉዳይ ነው፡፡
ስለዚህ ለትምህርቱ አወንታዊ ፍላጎት ያለውቸው ተማሪዎች በክፍል ውስጥ እርስ በእርሳቸው ጥያቄ
ይጠያየቃሉ፣ መልስ ሲመልሱ፣ ከመምህራቸው ጋር በመወያየት ተገቢ የሆነ ግብረ መልስ ወዘተ…ሲያገኙ፣
በአንፃሩ ደግሞ ለትምህርቱ አሉታዊ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች ጥያቄ ሲጠይቁም ሆነ መልስ ሲመልሱ
ወዘተ… አይታዩም በማለት ማስረሻ (2003) ያስረዳሉ፡፡
ከላይ ከቀረበው ሃሳብ በተጨማሪም ፍላጎት በተለይም ኢ-አፍ-ፈት ለሆኑ ተማሪዎች በትምህርቱ ሂደት ላይ
ተፅዕኖ ከሚያሳድሩ በርካታ ተላውጣዎች መካከል አንዱ በቋንቋውና በትምህርቱ ያለው ፍላጎት ነው፡፡
ተማሪው ከክፍል ውጪም ሆነ ከክፍል ውስጥ የሚገጥሙት ችግሮች ከፍላጎት ጋር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ
ግንኙነት አላቸው፡፡ለትምህርቱ ቀረበ ቋንቋና የትምህርት ስርአቱ፣ የማስተማሪያ መሳሪያዎች፣ የመምህሩ
የሚጠቀምባቸው ዘዴዎች፣ የተማሪዎች ባልንጀራ፣ ወላጆችና ማህበረሰቡ፣ ተማሪው ለትምህርቱ
አወነወታዊ ወይም አሉታዊ ፍላጎትእንዲኖራቸው ከሚያስችሉ ጉዳዮች ውስጥ በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው
(ስሚዝ 1971፣ 82፤ሀርመር 1990፣4)፡፡
ይህ ማለት ተማሪው ከላይ በተጠቀሱት ጉዳዮች ላይ አወንታዊ ፍላጎት ካለውና ውስጣዊ ተነሳሽነት ካለው
በፍላጎቱና በውጤቱ መካከል የጠበቀ ግንኙነት ይኖረዋል፡፡ በአንፃሩ አሉታዊ ፍላጎት ካለውና ውስጣዊ ተነሳሽነት
ከሌለው በፍላጎቱና በውጤቱ መካከል የጠበቀ ግንኙነት እንደማይኖረው በብዙ ምሁራን ጥናቶች ተረጋግጧል
(ታደለ 1990፣139)፡፡
ስለዚህ በተማሪዎች ተተኳሪው ትመህርት ፍላጎት ላይ ተፅዕኖ ሊያሳድሩ የሚችሉ ተላውጣዎችን ፈትሾ
በማየት በተማሪዎች ዘንድ የሚፈጠረውን የአወንታዊ ፍላጎት ገፅታን ማጎልበትና በአንፃሩ ደግሞ አሉታዊ
ገፅታን በመቀየር የሚቻለው በጥናት መረጋገጥ ሲቻል ነው፡፡
እንግዲህ ከላይ በዝርዝር የተጠቀሰውን ሳይንሳዊ ዳራን መሰረት በማድረግ አጥኚዋ በድሬዳዋ ከተማ
መስተዳድር ውስጥ ትኩረት ሰጥታ ወደምታጠናው በናሙናነት በሚመረጡ ሁለት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት
3
ቤቶች በ 2015 ዓ.ም የሚማሩ የ 9 ኛ ክፍል የኦሮሚኛ ቋንቋ አፍ-ፈት ተማሪዎች አማርኛ ቋንቋን
በማስተማር ሂደት ላይ ያላቸውን ፍላጎትና የፈተና ውጤታቸው ዝምድና የምታጠና ይሆናል፡፡
አማርኛ ቋንቋን እንደ ሁለተኛ ቋንቋ በሚማሩ በኦሮምኛ አፍ-ፈት ተማሪዎች ላይ የተለያዩ ጥናቶች
ተደርገዋል፡፡አበበ (1990) አፋቸውን በኦሮምኛ ቋንቋ የፈቱ ተማሪዎች በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ላይ
ያላቸው አመለካከት በአዋሽ መላካሳ አጠቃለይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በሚል ርዕስ ባቀረበው ጥናታዊ
ፅሁፉ፣ እንዳመለከተው በጥናቱ ውስጥ ከታቀፉት ሦስት አራተኛው እጅ አማርኛ ቋንቋን ለመማር ፍላጎት
እንደሌላቸው አረጋግጧል፡፡በተጨማሪም አሰፋ (1994) ሀዋስ ከፍተኛ 2 ኛደረጃ ት/ቤት አፋቸውን በኦሮምኛ
ቋንቋ የፈቱ የ 9 ኛ ክፍል ተማሪዎች ለአማርኛ ቋንቋ ያላቸው አተያይ በሚል ርዕስ ባቀረበው ጥናታዊ ጽሁፉ፣
በጥናቱ ውስጥ ከታቀፉት 52ተጠኚ ተማሪዎች አማርኛን መማር ምንም ጥቅም እንደማያስገኝላቸው
አስረድቷል፡፡
ከላይ ከቀረቡት ጥናቶች መገንዘብ የሚቻለው አማርኛ ቋንቋ ትምህርትን እንደ ሁለተኛ ቋንቋ የሚማሩ
አፋቸውን በኦሮምኛ የፈቱ ተማሪዎች ትምህርቱን ለመማር ያላቸው አመለካከትና አተያይ አናሳ እንደሆነ
ያመለክታል፡፡ ይህ ደግሞ በተማሪዎቹ ውጤት ላይ የራሱ የሆነ አሉታዊ ተጽዕኖ ስላለው ለአማርኛ ቋንቋ
ትምህርት ትኩረት እንዳይሰጡ ሊያደርግ ይችላል፡፡
የዚህ ጥናት መነሻ ችግርም በኦሮምኛ ቋንቋ አፍ-ፈት የሆኑ ተማሪዎች የ 8 ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ በኋላ
ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሲገቡ አማርኛ ቋንቋን ለመማር ያላቸው ፍላጎት በጣም አናሳ በመሆኑ
ምክንያት በመማር ማስተማር ሂደት ዙሪያ በሚደረጉ ስብሰባዎች ላይ የመወያያ ነጥብ ሆኖ በተደጋጋሚ
እየቀረበ እንደሚያከራክር አጥኚዋ ካላት የረጅም ጊዜ የማስተማር ልምድ ችግሩን ተመልክታለች፡፡ስለዚህ
አጥኝዋ ይህን ችግር መነሻ በማድረግ በድሬዳዋ ከተማ መስተዳድር በናሙናነት በሚመረጡት ሁለት 2 ኛ
ደረጃ ት/ቤቶች የሚማሩ አፋቸውን በኦሮምኛ ቋንቋ የፈቱ የ 2015 ዓ.ም የ 9 ኛ ክፍል ተማሪዎች የአማርኛ
ቋንቋ ትምህርት ለመማር ያላቸውን ፍላጎትና የፈተና ውጤታቸው ዝምድናን ለመፈተሸ ተነሳስታለች፡፡
4
1.3.የጥናቱ መሰረታዊ ጥያቄዎች
ይህ ጥናት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መሰረታዊ ጥያቄዎች ይመልሳል ተብሎ ይታሰባል፡፡
1. በኦሮምኛ ቋንቋ አፋቸውን የፈቱ ተማሪዎች ለአማርኛ ቋንቋን ትምህርት ያላቸው
ፍላጎት ምን ይመስላል?
2. በኦሮምኛ ቋንቋ አፋቸውን የፈቱ ተማሪዎች ለአማርኛ ቋንቋ መማር ማስተማር
ግብአቶች (ለመማሪያ መፅሃፉና ለመምህራን) ያላቸው ፍላጎት እንዴት ይገመገማል?
3. በኦሮምኛ ቋንቋ አፋቸውን የፈቱ ተማሪዎች አማርኛ ቋንቋ ትምህርትን ሲማሩ ወላጆች፣ ጓደኞችና
ማህበረሰቡ በተማሪዎች ላይ የሚያሳድሩት አሉታዊ ተፅዕኖ አለን?
4. በተማሪዎች ፍላጎትና በውጤታቸው መካከል ምን አይነት ዝምድና ይኖራል?
1.4 የጥናቱ ዓላማ
የዚህ ጥናት አብይ አላማ፣ አፋቸውን በኦሮሚኛ ቋንቋ የፈቱ የ 9 ኛ ክፍል በኦሮምኛ ቋንቋ አፋቸውን
የፈቱ ተማሪዎች ለአማርኛ ቋንቋ መማር ያላቸው ፍላጎትና የፈተና ውጤታቸውን ዝምድና መፈተሸ፡፡
1. በኦሮምኛ ቋንቋ አፋቸውን የፈቱ ተማሪዎች አማርኛ ቋንቋ ትምህርትን ሲማሩ
ያላቸውን ፍላጎት ለይቶ ማመልከት፣
2. በኦሮምኛ ቋንቋ አፋቸውን የፈቱ ተማሪዎች ለአማርኛ ቋንቋ መማር ማስተማር
ግብአቶች(ለመማሪያ መፅሃፉና ለመምህራን) ያላቸው ፍላጎት መፈተሸ፣
3.በኦሮምኛ ቋንቋ አፋቸውን የፈቱ ተማሪዎች አማርኛ ቋንቋ ትምህርትን ሲማሩ
ወላጆች፣ ጓደኞችና ማህበረሰቡ በተማሪዎች ላይ የሚያሳድሩት አሉታዊ ተፅዕኖ አለን፣
4. አሉታዊ ፍላጎት በኦሮምኛ ቋንቋ አፋቸውን በፈቱ ተማሪዎች ፈተና ውጤት
ላይ ሚኖረው አሉታዊ ተጽዕኖ ምን ያህል እንደሆነ በፍተሻ ማረጋገጥ የሚሉት ናቸው፡፡
1.5. የጥናቱ አስፈላጊነት
ጥናቱ የሚከተሉትን ጠቀሜታዎች በማስገኘት ረገድ አስፈላጊ ነው ተብሎ ይታሰባል ፡፡
1. አፋቸውን በኦሮምኛ ቋንቋ የፈቱ ተማሪዎች የአማርኛ ቋንቋን ለመማር ያላቸውን
ፍላጎት ደረጃ ለማሳየት፡፡
2. አፋቸውን በኦሮምኛ ቋንቋ የፈቱ ተማሪዎች የአማርኛ ቋንቋን የመማር ፍጎት ላይ
አሉታዊ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ጉዳዮች ምን ምን እንደሆኑ ለመምህራን፣ ለትምህርት
ባለሞያዎች እና ለሌሎችም ለሚመለከታቸው አካላት መረጃ ሊሰጥ ይችላል፡፡
3.ለመምህራን በኦሮምኛ ቋንቋ አፋቸውን የፈቱ ተማሪዎች የአማርኛ ቋንቋ የመማር
ፍላጎት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ የሚያሳድሩ ጉዳዮች መፍትሄ ለይቶ ለማመልከት
ያስችላል፡፡
4.ወደፊት በዚህ ርዕስ ላይና ዙሪያ ጥናት ለሚያደርጉ ሰዎች መነሻ ሀሳብ ይሆናል
5
ተብሎ ይገመታል፡፡
1.6 የጥናቱ ወሰን
ይህ ጥናት የሚመለከተው በድሬዳዋ ከተማ መስተዳድር ውስጥ የሚገኙ ሁለተኛ ደረጃ
ትምህርት ቤቶችን ማዳረስ ስለማይችል በስሩ በሚገኙ ሁለት ሁለተኛ ደረጃ
ትምህርት ቤቶች በ 2015 ዓ.ም የሚማሩ አፋቸውን በኦሮምኛ ቋንቋ የፈቱ የ 9 ኛ
ክፍል ተማሪዎች ብቻ ናቸው፡፡ በመስተዳድሩ ውስጥ በአማርኛ ቋንቋ አፋቸውን
የ 9 ኛ ክፍል ተማሪዎች ለአማርኛ ቋንቋ ያላቸውን ፍላጎትና የፈተና ውጤታቸው ላይ
ብቻ የሚፈትሽ ይሆናል፡፡
ምዕራፍ ሁለት
ክለሳ ድርሳናት
6
2.1. ፍላጎት ምንድ ነው?
የፍላጎትን ምንነት በሚመለከት የተለያዩ ምሁራን የተለያዩ ትንተናዎችን ሲሰጡ ይስተዋላል፡፡ይሁን እንጂ
የሁሉም ምሁራን ሀሳብ ወደ አንድ ምድብ ሊካተት የሚችል መሆኑን Skinner (1985) አስረድቷል፡፡ በዚህ
ጉዳይ ላይ የተለያዩ ምሁራን የሰጡትን ብያኔ እንደሚከተለው ለመዳሰስ ይሞከራል፡፡ Abraham (1954)
ፍላጎት የሚለውን ቃል ሲያብራራ፣ የሰው ልጅ ለህልውናው ወይም ለሞራሉ የሚያስፈልገውን እንዲያሟላ
የሚያስገድደው፣ የሚጎትተው፣ ለተግባሩ የሚያነሳሳውና የሚገፋፋው ውስጣዊ የመሻት ስሜቱ እንደሆነ
ይገልጻል፡፡
ከላይ ከተሰጠው ሃሳብ መረዳት እንደሚቻለው ፍላጎት ማንኛውንም ተግባር ለማከናወን የሚያስችልና
ውስጣዊ መነሳሳትን የሚፈጥር ሀይል እንደመሆኑ መጠን በመማር ማስተማሩ ሂደት ውስጥ ያለ ፍላጎት
የሚከናወን ማንኛውም እንቅስቃሴ ውጤታማ ሊሆን እንደማይችል መገንዘብ ያሻል፡፡ ፍላጎት የሰብዕና
መገለጫ አንዱ አካል ሲሆን እንደ አመለካከትና ተነሳሽነት ሁሉም በስነ-ልቦና ጥናት ከሚተኮርባቸው
ተላውጦዎች አንዱ እንደሆነ Hamlin (1996) ያስረዳል፡፡ከዚህም በተጨማሪ Torne (1997) እንደገለጸው፣
ፍላጎት የአንድ ግለሰብ ስሜትና ዝንባሌ የሚገለጽበት ወይም ደግሞ ግለሰቡ የአንድን ነገር ምንነት ለማወቅ
የሚገፋፋው ሃይል እንደሆነ አስረድቷል ፡፡ እንደ Lee (1976) አገላለጽ፣ ፍላጎት በአንድ ሁነት ውስጥ
ለመሳተፍ ወይም ድሪጊቱን ለመፈጸም የሚያስችል ውስጣዊ መሻት ነው በማለት አስረድቷል፡፡ በተጨማሪም
Evans (1965) ፍላጎት ሰው የሚሰራውን ወይም የሚያደርገውን ነገር ሊወስን የሚችል ሀይል እንደሆነ
አመልክቷል፡፡ እንዲሁም Hurlock (1996) ፍላጎት ማለት ወደተወሰነ ግብና አላማ ሊመራ የሚችል ሃይል
እንደሆነ ያስረዳል፡፡ Skinner (1985) በበኩሉ ፍላጎት የታቀደን አላማ ከግብ ለማድረስ የሚከናወንን ተግባር
መውደድና አለመውደድን፣ ውስጣዊ ተነሳሽነትን፣ ለተፈለገው ነገር ትኩረት እንዲሰጥና በአንድ ነገር ለመሳብ
ወይም ላለመሳብ ምክንያት የሚሆን ውስጣዊ ተግባር እንደሆነ ያስረዳል፡፡
ከላይ ከቀረበው የተለያዩ ምሁራን ሀሳብ መረዳት የሚቻለው ፍላጎት አንድ ነገር የመውደድና የመጥላት ሀይል
ሲሆን፣ በአንድ በተወሰነ ነገር ላይ የማትኮር ሁኔታና ወደ ማናቸውም ተግባርም የሚመራ አንድ ሃይል መሆኑን
መረዳት አያዳግትም፡፡ስለሆነም ፍላጎት አንድን ተግባር ለማከናወንና ለመፈፀም ፍቃደኛ የመሆን ወይም
ያለመሆን መልስ የሚሰጥበት ውስጣዊ ግፊት ወይም መሻት ነው ፡፡
2.2. የፍላጎት ጠቀሜታ
ፍላጎት በትምህርትም ሆነ በተለያዩ እንቅስቃሴና ተግባራት ውስጥ አንድን ድርጊት ለማከናወንና ውጤታማ
ለመሆን የበኩሉን አስተዋጾ ሊያደርግ እንደሚችል የተለያዩ ምሁራን ይገልፃሉ፡፡Garry (1970) የፍላጎትን
ጠቀሜታ አስመልክ to እንደገለፀው፣ አላማ ጥንካሬ እንዲኖረው ፍላጎት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው፡፡ ይህም
በመሆኑ አንድን ተግባር የሚያከናውን ማንኛውም ሰው ለተግባሩ የጠና ፍላጎት ካለው ስራውን በትክክል
እንዲያከናውን ያደርገዋል፡፡ አላማን መሰረት አድርጎ የሚከናወን ተግባር ከፍላጎት ጋር ተያይዥነት ያለው
መሆን አለበት፤ ምክንያቱም ሙሉ ሀይልን ለመጠቀምና ተግባራትን በአጥጋቢና በጥሩ ሁኔታ ለማከናወን
የሚረዳና ተነሳሽነትን በሰዎች ዘንድ የሚፈጥር ሀይል ነው፡፡Harmer (1991) እንዳስረተዋል፣ ሰዎች ለአንድ
7
ተግባር ወይም ጉዳይ ፍላጎት የሚኖራቸው ከሆነ ተግባሩን ለማከናወን ውስጣዊ የሆነ ተነሳሽነት ወይም ግፊት
እንዲኖራቸው ያስችላቸዋል፡፡
በአጠቃላይ ፍላጎት የመማር ማስተማሩን ተግባር ለማከናወን ብቻ የሚያስፈልግ ሳይሆን ማንኛውንም
በክፍልም ሆነ ከክፍል ውጪ የሚከናወኑ ተግባራትን ለመፈፀም ወይም ለማከናወን ወሳኝነት እንዳለው ከላይ
የቀረበው የተለያዩ ምሁራን ሀሳብ ያመለክታል፡፡ ይህ ሳይሆን ቀርቶ ለቀረበው ትምህርት ፍላጎት የሌለውን
ተማሪ ለማስተማር መጣር ወይም መሞከር ውጤቱ ከድካምና ልፋት ያለፈ ሊሆን እንደማይችል መገንዘብ
ተገቢ ይሆናል፡፡
2.3. ፍላጎትና የሁለተኛ ቋንቋ ትምህርት
ፍላጎት የኢ-አፍ-ፈት ተማሪዎች ለትምህርት በቀረበላቸው ሁለተኛ ቋንቋ ትምህርት ያላቸው ፍላጎት
በቋንቋው ስኬታማ መሆን አለመሆን ሊያመለክት እንደሚችል በተለያዩ ምሁራን ዘንድ ይነገራል፡፡ Sposky
(1989) ፍላጎት በሁለተኛ ቋንቋ ውስጥ ያለውን ሚና ሲገልጽ፣ የቋንቋው ተማሪ አዎንታዊ አመካከት
አዎንታዊ የመማር ፍላጎትን እንደሚያመጣ ሁሉ አሉታዊ አመካከት ደግሞ አሉታዊ የመማር ፍላጎትን
እንደሚያስከትል ወይም እንደሚያመጣ ያስረዳል፡፡ በመሆኑም እንደ Gardner (2007) እይታ ደግሞ
በሁለተኛ ቋንቋ ትምህርት የተማሪዎች አመለካከትና ፍላጎት በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አስፈላጊውን
መረጃ ማግኘት ከተቻለ፤ በዙሪያው የሚከሰቱ ችግሮችን አስቀድሞ ለመፍታትና የመማር ማስተማሩን ሂደት
የሰመረ ለማድረግ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን አስረድቷል፡፡ ይህ ካልሆነ ግን ተማሪው ቋንቋውን ለመማር
ፍላጎት ከሌለውና ሁለተኛ ቋንቋውን ለምን አላማ እንደሚማር ካላወቀ ለቋንቋው ትምህርት አሉታዊ
አመለካከት እንደሚኖረው በማለት ይገልፃል፡፡
በአጠቃላይ የተማሪዎችን ፍላጎት በማወቅ የመማር ማስተማሩን ተግባራት ለማከናወን መንቀሳቀስ
ተፈላጊውን ውጤት ለማግኘትና የመማር ማስተማሩ ሂደት የተቃናና የሰመረ እንዲሆን ከማስቻሉም በላይ
ተማሪዎች በሁሉም የክፍል ተግባራት ውስጥ እንዲሳተፉ ስለሚያስችል የተማሪዎቹ ፍላጎት ምን
እንደሆነአስቀድሞ ማወቅናለተግባራዊነቱ መንቀሳቀስ ተገቢነው፡፡
8
ከላይ ከረበው ሃሳብ በተጨማሪም Skinner(1985) ሲያብራሩ፣ ተማሪው የሚሰጠውን ትምህርት ከልብ
የማይከታተል ከሆነ፣ ትምህርቱ ሲሰጥ ከልብ የማያዳምጥ፣ የሚሰጠውን ትምህርት በሚገባ የማይረዳ፣
በመማሪያ መፅሀፉ ውስጥ የቀረበውን ምንባብ የማያነብና በመፅሀሩ ውስጥ የተካተቱ ጥያቄዎችን ወዘተ
የማይሰራ ከሆነ ተማሪው የመምር ፍላጎት የሌለው መሆኑም ያመላክታል ይላሉ፡፡ስለዚህ ተማሪው ለሚሰጠው
ትምህርት ፍላጎት እንዲኖረው የተለያዩ ዘዴዎችን መጠቀም ያስፈልጋል፡፡ከዚሁ በተጨማሪም ደግሞ ተማሪው
በትምህርቱ ፍላጎት እንዲኖረው መምሀራንም ሆኑ ማህበረሰቡ ተማሪዎች በትምህርታቸው ጥሩ አመለካከት
እንዲኖራቸው መቀስቀስ ይጠበቅባቸዋል፡፡ አለበለዚያ ግን ለትምህርቱ ፍላጎት የሌለው ተማሪ ማስተማሩ
በክፍል ውስጥ ለሌለ ተማሪ እንደ ማስተማር ይቆጠራል፡፡
በአጠቃላይ ከቀረበው የምሁራኑ ሃሳብ መረዳት የሚቻለው ፍላጎት ለትምህርት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳለው
ነው፡፡ተማሪው ትምህርቱን በአግባቡ እንዲከታተል በክፍል ውስጥ የሚከናወነው የመማር ማሰተማር ሂደት
በተማሪ ፍለጎትን መሰረት ያደረገ ሊሆን ይገባል፡፡በመሆኑም የተማሪውን የመማር ፍላጎት ለማሳደግ
የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት የተማሪው የመማር ፍላጎት ከፍ እንዲል አስተዋፅኦ ማድረግ አለባቸው፡፡
ከላይ ከቀረበው ሃሳብ በተጨማሪም Skinner (1959) እንደገለፁት የተማሪዎችን ፍላጎት ማጥናት
ስለተማሪው ማንነት ለማወቅ ይጠቅማል፡፡ ተማሪው ለትምህርቱ ያለው ፍላጎት አወንታዊ ከሆነ ያህንኑ በጥሩ
ሁኔታ ጠብቆ ለማቆየት የተማሪዎችን ፍላጎት አስቀድሞ ማወቁ ወሳኝ ነው፡፡ ስለዚህ የተማሪው ፍላጎት
አስቀድሞ ማወቅ ለሚቀርበው ትምህርት እንደ መነሻ ሆኖ ያገለግላል፡፡
9
2.6. የሁለተኛ ቋንቋ ትምህርት ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ጉዳዮች
በአንድ ተማሪ የሁለተኛ ቋንቋ የመማር ሂደት ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ተላውጦዎች በርካታ እንደሆኑ የመስኩ
ምሁራንያስረዳሉ፡፡ ምሁራኑ ካነሷቸው ውስጥ ፡- የመምህሩ ስብእና፣ ወላጆች፣ ማህበረሰቡ፣ የመምህሩ
የማስተማሪያ ዘዴ፣ጓደኞች ወዘተ ይጠቀሳሉ፡፡ተማሪዎች ሁለተኛ ቋንቋ ሲማሩ እነዚህ የተጠቀሱት
ተላውጦዎች በትምህርታቸው ላይ አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ ተጽዕኖ በማሳደር ረገድ የበኩላቸውን
አስተዋጽኦ እንደሚያሳድሩ Gardner (1968)፣ እና Harmer (1990) ያስረዳሉ፡፡ ታደሰ (2004) አገላለጽ፣
የሁለተኛ ቋንቋ ተማሪዎች ታላሚውን ቋንቋ ሲማሩ አሉታዊ ተጽእኖ ሊያሳድሩ የሚችሉትን
እንደሚከተለው ዘርዝሯል፡፡
የሁለተኛ ቋንቋ ተማሪዎች ቢያንስ አንድ ሌላ ቋንቋ፣የአፍ መፍቻ ቋንቋቸውን ስለሚያውቁ ግፊቱ
የመጀመሪያ ቋንቋ ማወቁን ያህል ጠንካራ ያለመሆን፣
የሁለተኛ ቋንቋ ተማሪዎች አንድ ሌላ ቋንቋ ቀደም ሲል በማወቃቸው ያ ቋንቋ ከሁለተኛው ቋንቋ ጋር
እየተጋጨ ስለሚያስቸግራቸው፣
የሁለተኛ ቋንቋ ተማሪዎች ቋንቋውን የሚማሩት በሚያጋጥማቸውና በሚመቻቸው ሁኔታ ወይም
በሁኔታዎች አስገዳጅነትና ዝግጅት ባለው የመማርሂደት (FormalLearning) በመሆኑ፣
የሁለተኛ ቋንቋን የሚማሩ ተማሪዎች የአፍ መፍቻ ቋንቋቸውን እንደሚለምዱ ህፃናት ያለመሰልቸት
ለረጅም ጊዜ መለማመድ(መማር) ያለመፈለጋቸው ነው፡፡
በአጠቃላይ ከላይ ከቀረበው ሀሳብ መረዳት እንደሚቻለው በሁለተኛ ቋንቋ ተማሪ የመማር ፍላጎት ላይ
በአዎንታዊም ሆነ በአሉታዊ ጎኑ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ የተለያዩ ውጫዊና ውስጣዊ ተላውጦዎች እንዳሉ
ነው፡፡ ከዚህ በማስከተል ተጽዕኖ ያሳድራሉ ተብለው በተለያዩ ምሁራን ዘንድ የቀረቡትን ተላውጦዎች
ለማየት ይሞከራል፡
10
አስረድተዋል፡፡ በተጨማሪም ታደሰ (2004) ተማሪዎች አንድን ትምህርት ከባድ ነው የሚል አመለላከት
ካላቸው በትምህርቱ ላይ አሉታዊ አመለካከት ሊኖራቸው እንደሚችል ሁሉ ትምህርቱ ጥቅም ይሰጣል
ብለው ካሰቡ ትምህርቱን ለመማር አዎንታዊ አመለካከት ይኖራቸዋል ሲል አስረድቷል፡፡
ከላይ እንደተገለጸው ተማሪው በተጠቀሱት ጉዳዮች ላይ አዎንታዊ አመለካከት ካለው የትምህርቱ ሂደት
የተቃና ይሆናል፤ ነገር ግን ተማሪው አሉታዊ አመለካከት ካለው በተቃራኒው በትምህርቱ ሂደት ላይ የራሱ
የሆነ አሉታዊ ጫና ይፈጥራል፡፡
በአጠቃላይ ከተሰጠው ብያኔ መረዳት የሚቻለው የሁለተኛ ቋንቋ ተማሪው ለትምህርት በቀረበው ሁለተኛ
ቋንቋ ላይ የሚኖረው አመለካካት ወይም አተያይ በተማሪው የትምህርት አቀባበል ላይ ስለሚንጸባረቅ
አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ ተጽዕኖ በማሳደር ረገድ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ምሁራኑ ከሰጡት አስተያየት
መረዳት ይቻላል፡፡
ከላይ ከቀረበው ሀሳብ መረዳት እንደሚቻለው ተማሪው በውስጡ ያለው የስነልቦና ሁኔታ በክፍል ውስጥ ያለውን
የመማር ማስተማር ውጤታማ ወይም ውጤት አልባ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንዳለው በማወቅ የመማር
ማስተማሩ ሂደት ውጤታማ እና የሰመረ እንዲሆን ተማሪዎቹን በማነቃቃታና በማደፋፈር በትምርቱ ላይ ተሳታፊ
እንዲሆኑ ሁኔታዎች ማመቻቸት ተገቢ ነው፡፡
ከላይ በተለያዩ ምሁራን የቀረበውን ሃሳብ መሰረት በማድረግ መረዳት የሚቻለው የተማሪው ጓደኞች
የማህበረሰቡ አባል እንደመሆናቸው መጠን ይዘውት ያመጡትን አዎንታዊም ሆነ አሉታዊ ተጽእኖ
በጓደኞቻቸው ላይ በማንጸባረቅ በመማር ማስተማሩም ሆነ በሌሎች ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ተጽእኖ
በማሳደር ረገድ ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው በማወቅ የማስተማሩን ሂደት ስኬታማ ለማድረግ ብጤዎች ላይ
ገንቢ የሆነ የአስተሳሰብ ለውጥ መስራትእንደሚገባ ነው፡፡
ስለዚህ የመምህሩ ስብእና በተማሪዎች የመማር ፍላጎት ላይ የራሱ የሆነ አዎንታዊ ወይም አሉታዊ ተጽእኖ
ሊያሳድር እንደሚችል ከላይ ከቀረበው የተለያዩ ምሁራን ሀሳብ መረዳት ይቻላል፡፡
በተጨማሪም ታደሰ (2004) ተማሪዎች ለቀረበላቸው ትምህርት ፍላጎት እንዲኖራቸው መምህራን በክፍል
ውስጥ በሚያስተምሩበት ወቅት የተማሪውን ጠንካራ ጎን ማጉላት፣ ከተማሪው ህይወት ጋር የተገናኘ ምሳሌ
መስጠት፣ ሁልጊዜ ድርቅ ያለ ዕውነታ ላይ ብቻ ባለማተኮር፣ የተማሪዎቹን ወቅታዊ ስሜት በመጠቀም እና
የማስተማሪያ ስልትን በመለዋወጥ የተማሪዎችን የመማር ፍላጎት ማነቃቀት እንደሚጠበቅባቸው ያስረዳል፡፡
ስለዚህ የቋንቋው ትምህርት በተገቢውና በተቃና መንገድ የመማር ማስተማሩ ተግባር እንዲካሄድ የቋንቋ
መማሪያ መጽሀፍት የተማሪውን ፍላጎት እና ዳራዊ ችሎታ መሰረት አድርገው መዘጋጀት እንዳለባቸው
መረዳት ያሻል፡፡
እንዲሁም እንደ ወንድወሰን (1989) አገላለጽ፣ የመማሪያ መጽሀፍት በተማሪው ፍላጎት ላይ ተመስርተው
በጥንቃቄ ከተዘጋጁ የተማሪውን የመማር ፍላጎት አነቃቅተው ለቋንቋውና ለትምህርቱ የሚኖረውን
አመለካከት አዎንታዊ በማድረግ ለጥሩ ውጤት ያደርሳል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ Dubin (1986) እንዳስረዳው
የመማሪያ መጽሀፍት የተማሪዎችን የመማር ፍላጎትና ለትምህርቱ ያላቸውን አመለካከት ለማበረታታት፡-
15
የመማሪያ መጽሀፍቱ መምህሩ እንዲያስተምር፣ ተማሪው እንዲማር የሚረዱ
ሆነው የተዘጋጁ እንጂ ጫና የሚፈጥሩባቸው ሆነው መዘጋጀት እንደሌለባቸው ነው፡፡
የሁለተኛ ቋንቋ ተማሪው ትምህርቱን ተፈትኖ የሚያገኘው ውጤት የተማሪውን የመማር ፍላጎት
በማነሳሳትም ሆነ በማዳከም የራሱ የሆነ ተጽዕኖ እንዳለው የተለያዩ ምሁራን የራሳቸውን አስተያየት
ሲሰነዝሩ ይስተዋላል፡፡ተዋበች (2003) Gardner (1985)ን፣ ዋቢ በማድረግ አዎንታዊ ተጽዕኖ ከከፍተኛ
ውጤት፣ አሉታዊ ተጽዕኖ ከዝቅተኛ ውጤትና ከደካማ የትምህርት ተሳትፎ ጋር ተዛማጅነት እንዳለው
በመግለጽ፣ ተማሪዎች ለሚማሩት ሁለተኛ ቋንቋ አዎንታዊ አመለካከት ካላቸው በትምህርቱ ንቁ ተሳታፊ
ከመሆናቸውም በላይ በራሳቸው የመተማመን ስሜት ሊያሳድሩ ይችላሉ፡፡ በራሳቸው የሚተማመኑ
ተማሪዎች ደግሞ የቋንቋውንም ትምህርት ፍላጎት እና ጥረት በተሟላ ሁኔታ ስለሚማሩ ውጤታቸው
የተሻለ ሆኗል ከሚል ድምዳሜ ላይ ደርሰዋል በማለት አስረድታለች፡፡
እንዲሁም Harmer (1991) ተማሪው ያለው ዳራዊ እውቀት በቋንቋው ትምህርት ፍላጎት ላይ ለውጥ
እንደሚያስከትል በመግለጽ፣ቀደም ሲል ውጤቱ ስኬታማ ካልሆነ ምናልባትም በሚቀጥለው ጥሩ ውጤት
አምጥቶ ማለፍ እንደማይችል ስለሚገምት በትምህርቱ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እንደሚያሳድር በማመልከት፣
ተማሪዎች በሚማሩት የቋንቋ ትምህርት የሚያገኙትን ውጤት ምክንያት በማድረግ በትምህርቱ ላይ
አዎንታዊ ወይም አሉታዊ ተጽዕኖ ሊያዳብሩ ይችላሉ በማለት አስረድቷል፡፡ በተጨማሪም ወንድወሰን
(1989) ታደለ (1990)ን በመጥቀስ እንደገለፀው፣ በቋንቋ ትምህርት ሂደት ተማሪው የሚገጥመውና በውስጡ
የሚያልፍበት ሁኔታ፣ የሁለተኛ ቋንቋ ትምህርት፣ የቋንቋው መምህር፣ የማስተማሪያ መሳሪያዎች፣
በአጠቃላይ የትምህርቱ ስርአትና ሌሎች ማህበራዊ የሆኑ ጉዳዮች፣ በመማር ማስተማሩ ሂደት ተማሪው
ከነዚህ ጉዳዮች ጋር በሚያደርገው መስተጋብርና እንቅስቃሴ በሚመነጭ አዎንታዊ ወይም አሉታዊ ተጽዕኖ
ሊያድርበት ይችላል፡፡ ይህ ደግሞ ተማሪው በትምህርቱ ሂደት ከሚያደርገው የመማር ጥረትና ውጤት ጋር
ይገናኛል በማለት ያስረዳል፡፡
በአጠቃላይ ከላይ ከቀረበው ሀሳብ መገንዘብ እንደሚቻለው ተማሪው በላሚው ትምህርት የሚያገኘው
ውጤት ተማሪውን በማበረታታት ወይም በማዳከም ረገድ ተጽዕኖ ማሳደር እንደሚችል ነው፡፡ ውጤቱ
16
ስኬታማ ከሆነ ትምህርቱን የመማር ፍላጎት እንደሚኖረው ሁሉ ውጤቱ ዝቅተኛ ከሆነ ደግሞ የመማር
ፍላጎቱም አናሳ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ ስለዚህ ተማሪው በትምህርቱ በሚያገኘው ውጤት የተነሳ
ታላሚውን ቋንቋ የመማር ፍላጎቱ ላይ አዎንታዊ ወይም አሉታዊ ተጽእኖ ማሳደሩ የማይቀር ነው፡፡
17
የጽሁፍ መጠይቅ፣የክፍል ውስጥ ምልከታ፣ቃለ መጠይቅና የ 2003 ዓ.ም. ተከታታይ ምዘናና የአንደኛ መንፈቀ
አመት አማካይ ውጤት ነው፡፡ የጥናቱ ውጤት እንዳመለከተው ብዙ ተማሪዎች ለቋንቋውና ለትምህርቱ
ያላቸው አመለካከት አናሳ እንደሆነ ከመጠቆሟም በላይ በተማሪዎቹ አመለካከትና በፈተናው ውጤታቸው
መካከል ዝቅተኛ አዎንታዊ አመለካከትና ከማለፊያ ውጤት ጋር ዝምድና እንዳለው አመልክታለች፡፡ እንደ
መፍትሄም ያስቀመጠችው ተማሪዎች ለአማርኛና ለሌሎች የትምህርት አይነቶች እኩል ፍላጎት
እንዲኖራቸው አንዱ ሌላውን በማይጫን መልኩ የተለያየ የስነጽሁፍ ክበባትና የሚኒ ሚዲያ ፕሮግራም
በመፍጠር ለታላሚው ቋንቋ ፍላጎታቸውን ማነሳሳት እንደሚቻል አስገንዝባለች፡፡
ይህን ጥናት ከቀረቡት ከወንደሰንና ከተዋበች ጥናቶች ጋር የሚያመሳስለው የአማርኛ ቋንቋ ትምህርትን እንደ
ሁለተኛ ቋንቋ በሚማሩ ተማሪዎች ላይ መካሄዱ እምዲሁም የሰነድ ፍተሻ መጠቀሙ፡፡ ሌላው የጽሁፍ
መጠይቅን ለመረጃ መሰብሰቢያነት በመጠቀሙ ከሶስቱ የቀደምት ጥናቶች ጋር ያመሳስለዋል፡፡ እንዲሁም ቃለ-
መጠይቅን ለመረጃ መሰብሰቢነት በመጠቀሙና 10 ኛ ክፍል ላይ ጥናቱ መደረጉ ከፀጋዬና ተዋበች ጥናት ጋር
እንዲመሳሰል አድርጎታል፡፡ በተጨማሪም ጥናቱ በከተማ መስተዳድር ውስጥ መደረጉ ከፀጋዬ ጥናት ጋር
ያመሳስለዋል፡፡
ምዕራፍ ሦስት
የአጠናን ዘዴ
ጥናቱ ገላጭ (Descriptive) የምርምር ንድፍን መሰረት አድርጎ የሚቀርብ ነው፡፡ ቃሉ እንደሚያመለክተው
ተመራማሪዋ አንድ ጉዳይ አንስታ ሁኔታዎች ብሩህ እስኪሆኑ ድረስ ምንነታቸውን፣ እንዴትነታቸውን፣
ማናነታቸውን፣ የድርጊቶችን አኳኀንና ምን በመሆን ላይ እንዳለ በገለፃ መልክ የምታቀርብበት ነው፡፡
18
ጥናቱ የገለፃ ስልት የተከተልበት ምክንያት የጥናቱን ርዕሰ ጉዳይ ለመግለጽ የሚያስችል ዘዴ በመሆኑና ለጥናቱ
አጋዥ የሚሆኑ መረጃዎችን ማለትም በጽሁፍ መጠይቅና በቃለ መጠይቅ የሚሰበሰቡትን መረጃዎች
ለመተንተን ምቹ በመሆኑ ነው፡፡
3.2 የናሙና አመራረጥ ዘዴ
3.2.1.የከተማመስተዳድአመራረጥ
በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ መስተዳድሮች ሁለት ሲሆኑ አጥኚዋ ለጥናቱ አስፈላጊውን መረጃ ለማግኘት
ይረዳው ዘንድ አመቺ (convenience sampling) ንሞና በመጠቀም የድሬዳዋ መስተዳድርን ትመርጣለች፡፡
ይህ መስተዳድር የምትመርጥበት ምክንያት አጥኝዋ ከዚህ መስተዳድር በቂ መረጃ፣ በቂ ትብብርና የሰው
ሀይል ማግኘት እንደምትችል በማሰብ ነው፡፡
19
3.3.1 የጽሁፍ መጠይቅ
በዚህ ጥናት ውስጥ በዋነኛነት የመረጃ መሰብሰቢያ ሆኖ የሚመረጠው የጽሁፍ መጠይቅ ነው፡፡ ያለው (2006)
እንደገለጸው፣ የጽሁፍ መጠይቅ በዋናነት የተመረጠበት ምክንያት፡-ቆጣቢ፣ የመላሾቹን ማንነት የማይገልጽ ና
ለሁሉም ተጠኚዎች አንድ አይነት ጥያቄ የሚያቀርብ ስለሆነ ነው፡፡
የጽሁፍ መጠይቆቹ የተዘጋጁት ክለሳ ድርሳኑን መሰረት በማድግ ሲሆን፣ በጽሁፍ መጠይቁ ተማሪዎች አማርኛ
ቋንቋን በማስተማር ሂደት ላይ ያላቸውን ፍላጎት መፈተሽ የሚመለከቱ ጥያቄዎች የሚካተቱ ሲሆኑ
ጥያቄዎቹም ሶስት ክፍሎች ያኖሩታል፡፡የመጀመሪያው ክፍል የተጠኚዎቹን ዳራ የሚመለከት ሲሆን፣
ሁለተኛው ክፍል ዝግ
ጥያቄዎችን እና ሶስተኛው ክፍል ደግሞ ክፍት ጥያቄዎችን ያካትታል፡፡ዝግ ጥያቄዎቹ የሊከርት ሞዴልን
መሰረት በማድረግ የተዘጋጁ ሲሆን፣ በጣም እስማማለሁ(5)፣ እስማማለሁ(4)፣ መወሰን ያቅተኛል(3)፣
አልስማማም(2)፣ ጭራሽ አልስማማም(1) የሚሉ አማራጮችን ተካተው በሰንጠረዥ የሚቀርብ ሲሆን
ክፍት (ልቅ) ጥያቄዎቹ ደግሞ የተጠኚዎችን ነጻ አስተያየት የሚሹ ይሆናሉ፡፡ መጠይቆቹ በአጥኝዋ ከተዘጋጁ
በኋላ በአማካሪው አስፈላጊው እርምትና ማስተካከያ ከተደረገባቸው በኋላ መጠይቆቹን ለተጠኚዎቹ
በማደል ሞልተው ሲጨርሱ አጥኝዋ መረጃውን ትሰበስባለች፡፡
ዋቢ መፅሃፍት
22
of Attiude and Motivation.London,Edward.Amold.
----------.(2007).Motivation and Second Language Acquision.porta.Linguarum,8,9-
20.GarderR.andLambert.(1972).Attitude and Motivation Second Lnguage
Learning.Rowley,Mass:Newburg house.
Harmer,J.(1983). The practice of English Learning Teaching.New
York,longman.
Harmer,J .(1990). The practice of English Learning Teaching .New York,long
man.Group ltd.
------------.(1991). Hand Book of Language Teachers.The Practiceof
Englihs Language Teaching.(New Education).new York, Longman.
Krashen.S.(1985).TheImput Hypothesis Issues are Implication.Harlow,Consman.
Language in Ethiopia. London: Oxford University Press..
Little.Wood.W.(1981).Communicative Language Teaching.Cambridge,
Cambridge University press.
Skinner.E.C .(1985). Educational Psychology .New York, prentice Hall. Inc.
---------------.(1989).Educational Psychology. 4thed. New Delhi: Mentice, Hallofindia
privetlimited.
Smith, Alfred,N.(1971).“importance of Attitude in foregn language learning”. The
modern Language Journals Vol,55,No 2.
Stewart.W.A.(1968).National Developmen and Language Diversity.in Fresh
man.J.(ed). Reading in Sociology of Language paris:Moutons and
co.printers.(44-216)
Stern,H.N.(1983).Fundamental Concept of Languag Teaching.London,Oxford
Universitypress.Inc.
-------------.(1992).Issues and Options in Language Teaching.0xford University
press.
23
ss.
Spolsky,Bernard.(1989).Condition for Second Language Learning.Oxford.CUP.
Tsii.M.B.(2003). understanding Expertisein Teaching case Studies of ESL
Teachers.Hongkong :Cambridge Universty press.
Ur,Penny.(1996).Acourse in Language Teaching Practice and Theory.Cambridge,
Cambridge:University Press.
Walki, A. Googel (2000).contextual factors in second language Acqusition
Htt/cal,Orga.resources / digest/005 Contextual,htm/
Webb,V.and Kembo-sure.(2000).African Voices an Introducation to the Language
and Lingustics of Africa.Cape Towen:oxford University press
Southern Africa.
William.M.M.Burden.B.(1997).psychology for Language Teacher.Asocial
Constiructivist Approach. Cambridge:Oxford University press.
24
ግምታዊ የጊዜ ሰሌዳ
8 የምእራፍ አራትን ስራ በአማካሪ ማስገምገም እና በተሰጠ አስተያየትና ከሚያዝያ 1 እስከ 15/2015 ዓ.ም.
እርምት መሰረት ማስተካከል፡፡
9 ምእራፍ አምስትን አዘጋጅቶ ለአማካሪ ማቅረብ፡፡ ከሚያዚያ 15-30 ቀን 2015 ዓ.ም.
10 የምእራፍ አምስትን ስራ በአማካሪ ማስገምገም እና በተሰጠ አስተያየትና ከግንቦት 1-ግንቦት 15/2015 ዓ.ም
እርምት መሰረት ማስተካከል፡፡
11 አጠቃላይ የጥናቱን ምዕራፎች አቀናብሮ ለአማካሪ ማቅረብ ከግንቦት 15 እስከ 30/2015 ዓ.ም
12 መስተካከል ያለባቸው ነገሮች ካሉ አስተካክሎ የመጨረሻውን ጥናት ከሰኔ 1 -20/2015 ዓ.ም
ማሳተም
25
ብር ሣን ብር ሣን
ብዛት
ለጽህፈት መሳሪያዎች
ባለመስመር ወረቀት በደስጣ 2 100 00 200 00
ልሙጥ ወረቀት በደስጣ 2 100 00 200 00
ቢክ እስክሪብቶ 20 5 00 100 00
እርሳስ 10 2 00 20 00
ላፒስ 2 10 00 20 00
ለልዩ ልዩ አገልግሎት
ለትራንስፖርት 2500 00
ፍለሽ ባለ GB8 2 300 00 600 00
ማጻፊያ 500 5 00 2500 00
ፎቶ ኮፒ 500 5 00 2500 00
ማስጠረዣ 3 100 00 300 00
ለረዳት መረጃሰብሳቢ መምህራን የአበል 3 100 00 300 00
ክፍያ ------ 3000 00
ፕሪንት ወይም ለህትመት 500 5 00 2500 00
መጠባበቂያ በጀት 2000 00
ጠቅላላ ድምር 16860 00
26
27