You are on page 1of 28

አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ

አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

የፕሮጀክት ባለቤት: አቶ አበባው ተፈራ


ስልክ ቁጥር: 0911973014
አዲስ አበባ - ኢትዮጲያ

አማካሪ ድርጅት - ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ/የተ/የግል ማህበር


የኃላፊ ስም - መንግስቱ ብርሃኑ
አድራሻ - ስልክ 0930011914
ኢሜል- mengistubirhanu@gmail.com
አዲስ አበባ - ኢትዮጲያ

የተስተካከለ

መስከረም 2012 ዓ.ም.


አዲስ አበባ
አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

የፕሮጀክቱ ቦታ: - አማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት፣ ሰሜን ሸዋ ዞን፣ በደብረብርሃን ከተማ በቀበሌ 07

የፕሮጀክቱ ባለቤት: - አቶ አበባው ተፈራ


የአማካሪ ድርጅት: ሀመን የምክር አገልግሎት ድርጅት ኃ/የተ/የግ/ማህበር
የጥናቱ አባላት:
1. መንግስቱ ብርሃኑ – የአካባቢ ጥናት ባለሙያ
2. ተፈራ አሰፋ – የአካባቢ ብክለት እና የማህበራዊ ጉዳይ ተንታኝ ባለሙያ
3. ዮሴፍ መለሰ– የኢኮኖሚ ባለሙያ
4. ፀጋዬ ቦሩ ቱራ – የብዝሀ ህይወት ባለሙያ

የፕሮጀክቱ ባለቤት መግለጫ


አቶ አበባው ተፈራ በዚህ በልብስ ስፌት ፋብሪካ የወሰን ዘገባ የተካተቱት መረጃዎች በሙሉ በእውነተኛ
እና በትክክለኛ መረጃ ላይ የተመሰረቱ መሆኑን ያረጋግጣል፡፡

የፕሮጅክቱ ባለቤት ሥም_________________________ ፊርማ _______________

የአማካሪው መግለጫ
ሀመን የምክር ኃ/የተ/ግ/ማህበር በፌዴራል አካባቢ፣ የደን እና የአየር ንብረት ለውጥ ኮሚሽን የተመዘገበ
እና ፍቃድ ያገኘ አማካሪ ድርጅት በዚህ የአበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ የወሰን ዘገባ የተካተቱት
መረጃዎች በሙሉ በእውነተኛ እና በትክክለኛ መረጃ ላይ የተመሰረቱ መሆንን ያረጋግጣል፡፡

የአማካሪው ሥም_____________________________ ፊርማ ____________________

1|ገጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

ማውጫ
ሠንጠረዥ ዝርዝር ................................................................................................................................................ 4

የምስሎች ዝርዝር.................................................................................................................................................. 4

1. መግቢያ ............................................................................................................................................................ 5

2. የአካባቢ ወሰን ዘገባ ሪፖርትን የሚያጠናው አማካሪ ድርጅት ................................................................................................ 5

3. ኘሮጀክቱ ጠቅላላ ገለፃና አማራጮች ........................................................................................................................... 6

3.1 የኘሮጀክቱን መነሻ ሃሳብ ................................................................................................................................................6


3.3. የአመራረት ዘዴ .........................................................................................................................................................7
3.4. ለፕሮጀክቱ የተለያዩ አማራጮች ..............................................................................................................................8
3.4.1 ኘሮጀክቱ ባይተገበር ..............................................................................................................................................8
3.4.2 ፕሮጀክቱ የሚቋቋምበት ቦታ ..................................................................................................................................9
3.4.3 የቴክኖሎጂ አማራጭ ............................................................................................................................................9
4. በምዕራፎች የተከፋፈለ የፕሮጀክት የትግበራ የጊዜ ሰሌዳ .................................................................................................. 10

4.1 ቅድመ ግንባታ ወቅት ..................................................................................................................................................10


4.2 የግንባታ ወቅት .........................................................................................................................................................10
4.3 የትግበራ ወቅት ........................................................................................................................................................11
4.4 የፕሮጀክቱ መዝጊያ ወቅት ...........................................................................................................................................11

5. የባዮፊዚካልና ማህበረ-ኢኮኖሚ መሰረታዊ መረጃዎች ትንተና ........................................................................................... 11

5.1. ጥናቱ የሚያካትተው የቦታ ስፋት ...................................................................................................................................11


5.2 አካባቢያዊ መግለጫ ..................................................................................................................................................11
5.2.1 ባዮፊዚካል መረጃዎች ..........................................................................................................................................11
5.2.2 ሶሺዮ-ኢኮኖሚ ሁኔታ .........................................................................................................................................13
6. የአካባቢ ተፅዕኖዎች ............................................................................................................................................ 15

6.1. በጐ ተፅዕኖዎች ........................................................................................................................................................15


6.1.1 የሥራ ዕድል ፈጠራ .............................................................................................................................................15
6.1.2 የመንግስትን ገቢ ማሳደግ......................................................................................................................................15
6.1.3 የማህበራዊ ተቋማት መሻሻል .................................................................................................................................15
6.2 አሉታዊ ተፅዕኖዎች ............................................................................................................................................16
6.2.1 በግንባታ ወቅት የሚደርሱ ተፅዕኖዎች ......................................................................................................................16
6.2.2 በትግበራ ወቅት የሚከሰቱ አሉታዊ ተጽእኖዎች ....................................................................................................16
7. የማህበረስብ ወይይት እና ምላሽ .............................................................................................................................. 17

8. የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናት ቢጋር .................................................................................................................................. 19

8.1 መግቢያ .................................................................................................................................................................19


8.2. የፕሮጀክቱ ዓላማዎች ................................................................................................................................................19
8.3 የጥናቱ ዓላማዎች ......................................................................................................................................................19
8.4 የፕሮጀክት ቦታው መገኛና አዋሳኞች ...............................................................................................................................20
8.5 የጥናቱ ስልት ወይም ዘዴ .............................................................................................................................................21
8.6 የእምቅ ተፅዕኖዎች ልየታ ቼክሊስት ................................................................................................................................22

2|ገጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

8.6.1 የተፅዕኖ ስፋት ...................................................................................................................................................22


8.6.2 የተፅእኖ ባህሪ /ተፈጥሮ/ ከፍተኛነት........................................................................................................................22
8.6.3 የተፅዕኖ ቆይታ /ጊዜ/ ..........................................................................................................................................23
8.6.4 ተፅዕኖው የመከሰት አጋጣሚው ሁኔታ....................................................................................................................23
8.7 አሉታዊ ተፅዕኖዎች....................................................................................................................................................24
8.8 የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማው ጥናት ቡድን ..........................................................................................................................24
8.9 የህዝብ ምክክር ........................................................................................................................................................25
8.10 የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናት ሰነድ ይዘት ...............................................................................................................................25
8.11 የጊዜ ሰሌዳ .............................................................................................................................................................26

3|ገጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

ሠንጠረዥ ዝርዝር

ሠንጠረዥ 1፡ ዓመታዊ የጥሬ ዕቃ ፍላጐት .................................................................................................... 6


ሠንጠረዥ 2፡ ዓመታዊ የየምርት አይነት....................................................................................................... 7
ሠንጠረዥ 3፡ የፋብሪካው የቦታ X እና Y ኮርዲኔት ........................................................................................ 20
ሠንጠረዥ 4: የተፅዕኖ መጠንና ስፋት ....................................................................................................... 22
ሠንጠረዥ 5፡ የተፅእኖ ባህሪ /ተፈጥሮ/....................................................................................................... 23
ሠንጠረዥ 6: የተፅዕኖ ቆይታ /ጊዜ/ .......................................................................................................... 23
ሠንጠረዥ 7: ተፅዕኖው የመከሰት አጋጣሚው ሁኔታና ................................................................................... 24
ሠንጠረዥ 8፡ በጥናቱ ተሳተፉ ባለሙያዎች ዝርዝር ....................................................................................... 25
ሠንጠረዥ 9: የአካባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖ ጥናት ሥራ የሚካሄድበት የጊዜ ሰሌዳ .................................................. 26

የምስሎች ዝርዝር

ምስል 1፡ የልብስ ስፌት ፋብሪካው የማምረት ሂደት ......................................................................................... 8


ምስል 2 ፡ የልብስ ስፌት ፋብሪካው የግንባታ ቦታ ........................................................................................ 12
ምስል 3፡ በምክክር መድረኩ ላይ ተሳታፊ የሆኑ የህብረተሰቡ አካላት ................................................................. 17
ምስል 4፡ የፋብሪካው የቦታ ካርታ ............................................................................................................ 21

4|ገጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

1. መግቢያ

ይህ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት፣ በሰሜን ሸዋ ዞን፣ በደብረብርሃን ከተማ በቀበሌ 07 አስተዳደር
በ14,000 ካሬ ሜትር ላይ በአቶ አበባው ተፈረ ባለቤትነት ለሚቋቋመው የልብስ ስፉት ፋብሪካ የአካባቢ
ወሰን ጥናት ዘገባ ነው፡፡

የአካባቢ ወሰን ጥናት ሂደት ለአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ የመጀመሪያው ደረጃ ሲሆን ዓላማውም ዋና ዋና
የአካባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖዎችንና ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን በመለየት ለአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማው ጥናት
አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ብቻ ትኩረት እንዲያደርግ የሚያስችል ሂደት ነው፡፡ በተጨማሪም የአካባቢ
ወሰን ጥናት ሂደት ለአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርት ዝግጅት የሚረዱ ግብዓቶችን የያዘ ሲሆን እነዚህም
ስለፕሮጀክቱ አጭር መግለጫ እና አማራጮች፣ ፕሮጀክቱ በመቋቋሙ ምክንያት ጉዳት የሚደርስበትን
አካባቢ፣ የማህበረሰብ ተሳትፎ፣ አካባቢያዊና ማህበራዊ ተፅዕኖዎች፣ የጥናቱን ቢጋር ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
በጥናቱ ወቅት ፋብሪካው በሚቋቋምበት አካባቢ የሚኖሩና ከፕሮጀክቱ ተጠቃሚም እና ተጐጂ
የህብረተሰብ አካላትን በማወያየት ሃሳባቸው በዋናው የዚህ ሰነድ አካል እንዲሆን ተደርጓል፡፡

2. የአካባቢ ወሰን ዘገባ ሪፖርትን የሚያጠናው አማካሪ ድርጅት

የፕሮጀክቱ ባለቤት አቶ አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካን የአካባቢ ወሰን ዘገባ ሪፖርት እና የአካባቢ
ተፅዕኖ ግምገማ (አተግ) ሪፖርት ለማዘጋጀቱ ለሀመን የምክር አገልግሎት ኃ/የተ/የግ/ማህበር የሥራ
ውክልና የተሠጠው የአማካሪ ድርጀት ሲሆን፤ የአማካሪው ቡድኑም ነባራዊ የአካባቢን ባህሪይ
(የአካባቢውን መግለጫ) መሠረት በማድረግ የታቀደው የልብስ ስፌት ፋብሪካ በሚቋቋምበት እና ወደ ሥራ
በሚገባበት ወቅት ሊከሰቱ የሚችሉ ተፅዕኖዎችን፣ እንዲሁም ማቃለያ መንገዶቹን በማጥናት ሙሉ የአካባቢ
ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርት በመስራት ያቀርባል፡፡

የጥናት ቡድኑ ከሀመን ምክር አገልግሎት ኃ/የተ/የግ/ማህበር ሰራተኞች የተውጣጡ እና የሚከተሉትን


ባለሙያዎች የሚያካተት ነው፡፡ እነዚህም መንግስቱ ብርሀኑ- አካባቢ ጥበቃ ባለሙያ፤ ተፈራ አሰፋ-
የአካባቢ ብክለትና ማኅበራዊ ጉዳይ ተንታኝ ባለሙያ፤ ዮሴፍ መለሰ- ኢኮኖሚስት፣ እና ፀጋዬ ቦሩ ቱላ -
ብዝሃ ሕይወት ባለሙያ ናቸው፡፡

5|ገጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

3. ኘሮጀክቱ ጠቅላላ ገለፃና አማራጮች

3.1 የኘሮጀክቱን መነሻ ሃሳብ

የአበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ተለያዩ ያለቀላቸውን ልብሶች ማለትም ካናቴራዎችን፣ ጅንስ
ሱሪዎችን፣ ሹራቦችን እና ካልሲዎችን በመስፋትና በማዘጋጀት ሥራ ላይ በመሰማራት ምርቶቹን ለሀገር
ውስጥ እና ለውጪ ገበያ በማቅረብ የአገር ውስጥና የውጪ ንግድ የዘርፉን ገቢ ለማሳደግ ዓላማ አድርጐ
ተቋቋመ ነው፡፡ የፕሮጀክቱ ባለቤት አቶ አበባው ተፈራ ሲሆኑ በሀገሪቱ ውስጥ በተለያዩ የንግድ ዘርፎች
ተሰማራተው በመስራት ከፍተኛ ልምድ ያላቸው ናቸው፡፡ ፋብሪካው በዓመት በቁጥር 1,141,526
የተለያዩ አልባሳትን ለማምረት በዕቅድ የያዘ ሲሆን ፕሮጀክቱ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት
በሰሜን ሸዋ ዞን በደብረብርሃን ከተማ በቀበሌ 07 በ14,000 ካሬ ሜትር የሚቋቋም ይሆናል፡፡ የፕሮጀክቱ
ቆይታ ለ80 ዓመት ሲሆን የቆይታው ጊዜ ካበቃ በኃላ ለልብስ ስፌት ፋብሪካ ምርት ግብዓት የሚሆኑትን
ምርቶች ወደ ማምረት ይሸጋገራል፡፡

ፕሮጀክቱን የሚቋቋምበት ዋና ዓላማ አሁን ያለውን ሀገር ውስጥ የተዘጋጁ ልብሶች እጥረት መነሻ
በማድረግ ክፍተቱን ለመሙላት እና በየተዘጋጁ የተለያዩ ልብሶችን በአገር ውስጥ ባሻገር ለዓለም አቀፍ
ገበያ ለማቅረብ ነው፡፡

የልብስ ስፌት ፋብሪካው የጥሬ ዕቃነት የተለያዩ ግብዓቶችን ይጠቀማል፡፡ ከሚጠቀማቸው ጥሬ ዕቃዎች
በዋናነት የጥጥ፣ የፖሊስተር እና የናይለን ጨርቆችን እንዲሁም የፖሊስተርና የጥጥ ቅልቅል ጨርቆችን እና
የጅንስ ጨርቆችን በአገር ውስጥ ካሉ ፋብሪካዎች በመግዛት የሚጠቀም ይሆናል፡፡ ፋብሪካው
ያለቀላቸውን ምርቶች ስለሆነ የሚጠቀመው ምንም አይነት ኬሚካሎችን በግብዓትነት አይጠቀምም፡፡
ሠንጠረዥ 1፡ ዓመታዊ የጥሬ ዕቃ ፍላጐት
የጥሬ ዕቃው የአንዱ Cost (Birr)
ተ.ቁ. አይነት መለኪያ ብዛት ዋጋ LC FC Total Cost
1 ጨርቆችና ናይለንኖች ኪ.ግ 780,289 85.00 66,324,565.00 - 66,324,565.00

2 ቁልፎች ኪ.ግ 15,554 50.85 790,921.00 - 790,921.00


3 የስፌት ክሮች ኪ.ግ 8,789 74.55 655,220.00 - 655,220.00
4 መለዋወጫዎች - Lump sum - 3,440,263.00 - 3,440,263.00
5 ማሸጊያዎች - >> >> - 2,064,158.00 0 2,064,158.00
ጠቅላላ ድምር 73,275,127.00 - 73,275,127.00
6|ገጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር
አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

ሠንጠረዥ 2፡ ዓመታዊ የየምርት አይነት


አመታዊ ምርት አማካይ ዋጋ ጠቅላላ ዋጋ
የምርት አይነት መጠን (ኪ.ግ.) ዋጋ (ብር) በነጠላ (ብር ’000)
ካናቴራ (T-shirts) 185,069 105,754 259 27,390.20
ካናቴራ (Polo shirts) 185,068 89,177 300 26,705.30
ጅንስ ሱሪ 148,055 66,192 300 19,857.85
ሹራቦች 148,055 58,693 350 20,542.60

ካልሲዎች 74,028 821,710 15 12,325.65

ድምር 780,289 1,141,526 137 106,821.60

የፕሮጀክቱ ጠቅላላ የመነሻ ካፒታል የሥራ ማስኪያጃን ጨምሮ ብር 42.48 ሚሊዮን ነው፡፡ ከጠቅላላው
ፕሮጀክት 25% በገንዘብ ከባለሀብቱ የሚገኝ ሲሆን የተቀሪው 75% ወይም ብር 31,860,000.00 ከባንክ
ብድር ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የዕዳ መክፈያ መጠን እንደ አስፈላጊነቱ የኮንስትራክሽን ሥራዎችን
ለማጠናቀቅ፤ ማሽነሪዎችን እና የመኪና ግዥዎችን ለማካሄድ ጥቅም ላይ ይውላል፡፡ ብድሩም የ2 ዓመት
የእፎይታ ጊዜን ሳይጨምር በ10 ተከታታይ ዓመታት ውስጥ በየሩብ ዓመቱ ተመሳሳይ ዕዳዎች የሚከፈል
ይሆናል፡፡ ፋብሪካው በ50% የማምረት አቅም በመጠቀምና በዓመት በ5% በመጨመር እስከ 90%
የማምረት አቅም በመድረስ የተሻለ ገቢ ለማግኘት አቅዷል፡፡ ፕሮጀክቱ ወደ ሠራ ሲገባ ለ199 ዜጐች
የሥራ ዕድል ይፈጥራል፡፡

3.3. የአመራረት ዘዴ

ፕሮጀክቱ የተለያዩ አልባሳትን በማምረት ለአገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ ገበያ ለማቅረብ አስቧል፡፡ ይህን
ለማድረግ ኩባንያው ያለውን ሀብት እና አቅም በተገቢ ሁኔታ ይጠቀማል፡፡ በዚህም መሰረት ፕሮጀክቱ
የተለያዩ አልባሳትን ለማምረት በአሁን ወቅት በአልባሳት ኢንዱስትሪው ዘርፍ ያለውን ዘመናዊ ቴክኖሎጂና
የአመራረት ሂደት ይጠቀማል፡፡ ዝርዝር የምርት ሂደትና የቴክኖሎጂና የማሽኖች ግብዓት ሙሉ የአካባቢ
ተፅዕኖ ሰነዱ ሲዘጋጅ የሚቀርብ ይሆናል፡፡

7|ገጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

ምስል 1፡ የልብስ ስፌት ፋብሪካው የማምረት ሂደት

3.4. ለፕሮጀክቱ የተለያዩ አማራጮች

የአካባቢ ተፅዕኖ ሰነድ ሂደት ውስጥ ከሚካተቱት አንዱ ስለሚቋቋመው ፕሮጀክት የተለያዩ አማራጮችን
በማስቀመጥ የሚቋቋመው ፋብሪካ ከአካባቢ ጋር በተጣጣመ ሁኔታ እንዲሰራ ማድረግ ነው፡፡
አማራጮችም ፕሮጀክቱ የሚጠቀመው ቴክኖሎጂ፣ የሚጠቀመው ግብዓትና የፕሮጀክቱ የትግበራ ቦታን
መሰረት በማድረግ ከዚህ በታች የተለያዩ አማራጮችን ለማስቀመጥ ተሞክሯል፡፡

3.4.1 ኘሮጀክቱ ባይተገበር

ይህን አማራጭ በሁለት አይነት መንገድ ማየት የሚቻል ሲሆን የታቀደው የልብስ ስፌት ፋብሪካ
ቢተገበርና ባይተገበር የሚያስገኘው ጥቅምና ጉዳት አንጻር የሚታይ ይሆናል፡፡ የአበባው የልብስ ስፌት
ፕሮጀክት ሲተገበር ከፍተኛ የሆነ አዎንታዊ ተፅዕኖዎች የሚኖሩት ሲሆን ከእነዚህም መካከል በሚፈጠረው

8|ገጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

የሥራ ዕድል ምክንያት የቤተሰብ ገቢ መጨመር፤ የቴክኖሎጂ ልውውጥ ማጐልበት እና በተለያዩ ታክስ
ክፍያዎች አማካይነት ለመንግስት ገቢ ማስገባት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

በሌላ በኩል ከፕሮጀክት ግንባታ እስከ ምርት ማምረት ወቅት ድረስ የሚኖረው አሉታዊ ተፅዕኖዎች
መከላከል የውሃ አካለት ብክለት፣ የደረቅና ፍሳሽ ቆሻሻ አማካይነት የሚደርስ ተፅእኖ፤ የድምጽና የአየር
ብክለት፤ የአፈር መሸርሸር፤ የእጽዋት መቆረጥና መጥፋት ዋና ዋናዎቹ ተፅዕኖዎች ናቸው፡፡ እነዚህ እና
መሰል አሉታዊ ተፅዕኖዎች የማቃለያ እርምጃዎች በሚተገበሩበት ወቅት መቀነስ እና ማስወገድ ይቻላል፡፡
ነገር ግን ፕሮጀክቱ ባይተገበር የተጠቀሱት ጥቅሞች እና ሌሎች የአካባቢው ህብረተሰብ ተጠቃሚ
የሚሆኑበት ሁኔታ አይፈጠርም፡፡

በመሆኑም ፕሮጀክቱ አለመተግበር አማራጭ ላይ በፕሮጀክቱ አማካይነት የሚደርሱ እና በማቃለያ እርምጃ


በመተግበር መቀነስ እና ማስወገድ ላይ ትኩረት በማድረግ ቢተገበር ፕሮጀክቱ በመቋቋሙ የሚገኘው
የማህበራዊ-ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ማግኘት የማይቻል በመሆኑ ፕሮጀክቱ መተግበር የተሻለ አማራጭ
ይሆናል፡፡

3.4.2 ፕሮጀክቱ የሚቋቋምበት ቦታ

ፕሮጀክቱ ከመቋቋሙ በፊት በተደረገው የቦታ ቅድመ-ጥናት ደብረብርሃን ከተማ ለጥሬ ዕቃ አቅርቦት፣
ምርትን ወደ ገበያ ማድረስ እና የሰራተኛ ሰው ኃይል አቅርቦት እና ከሌሎች ከተማ ከአዲስ አበባ በቅርብ
ርቀት ላይ መገኘቱ ተመራጭ አድርጐታል፡፡

3.4.3 የቴክኖሎጂ አማራጭ

የልብስ ስፌት ፋብሪካው የተለያዩ ምርቶችን ለማምረት ብዛት ያላቸው የቴክኖሎጂ አማራጮች ቢኖሩም
ካሉት አማራጮች በአካባቢ፣ በሰው ደህንነትና ጤንነት ላይ ከሚያደርሰው ጉዳት አንጻር በማየት በጣም
ዝቅተኛ ተፅዕኖ ሊኖረው የሚችለውን አማራጭ በመምረጥ የሚተገበር ይሆናል፡፡ አማራጮችንም ለማየት
የተለያዩ የቴክኖሎጂ አምራቾችን መስፈርት በማወዳደር ቴክኖሎጂው ምርጫ ተካሂዷል፡፡

ከላይ የተዘረዘሩት የፕሮጀክቱ አማራጮች በስፋት በዋናው የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሰነዱ የሚተነተን
ይሆናል፡፡

9|ገጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

4. በምዕራፎች የተከፋፈለ የፕሮጀክት የትግበራ የጊዜ ሰሌዳ

የልብስ ስፌት ፕሮጀክቱ አራት ምዕራፎች ያሉት ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ ሦስቱ ዋና ዋና ምዕራፎች
የሚኖሩትና በሦስት ዓመት ውስጥ የሚጠናቀቅ ይሆናል፡፡ የመጀመሪያው ምዕራፍ ፕሮጀክቱ መሬት
ከተረከበበትና አስፈላጊውን የግንባታ ፈቃድ ካገኘበት ጊዜ ጀምሮ አንድ ዓመት የሚፈጅ ሲሆን የፕሮጀክቱ
የፋብሪካ አጠቃላይ የግንባታና የማሽኖችና የመሳሪያዎች ከውጪ ማስገባት፣ የማጓጓዝ እና ገጠማ ሥራ
ሁለት ዓመት የሚፈጅ ይሆናል፡፡

4.1 ቅድመ ግንባታ ወቅት

በፕሮጀክቱ ቅድመ ግንባታ ወቅት ለፋብሪካው ግንባታ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት የሚከናወንበት ሲሆን
ከሚከናወኑት ተግባራት መካካል፡-

• የፕሮጀክት ፕሮፖዛል ጥናት፣


• የቦታ መረጣ፣ የሊዝ ዋጋ ክፍያና ርክክብ፣
• የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሰነድ በአማካሪ ማሰራትና በሚመለከተው መ/ቤት ማጸደቅ፣
• አፈር ምርመራ ማድረግ፣
• ግንባታ የኮንትራት ውል ስምምነት መፈጸም፣
• ለግንባታ የሚሆኑ ቁሳቁሶች መረጣ ስራዎች የሚካተቱበትና በግንባታ ወቅት የሚከሰቱ
ተፅዕኖዎችን ማቃለያ እርምጃዎች በኮንትራት ውል ስምምነት ውስጥ በማካተት በግንባታው ወቅት
ተግባራዊ እንዲሆኑ የማመቻቸት ሥራ ይሰራል፡፡

4.2 የግንባታ ወቅት


በፋብረካው ግንባታ ወቅት ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል፡-

• የግንባታ ቦታ ጠረጋና ቆረጣ ሥራ ማከናወን፣


• የአፈር ሙሌትና የተረፈ-ግንባታ ማጓጓዝ ሥራ መፈጸም፣
• የግንባታ ቁሳቁሶች የማጓጓዝ ሥራ ማከናወን፣
• የውሃና የመብራት ዝርጋት ማከናወን፣
• የፍሳሽና የደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃ ግንባታ ማካሄድ፣

10 | ገ ጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

4.3 የትግበራ ወቅት

ፋብሪካው ግንባታው ተጠናቆ ወደ ምርት ማምረት በሚገባበት ወቅት ከመከናወነኑ ተግባራት መካከል፡-

• የፋብሪካው የሚያስፈልገውን የግንባታ ማሽኖችና መሳሪያዎች ግዥ የመፈጸምና የገጠማ ተግባር


ማካሄድ፣
• የሰራተኞች ቅጥር መፈጸም፣
• የተለያዩ የአልባሳት ምርቶችን የማምረት ሥራ ማካሄድ፣

4.4 የፕሮጀክቱ መዝጊያ ወቅት

ፕሮጀክቱ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ መሰረት የምርት ማምረት ሥራውን አጠናቆ ሲወጣ ፋብሪካው
በተቋቋመበት አካባቢ ላይ የደረሱ ጉዳቶችን ወደ ነበረበት በመመለስ እንዲያስተካከሉ ያደርጋል፡፡ የደረሱ
ጉዳቶችንም ለማስተካከል በዚህ ሰነድ ላይ የተመላከቱትን የተፅዕኖ ማቃለያ እርምጃዎችን ተግባራዊ
ያደርጋል፡፡

5. የባዮፊዚካልና ማህበረ-ኢኮኖሚ መሰረታዊ መረጃዎች ትንተና

5.1. ጥናቱ የሚያካትተው የቦታ ስፋት

ጥናቱ የሚካሄደው አከባቢ ነክ ህጐችን መሰረት በማድረግ እና በፕሮጀክቱ አካባቢ በሚደረግው የመስክ
ጉብኝት በማካሄድ ነው፡፡ ይህ ጥናት የሚያካትታቸው ፕሮጀክቱ ከሚቋቋምበት እስከ 5 ኪ.ሜ. ራዲየስ
ድረስ ያለውን አካባቢ በመዳሰስ ይሆናል፡፡

5.2 አካባቢያዊ መግለጫ

5.2.1 ባዮፊዚካል መረጃዎች

5.2.1.1 ፋብሪካው የሚቋቋምበት ቦታ

ወደ ሥራ የሚገባው ፋብሪካ በደብረ ብርሃን ከተማ ቀበሌ 07 በ14,000 ካሬ ሜትር የሚቋቋም ሲሆን
ለግንባታው የሚሆን መሬት ከከተማው አስተዳደር ለኢንዱስትሪ ከተከለለ ቦታ ተረክቧል፡፡ በደብረብርሃን
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ከአዲስ አበባ በሰሜን ምስራቅ 130 ኪ.ሜ. ወደ ደሴ በሚውስደው ዋና

11 | ገ ጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

አውራ ጐዳና ላይ ይገኛል፡፡ ደብረ ብርሃን ከተማ የኬክሮስ እና የኬንትሮስ ርቀት 9041'N 39032'E/
9.683oN 39.533oE እና 2,840 ሜትር ከፍታ ላይ ይገኛል፡፡

ምስል 2 ፡ የልብስ ስፌት ፋብሪካው የግንባታ ቦታ


5.2.1.2 የአየር ንብረት

ደብረብርሃን በ2840 ሜትር ከባህር ወለል በላይ የሚገኝ ሲሆን ደጋማ የአየር ንብረት ያለበት አካባቢ
ነው፡፡ የአካባቢው ዝናባማ ወቅት (ከሰኔ እስከ መስከረም) የሚጠቀስ ሲሆን አጭር ዝናብ (የካቲት,
መጋቢት/ ሚያዝያ) እና በበጋ ወቅት (ከጥቅምት እስከ ጥር) ያካትታል፡፡. አማካኝ ዓመታዊው የሙቀት
መጠን 50C እና በ 230C መካከል ልዩነት አለው፡፡. ዓመታዊ አማካይ ዝናብ መጠን 874 ሚሜ ነው፡፡

12 | ገ ጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

5.2.1.3 የአፈር አይነት

በፕሮጀክቱ አካባቢ ውስጥ ዋነኛ የአፈር አይነት የሸክላ አፈር ነው፡፡ በተጨማሪም የአካባቢውን አፈርና
የመሬት አቀማመጥ በማየት ቀደም ሲል ምንም አይነት የመሬት መንሸራተት እንዳልነበር ማወቅ ይቻላል፡፡

5.2.1.4 የመሬት አጠቃቀም ሁኔታ

የጥናት ቡድኑ በመስክ ምልከታ ወቅት እንደተመለከተው በአሁኑ ወቅት ለፕሮጀክቱ መሬት የግጦሽ መሬት
(45%) እና የእርሻ መሬት (40%) ይገመታል፡፡ ከዚህም ባሻገር ቀሪው የመሬት አካባቢ በመንገድ የተያዘ
ሲሆን በአሁኑ ወቅት አካባቢው ለኢንቨስትመንት የተከለለ ነው፡፡

5.2.1.5 የእጽዋትና የእንስሳት ሁኔታ

ፋብሪካው በሚገነባበት አካባቢ ከከተማው አቅራቢያ በመሆኑና ለኢንቨስትመንት እንዲውል አስቀድሞ


የተዘጋጀ በመሆኑ የብዝሀ ሕይወት ስብጥሩ የሳሳ ነው፡፡ በአካባቢው በብዛት የሚገኙት አካባቢ ያሉ ዋነኛ
መኖሪያዎች፣ የባህር ዛፍ፣ የእርሻ እና የግጦሽ መሬት ናቸው፡፡ የዱር እንስሳት ከተለመዱት እንደ ጅቦች እና
ቀበሮ ያሉ እንስሳትን ውጪ በአካባቢው ብዙም አይገኙም፡፡

5.2.2 ሶሺዮ-ኢኮኖሚ ሁኔታ

የኢኮኖሚው ሁኔታ በደብረብርሃን ከተማ ውስጥ በንግድ እና በመንግስታዊ እና መንግስታዊ ባልሆኑ


ድርጅቶች ተቀጥሮ መስራት ዋነኛ የአካባቢው ህብረተሰብ መተዳደሪያ እና የገቢ ምንጭ ነው፡፡ በሥራ
አጥነት ምክኒየት በከተማው ዙሪያ የሚገኙ ነዋሪዎች ወደ ከተማው ተሰደው ይገባሉ፡፡ በዚህም ምክኒያት
በከተማው ለሚቋቋመው የኢንቨስትመንት የሰለጠነና ያልሰለጠነ የሰው ኃይል ማግኘት ይቻላል፡፡

5.2.2.1 የህዝብ ብዛት

በማዕከላዊ ስታትስቲክስ የ2008 ዓ.ም. የትንቢያ መረጃ መሰረት የደብረብርሃን ህዝብ ቁጥር 100 ሺ 055
እንደሆነ ይገመታል፡፡ ከከተማዋ በኢንቨስትመንት፣ በንግድ እና ሌሎች እንቅስቃሴዎች ምክንያት
የከተማው ነዋሪ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነው፡፡ ከነዋሪዎች 94.12% ኦርቶዶክስ ክርስትናን የሚከተል
ሲሆን 3.32% ከሕዝበ ሙስሊሙ እና 2.15% የፕሮቴስታንት ሃይማኖት ተከታይ ናቸው፡፡

13 | ገ ጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

5.2.2.2 መሠረተ- ልማት

ለኢንቨስትመንቱ ቀረቤታ, የመሠረተ ልማት መሟላት ከሰለጠነ ለገበያ ያለው ቅርበት፣ ጥሬ እቃዎች
አቅርቦት እና የሰው ሀይል አቅርቦት, የፕሮጀክቱን አካባቢ ለመወሰን የሚረዱ ዋና ዋና ነገሮች ናቸው፡፡
በተጠቀሱት መስፈርቶች መሠረት ደብረብርሃን ከተማ ከመንገድ ተደራሽነት፣, የውሃ እና የኤሌክትሪክ
ኃይል አቅርቦትና ምቹ መሆን ለኢንቨስትመነት ተመራጭ አካባቢ እንዲሆን አድርጎታል፡፡ በተጨማሪም
ከተማው በፕሮጀክቱ አካባቢ የአካባቢው ህብረተሰብ አገልግሎት የሚሰጡ የጤና ተቋማት እና ትምህርት
ቤቶች አሉት፡፡ ስለዚህ በደብረብርሃን የተያዘው የፕሮጀክቱ አካባቢ በብዙ አቅጣጫዎች የበለጠ ተመራጭ
ነው፡፡

5.2.2.3 የውሃ አቅርቦት

ከከተማው አስተዳደር ፋበሪካው በሚቋቋምበት አካባቢ የውሃ አቅርቦት ያመቻቸና ባለሀብቱ ተጠቃሚ
የሚሆኑበት ምቹ ሁኔታ አለ፡፡

5.2.2.4 የጤና ተቋማት

በደብረብርሃን ከተማ ሁለት ሆስፒታሎች እና ሦስት የጤና ማእከላት የሚገኙ ሲሆን አንዱ ለፕሮጀክቱ
አካባቢ ይገኛል፡፡

5.2.2.5 ባህላዊና ታሪካዊ ቦታዎች

ፋብሪካው በሚቋቋምበት አካባቢ ምንም አይነት ባህላዊ ወይም ታሪካዊ ተቋማት የሉም፡፡

14 | ገ ጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

6. የአካባቢ ተፅዕኖዎች
6.1. በጐ ተፅዕኖዎች

የአበባው የልብስ ስፌት ፋብሪካው በሚቋቋምበት አካባቢ የሚኖረው በጐ ተፅዕኖዎች ከዚህ በታች
ተዘርዝረዋል፡-

6.1.1 የሥራ ዕድል ፈጠራ

ፋብሪካው ለአካባቢው ህብረተሰብ ቀጥተኛ ወይም ቀጥተኛ ያልሆነ የቅጥር ሥራ ይፈጠራል፡፡


በተጨማሪም ፕሮጀክቱ በአካባቢ ማህበረሰብ ውስጥ የአካባቢው ነዋሪዎች ትርጉም ያለው የሥራ
ዕድሎችን ለማመቻቸት እና ለአካባቢው ማህበረሰቦች የኢኮኖሚ አቅምን ለማጎልበት አስተዋፅኦ
ይኖረዋል፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ የአካባቢው ማህበረሰብ የኑሮ ደረጃቸውን ስለሚያሻሽል ሀብትና የገቢ
መፍጠር ዕድል ያገኛል፡፡ በዚህም መሰረት ፋብሪካ ለ199 ለሥራ አጥ ዜጐች የሥራ ዕድል የሚፈጥር
ሲሆን የተለያዩ ቀጥተኛ ያልሆኑ የሥራ ዕድሎችን መፍጠር ይቻላል፡፡

6.1.2 የመንግስትን ገቢ ማሳደግ

በታቀደው የልብስ ስፌት ፋብሪካ ለሚቋቋምበት በጠቅላላው ከታክስ ክፍያና በፈቃደኝነት ክፍያዎች እና
በሮያሊቲዎች እንዲሁም በተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) መልክ ለአካባቢው መስተዳደርና እና ለሀገሪቱ
ገቢን ያስገኛል፡፡

6.1.3 የማህበራዊ ተቋማት መሻሻል

የታቀደው ፕሮጀክት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የአካባቢውን ህብረተሰብ ሊጠቅሙ የሚችሉ እና


አካባቢ ያሉትን አንዳንድ ማህበራዊ አገልግሎት መስጪያ ተቋማትን ለማቋቋም እና ለማሻሻል ፋብሪካው
እገዛ የሚያደርግ በመሆኑ አገልግሎት አሰጣጥ ያሻሽላል፡፡

15 | ገ ጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

6.2 አሉታዊ ተፅዕኖዎች

በልብስ ስፌት ፋብሪካው በግንባታ እና በትግበራ ወቅት የተለያዩ አካባቢያዊና ማህበራዊ ተፅዕኖ የሚደርስ
ሲሆን በአካባቢ ወሰን ጥናት ልየታ ወቅት ከተለዩት መካከል አንደሚከተለው የቀረቡ ሲሆን ዝርዝር
ተፅዕኖዎች በሙሉ የአካባቢ ተፅዕኖ ሰነዱ ሲዘጋጅ የሚዘረዘር ይሆናል፡፡

6.2.1 በግንባታ ወቅት የሚደርሱ ተፅዕኖዎች

አፈር መሸርሸር ተጽእኖ


በግንባታው ምክኒያት የሚደርስ የፍሳሽ ቆሻሻ ብክለት
የድምፅ ብክለት
የአየር እና የአቧራ ብክለት
የሰራተኞች ወደ ግንባታው አካባቢ መፍለስ
የውሃ አካላት ብክለት

6.2.2 በትግበራ ወቅት የሚከሰቱ አሉታዊ ተጽእኖዎች

የፍሳሽ ውሃ ብክለት
የደረቅ ቆሻሻ ብክለት
የድምፅ ብክለት
የትራፊክ አደጋዎች
የሥራ ጤንነት እና ደህንነት

16 | ገ ጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

7. የማህበረስብ ወይይት እና ምላሽ

ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በሚካሄዱ የልማቶች ሥራዎች ላይ ህዝብን ማማከር እና ተሳታፊ እንዲሆን
የማድረግ ሥራው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል፡፡ በተለይ የህብረተሰብ ተሳትፎን ለመጠቀም
በወጡ አካባቢ ጥበቃ ነክ ህጐች መሰረት አዲስ በሚቋቋሙ ፕሮጀክቶች ላይ የህዝብ ተሳትፎ ወሳኝ ሆነው
እንዲተገበሩ እየተደረገ ነው፡፡

ስለፕሮጀክቱ በሚደርሱ አዎንታዊና አሉታዊ ተፅዕኖዎች ለመለየትና የአካባቢ ተፅዕኖው ግምገማ ጥናቱ
አካል ለማድረግ በፕሮጀክቱ በሚቋቋምበት አካባቢ የሚኖሩ በፕሮጀክት ትግበራ ተጠቃሚ፣ ተጐጂ፣
ፍላጐቱ ያላቸውና የሚመለከታቸው የህብረተሰብ አካላትን በማሳተፍ የህብረተሰብ የምክክር መድረክ
በአካባቢ ወሰን ልየታው ወቅት ተካሄዷል፡፡

ምስል 3፡ በምክክር መድረኩ ላይ ተሳታፊ የሆኑ የህብረተሰቡ አካላት

17 | ገ ጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

የህብረተሰቡ ምክክር በደብረ ብርሃን ከተማ ፕሮጀክቱ በሚገኝበት አካባቢ የተደረገ ሲሆን ከአካባቢው
ከተለያዩ የህብረተስብ አካላት ተሳታፊ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ በወይይቱ ወቅት ስለፕሮጀክቱ በበቂ ሁኔታ
ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን በማጠቃለያ ከቀረቡት ሃሳቦች መካከል የሚከተሉት ይጠቀሳሉ፡፡

ለህብረተሰቡ የቀረቡ የፕሮጀክት ዋና ዋና አካባቢያዊና ማህበራዊ አሉታዊና አዎንታዊ ተፅዕኖዎች


መካከል፤ በአዎንታዊ ከተነሱት ውስጥ ፕሮጀክቱ በአካባቢው ለሚኖረው ሥራ አጥ ዜጐች የሥራ ዕድል
መፍጠሩ እና ፕሮጀክቱ በአካባቢያቸው የሚኖረውን ማህበራዊ አገልግሎት ተቋማትን በማሻሻል ተጠቃሚ
ማድረግ እንደሚችል ገልጸዋል፡፡ ከዚህ ባሻገር በፕሮጀክቱ አማካኝነት ይደርሳሉ ተብለው ከተገመቱት
አሉታዊ ተፅኖዎች መካከል የአካባቢ ብክለት መከሰቱ (የደረቅና ፍሳሽ ቆሻሻ፣ የውሃና የአየር ብክለቶች) ፣
የትራፊክ አደጋ በፕሮጀክቱ ተሽከርካዎች ምክንያት መከሰት እና እንደ ኤችአይቪ ያሉ ተላላፊ በሽታዎች
ሊከሰቱ ይችላሉ በሚል አስቀምጠዋል፡፡

የፕሮጀክቱን የህዝብ ስጋት ያገናዘቡ ዋና ዋናዎቹ ጭብጦች ከዚህ በታች ቀርበዋል፡-

➢ ለአካባቢው ሰዎች የሥራ ዕድል ቅድሚያ አለመስጠት፣


➢ ከፋብሪካው የሚመነጩ ፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻዎች በተገቢው ሁኔታ እንዲወገዱ
አለማድረግ፣
➢ ከፋብሪካው የአየር ብክለት መከላከል አለመቻል፣
➢ ዝቅተኛ የደመወዝ ክፍያ፣

ከላይ ለተጠቀሱት በሚቋቋመው ፕሮጀክት አማካኝነት የሚመጡ ተፅዕኖዎች ከህብረተሰቡ ከቀረቡ


የማቃለያ እርምጃዎች መካከል የሥራ ዕድል በቅድሚያ ለአካባቢው የህብረተሰብ ክፍልች እንዲሰጡ
ማድረግ፤ ለፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ በተገቢውን አካባቢን በማይበክል መንገድ ማስወገድ፣ በፋብሪካው
አማካኝነት ለሚከሰቱ የአየርና የብናኝ ችግሮች የመቀነሻና በአካባቢው የማይለቀቅበትን መንገድ ላይ
መስራት፤ የትራፊክን አደጋ ለመከላከል ከአካባቢው መስተዳደር ጋር በጋራ መስራት እና ተላላፊ በሽታዎች
ላይ ለሰራተኞችም ሆነ ለአካባቢው ህብረተሰብ ተገቢውን ግንዛቤ ማስጨበጥ የሚሉት ተጠቅሰዋል፡፡

በፕሮጀክቱ አካባቢ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማወያየት የተያዘው ቃለ ጉባኤ ከዚህ ሪፖርት
መጨረሻ በዕዝል ላይ ተያይዟል፡፡

18 | ገ ጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

8. የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናት ቢጋር

8.1 መግቢያ

የአካባቢ ወሰን ዘገባ ሪፖርት የተዘጋጀው አዲስ ለሚቋቋመው የአበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ነው፡፡
ፕሮጀክቱ በሰሜን ሸዋ ዞን በደብረ ብርሃን ከተማ ቀበሌ 07 የኢንዱስትሪ ዞን ውስጥ ይቋቋማል፡፡
ፕሮጀክቱ መነሻ አድርጐ የተነሳው በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ውስጥ ያለውን ከውጪ ለሚገቡተት አልባሳት
ከፍተኛ የውጪ ምንዛሬ እጥረት ምክኒያት የአልባሳት የገበያ ዋጋ መናር መኖሩ ባለሀብቱን በዚህ ዘርፍ
ለመሰማራት አስቧል፡፡

8.2. የፕሮጀክቱ ዓላማዎች

የልብስ ስፌት ፕሮጀክቱን የሚቋቋምበት ዋና ዓላማ አሁን ያለውን ሀገር ውስጥ የተዘጋጁ ልብሶች እጥረት
መነሻ በማድረግ ክፍተቱን ለመሙላት እና በየተዘጋጁ የተለያዩ ልብሶችን በአገር ውስጥ ባሻገር ለዓለም
አቀፍ ገበያ ለማቅረብ ነው፡፡ ዝርዝር ዓላማዎቹም፡-

1. የተለያዩ የአልባሳትን በመስፋት፣ በማዘጋጀት እና በጥራት በማምረት ለአገር ውስጥና ለውጪ


ገበያ ማቅረብ፤
2. ከፍተኛ ጥራት ያላቸው ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ የውጭ ምንዛሪ ማግኘት፤
3. ፕሮጅክቱ ከሚያገኘው ትርፍ ላይ ለመንግስት ተገቢውን ታክስ ለመክፈል፤
4. ለሥራ አጥ የህብረተሰብ ክፍሎች የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር የሥራ አጥነት መቀነስ፤

8.3 የጥናቱ ዓላማዎች

የአበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ የአካባቢ ወሰን ጥናት ዘገባ የሚከተሉት ዓላማዎች አሉት፡-

1. ስለታቀደው ፕሮጀክት አጠቃላይ መግለጫ እና የምርት ማምረት ሂደት በዝርዝር ማስቀመጥ፣


2. የታቀደው ፕሮጀክት የሚቋቋምበትን አካባቢ ገፅታና እና ማህበራዊ ሁኔታ በዝርዝር መግለፅ፤
3. በፕሮጀክቱ ምክኒያት ከማህበረሰቡ እና ከሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚነሱ ስጋቶችን መለየት፤
4. ፕሮጀክት አማራጮችን መለየት እና መተንተን፤

19 | ገ ጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

5. በአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ጥናት ወቅት ትኩረት የሚደረግባቸውን የአካባቢ እና ማህበራዊ


ተፅዕኖዎች ላይ ትኩረት ማድረግ ናቸው፡፡

8.4 የፕሮጀክት ቦታው መገኛና አዋሳኞች

የልብስ ስፌት ፋብሪካ በደብረ ብርሃን ከተማ ቀበሌ 07 በ14,000 ካሬ ሜትር የሚቋቋም ሲሆን
ለግንባታው የሚሆን መሬት ከከተማው አስተዳደር ለኢንዱስትሪ ከተከለለ ቦታ ተረክቧል፡፡ በደብረብርሃን
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ከአዲስ አበባ በሰሜን ምስራቅ 130 ኪ.ሜ. ወደ ደሴ በሚውስደው ዋና
አውራ ጐዳና ላይ ይገኛል፡፡ ደብረ ብርሃን ከተማ የኬክሮስ እና የኬንትሮስ ርቀት 9041'N 39032'E/
9.683oN 39.533oE እና 2,840 ሜትር ከፍታ ላይ ይገኛል፡፡ የአበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካው
በሰሜን አረንጓዴ ቦታ፣ በደቡብ ባዶ ቦታ፣ በምዕራብ 11 ሜትር መንገድ እንዲሁም በምስራቅ 18 ሜትር
መንገድ ያዋሱኑታል፡፡

ሠንጠረዥ 3፡ የፋብሪካው የቦታ X እና Y ኮርዲኔት


ተ.ቁ. X - ኮርዲኔት Y - ኮርዲኔት
1 555165.684 1067034.030
2 555230.637 1067132.206
3 555337.665 1067108.606
4 555249.592 1066977.614

20 | ገ ጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

ምስል 4፡ የፋብሪካው የቦታ ካርታ

8.5 የጥናቱ ስልት ወይም ዘዴ

በአማካሪ ቡድኑ በአካባቢ ተፅዕኖ ሰነድ ግምገማ ጥናት ወቅት የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ
መረጃዎች ለመሰብሰብ የሚከተሉትን ዘዴዎች የሚጠቀሙ ይሆናል፡፡

• አካባቢያዊና ማህበራዊ ነክ የሆኑ መረጃዎችን መሰብሰብ፣ መገምገም እና ትንታኔ ማድረግ ሲሆን


መረጃዎቹም በመጀመሪያ ደረጃ በሚሰበሰቡ እና ቀደም ሲል ከተሰበሰቡ መረጃዎች መሰረት
በማድረግ የሚሰበሰቡ ይሆናሉ፡፡
• የመስክ ምልከታ በማድረግ ፕሮጀክቱ የሚቋቋምበትን አካባቢ የአየር ሁኔታ፤ የውሃ መጠን፣
የእፅዋት ሽፋን፣ የአፈር አይነት፣ መሬት አጠቃቀም፣ ባህላዊ ገጽታዎች (የአርኪዎሎጂ ቅሪቶች) ፤
የከባቢ አየር ልቀቶች እና ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ገጽታዎች ያካተቱ መረጃዎች የሚሰበሰቡ

21 | ገ ጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

ይሆናል፡፡ ሌሎች ጥቅም ላይ የዋሉ የጥናት ዘዴዎች የፅሁፍ ግምገማዎችን፣ ቃለ መጠይቆች እና


የመስክ ጉብኝቶች የመረጃ መሰብሰsቢያ አካለል ይሆኛሉ፡፡
በተጨማሪም በፕሮጀክቱ ትግበራ ምክኒያት ይከሰታሉ ተብለው የሚገመቱ ጉልህ አዎንታዊና አሉታዊ
ተፅዕኖዎችን ለመለየትና ለመተንተን የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማውን ለማደረግ የባለሙያ ልምድ፣ ቼክሊስት
ጥቅም ላይ የሚውሉ ይሆናሉ፡፡

8.6 የእምቅ ተፅዕኖዎች ልየታ ቼክሊስት

የግምገማ ጥናት ውጤቱን በማጠቃለያ ሰንጠረዥ (matrix) መልክ ማቅረብ እያንዳንዱ ተግባር
የሚያስከትለውን ተፅእኖ በመመዘን በደረጃ ለማስቀመጥ ከታች የተጠቀሱትን የትናት ቡድኑ ተጠቅሟለ፡፡

8.6.1 የተፅዕኖ ስፋት

የተፅእኖ መጠንና ስፋት ስር የተካተቱት በፕሮጀክቱ አማካኝነት የሚከሰቱ ተፅዕኖዎች ድንበር ተሻጋሪ
ሆነው ዓለም አቀፋዊ፣ በአገር ደረጃ ወይም በክልል ደረጃ መከሰታቸው እንዲሁም ፕሮጀክቱ
በሚቋቋመወበት ዙሪያ ወይም በፕሮጀክቱ በተከለለው ቦታ ብቻ የተወሰኑ ስለመሆኑ የሚገለጽበት ሲሆን
በሚከተለው መሰረት ደረጃ ተቀጦለታል፡፡

ሠንጠረዥ 4: የተፅዕኖ መጠንና ስፋት


የተፅዕኖ ደረጃ ነጥብ
በጣም ከፍተኛ /ዓለም አቀፍ/ 5
ከፍተኛ /አገር አቀፍ/ 4
መካከለኛ /ክልላዊ/ 3
ዝቅተኛ /አካባቢያዊ/ 2
በጣም ዝቅተኛ /በፕሮጀክቱ ቦታ/ 1

8.6.2 የተፅእኖ ባህሪ /ተፈጥሮ/ ከፍተኛነት

የታቀዱ የኘሮጀክት ተግባራት /እንቅስቃሴዎች/ በአካባቢ ላይ የሚያደርሱትን ተፅዕኖ ደረጃ በመስጠት


በዝርዝር ይቀመጣል፡፡ የአካባቢ ተፅዕኖው የሚያሳድረው ተፅዕኖ ክብደቱ አውዳሚ (Innocuous)
መሆኑና ዝቅተኛ፣ መካከለኛ ወይም ከፍተኛ መሆኑን የሚገለጽበት ነው፡፡

22 | ገ ጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

ሠንጠረዥ 5፡ የተፅእኖ ባህሪ /ተፈጥሮ/


ደረጃ ዝርዝር ነጥብ
በጣም ተፈጥሯዊ፣ ባህላዊና ወይም ማህበራዊ ሁኔታዎች እና ሂደቶች በቋሚነት ደረጃ የሚቀየር 4
ከፍተኛ ከሆነ፣
ከፍተኛ ተፈጥሯዊ፣ ባህላዊና ወይም ማህበራዊ ሁኔታዎች እና ሂደቶች በጊዜያዊነት የሚቀየር 3
ከሆነ፣
መካከለኛ ተፅዕኖዎቹ በአካባቢ ላይ በሚያደርሱት ጉዳት ምክንያት ተፈጥሯዊ፣ ባህላዊና ወይም 2
ማህበራዊ ሁኔታዎች እና ሂደቶችን የሚቀየር ከሆነ፣
ዝቅተኛ ተፅዕኖዎቹ በአካባቢ ላይ በሚያደርሱት ጉዳት ምክንያት ተፈጥሯዊ፣ ባህላዊና ወይም 1
ማህበራዊ ሁኔታዎች እና ሂደቶችን የማይለውጥ ከሆነ፣

8.6.3 የተፅዕኖ ቆይታ /ጊዜ/


የሚደርሰው ተፅእኖ የአጭር ጊዜ /0-5/ መካከለኛ /5-15 ዓመት/ እንዲሁም የረጅም ጊዜና ቋሚ የሚለውን
መዳሰስ፣ መገምገም ወይም በማጥናት የሚገለጽበት ነው፡፡

ሠንጠረዥ 6: የተፅዕኖ ቆይታ /ጊዜ/


ደረጃ ዝርዝር ነጥብ
ቋሚ ተፅዕኖዉ ፕሮጀክቱ የቆይታው ጊዜን አጠናቆ ከወጣም በኃላ የሚታይ 4
ሲሆን፣
የረጅም ጊዜ ተፅዕኖው ከ15 ዓመት በላይ የሚቆይና ከዚያ በኃላ የሚቆረጥ 3
የመካከለኛ ጊዜ ተፅዕኖው ከ5 እስከ 15 ዓመት ብቻ የሚቆይ 2
የአጭር ጊዜ ተፅዕኖው ከ 0 እስከ 5 ዓመት የሚከሰት 1

8.6.4 ተፅዕኖው የመከሰት አጋጣሚው ሁኔታ

የአካባቢ ተፅዕኖው የመከሰት አጋጣሚው ሁኔታና ተፅዕኖ የደረሰበት አካባቢ ወደ ነበረበት መመለስ የሚቻል
መሆኑና አለመሆኑ በዝርዝር የሚተነተንበት ይሆናል፡፡

23 | ገ ጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

ሠንጠረዥ 7: ተፅዕኖው የመከሰት አጋጣሚው ሁኔታና


የተፅዕኖ አይነት ዝርዝር
በእርግጠኝነት የሚከሰት ተፅዕኖው ለመከሰቱ 90% በላይ እርግጠኛ መሆን፣
አጠራጣሪ ተፅዕኖው ለመከሰቱ 70% በላይ እርግጠኛ መሆን፣
ሊከሰት የሚችል ተፅዕኖው ለመከሰቱ ከ40 እስከ 70% እርግጠኛ መሆን፣
ሊከሰት የማይችል ተፅዕኖው ለመከሰቱ ከ40% በታች እርግጠኛ መሆን፣

8.7 አሉታዊ ተፅዕኖዎች

ከዚህ በታች የተጠቀሱት ተጽእኖዎች በኘሮጀክቱ የሥራ ሂደት ወቅት ሊከሰቱ ይችላሉ ተብለው ታሳቢ
የተደረጉ ሲሆን ሙሉ የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርቱ ሲዘጋጅ በፕሮጀክቱ ቅድመ ግንባታ፣ ግንባታ፣
በትግበራ እና ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የሚኖረው በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሊፈጠሩ የሚችሉ ተፅዕኖዎች
በተገለፁት መነሻ ነጥቦች መሠረት የሚተነተኑ ይሆናሉ፡፡

➢ በአፈር ሀብት ላይ ሊደርሱ የሚችሉ ተፅእኖዎች


➢ በውሃ ሀብት ላይ ሊደርሱ የሚችሉ ተፅእኖዎች
➢ ከፕሮጀክቱ ከሚወጣው ደረቅ እና ፍሳሽ ቆሻሻ ምክኒያት ሊደርሱ የሚችሉ ተፅእኖዎች
➢ በአየር ጥራት ላይ ሊደርሱ የሚችሉ ተፅእኖዎች
➢ በእንስሳትና እፅዋት ላይ ሊደርሱ የሚችሉ ተጽእኖዎች
➢ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሊደርስ የሚችሉ ተጽእኖዎች
➢ በድምፅ ምክንያት የሚደርሱ ተጽእኖዎች
➢ በሰዎች ጤናና ደህንነት ላይ የሚደርስ ተጽእኖ

8.8 የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማው ጥናት ቡድን

የአበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ ይህን የአካባቢ ወስን ዘገባ ሪፖርትና ሙሉ የአካባቢ ተፅዕኖ ሰነድ
ለማዘጋጀት ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ/የተ/የግ/ማህበር አማካሪ ድርጅት ጋር የተዋዋለ ሲሆን የጥናት
ቡድኑም የሚከተሉትን ባለሙያዎች ያካትታል፡፡

24 | ገ ጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

ሠንጠረዥ 8፡ በጥናቱ ተሳተፉ ባለሙያዎች ዝርዝር


ተ.ቁ. ሙሉ ሥም የሙያ አይነት ኃላፊነት
1 መንግስቱ ብርሃኑ የአካባቢ ጥናት ባለሙያ ሥራ አስኪያጅ
2 ተፈራ አሰፋ የአካባቢ ብክለት እና የማህበራዊ ጉዳይ አባል
ተንታኝ ባለሙያ
3 ዮሴፍ መለሰ የኢኮኖሚ ባለሙያ አባል
4 ፀጋዬ ቦሩ ቱራ የብዝሀ ህይወት ባለሙያ አባል

የጥናት ቡድኑ ለአበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ጥናት ለማካሄድ
አስቀድሞ በዚህ ሰነድ ላይ የተካተተውን የአካባቢ ወሰን ዘገባ ሪፖርት አዘጋጅቶ ማቅረብ፣
የሚመለከታቸውን የህብረተሰብና ተቋማትን በፕሮጀክቶቹ ላይ ማወያየት፣ የአካባቢ ወሰን ዘገባ ሪፓርት
ሰነዱን በሚመለከተው አካባቢ ጥበቃ መ/ቤት በሚሰጠው አስተያየት መሰረት ማስተካከል፣ ሙሉ
የአካባቢ ሰነድን በማዘጋጀትና በተሰጠው አስተያየት በማስተካከል በሚፈለገው ሰነድ ቁጥር መጠን እና
በተፈለገው ውቅት ማቅረብ ግዴታ አለበት፡፡

8.9 የህዝብ ምክክር

የአበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ በፕሮጀክቱ ውስጥ ያሉ መንግስታዊ እና የግል ባለድርሻ አካላት
በአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ጥናት ወቅት ስለፕሮጀክቱ በቂ ሃሳብ እንዲኖራቸው የማረጋገጥ ግዴታ አለበት፡፡
ለዚህም የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናት ግምገማ ኤክስፐርቶች ከአካባቢው ማህበረሰብ እና ተፅዕኖ ጥናት ላይ
ሲተገብሩ ማንኛውም ባለድርሻ አካላት የተሟላ ምክክር ያደርጋሉ፡፡

8.10 የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናት ሰነድ ይዘት

የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናት ሰነዱ በአብክመ የአካባቢ፣ ደንና ዱር እንስሳት ባለስልጣን ባወጣው የአካባቢ
ተፅዕኖ ጥናት ግምገማ መመሪያ ቁጥር 001/2010 መሠረት የሚከተለው ይዘት ይኖረዋል፡፡
1. አጠቃላይ መግለጫ (Excutive Summary)
2. መግቢያ (Introduction)
3. የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናቱ ዓላማ
4. የጥናቱ ወሰን
5. የጥናቱ ስልት ወይም ዘዴ

25 | ገ ጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

6. በጥናቱ ወቅት የተወሰዱ ታሳቢዎች እና የነበሩ የዕውቀት ክፍተቶች


7. የፓሊሲ፣ የህግና የአስተዳደር ማዕቀፎች
8. የፕሮጀክት ገለጻ
9. የባዮፊዚካልና ማሀበረ-ኢኮኖሚ መሰረታዊ መረጃዎች ትንተና
10. የአካባቢ ተጽዕኖ ትንተና ማካሄድ
11. የተፅዕኖ ማቅለያ እርምጃዎች
12. የአካባቢ አያያዝ ዕቅድ
13. የአካባቢ ክትትል/ምርመራ ዕቅድ
14. በፕሮጀክቱ ትግበራ ተፅዕኖ የሚደርስባቸውና የሚመለከታቸው አካላት ምክክር ማካሄድ
15. ማጠቃለያና ምክረ-ሃሳብ
16. ዋቢ መፃህፍት/ማጣቀሻዎች
17. እዝሎች

8.11 የጊዜ ሰሌዳ

ሠንጠረዥ 9: የአካባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖ ጥናት ሥራ የሚካሄድበት የጊዜ ሰሌዳ


ተ.ቁ. ተግባራት የጊዜ ሰሌዳ (ከሰኔ 2011 - ጥቅምት 2012 ዓ. ም.)
ሰኔ ሐምሌ ነሐሴ መሰከረም ጥቅምት ሕዳር
1 ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ስለፕሮጀክቱ
ወይይት ማድረግ
2 ከህብረተሰቡ ጋር ወይይት ማድረግ
3 መሠረታዊ መረጃ መሰብሰብ
4 የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ጥናት ሰነድ ማዘጋጀት
5 ለሚመለከተው አካባቢ ጥበቃ መ/ቤት ማቅረብ
6 በአተግ ሰነዱ ላይ አስተያየት መቀበል
7 የአተግ ሰነዱን ማስተካከል
8 ለሚመለከተው አካል ማቅረብ
9 ሰርተፊከት ማግኘት

26 | ገ ጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር


አበባው ተፈራ የልብስ ስፌት ፋብሪካ አካባቢ ጥናት ወሰን ዘገባ

27 | ገ ጽ ሀመን የምክር አገልግሎት ኃ.የተ.የግ. ማህበር

You might also like